Thursday, July 25, 2024

ከመለሰ ዜናዊና ከጉስታቭ ኸርቭ የተማረው የጎጃሙ ሙሶሊኒ! ጌታቸው ረዳ 7/25


ከመለሰ ናዊና  ከጉስታቭ ኸርቭ  የተማረው የጎጃሙ ሙሶሊኒ!

ታቸው ረዳ

7/25/24

ትዝ ይላችሁ እንደሆን << የትግራይ የአባ ሰላማ ቄሮዎች እና የአምሓራ መነኮሳት በአክሱም>> በሚል  Ethiopian Semay  ድረገጽ  ላይ 10/3/23 ያቅረበኩት አክሱም ጽዮን ለመሳለም የዱት መንፈሳዊ እንጂ ፖለቲካዊ እውቀቱ የላቸው የአምሐራ ተወላጆች የሆኑ መነኮሳትን በትግራይ ብሔረተኛነት የተበከሉ (ፋናቲክ) የሆኑ የአከሱም ከተማ ወጣቶች መነኮሳቱን ሰብስበው  ሲያስጨንቁዋቸውና ሲያዋረዱዋቸው እንደነበሩ በቪዲዮ አሳየቻለሁ፡፡

ከዚህ ሌላ ትግራይ ውስጥ በ1968 ዓ/ም ልጆቻችሁን ወደ ሰላማዊ መንገድ ተመለሱ ፤ መንግሥት አዲስ ነውና እንነጋገር ይላችል ብላችሁ ለሽምግልና አነጋግሩዋቸው ተብለው በሕዝብ ተመርጠው ወያነ ወዳለበት ሽ አውራጃ ከተላኩት ሸማግዎች ውስጥ የ የቅርብ ቤተሰብ የሆኑት አቶ ገብረሊባኖሰ መዝገቦ በዓይን ምስክር በአቶ ገዛኢ ረዳ አንደበት ምን እንደተፈጸመባቸው ካሳተምኩት መጽሐፍ ቀንጭላስነብባችሁና ተመሳሳይ ድርጊት ወደ ፈጸሙት ጎጃም የበቀሉ የሙሶሎኒ ቡቃያዎች እንመለከታለን (የዘመነ “ካልቶች” ቢመራችሁም ዋጡት)፡፡

ጥያ ፦ ክቡር አቶ ገዛኢ ሆይ፦ ለሽምግልና የተላኩት ሸማግሌዎችም ሆኑ ከነሱ ጋር ግንኙነት ያልነበረዎት በራስዎም ጭምር ‘ተሓህት’ ያደረሰችባችሁ ግፍ ሊነግሩን ይችላሉ?

 መልስ ፟ አቶ ገዛኢ ረዳ፡-

አዎ ሳስታውሰው ይሰቀጥጠኛል፡፡ መቸም ይህ አረጋዊያንን ማዋረድ በእኔ ላይ የተፈጸመዉ ግፍ በእኔ አልተጀመረም በእኔም ላይም አልቆመም።ብዙ አስረኞች፤ያለ ጥፋት ተደብድበዉ በእሳት ተቃጥለው መላ ሰዉነታቸዉ “ደም” እና “መግል” ቋጥሮ “ለቁስል” እና “ለዘላቂ ስቃይ” “ለአእምሮ መታወክ” ከመዳረጋቸዉ በላይ በየቀኑ በእዉነቱ ከ3 አሰከ 4 አሰከ 7 ወይንም 8 ድረስ ከተለያዩ ቦታዎች የሰበሰብዋቸዉ አስረኞች ይገደላሉ። ሊገድልዋቸዉ-ሲፈልጉ፤ጥዋት-ጥዋት “ተሰናበትዋቸዉ” ይሉናል። እየጠሩ ሲወስድዋቸዉ የሚገደሉት ሰዎች “ለወንድሜ ንገሩልኝ፤ለእናቴ ለአጎቴ ንገሩልኝ”- “ደህና ሁኑ” ከእንግዲህ ወዲህ አንገናኝ ይሆናል! “እግዚአብሐር-ከእናንተ-ጋር-ይሁን”!እያሉ፤ይሄዳሉ።

በጣም ከሚያሳዝን ነገር፤ “አቶ ገብረሊባኖስ መዝገቦ” የተባሉ የተከበሩ ትልቅ ጨዋ ሰዉ በሽሬ አዉራጃ ዋና ከተማ በእንዳስላሴ ከተማ ኗሪ ፤ የሆኑት እኒህ ሰዉ ፤ያዉራጃዉ (ሸረ) ግምጃ ቤት ሂሳብ ሹም ሆነዉ ሲሰሩ፤ በወቅቱ ደርግ ትላልቅ የአገሬዉ ታዋቂ ሰዎች የሚባሉ ሰብስቦ “በረሃ ድረስ ሄዳችሁ “ምንድነዉ ነገሩ? ብላችሁ” አስኪ ነገሩ በሰላም የሚፈታ ከሆነ በሰላም ለመፍታት እንዲቻል በረሃ ድረስ ያሉበት ቦታ ሄዳችሁ የወያኔ መሪዎችን አነጋግራቸሁ ለዕርቅ አነጋግሯቸዉ። በሽምግልና የሚታይ ከሆነ እንሞክረዉ እና አስኪ ሄዳችሁ ህዘቡን ወክላችሁ አነጋግሯቸዉ” ፤በማለት እሳቸዉ እና ሌሎችም እንደዚሁ “ባላምባራስ ተወለደ ገብረስላሴ” የተባሉ የእንዳስላሴ ከተማ ጭቃ ሹም፦ሌላም ገስጥ ኪዳነማርያም የተባለ የትልቅ ባላባት ልጅ ከሽማግሌዎቹ ጋር ለሽምግልና ተመርጦ አብሮ ሄዶ ነበር (ልጁ በወቅቱ አባትየዉ ከሚኖሩበት ከተማ ሄደዉ ወያኔዎች የገደሏቸዉ መሆኑንም ጭራሽ አልሰማም፤ኣላወቀም ነበር)። ሽምግልናዉ ስላልወደዱት “አይሆንም ብለዉ ወደ መጡበት ከመመለስ ፈንታ እነሱንም ያለ ምንም ወንጀል ይዘዉ አስቀርዋቸዉ”።የታሰሩት ቀደም ብለዉ እኛ ከተማ ዉስጥ እያለን ከመያዛችን በፊት ነዉ። አብረዋቸዉ የነበሩ ሌሎች አስረኞች ጭምር ታስረዉበት ከነበረዉ “ግህነም” ከተባለ “የጋሀነመ እሳት አስር ቤት” መጥተዉ እኛዉ ጋር አብረን ተቀላቅለናል። ልክ እኔን በእሳት አቃጥለዉ እንደለበለቡኝ አነሱም ሰዉነታቸዉ በሙሉ በእሳት ተቃጥሎ ለብልበዋቸዋል።ገላቸዉ ቁስል ደም እና መግል ብቻ-ሆኗዋል።

በተለይ አቶ ገብረሊባኖስ መዝገቦ እኔ በእሳት ከተጠበስኩት በላይ ተጠብሰዋል።ምክንያቱም በጀርባቸዉ ደምም መግልም ይንዠቀዠቃል። መተኛት አይችሉም- የቁስሉ መጠን ለዓይን ይዘገንናል።አቶ ገብረሊባኖስ መዝገቦም ሆኑ ባለምባራስ ተወልደ ገብረስላሴ በጣም ደግ የተከበሩ ባላባቶች ናቸዉ።ባላምባራስ ተወለደ ገብረስላሴም የአከባቢዉ፤የሽሬ እንዳስላሴ ከተማ ማዕረግ/አድባር ነበር ማለት ይቻላል።ባላምባራስ ገብረስላሴ ወደ ምርመራ ሲወስዱት “አይዞህ ቆመንም ያዉ ሞት ነዉ፡ ብንሞትም ያዉ ሞት ነዉ- በርታ” ያልዋልክበት አበሳ ንገረን ቢሉህ ያላደረግከዉ ነገር በጭንቅ “አዎ” ብለህ አትመንላቸዉ፡ብየዉ ወስደዉ ደጋግመዉ እንደገና በእሳት እየለበለቡ እየደበደቡ ሲያሰቃዩት፡መከራ ሲበዛበት“የሚሉት ሁሉ ኣዎ! አላቸዉ”። ቀጥለዉም ለወጣት “ገስጥ ኪዳነማርያም “እዚህ የመጣኸዉ አባትህን ስለገደልንልህ የደም ብድር ለመመለስ ነዉ ወደ እኛ አዚህ ድረስ ደፍረህ የመጣኸዉ?” አሉት። አሱ ደግሞ አባትየዉ በእነሱ እንደተገደሉም ጭራሽ-አላወቀም-ነበር።

ሌላዉ ደግሞ ከዓድዋ ሰለኽለኻ ወደ ተባለች ትንሽ ከተማ እህቱን ለመጎብኘት መጥቶ የነበረ አንድ ህፃን ልጅ (ታዳጊ-ወጣት) ይዘዉት አብሮን ነበር። “አንተ ደግሞ እዚህ የመጣኸዉ ከምንጠጣበት ወንዝ መርዝ ልትጨምር ነበር የመጣኸዉ? ብለዉ፤ እሱንም በእሳት ለብልበዉ ገርፈዉ አሰቃይተዉ እንድንምርህ ከፈለግህ “አዎ” ማለት አለበህ ብለዉት “አዎ” አምናለሁ ብሎ ባልዋለበት ነገር አሳምነዉ አክስቱን ለመጠየቅ ወደ ሰለኽለኻ አብሮት ከዓድዋ ወደ ሰለኽለኻ የመጣዉ “ብርሃነ መስቀል ጎሽም” እንደገና መሓመድ የተባለዉ ወጣት ልጅ በአንድነት በአንድ ቀን ሁሉንም ወስደዉ ረሸኗቸዉ።

“…በወቅቱ “ኢድዩ” ወደ አካባቢዉ በብዛት ሰራዊቱን ይዞ እየገሰገሰ በፍጥነት ስለመጣ በድንገት ስለደረሰባቸዉ ወያኔዎች ተደናገጡ። ኢዲዩ መጥቶብናል እና እንግደላቸዉ ብለዉ እኛን ለመግደል ወያኔዎቹ ሌሊትኑ ወደ ታሰርንበት ዳስ ክፍል ገቡ እና አስወጥተዉ በተራ አስሰለፉን።“አዛዉንቱ አቶ ገብረሊባኖስ መዝገቦም ሲመረምሩዋቸዉ ሰዉነታቸዉ በሞላ በእሳት እያቃጠሉ እየደበደቡ ስላደከሙዋቸዉ / መራመድ ስለማይችሉ ልንሸከማቸዉ አንችልም ብለዉ አቶ ገብረሊባኖስ መዝገቦን በእንቅልፋቸዉ ተኝተዉ እንዳሉ በሦስት ጥይት ገደሏቸዉ። የገዛ ታጋያቸዉም በሃይለኛ ወባ ተይዞ ተኝቶ ስለነበር አሱንም አንሸከመዉም ብለዉ በጥይት ገደሉት…።”

ወስደዉ ከረሸንዋቸዉ በግምት ወደ 30 ወይም ወደ 35 የሚሆኑ ሰዎች መካከል ናቸዉ።ዝርዝር ስማቸዉ ቆይቼ ልገልጽልህ ነዉ። የጭካኔያቸዉ መጠን የሰዉ ፍጡረነትክን ያስጠላል። ትግሬነትክን ያስጠላል። በወቅቱ ያ ግፍ ስትመለከት “የትግራዋይነት ትርጉም ሃዘን መሆኑን ይሰማሃል”። ይህ ጭካኔ የሚያራምዱ ባዕዳን ሳይሆኑ ከምድሪቱ ከእኛዉ ትግራይ መሬት የተወለዱ የአምላክን ክብር የሚንቁ ከአብራካችን የወጡ የትግራይ ተወላጆች ያሳደግናቸዉ የምናዉቃቸዉ ልጆቻችን ናቸዉ” ይህ ሁሉ ግፍ በሕዝብ ላይ እየፈጸሙ፤ያሉት።

ገዛኢ ረዳ። ከቃለ መጠይቅ  ክትግርኛ ወደ አማርኛ የተረጎምኩት ክራው መጸሕፍ የተገኘ፡፡  አቶ ገብረሊባኖስ መዝገቦ የዚህ ጽሑፍ አቅራቢ (የጌታቸው ረዳ) ቅርብ ተሰብ ናቸዉ።

አሁን ወደ ጎጃሙ ሙሶሊኒ የዘመነ ካ ታጣቂ ተመሳሳይ ድፍረትና ድርጊት እንመልከት፤

ሰሞኑን በዘመነ የሚመራው <<የአማራ ፋኖ በጎጃም>>  አሸማቃቂ ፤ በጣም ነውር የተሞላባቸው ሁለት ድፍረቶች በኩራት የፈጸማቸው በቪዲዮ ቀርጾ እንዲሰራጩ አድርል፡፡

አንደኛው እሱ ራሱ ለብሶት የሚታይ (የታዋቂ ሰዎች መስል ተደርጎበት የሚለበስ ሰንደቅ ዓላማችን ቀለም ያለበት ካኒተራ) የታላቁ  እስክንድር ነጋ ፎቶ ያለበት የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማን እንዲቃጠል ያደረገ ሲሆን፡

አንደኛው አስነዋሪ ድርጊት!

 ልክ ከላይ የተሓህት ድርጊት እንደተመለከታችሁት ጎጃም አማራ ማሕበረሰብ ላይም የዘመነ ታጣቂዎች ለባሕላዊ ሕክምና እና የወባ በሸታ መከላከል ስርጭት ትምሕርት ከአካባቢ ሪዎች የተውጣጡ ናቸው የሚባልላቸው ሰልጥነው ወደ ገጠር መኖርያቸው ሲመለሱ በዘመነ ካ ታጣቂ ጦር ከየመኖሪያቸው እየተለቀሙ ባንድ ቦታ ተሰበሰበው ገበያ ላይ ሕዝብ በተሰበሰበበት “እኛን ከአብይ አሕመድ ለመሸንገል አብይ አሕመድ የላካችሁ ሸማግዎች ናችሁ” በሚል 4 ቱ ሲረሸኑ ከመረሸናቸው በፊት በርከት ካሉት ሸማግ እናቶችና ታዳጊ ወጣቶች፤ እንዲሁም የዚያ አካባቢ አሰተዳዳሪ ቄስ በእምብርክክ እየተንፏቀቁ ሕዝብ እንዲያያቸው “ዘነዘና ብትርና መሳሪያ የያዙ የዘመነ ካ  ታጣቂዎች ሲያጣድፉዋቸው እምብርክክ እንዲሄዱ የተደረጉ እናቶች፤ አረጋዉያን፤ ቀሳውስት አይተናል፡፡

እነዚህ አዛውንት ደክመው የልጅ ልጆቻቸው ወደ ሆኑት ወረበላ ታጣቂዎች የልመና ገጽታ ቢያሳዩም ይባስ ብሎ ፍጥነት እንዲጨምሩ በማስፈራራት  ሲያስጨንቁዋቸው ዓለም እንዲያያቸው በዩቱብ ተዘርግቶ እየታየ ስንብል፡፡

ይህ የዘመነ ካ ታጣቂ ሎ የፈጸመው አምሐራ በሆኑ አረጋዊያን አባቶችና የሸመገሉ እናቶች  አስነዋሪ ድርጊት የቪዲዮው ርእስ እንዲህ ይነበባል፡፤

<< ስርዓቱ የፈጠረው ምስ ካውንስል ሰብስቧቸው የቆዩ ባንዳዎችን በዚህ መልኩ አቀባበል ተደርጎላቸዋል ፤ የኮሎኔል ታደሰ ሙሉነህ ብርጌድ ፤ አለማየሁ ከ ሻለቃ>> ይላል፡፡

ድርጊቱ የፈጸሙት እየሸለሉ እየፎከሩ እየዛቱ  የታዩት የነዚህ ታጣቂዎች የበርጌድ ስም የተሰየመው “በፈቃዱ እጁን ለሻዕቢያ በመስጠት’’ አይሮፕላን አብራሪዎችን ሲያሰለጥን የነበረ በግፍ የታሰረ፡፡ በ“ዋሾው” አንዳርጋቸው ፅጌ የኢሳያስ መንግሥት ለመፈንቀል ተንኮል ሲሰራ ተነቅቶበት የተያዘ ነው እንጂ በሰላም አሥመራ ወስጥ በክብር ይኖር ነበር በማለት በሐሰት የወነጀለው፡ በግፍ በሻዕቢያ ለዘመናት ታሰሮ አብይና ኢሳያስ ሲዋደዱ መጨራሻ ዕድል አግኝቶ ተፈትቶ እስር ውስጥ ለአመታት ስለቆየ መራመድ ሰለማይችል “በተገፊ ወንበር” እየተገፋ አዲሰ አበባ ወደ አገሩ የገባው በኮሎኔል ታደሰ ሙሉነህ ስም እየተጠራ ያለው አረጋዉያን የደከሙ እናቶች፤ ፊታቸው የጠወለጉ ችጋርና የኑሮ ውጣ ወረድ ያንገላታቸውን ነው እምብርክክ በማስድ በሽለላና በቀረርቶ እየተጨፈረ ዓለም እንዲያያቸው የሆነው፡፡

እነዚህ ሰን ጎጃም ውስጥ ልዩ ስሙ ገርጨጭ በተባለ ወረዳ ሪ የነበሩት በእምብርክክ ካስድዋቸው 13 ወስጥ 4 ቱ ፡ 4ቱ  በጥይት ተደብድበው ከሞቱት ሰዎች ስም ዝርዝር

1)    1) ወረዳው ቤተ ክሕነት ሥራ አስኪያጅ የነበሩት  መሪታ ግሩም

2)   2) አቶ አዘነ ደም

3)   2)  አቶ  አስማማው አ

4)   4)  ወ/ሮ ላይን አየሁ ዳኛው   (የክስተንሺን ሰራተኛ)

ይህ የዘመነ ካ ሙሶሎኒያዊ የጫካ ሕግ /ግፍ/ በሚመለከት ቪ ኦ አማርኛ ዜናም ዘግቦታል፡፡

ሁለተኛው ጉድ ደግሞ አሁንም ዘመነ ካሴ የሚያዘው ሰንደቅ ዓላማችንን የሚያቃጥል ታጣቂ የባንዳዎች ስብስብ ደግሞ የእስክንድር ነጋን ምስል ያለበት ከናቲራ ሲያቃጥል በቪዲዮ አይተናል፡፡ ይህ ድርጊት የፈጸመው የዘመነ ታጣቂ ሰንደቅ ዓላማችንን ባለፉት 36 አመታት ሲቃጠልና ሲረክስ እያዩ ያደጉ ወጣቶች ናቸው፡፡ ዘመነም የነዚህ ትውልድ አንዱ ስለሆነ እርሱ ሳይፈቅድ ትግሬዎችና ኦሮሞች ሲያደርጉት እንደነበረው ሁሉ ድርጊቱ በቪዲዮ ሕዝብ በተሰበሰበበት ተቀርጾ በቪዲዮ አይሰራጭም፡፡

ሲያቃጥሉትም የተከበሩት ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለሰላሴን በዋልጌዎች ሲሰደቡ እንደነበረው ዓይነት ስድብ እሰክንድርንም <<ሌባ>> <<ሌባ>> እያሉ ከዚያም አልፈው እንገድልሃለንገድለንህም ሬሳህንም እናቃጠለዋል>> እያሉ የእርሱ ምስል ያለበት የስንደቅ አላማን ምስል ሲያቃጥሉ ነውር መሆኑን የነገራችው መሪ የለም፡፡

ሁለት ነገሮች አይደፈሩም!

(1) ከጠላት ሸሽቶ ገዳምና ቤተ-ጸሎት በተማጽኖ የገባ ተማጻኝ (የተጠለለ ሰው) ቤተ-ጸሎቱን የሚያስተዳድሩ ሐላፊዎችም  አሳለፈው ለአሳዳጁ አይሰጡም፡ ፈላጊውም የቤተ-ጸሎቱን አጥር ግቢ ጥሶ አምላክ ጥላ ሥር ሮጦ የተሸሸገን ሰው መንጭቆ አይወስድም፡፡ ፈላጊው ግቢውን አይጥስም (ፈጣሪን መጣስ ነውና)፡፡ ቤተ-ጸሎት ላይም ቦምብ ፤ ጥይት አይተኮስበትም፡፡ በእሳትም ማቃጠል ነውርና ወንጀል ነው፡፡

 (2) ምንም ይሁን  ሰንደቅ ዓላማው ላይም ፎቶ ቢለጥፈበትም በጽሑፍ ማወገዝ እንጂ ማቃጠል ነውር ነው፡፡ ሰንደቅ ዓላማ ማለት ገዳምና የማይደፈር ሃገራዊ አርማ/ምልክት ማለት ነው፡፡ የእስክንድር ፎቶ ሰላለበት፤ የዘመነ ምስል ስላለበት፤ አንበሳ ሰላለበት፤ የነገሥታቱ የነ ዮሃንስ፤ምንሊክ እና ሃይለሰላሴ ምስል ሰላለበትና ሰለጠላሃቸው ወድቃ የተነሳቺው ሰንደቅ ዓላማ ያለበተን ቀለም መርገጥና ማቃጠል ነውር ነው፡፡

አንድ ሰው የመለስ ዜናዊ መከራከያ ካልተከተለ በቀር፡፡ እርኩሱ መለስ ያለው፦ “ከጨርቁ በስተጀርባ” ያለው “ኢትዮጵያ፤ ዮሃንስ ፤ ምንሊክ ፤ ሃይለሰላሴ ፤ ኦርቶዶክሰና አማራን” እንጂ ጨርቁን ማንም ሰው ሊያውለበልበው ይችላል!” በማለት ያሰተማረውን አደገኛ ጣሊያናዊ ቅስቀሳና ሕግ ሰንደቃላማችን ይኸው ከላይ በጠቀስኩዋቸው በወጣቶቹ የአማራ ብሔረተኞችም ጭምር ተዋርዳ እየተቃጠለች ነው፡፡

ሰንደቅ ዓላማን ማሳነስና ማቃጠል የጀመሩት “ፋሺስቶች” ናቸው፡፡ የሙሶሎኒ ጀግኖ የሚባሉ ሙሶሊኒ የሚያደንቃቸው ተግባራቸውን የሚጋራቸው ሁለት ሰዎችን ልጥቀስ፡፡የፈረንሳዩ አብዮተኛ (1) Blanqui (the man of the barricades the organization of revolutionary violence) 

(2) Gustave Herv’e), from which Musolini took over the slogan “to us the national flag is a rag to be planted on a dunghill”

(1) ብላንኪ (አመጽ አዘጋጁ አብዮተኛ) 

(2) ጉስታቭ ሄርቪ)፣ “ለእኛ ብሄራዊ ሰንደቅ አላማ ማለት በቆሻሻ ጉድጓድ ላይ የሚተከል ጨርቅ ነው”  ይህ መፈክር ሙሶሊኒ ተረከቦ ያሰተጋባው ነበር፡፡

ከሙሶሊኒ የተረከበው ደግሞ ትግው መለስ ዜናዊ ነው፡፡ ከመለስ ቀጥሎ የጎጃሙ አዲሱ የሙስሎኒ ቡቃያ የዘመን ካሴ ታጣቂው ቡድን  ነው፡፡

በደማቅ የሚታዩ ሦስቱ ሕብር ቀለማት ዓይናቸው እያየ ሲያቃጥሉት ጥላቻ ምን ያህል ከፉ መሆኑ ያሳያል፡፡ ይህ አደገኛ አምሐራዊ በሔረተኛ ቡድን ልክ እንደ ትግሬ ብሔረተኞቹና እንደ ኦሮሞ ብሔረተኞቹ በሰንደቅ ዓላማና በአረጋውያን የሚዘምት “ገድየህ ሬሳህን አቃጥለዋለሁ በማለት ሁለት የፋሺስት ሥርዓቶችን የተጋተረ ፋሺቶች በሚፈንጩባት ከተማ ብቻውን ሰንደቅ ዓላማችንን እያወለበለበ የምኒልክን ሐውልት ሲያቆሽሹት እያጸዳ ፤ ፋሺቶች በደማሚት እንዳያፈርሱት የጠበቀ ፤ ቅርሶች ሲፈርሱ "ኡ ኡ!!" ያለ፡ ዓለም የሸለመው ፤ የተኛውን አዲሰ አበባ ወጣቱን እመቢተኛነትን ያሰተማረ አሰገራሚ የጽናት አርአያ የሆነውን ታላቁን እስክንድርን ገድሎ ሬሳውን ለማቃጠል (ጥላቻ ሕሊናን ያሳውራልና ፤ ስጋውንም ሊበሉት ይችሉ የሆናል) የሚዝት እጅግ አስፈሪ የፋሺስት ሕሊና ስናይ በቀላሉ ቸል ተበሎ መታለፍ የለበትም፡፡

ይህ ሞገደኛ አማራዊ የብሔረተኛ መንጋ (ቫየለንት ግሩፕ) ሕዝብ ሰብስቦአረጋዉያንን እምብርክክ ማስኬድና መረሸን ለሚገድሉት የእስክንድር ሬሳም እንደሚያቃጥሉ እየነገሩን ያሉት “አታቪስት Atavist)” (እንሰሳዊ ብሕሪ የተላበሱ ሰው መሳይ አራዊቶች) ባሕልን ፤ሃይማኖትን ፤ ሕግን የሚጻረሩ ስለሆኑ ካሁኑኑ “በፖለቲካና በብስለት የሚመራ አራሚና መሪ” ካላገኙ እያደገ ሲመጣ <<አማራዊ ኦነግ>> ሆኖ ካሁን በፊት ያየናቸው ኦነግ እየፈጸማቸው ያሉት ትግባሮች በከፋ መልኩ እንዳይፈጽሙ እሰጋለሁ፡፡

በመጨረሻም 

ዘመድኩን በቀለ ሰለተባለ (ካሁን በፊት ብዙም ያላወቅሁት) አሁን አሁን እያወቅኩት ስለ መጣሁት ሰው አንድ ነገር ልበልና እሰኪ ከዚህ በታች የተናገርውን እስክንድር ከአብይ ጋር እየሰራ መሆኑን ከአሥመራና ከብርሃኑ ነጋ ጋር በምስጢር ግንኙነት እንዳለው ውንጀላውን በማስረጃ ያሳየንና የጥንት ወዳጄ የነበረው የሊያስ ክፍሌ ንብረት ነው የሚባለው መረጃ ቲ/ቪ ይህንን ንግግር አስተላልፎለት ይሆን ወይስ በግል “ሚዲያው” ይሆን?

እንዲህ ይላል፡

<< እስክንድር ካለበት መከላከያው 5 ኪ/ሜትር ነው እሚቀመጠው፡፡ እስክንድርን አይነኩትም፡፡ሰንሰለቱ ያለው ከበረሃኑ ነጋ ጋር ነው፡ በብረሃኑ አድርጎ በአስመራ በኩል አድርጎ፤ በእነ ሃብቴ በኩል አድርጎ በእነ ኮሎል ፈንታሁን አድርጎ ሸዋ ነው የሚገባው>> (ዘምድኩን በቀለ)፡፡

ይህ ጤናው የተሟላ ሰው የሚናገረው ሰው አይመስለኝምና የሚያከብሩት ካሕናት ጸሎት አድርጉለት፡፡ይህ በጣም ፤ በጣም ካስገረሙኝ እስክንድር አሳምነውን አስግደሎታል ከሚሉ “እብዶች” ከሰማሁት ሁለተኛው ካሰገረሙኝ ውንጀላዎች ውስጥ ነው፡፡ ቱራማታይዝ የሆኑ ሕክምና የሚፈልጉ ብዙ ወንድሞችና እህቶች እንዳሉን አመላካች ነው፡፡

ሰላም ሰንብቱ

ጌታቸው ረዳ