Tuesday, May 11, 2021

የዘንደሮው “የዒድ አደባባይ” ጠብ ጫሪ መፈክር ገልጠን ስናየው! ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay) 5/10/2021

የዘንደሮው “የዒድ አደባባይ” ጠብ ጫሪ መፈክር ገልጠን ስናየው!

ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay)

5/10/2021

የነ አሕመዲን ጀበል ድማጻችን ይሰማ ግልጽ ጥያቄዎቻቸው ምን እንደነበሩ ማህደሮቻቸው እንደገና ላስፈትሻችሁ

ሰሞኑን አክራሪ ውሃቢ ተከታዮች ዛሬም መስቀል አደባባይ ካልሆነ ሌላ ቦታ በዓላችንን አናከብርም ብለው “ኢድ አደባባይ” የሚል ጠብ ጫሪ መፈክር ይዘው እንደታዩ ይታወቃል።አክራሪ ውሃቢ እስልምና በኢትዮጵያ እነ አቡከርም ሆኑ እነ አሕመዲን ጀበል በወያኔ ሥር ዓት ከመታሰራቸው በፊት ወጣቶችን እየሰበሰቡ ሃይመኖት እየሰበኩ ጣልቃ በማስገባት ክርስትናን እና ኢትዮጵያን እንዴት ሲያበጠለጥሉ እንደነበር በርካታ መስረጃ ንግግሮቻቸው እያቀረብኩ ሳስነብባቸሁ እንደነበር ይታወሳል። ምናልባትም ለፌስ-ቡክ እንግዳ ስለሆንኩኝ ብዙ ወዳጆቼ “ኢትዮጵያን ሰማይ” ሳታውቁት ኖራችሁ ስለሚሆን በድረገጼ ላይ ካቀረብኳቸው ሰነዶች አንዱ እነሆ ላስነብባችሁና የውሃቢ አክራሪ አስልምና ተከታይ ኢትዮጵያዊያን እስላሞች “አደፈጡ እንጂ ልብ እንዳልገዙ” እንድታውቁት ይረዳልና ይህንን አንብቡ።

 

 ይህ ጽሑፍ ለማንበብ በቀይ ቀለም እና አመላካች መስመሮች የተሰመሩባቸው ማገናዘቢያዎች ስላሉት ከፌስ ቡክ ይልቅ (Ethiopian Semay) ላይ ብታነብቡት ለማንበብ ይመቻል።

ይህ ጽሑፍ የላከልኝ ጸሐፊ ትዝ ባይለኝም በኢትዮ ሰማይ ድረገጽ ታትሞ የነበረ ጽሑፍ ነው። ግራኝ አሕመድ የነፃነት አርበኛ እያለ በመጽሐፉ ሲያሞካሸው የነበረው ጸረ ክርስትና ጽንፈኛው አሕመዲን ጀበል ዛሬ ምላሱን ለዳግም ሲያውተረትር እያደመጥነው ነው። ስለሆነም እንደገና ወደ ኋላ ተመልሰን የዚህ እንቅስቃሴ ህቡእ ፍላጎት ምንነት ዳግም መፈተሹ አስፈላጊ ስለሆነ እነሆ 6 አመት በፊት የነበረው የሙስሊሞቹ ፍላጎት ከሸሪዓ መንግሥት ምስረታ ፍላጎት ጋር የተገናኘ እንደነበረና ዛሬ ግን እስላማዊው አብይ አሕመድ አጀንዳቸውን አስፈጽሞላቸው እጅና ጓንቲ ሆነው እየሄዱ ነው። 6 አመት በፊት የነበረው የሙስሊሞቹ ጥያቄ ምን ነበር?

 22 ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያን ያስተዳደረ ሙስሊም የለም” (የሙስሊሞች የተቃውሞ ድምጽ)

(አንድ አድርገን ነሀሴ 5 2005 .)-

ባሳለፍነው ዕለተ ሀሙስ በሙስሊሞች የበዓል እለት አዲስ አበባ በብዙ ቦታዎች በተቃውሞ ስትናጥ መዋሏን የተለያዩ መገናኛ ብዙሀን ኢቲቪን ሳይቀር ተቀባብለው መዘገባቸው ይታወሳል፡፡ በተነሳው ግጭት ፖሊስ ብዙዎችን ማረፊያ ቤት ማጎሩም ይታወቃል፡፡ ባሳለፍናቸው 3 ቀናት ፖሊስ ጣቢያዎች የምሳ እና የእራት ሰሀን በያዙ ሰዎች ተከበው ውለዋል፡፡ በወቅቱ የታሰበበትና የተጠና ሰላማዊ ሰልፍ መሆኑን ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚገኙ መረጃዎች ያመለክታሉ የባነሮቹ ተመሳሳይነት የመፈክሮቹ ይዘት ተቃውሞ የተነሳበት ሰአትና ቦታ ሰልፉ ታሰበበት መሆኑን ያመለክል ፡፡

እንደ ስታስቲክ ኤጀንሲ መሰረት በአዲስ አበባ ውስጥ 72 በመቶ ክርስቲያኖችና 16 በመቶ ሙስሊም ማህበረሰብ ይኖራል የሚል መረጃ ቢኖረውም የወጣው ሕዝበ ሙስሊም ግን እውን ይህ ሁሉ ሰው አዲስ አበባ ውስጥ ይኖራልን? የሚያስብል ጥያቄ አስነስቷል ፡፡ በመሰረቱ በበዓላቸው ወቅት ከዚህ በፊት በኢድ በአረፋ እና በተለያዩ ወቅቶች የዕምነቱ ተከታዮች ወደ ገጠር የመግባት ሂደት የሚስተዋል ሲሆን በዚህ በዓል ግን የተገላቢጦሽ ሆኖ አልፏል ፡፡ሰዎች ከአዲስ አበባ ወደ ገጠር የሚገቡበት በዓል ሳይሆን ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ወደ አዲስ አበባ የመጡበት ሆኖ ተስተውሏል ይህ ሁኔታ በቁጥር ብዛታቸውን ለማሳየት እና ድምጻቸውን እጅጉን አጉልተው ለማሰማት እንደተጠቀሙበት ለመመልከት ተችሏል፡፡ ባሳለፍነው ዓመት 2004 . ሀምሌ ላይ በአወሊያ ትምህርት ቤት የተጀመረው ተቃውሞ ዛሬ እዚህ ደረጃ ሊደርስ ችሏል ፡፡ በወቅቱ ጥያቄው ከአወሊያ መስኪድ ከለሊቱ ስድስት ሰዓት በግላጭ በማይክራፎን ‹‹ጅሀድ›› በማወጅ ነበር ነገሩን የቆሰቆሱት ይህ የጅሀድ ጥሪን የተቀላቀሉ በርካቶች በወቅቱ ከፌደራል ፖሊስ ጋር በመጋጨት ብዙዎች መታሰራቸውን ብዙዎች ላይ ቀላልና ከባድ አደጋ መድረሱን የአንድ ዓመት ትውስታችን ነው፡፡ ይህ በሆነ ከአንድ ቀን በኋላ በአዲስ አበባ በአምስቱም አቅጣጫዎች በህዝብ ማመላለሻ መኪናዎች ወደ አዲስ አበባ ሲገቡ የነበሩ በርካታ የእስልምና ተከታዮችን መታወቂያቸውን ፖሊስ እየተመለከተ  ወደ መጡበት እንዲመለሱ ሲያደርግ እንደነበርም በወቅቱ ለመመልከት ችለናል፡፡ ለምሳሌ በናዝሪት መስመር 3 ቀናት ያህል ከአዳማ ወደ አዲስ አበባ የሚገቡ የህዝብ ማመላለሻ መኪኖች ፖሊስ መታወቂያቸው እያየ ሲፈቅድና ሲከለክል ነበር በመሰረቱ የሰዎችን ከቦታ ቦታ የመዘዋወር መብት ሕገ-መንግስቱ ቢፈቅድም ችግር ሲፈጠር በደቦ ከሀገር ወደ ሀገር መንቀሳቀስ ምንን ያመለክታል ? እውን እነሱ እንደሚሉት አዲስ መስኪድ ለመመረቅ ወይስ በክብሪት የተነኮሰችው እሳት ወደ ሰደድ እሳትነት ለመቀየር?

የሩቁን ያላስተዋለ አለቃ፣ ኃላፊ ወይም መሪ፣ አስተውሎም ያላመዛዘነ፤ አመዛዝኖም በጊዜ እርምጃ ያልወሰደ ከሆነ፤ በአደጋው ውስብስብ መረብ ውስጥ ገብቶ መተብተቡ አይቀሬ ነው፡፡ አሁንም እየተስተዋለ ያለው ይህ ነው ሲጀመር በእኩለ ለሊት በአዲስ አበባ  ‹‹ጅሀድ›› ያወጁትን ሰዎች በፍትህ መድረክ ላይ ፍርድ ስላልተሰጠ ነገሮች እዚህ ሊደርሱ ችለዋል ፡፡ እንደተጣደ ወተት መቼ ሊገነፍሉ እንደሚችሉ የማናውቃቸውን ነገሮች በዐይነ-ቁራኛ ማየት፤ ተገቢውን ማርከሻ ማወቅና በጊዜው መጠቀም ተገቢ ሆኖ ሳለ መንግሥት ሁሉን በአግባቡ እና በጊዜው ተገቢ መልስ መስጠት ባለመቻሉ እዚህም እዛም የሚሰሙ ሃይማኖታዊ መሰል ፖለቲካዊ ጥያቄዎች እየተበራከቱ ይገኛሉ፡፡

በሰልፉ ወቅት ከተነሱ በርካታ መፈክሮች ውስጥ አንዱ22 ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያን ያስተዳደረ ሙስሊም የለምየሚል ነበር፡፡

 ይህ ጥያቄ በሀገሪቱ ላይ እስላማዊ መንግሥት እንዲቋቋም የሚፈልጉ ሰዎች ጥያቄ ነው፡፡ አሁን ሰዎቹ ሃይማኖታዊ ጭንብላቸውን እንደለበሱ የወደፊት ራዕያቸውን ለማሳካት አንዱን ጥያቄ እንዲህ ብለው አቅርበውታል፡፡ የዛሬ ዓመት ገደማ ሙስሊም ወንድማማቾች ፓርቲ ለመመስረት ጥያቄ ማቅረባቸውም መዘንጋት የለበትም፡፡

የሃይማኖት ጉዳዮችን እንዲከታተል እና ከስር ከስር መፍትሄ እንዲሰጥ በሚኒስትር ደረጃ የተቋቋመው የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስትር ስራዎቹ ከሪፖርትነት ይልቅ መፍትሄ ሰጪ ሲሆኑ አይስተዋልም ፡፡ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ጥቂት አክራሪዎች ቤተክርስቲያን ሲያቃጥሉ ህዝበ ክርስቲያኑን በሰይፍ ሲያሳድዱ ሲብስብ የህይወትን መስዋዕትነት የሚያስከፍል ድርጊቲ ሲከውኑ ሚኒስትር መስሪያ ቤቱም ሆነ መንግሥት ይህ ነው የሚባል መልስ በጊዜው መስጠት ባለመቻላቸው ሰዎቹ የልብ ልብ እንዲሰማቸው አድርጓቸዋል ፡፡ ትላንት በቤተክርስቲያኖች ላይ ለተነሳው ሰይፍ መልስ የሚሰጥ አካል ባለመኖሩ ዛሬ ዱላዎችና ሰይፎችም ወደ መንግሥት አካላት ተነጣጥረው ይገኛሉ፡፡

 ከአመት በፊት በፓርላማ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ሁኔታውን በግልጽ ለተወካዮች ምክር ቤት ማቅረባቸው ይታወቃል፡፡ ሱኒ ሰለፊ ወሀቢያ ምን ማለት እንደሆነ ላልገባው የኢትዮጵያ ህዝብም ሆነ የህዝብ ተወካይ በግልጽ አስቀምጠዋል፡፡ ከሞላ ጎደል የማይመለከታቸውን የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተቋማት ከመወረፋቸው በስተቀር ምስሉ ላልገባቸው ወገኖች ግንጽ እንዲሆን ጥረዋል፡፡ ነገር ግን በተግባር የተነገረውን ነገር ለማስቆመ መንግሥት እርምጃ ሲራመድ ማስተዋል አልተቻለም፡፡ የአሜሪካ መንግሥት ከአዲስ አበባ ለስቴት ዲፓርትመንት የላከው በዊኪሊክስ ተጠልፎ የወጣው መረጃ እንደሚያመለክተው በኢትዮጵያ ውስጥ ወሀቢያን ሰፍረውበታል አስተምህሮታቸውን ያካሂዱበታል ካለባቸው ቦታዎች ውስጥ ደሴ ሀረር ጅማ እና አርሲ ይገኛሉ ፡፡ አሁንም ከአመታት በፊት የተተከለችው የአክራሪነት ፍሬ ከሳምንታት በፊት በደሴ ፍሬ እያፈራች መሆኗን መመልከት ችለናል፡፡

 ግብጽ አሁን ላለችበት ውጥንቅጡ ለወጣ ሁኔታ ትልቅቁንና የአንበሳውን ድርሻ የያዘው የሙስሊም ወንድማማቾች ፓርቲ ሕገ-መግስቱን ከሼሪያ ህግ በታች በማድረጉ እና መንግስቱም እንደ ኢራን እና መሰል ሀገራት እስላማዊ መንግሥት እንዲሆን መጣሩ ነበር ፡፡ አሁንም ኢትዮጵያ ወደዚህ መስመር እንድትሄድ የሚፈልጉ የቀን ቅዠተኞች ቀላል አይደሉም፡፡ ጥያቄያቸውምኢትዮጵያ ያስተዳደረ ሙስሊም የለምወደሚል ተሸጋግሯል፡፡ የትላልቅ ሰላማዊ ሰልፎች ጥያቄዎች በአንድ ጊዜ የሚመጡ አይደሉም ሲጀመርየመጅሊስ ምርጫ ይካሄድ መጅሊሱ እኛን አይወክለንም›› አሉ፡፡ ሲቀጥልመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ እናቋቁም”” ተባለ፡፡ ሲቀጥል መጅሊሱ እንደማይወክላቸው የሚያሳምን የህዝብ ድምጽ እናሰባስብ አሉ፤ በህዝቡም ድምጽ መጅሊሱ ፈቅዶ ‹‹ምርጫው አካሂዱ ትችላላችሁ›› አላቸው ፡፡ ሲቀጥል ‹‹ ምርጫ መካሄድ ያለበት በመስኪድ እንጂ በቀበሌ መሆን የለበትም›› የሚል ጥያቄ አነሱ እያለ እያለ  የታሰሩት የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ይፈቱየደሴው ሼህ ግድያ ድራማ ነውመጅሊሱ (ምክር ቤቱ) እኛን አይወክልምምርጫው ፍትሀዊ አይደለም አህበሽ የተባለው አስተሳሰብ ይቅርመንግስት በሀይማኖት ጣልቃ አይግባአወሊያ የሙስሊሙ ተቋም ነው እያለ እያለ አሁን22 ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያን ያስተዳደረ ሙስሊም የለምየሚል ጥያቄ ላይ ደረሰ………… ነገስ ጥያቄው ምን ይሆን?

አሁን የሀገሪቱ አስተዳዳሪ በስም አቶ /ማርያም ደሳለኝ Only Jesus (ጴንጤ) እምነት ተከታይ ናቸው ምክትሎቻቸው ሦስቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች ውስጥ ሁለቱ የእስልምና እምነት ተከታዮች ናቸው ፡፡ የምክር ቤቱ ቁንጮ አቶ አባዱላ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ ናቸው የኢህአዴግ /ቤት አላፊም ሙስሊም ነው፡፡ ከኦሮሚያ ክልል ከተመረጡ 169 የህዝብ ተወካዮች 70 በላዮቹ የእስልምና እምነት ተከታዮች ናቸው (ምንጭ -የምክር ቤቱ ድረ-ገጽ http://www.hopr.gov.et/HPR/faces/c/mps.jsp)

በጠቅላላው ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫ 547 መቀመጫ ውስጥ 220 በላይ የእስልምና ተከታዮች ናቸው:

ካሉት 16 ቋሚ ኮሚቴዎች 

(1)-አቶ ሳዲቅ አደም የሕግ፤ የፍትህና አለስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ

(2)-/ ፈቲያ ዩሱፍ የባህል፤ ቱሪዝምና መገናኛ ብዙኃን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሊቀመንበር

(3)-/ አይሻ እስማኤል የባህል፤ ቱሪዝምና መገናኛ ብዙኃን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሊቀመንበር

(4)-/ ጫልቱ ሳኒ የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ /ሊቀመንበር

(5)-አቶ መሐመድ አብዶሽ የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሊቀመንበር

(6)-አቶ መሐመድ ዩሱፍ አርብቶ አደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሊቀመንበር

(7)-/ ሙፈሪሃት ካሚል የትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሊቀመንበር

በመሆን ካሉት 16 ቋሚ ኮሚቴዎች ሰባቱን (7) እነሱ እንደተቆናጠጡት አጥተውን ይሆን? እነዚህ ቋሚ ኮሚቴዎች ናቸው: 

በሀገሪቱ ውስጥ ያሉት ሚኒስትር መስሪያ ቤቶች የሚቆጣጠሩት በም/ቤቱ የአማካሪ ኮሚቴ አባላት 21 ሰዎች ዝርዝር ውስጥ ዘጠኙ (9) ሙስሊሞች መሆናቸውን ሳያውቁ ቀርተው ይሆን?  ከዚህ በላይስ እንዴት አድርገው መውረር ነው የፈለጉት?  ‹‹አንድ አድርገን›› ይችን ለመረጃ ያህል ያወጣች የሀገሪቱ የበላይ ህግ የሚወጣበት ቦታ ምን አይነት ስብጥር እንዳለው ለማመላከት ሲሆን ጥያቄውን መጠየቅ እንኳን ቢኖርበት በማን መጠይቅ እንዳለበት ከማመላከት ውጪ ነገ መሪዎቻችንና ተመራጮቻችን እነማን እንደሚሆኑም ለማሳየት ጭምር ነው፡፡ ታዲያ እነዚህ ሰዎች አላማቸው ምን ይሆን ? እነዚህ ሰዎች እንደፈጣን ቢፍቋቸው ጥያቄያቸው ሌላ ሆኖ እንደሚገኝ ልናውቅ ይገባል፡፡

POSTED AT ETHIO SEMAY