Sunday, June 30, 2019

ነጭ ባንዴራ አውለብላቢዎቹ እና ደም ተፊው የ666ቶቹ ተቀጣሪው ጋኔል (ክፍል4) ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay)


ነጭ ባንዴራ አውለብላቢዎቹ እና ደም ተፊው የ666ቶቹ ተቀጣሪው ጋኔል (ክፍል4)
ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay)

ትችቴን ከመጀመሬ በፊት በሚከተለው ንግግር ጥቅስ ልጀምር፡

“አማራን ለማፍረስ ያልተሰራ ሴራ የለም። ይሄ ምድር ላይ የተቀበረ ሳይሆን ምድር ላይ ወጥቶ እያየነው ያለው ነው።” (ብ/ጀኔራል አሳምነው ጽጌ)

“በፍቅር ከመጡ አማራዎች ስለሆነን ልብሳቸውንም ቢሆን አጥበን ንቀበላቸዋለን። በጠብ ከመጡ ግን ልብሳቸው ላይ እናሸናቸዋለን። ለዚህ መዘጋጀት አለባቸው!” (ዘመነ ካሴ ለደብረማርቆስ ወጣቶች ካደረገው የድምፅ ንግግር ወደ ጽሑፍ ከለወጥኩት ጥቅስ)

አገሪቷን በደም እየበከለ ተመናምናም ቢሆን አገር ተብላ ስትጠራ የነበረቺው አገር “ወደ መቃብር” ልትጠጋ “አንድ አርብ” ብቻ ያስቀራት አብይ በሚል ስም የሚጠራው ትልቅነቱን ያዋረደ “የአናርኮ ፋሺሰቶቹ መሪ አብይ አሕመድ” በሚያስደነግጥ ሂደት “በ12 ወራት” አገራችን ከድጡ ወደ ማጡ አስገብቶ እናቶች፤አባቶች እና ህጻናት የደም እምባ እንዲያነቡ አድርጓል። ይህ ደም የጠማው ግለሰብ መጽሐፍ ቅዱስ የጠቀሳቸው የ666ቶቹ ተቀጣሪ አባልነቱን ተጠቅሞ ጸረ ኢትዮጵያ ሃይላት ከጀርባው አስቁሞ በሕዝባችን ደም ተጨማልቋል። ለ27 አመትም ሆነ የስለላው እርካብ ረግጦ መንግሥታዊ መንበሩን ከተቆጣጠረ በ12 ወራት ውስጥ በሕዝባችን ላይ የደረሰው አሳዛኝ ጥቃት ተጠያቂ ነው።

 የመጀመሪያው ጠላቱ አማራ መሆኑን ገና ከመነሻው የመጀመሪያው የትግራይ ጉብኝት አድርጎ ወደ ባሕር ዳር ሄዶ አማሃራዊ ችግሮች በሚመለከት ለቀረበለት ቅሬታና ጥያቄ  የመለሳቸው  ‘ጸረ አማራ መልሶች’ ሲመልስ ለማን እንደቆመ ግልጽ ካደረገበት ቀን ጀምሮ እስካሁን ድረስ በአማራ ሕዝብ ላይ ጥቃቱ ተጠናክሮ አሁን ላልንበት የነጀኔራል አሳምነው ጽጌ አሳዛኝ ሕልፈት እንድናይ የአብይ አሕመድ ጸረ አማራዊ የሴራ ውጤት ነው።

 ይህ አገር የማፍረስ ሴራው እንዲሳካም ‘ባንክ የሚዘርፉ፤ ቤተ ጸሎት የሚያቃጥሉ፤ሴቶች የሚደፍሩ፤ አረጋውይንን የሚደበድዱ የየኦሮሞ ዋልጌዎችን  መንግሥታዊ ከለላ እና ተሳትፎ እየተደረገላቸው ቸል ብሎ በማየት፤ የፈለጉትን ስራ እንዲሰሩ ፈቅዶ በሚሊዮን ዜጎች እያፈናቀለ ቤቶቻቸውን በማፍረስ እናቶችንና ህጻናትን ለዋይታ ጩኸት የዳረጋቸው ዋና ተጠያቂ የ66ቶቹ ተቀጣሪው “እርካብና መንበር” መጽሐፍ ደራሲው አብይ አሕመድ መሆኑን የሕግ እና የታሪክ ባለሞያዎች ሊዘገቡት ይገባል።

የዓለም የዜና መስመሮች አጣብቦ እያነጋገረ ያለው ሰሞኑን ጎጃም ውስጥ ባሕርዳር ከተማ የታየው የመገዳዳል አሳዛኝ ክስተት ከምን የተከሰተ ውጤት ሳይሆን አብይ አሕመድ የትግሬ የበላይነትን ከኦሮሞ ጋር አቀናጅቶ “ባንዳ አማራ ባለሥልጣኖችን” በማቀፍ ‘ዋልጌ የኦሮሞ ባለሥልጣኖችንና ሥርዓተ አልባ የሆኑ የኦሮሞ “ቄሮ” ነፍጥ አንጋቾች “ጉልበት አግኝተው” ሰላማዊ አማራ ገበሬዎች በሚኖሩበት ቦታ ሰርገው እየገቡ ሽብር እየነዙ፤ አማራዊ ስነ ሉቦና እና አማራዊ ታጋዮችን ለይቶ በማጥቃት ‘አዳክሞ ላንዴና ለመጨረሻ ተከብቦ በስርዓተ አልባ ቄሮዎች ጫማ ስር እንዲወድቅ እየተደረገ መሆኑን” የተመለከቱ “የአማራ አገራውያን ታጋዮች” የሰነዘሩት የጸረ-ከበባ ክስተት እንደሆነ መጠራጠር የለባችሁም

ይህንን ከበባ ተሎ ብሎ የገባቸው ‘ሃገራውያን የአማራ ታጋዮች’ “ብ/ጀኔራል አሳምነው ጽጌ፤ አርበኛ መሳፍንት ተስፋው፤ ወጣት ዘመነ ካሴ…ወዘተ” እየመጣ ያለው ከበባ በንግግሮቻቸው ግልጽ አድርገዋል። ስጋታቸው አደባባይ ላይ ሳያመነቱ ሊገልጹት የተገደዱበት ምክንያትም እየጎለበተ የመጣው “ኦሮሞዊ ጡንጫ” ስጋቱ ለነሱ ብቻ ሳይሆን ለአገሪቱም ስጋት እየሆነ መምጣቱ “የኦሮሞ ቄሮችና ሚሊሺያዎች እንዲሁም የኦሮሞ ባለሥልጣኖች በዜጎች ላይ ያደረጉዋቸው ማፈናቀሎች፤ግድያዎች፤ አመጾች፤ ዝርፍያዎች፤ ማስፈረራቶች፤ ነጠቃዎች፤ “ይህም የኔ ፤ ያም የኔ” የኦሮሞዎቹ “የኬኛ” ስግብግብ “ሁሉንም የማግበስበስ ባሕሪ” ያስከተለው ጥቃት ‘ከአማራ ህዳጣን ቤተሰቦች ጥቃት’ አልፎ በተቀሩት ዜጎች ላይም ያነጣጠረ “መፈናቀልና ግድያ” እያስተዋሉ ሲመጡ ስጋታቸው አደባባይ ላይ ሊያወጡት በመገደዳቸው መርሳት የለብንም።

ለምሳሌ ከጠቀስኳቸው ሦስት ሰዎች ከተናገርዋቸው ንግግሮችና ስጋቶቻቸው አንዳንዶቹን ልጠቅስ ነው። ጀኔራል አሳምነው ‘አፓርታይዱ አብይ አሕመድ’ በሕዝብ እሮሮ እና ተጋድሎ ወደ መንበረ ስልጣን ሲመጣ ከሞት ይፍታሕ እስር ብየና 9 አመት ታስረው ከእስር ተፈትተው የአማራ “ክልል” የጸጥታ ሹም ሆነው ሲያገለግሉ በነበሩበት ወቅት በአማራ ላይ ለ28 አመት የተሰነዘረው የዘር ማጥፋት ጥቃት እየተጠናከረ መምጣቱ ያሳሰባቸው እህ ጄኔራል ‘በወያኔ ትግራይ’ ታጣቂ ሃይሎች እና በታጠቁ ኦሮሞዎች” ከበባ ስር መውደቁ የአማራ ሕልውና ለመጨረሻ ጊዜ የሚፈታተን ችግር ስለሆነ ሕዝቡ ራሱን አስታጥቆ ራሱን መከላከል አዳይችል “በመንግሥት ደረጃ” ተጽእኖ ሲደረግ በማየታቸው፤  ውርደቱን ላለመቀበል ቆራጥ ውሳኔ በማድረግ “ ጥቃቱ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መቆም እንዳለበት” በመወሰን ያካባቢው ወጣት እያስታጠቁ እራሱን እና ሕዝቡን ከጥቃት እንዲከላከል ሲሞክሩ የኦሮሞዎቹ አፓርታይድ መሪ አብይ አሕመድ እርምጃው ስላልወደደለት ታፍኖ እንዲታሰር ወይንም ሴራ ጎንጉኖ እንዲገደል አብይ አሕመድ የቀየሰው መንገድ ሲታገሉ ከመሰዋታቸው በፊት ከተናገሩዋቸው ታሪካዊ ጥቅሶች አመላካች ንግሮቻቸውን እንመልከት::

የጀኔራል አሳምነው ጽጌ ስጋት፤
“አማራው መደራጀት አለበት። ሌሎቹ ወንድሞቻችን በዘር ተደራጅተው እኛ ዝም ማለት የለብንም። በአሁኑ ሰዓት አባቶቻችን የሄዱበት መንገድ ጊዜው ያለፈበት ነው! አያወጣም! በዘረኞች ምክንያት ተገፍተን ማንነታችን እንድንፈልግ ስለተጫኑን አማራው መደራጀት ግድ ይለዋል። ጠንካራ አማራ ከተደራጀ ጠንካራ ኢትዮጵያ መፍጠር ይቻላል፡፡”(ብ/ጄኔራል አሳምነው ጽጌ)

“ ሰሞኑን ሰፊ ስራ ጀምረናል። አሁን ያለው ሁኔታ እንዳለው አይቀጥልም፤ ሰሞኑን እንደሰማችሁት ችግራችን ከዚያ በላይ ነው፤ ሕዝቡ ራሱን ማደራጀት አለበት፡ ባካባቢው ሚሊሺያ፤ባካባቢው የጸጥታ ሃይል በጣም በተደራጀ ሃይል (ያንዣበበብንን ስጋት) ራሳችን ልንፈታው እንችላለን። ሕዝቡ ራሱን ማደራጀት አለበት፤ ራሱን ከዚያ በላይ ማዘጋጀት አለበት! ምክንያቱም አማራን ለማፍረስ ያልተሰራ ስራ የለም። ይሄ ምድር ላይ የተቀበረ ሳይሆን ምድር ላይ ወጥቶ እያየነው ያለው ነው።” (ብ/ጄኔራል አሳምነው ጽጌ)

 አባቶቻችን አንዳንድ ጊዜ የምትናገርዋቸው ንግግሮች አስተውላለሁ። አባቶቻችን ካሁን ባበሐዐበሐ ኋላ ፍትሕ ሲጓደል የሽምግልና፤የድርድር ንግግር አታድርጉ መሬት ላይ  ያለው እውነታ ለመናገር ሞክሩ፤ ከቻላችሁ ደግሞ እንደ “አቡነ ጴጥሮስ” መስዋእት ሁኑ” (ብ/ጄኔራል አሳምነው ጽጌ)

“በሦስት ቀጠና የተደራጀ የፌደራል የምርመራ ቡድን ክልልቻን ላይ መጥቷል። ይህ ሃይል ማኣከላዊ መንግሥት የላከው ይመስላል፤በፀጥታ ቢሮኣችን አውቅና የለውም፤ይህንን መዝግቡት፤ አስምሩበት።(ብ/ጄኔራል አሳምነው ጽጌ)

አሁን ያለንበት ዘመን ከሌሎቹ ዘመኖች እና ጊዜ የተለየ ጊዜ ነው።ለኛ ለአማራዎች በእጅጉ ከባድ ነው። በታሪክ ባላንጣዎቻችን አማራ ተወቃሽ ሆኖ ‘ያለ ሃጥያቱ’ እንዲሸከም ተደርጓል። በርእዮተ ዓለም ልንለያይ እንችላለን በአገር ህልውና ላይ ግን ድርድር የለም! አዴፓም፤አብንም፤ወጣቶችም ሽማግሌዎችም ሌላውም፤ ሌላውም አንድ መሆን አለብን። የሌሎችን አጀንዳ አስፈጻሚ መሆን የለብንም። የትግራይ ሕዝብ ወንድም ሕዝብ ነው፤እህት ሕዝብ ነው።ቲ ፒ ኤል ኤፍ እና የትግራይ ሕዝብ ይለያያሉ። ፓርቲዎች/ ድርጅቶች ከሳሚዎች/አላፊዎች ናቸው ሕዝብ ግን አያልፍም።”(ብ/ጄኔራል አሳምነው ጽጌ)

“አሁን እያየነው ያለው አጀንዳ ከሕግ በለይ ነው። አማራን የማፍረስ አጀንዳ ነው።”(ብ/ጄኔራል አሳምነው ጽጌ)

እኛ አረንጓዴ ብጫ ቀይ ሰንደቃላማችንን አዲስ አበባ ላይ ሰቀልነው፡ ኦሮምያ መሬት ላይ ደግሞ አወረዱት፤ ሌላ ቦታም አወረዱት!”(ብ/ጄኔራል አሳምነው ጽጌ)

“መጥፎ ሰዎች ሁሉ በሂደት ይጎዳሉ። ፈለግን አልፈለግንም ለሕግ ይቀርባሉ።ማንም በማንም ደም ተጠምቆ እዚህ ወምበር ላይ የሚቀመጥበት አይደለም። ከቻለ በራሱ መንገድ መንገዱን ይፈልገዋል። ፍለጎትን ለማስጠበቅ ከሆነ ደግሞ፤ ያ ዛሬ ብዙ መንገድ አያስኬድም፡ …ይስተካከላሉ።”(ብ/ጄኔራል አሳምነው ጽጌ)

የሌላ ሃይል ተላላኪ የሆኑት ሰዎች ተቁዋሙ እንዲያስተካክል ተነጋግረናል፤ካልተስተካከለ ደግሞ እኛ እናስተካክለዋለን።”(ብ/ጄኔራል አሳምነው ጽጌ)

እነ ዘመነ ካሴን በሚመለከት ያነሳችሁት ጥያቄ የክልሉ የፀጥታ ክፍል ሳያውቀው በማንም የበላይ ሃይል ትዕዛዝ፤በየትኛውም የስልጣን እርከን ያለ ባለስልጣን የፈለገው ንግግር ያድርግ ማንም ሰው ከዚህ ምድር ውስጥ ተወስዶ ወደ ሌላ አይሄድም።” (ብ/ጄኔራል አሳምነው ጽጌ)

በዕድሜ ጠገቡ ከጫካ የተመለሰ  አርበኛ መሳፍንት ተስፉ ከተናገራቸው ጥቅሶች ውስጥ

ሕዝቡ የታጠቀውን ትጥቅ እንኳ ሕጋዊ አድርጎ ሊያስመዘግብ ሲፈልግ በአማራ መስተዳድሮች ተኮርኩዶ ተይዟል። አሁን ግን የሚፈቅድ ከተገኘ ዝግጁ ነን።” (አርበኛ መሳፍንት ተስፉ ለጎንደር ወጣቶች ካደረጉት ንግግር)

አማራና ቅማንት እያሉ የሚያጣሉን የወያኔ ባንዳዎች እንጂ የትግራይ ሕብ እማ እህት እና ወንዳማማቾች ነን። ግን የትግራይ ሕዝብ በወያኔ በልቶ ጠጥቶ ካልጠገበ ልክ እንደኛው ትንሽ አቧራ በወያኔ መሪዎች ላይ እንዲያስነሳ እንጠይቀዋለን።” ((አርበኛ መሳፍንት ተስፉ ለጎንደር ወጣቶች ካደረጉት ንግግር)

ከወጣት ዘመነ ካዜ ታሪካዊ ንግግር ያገኘሁት ጥቅስ
ትናንት ከሰሜን አቅታጫ ስንባረር ፤ ትናንት ከምስራቅ አቅጣጫ ሲያሳድዱን፤በኢትዮጵያዊነት ስም ስንለምን “አማራ ናችሁ” ሲሉን ነበር። መፈናቀሉ መገፋቱ፤መገደሉ፤ መሽቀንጠሩ መርሮን “ካላችሁ እማ እሺ ‘አማራ ነን’ ስንል “የለም ኢትዮጵያውያን ናችሁ ማለት ጀምረዋል። ትናንት በአርባ ጉጉ፤አሶሳ ወተር፤በበደኖ በማንኛውም የኢትዮጵያ “ማኣዝናት’ ሁሉ ‘ኣይሆኑ ስንሆን’  “አረ በሕግ አምላክ” ባቀናነው አገር እኩል እንኑር ብለን ስንለምን ፤ኢትዮጵያውያን ነን ስንል “አማራዎች ናችሁ” ብለው ያባረሩን ከንፈር እንኳ ያልመጠጡልን ሰዎች “አማራ መሆናችንን ስንነግራቸው”  ኢትዮጵያዊ መሆናችን ሊነግሩን ዓባይን ተሻግረው ጠላዋ እንዳማረላት ሴት ይወጣሉ ይገባሉ!”

ማን ነው የነ እምየ ምኒሊክ የነ በላይ ዘለቀ የንጉሥ ሚካኤልን ልጆች ደፍሮ ስለ ኢትዮጵያዊነት ላመስተማር ደፍሮ የመስበክ ሞራል ያለው?!”

አሁን ስለፖለቲካ የምናወራበት የቅንጦት ውቀት ስላልሆነ “አብን ነን ሳንል፤አዴፓ ነን ሳንል፤ ይህ ነኝ፤ ያ ነኝ፤ “ሳንል” ከገባንበት የሕልውና ፈተና ሰብረን እንድንወጣ በጋራ እንስራ ብለን ስንጀምር፤ “በመካካላችን የነበረው ስንጥቅ ሊደፈን ሲመስላቸው” አብይ አሕመድ “ብርሃኑ ነጋን በፍጥነት ወደ ባህር ዳር ላከው”። አልተሳካም!!”

የአማራ ልጆች ለሕልውናቸው ባንድ ቆመው ሊታገሉ ነው ብለው ሲያስቡ ከበባው ሰብረው ሊወጡ ነው ብለው ሲያስቡ፤እነ አብይ እና እነ ለማ “አዲስ አበባ ላይ የጀመሩትን ፕሮጀክት” በፍጥነት ለማጠናቀቅ ሲፈልጉ “እኔን ዘመነ ካሴን ኢትዮጵያዊነትን ሊያስተምሩኝ ብርሃኑ ነጋን ወደ ባሕር ዳር ላይ ላኩልኝ ነው የምላችሁ!!”

አዲስ አበባ ላይ በፍጥነት ምን እየተሰራ እንዳለ ብትሰሙ ጨርቃችሁን ትጥላላችሁ። ለውጡ ገና አልተጀመረም! በአራት አቅጣጫ ከበባ ውስጥ ነን!!”

“እኔ ስለ ኢትዮጵያ ለማወቅ የአባቴን ቀረርቶ እየሳመሁ ያደግኩት ይበቃል፤ ምንም ሰባካ አያስፈልገኝም። እኛ ኢትዮጵያውያን ነን!” ምነው ይህ ግፍ ይፈጸምብናል። እኛ እንደ አይሁዶች እንጠቃ እንዴ? ኦሮሞው፤ ሓድያው ሶማሌው…. ወንድማችን እህታችን ናቸው ብለን ተጋብተን ወልደን ተዋልደን ባሕላችን ሰጥተን፤ የነሱንም ተቀብለን፤ ብምኖርባት የወላጆቻችን አገር “አማራዎች ናችሁ” እያሉ ያሳድዱናል!” ታዲያ ዛሬ ምን ቆርቸው ነው “እሺ አማራዎች ነን” ስንላቸው “ኢትዮጵያውያን ናችሁ” ማለት የጀመሩት?”

“እኔ ዘመነ ካሴ ጨዋ ፤የዋህ፤ሳቅ እና ቀልድ ተጫዋች ወጣት ነኝ። ሰላዊ ሰው ነኝ፤ ባራት መዓዝን ከብበውናል። ጦርነት እየጎሰምኩ ግን አይደለም። የመለማመጥ ፖለቲካ አልወድም፤ ሰላም እወዳለሁ፤ሰላማዊ ሰው ነኝ። ግን ሲነኩኝ አልወድም፡ ምክንያቱም አማራ ነኝ!”

“በየትም ሕብረተሰብ፤ በዚች ምድር ውስጥ “መብቱን” በልመና ለምኖ አግኝቶ አያውቅም! ስትደራጅ ጉልበት ሲኖርህ ትፈራለህ “የሰላም እንቅልፍ ተኝተህ ታድራለህ!”

“አማራዎች ነን ሰው እንወዳለን፤ ግን እንደ አንድ ወጣት በራችን ሲንኳኳ እየሳመሁ ነው።”

“በፍቅር ከመጡ አማራዎች ስለሆነን ልብሳቸውንም ቢሆን አጥበን እንቀበላቸዋለን። በጠብ ከመጡ ግን ልብሳቸው ላይ እናሸናቸዋለን። ለዚህ መዘጋጀት አለባቸው!” (ዘመነ ካሴ ለደብረማርቆስ ወጣቶች ካደረገው የድምፅ ንግግር ወደ ጽሑፍ ከለወጥኩት ጥቅስ)
  
እንዳነበባችሁት እነኚህ በአማራነታችን ውርደት አንቀበልም፤በቃን! ብለው የአገር በቀል ፋሺሰቶችና የውጭ አገር ሴረኞች በአማራው ላይ ያነጣጠሩት የዘር ጥቃት ያስመረራቸው እነኚህ ዜጎቻችን የተናገሩትን ምሬት ተመልክተናል።

የሚቀጠለው ደግሞ ለአብይ አሕመድ ያደሩ ‘ነጭ ባንዴራ አውለብላቢ ባንዳ አማራዎች’ ስለ ሁኔታው አስመልክተው የሰነዘሩት ባንዳዊ ንግግሮችን እንመለከታለን።

ለዛሬ የምንመለከተው በመጀመሪያ በወያኔ እስር ቤት ውስጥ እያለ በራሱና በቤተሰቡ ላይ የግብረሰዶም ጥቃት ማስፋራሪያ ደርሶበት ነበር ተብሎ የሚታማው “የሓፍረት ትርጉም የማያውቀው” አንጋፋ ተዋናዩ የደበበ እሸቱ መልእክት እንቃኝ።

ደበበ እሸቱ እኔ ከምገልጠው በላይ መግለጽ የሚችለው ብርቅየ የታሪክና የፖለቲካ ስነ ፍልጠት ተሟጋች የሆነው ወዳጄ ወጣት አቻምየለህ ታምሩ ስለ ደበበ እሸቱ ማንነት የገለጸበት ትችት ልጥቀስ።

“መመከር ያለበት ማነው?” ለአርቲስት ደበበ እሸቱ «ምክር» የተሰጠ መልስ (አቻምየለህ ታምሩ) በሚል ርዕስ እንዲህ ይላል።

“አርቲስት ደበበ እሸቱ በትናንትናው እለት ‘አገዛዝ በተለዋወጠ ቁጥር’ አሰላለፋቸውን የሚያስተካክሉ ሆድ አደር ሰራዊቶችን ሰብስቦ በ1997 ዓ.ም. ይቃወመው የነበረውን የወያኔ አምባሻ ያረፈበት ባንዲራ በኋላው ሰቅሎ አማራውን ሰማዕት ጀኔራል አሳምነው ጽጌን በነውረኛ ቃላት እያወገዘ ለዐቢይ አሕመድ ያለውን ታማኝነት ለማስመስከር ሲኳትን ውሏል።

ደበበ እሸቱ ሰማዕቱን ጀኔራል አሳምነው ጽጌን ከኮነነባቸው ዘግናኝ አገላለጾች መካከል «ሕሊና ቢስ»፤ «በአውሬያዊ ባሕሪ የተለከፈ» ፤ «ከእስር ሰንሰለት ነጻ ባወጣው ላይ የመሳሪያ ምላጭ የሳበ የሞት መልዕክተኛ» የሚሉ ልብ ሰባሪ ቃላት ይገኙበታል። ደበበ እሸቱ እንዲህ ያለ ለመስማት የሚቀፍ ውግዘትና ኩነኔ በጀኔራል አሳምነው ላይ ያወረደው የሰማዕቱ ጀኔራል ዐይን እንኳ ሳይፈርጥ ነው።

ደበበ በጀኔራል አሳምነው ላይ ይህን ያህል ውግዘት ያወረደው ጀኔራል አሳምነው አጠፋ የተባለውን ነገር አጣርቶ አውቆ አይደለም።ጀኔራል አሳምነው አጠፋ የተባለውን እንኳን በቦታው ያልነበረው ደበበ እሸቱ ይቅርና ነበርን ያሉትን የብአዴን መኳንንት እንኳ ስለ ሁኔታው የሚነግሩን ትርክት ርስበርሱ የሚጣረስ ነው። የደበበ ውግዘት መነሻ ስለሆነው ነገር ያለው እውቀት ሳይሆን ዐቢይ አሕመድ የአገር ውስጥ መረጃውን አፍኖ በአለማቀፉ ሜዲያዎች ዘንድ እንዲናኝ የተደረገው «አማራ መንግሥቴን ሊገለብጥ ተነስቷል» የሚለው ከመጠን በላይ የጮኸ በአማራ ላይ የተሸረበ ሴራ ነው።
ደበበ እሸቱ ራሱ የሴራ ሰለባና በፋሽስት ወያኔ የፈጠራ ክስ በሽብር ተወንጅሎ ዘብጥያ የወረደ ሰው ነበር። የሴራ ሰለባ የነበረው ደበበ ግን የሴራውን ሰለባ ሰማዕቱን አሳምነውን በሚዘገንን ቃላት ሲያወግዘው ሰማን።

ደበበ እሸቱ በ1999 ዓ.ም. ከተፈታ በኋላ እንደገና ዘብጥያ የወረደው ከግንቦት ሰባቱ መሪ ከብርሀኑ ነጋ ጋር በስልክ ግንኙነት ሲያደርግ በወቅቱ የኢንሳው የጃሚንግና ስልክ መጥለፍ ኃላፊ የነበረው ዐቢይ አሕመድ ንግግሩን ቀድቶ ለፋሽስት ወያኔ በመሰጠቱ ነበር።…” እያለ አቻም ስለ ደበበ እሸቱ ሰፋ ባለ ትችት ተችቶታል።

 አዎ አቻም አውነቱ ነው፡ በአሸባሪነት ከተፈረጀው ከብርሀኑ ነጋ ጋር ማውራቱን እየኮነነ ደበበ ራሱ መናገሩን በድብቅ ተቀድቶ የተለቀቀውን የቪዲዮ ምስል ያተመለከትን ሰዎች እናስታውሳለን።በዚያ ቪዲዮ ደበበ ምን ብሎ ነበር እዚህ ላስታውሳችሁ፡
ደበበ በቪዲዮ ሲታይ የነበረበትን ምስሉ ይህ ፎቶግራፍ ነበር፤
 “መንግሥት እኮ በግልጽ አስቅምጧል” ይላል ደበበ ዕንባ እየተናነቀው። “ግንቦት ሰባት አሸባሪ ድርጅት ነው ብሎ አስቀምጧል። እዚህ አገር ሁኜ፣ በየዕለቱ የሚሰጠውን መረጃ እያየሁ፣ አሸባሪ ነው ተብሎ ከተፈረጀ ድርጅት ጋር ለምንድነው በምንም መልኩ ይኹን ግንኙነት ያደረግኩት! ይኸ ነው የሚያስጸጽተኝ!”

እያለ ተዋናዩ ደበበ እሸቱ  በራሱ ላይ በመፍረድ አገር ጉድ ያስሰኘ ኑዛዜው አስተላልፎ እንደነበር እናስታውሳለን።ያንን አስመልክቶ ለምን እንዲህ ያለ አስገራሚ ድንጋጤና መምጰርጰር እንዳሳየ ተንታኞች ሲገልጹ እንዲህ ሲሉ ዘግበውት ነበር።

Woyanne threatened to sodomize Debebe Eshetu’s family (December 1, 2011, Updated on January 10, 2013 by Elias Kifle)

በሚል ርዕስ “የኢትዮጵያን ረቪው ኦን ላይን ድረገጽ አዘጋጅ ኤልያስ ክፍሌ’ ስለ ሁኔታው አስመልክቶ በጻፈው ለደበበ መልስ እንዲህ ብሎ ነበር፦

The star witness of Bereket’s fictitious docudrama is popular actor and member of the opposition UDJ Party. The video shows Artiste Debebe talking about various plots and the discussions he had with me and Dr Berhanu Nega. I cannot speak for Dr Berhanu, but none of what Debebe said about me is true. It’s a total fabrication. After hearing what Debebe had to say, I was convinced that he must have been tortured or something real bad had happened to him to say all the things he said, because no such conversation had taken place.

Yesterday, members of the Ethiopian Review Intelligence Unity in Addis Ababa sent me a report confirming what I had suspected. According to the report, Meles Zenawi’s deputy head of security, Esayas Woldegiorgis, gave a script to Debebe Eshetu to study and repeat in front of cameras every thing in the script in a convincing way or else his grand children and other members of his family will be sodomized with a bottle. This information is according to a close member of Debebe Eshetu’s family.

Sodomizing opponents, which is foreign to Ethiopian culture, is a method that Meles brought from his country Yemen. Victims of sodomy are extremely traumatized and that they are too ashamed to tell even those closest to them. In recent past, at least two prominent opposition politicians I know of who had been subjected to sodomy. I will not mention their names to keep their privacy. But in time, they themselves may be willing to talk about it in public so that the perpetrators face justice.”….. እያለ ስለሁኔታው ኤልያስ ክፍሌ ዘግቦ ነበር።

እንግዲህ ደበበ እሸቱ አልያስ እንደዘገበው በቤተሰቡ ወይንም “something real bad had happened to him to say all the things he said, (እንዲያ ሆኖ ያ ሁሉ ፈጠራ ለመናገር ያበቃው ለኛ ግልጽ ያልሆነ አንድ ነገር ተፈጽሞበት ኖሮ እንጂ ) በሚል ኤልያስ ክፍሌ ተዋናዩ ያሳየው አስደንጋጭ የመጰርጰር ባህሪ (December 1, 2011, Updated on January 10, 2013 by Elias Kifle) ለታሪክ ዘግቦታል።

ታዲያ አቻም የለህ አንዳለው “በውሸት ተወንጅሎ በሽብር ተከሶ የታሰረው ደበበ ያኔ የስልክ ንግግሩን የጠለፈው ዐቢይ አሕመድ በጀኔራል አሳምነው ጽጌ ላይ ያቀረበውን ተመሳሳይ ውንጀላ ተቀብሎ ለማውገዝ መነሳቱ ከምን የተነሳ ነው? ለሚለው ጥያቄ “ደበበ እሸቱ ንግግሩን ቀድቶ ዘብጥያ እንዲወርድ ላደረገው ለዐቢይ አሕመድ ያለው ፍቅር እጅግ ከመጠን ያለፈ እንዲሆን የሆነው አቻም እንደገለጸው “ተዋናዩ ደበበ እሸቱ ለቀድሞው አጋቹ ለዐቢይ አሕመድ እያሳየው ያለው ፍቅር ፈረንጆቹ Stockholm Syndrome ከሚሉት የአጋችና ታጋች ፍቅር በላይ እንደሆነ ያስቀምጠዋል።

ያ ሁሉ የቅንጅቱ የእስርቤቱ አስደንጋጭ ሁኔታ ኤልያስ ባስቀመጠው ሁኔታ ያለውን ሊለው “ስለተገደደ” እንዲያ ያለ መንቀጥቀጥ እና ለወያኔ የሽብር ሕግ ተገዢነት ማሳየቱ ሁላችንም በሚገባን የተገደደበት ምክንያት ሆነ ብለን እንለፈው። ዛሬ ነጻ በታባለበት እስር ባልገባበት ሁኔታ አብይ አሕመድን ያክል እጅግ አደገኛ ሰው “መጠን እና ቅጣ በሌለው አገላለጽ” በማምለክ ‘የቢሲ አማርኛ ጋዜጠኛ  ደበብን “ወደ መንግሥት እየተጠጋ ነው ብለው የሚተቹህ ሰዎች ገጥመውኛል” በማለት ጥያቄ ላቀረበለት ጥየቄ ሲመልስ

“ደግ አደረኩ! ነፃነቴን የሰጠኝ ዐቢይ ነው። ዶ/ር ዐቢይ ነው ቤተ መንግሥት ያስገባኝ። ዶ/ር ዐቢይ ነው ፕሮግራም ምራልኝ ያለኝ። ከመሸማቀቅና ማን አየኝ ከሚል መሳቀቅና መገላመጥ ያወጣኝ ዶ/ር ዐቢይ ነው። ስለዚህ ያደላሁት ወደ መንግሥት ሳይሆን ወደ ዶ/ር ዐቢይ ነው። ለእሱ ደግሞ መልሴ ደግ አደረኩ ነው።” የሚል ነበር።

የደበበ እሸቱ አሳዛኝና አስደንጋጭ ባሕሪው መንግሥትም ሆነ መሪም ይሁን ለቡድን ማሽቃበጡ ዛሬ አልጀመረውም። የጸሃፊው ስም ማግኘት ያልቻልኩኝ ‘በፌስ ቡክ’ የተለቀቀ አንድ አጭር ትችት የደበበ አሽቃባጭ ባሕሪ እንዲህ በእንዲህ ይገልጸዋል፡-

“ደበበ እሸቱ ማለት የደርጉ ቡድን ግርማዊነታቸውን ከቤተመንግሥታቸው እንዲወጡ ተደርጎ በቮልስዋገን ሲወሰዱ የመጨረሻውን  መርዶ ከደርጎች ጋር ሆኖ ያነበበ ታሪካዊ አድርባይ ሰው ነው። በኛ ትውልድ “አሳምነውን” እንደዚያ እያዋረደ የአብይን መልዕክት ሲያስተላልፍ በጣም ደም ያፈላል። ሲጀመርም እነ ቴዲ አፍሮን የሚያክሉ በዓለም የሙዚቃ ደረጃ ሰንጠረዥ (ቢልቦርድ) ስራቸው በአንደኛነት ለመቀመጥ የቻሉ አርቲስቶን ባፈራች አገር፤ ይህ “የአዜማ እና የአብይ ተላላኪ” እንደዚያ “አፉን ሲከፍት” ምን ያህል እንደተናቅን መገመት አይከብድም። ያ ሁሉ 
“አርቲስት ነኝ ባይ ሆዳም” አማራነትን ማዋረዱ አይነጋ መስሏቸው ያስብላል።”

ሲል ስለ ደበበ እሸቱ አድርባይነት አዲስ ባሕሪ ሳይሆን ከ1966 ዓ.ም ጀምሮ የተከተለበት ተከታታይ ባሕሪው እንደነበረ ታዛቢዎች ገልጸዋል።

አብይ አሕመድ እነዚህ እና እነዚህ የመሳሰሉ አጎብጋቢ ግለሰቦችን ወደ ጎኑ በማስጠጋት የአማራን ማሕበረሰብና የኢትዮጵያ ማሕበረሰብ ግፍ ቀጣይነት እንዲኖሮው አስተዋጽኦ በማድረግ በአርበኞች እና አገር ወዳድ ዜጎች ላይ ይቅር የማይባል የተባባሪነትና ውግዘት በማስተላለፋቸው ታሪክ ይጠይቃአቸዋል።ጊዜ ሲለወጥ በስራቸው ይሸማቀቃሉ።የንጹሃን እና የግፉኣን አምባ ሃቀኛ ፍትሕ ሲሰፍን እምባቸው ይታበሳል። ነጭ ባንዴራ አውለብላቢዎቹ እና ደም ተፊው የ666ቶቹ ተቀጣሪው ጋኔል በቅርቡ በእግዚአብሐር ሰይፍ ቅጣቱን ያገኛል። (ይህ የኔ ትንቢት በማርች 2019 የጻፍኩትን ተመልከቱ አሁንም በአብይ እና በመሰሎቹ ይቀጥላል) ልብ ካላላችሁት የጻፍኩትን ላስታውሳችሁ፦

"የኦሮሞ ንጉሠ ነገሥቶቹ የአብይ አሕመድ እና የለማ መገርሳ አሽከሮች!  TUESDAY, MARCH 12, 2019(Getachew Reda ኢትዮ ሰማይ) በሚል ርዕስ እንዲህ ብየ ነበር፦

"ኢትዮጵያ አጆችዋን ወደ ፈጣሪዋ ዘርግታ የፋሺስቶቹ መሪ ‘መለስ ዜናዊን’ ከፊታችን እንዳስወገደው ፤ አሁንም ኢትዮጵያ እጆችዋን በገለጣፎ የእናቶች እና የህጻናት እምባ በኩል እጆቿን ዘርግታለች እና እናንተም በተራችሁ እንምባችሁ ሲፈስ በቅርቡ እናያለን!! ባጭሩ መጥሪያችሁ ተዘጋጅቷል እና ወደ ሃያሉ ፈጣሪ ትጠራላችሁ ማለት ነው!! ይህ ትንበያ ከሃቅ የራቀ እንዳይመስላችሁ። ካሁን በፊት በመለስ ዜናዊ አድርገናል (አልጄሪስ ስምምነት በተመለከተ ካናዳ ሓዋሪያ ጋዜጣ የጻፍኩትን ትንበያ ተመለክቱ) ፤ያ ትንበያ ዛሬም በናንተ ይደገማል!” ብየ ነበር። 

ይህ ባልኩኝ በሦስተኛው ወር ሰሞኑን  ባሕርዳር ውስጥ የተከሰተው የእግዚሔር ቁጣ አይታችኋል። ("የኦሮሞ ንጉሠ ነገሥቶቹ የአብይ አሕመድ እና የለማ መገርሳ አሽከሮች! ጌታቸው ረዳ ኢትዩ ሰማይ MARCH 12, 2019) ከሚል የጻፍኩት ትንቢታዊ ጥቅስ።

 ለተሰውት ሙታኖች ቤተሰብ ጽናቱን ይስጣችሁ።

ጌታቸው ረዳ (Ethio Semay አዘጋጅ)