Wednesday, November 4, 2020

ኢሳያስ አፈወርቅ የውጭ ጉዳይ ተጠሪ አድርጎ ሹሞኛል ብሎ ያለ ሓፍረት የነገረን ኤርትራዊው አብይ አሕመድ ባድሜን የወረረ የሻዕቢያ መንጋ እንዴት እንደገለጸው ዛሬ ሰምታችሁታል? ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay) November 4/2020

 

 

ኢሳያስ አፈወርቅ የውጭ ጉዳይ ተጠሪ አድርጎ ሹሞኛል ብሎ ያለ ሓፍረት የነገረን ኤርትራዊው አብይ አሕመድ ባድሜን የወረረ የሻዕቢያ መንጋ እንዴት እንደገለጸው ዛሬ ሰምታችሁታል?

ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay)

November 4/2020

የኢሳያስ አፈወርቅ ውጭ ጉዳይ ተጠሪ ነኝ ብሎ እራሱ ሰላይነቱን ሳይደብቅ በግልጽ የነገረን “የኦነግ ኮለኔል” አብይ አሕመድ “ዘሐበሻ ኦፊሻል” በተባለ ዮቱብ ሚዲያ ላይ “Ethiopia: ሰበር - ዶ/ር ዐቢይ አሁን ወጥተው ስላለው ሁኔታ ተናገሩ | Statemnet by Dr Abiy Ahmed” በሚል የለጠፈው የስዕለ ድምፅ ርዕስ ባድሜን ወርሮ ለ70 ሺሕ ህይወት ምክንያት የነበረው ወደ ሰዎች መንደር የመጣውን ወራሪው የሻዕቢያ “የጅብ መንጋን” አስመልክቶ አብይ ሕመድ እንዲህ ይላል። ትክክለኛውን አማርኛ አጠቃቀሙን በራሴ ግልጽ ላድረግላችሁ እንዲህ ይላል፡


“ለ20 አመታት የትግራይን ሕዝብ ይጠብቀው የነበረው፤ “ከአንበሳ መንጋ” የታደገውን ሠራዊት ተተናኩሎታል…” እያለ በሰሜን የተመደበውን የአገር መከላከያ ብሎ ራሱን የሚያሞካሸው ድሮ የወያኔ ዛሬ ኦሮሙማዎች የሚያዙት ሠራዊት ለማሞገስ በሞከረበት አገላለጹ “ከአንበሳ መንጋ የታደገውን ሠራዊት” ብሎ የሚለውን “አምበሳ መንጋ” የአለቃው ሻዕቢያን ሠራዊትን ነው።


እንግዲህ ይህ ሰው አገር እመራለሁ የሚል ነገር ግን “ሲናገር ኢትዮጵያዊ በተግባር ኦነጋዊና ሻዕቢያዊ” የሆነው ይሄ ሰላይ ኢትዮጵያንን ሲገድል፤ሲረሽንና ሲያፈናቅል የነበረን የጅብ መንጋ “ወደ አንበሳነት” ቀይሮ የአንበሶች መንጋ ሲል በኤርትራዊነቱ የውጭ ጉዳይ ተጠሪነቱን ለመግለጽ ኢትዮጵያዊ ነኝ እያለ የጠላትን ሠራዊት “የአንበሶች ሠራዊት” አድርጎ በመሳል ማንነቱን በድጋሜ ዛሬም ሳያፍር ግልጽ አድርጓል።


ኢሳያስ አፈወርቅ ዕድለኛ ነው ማለት ይቻላል። ከትግራይ ያጣውን የመለስ ዜናዊ ምትክ ጂማ ያደገው ዛሬ የኤርትራ የውጭ ጉዳይ ተጠሪ ነኝ ብሎ የነገረን አብይ አሕመድ አዲስ ሎሌ አግኝቷል። በዚህ ግኝት መሰረት አብይ አህመድ “ኢሱ” በማለት የሚያቆለጳጵሰው ኢሳያስ “ኢትዮጵያን ለማፈራረስ” በዕቅድ ሲሰራ የነበረውን አጀንዳው ዛሬ አብይን የሚያክል ሎሌ ኦሮሙማ በኩል በማግኘቱ የአመራንና የተቀረው የአገሪቱ ሕልውና አደጋ ላይ ነች።


ለወደፊቱ አሁን ስላለው ሁኔታ በሰፊው የምተነትነው ሲሆን፤ ትግራይ ላይ የተኮፈስ የ29 አመቱ ሽፍታ ‘ትግራይን’ ለመገንጠል ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያን ወደ ሶርያነት ለመቀየር በዕቅድ ሲሰራበት የነበረ ፋሺሰታዊ ቡድን መሆኑን ብዙ ጊዜ የተናገርኩት ስለሆነ የጦርነቱ አይቀሬ ገና አብይ ወደ ሥልጣን ከመምጣቱ በፊትም ሆነ ከዚያም በሗላ የሰጠሁዋቸውን ቃለመጠይቆች አፈላልጋችሁ አድምጡ (ብዙዎቹ ቃለ መጠይቆች ዲያስፖራ ያሉ ተቃወሚ ነን የሚሉ ሚዲያዎች አጥፍተዋቸዋል)። ሆኖም ዛሬ ዋናው ማተኮር ያለባችሁ፤ ይህ ጦርነት በምንም መልኩ ማስቀረት አይቻልም። ምክንያቱም ይህ ጦርነት ሁለቱም ሃይሎች “ምኒሊክ ቤተመንግሥት ያለው ኦሮሙማው ሃይል እና ወደ ትግራይ የሸሸው ሠልጣኑ በአሳፋሪ ሁኔታ ያላንዳች ጥይት የተቀማው የወያኔው ቡድን መካካል ሠልጣን የመጠበቅና ሥልጣን የማስመለስ ስለሆነ ሕዝብ ደገፈውም አልደገፈውም ብምንም መልኩ የሚቆም አይደለም።


ምክንያቶቼን ልግለጽ 

1ኛ- 

ወያኔ/ትግራይ ፐራያ (የተገለለ ቡድንና የተገለለ ሕዝብ ነው)። ይህም ማለት ወያኔ አብረው ሲዘርፉና ሲገድሉ ከነበረው የማዓከላዊው (ኦሮሙማው) ቡድን ጋር ስለተጣላ የምጣኔ ሃብትም ሆነ የፌደራል ዕርዳታዎች፤ የየብስና የጠረፍ መገናኛዎች በሙሉ ተቋርጧል። እራሱ “አገር” ብሎ ለይስሟል (ቢያነስ በለሰለሰ ቃል ዲፋክቶ ነኝ ብሏል)። አማራን በጠላትነት ፈርጇል፤ ስለዚህ የመገናኛ አውታሮችና ሲያገኛቸው የነበረው የምጣኔ ልውውጦች በጎንደርም ሆነ በወሎ የደረቀ ወንዝ ሆኖበታል። በኤርትራም በኩል እንደዚሁ።


ስለዚህ ያለው አማራጭ ያለ ምንም ጦርነትም “በፓራያነት (ታጥሯል) የመኖረም ዕድሉም” አስጨናቂ ስለሆነበት ኢሳያስ ያደረገው የባድሜ ትንኮሳ ዛሬ ወያኔም “በፓራያ እስቴት ስለተሰቃየ” ሰሜን ላይ የነበረው መከላከያ ጦር በሚባለው ላይ “የቶክስ ትንኮሳ” ማድረግ በመታጠሩ ምክንያት የጭንቅ ትንኮሳ ጀምሯል።


2ኛ- ወያኔ ይበልጥኑ ትኩረቱ ኢሳያስን በማስወገድ ላይ ያተኩራል። የባሕር ወደብ ማስገኚያ መንገዱ ኤርትራን ወደ “ከያስ” ወደ “ቀውስ” በማስገባት ጦርነት በመለኮስ ኢሳያስ የሚመካበት የጦርነት ፍላጎት የሌላቸውን የ15 አመት ዕድሜ ያላቸው ኤርትራዊያን ወጣቶች እጃቸው ለወያኔ እንደሚሰጡ በማስላት የኤርትራ ተቃዋሚ የሚባሉት “ጥርስ የሌላቸው ውጭ አገር ያረጁ ያፈጁ ኤርትራውያን ተቃዋሚዎችን” በማሰባሰብ አስመራ ውስጥ ያለው ሥርዓት በማናጋት “ትግራይ ትግርኝን” ወደ ጠረጴዛ ድርድር በማምጣት ቢያንስ የመሸሺያና የንግድ በር ማስገኛ ለመከፍት ይጥራል። ስለዚህም ጦርነቱ በሕዝብ ተደገፈም አልተደገፈም “ወያኔ” “በፓራያ እስቴት” እራሱ የቃዠበትን የእስር ሰንሰለት በማጥለቁ ወያኔ ወደ ሥልጣን መምጣት የማይተገበር ሕልም ስለሆነበት መፍቺያ መንገዱ ስለጠፋው የመገንጠልን ዓላማ “አማራጭ አድርጎታል”።


3ኛ_- አብይ ፈለገም አልፈለገም ጦርነቱ ለማስቆም አቅም የለውም። ምክንያቱም ጦርነቱ የቀሰቀሰው እንደሰማችሁት ወያኔ ነው። አብይ ጦርነት ሳይሆን ሕዝብን እያታለለ “ፓርክ” ውስጥ የሕጻናትን መኪና በማሽከርከር፤ ትራፊክ እያስቆመ “አብይ ነኝ” ማለት፤ በምያምሩ ጉንጉን አበባዎች በተዋቡ የግብዣ ጠረጴዛዎች ሆኖ “ፔንጤዋ ሚስቱ እና እርሱ” እየፈኩ “ሆዳም” ተጋባዥን በሽቶና በጠጅ እንዲዝናኑ በማድረግ እያስጨበጨበ ፤ሃብታሞች ጋር እየተሻሸ የሥልጣን ዕድሜውን በሰላም ለማራዘም ነው ዋናው ፍላጎቱ። ወያኔ ደግሞ እነዚህ በአበባና በሽቶ የታወዱ የሥልጣን ማሳያ ጠረፔዛዎች በአብይ ስለተነጠቀ ሰላም የሚባል በሕልሙም አያስበውም።


4ኛ- ወያኔ በወንጀል ስለተጨማለቀ የ27 አመት ወንጀሉ ዕርቅም ቢሆን እራሱን ማጋለጥና ማዋረድ ስለሚሆንበት ጦርነት አማራጩ አጀንዳው ነው።


5ኛ- ወያኔ አመሰራረቱ “ፋሺስት ነው”። ፋሺሰት ደግሞ ጉልበትን እንጂ ድርድርን ስለማይቀበል እርሱ በሚፈልገው መንገድ (ይህችን አስምሩልኝ) አርሱ በሚፈቅደው የዕርቅና የድርድር ስልት ካልሆነ ‘ሕዝባዊ ድረድር’ በማድረግ ሰላም ለመፍጠር ፍላጎቱም መሰረታዊ ተፈጥሮም አይፈቅድለተም። ይህ ያልኩበት ምክንያት የወለቃይትን ጉዳይ ለምሳሌ ላንሳ ።


በማርች 2016 የጻፍኩትን ልጥቀስ “ትግሬዎች እኔም ወልቃይቴ ነኝ!” እያሉ የወያኔ ወረራ በማውገዝ ለታሪክ ያስመዝግቡ! ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያን ሰማይ ድረገጽ አዘጋጅ) በሚል ርእስ በሚዲያ የለጠፍኩትን ጉግል ብታደርጉ ይህንን ጥቅስ ታያለችሁ፦


“የወልቃይት አማራ ወንዶች እየተገደሉ፤እየታፈኑ የወልቃይት ሴቶች “በትግሬ ወንዶች” እየታመጹ አዲስ የትግሬ ትውልድ በወልቃይት መሬት እንዲባዛ እንደተደረገ ወልቃይቴዎች እራሳቸው በተደጋጋሚ በሕዝብ መገናኛ መስመሮች እየተጋበዙ በሚያደርጓቸው ቃለ መጠይቆችና የጽሑፍ ማስረጃዎች የተገለጸ ነገር ነው። ለምሳሌ ይህንን መረጃ ይመልከቱ፤-Government carries out secret mass sterilization among Amhara womenhttps://youtu.be/2iRwEudb3NM (ከጌታቸው ረዳ -አትዮጵያን ሰማይ)።


ስለዚህ ወያኔዎች ፋሽታዊ ወንጀል ስለፈጸሙ ይህን በሚመለከት ትግሬዎች “እኔም ወልቃይቴ አማራ ነኝ የወልቃይት ደም ደሜ ነው” የሚል ደምጽ ሊያስደምጡን አይፈልጉም። ወልቃይት ወደ ቦታው ከመመለስ ይልቅ “ወደ ጦርነት” እንግባ የሚል ከእነ “አበርሃ ደስታ” ጭምር የሰማነው መስመር ስለሆነ ትግሬዎች አማራጩ “ጦርነት ብቻ” እንደሆነ ተቀብለዋል።


6ኛ- የትግራይ ሕዝብ በተለይ “ወጣቱ የትግራይ ብሔረተኛው ምሁር ክፍል” በአክራሪ ብሔረተኛነት እየተኮፈሰ በፋሺታዊ ትምክሕት ስለሰከረ ኢትዮጵያን ሕዝቧ “ሕዝባችንና አገራችን አይደለም” ብለው አገር መመስረት አማራጭ ነው ብለው ስለወሰኑ የጦርነት ከበሮ ከደለቁ አመታት አልፎአቸዋል። ስለዚህም ብዙ ገንዘብና ጥናት በማድረግ መጻኢት ትግራይን ለመመስረት ተስማምተዋል። ስለሆነም ይህ ክፍል “በትዕብት የተወጠረ ስለሆነ” አንሺውና ጣዩ “ጌዜ” መሆኑን ስለማይገባው ዛሬም የደርግን ጦርነት እንደግመዋለን የሚል ትምክሕት ይዞ በትግራይና በአማራ ሕዝብ ደም እጆቻቸው የተጨማለቁ ፍርድ ያላገኙ የወያኔ መሪዎችን በመንከባከብ የልብ ልብ ሰጥቶ የድሃ ልጆች ወደ ጦርነት እየማገዱ እንዲሄዱ ሙሉ አገልጋይነታቸው ስለገለጹለት ወያኔ ትግራይ ውስጥ ሙሉ አዛዥና ናዛዥነቱ እንዲቀጥል ፈቅደውለታል።


7ኛ- ከጫካ ሕሊና ስላልወጡ በሰብአዊትና በዘመናዊ ስልጣኔ አያምኑም ስለሆነም መለስ ዜናዊ የነገረን ላስታውሳችሁና ልደምድም። ቃለ መጠይቅ ያደረገው ከ BBC HardTalk ጋዜጠኛው Stephen Sackur ጋር ያደረገው ቃለ መጠይቅ እንዲህ ይላል፦


“….you're also telling me that if things go wrong, as they might, you said, this country could slip into anarchy like Rwanda. You said that to me. Does that suggest you've established a level of stability and confidence in the future that can sustain this country?"

Meles - "We are not out of the woods yet..."


ሲል የባንዳዎቹ መሪ የነበረው በእግዜር ቁጣ የተቀዘፈው አሁንም ከጫካ ሕሊና እንዳልወጡ ግልጽ ያደረገው ጉዳይ ነው። ስለሆንም ከጫካ ሕሊና ያልወጣው ወያኔ በረሃ ውስጥ ሲርመሰመስ በነበረበት ባሕሪ ጦርነት እንደኳስ ጨዋታ ስለሚመከለተው በሚሊዮን ትግሬዎች ቢሞቱና አካላቸው ቢረግፍ ለወያኔዎችና ለትግራይ ምሁራን የኳስ ጨዋታ ነው ብለው ስለሚያምኑ በተለይ አውጭ ያሉ የትግራይ ምሁራን አጨብጫቢዎች የኳስ ጨዋታውን” ለማየት በጉጉት ይፈልጉታል።


8ኛ- ማጠቃለያ መልዕክቴ፡-


ስለዚህም በወያኔና በኦሮሙማ የሚካሄደው ጦርነት የሥልጣን መራኮቻ ሜዳ ስለሆነ በተለይ አማራዎች “ወደ ሥፍራችሁ ሊወጉዋችሁ ሲመጡ ብቻ እራሳችሁን ለመከላከል ካልሆነ የአብይና የወያኔ መጠቀሚያ ከመሆን ተቆጠቡ እላለሁ”። ወያኔ ከባድሜ መልስ በሗላ ጦርነቱን የረዱትን ዘጎቻችን ነበር እስርቤት አስገብቶ ለስቃይ የዳረጋቸው፡ አሁን ደግሞ አብይን ለመደገፍ ብላችሁ ወያኔን ካስቆማችሁት በሗላ አብይ ተመልሶ መለስ እንዳደረገው ስለሚያደርግ ጥንቃቄ ያስፈልጋል።

አመሰግናለሁ

ጌታቸው ረዳ

Ethiopian semay ጌታቸው ረዳ