Sunday, June 27, 2010

ይድረስ ለጎጠኛዉ መምህር አዲስ መጽሐፍ ደራሲ ጌታቸዉ ረዳ

ሁለት መጻህፍት ገበያ ላይ ዉለዋልደራሲ ጌታቸዉ ረዳ (408)561-4836 getachre@aol.com መግብያ ቀደም ብሎ ያሳተምኩት የትግርኛ መጽሐፍ በሕትመት ብልሽት ምክንያት መስተካከል ያለባቸዉ ገጾች በማስተካከል ላይ እንዳለሁ በወያኔዉ ታጋይ በአታኽልቲ ሓጎስ የተጻፈ “አይንተሓማመ”-የሚል መጽሐፍ አንድ የኔ ቤተሰብ ከመቀሌ ይዞልኝ መጥቶ እሱን አንብቤ ስጨርስ ስለ መጽሐፉ ጎሰኛነት አዉሮጳ ሃገር ለሚኖር ወዳጄ ሳነጋግረዉ፤ ወዳጄም በማከል “ማንም ይሁን ምን በወያኔዉ ታጋይ በመምህር ገብረኪዳን ደስታ የተጻፈ የትግራይ ሕዝብ እና የትምክሕተኞች ሴራ ከትናንት እስከ ዛሬ”መጽሐፍ በጣም አስቀያሚ የሆነ መጽሐፍ ታትሞ አያዉቅም ፤እሱን ፈልገህ ማንበብ ይኖርብሃል”ሲለኝ የመጽሓፍ ምንነት ካሁን በፊትም ከሌሎች ሰዎች ተነግሮኝ ስለነበር፤መጽሐፉን ፈልጌ ለማንበብ ጉጉት አድሮብኝ ስፈልግ ብዙ ጊዜ ፈጅቶብኝ እዚሁ ሳንሆዜ ከተማ የሳንሆዜ ቤይ ኤርያ የኢትዮጵያ ራዲዮ ዋና አዘጋጅ ወዳጄ ኢንጂኔር አበበ ሃይሉን ስጠይቀዉ በእጁ እንደሚገኝ እና እንደሚሰጠኝ ቃል ገብቶልኝ፤ ሰጥቶኝ -ከመጀሪያ እስከ መጨረሻ ድረስ ያሉት አንድ ባንድ ለማንበብ ሞክሬ የመጽሐፉ ጸረ አማራነት፤ትምክሕቱና የተዛባ የታሪክ አቀራረቡ ህዋሳቶቼ ክፉኛ ስለተፈታተኑት ከገጽ ወደ ገጽ ስሸጋገር ጥርሴን ነክሼ በመከራ ነበር አንብቤ የጨረስኩት። ደራሲዉ መምህር ገብረኪዳን ደስታ “በ1998 ዓ.ም. የጻፈዉ “የትግራይ ሕዝብና የትምክሕተኞች ሴራ ከትናንት እስከ ዛሬ”መጽሐፉ አጼ ምኒልክን በትግራይ ደመኛነት፤በከሃዲነት፤ለባዕድ ያደሩ ቅጥረኛ፤ወደ ዓድዋ የዘመቱት በወቅቱ ከማንኛቸዉም አካባቢ በጥሬ ገንዘብ (ብር)እና በከብት ቀንድ ሃብት ሓብታም የነበረችዉን ትግራይ ለመዝረፍ እና በጎሳ ፤በነገድ፤በቀለም ልዩነት የማያምነዉ ንፁህ የትግራይን ሕዝብ የአዉራጃዊነት ስሜት እንዲያድርበት በማስተማር እርስ በርሱ እንዲጋጭና ሃያልነቱን ለማዳከም እና ለማንበርከክ አቅደዉ በትግራይ ሕዝብ ብዙ በደል ፈጽመዋል በማለት ይከ’ስሳቸዋል።ደራሲዉ ምኒልክን በጸረ ኢትዮጵያዊነት እና በሃገራዊ ክሕደት የኮነናቸዉን ያህል በአዲስ አበባ ከተማ በየወሩ እና በየቀኑ የሚታተሙ የግል መጽሄቶችና ጋዜጦችም እንዲሁ “ጋዜጦቹ የትምክሕተኞች ዓላማ ተግባራዊ ለማድረግ የሚታተሙ ናቸዉበማለት የግል ጋዜጦችን ይከ’ሳቸዋል። ጋዜጦቹ በትምክሕት ሃይሎች የሚዘጋጁ ሲላቸዉ “በጀግኖች (የወያኔ ታጋዮች) የዓመታት ተጋድሎና የሕይወት መስዋዕትነት የተገኘዉን የዲሞክራሲ መድረክ ሕዝባችን እርስ በርሱ ለማናቆርና ለማተራመስ ተጠቅመዉበታል” ሲል ይወነጅላቸዋል። ስለዚህም ይላል “ተጋዳላይ” ገበረኪዳን “እነዚህ አህጉራዉያን ትምክሕተኞች በትግራይ ሕዝብ ላይ የሚነዙት የጥላቻና የዕልቂት መርዝ ከዕለት ወደ ዕለት እየከፋ በመሄዱ ነዉ በመጠኑም ቢሆን ማንነታቸዉ ለማጋለጥ በትግርኛ ቋንቋ የጀመርኩትን ስራ ትቼ ይህንን መጽሐፍ በአማርኛ ቋንቋ ለመፃፍ የተገደድኩት። “የያዘዉን ከወረወረ ፈሪ አይባልም” እንደሚባለዉ ነዉና እኔም የትግራይን ሕዝብ ደመኛ ጠላቶች ማንነት በማጋለጥ በኩል ማድረግ የምችለዉን ነገር በማድረጌ የመንፈስ እርካታ ይሰማኛል። ከዚያ በሗላ ግን የትግራይ ምድር ያበቀለቻቸዉ ምሁራን የታሪክ ተወቃሾች ላለመሆን የትምክሕተኞችን የዉሸት ብዕር በማሽመድመድ የትግራይን ሕዝብ ሐቀኛ ታሪክና ማንነት በአግባቡ እየመዘገቡ ለቀጣዩ ትዉልድ የማስተላለፍ ህዝባዊ ግዴታ አለባቸዉ። በሌላ አነጋገር “ትግሬ ታሪክ ይሰራል እንጂ ታሪክ አይጽፍም”የሚሉትን የትምክሕተኞች የትናንቱ ፌዝ ነገና ከነገ ወዲያ በትግራይ ምሁራን የሚሰነዘር ተሳልቆ ሆኖ መቀጠል አይኖርበትም…”(ገ/ኪዳን ደስታ -በምጽሓፉ መግብያ ላይ ካሰፈረዉ)። በማለት የትግራይን ምሁራን ዉሸት እንዲዘግቡ፤ጸረ አማራነት ፤ ጸረ አንድነት እና ጸረ ኢትዮጵአዊነትን የሚሰብኩ መጻሕፍቶች እንዲጽፉ ተማጽኗል። እኔም በትግራይ ተወላጅነቴ አሁን ያለዉ ወጣት ትዉልድና መጪዉ ትዉልድ የመጽሐፉን አደናጋሪነት እና መሰሪነት፤ትምክሕትና ጠባብ የጎሰኛነት ስሜት እንዳይመርዘዉ የእነ ገብረኪዳን እና የወያኔ የዉሸት ቅስቀሳዎች፤አናካሽ ስለቶቹ እንዳይቀጥሉ ሕብረተሰቡ በራሱ ጐሰኞች ላይ የጠነከረ እና የጠራ አቋም ለመዉሰድ እንዲረዳዉ የበኩሌን ሃላፊነቴን ለመወጣት ይህ መጽሃፍ ለትዉልድ ኣስተላልፌያለሁ። እኔ አክሱም ተወልጄ ፤ አክሱም አድጌ፤ እትብቴ አክሱም አፈር ላይ ተቀብሯል።የአክሱም ተወላጅ ነኝ። አከላቴ ሁሉ የተገነባዉ በአክሱም ዓየር ዉሃ እና እህል፤ባህል፤በበጎ አክሱማዊ የሃይማኖት ስነምግባር ታንጾ ያደገ፤ አሁንም መንፈሴን ያነፀዉ አክሱማዊ ቅብኣ ሜሮን ጠረኑ አልለቀቀኝም። ሕሊናየ ሁሉ ትናንትም ዛሬም አሁንም ለወደፊቱም እዛዉ ባደግኩበት እትብቴ አድሮ ጥዋት አሜሪካ ተመልሶ አገኘዋለሁ። ወያኔ የመሰረቱ አብዛኛዎቹ አብሮ አደጌ ወይንም የትምህርት ጓዶቼ ናቸዉ። ገብረኪዳንም እንዲሁ እንደ እኔ የትግራይ ተወላጅ ዓድዋ ተወልዶ ዓድዋ ያደገ ነዉ። ሁለታችንም ያደግንበት መንደር በመኪና የ30፡00-የሰላሳ ደቂቃ ርቀት ነዉ። ስለዚህ ትግራይ እና የትግራይ ስቃይ እና ብልጽግና የምናዉቀዉ እኩል ነዉ። ልዩነታችን በኢትዮጵያዊነታችን ላይ ያለዉ እይታና ራዕይ ነዉ።አሁን ወያኔን የሚመሩ እና የሚከተሉዋቸዉ አብሮ አደጎቼ፤- ገና አብረን ስናድግ እንዲህ ዓይነት የታሪክ ዓመጽ ይፈጽማሉ የሚል ሕልምም ምልክትም አይታያቸዉም ነበር (በጣም ከጥቂቱ በቀር)። እንዴት እንዲህ የጠላት አስደሳችና አስፈጻሚ ሊሆኑ እንደቻሉ ለኔ እንቆቅልሽ ነዉ። ልዩነታችን በሁለት ተቃራኒ እምነቶች እና እይታዎች የተሰመረ ነዉ። በማሃላችን የለየን በቀይ መስመር የተሰመረ የሞትና የሽረት ትንንቅ የሚካሄድበት የመግደያ መስመር አለ። በመግደያዉ መስመር ላይ ኢትዮጵያን ለመግደል የሚያጠምዱበት ሙት የመግደያ መሬት ነዉ። ቅራኔየ አገሬን ከመግደያዉ መስመር ለማስገባት ሌት ተጠቀን ከሚጥሩ ከሃዲዎች ጋር ነዉ። ልዩነታችን የርዕየተ ዓለም ልዩነት ብቻ ሳይሆን አገርን በመግደልና በመከላከል ላይ ያለ ልዩነት ነዉ። ትግራይ የኢትዮጵያ ቅኝ ግዛት ነች የሚል ቅዠት ቃዥቶ ፯ በመታገያዉ ደብተሩ ላይ ያስተማረ፤ ራሱን ከድቶ የትግራይን ሕዝብ ለማስካድ ከሚቃዠ ቡድን እና፤ ስልጣናችን ከተቀማን ኢትዮጵያን እንበታትናታለን፤ትግራይን ከኢትዮጵያ እንገነጥላለን፤ መንድር መንደራችንን እንይዛለን ከሚለዉ አገር ገዳይ፤ እትብትና የቤተሰብ ሐረግ ከበጣጠሰ እና ዛሬም ትግራይን እና ሌላዉን ለመበተን ዛቻዉ ያልበረደለት ጸረ አማራ ሃይል ከሆነ የጥላቻ ቡድን ጋር ነዉ። ልዩነታችን ጎሰኝነትን ለማስፋፋት ብዙ ሺሕ የትግራይ ወጣቶችን ሕይወት በጦርነት ማግዶ ለጥቂት የወያነ ትግራይ “ዘበናይ መሳፍንቶች” የስልጣን ማመቻቺያዉ ካደረገ ቡድን ጋር ነዉ። ትግሌ አገሬንም ሆነ እትብቴ የተቀበረባትን ከተማና ቤተሰቦቼን እንዳልጎበኝ በጠመንጃ ከሚያስፈራሩኝ ሕግ አልባ የወያነ ትግራይ መሳፍንቶች ጋር ነዉ። ባጠቃላይ ትግሬነቴን በመግፈፍ “ሸዋዉያን ተጋሩ”በሚል ስም ሰይሞ በአማራዉና በትግሬዉ መካከል ጥላቻና ጎሰኛነትን መመርያዉ ካደረገ የትግሬነታችንን ትዉልደ ሐረግ ሰጪ እና ከልካይ አድርጎ ራሱን ከሾመ አጥንት ቆጣሪ ጎሰኛ ቡድን ጋር ነዉ። ምኒልክ የሸዋ ሰዉ ናቸዉ፡ ሸዋነታቸዉ እንደ የትግራይ ጠላት አያስቆጥርባቸዉም። ምኒልክም ሆኑ የሸዋ፤የጎጃም፤የወሎ፤የጎንደር አማራዎች የትግራይ ደመኞች ሳይሆኑ “የክፉ ቀን ወዳጅ”መመክያ እና “በክፉ ቀን ድረሱልን ተብለዉ የደረሱ፤ ትናንትም ዛሬም ለወደፊቱም ለትግራይ ሕዝብ አጋርነታቸዉ የማይታጠፍ ኢትዮጵያዉያን፤ የትግራይ ሕዝብ የደም፤የስጋና የአጥንት ዘመዳሞች ፤የባሕል እና የሕሊና ትስስሮቻቸዉ ከአንድ ዘር ኢትዮጵያዊ ትዉልድ እና አገር አብራክ የተወለዱ ናቸዉ።ስለሆነም “የትግራይ ህዝብና የትምክሕተኞች ሴራ ከትናንት እስከ ዛሬ”ዳራሲ ተጋዳላይ መምህር ገብረኪዳን ደስታም ሆነ የሚያመልከዉ የራሱ ድርጅት “ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ” በአማራዉ ሕዝብ እና በጠቅላላ ላገሪቱ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ላሳዩት የትምክሕት ባሕሪያቸዉና ንቀት እንዲሁም ለአናካሽ ሴራቸዉ ሁሉ ይቅርታ መጠየቅ ይኖርባቸዋል እላለሁ። የትግራይ ነባር ታሪካችን ወያነ ከሚያስተምረዉ የተዛባ ትምህርት እጅግ ተቃራኒዉ ነዉ።የአክሱሟ ታቦተ ጽዮን በጠላት ስትፈለግ ለአክሱም መኳንንቶች፤ቀሳዉስቶች፤ንጉሡ እና ለንጉሣን ቤተሰቦቹ የሸዋ ሕዝብና ዋሻ ነበር አጋር ሆኖ በአክብሮት አኑሮ ከጠላት የተከላከለዉ። አምበሳ ዉድም በሃይለኛዋ ጠላት በአገዋ ንግሥት እንዲገደል ሲፈለግ ከአክሱም ሸሽቶ መጠለያዉ ያደረገዉ ያዉ ሸዋ ነበር። ታዲያ ሸዋ ወይንም የአማራ ሕዝብ እንዴት በጠላትነት ተቆጥሮ በወያኔ የዘረኛ መርሕ ያላመንን አንዳንዶቻችን የትግራይ ተወላጆች “የሸዋ ትግሬዎች” ተብለን ሸዋን አንደ ዓይነተኛ ጠላት ተቆጥሮ የቅጽል ስም ይሰጠናል? በዚህ አጋጣሚ ለትግራይ ተወላጆችና ምሁራን የማስተላልፈዉ መልዕክት ሌላዉን በዘረኝነት እየከሰሱ የራስን ጉድፍ ሳያዩ በሌላዉ ዓይን ላይ የሚታየዉን ጉድፍ ለማመላከት የሚጥሩት ወያኔዎች ለ36 ዓመት ያስተጋቡትን ጸረ አማራ ቅስቀሳቸዉ ፰ እንዲያቆሙ ይረዳ ዘንድ የትግራይ ተወላጆች ግልጽ አቋም እንዲይዙ እጠይቃለሁ። ጸረ አማራነታቸዉና አልፎም በትግራይ ዉስጥ በአዉራጃዊነት ባምቻ ጋብቻ በአጥንት በደም በወረዳ በወንዝ ትስስር በጎጠኛነት የተለከፉ መሆናቸዉ እኛ ወያኔን በምንቃወም የትግራይ ተወላጆች ብቻ ሳይሆን ወያኔን ከመሰረቱ ከፍተኛ መሪዎች እና አብዛኛዉ ታጋይ የነበረ ሁሉ በግልጽ የወያኔ ዘረኛነት አጋልጠዋል። ወያነ ትግራይ በስማችን ብዙ ወንጀል ፈጽሟል። ወያነ ትግራይ እጅግ ሲበዛ ጐሰኛ እና ፋሽስታዊ ድርጊቶችን አከናዉኗል። በሃገር ክሕደት ቀዳሚዉን ማሕደር ይዟል።የትግራይ ተወላጆች ቆም ብለን ማሰብ እና ኢትዮጵያዊነታችንን፤ሉዓላዊነታችን እና ሰንደቃላማችንን ያረከሰዉን ወያኔን መቃወም የታሪክ ግዴታችን ነዉ።
ወደ መጽሐፌ ይዤያችሁ ከመግባቴ በፊት ወያነ ትግራይ የአማራዉን ሕብረተስብ የሚጠላ ጐሰኛ አይደለም ብለዉ ወያነ ትግራይን ለመከላከል የሚሞክሩ የወያኔ አማኞች ሊኖሩ ስለሚችሉ ማስረጃዉን ለማቅረብ እንዲመች ወያኔን ከመሰረቱት የመጀመሪያዎቹ መስራች ታጋዮች አንዱ አስገደ ገብረስላሴ “ጋህዲ” በተባለዉ በቅጽ 2 የትግርኛ መጽሐፉ ላይ የሰጠንን አንዲት ጠቃሚ መረጃ ወደ አማርኛ ተርጉሜ ካቀረብኩ በሗላ፤ የወያኔ ታጋይ ገብረኪዳን ደስታ “የትግራይ ሕዝብና የትምክሕተኞች ሴራ ከትናንት እስከዛሬ” በሚለዉ ጎሰኛ መጽፉ ላይ የአማራዉ ሕብረተሰብና አጼ ምኒልክን “የትግራይ ደመኞች” በማለት የከሰሳቸዉን ክሶች ተቀባይነት እንደሌላቸዉና መጀመሪያ ወያኔ የራሱን ጎሰኛ እና ፋሺስታዊ ባሕሪ መፈተሽ እንደሚኖርበት የተከራከርኩበትን ወደ “ይድረስ ለጎጠኛዉ ምመህር”መጽሐፌ ይዤያችሁ እገባለሁ።
<<ህወሓት በ1969 ዓ.ም. የካቲት ወር ወደ በረሃ ሲወጣ የብሔር ጭቆና እና የመደብ ጭቆና በመቃወም የብሄሮች መብት በራስ የመወሰን መብት ለማረጋገጥ እኩልነትና አንድነት የተረጋገጠባት ኢትዮጵያ ለማምጣት ያለመ ነበር። ከጥቂት ጊዜ በሗላ የተገለጸዉ ዓላማዉን ሰርዞ <<ጥያቄያችን ሃገራዊ ጥያቄ ሆኖ ከባዕድዋ ቅኝ ገዥ ኢትዮጵያ ነፃ ወጥተን ነፃ አገር ለመመስረት ነዉ እየታገልን ያለነዉ። “ምስ አምሓሩ ሓቢርካ ምንባር አይካኣልን”ከአማራዎች ጋር አብረህ መኖር አይቻልም (ጋህዲ ቁጥር 2 ገጽ 136)”>>የሚል መተከል ቀረበ።(ጋህዲ ቁ 2 ገጽ 136-የትግርዉን ቅጅ ይመልከቱ)። እንደዉም ከነጭራሹ ይላል አስገደ ገብረስላሰ በጋህዲ መጽሐፉ ላይ << እንደ እነ ኢዲዩ እና ኢሕአፓ ያሉ በትግራይ መሬት ዉስጥ የሚንቀሳቀሱ ኢትዮጵያዊ የፖለቲካ ሽምቅ ተዋጊዎች “ከአገራችን” ይዉጡልን እነኚህም የትግራይ ጠላቶች ናቸዉ፡ ብለን ለትግራይ ሕዝብ እናስተምረዉ። ጥያቄያችን “አገራዊ” (የኮሎኒ ጥያቄ) ስለሆነ ከእነኚህ ድርጅቶችም የጊዜ ጉዳይ እንጂ ዉለን አድረን ጦርነት መግጠም ስለማይቀረን፤ልክ እንደ ደርግ እነሱም ጠላቶቻችን ናቸዉ።ከነጭራሹ “አማራዎች” ከአገራችን ይዉጡልን…>> (ጋህዲ ቁ 2 ገጽ 137 )
<<…በማለት ኢትዮጵያዊ ፓርቲዎች በገዛ አገራቸዉ ትግራይ ዉስጥ የመንቀሳቀስ መብታቸዉን የሚጻረር/የሚያግድ አቋም ይዞ ተንቀሳቀሰና፤እንዳለዉም ከተጠቀሱት ኢትዮጵያዊ ድርጅቶች አመቺ የመምታትና ከሕዝቡ የመነጠል ሁኔታና ሴራ እስኪያመቻች ድረስ ድርድር እናድርግ እያለ ሲደራደር ቆይቶ ራሱን ካደላደለ በሗላ፤ አቅሙን ገንብቶ አስተማማኝ ደረጃ ደርሶ፤ መጨረሻ ወደ ጦርነት በመግባት ኢትዮጵያዊ ድርጅቶች ከተባሉት ሁሉ የነበረዉ ቅራኔና ግንኙነት በጦርነት ደመደመዉ”>> ጋህዲ ቁ-2-ገጽ 137 ትግርኛዉ ቅጅ)። <<ኢህአፓ በአጋሜ አዉራጃ ዉስጥ በአሰፈ ሰበያ እና በወረዳ ጉሎ ሞዀዳ በወያነ ትግራይ የጠባብነት ጨረታ አሸናፊነት ተበልጦ ከትግሉ ከወጣ በሗላ ።ከዚያ በሗላ የጠባብ ብሔረተኝነት በሽታ በመላዋ ትግራይ እንደ ተላላፊ በሽታ ተስፋፍቶ ወደ ሕዝቡ በመተላለፉ አብዛኛዉ የትግራይ ሕዝብ ፀረ አማራ ተንቀሳቀሰ።”>> (አስገደ ገ/ስላሴ የወያኔ የመጀመሪያ መስራች አንዱ፦ ጋህዲ ቁ/2 ገጽ 155 የትግርኛዉ ቅጂ 2001 ዓ.ም.) ዉድ አንባቢ ሆይ! ይህንን.እጅግ-አሳፋሪ፤ፋሺስታዊ፤ጸረ-ኢትዮጵያ፤ጸረ-አንድነት፤ሃገራዊ-ክህደት፤ጠባብ ጐሰኛነቱና ትምክህቱን ስንመለከት፤“ትግራይ የኢትዮጵያ ቅኝ ግዛት ነች!” “አማራዎች ከትግራይ መሬት መዉጣት አለባቸዉ!” “እኛ ትግሬዎች ከአማራ ሕዘብ ጋር መኖር አንችልም!” በማለት የትግራይን ሕዝብ ኢትዮጵያዊነት በመካድ በመመርያዉ አስፍሮ ያስተማረ ወያኔ ሌላዉን ትምክሕተኛ ወይንም ዘረኛ በማለት አፉን ሞልቶ የሚናገርበት ሞራል አለዉን? ወደ ታሪኩ ይዤያችሁ ልግባ። ደራሲዉ ሐምሌ 1 2002 ዓ.ም getachre@aol.com www.ethiopiansemay.blogspot.com ጌታቸዉ ረዳ P.O.Box 2219 San Jose, Ca 95109 ይድረስ ለጎጠኛዉ መምህር ዋጋ $20.00 ጠቅላላ ከነመላክያዉ ሓይካማ! (ትግርኛ - ሌላ ይዘት ያለዉ መጽሓፍ ነዉ) $15.00 ከነመላክያዉ ጠቅላላ ትግርኛዉ ለሁለተኛ ጊዜ ታርሞ የታተመ ነዉ (ከፊተኛዉ በጣም ይለያል)።