Tuesday, February 4, 2020

ኢትዮጵያን ለማፍረስ የተላከው 7ኛው የኦሮሞዎች ንጉሥ በጌታቸው ረዳ Ethio Semay (ኢትዮ ሰማይ)



ኢትዮጵያን ለማፍረስ የተላከው 7ኛው የኦሮሞዎች ንጉሥ
በጌታቸው ረዳ Ethio Semay (ኢትዮ ሰማይ)
2/4/20
በሚቀጥለው ሰሞን የአብን የድርጅት ክፍል ሓላፊ ነው የተባለው ስለ አዜማ ድጋፍ አንስቶ ስለ አማራ ወጣቶች የወሰዱት ትክክለኛ የቁጭት መልስ የተመጻደቀበትን አለቅላቂ ባሕሪነቱን ትችት አቀርባለሁ። ይህ የአብን የድርጅት ክፍል አመራር ተብየው ገና እሱ ከመወለዱ በፊት ግንቦት 7 የተባለው ዛሬ ኢዜማ በአማራ ልጆች ህይወትና በድርጅቱ አመራሮች ላይ ሲያደርገው የነበረውን ወንጀሉን ያወቀ አይመስልም። ስለዚህ ነው ማለቅለቁና ዲሞክራሲያዊነ ት መመጻደቁን በአማራ ወጣቶች ላይ ለመጸዳዳት የሞከረው።በሚቀጥለው ጊዜ ትችቴን እስካቀርብ ድረስ ለዛሬ ግን የኢትዮ ሰማይ ተከታታዮች ይህንን ለዛሬ ያቀረብኩት ኢትዮጵያን ለማፈርስ የተላከው 7ኘው የኦሮሞዎች ንጉሥ” የሚለውን ትችቴን አንብቡ። መልካም ንባብ።

አንድ ዘመናዊ ትምህርት ቤት ያልተከታተለ ልጅአለም (ዘነበ) የተባለ ጫካ ውስጥ
የኢሕአፓ አባል የነበረ የወልቃይት ተወላጅ እዚህ እኔ ከምኖርበት ከተማ ውስጥ ከ20 አመት በፊት ኢትዮጵን ሊገዛ የሚመጣ መሪ በሃይማኖቱ እስላም ነው፤ አገሪቷን ግን አሁን ካለው ሁኔታ በከፋ መልኩ ልክ እንደ “ግራኝ አሕመድ” ወደ አደገኛ ብጥብጥ ይወስዳታል ብሎ በሕልሙ የተከሰተለትን ንግርት ደጋግሞ ሲነግረኝ እኔም ትንቢቱን ላለመናቅ ፈገግ ብየ በማድመጥ ንግገሩን ”ከምር ሳልወስደው” ዝም አልኩኝ።ልጁ የሚኖሮው ኮሎራዶ ይመስለኛል (ባልሳሳት) አሁን አሁን ሳስበው የልጁ ስልክ አጣሁት እንጂ ደውየ “የነገርከኝ ነገር አውነት ነበር” ብየ ልነገረው ነበር።

7ኛው ንጉሥ ነኝ ብሎ ወደ ሥልጣን ለመምጣት ያልሰራሁት ጥረት አልነበረም ብሎ ራሱ ለሕዝብ የተናገረው አብይ አሕመድ ከሰይጣንም ሆነ ከኦነግ ፤ከአሜሪካ ከሻዕቢያም ሆነ ከወያኔ እየተመሳጠረ ያችን የተመኛትን ንግሥና ለማግኘት ነግሶ አገሪቷን ወደዚህ ብጥብጥ መውሰዱን ሳስበው 'የላንች ቦክስ' ሬስቶራንት ባለቤት የነበረው በሕልም የተከሰተለትን “ዘነበ” ትዝ አለኝ።

የኢትዮ ሰማይ ድረገጽ ተከታታዮች እንደምን ሰነበታችሁ? ትናት አብይ አሕመድ ለኦነግ/ወያኔ ፓርላማ አባሎች ሰብስቦ በቦሌ መንገድ የተከላቸው የፈኩ አበባዎች እየተመረጡ በሌቦች መወሰዳቸው ሲናገር አባሎቹ አደራሹን በሳቅ ሲያላግጡበት “የሚያሳዝን” እንጂ “የሚያስቅ” አይደለም ብሎ የገዛ ፓርላማው መሳቂያ ሆኖ መዋሉን አድምጠናል።

ስለታገቱት የዩኒቨርሲቲ ወጣት ሴቶች ተጠይቆ አጋቾቻቸው ማን እንደሆነ እና የትስ እንዳሉ የሚያውቀው ነገር እንደሌለ ሲነግራቸው የተገረማችሁ እንደምትኖሩ አውቃለሁ። ምክንያቱም አገልጋዮቹ አጋቾቹ ጋር ድርድር እያደረጉ እንዳሉ እና የት ታግተው እንዳሉ በትክክል ቦታው እንደሚያውቁት ለሕዝብ ሲናገሩ ስላደመጣችሁ በሁለቱም መካከል ያለው የመልስ አሰጣጥ ልዩነት ነው ሊያስገርማችሁ የሚችለው። ሆኖም አገልጋዮቹ የሚዋሹት ንጉሳቸው እንዲዋሹ ሲያዛቸው ብቻ ነው የሚዋሹት። ንጉሡ “እኔ ዲሞክራት መሪ ነኝ” ብሎ በቃሉ ይናገር እንጂ በተግባርም በቃሉም 7ኛው ንጉሥ ነኝ ብሎም ሲናገር ስለሰማነው ንጉሡ ሳያውቅ፤ ሎሌዎቹ አንድም ነገር እንዲናገሩ አይፈቅድላቸውም።ለዚህ ነው ስለታገቱት ልጆች የተምታታ ንግግር ሲነገር ቆይቶ መጨረሻ የታገቱትን ወላጆች ጠርቶ “በሕይወት እንዳሉ ተነግሮናል፤ደስ ብሎናል” ብለው በሚዲያ እንዲናገሩ የአእምሮ አጠባ አድርጎ አሞኝቶ ሲለቃቸው የዋሻቸውን ንግግሩን አምነውት ለሕዝብ መገናኛዎች የተነገሩትን ሰምታችሗል። መጨረሻ ላይ እቅጩን ለሕዝብ ተናግሯል።

እኛ ኢትዮጵያውያን የነገሮችን የመርሳት መጥፎ ባሕሪ ስላለን የተደረጉብንን ጥቃቶች ካላስታወስናቸው ማንም እየመጣ በቃላት እየደለለ ጥቃቶች እየተፈጸሙብን መቀጠሉ አይቀሬ ነው። ገናናው መስዋዕቱ አሳምነው ጽጌ ‘ከ500 አመት በፊት የተፈጸመው ጥቃት በከፋ መልኩ እየመጣብን ነው’ ስላለው ትንቢታዊ ንግግሩን ስታስታውሱ እየፈጸመ ያለው ጉድ ትክክለኛነቱን ማየት አይቸግራችሁም።


በ16ኘው ክ/ዘመን ጋላዎች ከጫፍ ድምበር ዘልቀው ወደ መሃል አገርና ወደ ሰሜን እንዲሁም ወደ ምስራቅና ምዕራብ ኢትዮጵያ ገብተው ሰፊ ወረራ የፈጸመው ከብት አርቢው “የጋላ” ነገድ ለዛሬዎቹ “ዎሮሞዎች” ባሕልና ቋንቋ ብቻ ሳይሆን የባሕሪ ውርሻ አውርሶአቸው እነሆ ዛሬ አገሪቱን ጥንት ጋላዎች ያካሄዱት የዘር ማጥፋትና የመሬት ወረራ እየፈጸሙ ወጣት ልጃገረዶች ከየት/ገበታቸው እንደ አቻቸው ናይጄሪያ “ቦኮ ሓራም” ጸረ ዘመናዊ ሥልጣኔ ሆነው ኢትዮጵያ ውስጥ ሽብር ነዝተው የነውጥ ምድር አድረገው “ኢንዲጂነሱን/ጥንታዊ ባለቤትየውን” በመጤ ፈርጀው በፍርሓት ሸብበውታል። የነዚህ ምድር የሚያስተዳድረው የሽብርተኞቹ መሪ 7ኘኛው ንጉሥ አብይ አሕመድ ለኢንተርሃሙዌዎቹ መሪ በመንግሥት ወታደሮች ጥበቃ እንዲደረግለት በማድረግ አብይ አሕመድ በዓረቦችና በአሜሪካኖች እየታገዘ “ኢትዮጵያን የማፍረስ ይፋዊ አዋጅ አውጆ ምድሪቱ በሽብር እያናወጣት ይገኛል።

አብይ አሕመድ በእስላምነቱም በጴንጤነቱም ለተገንጣይ ኦሮሞዎችና ለሻዕቢያ እንዲሁም ለዓረቦችና አሜሪካኖች መንግሥት በሰላይነት ማገልገሉን በደቂቅ ስትመረምሩት አሁን ላላው አገር የማፍረስ ባሕሪው መሰረት አለው።፡ወሮበላ ቡድን ልጃገረድችን ከትምሕርት ገበታቸው ማፈንና ማሽሸበር የሚነሳሳው ምክንያት መንግሥት ሲዳከም ብቻ ሳይሆን ሥርዓተ አልባነትን የሚከተል አበረታች መንግሥት ሲሰፍን ነው። ልጃገረድችን የሚያፍንና እንደቦኮ ሓራም ዘመናዊ ትምሕርት እንዳይቀጥል የሚያውክ 'የኦሮኦሞ ቄሮ' አሸባሪ ቡድን ሌላ ቀርቶ “የአዲስ አበባ ኗሪዎች ዕጣን ለማጨስ ሲፈልጉ የኦሮሞ ፈቃድ ያስፈልጋቸዋል” ብሎ አዋአጅ እስከማወጅ ድረስ ሊደርስ የቻለበት ምክንያት ንጉሳቸውን አብይ አሕመድ በመተማመን ነው። በዎሮሞ እስላማዊ ንጉሥ የተያዘቺው አዲስ አባባ “ስብሰባ ለማድረግ የሚፈቀድላቸው” እስላሞች፤ቄሮዎችና ዎሮሞዎች ብቻ ናቸው።

የዎሮሞ ድርጅቶች በጠቅላላዉ በአንድ ጥላ ስር ናቸው። ኢኮኖሚ፤ ፖለቲካውና ጦር መሳሪያ በእጁ ነዉ። አንድ ወዳጄ እንደሚሉት ከህወሓትም ጋር በጣምራ እየሰሩ ነዉ። ለዚህም ማስረጃ የሚሆነን “ትናንት” በፓርላማው ተገኝቶ ባደረገው ንግግር 17 በላይ የሚሆኑ የህወሓት ሚኒሰትሮችና በብዙ ሺሕ የሚሆኑ የትግራይ ተወላጆች የመንግሥት ተቀጣሪዎች እንዲሁም 35 የፓርላማ ተጠሪዎች እቦታቸው ላይ እንዳሉና ለመንካትም ለማባረርም ምንምን ፍላጎትና ዕቅድ እንደሌለው ተናግሯል።አሁን አሁን ሳስበዉ አብይ ወደ ስልጣን ከመምጣቱ በፊት በተለይ ከኦሮሞ ድርጅቶች ጋር አብረዉ የገቡት ቃል እንዳለ በእርግጠኛነት መናገር ይቻላል።

ኢትዮጵያን ለማፍረስ የታቀደለንን የአፓርታይድ አስተዳዳር ዎሮሞዎቹ በአንድ ጥላ ስር ተሰባስበው አዲስ አባባ የኛ ናት፤ በኛ ፈቃድ ትኖራላችሁ እያሉ አዋጅ ሲያውጁ አብይ አሕመድ ምንም ያለው ነገር የለም ብቻ ሳይሆን “ኦሆዴድም” ተመመሳሳይ መግለጫ እንዲወጣ አድርጓል። ለዚህ ነው “ንጉሡ” በባልደራሱ እስክንድር ነጋ ላይ ጦርነት ያወጀበት። ጦርነቱም ግልጽ ሆኖ ወደ ኳስ ሜዳ እንደማይገባ ሁሉ አስከልክሎታል። ከወያኔ ዘመን እጅግ የባሰ ዘረኛነት!

ይህ ከ40 አመታት በላይ የታቀደ በ20 ወራት ውስጥ የተከናወነ የኦሮሞ ሊሂቃን ያቀዱት የወረራ ፕሮጀክት/ዘመቻ ነው። ሥልጣን ላይ የተቀመጠው የኦሮሞዎቹ 7ኛው ንጉሥ “አብይ አሕመድ ዓሊ” እውቅና እየተተገበረ አገርን በጥበብ የማፍረስ ዘዴው ሚዛን ላይ ሲቀመጥ፤ ውድመቱ ከወያኔዎች ጥቃት እኩልነቱን አልፎ የከፋ ግልጽ የጥቃት ዘመቻው እየተካሄደ ነው። ስለዚህ ዜጎች የዘመናችን 7ኛው ንጉሥ የግራኝ አሕመድ ታሪክ ደጋሚው አብይ አሕመድ በየወራቱ አስፈሪ ጭራቅ እየሆነባቸው በመምጣቱ “የመንግሥት ያለህ” እያሉ ኢትዮጵያዊ መሪ በማፈላለግ ላይ ያሉት።

ወጣቶች አገራቸው ኢትዮጵያ ከውድመትና ከሽብር እንዲታገዱ ይህ በዘመናችን የተከሰተው ጅማ የተወለደው አደገኛው የግራይ አሕመድ ታሪክ ደጋሚ ከፍተኛ ወረራና ሽብር መጋፈጥ አለባቸው። በተለይም አማራው ወጣት ፊት ለፊት ካልተጋፈጠው የወያኔ ታጋይ በነበረው ማሃይሙ የነ “ደመቀ መኮንን አለቅላቂው” በወልቃይቴው በኮለኔል ደመቀ ”ካሃዲ” ተብሎ የተሰደበው መስዋዕቱ አርበኛው የቁርጥ ቀን ኢትዮጵያዊው “ዳግማዊው በላይ ዘለቀ’ የአሳምነው ጽጌን ማስጠንቀቂያ እውን እየሆነ ስለሆነ ባንክ ለመዝረፍና ወጣት ልጃገረዶችን ላማገት እንዲረዳው ኦነግን መሳሪያ የሚያስታጥቀው “የኦዴፓ ድርጅት” እና የድርጅቱ መሪ አብይ አሕመድና በሥሩ ያሉት ሎሌዎቹን ተፋለሙ። ንጉሡ ወደ ዙፋን ሲመጣ ተቃውሜዋለሁ፤ አሁንም እቅጩን አውቃችሁ ተፋለሙት። ይህ ሰው ትውልድ ገዳይና አደገኛ አገር አፍራሽ ነው!

አመሰግናለሁ፤ ጌታቸው ረዳ (ኢትዮ ሰማይ)