Wednesday, June 13, 2018

አገሪቷ ወደ ብረት ትግል መግባትዋ አይቀሬ ነው ስላችሁ አላመናችሁኝም ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay)


አገሪቷ ወደ ብረት ትግል መግባትዋ አይቀሬ ነው ስላችሁ አላመናችሁኝም
ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay)
እንዲህ ብየ ስል ብዙ ወዳጆቼ አላመኑኝም። ወደ ብረት መግባትዋ አይቀሬ ነው ብቻ ሳይሆን ላንድ የቅርብ ወዳጄ ያወያየሁት ‘ለምስኪኑ አብይ እጅግ እሰጋለታለሁ” ነበር ያልኩት።እንደ ቁም ነገር አልወሰደውም። እኔ ግን  በጣም ነው ያሳሰበኝ። እኔ እና አብይ የለያየን የአማራ መፈናቀል ያለማቀሙ በሚመለከት እንደሆነ ደጋግሜ ተናግሬአለሁ። ችግሬ ያ ብቻ ነው። አብይ ገጽታው ስመለከተው  ኢትዮጵያዊነት የተላበሰ ሆኖ ገጽታው የዋህ እና ገራገር የትናንት ሰው ሆኖ አግኝቼዋለሁ። ኢትዮጵያዊ “ከርስ” (አንጀት) ያለው ይህ ገራገር ሰው፤ ስልጠን የተቆጣጠሩት በኤርትራና ትግራይ ዲቃላዎች ጥይት (መርዝ) እንዳይጎዳ የነበረኝን ስጋት አሁን አሁን እየጨመረ ሄዷል። እነዚህ ባንዳዎች ሰሞኑን እየተገለባበጡበት ያለውን አሳፋሪ የድንጋጤ ትዕይንት ስለ አልጄሪስ ስምምነት አስመልክተው እንደገና መቀሌ ከተማ ተሰብስበው 6/13/2018 (ሰኔ 6/2010 ዓ.ም )ያሳለፉት ውሳኔ ጉዳይ ስመለከት ስጋቴ ትክክለኛ እየሆነ መምጣቱ ያረጋግጥልኛል።

የአልጄሪሱ ስምምነት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ተቀብለናል ብሎ ለእኩያዎቻቸው ለኤርትራ ባንዳዎች ጥሪ ካደረገ በላ እኔ ‘እምቢታ እንዲያሰማ’ ለሕዝብ ያደረግት ጥሪ ሰምቶ የትግራይ ሕዝብ ግልብጥ ብሎ በሰለማዊ ሰልፍ ‘አንቀበልህም’ ብለው እቅጩን ሲነግሩት (አንዳድ ታጋዮች ቢሰሙ ብየ እሰርዋቸው ብየም ጥሪ አቅርቤ ስለበር) ሁኔተው ስላሰጋቸው ‘ስልጣናቸው እንዳይናጋ ተደናግጠው’ ድጋሜ ስብሰባ አድርገው የለመዱበትን የውሸት እና የመገለባበጥ አሳፋሪ ባሕሪያቸው ተጠቅመው፤ “ሚሴ” አደናቀፈኝ ዓይነቱ ማምለጫ የሆነ መግለጫ አውጥተዋል። መግለጫው ለመመልከት በዚህ መስኮት ይመልከቱ፤
ትግረኛው (መግለጺ ማዕከላይ ኮሚቴ ህወሓት) በሚል

አማርኛው ትርጉመም ደግሞ እዚህ ይመልከቱ

እኔን ያሳሰበኝ እና ትኩረቴ  የተገለባበጠበት ያለው ስለ የድንበሩ ጉዳይ  አስመልክቶ ያሳለፈውን ውሳኔ ሳይሆን በሕዝብ እየተሞገሰ ያለው በኦሮሞዎቹ እና በአማራዎች እየተካሄደ ያለው “ጥገናዊ” የለውጥ ማዕበል የደነገጠ መሆኑን ሳያመነታ መግለጹን ነው። ይህ የበሰበሰ የሻገተ የ17ኛው ክ/ዘመን የዘመነ መሳፍንት አስተዳዳር የተላበሰ ፋሺስታዊ ጉጅለ “በስብሼአለሁ ብሎ እራሱን ለትሃድሶና ለኑዛዜ” ቢያቀርብም ፤ በአብይ አህመድ እየተካሄደ ያለው ጥገናዊ አርምጃ እንዳልወደደው በሚከተለው ዐረፍተ ነገር መግለጹ ስመለከት ይህ በጣም ላ ቀር የሆነ ፋሺስታዊ የባንዳዎች ጉጅለ የነበረኝን ስጋትና ጥርጣሬ እውነት መሆኑን ያመላከተ ነጥብ ነው።

የሚከተሉት ነጥቦች ልብ እንበል፦

1)    “በዚህ ረገድ በጥልቀት የመታደስ እንቅስቃሴው የደረሰበት ደረጃ በኢሕአዴግ እንዲገመገም የህወሓት የማዕከላዊ ኮሚቴ ይጠይቃል።” ይላል። ይህ ምን ማለት ነው? እስካሁን ድረስ በአብይ አህመድ መሪነት የተወሰዱ እርምጃዎች ባንዳዎቹ እንዳልተደሰቱ ያሳያል። ስላልተደሰቱም ‘እስካሁን ድረስ የተወሰዱ እርምጃዎች እንዲገመገሙ” ይጠይቃል። ለምን ግምግማ? ብለን ስንል “አብይን ለመቃወም መንገድ አጥተው ስለነበር” ይችን አጋጣሚ በመጠቀም “ጭቅጭቅ” በመፍጠር እየተካሄደ ያለው ጥገና ውሎ አድሮ ባንዳዎቹንም እያሰጋ ስለሄደ “መፈንቅለ አብይ” ለማድረግ እንዲያመቻቸው ግምግማ በመጠየቅ የለመዱትን የጠብ አጫሪነት እና የሴራ ገመድ ለመግመድ እንዲያመቻቸው ነው “ጭቅጭቅ” እንዲደረግ እንጠይቃለን ብለው ጥያቄ እያቀረቡ ያሉት።

2)   ሁኑ ወቅት በኢህዴግ ደረጃ እየተካሄዱ ያሉት የ ኢሕአዴግን  ሕገ ደምብና ተቋም ያልተከተለ አሰራር የአመራር ምዳባዎች እንዲታረሙ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ  ይጠይቃል።

ይህ ከላይ የሚያሳየን ዓረፍተነገር። ስለ የወያኔዎች ቱባ ቱባ ባንዳዎች ወያኔ ከመደባቸው የሰው ልጆች ማሰቃያ ቦታዎች ከስልጣናቸው ማዘዋወርና አንዳንዱም በጥሮታ ማስወገድ (?) እንዳልተመቸው ያሳያል። የተወሰዱት እርምጃዎች ብቻ ሳይሆኑ አሁንም ስልጣን ላይ ያሉት ከእነዚህ መቀሌ ውሰስጥ ተሰብስበው አሳፋሪ ውሳኔ ያሳለፉ ባንዳዎችም ለወደፊቱ እነሱንም ጭምር እሳቱ እየተጠጋቸው እንዳለ አይቀሬ መሆኑን ስላወቁ ካሁኑኑ መቆም እንዳለበት ይጠይቃል። በዚህ የሚቀጥል ኮሆነ ግን የብረት አርምጃ እና ፍጥጫ እንደሚገቡ በውስጥ አገላለጽ አብይ እና ጉጅሌውን እያስጠነቀቁት ነው ማለት ነው።

አብይ እዚህ ላይ (ኦሮሞዎች) እና የአማራ ሕዝብ የተጀመረው ጥገናዊ ለውጥ ወደ ተጨባጭ ለውጥ ለማሸጋጋር በጋራ ለውጡን ደግፈው ባንዳዎቹ በሕዝብ እንዲተፉ ማድረግ እና ሕዝብ አብይ እንዲደግፍ አድርጎ ባንዳዎቹ ጠመንጃቸው ብቻ ተገን አድርገው ከሕዝብ እንዲነጠሉ ማድረግ ከፍተኛ መስዋዕት የሚጠይቅ አስጊ ሁኔታ ገበተናል። ለዚህ ነው አስቀድመን ጥቂት ሰዎች እነዚህ ሰዎች “አልሞቱም” ፋሺስቶች ምንም ቢሆን ስልጣን በመደራደር አይለቁም ፤ ተፈጥሮው አይፈቅድለትም ስንል የነበርነው። አሁንም ወያኔዎቹ ኢትዮጵያን መዝረፍ ፥ መግደል ፥ የዘር ጽዳት ማድረግ ፥ ዜጎችን ማዋከብ ፥ አረጋዊያን እናቶችን መደብደብ ፥ ልጆቻቸውን መግደልና መሰወር ፥ በተቃዋሚ እስረኞች ላይ ግብረሰዶም እንዲፈጸም ማድረግና ክብራቸው እንዲዋረዱና ሕሊናቸው አንዲቃወስ ማድረግ ፥ አገርና ድምበር መሸጥ ፥ ምስጢሮችን አሳልፎ ለጠላት መስጠት የሚችሉበትን የ27 አመት የጨላማ ዘመን ማስቀጠል ካልቻሉ “ትግራይን” አጋዚያን ብለው በመሰየም ወደ ትግራይ ትግርኚ ግንጠላ መሄድ እንደሚችሉ አስቀድሞ ስብሓት ነጋ ወደ እየ መንደራችን እንበታተላለን ሲል የነገረን ስለሆነ አዲስ ዜና እንደማይሆንባችሁ እርግጣና ነኝ።

ወያኔዎች ባልጠበቁት ሁኔታ እና ጊዜ ለረዢም ጊዜ የበሰበሱበት ጊዜው ያለፈበት በስባሳ ኮሚኒስታዊና ፋሺስታዊ መስመራቸው ስለተንገራገጨባቸው ተደናግጠዋል። አገሪቷ ወደ ብረት ፍጭት መግባትዋ አይቀሬ ነው ብየ ደጋግሜ በቃለ መጠይቆቼ ስናገር የነበረውም ለዚህ ነው። እንደዚህ ስላችሁም አላመናችሁኝም። ፋሺስቶች ባህርያቸው ስልጣን ላይ መሞት ወይንም ተዋርደው መልቀቅ ነው። የትግራይ ባንዳዎች ምርጫ ስልጣን ካልቀጠሉ አገሪቱንም ትግሬንም በትነው ወደ ጫካ መግባትና አናርኪ መፍጠር ነው። ለኤርትራና ትግሬዎች ያልሆነች ኢትዮጵያ “ትበተን” ብለው ሲናገሩት የነበረው የትግሬዎቹ የቆየ “መፈክር’ እና አማራጭ ባህሪ ነው።
              ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay)