Friday, June 5, 2009

ኢሳያስ አፈወርቂ ኤርትራዊ ወይስ ትግሬ (ኢትጵያዊ)?

ኢሳያስ አፈወርቂ ኤርትራዊ ወይስ ትግሬ (ኢትጵያዊ)? ጌታቸዉ ረዳ www.Ethiopiansemay.blogspot.com
ከላይ የሚታየዉ የኢሳያስ የልጅነት ፎቶግራፎች ምንጭ ከEthiopiansemay.blogspot.com ዝግጅት ክፈል ነዉ፣፣ “ኢሳያስ አፈወርቂ ኤርትራዊ ወይስ ትግሬ (ኢትዮጵያዊ)?” በሚል ርዕስ በምኒሊክ መጽሄት ላይ ሰኔ 1993 ዓ.ም በዶ/ር ፍስሃ ጽዮን መንግሥቱና ጓደኞቹ ስለ ኢሳያስ አፈወርቂ ትዉልድ እና ዜግነት ሰፋ ባለ መልኩ ቀርቦ ነበር። በዛ ጽሁፍ ዉስጥ የኢሳያስ አፈወርቅ ወላጆች የትዉልድ ስፍራ እና የቤተሰብ ስም ዝርዝር በስፋት ከመቅረቡ ሌላ “ትልቁ የኤርትራዊያኑ ስህተት የማንነቱን መሠረት የማያዉቁ መሆናቸዉን ነዉ”-በማለት አብዛኛዎቹ ኤርትራዉያን በትግራይ ሕዝብ ላይ ያላቸዉ የተሳሳተ አመለካከት እና ንቀት ለምን ማንጸባረቅ እንደሚፈልጉ በጥልቅ አትቷል።በዚህ ጽሁፍ የማቀርብላችሁ“ኤርትራዉያኖቹ-ለምን በትግራይ/ኢትዮጵያዉያን ላይ ንቀት እንደሚያሳድሩ ሳይሆን፣ ትኩረቱ በኢሳያስ አፈወርቂ ብቻ ይሆናል፣፣ ከዚህ መረጃ በመነሳት የማቀርብላችሁ.እንደሚታወቀዉ ሰሞኑ በሻዕቢያ ቴሌቢዥን የተላለፈዉ በአቶ ኤልያስ ክፍሌ እና የኢትዮጵያ አርበኞች ግምባር ብሎ ራሱን የሚጠራ የዉጭ ዩዳይ ተጠሪ አቶ ስለሺ አማካይኝነት አስመራ ድረስ በመሄድ ከሻዕቢያዉ መሪ ከኢሳያስ አፈወርቅ ጋር ያደረጉት ቃለ መጠይቅ ለሕዝብ ይፋ መደረጉን ታስታዉሳላችሁ። ቃለ-መጠይቁን የተከታተላችሁ ሁሉ እንደምትገነዘቡት ጋዜጠኞቹ በአማርኛ ሲጠይቁት ኢሳያስ ሲመልስ የተጠቀመበት ቋንቋ የገዛ ቋንቋዉ በአማርኛ ሳይሆን በባእድ-በእንግሊዞች ቋንቋ-ነበር።ይህ-“ስልጡን”ኤርትራዊ “አጋሜዎች” የሚጠቀሙበት አማርኛ ቢጠቀም ስልጡንነቱ እንዳይራከስበት በማለት ይሆን? የሚል ጥያቄ ባብዛኛዎቻችሁ ሕሊና እንደሚኖር እርግጠና ነኝ። በዚህ መሰረት አድርገን ሰዉየዉ አማርኛ ለምን እንደተጠየፈ የኢትዮጵያን ረቪዉ አዘጋጅ አቶ ኤልያስ ክፍሌ ተጠይቆ ሲመልስ “አማርኛ የመናገር ችሎታዉ ደካማ ስለሆነበት ነዉ …” የሚል መልስ እንደሰጠ አንድ ቦታ ላይ ያነበብኩ መሰለኝ፣፣ ነገሩ ከብዙ ዜ ጀምሮ የተከታተለዉ ሰዉ ከተሰጠዉ መልስ የተለየ ነዉ፣፣ መረጃዎቹ የሚያሳዩት ለአማርኛ ያለዉ ጥላቻ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ምግብ ለሆነ ለእንጀራችንም ጥላቻ እና ንቀት ያለዉ መሆኑን ከፈረንሳይ መጽሄቶች ጋር ያደረጋቸዉ ቃለ ምልልሶች ያረጋግጣሉ፣፣ መረጃዎቻችን በመጠኑም ቢሆን ለማሳየት እንሞክራለን፣፣
ግልጽ ላልሆነላቸዉ ሰዎች ኤርትራዊ ነኝ የሚለን የኢሳያስ ማንነት እና ትዉልድ ካሁን በፊት ላላወቃችሁ አዳዲስ ወጣቶች ማህደሩን እንደገና ወደ ፊት በመሳብ ላለንተ አቀርባለሁ። አማርኛዉን ወደ ጎን በመተዉ -በዓረብኛ ቋንቋ፤ እና በ እንግሊዝኛዉ የመጠቀሙ አባዜ ከምንም የመነጨ ሳይሆን የኢሳያስ ኢትዮጵያዊነት/ትገሬነት እንዳይታወቅበት የሚያደርገዉ ከንቱ የደካሞች- የበታችነት የሕሊና ስሜት እና ራስን የማጣት የዕብደት ምልክት መሆኑን አንባቢዎች እንድታዉቁት “ኢሳያስ አፈወርቂ ኤርትራዊ ወይስ ትገሬ/ኢትዮጵያዊ?” ከሚለዉ ትንታኔ በመጀመር ኢሳያስ የትግራይ ተወላጅ ሆኖ የኢትዮያ ምግብ የሆነዉ እንጀራ የማጥላላት እና እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቋንቋ የሆነዉን አማርኛ ከእንግሊዞች እና ከዓረቦች ቋንቋ እያሳነሰ ማየት ለምን እንደመረጠ ለመሸፋፈን የሞከረዉ የትዉልድ ታሪኩንና የተያያዙ አጫጭር ትንታኔዎች እንመለከታለን፣፣
ኢሳያስ አፈወርቂ ኤርትራዊ ወይስ ትግሬ/ (ኢትዮጵያዊ)?
“ኢሳያስ አፈወርቂ ኤርትራዊነት ተረት ነዉ ወይስ እዉነት ነዉ? የኢሳያስ አፈወርቂ አባት አቶ አፈወርቂ አባት አቶ አፈወርቅ አብርሃ ይባላሉ፣፣ እናቱ ወይዘሮ አዳነች በርሄ ይባላሉ፣፣ ልጆቻቸዉም (1) አቶ አማረ አፈወርቅ (አፈወርቂ) (ይህ ስያሜ ኤርትራዊነትን ለማስመሰል ነዉ፣፣) (2) አቶ ኢሳያስ አፈወርቅ (3) አቶ አማኑኤል አፈወርቅ (4) አቶ ኤርሚያስ አፈወርቅ (5) አቶ ዮናስ አፈወርቅ (6) ወ/ሮ ጽጌረዳ አፈወርቅ (7) ወ/ሮ አርዮን አፈወርቅ
ከኤርትራ ፕረዚዳንት ቤተሰብ በስተጀርባ ያለዉ ታሪክ፣- የኢሳያስ አባት አቶ አፈወርቅ የመጡት ከትግራይ ተምቤን ሲሆን ዘራቸዉ የኢትዮጵያ አካል ከሆነዉ ከአጋሜ አዉራጃ የተዉጣጣ ነዉ፣፣ የአቶ ኢሳያስ አባት ይሰሩ የነበሩት በትግራይ አስተዳደር ክፍለ ሃገር በመቀሌ መዲና ነበር፣፣ ጡሮታ እስከወጡ ም ድረስ በመሬት ንብረት ይዞታ ማሻሻያ ሚኒስቴር ዉስጥ ነበር የሚሰሩት፣፣ ጥቁር ሙሉ ልብስና ጥቁር ክራባት ለባሽ ተብለዉ ይጠሩ እንደነበር ይነገራል፣፣ (“ካንትሪ ጀንትል ማን”ተብሎ አንዳንዴ ከሚታወቀዉ ከጥቁር ሱፍ የተሰራ ክብ ቆብ ከራሳቸዉ አይለዩም ነበር፣፣ ጋዜጣም ከእጃቸዉ በፍጹም አይለዩም ነበር፣፣ (በቅንፍ የተጨመረዉ- ጌታቸዉ ረዳ)፣፣ በናታቸዉ በኩል የኢሳያስ አጎቶች፣- (1) ደጃዝማች ሰለሞን አብርሃ (2) ካፒቴን መኮንን አብርሃ (3) አቶ ሓጎስ አብርሃ ናቸዉ፣፣
የአቶ ኢሳያስ አጎት ደጃዝማች ሰለሞን አብራሃ (በጊዜዉ ሲጠርዋቸዉ በነበሩ ጋዜጦች አጠራር “ሰለሞን አብሃም” በቅንፍ የተጨመረ- ጌታቸዉ ረዳ) በሃይለስላሴ ዘመነ መንግሥት ማለት (በ1946 ዓ.ም) የወሎ እንደራሴ ሆነዉ ያገለገሉ ናቸዉ፣፣ በዚያ ጊዜ መቀሌ ከተማ ዉስጥ ተደራጅቶ የነበረዉ የባህል ቡድን አስመራን ከጎበኘ በሗላ ወደ ደሴ መጣ፣፣ እንደራሴዉ ደጃዝማች ሰለሞን ለክብር እንግዶቹ በተዘጋጀዉ የእራት ግብዣ ላይ ምስጋናቸዉን ለቡዱኑ ከገለጹ በሗላ እሳቸዉም ትግሬ መሆናቸዉን አንስተዉ የባህል ቡድኑ የትግራይ ባህላዊ ሙዚቃ እና ባህላዊ ዉዝዋዜ ለማስፋፋት ላደረገዉ አስተዋጽኦ አድናቆታቸዉ ገለጹ፣፣ በተጨማሪም የደጃዝማች ሰለሞን እናትም አጋሜ አዉራጃ ዉስጥ ተወላጅ ትግሬ መሆናቸዉን እና አባታቸዉም በትግራይ ክ/ሃገር ዉስጥ የተምቤን ተወላጅ መሆናቸዉን አንስተዉ ለባህል ቡድኑ ገልጸዉላቸዋል፣፣ የባሕር ሃይል ካፒቴን የሆኑት ካፒቴን መኮንን አብርሃ የኢቴጌ መኮንን ትምሕርት ቤት ተማሪ የነበረቺዉ የደጃዝማች ገብራይ ልጅን አግብተዉ ሦስት ልጆች እንደወለዱ ይታወቃል፣፣ አቶ ሐጎስ አብርሃም ቢሆን በአዲስ አባባ የተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት የጥንት ተማሪ ሲሆን ለዚያዉ ተማሪ ቤት የእግር ኳስ ቡድን በረኛ ነበር፣ ሆኖም በበሽታ ምክንያት ትምህርቱን አቋርጦ ለጥቂት ጊዜ በብሔራዊ ባንክ ስራ ተቀጥሮ እየሰራ እንዳለ ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለየ ይታወቃል፣፣
የአቶ ኢሳያስ አፈወርቂ አያቶችና ሌሎች ዘመዶቻቸዉም - በሚመለከት፣-
በእናቱ በኩል የኢሳያስ አፈወርቂ አያት (የእናት እናት)ወይዘሮ መድህን “በራድ” ይባላሉ፣፣ በራድ (ተብለዉ በቅጥያ ስም የተጠሩበት ምክንያት ወ/ሮ መደህን በጠጅ ስራ ንግድ ተሰማርተዉ ይኖሩ ስለነበር “ጠጅ”ባካባቢዉ የሚቀዳዉ “በራድ” ተብሎ በሚታወቀዉ “ማንቆርቆርያ” ስለነበር ነዉ፣፣ መድህን የኢሳያስ እናት የወይዘሮ አዳናች በርሄ እናት ናቸዉ፣፣ ኢሳያስ የልጅነት ትምርቱ የተከታተለዉ በሴት አያቱ በወይዘሮ መድህን ተንከባካቢነት ነዉ፣፣ በቅንፍ የተጻፈዉ- ጌታቸዉ ረዳ)፣፣ ወ/ሮ መድህንም በትዉልዳቸዉ ዓድዋ ሲሆኑ፣ የፊታዉራሪ ኪዳነ መስቀል አጎት ናቸዉ፣፣ ፊታዉራሪ ኪዳነ የአቶ የማነ ኪዳነ (የየማነ ጃማይካ)-አባት ናቸዉ ይባላል ፣፣ ይህ እዉነት ከሆነ የአቶ የማነ ኪዳነ (ጃማይካ)-እና አቶ ኢሳያስ አፈወርቂ “በኢትዮጵያ አጠራር” ወንድማማቾች ናቸዉ ናቸዉ፣፣ በአዉሮጳዉያኖች አጠራር ግን “የአጎት ልጆች ናቸዉ”፣፣ባጭሩ አሥመራ የሚገኙ አክራሪ ጠላቶች ናቸዉ የሚባሉት አብዛኛዎቹ የትግራይ ዝርያ የሆኑና በተለይ ከትግራይ በጠቅላላም ከኢትዮጵያ ጋር ጠንካራ የስጋ ፣ የአጥንት እና የደም ቁርኝት ያላቸዉ ናቸዉ፣፣
የኢሳያስ አክስት (የኢሳያስ እናት እህት) ወ/ሮ ሃና ይባላሉ፣፣ የአቶ በላይ ባለቤት ናቸዉ፣፣ አቶ በላይ የዓድዋ ሰዉ ናቸዉ፣፣ እንደሚባለዉም ልጆቻቸዉ ስዊድን ሃገር ዉስጥ ይኖራሉ፣፣ በእናታቸዉ በኩል የአቶ ኢሳያስ አጎት የሆኑት ከዓድዋ ተወላጅ ከሆኑት በአሁኑ ጊዜ ጀርመን ዉስጥ የሚኖሩ ወ/ሮ ዘዉዴ የሚባሉትን ወልደዋል፣፣ ከላይ በተገኘዉ መረጃ መሰረት የአቶ ኢሳያስ ኤርትራዊነት ኤርትራ መሬት መወለዳቸዉ ብቻ ነዉ፣፣የአቶ ኢሳያስ ባለቤትም ወ/ሮ ሳባ ሃይለ ይባላሉ፣፣ ኤርትራዊት ናቸዉ፣፣
ይህ የሚያስገርም ነገር ነዉ፣፣ለእዉነተኛ ኤርትራዉያኖችና በጭፍን ኢሳያስን በጭፍን ለሚደግፉ ይህ ግልጽ የሚሆነዉ ከብዙ ዘመናት በሗላ ነዉ፣፣አእምሮአችን ዉስጥ ስለ ኤርትራዊዉ ፕረዚደንት ማንነት ታሪክ አዳዲስ ነገሮች እየታወቀ ሲመጣ ስሜታቸዉ እንደሚለወጥ አያጠራጥርም፣፣ ኤርትራዎቹ አስመልክቶ ልጆቻቸዉንና ሌላም ዓይነት መስዋእትነት ለሰላሳ ዓመታት የከፈሉ ፣የኢሳያስ ዉሸትና ተግባር በጣም አስነዋሪ፣ የክፍለዘመኑ የእዉነት ታሪክ ያለመሆኑ ቀስ በቀስ እየተረዱት እንደሚሄዱ እርግጠኞች ነን፣፣
እነኚህ ሰዎች ለሰላሳ ዓመታ ቤተሶቦቻቸዉ ይህንን አመጸኛ ሰዉየ ሥልጣን ላይ ለማቆት መስዋእትንት የከፈሉና የዉሸት የ ኤርትራዊነቱ ዜግነትበጭፍን ይደግፉ ነበር፣፣ ከዚህ በፊት አቶ ኢሳያስ ትግሬ ነዉ ያላልንበት ምክንያት ስለሟች ወላጆቹ ማንነታቸዉ በቂ መረጃ ስላልነበረንና ሕዝባችንን ባልተረጋገጠ ነገር ለማጣደፍ ወይም ስሕተት ነገር ላለመስጠት ስለፈለግን ነዉ፣፣ በጥብቅ ለማስገንዘብ የምንፈልገዉ ይህንን መረጃ የሰጡን ግለሰቦች ሰለ ኢሳያስ በቂ ዕዉቀት እንዳላቸዉ ስለቤተስቡና ዘመዶቹ በቂና ምስጢራዊ ዕዉቀት እንዳላቸዉ እናዉቃለን፣፣ በዚህ ጉዳይ ላይ ጥርጣሬ ላላቸዉ ሰዎች በዚህ አጋጣሚ ለሁሉም ኤርትራዊያኖች የራሳቸዉ ጥናት አካሂደዉ ድምዳሜ ላይ እንዲደርሱ እንማጸናለን፣
ለኢሳያስ ተከታዮች አስቸጋሪ አማራጮች፣-
አንዳንድ የኢሳያስ ታማኝ ተከታዮች ኢትዮጵያዊያንን እንደ ጠላቶቻቸዉ ያዩዋቸዋል፣፣ በሚያሳፍር አባባል “ከአጋሜ ወይም ከድሆች ካልሰለጠኑ ኢትዮጵያዊያን ጋር ምንም ግንኙነት ለማድረግ እንደማይፈልጉ ይናገራሉ”፣፣ እንደዚህ ያሉ አስመራ ዉስጥ ወይም በስደት ሌላ ሀገር ዉስጥ የሚኖሩ “ስልጡን” ኤርትራዊያን ምንም እንኳ ጥቂት ቢሆኑም ራሳቸዉን እንደሃብታሞችና ስልጡኖች ይቆጥራሉ፣፣ ከትግራይ የሚመጡ “አጋሜዎችም”ይንቃሉ፣፣ እነኚህ አንዳንዶቹ ኤርትራዊ ያልሆኑ ያለ ፅዳት ስራ ወይንም እንደ ቤት ስራተኛነት እና ግምበኛነት ያለ የስራ መስክ የሆኑት በጠቅላላዉ ኤርትራዊ ሊሰራዉ የማይፈቅደዉን ስራ መስራት እንዳለባቸዉ ያምናሉ፣፣ አንድ ትግሬ ወይም ኢትዮጵያዊ የኤርትራ ፕረዚዳንት ይሆናል ብሎ ማስብ ዘበት ነዉ፣፣ ኢትዮጵያዊ ዜጋ እንዳያስተዳድረን ብለን አይደለም ወይ ሰላሳ ዓመት የተዋጋነዉ!? ይላሉ፣፣
ኤርትራዉያኖቹ ከኢትዮጵያዊያኖቹ ልዩ ፍጡር ናቸዉ ብሎ ለማለት፣ እንደቻይና ወይም እንደበርሊን ግንብ እንዲገነባ የሚፈልጉ ወይም አጋሜዎችንና ያልሰለጠኑ ድሃ ኢዮጵያዊያኖችን የሚንቁ ታማኝ የኢሳያስ ተከታዮች፣ አሁን ይህ አረመኔ አምባገነን በእርግጥ ኤርትራዊ አለመሆኑና ትዉልዱ ትግሬ/ኢትዮጵያዊ መሆኑን ሲረዱ ደንግጠዉ ተሸማቅቀዉ መሪነት እንደማይገባዉ ይረዳሉ፣፣
ኤርትራዊያኖች አዲስ ጅምር ለማድረግ ስለ ኤርትራዉ ፕረዚደንት መመለስ ያለበቻዉ ጥያቄዎች፣-
ከላይ ከተባለዉ አንፃር ቢያንስ ሚከተሉትን ጥያቄዎች መመለስ አለባቸዉ፣፣ (1)የኤርትራ ፕረዚዳንት ለምን የትግራይ/ኢትዮጵያ ትዉልድ እንዳለበት እያወቀ በጠቅላላ የ ኢትዮጵያ በተለይም የትግራይ ጠላት ሆነ?ለምን በእናቱ እና በአባቱ በወላጆቹ አገር ጦርነት አካሄደ? (2)ለምን ዋሽቶ የትግሬይ/ኢትዮጵያ ታሪክ መስረቱን ደልዞ ንፁሕ የኤርትራ ደም ካላቸዉ ዜጎች የበለጠ የኤርትራዊነት ብሔረተኝነት አሳየ? (3) ለምን ትግሬ/ ኢትዮያዊ የሆነዉ ኢሳያስ የሰላም ድልድይ ከመሆን ይልቅ ለራሳቸዉ ጥቅም ቅኝ ገዢዎች የከፋፈሏቸዉ የኤርትራ እና የኢትዮጵያ ሕዝቦች በማጋጨት አፋጃቸዉ? (4)የሃገራቸዉን ነፃነት ለማስከበር አኩሪ ታሪክ ያስመዘገቡ የራሱ የሆኑ ወገኖቹ የትግራይ እና የኢትዮጵያ ሕዝቦች ለምን ያፍርባቸዋል? (5) ለምን የራሱን መሰረት እንደሌለዉ ይቆጥራል? (6) ኤርትራዊያኖች የሰላሳ ዓመትመስዋእት ለምን ለአንድ ሰዉ ጥቅም ተብሎ የተከፈለ ከሆነ ለምን ተከፈለ? (7) ኤርትራ እና ኢትዮጵያኖች በመከባበር ወንደማማችነታቸዉ ከማጠንከር ይልቅ ለምን በኢሳያስ ሰበብ ደም ተፋሰሱ?ለምንስ ጦርነት ተመረጠላቸዉ? (8) የኢሳያስ ቤተሰቦች ለምን ስለ ትዉልዳቸዉ እዉነቱን ከመናገር ዝምታን መረጡ?ለምን ቤተሰቦቹ አኩሪዉ የትግራይ/ኢትጵያዊ ህዝበ አካል መሆናቸዉ ለመናገር ይፈራሉ? (9) የኢሳያስ ቤተሰብ ለምን የጥንቱን የአክሱምን ስልጣኔ ኢትዮጵያዊ ባህልና ታሪክ ይክዳሉ? (10)ብዙዎቹ ኤርትራዊያኖች ወደፊት የሃገራቸዉ ልማት መሰረት ኢትዮጵያ መሆኗን እያወቁ ኢትዮያን ለሰላሳ ኣመታት ተዋግተዉ ይባስ ብሎ ደግሞ ይልቁንም በ1991 እንደገና ለምን ዉግያ ዉስጥ በመካፈል ብዙ መስዋዕት ከፈሉ? (11) ኤርትራዊያን ጊዜያቸዉና ዕድሜአቸዉ ተጠቅመዉ ለሰላምና ለእድገት ከማዋል ይልቅ ከወንድመማቾች ጦርነት ምን ፋይዳ ይገኝበታል ብለዉ ለምን ራሳቸዉን አይጠይቁም?”””
በማለት ዶ/ር ፍስሃጽየን መንግሥቱ እና ጓደኞቹ ከላይ የተመለከታችሁት በጣም አስደናቂ ትንተና እና ብዙ መልስ የሚሹ ጥያቄዎች አቅርበዋል፣፣ እንግዲህ የሰሞኑን የኢሳያስ አፈወርቂ ቃለ መጠይቅ ስለ ኢትዮጵያ መቆርቆር እና “ኤርትራ” የምትባል “ልዩ አገር” መሆኗን እና ከእንግዲህ ወዲህ ስለ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ታሪካዊ/ባሕላዊ/ፖለቲካዊ/ማሕበራዊ ጉዳይ እና በኢትዮጵያዊያን በኩል ሊነሳ የሚችል ማንኛዉም ሕጋዊ ጥያቄ እንደማይኖርና “የተዘጋ ምዕራፍ” በማለት የሰጠዉ የቃለ መጠይቅ መልሱ ይታወሳል፣፣ ኢሳያስ ስለራሱ ማንነት ለሰላሳ ኣመት ሲዋሽ ሲያደናግር ቆይቷል፣፣ ትግሬነቱ/ኢትዮጵአዊነቱ እንዳይታወቅበትም ከኤርትራኖቹ በላይ ኤርትራዊ ሆኖ በመቅረብ “ሕዘብ ከሕዝብ የሚያጋጩ ዉሳኔዎችና ትንኮሳዎች በመመርያ ደረጃ እና ጸረ ኢትዮጵያ/ትግራይ የሆኑ እርምጃዎችን ሲወስድ እንደቆየ የታወቀ ነዉ፣፣ በተለይም ጸሃዎቹ እንደሚሉት “ግማሽ ትግሬ -ግማሽ ኤርትራዊ”ከሆኑት ጋሻ ጃግሬዎቹ ጋር ተባብሮ የኤርትራን ሕዝብ አሳስቶ ለስልጣን ሲል በኢትዮጵያ እና ሕዝቧ ላይ ከፍተኛ ደባ ከመፈጸሙ በላይ (ልክ የአክሱማዊዉ “ከሃዲ” የወልደ አብ ወልደማርያም ፈለግ በመከተል) ሁለቱ ሕዝቦች የተለዩ ሕብረተሰቦች አድርጎ በመስበክ ከፍተኛ የደም መፋሰስ እንዲካሄድ ምክንያት ሆኗል፣፣
ኢሳያስ ኢትዮጵያዊነቱን ሊጠላ ወይም ሊደብቅ የቻለዉ ለራሱ ብቻ የሚታወቅ ምክንያት ቢኖረዉም፣ ጸሃፊዎቹ እንደገለጹት አልፎ አልፎ ኢሳያስ በሕሪያቶቹ እንዳእስስት ሲለዋዉጥ ይታያል፣፣ ደስ ሲያሰኘዉ -እኛ ከሌሎቹ በተለይም ከትግራይ ሕዝቦች በብዙ መልኩ የተሳሰርን ነን ሲል፣ ሌላ ጊዜ ከጣሊያን ሃገር የተላኩ ሃገር እና ንብረት የሚዘርፉ የፋሽስቶች ዱርየዎች “ያሰመሩበትን የዉሸት ድምበር”እና “ከፋፋይ ፖለቲካ”በመቀበል የምድሪ ባሕሪ ሕዝቦች “ኤርትራዊያኖች” እንጂ “ኢትዮጵያዊያኖች” እንዳልሆኑ ይሰብካል፣፣ ይህ ደግሞ በብዙ ንግግሮቹ የተገለጹ ናቸዉ፣፣ በበለጠ ግን ጸሃፊዎቹ በሚከተለዉ ግልጽና አጭር አገላለጽ እንዲህ ሲሉ ይናገራሉ “ኢሳያስ በዙርያዉ ያሉትን አንዳንድ ግለሰቦችን የምናወግዝበት ምክንያት እዉነተኛ ማንነታቸዉን ስለሚደብቁና ይህንን ማንነት ለመደበቅ ሲሉ “ጨካኝ ሆነዉ” ዉጤቱ ሞትና ዉድመት በሆነ የማያባራ ጦርነት ዉስጥ ሕዝቡን አስገብተዉ ለስቃይና ለዉርደት መዳረጋቸዉ ነዉ፣፣ ዘግናኙ የኢሳያስ የጦርነት ሱስ፣ የችግር የዉድመት፣ እንዲሁም የራሱን እውነተኛ ማንንት የታሪክና የባህል ከሃዲነት ተምሳሌት ነዉ፣፣ የማያጠራጥር ነገር ቢኖር ኢሳያስ ሁልጊዜ የሸፍጥ ልምድ ያለዉና በግድያ የሚኖር ግለሰብ ነዉ፣፣”ሲሉ ስለ ኢሳያስ ማንነት ገልጸዉታል፣፣ እንግዲህ ኢሳያስ በኤርትራኖች ዓይን ማንነቱን በእንዲህ ሲገልጹት አንዳንድ ኢትዮጵያዉያን ዜጎች ወደ ኤርትራ ምድር በመዝለቅ የ የእርሱን እርዳታ በመሻት ወይንም የኢሳያስ ሰብአዊነት በበጎ ሲሰብኩ መስማት አብዛኛዎቻችሁ ምንኛ እንደሚያሳዝናችሁ መገመት አያዳግትም፣፣ እንኚህ ሰዎች፣ ለማንኛዉም ከኢሳያስ የሎጅስቲክ እርዳታ በማግኘት፣ኢትዮጵያ ዉስጥ ካለዉ ሌላኛዉ የታሪክ አተላ ከሆነዉ የአሜሪካና የዓረቦች ቅጥረኛ የደደቢቱ መንጋ “ከወያነ ትግራይ”ነጻ ለማዉጣት የሚታገሉ ዜጎቻችን ናቸዉ በማለት እቅዳቸዉን በበጎ የተነሳሱበት ነዉ እንኳ ብንል፣ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ ጉዳይ አሁን ባለበት ሁናቴ፣ ኢትዮጵያም የባሕር በሮቿን ተነጥቃና አስነጥቃ ይቀጥል ከተባለ ፣ ያዉም ኢሳያስ የዚህ መርህ ቀንደኛዉ አራማጅ መሆኑንና ጉዳዩም “የተዳፈነ የወደፊት እሳት”እንደሆነና ፣ ኢሳያስ የሚያክል አረመኔ የብዙ ሺህ ሰዉ ኢትዮጵያዊ ህይወት ለሕልፈት የዳረገ ጸረ-ኢትዮጵያ መሆኑን እያወቁ አስመራ ድረስ ሄደዉ “ወያነ ትግራይ”ብሎ ራሱን የሚጠራ ሌላኛዉ “የትግራይ ሻዕቢያ”ለመጣል ወታደራዊ ትጥቅና ስልጠና እንዲረዳቸዉ ለመማጸን እየተሰባሰቡ ናቸዉ እየተባለላቸዉ ያለዉ የግንቦት 7 (ዜናዉ እዉነት ከሆነ) እና ሌሎቹ ኢትዮጵያዉያን ወንድሞቻችን ከዚህ አረመኔ በምን መልኩ እና አስከ የትኛዉ ርቀት ሊያታግላቸዉ እንደሚችል አስካሁን ድረስ ለኔ ግራ የገባ እንቆቅልሽ ነዉ፣፣ ለማንኛዉም ጊዜ ደጉ ነዉና ሁሉም አስኪ በትዕግስት እርምጃቸዉን እንመለከት እያልኩ፣ ኢሳያስ አፈወርቅ ኢትዮጵያዊነት ዜጋነቱ ብቻ ሳይሆን የካደዉ የኢትዮጵያ በሕል ምግብና አኗኗርም ሲያጣጥል ተዘግቧል ብየ ቀደም ሲል የጠቀስኩላችሁን ጉዳይ ለማስታወሻችሁ (for your file) ይሆን ዘንድ- ለምሳሌ እንጀራ እና አስፓጌቲን በማወዳደር እንጀራ የ ያልሰለጠኑ ህዝቦች ምግብ ሲል አስፓጌቲ ደግሞ የሰለጠኑ ህዝቦች ምግብ በማለት የኢትዮጵያን ባህልና ሕዝብ ለማሳነስ በመሞከር እራሱን ከኢትያዊነቱ ለማስራቅና ለመሸፈን ያላደረገዉ ደካማ ጥረት እንደሌለ ካሁን በፊት ከአንዱ ከፈረንሳይ ጋዜጣ ጋር ያደረገዉ ቆይታ ጠቅሼ ልሰናበታቸወሁ፣፣ ከዚህ በታች የተገኘዉ ጽሑፍ በትሁትነታቸዉ የሚመሰገኑ ለኢትዮጵያዉያን ቀና መንፈስ ያላቸዉ የሆኑት ኤርትራዊዉ ምሁር ፕሮፌሰር ተስፋጽየን መድሃንየ “Towards Confederation in the Horn of Africa” በተባለዉ አዲሱ መጽሓፋቸዉ በገጽ 137ላይ ከፈረንሳይ ቋንቋ ወደ እንግሊዝኛ ተተርጉሞ “በሪፖርተር እና በኢትዮጵያ ፈረስት ድረገጾች” ላይ ታትሞ የነበረዉን ኢሳያስ ከፈረንሳይ ጋዜጦች ጋር ያደረገዉ ቃለ መጠይቅ እንዲህ ሲሉ አቅርበዉታል፣፣
“… Similar to such an incorrect view of history is disdain for Ethiopian cultures and traditions, which are also shared by Eritrea. The propaganda of the cadres of the regime occasionally denigrates the traditional ways of Ethiopian life of Ethiopian life, which is unwittingly disparaging towards Eritrean tradition as well. President Isayas himself is known to have made some vulgar and primitive comments in this regard. In an interview with a French journalist, he bellitted the cultural ways of life- e.g-, traditional homes and staple food-, which he associated with backwardness. He also sneered at Ethiopia’s “evolutionary and traditional” process of development. In the same breath, he expressed admiration for things European such as villas and spaghetti, which he regarded as evidence of modernity-seemingly concedering Italian colonial rule of Eritrea as a “revolutionary” process. (30. Fabiene Le Heuerou, “The Birth of Eritrea” (Interview with Isayas Afewerki-English translation). The Reporter (Addis Abeba- December 8, 1999), in (Ethiopiafirts.com-Dec, 1999) In effect, the president was contending that Eritrea was more advanced and more modern than Ethiopia. After all, in the words of the president, “the Italians have put the foundations on which the Eritrean identity was built by way of transforming the society economically, politically, culturally and socially.”31 (Ibid) To the Ethiopians, this remark was both foolish and nauseating. By it President Isayas distinguished himself as “the first man to praise colonialism, especially facist Italy’s style”.(32)(Getahun gebre-Amlak “In Issayas Landl, Wonders never End, (Ethiopiafirst.com) Dec.30,-1999.) Actually his hypothesis on cultural and modernity was ridiculed by Ethiopian commentators, some of whom stressed in satirical language (at which they are very good) that no matter how Europeanised (a’ la Isayas) Eritrea may be, it is no match for backward Ethiopia. (33) With reference to President Isayas’ remark an Ethiopian commentator wrote- “When Isayas finishes eating his spaghetti to complete his metamorphoses into the likes of his Western masters and joins the club of high tech warriors (being facetious here) Ethiopia shall still whip Eritrea with only spear and arrows.”(M.Azene- May 2000). It was a good example of the ‘we are special people’ syndrom” expressed by a leader who “lives in total delusions” (34) (Getahun Gebere-Amlak- 1999). Such contemptuous views of Ethiopia history and culture, pose obstacles to co-operation and association. Remarks of the kind made by president Isayas lead some Ethiopians to oppose confederation arguing that Eritreans are racist, hate Ethiopia and still love Italy. Undoubtedly, a few Eritreans need to be advised to exercise due care lest they express arrogance towards Ethiopians.} Tesfatsion Medhanie- (Towards Confederation in the Horn of Africa- (P.137, 138, 139) ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር! ጌታቸዉ ረዳ www.Ethiopiansemay.blogspot.com