Tuesday, July 13, 2021

የተደማሪ አምበጣዎች መሪ አብይ አሕመድ ከሠልጣን ይውረድ! ለሰላማዊ አመጽ የጥሪ ድምፅ!! ጌታቸው ረዳ Ethiopian Semay 7/13/2021

 

የተደማሪ አምበጣዎች መሪ አብይ አሕመድ ከሠልጣን ይውረድ!

ለሰላማዊ አመጽ የጥሪ ድምፅ!!

ጌታቸው ረዳ

Ethiopian Semay

7/13/2021



መግቢያ፡

በነዚህ ሁለት ነጥቦቸ ልጀምር።

ያልታጠቀ ሚሊዮን ሕዝብ ለጠላት እንዲጋለጥ አብይ አሕመድ ተዋጊ ሰራዊት ወደ ሗላ እንዲያፈገፍግ አድርጓል። ስለዚህም ትሪዝን (ክሕደት) ተፈጽሟል።

የአማራ ክልል ሥራ አስፈጻሚ ተብየው “የኦሮሙማዎቹ ባርያ” ከሰጠው ወቅታዊ መግለጫ ውስጥ አንድም የረባ ነጥብ አላስቀመጠም። ሠራዊቱ ለምን ከኮረም እና አላማጣ እንዲያፈገፍግ እንደተነገረው ለጌቶቹ የጠየቀበት ነጥብ አላስቀመጠም። ለምን? ባለመጠየቁ የሴራው ተባባሪ ነው።

8 ወር ሙሉ ጦርነት ሲካሄድ አብይ አሕመድ የትግራይ ገበሬ እርሻው እንዲያርስ በሚል ያ ሁሉ ጀግና ተዋጊ እና አዋጊ ኮለኔሎችን አስማርኮ እና አስገድሎ ሰራዊታችን ከትግራይ እንዲወጣ አደረገ። የተዋጉ አዋጊ መኮንኖች “አብይ እንደከዳቸው አድምጠናል” ። አብይ በሰራው ሴራ ከመቀሌ ሲወጣ ተቃዋሚ ወያኔዎች ታፍነው እንዲጠፉ ተደረገ።፡አሁን ደግሞ የአማራን ማሕበረስብ ለተጨማሪ ጥቃት እንዲጋለጥ ከኮረም፤ ከአላማጣ ጦሩ እንዲወጣ አዝዞ የአካባቢው ኗሪ በትግራይ ታሊባኖች “ጥርስ” እንዲታኘኽ ተደረገ፤ የቀረውም ሸሸ። ኢትዮጵያዊ ፓርላማ ቢኖር ኖሮ አብይ በስቅላት ይፈርደው ነበር።

ተቃዋሚ ተብየው ማፈሪያም፤ ምርጫ የሚባል ቀልድ አትግቡ ስንል አብይን አስመርቀው ለዘላለም አስገዙን። አብን የሚባል “ሚዲዮክር” ድርጅት ሕዝብን ለአመጽ ማስነሳት አልቻለም። ድሮም አሁንም!! አማራ የነ ደመቀ መኮንን 30 አመት መጫወቻ ሆነ። አሁን መደረግ ያለበት “አማራ ማሕበረሰብ ሞት የማይቀርለት ዕጣ ከሆነ” እራሱን ከሞት ለማዳን የነ ደመቀ መኮንን መንግሥት አልገዛም ብሎ አመጽ ማንሳት ቀዳሚና አንገብጋቢው አጀንዳ መሆን አለበት። ምክራችንን ስሙ! ኢሕዴን እስካለ ድረስ የአብይ ኦሮሙማዎቹ እና የትግራይ ታሊባኖች አማራውን ከማጥፋት አይቦዝኑም።

ሞት ተበይኖብሃል ስለዚህ ለሰላማዊ አመጽ አሁኑኑ ተነስ!

አመሰግናለሁ

ጌታቸው ረዳ