Monday, November 9, 2020

ጦርነቱን አስመልክቶ የተለያዩ ንዑስ ርዕሶች እንመልከት፡ ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay ኢትዮ ሰማይ) 11/10/2020

 

 

 

ጦርነቱን አስመልክቶ የተለያዩ ንዑስ ርዕሶች እንመልከት፡

ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay ኢትዮ ሰማይ) 11/10/2020

1ኛ-የውጭ አገር ጣልቃ ገብነት

2ኛ፦በሃይል ወደ ትግራይ የተጠቃለሉ መሬቶችን ወደ ነበሩበት ስለ መመለስ

1ኛ- በማስታረቅ ሰበብ የውጭ አገር ጣልቃ ገብነትን በሚመለከት

29 አመት የአማራ ሕዝብ የዘር ጭፍጨፋና የክርትያኖች መታረድ ያላሳሰባቸው የውጭ አገር የዜና ማሰራጫዎች፤ የውጭ አገር ዲፕሎማቶችና የአሜሪካ ኮንግረስ አባላት ትግራይን ለመገንጠል እንዲያመቸው “ከመከላከያ የጦር መሳሪያ ክምችት” ላይ ዘመናዊ መሳሪያዎችን ለመቀማት እሳት የለኮሰን ቡድን ለማስቆም እየተደረገ ባለው ፍልሚያ ውስጥ “የኮለኒያሊስቶች ምላሳችውን” መሰንዘር ጀምረዋል። ሩዋንዳን የሚያክል የዘር ፍጅት የሚያስንቅ ዛሬ በኢትዮጵያ ውስጥ እየተፈጸመ ስላለው ወንጀል አንድም ነገር ሳይሉ ዛሬ ደርሰው የሰላም መልዕክተኞች መስለው ስለ ጦርነቱ ማስቆም መለፍልፍ ለቀጠናችን አስበው እንዳልሆነ አንባቢዎቼ እውቁት።


ስለዚህ አያገባችሁም በልዋቸው። ይልቁንስ እውነት የሕዝብ ደህንነት የሚያሳስባቸው ከሆነ ‘የዘር ጭፍጨፋ ባደረጉት የወያኔ መሪዎች እና አገር እንመራለን ብለው ያለ ሕዝብ ይሁንታ  ሥልጣን የተቆጣጠሩትን የብልጽግና/(ኦሆዴድ) መሪዎች ለአማራና ለክርስትያኖች መታረድና መፈናቀል ተጠያቂዎቹ “ሽመልስ አብዲሳ፤ አብይ አሕመድና መሰሎቹ” ወደ ዓለም አቀፍ ፍርድ ቤት እንዲጠየቁ ኮለኒያሊስቶቹ የሚረዱበት መንገድ ካለ ይህንን ጥያቄ አጸፋዊ መልስ እንዲሰሙት ማድረግ ያስፈልጋል።


2ኛ፦በሃይል ወደ ትግራይ የተጠቃለሉ መሬቶችን ወደ ነበሩበት ስለ መመለስ በሚመለከት፤

ይህ ርዕስ ባለፈው ጠቅሸዋለሁ። በጉለብት ተነጥቀው ወደ ትግራይ ትግርኚ ምስረታ የተጠቃለሉት የጎንደርና የወሎ ለም መሬቶችና ኗሪዎች በዚህ ጦርነት በቁጥጥር እየዋሉ ያሉ እነዚህ ወረዳዎችና ከተሞች በማንኛውም ምክንያትና የሰላም ዕርቅ ድርደር “ሰበብ” አብይ አሕመድ መልሶ ለትግራይ እንዳይመልሳቸው ካሁኑኑ በግልጽ አማርኛ እንዲነገረው ያስፈልጋል።

ወያኔ ቅርቃር ውስጥ መግባቱ አይቀሬ ቢሆንም አብይ አሕመድ አስተማማኝ መሪ ስላልሆነ መጨረሻም ባድሜ ላይ መለስ ዜናዊ እንዳደረገው የካሃዲ ውሳኔ ዛሬም በአጋጣሚ በሃይል ወደ ትግራይ የተወሰዱ የወልቃይትና የወሎ መሬቶችና እዛው ውስጥ በአማራነታቸው ምክንያት “የቀን ሙያተኞች ሆነን ኩንታል እንኳ ተሸክመን ስሙኒ ላለማግኘት የነገድ ልዩነት ይደረገብን ነበር” ብለው የዳንሻ ከተማ ትንናት በቁጥጥር ሲውል ኗሪዎቹ የሰጡት ቃለ መጠይቅ መሰረት ግፍ ስለተፈጸመባቸው በእነዚህ ኗሪዎች ላይ አብይ አሕመድ ስሜት ስለማይሰጠው መልሶ ለትግሬዎች በመመለስ ክህደት ይፈጽማል የሚል እምነት አለኝ። ለዚህ ነው ጦርነቱ ሲጀምር ታስታውሱ እንደሆነ በጻፍኩት ጽሑፍ የአማራ ሲቪል ሚሊሺያዎች ወደ ጦርነቱ ቅድሚ እንዳትሰለፉ ወደ እናንተ ከመጡባችሁ ብቻ እራሳችሁን ለመከለካል ተዋጉ ካልሆነ “የወታደሩ ስራ ለወታደሩ ስጡት” ምክንያቱም በሗላ ደማችሁ ፈስሶ የምትይዝዋቸው ቦታዎች መልሶ በድርድርና ሰላም ሰበብ ለወያኔዎች ሊያስረክብ ይችላል ብየ ጽፌ ነበር። ያንን አይሆንም የሚል ሰው ካለ ይንገረኝ።

 ይህ ብቻ ሰሳይሆን ወደ አስመራ ሮጦ ለኢሳያስ የገባለትን ለወዳጅነቱ መሰረታዊ ምክንያት የሆነቺውን ባድሜን ለኢሳያስ ያስረክበዋል። ይህ ቦታ ቢሰያስረክበውም ኢሳያስ ቦታውን በሰላም ማስተዳደር ይችላል ወይ የሚለው ጥያቄ ግን አብይ ጥያቄ ነው። በዚህ ፍልሚያ ኢሳያስ እጁ ካስገባ የራሱንም ሥርዓት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ይናጋል። በሗላም አብይ ሲወገድ ጦርነት ይኖራል። ምክንያቱም አብይ የባድመና አከራካሪ ቦታዎች በመተባበር ሰበብ በኤርትራ ወታደሮች እንዲይዙትና ወያኔዎችን እንዲዘጋለት ይፈቅድለታል። ያኔ ውጣ የሚለው ሃይል አይኖርም።

ዞሮ ዞሮ ወያኔ ቅርቃር ውስጥ ገብቶ ወደ “የሽምቅ ውግያ” መግባቱ ስለማይቀርና ቀጠናው ወደ አደገኛ ሥርዓተ አልባነት ስለሚገባ “በመጨረሻም” አብይ አሸናፊነቱን ካረጋገጥ በሗላ ልፍስፈስና ሥልጣን ጥመኛ መሆኑና እንዲሁም አስታማማኝ መሪ ስላልሆነ፤ ሕዝብ ካስጨረሰ በሗላ የራሱን ስም በገናናነት አስመዝግቦ የጎንደርና የወሎ መሬቶች እንዲሁም የባድመ መሬቶችን መልሶ እንደሚያስረክባቸው በእርግጠኛነት እንግራችሗለሁ። በዚህም ብዙ የሰላማዊ ሰልፎችና ውጥረቶች አገሪቷ ታስተናግዳለች። አማራዎቹ ከጀግናው አሳምነው ጽጌ ሞት በሗላ ጠንካራ መሪ ስለሌላቸው በዚህ ጉዳይ የአማራ መሪዎች የተለያየ መስመር በመያዝ ይከፋፈላሉ። ይህ ሲሆን አብይ አሕመድ በለመደው መንገድ ያዳክማቸዋል።

አመሰግናለሁ’

ጌታቸው  ረዳ (Ethiopian Semay)