Monday, August 19, 2019

በሰይጣን ግዛትም ሥላሤዎች አሉ – እንተዋወቃቸው፡ – ወልደ ማርያም ዘገዬ (posted at Ethio Semay)


በሰይጣን ግዛትም ሥላሤዎች አሉእንተዋወቃቸው፡ወልደ ማርያም ዘገዬ (posted at Ethio Semay)
በፈረንጅኛው Trinity ባማርኛው ሥላሤ አብን (the Father) ወልድንና (the Son) መንፈስ ቅዱስን (the Holy Spirit) ይይዛል፡፡ በምሥጢረ ሥላሤ ትምህርት ሥላሤዎች አንድም ሦስትም ናቸው፡፡ አብ ወላዲ፣ ወልድ ተወላዲ፣ መንፈስ ቅዱስ ሠራፂ በሚል አገባብ ይታወቃሉ፡፡ ይህ እንግዲህ በሥነ መለኮት ወይም ቴዎሎጂ ሃይማኖታዊ የዕውቀት ዘርፍ የሚተነተን ነው፡፡
እስካሁን ባለው የሥነ መለኮት ትምህርት ፀላዔ-ሠናያት የሆነው ሣጥናኤል እምቅድመ ፍጥረተ አዳም ወሔዋን ዘመን  ጀምሮ ከእግዚአብሔር መንግሥት በጠባዩ መማረጥ ሳቢያ ከገነተ ሰማይ ወደ ደይነ ምድር መወርወሩንና መሰል ሰብኣዊና ረቂቅ ፍጡራንን ወደ ግዛቱ ከመጠቅለሉ ውጭ እንደ እግዚአብሔር መንግሥትሥላሤየሚባል ሥነ ተፈጥሮ የለውም፡፡ ሰይጣን በልማድ እንደምናውቀው የክፋት ምንጭና የብልግናዎች ሁሉ ቁንጮ መሆኑን ነው፡፡ ሣጥናኤል፣ ጋንኤል (ሲበዛ አጋንንት) ዲያብሎስ፣ ሉሲፈር ወዘተ. በሚባሉ የክትና የሠርክ ስሞች የሚታወቀው ሰይጣን የሞት፣ የስደት፣ የጠብ፣ የግጭት፣ የስቃይ፣ የመከራ፣ የርሀብ፣ የበሽታ፣ የዕልቂት፣ የድርቅተምሣሌትና ዋና መንስዔ እንደሆነ የሁላችን ግንዛቤ ነው፡፡ አንዳንድ ሰዎች የሰይጣንን ኃይል ለተለያዬ ዓላማ ይጠቀማሉ፡፡ ገንዘብና ሥልጣን ለማግኘት ሲባል ከትንሽ ገንዘባዊ መስዋዕትነት እስከሰው ነፍስ ጭዳነት ለሰይጣንና አጋፋሪዎቹ በማቅረብ ብዙ የሀብትና የሹመት ደረጃዎችን የሚወጡ እንዳሉ ይታወቃል፡፡ የሁሉም መጨረሻ ግን አያምርም፡፡ አንድ መዋቲ ሰው ደግሞ በሰይጣን ከሚያልፍለት በእግዚአብሔር ደጅ በድህነት ኖሮ ቢሞት ይሻለዋል፡፡ የሰው ወርቅ አያደምቅም፡፡ …. ሰይጣን ብድርን ሲያስከፍል በነፍስ እንጂ በቁስ አይደለም፡፡ ሰዎች ይህን ቢረዱ ከሚታየው የሰው ለሰው መጨካከን ከዕጥፍ በላይ ይቀንስ ነበር፡፡
ከዚህ ተፈጥሮው በመነሣትም በግብርም በአስተሳሰብም እርሱን የሚመስሉ ፍጡራን ከሰዎችም ሆነ ከሌሎች እንስሳት ሲገጥመንሰይጣንእንላቸዋለን፡፡ ዓለማችን እጅግ ብዙ የሰይጣን ምሣሌዎችንና ቀጥተኛ ወኪሎችን አስተናግዳለች፡፡ እነዚህ ሰይጣናት (devil-incarnates) የንጹሓን ዜጎችን የዕለት ከዕለት ሰላም ከማወክ አልፈው ለበርካታ ጦርነቶችና ግጭቶች መንስኤ በመሆን በሚሊዮን ለሚቆጠሩ የዓለማችን ዜጎች ዕልቂት ዋነኛ ምክንያት ሆነዋል፡፡ ከነዚህ ሰይጣናዊ ሰዎች ሂትለርን ከጀርመን፣ ሙሶሊኒን ከጣሊያን፣ መለስን ከኢትዮጵያ እዚህ ላይ በዋቢነት ብንጠቅስ አይበዛባቸውም፡፡ እነዚህ ከሞታን ሠፈር የምናስታውሳቸው የአጋንንት ወኪሎች ናቸው፡፡ የዓለማችን ቅርጽ እንዲህ ማስጠሎ የሆነው የነዚህሰዎችአሉታዊ ሚና ጎልቶ በመውጣቱ ነው፡፡ ጊዜያቸውም ስለሆነ፡፡
በአሁኑ ወቅት በሕይወት እየኖሩ ሰይጣንን በሚያስከነዳ ክፋትና ተንኮል ሀገርንና ሕዝብን እንደዶሮ እየገነጣጠሉ የሚገኙ የሰይጣን ልጆች ደግሞ በየሀገሩ አሉ፡፡ እንደኢትዮጵያ ግን በሌሎች አይበዙም፡፡ ኢትዮጵያ መንግሥትም ባለቤትም ስለሌላት በተለይ በአሁኑ ወቅት እነዚህ የአጋንንት ውላጆቸ እንደልባቸው እየፈነጩ ይታያሉ፡፡ የዘመንን ፍልስፍናዊ ቅኝት በሚገባ መጠቀም ማለት እንደነሱ ነው፡፡ ከነዚህ መካከል ዋና ዋናዎቹና ይህን ካምፕ በፊታውራሪነት የሚመሩት የሚከተሉትኢትዮጵያውያንናቸው፡፡
1.    ሕዝቅኤል ጋቢሣ (ፕሮፌሰር ይሉታል)
2.    በቀለ ገርባ
3.    ጃዋር ሞሀመድ

እነዚህ ናቸው በሀገራችንየሰይጣን ሥላሤዎች ናቸውያልኳቸው፡፡ አንድም ሦስትም እየሆኑ ሀገርንና ሕዝብን ለማጨራረስ ቀን ከሌት  ያለ አንዳች መታከት የሚባዝኑት የኢትዮጵያ ቀንደኛ ጠላቶችን ማወቅ ተገቢና ወቅታዊም ነው፡፡ እነሱም ይህን አያጡትም፡፡
ሕዝቅኤል ጋቢሣ ሌላው ሁሉ ቀርቶ የአብራኩ ክፋይ የሆነች ልጁ ከዩኒቨርስቲ በቅርቡ ተመርቃ በኢትዮጵያ ባንዲራ ስትደምቅበት የሰይጣን ሽንት የሆነው እርጉም አባቷ ግን የሚሠራው ሁሉ የልጁን ሀገር ድራሽ ማጥፋት ሆነ፡፡እበት ትል ይወልዳልይባላል፡፡ የዚህን የሰንበት ጽንስ ዕኩይ ተግባር እኔ ልቅርና አባቱ ሰይጣን ራሱ ዘርዝሮ አይጨርሰውም፡፡ የሚናገረውና የሚጽፈው ሁሉ እንዳንዳች ነገር የሚቆንስና የሚገለማ ነው፡፡ በምን ቀን ይህን መሰሉ የአጋንንት መንፈስ እንደተጣባው አይታወቅም፡፡ ዘመድ አዝማድ ቢኖረው የሰውዬው ደዌ ብዙዎችን ሳይበክልና የጋራ መኖሪያችንን ሳያወድም ክፍል ተቆጥሮለት ወደ ታወቀ ጠበል ወስዶ ማስጠበል ነበር፡፡
በቀለ ገርባ የሚሉት በሽተኛ ደግሞ አለ፡፡ ከሰው ልጅ ተፈጥሮ በማፈንገጥኦሮሞ ወንድ ከኦሮሞ ሴት ውጭ ከተኛ ዘሩን እንዳጠፋ ይቆጠራል…” ብሎ ሲናገር ቅንጣት የማያፍር ጥቁር ሰይጣን ነው፡፡በኦሮምኛ ካላናገሯችሁ ምንም ዕቃ አትሽጡላቸው፣ነጋቲ ቡላበሏቸውየሚልና ግም ነጭ ጭቃ አናቱ ላይ ተሸክሞ የሚዞር በሰው አምሳል የተፈጠረ የለዬለት ጋኔን ነው፡፡ ለስሙ የቋንቋና ሥነ ጽሑፍ መምህር ነው፡፡ ግን የቋንቋና ማኅበረሰብን ዕድገትና ዘፈቀዳዊ ግንኙነት አያውቅም፡፡ ቋንቋ ባሕርያዊ እንዳልሆነም የማይረዳ ገልቱ ነው፡፡
ጃዋር እንኳን ከሰይጣንም በላይ ነው፤ ሰይጣን ቢሞት የሚተካው አልጋ ወራሹ ጃዋር መሆን አለበትሰይጣን የሚሞት ከሆነ፡፡ እንደሚታማውና መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ይህ ጋንኤል ኢትዮጵያን ለመበታተን እንደ ግብጽ ባሉ ፀረ ኢትዮጵያ ኃይሎች የተመለመለና በብዙ ሚሊዮን ዶላር ተገዝቶ ሥራውን በስኬት እየተወጣ ያለ ጎልማሣ ነው፡፡ ይህ ሰው እስካለ ድረስ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን ገና ብዙ ፍዳ ያገኛቸዋል፡፡ (ይህ አባይ የሚሉት ወንዝ ምነው ጋና ወይ ካሜሩን ውስጥ በሆነ! ጠቅሞ ላይጠቅመን አሣራችንን አበላን አይደል?) የተከፈተለት ሚዲያ ከፌዴራል መንግሥት በግልጽም በድብቅም ድጋፍ እንደሚያገኝ ከመነገሩም በተጨማሪ የላኩት ኃይሎች ስለገንዘብ ምንም እንዳያስብና እንዳይጨነቅ ዋስትና የገቡለት ይመስላል፡፡ ለዚህም ሣይሆን አይቀርም እንደኢሳት ያሉ ጣቢያዎች ነጋ ጠባ የገንዘብ ዕርዳታ በመለመን ሥራ ሲጠመዱ የጃዋር ኦኤምኤን (OMN) ግን እንኳንስ ገንዘብ ሊለምን ለሠራተኞቹ የሚከፍለው ደሞዝ ራሱ ከማንም ጋር የማይወዳደርና ሥራ አስኪያጁ ጃዋርም ጥይት በማይበሳው እጅግ ውድ መኪና የሚንፈላሰስ፣ ወፍ ከሰማይ በሚያወርዱ ሥልጡን ኮማንዶዎች ከሀገሪቱ /ሚኒስትር በበለጠ የሚጠበቅና ተሰሚነቱና ተፅዕኖውም ከማንም በላይ የሆነው፡፡ ይህን ሁሉም ያውቃል፡፡ ክርስቲያን ታደለ የሚባል የአብን ምክትል /መንበር(?) ወዶና ፈቅዶ ያልተወለደበት አማራነት ወንጀል ሆኖበት በጎሣዊ ማንነቱ ሰበብ ከበርካታ መሰሎቹ ጋር ተይዞ ሲታሰርና ሲሰቃይ ጃዋር ግን ሲዳማን ከደቡብ ለመገንጠል በግልጽ ዐዋጅ ዐውጆ ለብዙ ሕዝብ ዕልቂትና ለንብረት ውድመት ዋነኛ ተጠያቂ መሆን ሲገባው ማንም ዝምቡን እሽ አላለውምየሚገርም የነገሮች ሂደት፤ በታሪክ የሚያስጠይቅ ልዩ ኦህዲዳዊ የአስተዳደር ዘይቤ፤ በታሪክ ማኅጸን የተረገዘው ህግ ሲወለድ እስከሞት ሊያስቀጣ ለሚችል ከፍተኛ ወንጀል የሚዳርግ በዘረኝነት ላይ የተመሠረተ ሸውራራ ኦነጋዊ መንግሥት የተተከለበት አስደናቂ ዘመን፡፡ ይህ የሚያሳየው የፌዴራል መንግሥት ተብዬው የኦህዲድ ባለሥልጣናትም  ጃዝ ብሎ ጃዋርን በላከው ኃይል ተፅዕኖ ሥር መውደቃቸውን ነው፡፡ እንጂ በአንድ ሀገር ውስጥ የተለያየ ሕገ መንግሥትና አስተዳደር ያለ በሚያስመስል ሁኔታ አማራውን እያጠቁ ኦሮሞው አገር ምድሩን እንዲቆጣጠርና ጽንፈኞች ያሻቸውን እንዲያደርጉ ፈረሱም ሜዳውም ባልተለቀቀላቸው ነበር፡፡ ይህ አሣፋሪ ዘመን ማለፉ አይቀርም፡፡ ሲያልፍ ግን ብዙ ጠባሳ እንዳይጥል አእምሮን ከአሁኑ በቅጡ መጠቀም ይገባል፡፡ በዱባ ጥጋብ የሚፈነጥዝ ዘረኛና ሤረኛ ሁሉ ቆም ብሎ የማሰቢያ ጊዜው አሁን መሆኑን መረዳት አለበት፡፡እዩኝ፣ እዩኝ” “ደብቁኝ፣ ደብቁኝ እንደሚያስከትል ከወዲሁ ካልተረዳን ዛሬ ትናንትን እንዳልሆነ ሁሉ ነገም ዛሬን አይሆንምና ቢያንስ ለመጪው ትውልዳችንና ለልጆቻችን በማሰብ ከፈረሰኛ የስሜት ደንገላሣ ወጥተን በጥሞና እናስብ፡፡ እነደቻሣና ኩምሣ እየሰማችሁኝ ነው? ከነሐጎስና ገረግዚሃር ካልተማራችሁ ከማን ልትማሩ ትፈልጋላችሁ? ዕደጉ እንጂ! እኛምወፌ ቆመችእንበላችሁ፡፡ እንደቀጨጫችሁ አትቅሩብን፡፡ የናንተ ማደግና መለወጥ ለጋራ ቤታችን ወሳኝ መሆኑን ተገንዘቡ፡፡
ስለ አጋንንታዊ ሥላሤዎች ይችን ታህል ካወራን ለዛሬ ይብቃኝ፡፡ እምነታችንን አጥብቀን እንራመድ፡፡ ለአጋንንት መድኃኒቱ የእምነት ጽናት ነውና በፈጣሪ ብቻ እንታመን፤ ለርሱም ችግራችንን እንንገረው፡፡ መሥራት ያለብንንም እንሥራ፡፡ ዝም ብለን ግን አንቀመጥ፡፡