Wednesday, December 7, 2011

የኢትዮጵያን ሰማይ ዘገባ በዚህ ሳምንት


To see the page/font with a wider range, please press the key Ctrl and + sign. To view the page/font with a narrow range, please press the key CTRL and _ sign.

የሚታየው የወያኔ ገበና ማህደር አዲሱ መጽሐፍ ለመግዛት $30.00 ዶላር ሲሆን ይድረስ ለጎጠኛው መምህር መጽሐፍ ደግሞ $25.00 ወይንም ሓይካማ የሚለው የትግርኛ መጽሐፌ ደግሞ $15.00 ዶላር ብትልኩ መጽሐፎቹን ማግኘት ትችላላችሁ።Getachew Reda P. O.Box 2219 San Jose, CA 95109 getachre@aol.com Phone (408) 561 4836

የኢትዮጵያን ሰማይ ዘገባ በዚህ ሳምንት
ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያን ሰማይ) www.Ethiopiansemay.nlogspot.com (getachre@aol.com)









በዚህ አምድ ትንንሽ ንኡስ ክፍሎች እና አንድ ትልቅ አርዕስት ይቀርባል።

1-     ለመፈርጠጥ አስቀድመው የተናዘዙት ጋዜጠኞች
2-     በአፍቃሬ ሻዕቢያው ኤሊያስ ክፍሌ እና በጸረ ትግሬ ቅስቀሳ የታወቀው የከረንት አፈይርስ ዲስካሽን ፎረም ተፈጠረ የተባለው ስምምነት/ትብብር (ግምባር)
 3     ታማኝ በየነ  ሰሞኑ በሰጠው የወያኔ አኬልዳማ መልስ በሚመለከት
 4     ግብረሰዶም ምርምራ በወያኔ ተቃዋሚ የፖለቲካ እስረኞች ላይ ስለመፈጸሙ ጉዳይ በሚመለከት
5-   የሟቹ ሳይንቲስት እጅጉ ቅጣው ንግግር (በሚቀጥለው ሳምንት የሚቀርብ ነው። አገራዊ ፍቅርን እና የኢትዮጵያዊ ኩሩ ማንንት የተሞላበት ንግግር ስለሆነ ተከታተሉት)
 ከኤርትራ በኩል እየተላኩ በግምቦት 7 በኩል ሽብር እየፈጠሩ ነው ብሎ ወያኔ ግንቦት 7ን ሲከስ “ግንቦት 7 እና ደጋፊዎቹ” ደግሞ “ውሸት ነው፤ የወያኔ ቲያትር ነው፤ እኛ የለንበትም” ሲሉ (በመግለጫው ደግሞ ወያኔ “መውጫ መግቢያ” እያሳጣነው ነው በርቱ ይበል እንጂ) ከወደ ኤርትራ ለ20 አመት የሰለጠኑ ሽምቅ ተዋጊዎች ሸዋ አከባቢ ይሁኑ ወሎ አካባቢ እያቆራረጡ ወደ መዲናዋ እየገሰገሱ ይሁን ባናውቅም። የት አንዳሉ ባናውቅም ለኢንተርኔት ምስጋና ይግባው እና  Raya Liberation Front (RLF) ወይንም  “Raya Rayuma” የተባለ ታይቶ ተሰምቶ የማይታወቅ አዲስ የራያ ነፃ አውጪ የተባለ “ጥይት ሳይተኩስ” “ጫካ ሳይወጣ” ከወያኔ ጋር አብሮ እየበላ እየጠጣ ወያኔን መውጫ መግቢያ አሳጥተነዋል። የሚል ደግሞ መጥቷል።
የወያኔ የኪነት ክፍሎች አብቶቡስ የገለበጠው እሱ መሆኑን እንዲሁም ወያኔው ኢያሱ በርሐን የገደለው ይሄው ድርጅት መሆኑን የሚቀባጥር “ቁጭ በሉ ላሞኛችሁ” የመንደር ወሬ ለአትላንታው የኢ ኤም ኤፍ ጋዜጠኛው ለመቶ አለቃ ዳዊት ከበደ ወየሳ ዜናውን እንድትዘግብልን ዜናውን ተቀበለን፡ ተብሎ በዛው ድረገጽ የተጻፈው ከሰማይ የወረደ ወያኔን መውጫ መግቢያ የሚያሳጣ ነፃ አውጪ ድርጅት አንደኔው በጉጉት እየተበቃችሁ ይሆን? ወይ ትጉዱ! አለ ትግሬ።
አይዞህ ተነስ፤ አንደ ሊቢያ እንደ ሶርያ እንደ ግብፅ ትግልህን አቀጣጥል ፤መስዋዕት ክፍል፡ እያሉ ሕዝቡን ላመስነሳት ሲጽፉ የነበሩ ብዕርተኞች/ጋዜጠኞች እና አሽሙረኞች ሁሉ አይዞህ ከጎንህ አለን፤ ተነስ፤ መስዋእት ክፍል በወያኔ አለንጋ አትበርግግ፤ እንደ ቦአዚዝ እራስህን አቃጥል” ሲሉ የነበሩ ጋዘጠጠኞች፡ ቦአዚዝን ተክቶ የመስዋዕትንትን አርአያነት በራሱ ሕይወት ፈርዶ በተግባር ባርበኝነት ያለፈው “የኔሰው” የተባለው ኢትዮጵያዊው “ቦአዚዝ” ብቅ ሲል አርአያነቱን ከመከተል እና ትግሉን ከማቀጣጠል ይልቅ “የወይን ጎማ እግሩ” ፋሽስታዊ አለንጋ ሲወዛወዝ አይተው እንደ ምጢጢ “ወፍ” ብር ብለው ከእኛው ከፈሪዎቹ መንደር የመደባለቃቸው ጉድ ምን ትሉታላችሁ?
የአውራምባው ዳዊት ከበደ ሲቢጀይ የተባለው ዓለም አቀፍ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች (?) ሽልማት ማግኘቱን ይታወቃል። ማሕበእነ ኤልያስ ወንድሙ (የጻሐይ አሳታሚ ድርጅት ባለቤት ሎስ አንጀለስ እና ምናልባትም “የሻዕቢያው ወዳጅ “ኤልያስ ክፍሌም ሳይኖርበት አይቀርም - በጠቋሚነት እና በማሕበሩ አባልነት አሉበት ይባላል።) እንግዲህ ዳዊት በ ‘ሲቢጄ’ አለም ዓቀፍ እውቅና አግኝቶ “በሲኤን ኤን” ጋዜጠኛዋ ቃለ ምልልስ ስያደርግ “ሲቢጄ” የተባለው ድርጅት ስለ እሚሰማው ሦስት ነገሮችን እንዲያብራራ ጠይቆት ነበር። ከመለሳቸው ሦስቱ ልጥቀስ

 1- “I can’t leave without the profession I have now”  2- “unless it becomes a matter of life and death, I will never leave Ethiopia” 3- “I am not an opposition. If I believe for the betterment of this nation, I will never hesitate criticizing whatever power…..This my ultimate…..”
ኢትዮጵያዊው ቦአዚዝ ተብሎ የተሰየመው የኔ ሰው ገብሬ ግን የጋዜጠኞቹን አይዟችሁ በርቱ፤ተነሱ መስዋእት ክፈሉ ቅስቀሳ እና የወያኔ አፈና እና የወንጀል ገበና እየተመለከቱ ራሳቸው በሞትና በሽረት ትግል አሳትፈው መስዋእት ሲሆኑ፡ ጋዜጠኞች ግን ሞት መጣ “በቃ!” እያሉ ሕዝቡን ለወያኔ ጥለንለት መፈርጠጥ ነው ያሉትን በተግባር አሳይተውናል። ይሄ “ሲ ቢ ጄ” የተባለው ቅራ ቅንቦ ምን የሚሉት መመዘኛ እያስቀመጠ ነው “ሽልማት” የሚለጥፍላቸው እኔ አልገባኝም። ዳዊት ቃሉን ስላከበረ እንዴት መውቀስ እንችላልን? “የሞት የሽረት ነገር ከመጣ አገሬን ለቅቄ እፈረጥጣለሁ አለ። አደረገው፡ ለምን እንውቀሰው። ቢያንስ አስቀሰድሞ ነግሮናል። ገጠር ውስጥ ያለቺው ታላቋ እህቴ “ዝሞተ ሞተ እዩ ምቕዳም አይግበርካ” ትላለች። የሞተ ሞተ ነው፤ ለሞተው ይብላልኝ እንጂ….የሞተው ሰው  አያድርግህ እንጂ ፤/ለመሞት ግምባር ቀደም አይድርግህ እንጂ ….”። አውነት ነው። የሞተው ይብላልኝ እንጂ አስቀድመው የተናዘዙትማ እንዴት አንውቀሳቸው?
2-    በአፍቃሬ ሻዕቢያው ኤሊያስ ክፍሌ እና በጸረ ትግሬ ቅስቀሳ የታወቀው የከረንት አፈይርስ ዲስካሽን ፎረም ተፈጠረ የተባለው ስምምነት/ትብብር (ግምባር)
 የሰሞኑ ጉድ በተለይም ባንዳንድ ኢትዮጵያውያን  አፍቃሬ ኢሳያስ አፈወርቂ/የሻዕቢያ አፈቀላጤዎች እና  በጸረ ትግራይ ፓልቶክ መሃንዲሶች (ኢካድ ፎረም/ኢትዮፕያን ካረንት አፈይርስ ዲስካሽን ፎረም) መሃል ተደረገ የተባለው የትግል ጥምረት ለተቃዋሚ ራዲዮ ጣቢያዎች ማጠናከሪያ እንዲሆን “በየወሩ ቋሚ የገንዘብ ዕርዳታ” እንዲደረግ፤ እንዲሁም  በወያኔ ሱቅ ቤቶች ምግብ ቤቶች ሕዝቡ እንዳይገበያይና እንዳይመገብ፤አፍቃሬ ኢሳያስ አፈወረቅ በሆነው የኢትዮጵያን ሬቪው ባለቤት በ“ኤሊያስ ክፍሌ” የሚመራው (አል ማርያም፤አክሎግ እና የመሳሰሉት ሰዎች አሉበት የሚባለው የቦይ ኮት መርሃ ግብር ዘመቻ አቅድ አቀነባባሪ ቦርድ) ተደረገ የተባለው የዘመቻው ስምምነት አንብበናል።
በእዛው ምሽት በካረንት አፈይርስ የተደመጡ ካንዳንድ ታዳሚዎች (በጸረ ትግራይ ሕዝብ ቅስቀሳ የታወቀቺው “ሙያየ ምስክር” የተባለቺው ሴት ነበር ዝግጅቱን የመራቺው) የቀረቡ አጸያፊ እና አስፈሪ ንግግሮች አንዲሁም





ባንድ አስተያየት ሰጪ ግለሰብ "በስመ ትግሬ ሁሉም ወያኔዎች ናቸው እየተባሉ በማይገባ እርምጃ በትግሬ ወገኖቻችን ላይ የተሳሳተ እርምጃ እንዳንወስድ በቂ ጥንቃቄ መደረግ አለበት የሚለውን፤ በተለይ “ኤልያስ ክፍሌ መረጃ ሲያቀርብ “በስማ በለው” መረጃ እየተቀበለ መለጠፉን የተለመደ የድረገጹ ባሕሪ መሆኑን አንድ ከስዊዘር ላንድ ኗሪ የሆነ የብርቱካን መዲቅሳ ደጋፊ “በዛው ከተማ ስትጋበዝ የወያኔ ደጋፊ የሆነ እገሌ ነው የጋበዛት በማለት ስሜን አጥፍተኸዋል” ስለዚህ አሁንም እንደዚያ ያለ ስህተት እንዳትደግም “ጥንቃቄ አድርግ” ብሎ የሰነዘረው ጠቃሚ ሃሳብ አልቀረበም። ሌላው ይህ እንዲህ ያለው ግለሰብ ጥንቃቄ አድርግ ሲል ቆይቶ “እንደ እኔ ፍላጐት ቢሆን ኖሮ የወያኔ ንበረቶች/መኖርያቤቶች በእሳት ማቃጥል እምርጥ ነበር” ያለውን- የወያኔ ንብረት/ቤት ለማቃጥል ሲባል “ህጻናትን ወላጆቻቸውን፤ፖለቲካቸው ውስጥ ያልተሳተፉበት ዘመዶቻቸው ተቃጥለው እንዲሞቱ የቅስቀሳ ንግግር ለምን ተቆርጦ ለኤልያስ የተጠየቁ እና እሱ የመለሳቸውን ብቻ ቀርበው ጤነኛ ውይይት እንደነበር ተመስሎ ቀረበ?

 በወቅቱ ይህ አደገኛ ቅስቀሳ ሲሰነዘር “ለምን እንዲህ አልክ” ብላ የመድረኩ መሪዋ ማረም አልቻለችም? ምክንያቱም በእራሷ አንደበት (በዛው ወቅት ለደ/ር አክሎግ ቢራራ ስትናገር “የናንተን አቋም አላውቅም እንጂ ለእኔ ትግሬ በሙሉ ወያኔ ነው፡ ያለችበትን ብቻ ሳይሆን ከሦስት ሳምንት በፊትም በሌላ ፓል ቶክ ክፍል ገብታ “ከዛሬ ጀምሮ እኔ ዘረኛ ነኝ” “ጸረ ትግሬ ነኝ” ያለቺበትን ንግግር ካንደበቷ የወጣውን ንግግር በድምፅ መቅጃ ተቀርጿል እና ከአንዲት ናላዋ የዞረባት ዘረኛ ሴት ስነ ስርዓት ለማስከበር ብቃቱም ባሕሪዋም አይፈቅድም እና አድምጠነዋል።
በወያኔ ደጋፊዎች ንግድ ላይ ማዕቀብ መጣል አስፈላጊ ነው ተገቢም ነው። ነገር ግን “ቤታቸውን /ንብረታቸውን ማቃጠል የሚሰጠው ውጤት ምን እንደሆነ እና የሚያስከትለው የፍጅት መዘዝ ሳያጤኑ በስሜት የሚሰነዘር የፓል ቶክ ስካር “ቁጥር እና ተገቢው ሕጋዊ ገደብ ቢደርግበት ይሻላላል”። የኔ ወንድም ገና በሎጋ እድሜው ጀምሮ ጫካ በመግባት የወያኔ ታጋይ ሆኖ ታግሏል። በቅርቡ ቦታው ልነግራችሁ የማልፈለገው ኢትዮጵያ ከተማ ውስጥ እሱ እና ሌሎች ትግሬዎች በሚኖሩበት መንደር ላይ በጀርባ ተደብቀው እሳት በመልቀቅ የወንድሜ መኖርያ እና ሌሎች የትግሬ ቤቶች በቃጠሎ ወድመው መኖርያ አጥተው የትም ወድቀው ነበር። ይታያችሁ ወንድሜ  የተማረ አይደለም ይህ ወጣት ወንድሜ ትምህርቱን ትቶ ወያኔዎችጋር ተደባለቀ። የሚያውቀው ትምህርት “ወያኔ” እንጂ ሌላ “ትምህርት” አያውቅም። ትንንሽ ልጆቹ እና ምንም የማያውቁ እሱን ለመጠየቅ የመጡ ዘመዶቻችንም አብረው ለእሳት ሲዳረጉ አብሮ የሚጐዳ ነገር በህሊናችሁ ፍረዱት።  ስለዚህ በቢራ ሞቅታ ወይንም በዘረኝነት ባሕሪ እንዲህ ያለ አስነዋሪ ንግግር በየፓል ቶኩ ከሚሰነዝሩ ጸረ ትግሬ ፓል ቶክ ክፍሎች እና አፍቃሬ ኢሳያስ አፈወርቂ መካካል ተደረገ የሚባለው ትብብር የሚገኝ ዕርዳታ በኔ ትርጉም “እርዳታ ይደረግልን ብለው የሚጠይቁ የራዲዮን ባለቤቶች ቢቀራቸው ጥሩ ነው። የትግርኛው አባባል
“ኣቕሓ ስኢንና ሓቢርና
በላዕና እምበር መዓዝ ዓዕሩኽ ኮይንና”
“ዕቃ በማጣታችን አብረን በላን እንጂ  መቸ ጓዶች ሆንን”  ቢሉንም
መልሴ  (ንብር ነቢራ ዕውር ተመርዒያ)  “ ያ ሁሉ ረዢም ጊዜ ባል ስታማርጥ ዓይኑ ደቃቃ ነው፤ ዓይኑ ሸውራራ ነው፤ ወገቡ ወልጋዳ ነው… ስትል ኑራ ኑራ ዕውር ተዳረች” (ዓይነ ስውራን ጓደኞች አሉኝና አስቀድሜ ይቅርታ እጠይቃለሁ ይህ የጥንት ምሳሌ በመጠቀሜ)።
ኑራችሁ ኑራችሁ “ዘረኞች ጋር እና አፍቃሬ ኢሳያስ ሻዕቢያ” ጋር መሞዳመድ እና ገንዘብ መቀበል ክብር ይቀንሳል ነው የኔ የዘወትር ምክሬ። ከአፓርታይዷ ደቡብ አፍሪካ ጋር የንግድ፤የትግል፤የዲፕሎማሲ እና ማሕበራዊ ግንኙነት ሲያደርጉ በነበሩት ላይ ውግዘት ሲደርስባቸው የነበረበት ምክንያት “ደቡብ አፍሪካ እንደ ተቋም “ዘረኛነትን” የሚያራምድ ተግባር እና ቅስቀሰቀ በማካሄዱ ነው። ወያኔን የምናወግዝበት ምክንያትም የሄው ነው። አሁንም በየፓል ቶኩ የ“ወያኔ/መለስ” አባሎችን ከማውገዝ ይልቅ በእኛ በትግሬዎች ላይ የሚደረግ ግልጽ የጥላቻ ዘመቻ ከሚያካሂዱ ክፍሎች ዘንድ በመሄድ “ቃለ መጠይቅ ማድረግ፤ግምባር መፍጠር፤የገንዘብ ዕርዳታ መቀበል….” የመሳሰሉት ተግባሮች እናወግዛቸዋለን።
3ኛ- ታማኝ በየነ ሰሞኑ በሰጠው የወያኔ አኬልዳማ መልስ በሚመለከት
 ታማኝ ጀግኖቻችን ከምንላቸው ደፋር ጀግና፤ ጥሩ ተሟጋ ች አንዱ ነው። ግን ትግሬዎች ሲመስሉ “ሕማቕካ ዎሆይ ይበልካ” (ወንድምህ (ድክመትህ) እንደ አውድማ ከብት “ዎሆ!” ብሎ ቢቆጣጠርልህ አትጥላው’። ይባላል። እኔ በታማኝ ያለኝን እርምት ወይንም ስለሱ አንድ ባልኩ ቁጥር እሱ ወይንም ሌሎች የሚከፉ ካሉ፤ በክፋት እንዳልሆነ አውቁልኝ። እሱ ስለ እኔ እንዳለው ትዕቢት ሳይሆን እኔ ስለሱ ያለኝ አክብሮት እንጂ ትዕቢት/ንቀት የለብኝም እና ነው።
አሁን ወደ እርምቱ ልግባ። ሰሞኑን ወያኔ ከሽብርተኞች ጋር ግንኙት አድርገዋል፤ የተለያዩ ቅስቀሳዎች ለማድረግ ይዣቸዋለሁ ወዘተ… በማለት የያዛቸው ሰዎች (ፖለቲከኞች….) በሚመለከት “አኬልዳማ” በሚል ርዕስ  አገኘሁባቸው ያለውን የምርምራ ውጤት በተንቀሳቃሽ ምስል ለመረጃ ብሎ ያስተላለፈውን ማሕደር ተመልክተናል።
እያንዳንዳችን የየራሳችን ግንዛቤዎች አሉን። ሁሉም የየራሱ ግምገማ መያዙ እንደተጠበቀ ሆኖ ታማኝ ያቀረባቸው ግምገማዎች ሁላችንም አድምጠነዋል። የወያኔ ሽብር ምን ያህል የተለጠጠ እንደ ሆነ ከጫካ ባሕሪው ጀምሮ በዘመዶቻችን ላይ ያደረሰው ሽብር የምታውቁት ይመስለኛል። በምጽሓፍም በቃለ መጠይቅም ያቀረብኳቸው መረጃዎች ተመለክቱ።
የኔ ችግር ወያኔ ሽብርተኛ ነው አይደልም በሚለው አይደለም። ወያኔ ሽብርተኛ ነው፤ፋሺስት ነው….የፈለጋችሁት የጋኔል ስም ብትሰጡት የሚገባው ነው። ችግሬ ግን ወያኔ ስለምንቃወም  በኢትዮጵያ ምድር ውስጥ ከ36 በላይ ተሰነዘሩ የተባሉ የሽብር ተግባሮች ወያኔ እንጂ ሌላ ድርጅት አልፈጸመውም እየተባለ ለዛውም “ዊኪ ሊኪ” “አሜሪካ ኤምባሲ የተላለፈው የመረጃ ራፖር” “ሲናኒሞስ” እንዳስተላለፈው መረጃ እያተባለ “ስማቸው የማይጠቀስ የፖለቲካ ተንታኞች እንዳሉት” እየተባለ እንደ መረጃ እየተወሰደ “ወያኔ” የቀነባበረው ያፈነዳው ቦምብ፤ ክርስትያኖች ወያኔ ያረዳቸው ያቀነባበረው ሴራ እንጂ ሌላ ጸረ ኢትዮጵያ ድርጅት/ሃይል የለም ወይንም እጅ የለበትም፡ እየተባለ ሌሎችን ሽብር ፈጻሚዎች ነፃ ለማድረግ የሚደረገው “በማውቅ አለማወቅ” (ለነሱ ልተው) በጣም አሳስቦኛል።ሽብር ፤ግድያ፤ቦምብ፤የጸሎት ተቋማት ማቃጠል፤ሰዎችን ማረድ የሚያከናውነው “ወያኔ” ብቻ ከሆነ እንደምንሰጋው ኢትዮጵያ ብዙ ጠላት የላትም  እና አገሪቱ ጠኔኛ ነች ማለት ነው።
ለምሳሌ ታማኝ ለ“አኬልዳማ” መልስ ሲሰጥ የመሰለውን አስተያየት ሰቷል። ችግር የለኝም። ችግር ያለብኝ አንድ ነገር ልጥቀስ። “እኔ ኦነግን ፈጸመው ከሚባልለት ድርጊት ነፃ ለማቀውጣት አይደለም” ይል እና የበደኖን የአማራ ሕዝብ እልቂት የሚያሳይ የፊል/የስዕል መረጃ ሲያቀርብ “ወያኔ ይህንን ዕልቂት ሲፈጸም አስተካክለው በካሜራ ይቀርጹት ነበር” ብሏል።አኔ ይህን አባባሉ ስህተት አለበት። ምክንያቱም እስካሁን ድረስ የተመለከተኳቸው መረጃዎች ወያኔዎች ያቀረቡት መረጃ በበደኖ አካባቢ “የ ኦሮምኛ ስም ያለው ገደሉ
አሁን ዘንግቼዋለሁ “ቁንድፍቱ” (?)” የሚገኝ ገደል ውስጥ ከገደሉ የተወረወሩ ሬሳ/ሰዎች ነብሳቸው በገመድ ተጐትቶ ሲወጣ እንጂ ከነ ነብሳቸው ሲገፈተሩ የሚያሳይ መረጃ አላሳየንም። እኔም ካሁን በፊት አላየሁም። ወያኔ የድርጊቱ ተጠያቂ መሆኑን አያከራክረንም። ኦንግም ከድርጊቱ ተጠያቂነት አያመልጥም (ኢሳቶች የዲማ ነገዎን “እኛ በዚያ አካባቢ አልነበርንም፤ ቁጥጥር አልነበረንም “ “አንዳንድ አበላቾቻን በግለሰብ ተነሳስተው አድርገውትም ላያደርጉትም ይችላሉ፤ እኔ እሱን አላውቅም….” የሚለውን የተምታታ ምስክርነትና ቃለ መጠይቅ እንደ መረጃ ለመናገር ቢቃጣቸውም፡ “ኦነግ እና የነጋሶ ጊዳዳ ‘ኦ ፒ ዲ ኦ’ ድርጅት ታጋዮች መካከል  ከእርስ በርስ የሴቶች ጡት መቆራረጥ እና የሰው የጭን ስጋ በቢላዋ እየቆረጡ በሃይል ወደ አፋቸው መጎራረስ (የነጋሶ ጊዳዳ መጽሐፍ (“ዳንዲ - የነጋሶ መንገድ” ያላቸው ሰዎች አንዳነበቡልኝ እና ከሰዎችም እንደተነገረኝ የኦነግ ታጋዮች በበደኖ ካባቢው እንደ ነበሩ ነው) እንደደረሱ እና ሁለቱም ድርጅቶች ባልታጠቀው የአማራው ሕብረተስብ ሰላማዊ ኗሪ የደረሰው ዕልቂት ተጠያቂዎች መሆናቸው መረጃዎቹ ናቸው።
ሆኖም ታማኝ እያለን ያለው፡- ኦነግን ‘ከወንጀሉ ነፃ ለማውጣት አይደለም’ ይበል እንጂ ከአንደበቱ ይፋ እየተናገረን ያለው ግን የሃውዜኑ ዓይነት የገብረመድህን ትረካ ነው። ወያኔዎች ድርጊቱ ሲፈጸም ካሜራቸው አነጣጥረው ነበር የዘገቡት ካለን “ወንጀሉ ሲፈጸም በካሜሬ እየቀረጹ እንደነበር ከሳያን ወያኔ በተባባሪነት በወንጀሉ ተከሳሽ ነው (ሌሎች ክፍሎች የፈጽሙት መሆኑን ፊልሙ የሚያሳይ ከሆነ)። ካልሆነ ድግሞ ድርጊቱ የፈጸመው ክፍል በመረጃው እስካሁን ድረስ ያየነውን “ሬሳ ከገደል ሲወጣ” እንጂ ፈጻሚው ማን እንደሆነ በፊልሙ አላየንም። ስለዚህ በወቅቱ ዲማ ነገዎ የማስታወቂያ ሚኒሰትር ስለነበር ፈጻሚዎቹ ሲፈጽሙት ፊልም አለ የሚል ከሆነ በጉግት እንጠብቃለን። ወይንም “ወያኔዎች” ከደሙ ንጹሕ ነን የሚሉ ከሆነም “ድርጊቱ ሲፈጽም” የተነሳ ክፍል ካለ ፊልሙ ለሕዝብ ይፋ በማድረግ ወያኔዎች ከዚህ ክስ ራሳቸውን ነፃ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
ይህ ሐተታ ሆነ ብየ የማቀርበው እጅግ አወዛጋቢ ነው የሚሉ ክፍሎች የጠራ ነገር ለማግኘት (“ትሪገር”) የተደባባቀውን መወነጃጀል ተንኩሶ ይፋ እንዲወጣ ይረዳ ዘንድ እንዲረዳን በማለት ነው።
ለነገሩ አልን እንጂ በኦነግ ወታደሮች እና ያካባቢ የኦነግ ቀበሌ ተጠሪዎች (ኦነግ በመንግሥት ጥምረት ውስጥ እያለ) አርሲ የተፈጸመው ጭፍጨፋ የወንጀሉ ተካፋዮች ስም ዝርዝር (አንዳንዶቹ አሜሪካ እና ካናዳ ተደብቀው በ ኦነግ ጥገንነት/ደጋፊነትበሰላም እየኖሩ ያሉትንም) ዝርዝር ሐተታ የተዘገበ ነውና “የግድ ኦነግ በበደኖ ተካፈለ አልተካፈለ” ከወንጀሉ ነፃ አይሆንም።
4ኛ - ግብረሰዶም ምርምራ በወያኔ ተቃዋሚ የፖለቲካ እስረኞች ላይ ስለመፈጸሙ ጉዳይ በሚመለከት፦
 አስኪ በዚህ ጉድ የተመለከተው Woyanne threatened to sodomize Debebe Eshetu’s family December 1st, 2011  By Elias Kifle በሚለው ርዕስ አንጀምር።እውነት እንደዚህ ዓይነት ድርጊት ተፈጽሟል? ቢፈጸምስ እንዲህ ያለ ጉድ እንደ ዜና ለሕዘብ ይፋ መውጣት ነበረበት? ትግሬዎች “ሸራፍ ስኒ መንፈሲ ጽዋ፤ ሸራፍ ዕትሮ መነፈሲ ስዋ” ይላሉ (ሸራፋ ጥርስ ነገር ያወጣል፤ሸራፋ ጋን ጠላ ያነፍሳል” ማለት ነው። በሌላ አባባል “ካብ ተዛራቢኡስ ደጋሚኡ (ከተናጋሪው ደጋሚው ይብሳል) ማለት ነው።
ኤልያስ እንዲህ ያለ ጸያፍ ነገር እንደ ዜና ማቅረቡ ብዙ ጉዳቶች አለበት። እንዲያ ብሎም አልተወሰነም አንዲህም ይላል; “Sodomizing opponents, which is foreign to Ethiopian culture, is a method that Meles brought from his country Yemen.” እኔ የማውቀው መለስ ዜናዊ ኢትዮጵያዊ  (ነግር ግን ባንዳ) እንጂ የመናዊ መሆኑን አሁን ለመጀመሪያ ጊዜ ነው እየሰማሁ ያለሁት። መለስ ዜናዊ እናቱ እና አባቱ የመናዊ መሆናቸው መረጃ ከላቀረበልን የዘገባው ተልእኮ ከሻዕቢያ ዘጋቢዎች የሚለይ ዘገባ አይደለም።
 
ይሄ ጉድ ደግሞ ተመልከቱልኝ “Victims of sodomy are extremely traumatized and that they are too ashamed to tell even those closest to them. In recent past, at least two prominent opposition politicians I know of who had been subjected to sodomy. I will not mention their names to keep their privacy. But in time, they themselves may be willing to talk about it in public so that the perpetrators face justice.”

ይህ ጉደኛ ዜናስ ምን ትሉታላችሁ? ሁለት የፖለቲካ ትላልቅ/ እውቅ መሪዎች በወያኔ እስር ቤት እያሉ ግበረሰዶም ተፈጽሞባቸዋል። ለክብራቸው ስል ማንነታቸው አልገልጽም፡፤ ነገር ግን ከጊዜ ብዛት እራሳቸው ሚስጢሩን ለማጋለጥ ፈቃደኞች ይሆኑ ይሆናል። ነው የሚለን ኤልያስ። ተፈጽሞ ይሆናል እንበል፡ እና ግን ኤሊያስ በምን ማሳመኛ ባሕሪው ነው ማመን የሚቻለው? ምናልባት ወያኔዎች ራሳቸው በተዘዋዋሪ ዜናው እንዲለጥፈው እና ተቃዋሚ መሪዎች ለወደፊቱ እንዲህ እንዳይፈጸምብን ፖለቲካውስጥ አንሰተፍም በማለት ሞራላቸው እንዲነካ እንዳይቃወሙት  ማስፈራሪያ እንዲሆን  የተሰራጨ የወያኔ ተንኰል ቢሆንስ? ኤሊያስ ብዙ የተሳሳቱ የዜና መረጃዎች ካሁን በፊት ይዘግብ እንደ ነበር የምታስታውሱት ነውና ሰውየው የሻዕቢያ በሽታ ልክፍት ስለተናወጠው ኢትዮጵያዊ ባሕሪ እና ባሕል ርቆታል። መነገር እና የማይነገር ባሕል ከመጤፍ አልቆጠረውም።
“ዚስ ኢዝ አሜሪካ፤ ዚስ ኢዝ ካናዳ የኢትዮጵያ ሰንደቃላማ ቢሰቀል ቢቃጠል ቢደበቅ ጉዳየ አይደልም” ሲለን የነበረው ከወደ ኦታዋ ካናዳ የሚኖረው ልጅ ተክሌ ተባለው የኢካዴፍ ድረ ገጽ ዋና አዘጋጅ እና የብርሃኑ ነጋ አቀንቃኝ ይህን አስመልክቶ የሚከተለውን በጣም አስነዋሪ ጥያቄ አቅርቧል

 “Even a year after Birtukan was released, we do not know anything about what happened to her inside the jail that made her admit the crime she did not commit, other than the solitary confinement. I am not underestimating the solitary confinement. I also do not believe that Birtukan made a confession of the crime she did not commit in front of a camera only because of a solitary confinement. Because based on the story we knew, Birtukan allegedly made the confession long time after she came out of solitary confinement. Since we have not heard anything from her, other than some of the fragments of minor evils she told us about on a couple of occasions, we can only guess or speculate what happened to her. If we succeed in convincing Birtukan to tell her story to the world, then that will be one more piece of evidence of the cruelties this TPLF/EPRDF commits, and it will put the TPLF on the defensive position. That will also help our heroes who are currently in jail to sustain them longer. In the absence of action from people who were subjected to horrific brutality inside TPLF jails, the remaining prisoners will slowly give up.
እንዲህ ያለ ኢትዮጵያዊ ስነ ምግባር የጐደለው ጋጠ ወጥ ወጣት ፖለቲከኛ አይቼም ሰምቼም አላውቅም። እኔ ጌታቸው ረዳ ብርቱካን መዲቅሳን  ባሳየቺው የፖለቲካ ድክመት ልቃወማት ብችልም ድክመቷን ነው እንጂ አሁን ይህ ስድ ግለሰብ የተፈጸመባትን የጨለማ እስር አሳንሶ እስር ውስጥ እያለች “…..” ሌላ ነገር ተፈጽሞባት ይሆናል እንጂ ላላደረገቺው ወንጀል ፈጽሜአለሁ ለማለት ባልበቃች ነበር ብሎ ክብሯን ለማንኳሰስ መሞከሩ እጅግ በጣም ኢትዮጵያዊነት የራቀው የጥያቄ ባሕሪ ስለሆነ እቃወመዋሉ።ሁላችሁም ይህ ያልበሰለ ወጣት አውግዙት። የህ ወጣት የተረገመ የኢትዮጵያ “ኩስ” ነው።

እንዲያ በሚለውም አልተወሰነም። እንዲህም ሲል ሌሎቹን ሁለት ታላለቅ የተቃዋሚ የፖለቲካ መሪዎች ተፈጸመባቸው የተባለው ግብረሰዶማዊ ጥቃት እነማን እንደሆኑ እንዲነግሩን ይወተውታል። ጉድ ነው! Elias also said in his remark that he would do the same if he is in Debebe’s position. I would also do the same if I were Birtukan or Debebe. However, I do not agree with Elias’s remark in our private email exchanged that “some people are criticizing me for even writing about Debebe Eshetu’s situation. Right now I want to focus on Woyanne, so I am trying to minimize controversial issues such as this.” I have two answers for that. First, these days, I do not understand why politician and activists fear to confront controversial issues head-on.” “It is in the best interest of our country and our politics for Birtukan and in a few moments Debebe Eshetu to tell us what made them say what they said. I can only assume that TPLF has brutalized them. However, unless the people who experienced the brutality tell us what exactly happened, Reyot, Eskindir, Andualem and Beqele, Olbana are next in line for the brutalization and subsequent confession of the crime theydid not commit.”…..” “Therefore, I appeal to Ms. Birtukan Mideksa, to speak out to the world what they did to her so that her testimony would be Olbana, Reyot, Eskindir’s and et al insurance …. “ 

ውድ ወገኖቼ፡ ይህ ጋጠ ወጥ ወጣት ብርቱካን እንድትነግረው የሚማጸነው እና ሌሎች  እስር ቤት ውስጥ አያሉ ሁለት የፖለቲካ ተቃዋሚ አውቅ ሰዎች ተፈጽሞባቸዋል እያለን ያለው  የግብረሰዶም ጥቃት (በሻዕቢያው ወዳጅ በኤልያስ ክፍሌ ውዥምብራም ዜና የተዘገበው) ጥቃቱ ቢፈጸምጸምባቸው እንጂ  “እንዲህ ጨለማ ቤት ውስጥ አመት ሙሉ ቢቀመጡም ያላደረጉት ወንጀል አድርገናል ብለው አያምኑም ነበር” ሲል ምን ያህል ስድ እና ኢትዮጵያዊ ባሕል እና ስነ ምግባር እየራቀው እንደሄደ መገንዘብ ትችላችሁ። ይህ ወጣት ብርቱካን ምን ጥቃት ደረሰብኝ ብላ ልትነግረው ነው የሚጠይቅ? ምን ጉድ ነው እያሰማን ያለው? እባካችሁ ባሕላችሁን አትናቁ። የሚነገር እና የማይነገር ጽያፍ እና ነውር ነገር ለይታችሁ እወቁ። ባሕላችን እና ነውራችን ከፖለቲካ ጋር አትደባልቁ። ይሄ ወያኔ የሚባል ስንት ግሳንግስ ሰብስቦ ነው ወደ ውጭ እየላከልን ያለው?  ወይ ዘመን!
  በሚቀጥለው ሳምንት
4ኛ--የሟቹ አገር ወዳድ አርበኛ የሳይንቲስት እጅጉ ቅጣው ንግግር አቀርብላሁ።