Tuesday, August 27, 2019

የኦሮሞ ልጆች የጫካ አገዛዝ ሕግ እና እናቶች በፖሊሶች የመደብደብ ጉዳይ ጌታቸው ረዳ የኢትዮ ሰማይ ድረገጽ አዘጋጅ 08/27/2019


የኦሮሞ ልጆች የጫካ አገዛዝ ሕግ እና እናቶች በፖሊሶች የመደብደብ ጉዳይ
ጌታቸው ረዳ የኢትዮ ሰማይ ድረገጽ አዘጋጅ
08/27/2019
ርዕሱ አሁን ለሚገዛን  ሥርዐተ አልባው የኦሮሞዎቹ ሥርዓት እንደሚስማማ ሰየምኩት እንጂ ርዕሱ “የጫካ ልጆች የአገዛዝ ሕግ” በሚል ርዕስ እንደ አገራችን ዘመን አቆጣጠር በ1995 ዓ.ም በገጽ 13 “ዜጋ” በሚባል መጽሔት አዲስ አበባ ካሳተምኩት ጽሑፌ የወሰድኩት ነው።

ይህ ተመሳሳይ ርዕስ የወሰድኩበት ምክንያት በጠቀስኩት አመተምሕረት አዲስ አባባ ከተማ ውስጥ በልደታ ቤተክርስትያን ምእመናን እና በወያኔው ፓትርያሪክ መካካል ከሕዳር 9/1995 ዓ.ም ጀምሮ የተፈጠረ ውዘግብና ግጭት አስመልክቶ የታየው የፖሊሶች ጭካኔ በማመሳሰል ትናንት አንድ ወዳጄ አንድ የጠገበ የአብይ አሕመድ የአዲስ አበባ ፖሊስ አንዲት አዛውንት ከልጃቸው ጋር ያለ ምሕረት እንደ አውሬ ምድር (እባብ) ራስ ራሳቸውን በዱላ ሲቀጠቅጣቸው የሚያሳይ ቪዲዮ ስመለከት ከላይ የጠቀስኩትን በልደታ ቤተክርስትያን ውስጥ የወያኔ ፖሊሶች (በ1995) ያሳዩት የጭካኔ እርምጃ በእኚህ አዛውንት እናት ላይ ያየሁት ግፈኛ ዱላ ስለታወሰኝ ርዕሱ እና ድርጊቱ ተመሳሳይ ሆኖ በማግኘቴ  “የጫካ ልጆች የአገዛዝ ሕግ”  ከሚለው ጽሑፌ በመውሰድ “የኦሮሞ ልጆች የጫካ አገዛዝ ሕግ እና እናቶች በፖሊሶች የመደብደብ ጉዳይ” (አብይ/ኦነግ)” ብየ ርዕሱን ለወጥ አድርጌ ተጠቅሜበታለሁ።


መጀመሪያ ትናንት አዲስ አባባ ከተማ በአንድ ጥጋበኛ የአብይ አሕመድ ፖሊስ ባልደረባ በእናት አዛውንት እና በልጃቸው ላይ ያወረደው በጫካ ሕግ የተመራ አስነዋሪ የድብደባ ግፍ ከመተቸቴ በፊት በ1995 ዓ.ም የታየው የልደታ ቤተክርስትያን ምዕመናን እና የጫካ ልጆች (የወያኔ) ፖሊስ ግፍ በመዘርዘር ሁለቱም ተመሳሳይነታቸውን ለማሳየት በመጀመሪያ ስለ ልደታ ምዕመናን ምን እንደተደረገ ላስታውሳችሁ። ከዚያም ወደ ዛሬው ወደ ኦሮሞዎቹ አስተዳደር እንመለከታለን።

ወደ ዝርዝሩ ከመግባቴ በፊት ባጭሩ የጭቅጭቁ መነሻ በሕዝቡ የተወደዱ እና የተከበሩ የልደታ አስተዳዳሪ የነበሩት ተነስተው በወያኔ ካድሬ አስተዳዳሪ ለመተካት (ከምክንያቶቹ አንዱ) በሃገረ ስብከት ጽ/ቤት እና በአባ ጳውሎስ (የወያኔ ፓትርያሪኩ) ትዕዛዝ ሲተላለፍ የልደታ ምዕመናን ውሳውን ፖለቲካዊ በመሆኑ አንቀበልም ብለው ተቃውሞ ባመሰማታቸው የወያኔው ፓትርያሪኩና የመለስ ዜናዊ አሽከር ፖሊሶች የደረጉትን ጭካኔ ባጭሩ እንዲህ ነበር።

መሳሪያ የታጠቀ ሃይል ቤተክርስትያኒቱን ወረራት። እንደ አንድ የጣሊያን ወራሪ ጠላት ወደ ውስጥ ቤተ መቅደሱ በመግባት በእናቶች እና አዛውንቶች ላይ ብትር መሰንዘር ጀመሩ። ሕዝቡ ለጸሎት አብርቶ  ይዞት የነበረውን ቅዱስ ጧፍ  እንደያዘ ነበር በፖሊስ ብትር እየተደበደበ ከቤተክርስትያኒቱ እንዲወጣ የተደረገው። ያ እንዳይበቃ ወታደሮቹ እየተንደረደሩ በእርግጫ እና በቆመጥ እየደበደቡ ሕዝቡን ከመሬት ላይ እየጣሉ በጫማቸው እየረገጡ ይደፈጥጡት ነበር። ከዚያ በላ ነበር ዜጋ በተባለው ወርሓዊ መጽሔት ላይ ያንን ዜና ስሰማ “የጫካ ልጆቹ የአገዛዝ ሕግ” በሚል የጻፍኩት።

በዚያ ጽሑፌ ላይ ትንሽ ላስታውሳችሁ። የጫካ ልጆቹ ሕግ ምን እንደሆነ ከታች እስከ ላይ ያሉት የሚመሩበት መመሪያቸው ጭካኔ እና ግፍ ስለሆነ ከተማ ላይ የሚፈጸሙት ግፍ አሁን ደግሞ የአማልከቶች ቤት ሳይቀር እንዴት እየደፈሩ እንዳሉ ተመለክቱ። ስል የሚከተለውን በወቅቱ ኢትዮጵያ ውስጥ ሆና የቪ ኦ ኤ ዘጋቢ የነበረቺው  ሔለን መሓመድ ያስተላለፈቺውን ዘገባ ጥቅስ ባጭሩ ጠቅሼ የነበረውን ዘገባ ላስንብበቻሁ እና ወደ ሕግ አልባው የኦሮሞዎቹ የነ አብይ አሕመድ ፖሊስ ያደረገው ግፍ እንመለከታለን።

“ሕዝቡ መጮህ ጀመረ፤ እያለቀሰ ስሞታውን ያሰማል።ርክክቡ ከተፈጸመ በላ ሁኔታው የተረጋጋ መሰለ። ከጥቂት ደቂቃ በላ ብረት ቆብ ያጠለቁ፤ ጋሻ ያነገቡ ፖሊሶች ወደ ቤተክርሰትያኒቱ ቅጥር ግቢ በሁለት መርሰዲስ ተጭነው በመግባት ሕዝቡ ሳይሆን ፖሊሶቹ ፀጥታውን አደፈረሱት። ሁለት ስቪል የለበሱ ግለሰቦች አንድ 16 አመት የሚሆነው ታዳጊ ወጣት ጠምዝዘው ሲደበድቡት አይቻለሁ።

ወጣቱ ራሱን ለማዳንና ለማስለቀቅ በሚታገላቸው ጊዜ አንደኛው ፖሊስ ከወገቡ ሽጉጡን በማውጣት ጭንቅላቱ ላይ ከመደገኑ ባሻገር በሽጉጡ መያዣ ጭንቅላቱን ፈጠፈጠው። ሌሎች 6 ፖሊሶች ተጨምረውበት በአጠቃላይ ለ’8’ ሆነው ታዳጊውን ወጣቱን በአሰቃቂ  ሁኔታ ከደበደቡት በላ፤ከሌሎች መሰሎች ጋር በመኪና  ጭነው ወረዳ ሃያ ሁለት ፖሊስ ጣቢያ ወሰድዋቸዋል።” የሔለን መሓመድ ዘገባ ለቪ ኦ ኤ አዲስ አበባ”።

እንዲህ ነበር የወያኔ ፖሊሶች ጭካኔ እስከ ቤተመቅደስ ድረስ እየገቡ እናቶችን አረጋውያንን ህጻናትን ሲደበድቡ ታሪክ የዘገባቸው። ዛሬ ደግሞ ትናንት እንድ የቅርብ ወዳጄ የላከልኝ ቪዲዮ-ተመለከትኩ። https://www.facebook.com/100035912120492/videos/142737860266617/ ሁኔታው አዲስ አበባ “ዋርካ ትሬዲንግ ሃውስ” በሚል የንግድ በራፍ ላይ ሁለት የታጠቁ ፖሊሶች (ኦሮሞ ፖሊሶች እንደሆኑ በስፋት ተነግሯል) አንደኛው ጋጠ ወጥ ፖሊስ “ጦር ሜዳ” ያለ እስከሚመስለው ድረስ በያዘው ክለሽንኮቭ ጠመንጃ ጥይት ወደ ሰማይ በመተኮስ ጀግንነቱን ለማሳየት በባዶ ሜዳ ላይ እና ባዶ እጁ ሆኖ ቆሞ ሲመለከተው በነበረው የአካባቢው ተመልካች ሕዝብ ፊት እየተወጣጠረ በኩራት ሲንጎማለል ይታያል። አንደኛው ጋጠ ወጡ ፖሊስ ደግሞ አንድ ታዳጊ ወጣት በካቴና ሁለት እጁን አስሮ መሬት ላይ ጥሎ  በዱላ ሲነርተው አጠገቡ የቆሙት እናት የልጃቸውን ያለ ሕግ መደብደብ አንጀታቸው አላስችሎ በሎአቸው በመቃወም ከድብደባው ሊያስጡልት ሲታገሉ ‘ጋጠ-ወጡ’ ፖሊስ እሳቸውን በመዳፈር ገፍትሮ ሊጥላቸው እና ሊደበድባቸው ሲሚከር እሳቸውም ልጃቸውን ለማስጣል ሲታገሉ ጋጠ ወጡ ፖሊስ እኚህን አያቱን የሚያክሉ አዛውንት እንት ሲያንገላታቸው ይታይል።

በጣም የሚያስደንግጠው ትዕይንት ያልተገሩት እና ያልሰለጠኑት የአብይ አሕመድ የጫካ ልጆች የኦሮሞ ፖሊሶቹ ጋጠ ወጥነት ያስገረምን ሳይበቃ እዛው ቆመው አካባቢውን ዙርየውን ከብበው ይህ ግፍ እና ድብደባ ሲፈጸም ቆመው የሚመለከቱ በጣም በርካታ ጎልማሶች ፖሊሱን ከመቃወም እና ልጁን ከድብደባ ከማስጣል ይልቅ ልጃቸውን ከመሞት ለማዳን ሲታገሉ የነበሩትን እናት “በሃይል ጎትተው ከልጃቸው በማስራቅ” ፖሊሱ በልጁ ላይ ተጨማሪ ድብደባ እንዲፈጸምበት ለፖሊሱ ዕድል በመስጠት “ተባባሪ ሆነው” መታየታቸውን ኢትዮጵያውን ዜጎች የዘቀጡ አሳፋሪ ማሕበረሰቦች ሆነው ያየሁበት አጋጣሚ ነው።

በዜግች ግብር ተሰብስቦ ደሞዙን የሚከፍሉት ተቀጣሪ ፖሊስ አንድን ዜጋ በካቴና እጆቹን ጠፍሮ ሲደበድበው እና አዛውንት እናቶችን ሲደብድብ ከዚያም አልፎ እንደ ጀብድ ተቆጥሮ ጥይት ወደ ሰማይ እየተኮሱ ሰላማዊ ሕዝብን የሚረብሹ በአፍሪካ መዲና የሚታዩ የጫካ ፖሊሶችን መቃወም ሕዝቡ እንዴት ያቅተዋል። ታስታውሱ እንደሆን ከ26 አመት በፊት ሎስ አንጀለስ አሜሪካ ውስጥ “ራድኒ ኪንግ” የተባለ ጥቁር በፖሊሶች ተከብቦ መሬት ላይ ጥለው እጆቹን በካቴና አስረው ያለ ምሕረት ሲቀጠቅጡት በታየው ቪዲዮ የተነሳ ጥቁሮች በንዴት ተነሳስተው የሎስ አንጀለስ ማዕከላዊውን ከተማ የሱቅ እና ንግድ እንዲሁም መንግሥታዊ ህንጻዎችን አንዳለ በእሳት እንዳጋዩት ይታወሳል። እንዳለመታደል ሆኖ ኢትዮጵያውያን ለ28 አመት አንደ አህያ የለመድነውን ድብደባ ከምንም ሳንቆጥር አናቶች ሲደበደቡ ልጆቻቸው አብረው ሲደበደቡ እያየን ያለ መቃወማችን ምስጢሩ ዛሬም ሊገባኝ አልቻለም።

የትግሬዎቹም ሆነ የኦሮሞዎቹ አፓርታይድ አገዛዝ አዲስ አባባ እና አካባቢዋ ጋጠወጥ ፖሊሰቻቸው አስማርተው አዲስ አባባን ልክ እንደ ሞንሮቪያ (ላይቤሪያ) የጋንጎች (ሞብ) አስተዳደር ሕዝቡ በስርዓተ አልባ ዘራፊዎች እና በሕጋዊ ታጣቂ ፖሊሶች እየተረበሸ የሰቀቀን ኑሮ እያሳለፈ ነው። ከሦስት አመት በፊት ኦሮሞ “ክልል” ውስጥ አንዲት አዛውንት  እናት ፖሊሶች ልጃቸውን ገድለውባቸው ሲያበቁ እናትየዋ በልጃቸው ሬሳ ጎን ቁጭ ብለው ሲያለቅሱ ማልቃሳቸው የተመለከቱ ጋጠ ወጥ ኦሮሞ ፖሊሶች እናትየዋን በዱላ መደብደባቸውን በ ቪ ኦ ኤም ሆነ በራሴው ባሳተምኩት መጽሐፍ በሰፊው በታሪክ የተመዘገበ ነው። ዛሬም በአፓርታይዱ አብይ አሕመድ ዘመን እናቶች በፖሊሶች መደፈራቸውን እና መደበብደባቸውን አልቆመም። አሳዛኙ ግን ተቃዋሚው እና ኗሪው ይህንን ግፍ እየተመለከተ አይቶ አንዳለየ የመሆኑ አስደንጋጭ እና አስገራሚ ምስጢር እንዴት እንፍታው? ፔቲሽን ማዘጋጀት የምትችሉ ሰዎች እባካችሁ ይህንን ግፍ ለአዲስ አበባ ፖሊስ እና ፍትሕ አሰፍናለሁ ብላ ለምታወራው የአብይ አሕመድ የፍትሕ ሚኒሰትርዋ ወ/ሮ ማዓዛ አሸናፊ ጽ/ቤትዋ ድረስ የተቃውሞ ደብዳቤ በመጻፍ በሁለቱ ፖሊሶች ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው አቤቱታችንን እንላክ።ይፈጸማል ወይ? ያ ሌላ ጉዳይ ነው። ግን ለታሪክ እናስመዝግብ። ሁላችንም የየበኩላችን ትንሽ ትንሽ ብንሰራ ግፉ እንዲህ ስር አይሰድም ነበር። በተልይም በፌስ ቡክ ያላችሁ እህቶችና በሴቶች መብት ቆመናል ለምትሉ የሴቶች ማሕበሮች የእናቶችን ግፍ ማስቆም ይጠበቅባችሗል። አብረን እንጩህ ! ድማጻችሁን አስሰሙ!! ቪዲዮውን ለመመልክት ይህንን በፌስ ቡክ የተለጠፈውን ይመልከቱ።
አመሰግናለሁ ጌታቸው ረዳ (ኢትዮ ሰማይ ድረገጽ አዘጋጅ Ethio Semay)