Wednesday, November 6, 2019

ሁላችሁም ጫ በሉና አድምጡኝማ! አምባቸው ደጀኔ (ከወልዲያ) (Ethio Semay ኢትዮ ሰማይ ድረገጽ የተለጠፈ)


ሁላችሁም ጫ በሉና አድምጡኝማ!
አምባቸው ደጀኔ (ከወልዲያ)
(Ethio Semay ኢትዮ ሰማይ ድረገጽ የተለጠፈ)
ባለ ሁለት ምላሱ አብይ አሕመድ (ባንድ ራስ ሁለት ምላስ)
" የአቢይ የንግግር “ፊያቶ” እንዲህ አልነበረም፡፡ ትንታግ ምላሱ ጉሮሮው ውስጥ ሲወተፍ አይተናል፡፡ አንዲት ቃል ለማውጣት ሴኮንዶችን ፀጥ ረጭ ሲል ታዝበናል፡፡ ፊቱ በረዶ ሲዘንብበት አስተውለናል፡፡ የምናውቀው ግርማ ሞገሱ ከድቶት ሁለመናው ጥላቢስ ሲሆን በበኩሌ አይቻለሁ፡፡ የክፋት መጨረሻው እንደዚህ ነውና አልገረመኝም - የርሱ ግን ፈጠነብኝ፡፡ አለወትሮው ቃላትን ሲደጋግምና ሲንተባተብ ተመልክተናል፡፡ የደም ዋጋ ገና ከዚህ በላይ ብዙ ያስከፍለዋል፡፡"……  ከጽሑፉ የተወሰደ. ሙሉውን ከዚህ በታች ያንብቡ…

የሀገራችን ጉዳይ እንደሰሞኑ የተንተከተከበት ወቅት ኖሮ አያውቅም፡፡ በፍጹም!
ምክርን አትናቁ፡፡ ከየትም ቢመጣ ገምቢ ሃሳብንና አስተያየትን መቀበል የበሳል ሰው ምልክት ነው፡፡ ባይጠቅማችሁ አትጎዱበትም፡፡ ይህን አስተያየት የሚጽፍላችሁ ሰው የዛሬ 30 ዓመት ጀምሮ ስለሀገሩ እጅግ ብዙ ነገሮችን ሲጠቁም ነበር፡፡ ያኔ ስለሀገር ይጽፉ ከነበሩ ታላቆቹ አንዱ - ዳንዴው ሰርቤሎ (ጋሽ ግርማ ፈይሣ)  - በቅርቡ ወደማይቀርበት አገር ሄደ፤ ሌሎቹ ተስፋ ቆርጠው ወይም ለሥጋቸው አድልተው መጻፍን እርግፍ አድርገው ትተውታል ወይም በገዛ ፈቃዳቸው ጡረታ ወጥተዋል፡፡ ይህ ሰው ግን “ጉዱን አያለሁ” ብሎ እስካሁኒቷ ቅጽበት ቀጥሏል፡፡ ያኔ በዚህ ሰውዬ የወጣትነት ዘመን ገና በአሥራዎቹ ዕድሜ የነበረ አቢይ የተባለ የአሁን ጎልማሣ ሳይመጣ ሰውዬው ብዙ ደክሟል፡፡ ወሮታ ክፈሉኝ እያለ አይደለም አሁን፡፡ እያለ ያለው “እባካችሁን ጆሮ ስጡኝ!” ነው፡፡ ይህ ሰው ከጻፋቸው ወደ አንድ ሽህ የሚጠጉ መጣጥፎች ውስጥ የተወሰኑትን ብንፈትሽ ከሚጽፋቸው ነገሮች በጣም ብዙዎቹ በተግባር መታየታቸውን ማመሳከር ይቻላል፡፡ አሁንም ጆሮ እናውሰው፡፡ ዓይነተኛውን የዕድሜ ዘመኑን ላባካነበት ሌላው ቀርቶ የሚለውን በመስማት እንካሰው፡፡

ዶ/ር አቢይ ደክሞታል፡፡ ትንፋሹ እየተስለመለመች ናት፡፡ በኔ ግምት በአጭር ጊዜ ውስጥ እጅግ ብዙና ሊታመኑ የማይችሉ በታሪክ አስወቃሽ ድርጊቶችን በመፈጸሙ እነዚያ ዕኩይ ድርጊቶች በህልሙም በእውኑም እየመጡ ሰላሙን ስለሚነሱትና በርሱ ዕውቅና ወይም ትዕዛዝ የተገደሉ በተለይም የአማራው አመራሮች ነፍሳት ዕረፍት እያሳጡት በመሆናቸው በጣም እየተጨነቀና በአካልም በመንፈስም ክፉኛ እየዛለ ይገኛል፡፡ ከሰሞኑ ጃዋርን ነፃ ለማውጣት ካደረገው ከንቱ ንግግር የተረዳሁት ይህንንና ብዙ ሌላም ነገር ነው፡፡

የአቢይ የንግግር “ፊያቶ” እንዲህ አልነበረም፡፡ ትንታግ ምላሱ ጉሮሮው ውስጥ ሲወተፍ አይተናል፡፡ አንዲት ቃል ለማውጣት ሴኮንዶችን ፀጥ ረጭ ሲል ታዝበናል፡፡ ፊቱ በረዶ ሲዘንብበት አስተውለናል፡፡ የምናውቀው ግርማ ሞገሱ ከድቶት ሁለመናው ጥላቢስ ሲሆን በበኩሌ አይቻለሁ፡፡ የክፋት መጨረሻው እንደዚህ ነውና አልገረመኝም - የርሱ ግን ፈጠነብኝ፡፡ አለወትሮው ቃላትን ሲደጋግምና ሲንተባተብ ተመልክተናል፡፡ የደም ዋጋ ገና ከዚህ በላይ ብዙ ያስከፍለዋል፡፡ የነአምባቸው ደም፣ የነአሣምነው ደም፤ የነሰዓረ ደም... የውሻ ደም አይደለም፤ የዶሮ ነፍስ አልያዙም፡፡ እነዚህ ውድ ዜጎች በዚህ ሰው ምክንያት ጭዳ መሆናቸውን ለመረዳት ከስድስተኛው ስሜታችን ሩቡን ያህል ብቻ እንዲሠራ ማድረግ በቂ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ጉዳይ በተለይ በአሁኑ ቅጽበት ምሥጢር አይደለም፡፡ ሁሉም ነገር ግልጽ ነው፡፡

እንግዲያውስ እንዲህ እናድርግ፡፡ እንዲህ የምናደርገውም የትንቢቱን ቃል ለማለዘብ እንጂ ትንቢትን ማስቀረት ወይ ማስለወጥ ስለሚቻል አይደለም፡፡ ሁሉንም አይተን የሚበጀንን እንይዝ ዘንድ መለኮታዊ ፍርጃ እንደተጣለብን መገንዘብ ብልኅነት ነው፡፡

ሁሉም ሰው ወደ ፈጣሪው ይጸልይ፡፡ በፈጣሪ ፈቃድ ወያኔዎች ዳር ይዘው  በሁሉም ረገድ እነሱን የተኩና በነሱም የሰለጠኑ አቢይንና ወንድሙን የመናዊውን ጃዋርን ተመስሎ የመጣብን ውርጅብኝ ከባድ ነው - እያስገመገመ ያለው አደጋ ከነሦርያና ሩዋንዳም ይከፋል፡፡ በሀገራችን ታይቶና ተሰምቶ የማይታወቅ ክስተት ሰሞኑን ብልጭ ብሎ ንጹሓን ዜጎች - ሕጻናትና አእሩግ በሽተኞች ሣይቀሩ - እንደበሬ ታርደዋል፡፡ አዲስ አበባ ውስጥ በተከናወነ ድራማ “ተከብቤያለሁ” ብሎ በማኅበራዊ ሚዲያ የድረሱልኝ ጥሪ ማቅረብና ባሌ ውስጥ የምትገኝ የአምስት ዓመት ዕድሜ ሕጻን መታረድ በምን ሊገናኙ እንደሚችሉ ፈጣሪ ብቻ ነው የሚያውቀው፡፡

ይህ ነገር የሃይማኖት ጉዳይ እንዳይመስላችሁ፡፡ ይህ ጉዳይ እንደሚተረክልን የዘረኝነት ጦስ እንዳይመስላችሁ፡፡ ኢትዮጵያን ድራሹዋን የማጥፋት ጉዳይ ነው፤ የሚባለው ሁሉ ሽፋን እንጂ እውነተኛ ምክንያት አይደለም፡፡ ይህ ሤራ ዓለም ኣቀፍ ነው፡፡ ከፈለጋችሁ ከአባይ ወንዝም አገናኙት ወይም ከአይገበሬው የሀበሾች ነጭን የማሸነፍ ጀግንነት ወይም እውነተኛ የክርስቶስ የማዕዘን ራስ ሊሆን ከሚጠበቅበት የኦርቶዶክስ እምነትም ጋር አያይዙት ይህች ሀገር በኢሉሚናቲዎች ጥርስ ከገባች ዘመን የላትምና ይህ ክስተት ኢትዮጵያን ከነታሪኳ ለማየት ካለመፈለግ የሚመነጭ የምዕራባውያን ታላቅ ሤራ ውጤት ነው፡፡ የቀን ከሌት ህልማቸው ይህችን አገር ማጥፋት በመሆኑ ምን ጊዜም ምቹ ሁኔታን መፍጠር ባይቻላቸው ራሱ እስኪፈጠርላቸው በጉጉት ሲጠብቁ ኖረዋል፡፡ አሁን ደግሞ በጣም ምቹ ሁኔታ ተፈጥሮላቸዋል፡፡ አቢይን የመሰለ ፀረ ኦርቶዶክስና ጃዋርን የመሰለ ፀረ እስልምና ጉዶች በኢትዮጵያ ምድር ግዘፍ ነስተው ሁሉንም ነገር ተቆጣጥረዋል - የሚቃረኑ ለመምሰል የሚጥሩት ትያትር ሁሉ ፋይዳቢስና በቀላሉ የሚነቃበት እየሆነም ተቸግረዋል፡፡ ድራማቸው ሁሉ ሳይተውኑት ጭምር የሚታወቅና ምን ሊተውኑ እንደሚችሉ ሳይቀር የሚተነበይም ነው፡፡ ታሪካዊ ጠላቶቻችንም ከነዚህ የውስጥ ምንደኞች ጋር በመተባበር ውዱንና የክቱን የኖቤል ሽልማታቸውን ሣይቀር ለዚህ ጦርነታቸው አውለው በማታለልም፣ በማፍዘዝም፣ ጠና ሲል ደግሞ በጦር መሣሪያም ጭምር ይህችን ሀገር ለማጥፋት ክተት ዐውጀዋል፡፡ ያፈነገጠ ፕሮቴስታንቲዝምና የሆሊውድ/ቦሊውድ ፊልምና ሙዚቃ ኢንዱስትሪዎችም የዘመቻቸው አካላት ናቸው፡፡ አዲስ ነገር አልነገርኳችሁም፡፡ “ስንቶቻችን ይህንን እናውቃለን?” የሚለው ግን መመለስ ያለበት ጥያቄ ነው፡፡ ምክንያቱም ብዙዎቻችን ስንታይ አዚም የተጣለብን ይመስል ስለማንኛውም ሀገራዊ ጉዳይ ሳንጨነቅ ተጋድመን ዕንቅላፋችንን እንደቃለንና፡፡

አማራና ኦሮሞ፣ ትግሬና ጉራጌ አንባባል፡፡ ይህን የሤረኞች መከፋፈያ እንተወው፡፡ መተማመንን መፍጠርና በጋራ መታገል ይህችን አገር ከተደገሰላት የመከራ ዶፍ ይታደጋታል፡፡ በትንሹ በትልቁም አንደናገጥ፡፡ የሚሆነው ሁሉ ሊሆን እንዳለው እንመን፡፡ ከእስካሁኑ የተመሰቃቀለ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ሕይወታችን ግን እንማርና በአፋጣኝ እንስተካከል፡፡ ምክንያቱም ጊዜ የለንም፡፡ እንሩጥ!

ጥሩ ጥሩ ኦሮሞዎች፣ ጥሩ ጥሩ ትግሬዎች፣ ጥሩ ጥሩ አማሮች.... እየተሰባሰባችሁ እየተመካከራችሁ እየተፈቃቀራችሁ ለሥልጣንና ለገንዘብ ያላችሁን ፍቅር እየተዋችሁ በአንተ ትብስ አንቺ ትብሽ ሀገርን ለማዳን ጥረት አድርጉ፡፡ ገንዘብም ሆነ ሥልጣን የሚጠቅመን ሀገር ስትኖር ነው፡፡ በአሁኑ ሁኔታችን ቢሊዮን ብርም ዓለምን የሚያስገዛ ሥልጣንም ዋጋ የላቸውም፡፡”ቀድሞ የመቀመጫየን” ብላለች ዝንጀሮ፡፡

በተለይ ብአዴን ወይም አዴፓ ራሱን ያጥራ፡፡ ይህ ሕዝብ ነገ ግልብጥ ብሎ ቢወጣ የመጀመሪያው ተጠቂ አዴፓ ነውና በቶሎ ወደ ትክክለኛ ቦታው ይመለስ - ኖሮት ወደማያውቀው ትክክለኛ ቦታ፡፡ ውስጡን ያጽዳ፡፡ በሕወሓትና ኦህዲድ የተሰገሰጉበትን የሁለት ዓለም መዥገሮች ይመንጥር - አሁኑኑ፡፡ እውነቱን ለመናገር ነገ ጊዜ የለንም፡፡ የነገሮች ፍጥነት በሚገርም ሁኔታ ብርሃናዊ ሆኗል - እጅግ ፈጣን!

መሆን ያለበት ባይቀርም ወደ ፈጣሪ ካለቀስንና ፍቅርንና መተዛዘንን ከተላበስን የመከራ አዝመራው ሊቀንስልን ጊዜውም ሊያጥርልን ይችላል፡፡ በየከተማው ያለው አሥረሽ ምቺው ይቅር፡፡ ከፈጣሪ መንገድ የወጡ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን በቶሎ እንዲመለሱ እንምከር፤ በህግ አግባብም እናስተካክላቸው፡፡ ቅጥ ያጣውን ገንዘብ ወዳድነታችንን ልጓም እናብጅለትና ሙስናን ከደም ዝውውራችን እናውጣው - አንዱና ትልቁ ጠላታችን እርሱም ነውና፡፡ በእውነተኛው ገቢያችን  ብቻ ለመኖር ጥረት እናድርግ፡፡  ዳንኪራና ጮቤ እንዲሁም ከተፈጥሮ ህግጋት የወጣ መጥፎ ምግባር ሶዶምንና ገሞራን ምን ያህል ድምጥማጣቸውን እንዳጠፋቸው እናስታውስ፡፡ አሁን ጊዜው የሱባኤ ነው:፡ በሙስሊሙም በክርስቲያኑም የሱባኤና የቱበታ ወቅት ይሁን፡፡ በጽኑ እምነትና በንጹሕ ልብ ተጠይቆ ፈጣሪ እምቢ ብሎ አያውቅም፡፡

የእነ አቢይ ልጆች እነሥራኤል ዳንሣ ሕዝቡን ከምዕራብ አፍሪካ በተገዛ መተትና ድግምት እንዴት እያፈዘዙትና ወኔውንም ገንዘቡንም እየሰለነቡት እንደሆነ እየታዘብን ነው፡፡ የነዚህ አጋንንት ግብር በጠባብ አዳራሽ ተወሰኖ ቢቀር ብዙም ባልከፋ - “ወደሽ ከተደፋሽ ...” እንዲሉ ነውና፡፡ ግን ያ ዓይነቱ አንደርብ የምኒልክን ቤተ መንግሥት በግላጭ ተቆጣጥሮ በአዶ ከብሬ የቁጭ በሉ ትብታቡ ኢትዮጵያን ገደል እየከተታት መሆኑ ከማሳሰብም በላይ ነውና ሁላችንም ወደየኅሊናችን ተመልሰን ይህች ሀገር በትንሽ መስዋዕትነት መፍትሔ የምታገኝበትን ዘዴ እንፈልግ፡፡ ግዴለሽነት ብዙ ዋጋ ያስከፍላልና ከሰው ሳይሆን ከራሳችን እንጠብቅ፡፡ በሌሎች መስዋዕትነት ነፃ መውጣት እንደአካሄድ የሚቻል ቢሆንም እኛ ያልተሳተፍንበት ነፃነት በዘራፊ ወንበዴ ሊቀማና ያልተፈለገ አቅጣጫ ሊይዝ እንደሚችል ከተሞክሮ እንማር፡፡ በረባ ባልረባው አንከፋፈል፤ ቂምም አንያያዝ፡፡ በሃሳብ መከፋፈልና ቂም መያያዝም እኮ የሚያምረው በቅድሚያ የጋራ ሀገር ስትኖር ነው፡፡ በተገኘህበት ሊያርድህ ሜንጫና ሠይፍ ይዞ ወዳንተ እየተመመ ያለ የጥፋት ሠራዊት ከጎንህ አስቀምጠህ “የዛሬ ስንት ዓመት እንዲህ ብለኸኝ፤ ያኔ እንዲህ ብለሽኝ... እ?... ካንቺ ጋራ ?... ካንተ ጋራ? ... እስላምና አማራ! ‹አሄሄ! ‹የወጋ ቢረሣ የተወጋ አይረሣ!› አሉ!› ...” መባባሉ የመርገምት እንጂ የአስተዋይነት ምልክት አይደለም፡፡ እየኖሩ እንጂ እየሞቱ መወቃቀስ ለጠላት ካልሆነ ወገኔ ነው ለምትለውና ወገንህ ሊሆን ለሚጠበቅበት ለሚገባውም ሰው አይጠቅምም፡፡ በቃኝ እባክህን፡፡ ለቀና የሃሳብ ልውውጥ - martyrof2011@gmail.com