Sunday, October 4, 2020

27 አመት በወያኔ ትግሬዎች 2 አመት በ ኦሮሙማ ኦሮሞዎች በቅኝ ግዛት እየማቀቅክ የምትገኝ ኢትዮጵያዊ ሆይ ዘሬስ ቀለበት ውስጥ እነዳስገቡህ ገባህ አይደል? ጌታቸው ረዳ (Ethio Semay) October 4, 2020

 

27 አመት በወያኔ ትግሬዎች 2 አመት ኦሮሙማ ኦሮሞዎች በቅኝ ግዛት እየማቀቅክ የምትገኝ ኢትዮጵያዊ ሆይ ዘሬስ ቀለበት ውስጥ እዳስገቡህ ገባህ አይደል?

ጌታቸው ረዳ (Ethio Semay)

October 4, 2020

ወደ ርዕሴ ከመግባቴ በፊት  Ethio Semay አጋጥሞት የነበረው የቴከኒክ ችግር ወደ ነበረበት ተመልሷል። መጎብኘት ትችላላችሁ።

አሁን ወደ ጥያቄየ ልግባ።

በርዕሱ እንደምትመለከቱት 27 አመት በትግሬዎች አሁን ደግሞ በኦሮሞዎች 2 አመት ሙሉ በውስጥ የቅኝ (በአፓርታይድ) ግዛት አስተዳደር ውስጥ ተይዛ ከጣሊያኖች በከፋ ሁኔታ ሕዝቧ ፍዳውን እያየ እንደሚገኝ እንደ ዱሮው “አሌ ብላችሁ” ልትሞጉቱኝ እንደማትችሉ እርግጠና ነኝ። አሌ የሚሉ ቢኖሩ በየፌስቡኩ እና አገር ውስጥም ያው የአፓርታይዱ እበላ ባይ ወይንም ግብዝ ሕሊና የተሸከሙ ምናምነቴ አሽከሮች እዚህም እዛም አሉ። ጥያቀዬ  የወቅቱ ፓለቲካ አልገባ ብሎአቸው በአዝጋሚ ሂደት እንደምትጓዘው “tortoise/ኤሊ”  የሚንፏቀቁትን ሳይሆን ለ27 አመት ወያኔ ዛሬም ለ2 አመት ሙሉ በወያኔ እግር የተተካው የወንጀለኞችና የሽብርተኞች ስብስብ ቡድን (አብይ አሕመድ ዓሊ እራሱም አሸባሪዎች ገራፊዎች ነን ብሎ እንዳመነው እና ፍርዱን ያልተቀበለው የወንጀለኞች ስብስብ) ኦሮሞ ሪፑብሊክ ለመመስረት አገራችንን በቅኝ ግዛት ይዞ ወደ ማፍረስ አደጋ ሊወስዳት ነው ብየ ስናገር አላምንም ብላችሁ ስትፋክቱ ለከረማችሁ ኢትዮጵያዊያን ነው ጥያቄየን እንድትመልሱ የምጠይቃችሁ። አሁንስ የዚህ የወንጀለኞች ስበስብ ቡድን ምንነት ገባችሁ?

ይህ ቡድን የወያኔ አሽከር ሆኖ ለ27 አመት የሕዝባችንን የባሕል፤የሞራል እሴቶቹ እንዲላሽቅ በማድረግ ወጣቶችን ተሰምቶም ታይቶም በመይታወቅ የግብረገብ ውድቀትና የውጭ ባሕል ወረርሺኝ ተጠቂ ሆኖ፤ ወላጆቹ ያቆዩለትን ሰፊ አገር እና የባሕር ወደብ ከነሰንደቃላማዋ ጋር እየናቀ፤ የኢትዮጵያ ጠላቶች ባንዴራ እያውለበለበ “ወንድማማች ነን እያለ” የተገዢነት ባህል እንዲያዳብር ተደርጎ አሁን ላለው  ምስቅልል እና ውርደት ተዳር ጓል።

 

ሰው አደባባይ ላይ ከነነበሱ በመኪና እየጎተቱ፤ ነብሰጡር በቢላዋ እየቀደዱ ሽል ፍጥረት ገድለው የእናቶችን ኩላሊት በካራ በጥሰው መብላት የማይሰቀጥጠው ትውልድ ተከስቶ በአይናችን እያየን ይኼው ኢትዮጵያ በዚህ ዘመን ትድናለች በማይባልበት እርከን ገፍተርዋታል። አሁንስ የተከበብክበት ቀለበት ምን እንደሚመስል ጎብቶሃል? ለዚህስ ተጠያቂው ማን ነው?

ቀዳሚ ተጠያቂው ለበርካታ አመታት “ይህ ሕዝብ በጠላት ቀለበት ውስጥ ተከብቦ መግደያ መሬት ውስጥ ገብቷል እና ከጠላቶቹ  ጋር አትሞዳሞዱ “ስል ስጮህ” እኔን እየዘለፈ አጋሰሱ ምሁር አልሰማ ብሎ ይኼው የዋሁን ሕዝባችን ለስቃይ በመዳረግ ዛሬም ሐፍረት ሳይሰማው  ከገዢዎች ጋር እየጨፈረ አልመከር ብሎ አሽቸግሯል።

ትናትም ዛሬም አገራችን በቅኝ ግዛት እንድትያዝ ያደረገው ይኸየው “ኢቮሊሽኑ” ያላገባደደው ምሁር ነኝ ባዩና አንደ ቶረተይልስ የሚያዘግመው የወንጀለኞቹ ፎቶግራፎችና ንግገሮችን በየፌስቡኩ እያዳመቀ ያለ ምንም ሐፍረት የሚለጥፈው “በግብዝነት የሚንሿዋሻው” መንጋ ካድሬዎቹም  አብረው እያጫፈሩ እንዳሉትም አትርሱ ።

የአማራው ሰንፍና እ’ማ አይወራ ነው።


አማራው ምሁር ጀሮ ዳባ ባለበት ወቅት፤ አማራው እንዲነሳ እና ራሱን ከሞት እንዲከላከል ብዙ መጽሐፍቶች ጽፌአለሁ።ብዙ ስደብ ፤ብዙ መነጠል ደርሶብኛል፤ አገር እንዳልገባ ተከልክያለሁ። ብዙ መስዋእት ከፍያለሁ።  ያልገባኝ ነገር እሁንም፤አሁንም ሳስበው ያልገባኝ የውርደቱ ተጠቂ እና የውርደቱ አጥቂ እራሱ አማራ ሆኖ ሳየው ፤ዛሬም እዛው እየተላወሰ ሳየው ዛሬም እንቆቁልሹ አልፈታ ብሎኛል።

(አማራ ስል (ገበሬውን አደለም) ምሁሩን ነው። ነፃነት የሚባለው ‘አስቂኝ ነፃነት’ የሐፍረት ማቅ ለብሳ “እርቃንዋ ሆና በምትወዛወዘዋ ኤርትራ ምድር” ድረስ ሄደው በ1984 ዓ.ም አስመራና ከረን ከተሞች ተገኝተው “ለኤርትራ ስቃይ” እኛ አማራዎች ነን እና “ ይቅርታ እንድታደርጉለን ይቅርታ  እንጠይቃለን’ ብለው ጥቂቶች ከጎጃም እና ከአዲስ አበባ የተመረጡ ሆዳም አማራዎች  እና ብአዴን ውስጥ የተሰገሰጉት ኤርትራኖች በሆኑት እነ ታምራት ላይኔ ፤ አዲሱ ለገሠ (ኦሮሞ) ተፈራ ዋልዋ (ኤርትራዊ ጌድኦ) ፤ በረከት ስምኦን (ኤርትራዊ) ፤ ታደሰ ካሳ (ትግሬ/የሰቆጣ አገው)፤ ካሳ ተክለብርሃን (ትግሬ/የሰቆጣ አገው) ፤ሕላዌ ዮሴፍ (ኤርትራዊ) በአማራው ስም ይቅርታ ጠይቀዋል።


በነዚህ ወንጀለኞች ትዕዛዝ በሚሊዮን የሚቆጠር አማራ ለስደት፤ ለሞትና ለስቃይ ተዳርጎ እያለ፤ ከሁለት አመት በፊት ወንጀለኞች ነን ብለው “ምለው ጥለው” አይደግመንም ብለው ሕዝብን አሞኝተው ወደ ሌላ ሥልጣን ዕርካብ ከወጡ በሗላ የከፋ ጭፍጨፋ አድርሰውበት እያለ ያም ቢሆን  ዛሬ የባሰውኑ የአማራ ወጣት ከፉከራ ውጭ ያሳየው ተጨባጭ ትግል የለም።

አማራው የዘር እና የሃይማኖት ጭፍጫፋ ተካሁዶበታል። በርካታ የዩኒቨርሲቲ አማራ ወጣት ሴቶች ታፍነው ጠፍተዋል። እንደ እነ እስክንደር እና ከነልጅዋ ጡት እያጠባች የታሰረቺው ጀግኒት አስቴር እንዲሁም ልደቱ አያሌው፤ይልቃል ጌትነት የመሳሰሉ ጥቂት ጀግኖች ይህንን የወንጀለኞች ጥርቅም በይፋ ተጋፍጠው ለእስር ሲዳረጉ፤ በጎንደር እና በጎጃም የተነሳው “ፋኖ” የተባለው  የደፋሮች ተዋጊ አልገዛም ሲል እርቅ በሚል ሰበብ አኮላሽተውት እና እምቢ ያሉትንም በሆዳም አማራ ትብብር ታድነው በጥቆማ እየተገደሉ ናቸው።

የዘመናችን ኢትዮጵያዊ አስገራሚ ጀግና አሳምነው ጽጌ የመሰለ “የወንዶች ልክ” ለሞት ተዳርጎ እያወቀ የአማራ ወጣት ከፉከራ እና ከሙዚቃ ቀረርቶ ያለፈ አገር አንቀጥቅጥ ሕዝብን የሚያነሳሳ የቁጭት እና የቁጣ የይለይለት ትግል አላደረገም። ለምን? መልስ ስጡ ልስማችሁ!

በብአዴን ተረከዝ እየተጓዘ ያለው አብን የተበለው “ጉድ ፎር ናቲንግ”  የአማራ እናቶች፤ህጻናት እና አረጋውያን የእንሰሳት ህይወት መስሎት የአማራ እናቶች ደም እና ሬሳ ሳይደርቅ፤ ሬሳቸው አፈር ሳይለብስ  ከአማራ ገዳዮች እና ጸረ ኢትትዮጵያ ሃይሎች ጋር እየተሞዳሞደ ቁጭ ብሎ ከእባብ የዕርግ እንቁላል ሲጠብቅ ማየት እጅግ የሚገርም አስደንጋጭ ክስተት ነው። አንዳንዱ ደግሞ “ፖለቲከኞች ስለሆኑ ለነሱ እንተው” የሚሉ አማራ ወጣቶች የሚጽፉትን ሳነብ “ይህ አርግፍ አድርጎ ፖለቲከኞን የማመን፤ፖለቲከኞችን ያለመወጠርና ሁሉም ነገር በነሱ ላይ የመተው  “ሲንድረም” መቼ እንደሚተው ሳስበው ችግሩ የሚፈታ አይመስለኝም።

27 አመት በወያኔ ትግሬዎች 2 አመት በ ኦሮሙማ ኦሮሞዎች በቅኝ ግዛት እየማቀቅክ የምትገኝ ኢትዮጵያዊ  ሆይ! ዘሬስ ቀለበት ውስጥ እንዳስገቡህ ገባህ አይደል? ጉሮሮየ እስኪደርቅ ሌት ተቀን ስነግርህ የነበረው ማስጠምቀቂያ እወን አልሆነም ልትለኝ ነው? የምፅአተ አማራ ደራሲ ክቡር አቶ ተክሌ የሻው እንዳሉት “ሁልጊዜ ጉድ፤ ዘወትር ጉድ፤ ዝምታና ጉዱ እስከመቸ?”

ጌታቸው ረዳ (Ethio Semay)