Sunday, September 13, 2015

የአመቱ ምርጥ ባለጌ ሰው!

የአመቱ ምርጥ ባለጌ ሰው!

መስከረም 1/2008 ዓ.ም አዲስ አመት የኢትዮጵያ ሰማይ ድረገጽ አዘጋጅ “የአመቱ ባለጌ ሰው” አፈላልጎ በብልግናው የመረጠው “የአመቱ ባለጌ ሰው” ባሕርዳር የሚኖረው  “አለምነህ መኮንን” ነው። አለምነህ መኮንን በነገዱ “አማራ” ነው። ወያኔ “አማራ ክልል” ብሎ ጸረ አማራ አጀንዳው ለማራመድ እንዲመቸው የወያነ ትግራይ ባንዴራ ቅጅ የሆነውን ባለ ሁለቱ ሕበረ ቀለም (ቢጫና ቀይ) ባንዴራውን በአግድም ተሰምሮ የተሰፋለትን የባንቱስታ ባንዴራ ፤ ለአማራ ሕዘብ ባንዴራ መለያ ብሎ በመስጠት ተግባራዊ ካደረጉት እንደ ግኡዝ ጭቃ አድቦልቡሎ ወያኔ ከሰራቸው፤ስብእናቸውን አውልቀው ከጣሉ ባርያዎች አንዱ አለመንህ መኮነን ነው።

 አለምነህ የመሳሰሉት ወያኔ እንደ እንጨት ጠርቦ በምስሉ የቀረጻቸው፤እራሳቸወን የማይመስሉ፤ ትንንሽ ሕሊና ያላቸውን ሰዎችን በማደራጀት ትግራይ ሜዳ ውስጥ የሕሊና አጠባ አድርጎ ተሸክሞአቸው አማራውን ሕብረተሰብ እንዲዘልፉለት ከሾማቸው የወያኔ ብአዴን አማራዎች መካካል አለምነህ መኮንን ግምባር ቀደሙ  ነው።

 

አለምነህ መኮንን ከነ ደመቀ እና ከነ ወንድወሰን የመሳሰሉ ግማሽ አማራ ሙሉ ኦሮሞ የሆኑ በስም አማራ የተሰየሙ እነዚህ የወያኔ አሽከሮች ወያኔ ሲሞት ከወያኔ ጋር ለመሞት አርሱን የሚተካ ተመሳሳይ ባንቱስታዊ መሪ ከመጣ ደግሞ ለማገልግልቃል የገቡ የአማራን ሕብረተሰብ ከሚያስሰድቡና ከሚሳደቡት ማፈሪያዎቹ አለምነህ መሳዮች በርካታ ናቸው። ወያኔ እንደ በቋንቋ ክልሎ ካዘጋጃቸው ባንቱስታን ክልልች አንዱ “የአማራ ክልል” ሲሆን ፤ ይህ ክልል በምክትል ፕረዚዳንት እና የብአዴን ጽ/ቤት ሓለፊ ሆኖ የሚሰራው አለመነህ ነው። አለቆቹ አማራን ስለዘለፈላቸው አሜሪካ ድረስ ልከው ሰሞኑን ካንሳስ ሲቲ አየር ማረፊያ ጣቢያ እንደታዬ  ዜናዎች እየዘገቡ ነው።

 

ይህ ሰው አባቱን እናቱን ዘመዶቹን በጠቅላላ አማራውን ሕብረተሰብ ምን ብሎ አንደተሳደበ ላስነብባችሁ።

 

<<“ስንፋጭ” ትምክህት የተጠናወተው፡፤ትምክሕትነቱን ያልተወው፤ በባዶ እግሩ እየሄደ መርዝ ንግግር የሚናገር፤ ከሌሎች ሕዝቦች ጋር ተግባብቶ መኖር የማይችል፤ የሸተተው እግሩ እንዳይሸት ከጫማው ስር ‘የባሕር ዛፍ ቅጠል ያደረግበታል”፤ /ዚስ ኢዝ ቴክኖሎጂ!………ባዶ እግሩ እየሄደ የሚናገረው ንግግር ግን መርዝ ነው። ልሃጩን ማራገፍ አለበት! ይኼ ላሃጭ ሳይራገፍ ከሌሎች ጋር በጋራ መኖር አይቻልም።“አማራው ይህ ሰንፋጭ ትምክሕቱ በቤንሻንጉል እና በተቀሩት አካባቢዎች ለመሰደድ ምክንያት ሆኖታል።>>

 

 <<…ማንኛውም ሙትቻ ፓርቲ ሁሉ መነሻው አማራ ክልል ነው።>> ይላል።

 

 ምክንያቱንም ሲገልጽ

 

 “ትምክህተኝነትን እንደ ምግብ ስለሚመገበው ነው። ያንን ምግብም እየተመገበ ያቅራራል”>>

 

  እያለ ተሰብሳቢ ካድሬዎቹን ሳቅ በሳቅ እያደረገ በሕዝብ ክብር ሲያላግጥ በድምፁ የተቀዳ ዋልጌ ግለሰብ ነው። ኦሮሞ ጽንፈኞች እና የወያኔ ትግራይ ተከታዮች ይህንን ንግግሩን ወድደውለት እየጠቀባበሉ ልክ ነው አብሮ መኖር የማይችል ትምክሕተኛ እያሉ ሲያራግቡት ሰነበቱ።

 

ይህ ወላጆቹን እና ሕዝብን የሚሰድብ ስድ ግለሰብ፤ <<“አማራ ይህ ሰንፋጭ ትምክሕቱ በቤንሻንጉል እና በተቀሩት አካባቢዎች ለመሰደድ ምክንያት ሆኖታል።>>፡ሲል ተሳድቧል። ያውም እዛው በአማራዎች  አገር ፤ አማራዎች በሚኖሩበት በባሕርዳር ከተማ! ወይ ዘመን! አያሰማን ጉድ የለ!  የአንድነት ፓርቲ አመራሮች እነ ሃብታሙ አያሌው ወደ ባሕርዳር ሄደው ተቃውሞ አስሰምተዋል።

 

ከትንሽም ትንሽ ሰው መሆኑን የሚያሳይ “ይቅርታ ከመጠየቅ ይልቅ፤ የተቀዳው ድምፅ ይፋ ሲሆን ‘የሚመልሰው በማጣቱ ተደናግጦ ለካድሬዎቹ ጋዜጠኞቹን ሰብስቦ (አፋጥጠው ከነማስረጃው ሊወጥሩት እንደማይችሉ ስላወቀ)፤ ይህ እኔ አልተናገርኩም፤ የቴክኖሎጂ <<“የቆርጦ ቀጥል ስራ ነው”>> ሲል ንግግሩ ከሚያሳውቅበት ድንጋጤ ጋር ወዲያ ወዲህ ሲረግጥና ሲዘላብድ ተደምጧል። አለቆቹና ካድሬ ጸሐፊዎቹ በወያኔ ድረገፆች ላይ (አውራምባ ድረገጽ፤ትግራይ ኦን ላይን፤  አይጋ… ላይ የተጻፈውን ተመልከቱት)፤ እሱን ለመከላከል ሲሉ ያልፈነቀሉት የሽፋን ጥረት አልነበረም። ሆኖም አገር ውስጥ የሚገኘው ‘ዩ-ዲ- ጄ’ የተባለው ፓርቲ የፔትሽን /የፌርማ የማሰባሰብን ስራ በመስራት ከሥራው እንዲባረር ቢጥርም፤ <<“ክቡር መሪያችን ከሞታቸው በፊት….”>> እያለ ጌታውን መለስ ዜናዊን ሲያሞካሽ ያደመጡት ጌቶቹ ከሥራው ሊያግዱት አልፈለጉም እና እዛው ሆኖ አማራውን ሕዝብ መዝለፉን እንዲቀጥል አድርገዋል። ሆኖም የባሕር ዳር ሕዝብ በነቂስ በመውጣት <<“ከባዶ ጭንቅላት፤ ባዶ እግር ይሻላል!”>> የሚል መፈከር ይዘው አዳባባይ ወጥተው፤ “ስድ አደግ”፤ “ሙጀሊያም አፍ” እና “የወያኔ መጸዳጃ የሚል ቅጥያ ስም  ተሰጥቶታል።     

ይህ ስድ አደግ’ ሙጀሊያም፤ ስድ ፤ አማራውን ሕዝብ የዘለፈበትን ስድ አንደበቱን ለማድመጥ የሚከተለውን የአውዲዮ አድራሻ ይጫኑ። የአመቱ ባለጌ ሰው እንዴት እንደመረጥኩት መረጃው እራሱ ይናገራል።

Alemneh Mekonnen TPLF puppet NEWS Read by Afewerk Agidew of ESAT

https://youtu.be/CB0DFO-V3O4

 

አመሰግናለሁ፤

 ጌታቸው ረዳ

(ኢትዮጵያን ሰማይ)