Saturday, February 24, 2024

ደቂቀ እስጢፋ (የሰይጣን ተከታዮች/የሰይጣን ልጆች) አዲስ መጽሐፋ ጌታቸው ረዳ Ethiopian Semay ድረገጽ አዘጋጅ 2/24/2024

 

ደቂቀ እስጢፋ (የሰይጣን ተከታዮች/የሰይጣን ልጆች) አዲስ መጽሐፋ

ጌታቸው ረዳ

Ethiopian Semay ድረገጽ አዘጋጅ

2/24/2024

የትግሬ ሊሂቃን ውሸትና የአባ ኢስጢፋኖስና ተከታዮቻቸው ገበና የሚያብራራ አዲስ መጽሐፍ “ደቂቀ እስጢፋ” አፄ ዘርአ ያዕቆብ አባ እስጢፋኖስን ‘ሰይጣን” ብሎ ስለሚጠራቸው ደራሲዋም የአባ እስጢፋኖስ ተከታዮችን “ደቂቀ እስጢፋ” በማለት የመጽሐፉ ርዕስ ሰይማዋለች) በዶ/ር መስከረም ለቺሳ በማስረጃ መርምራ የጻፈቺው አስገራሚ መጽሐፍ በገባያ ውሏልና እያነበብኩት ስለሆነ አንብቤ ስጨርስ ግምገማ እስክሰጥ ድረስ ታገሱኝና “ሲቦተለክ የነበረው የትግሬ ልሂቃን መሰሪ ውሸትና በጭፍን ሲጋልቡ የነበሩ ስለ ደቂቀ እስጢፋኖስ የጻፉ አንዳንድ ኢትዮጵያዊያን ሊቃውንት እንዴት ሲያጃጅሉን እንደነበር ስለ ደቂቀ እስጢፋኖስና መሪያቸው አባ እስጢፋኖስ ጉድ” ለማንበብ ፍላጎት ላላችሁ መጽሐፉን ለማግኘት አዲስ አበባ ድረስ በማስላክ ይህ አዲስ የታሪክ ግኝት እንዳያመልጣችሁ እመክራለሁ።ገልጠን ብናየው የሚያስብል ዓይነት የትግሬዎቹ የደቂቀ እስጢፋኖስ ገመና አነብባለሁ ብየ አልሜም አለውቅም ነበር።

ደራሲዋን ለማግኘት      meski_lechi@yahoo.com

Tel: 251 978 21 22 23 በመደወል መጽሐፉን ማግኘት ትችላላችሁ።

ይህ መጽሐፍ ለዘመናት የቆየ ብዙ ምሁራን አጼ ዘርአያ ያዕቆብን በመውቀስ ሲያሳስቱን የነበሩትን የደቂቀ እስጢፋኖስ ታሪክ ምንነቱን እርቃኑን ገላልጦ ያሳየን መጽሐፍ ስለሆነ ሊነበብ የመገባ አዲስ ግኝት ነውና  ውሸትን በእውነት መክቱ።

ለአንዳንድ ማንበብ ፍላጎት ለሌላቸው ደደብ ኢትዮጵያውያኖች መልዕክት፡

ለምን ሰደብክን ለምትሉ ደደብ ከሆናችሁ እናንተን ይመለከታል፤ ካልሆነ እናንተን አይመለክትምና መልዕክቱን መቀበል ነው። ብዙ ደደቦቹ ኢትዮጵያውያን አንዲህ ላለ አዲስ ግኝት ሲገኝ መጽሐፉን ገዝቶ ሕሊናን አዳብሮ ደራሲውንም ማበረታታት ስላልለመዳችሁበት፤ ያንን ዳተኝታችሁን በማስወገድ እንደ ዶ/ር መስከረም ለቺሳ ያለ ትንታግ ወጣት ምሁራንና ደራሲዎችን አበረታቱ።

ከደራሲዋ የተጠቀሰ

ደቂቀ እስጢፋን አስመልክቶ ምእመኑ (በተለይ የገጠሩ ማኅበረሰብ) ዘንድ ያለው እውቀት፡ በመገናኛ ብዙኃን የምናደምጣቸው ምሑራንና ሰባክያን ከሚሉት ጋር ሲነጻጸር፡ ፈጽሞ የተለየ ነው።.....

ተቀጥላ (appendix) በሚለው የመጽሐፉ የመጨረሻ ማሳረግያ ገጾች ላይ ከደራሲዋ እንዲህ የሚል ይነበባል፡-

<<…..የሚከተሉት ማስረጃዎች፤ ስለደቂቀ እስጢፋኖስ ከምእመናን እንዲሁም ከጥቂት መነኮሳትና ካህናት ያገኘቸው ናቸው። አንዳንዶቹ የደረሱኝ በጽሑፍ ሲሆን ሌሎቹን ደግሞ ያገኘሁት በቃል ነው።… ከተለያዩ ግለሰቦች የተገኙ እንደመሆናቸው በመረጃው መካከል ዩሃሳብ መጣረስ የሚመስሉ ነገሮች ሊኖሩ ይችላሉ። ያን ማጣራት፤የአንባቢዎች ፈንታ ነው። እኔ ግን የደረሱኝ መረጃዎች ፤እንዳለ አቅርቤአለሁ።

በማለት ደራሲዋ ከተጠቀሱ ስለ ዘመናችን የደቂቀ እስጢፋኖስ ተከታዮች ምንነትን ባህሪ የደረሳትን ስታስነብብ ፤ ከተጠቀሱት መረጃዎች አንዳንዶቹን ለናንተ ልጥቀስ፡

“ልጄ፤ስለነዚህ ሰዎች መረጃ ስትጠይቅ ጠንቀቅ በል፡ በጣም አደገኞች ናቸው።”

“ደቂቀ እስጢፋኖስ ማለት እኮ፤ቅባቶች ናቸው። ወደ ጎጃም አንዳንድ ቦታዎች ብትኼጂ ‘እኛ ደቂቀ እስጢፋኖስ ነን’ ይላሉ።’ቅባቶች ነን’ ማለታቸው ነው። በተዋህዶ አያምኑም።”

“ ደቂቀ እስጢፋኖስ ማለት በጣም ሃብታሞች ናቸው። አብያተ ክርሰትያናት ኮሚቴዎች ውስጥ በመግባት አጫቃጫቂ የኾኑ ነገሮችን ሥዕሎችና ቅርጾች እንዲቀመጡ በማድረግ፤ሥርዓት እንዲፋለስ ያደርጋሉ። እነርሱ ቤተክርስትያን ውስጥ በሚሠሩት ሥራ ምክንያት ቤተክርስትያን ትቃጠላለች።”

“ደቂቀ እስጢፋኖስ ማለት፤ ዋልድባ ቤተ ጣዕማ ያሉ ሰዎች የሚከተሉትን እምነት የያዙ ማለት ናቸው፡ ዘጠኝ መለኮት ብለው ነው የሚያምኑት። እምነታቸው ወደ ካቶሊኩ ያደላል።”

 “ደቂቀ እስጢፋኖሶች በእኛ (ኦርቶዶክሶች) ቤተክህነት ውስጥ አሉ። እንዲያውም የሚጠመጥሙት፤እንደመሪጌቶቻችን ነው። መሪጌታ ነው የሚመስሉት። ግን አይደሉም። ቅኔውን፤ዶግማውን ይመራሉ። ግዕዙን ምኑን ይማራሉ። ሲጀመር፤ከመጀመሪያው ዓላማቸው ከኦርቶዶክሱ መሃል ኾኖ፤ኦርቶዶክሱን መስሎ ግን ኦርቶዶክሳዊ ያልኾነ ሥራ መሥራት ነው። ልክ ‘የአብርሃም ልጆች ነን ትላላችሁ፤ ነገር ግን የአብርሃም ሥራ አትሠሩም’ እንደተባሉት ማለት ነው። መንፈሳዊ እይታ ያለው በደምብ ለይቶ መዝዞ ሊያወጣቸው ይችላል። ነገር ግን፤ጊዜው እስኪደርስ ድረስ ፤እውነት እስክታሸንፍ፤እስከዚያው ይቆያሉ።”

የደቂቀ እስጢፋኖስ ዓላማ፤ምንኩስናን በሕዝቡ ዘንድ ማስጠላት ነው። የሚያያቸው ሰው ‘እነሱ እንዲህ ከኾኑ ፤መንኩሰውም ግብረሰዶማዊ ከኾኑ፤ታድያ ሃይማኖት ምን ጥቅም አለው?’ እንዲሉ ይፈልጋሉ።’ጾም ጸሎት፤ምግባር ታዲያ፤ ምን ጥቅም አለው?’ እንዲሉ ያደርጋሉ።”……

"ደቂቀ እስጢፋኖስ የሚባሉት፡ አሉ፤ በጎጃም፣ በወሎ፣ አዲስ አበባ ደግሞ፡ መገናኛ ላይ ብዙ ናቸው። እኔ ንግሥ ለማክበር በየቦታው ስለምኼድ፡ አዋራቸዋለሁ። ሳያቸው በደንብ ለይቼ አውቃቸዋለሁ። የቡዳ ዘሮች የሚባሉት ናቸው። ግንባራቸው ይከብዳል። ከነርሱ ጋር አውርቼ፡ ማታ እንቅልፍ አይወስደኝም። እቃዣለሁ።በምንድነው የምታምኑት?’ ስላቸው፡ቅባትይላሉ። ተዋሕዶን አይወዷትም።ደቂቀ እስጢፋኖሶች ነንብለው በግልጽ ይናገራሉ። እና፡ተዋሕዶየሚለውን ቃል አይወድዱትም። ቀን ሰው አይተው፡ ማታ ይመጣሉ።ወደንሃልብለውኝ ወንዶቹ አንድ ቀን ማታ መጡብኝ። ግብረ ሰዶም ለመፈጸም። እንዲህ ናቸው። እነሱን ሳያቸው በጣም ነው የምረበሸው። የተዋረሰ ክፉ መንፈስ አለባቸው። በጸበል ራሱ በቀላሉ አይለቅም። በገቡ ቁጥር ዝም ብሎ መጮህ ነው። ከነርሱ የተወለደች አንዲት ልጅ አውቃለሁ። ኹል ጊዜ ትጠመቃለች። ግን መንፈሱ ሊወጣላት አልቻለም። ስቃይ ነው።

(ደቂቀ እስጢፋ፥ ገጽ 302—307

እያሉ ሰዎች ለደራሲዋ የሰጡት አስተያየት ስለ የዛሬዎቹ ደቂቀ እስጢፋኖስ ባሕሪ ከላይ አንደተጠቀሰው ይነበባል።

ስለ ዋናዎቹ ደቂቀ እስጢፋኖስ ለማወቅ ግን በጣም ሰፊ ሃይማኖታዊና የመሳሰሉ መረጃዎችና ማስረጃዎች በዘመኑ የተጻፉ የግዕዝ መጻሕፍተና የንጉሡ ክርክርና መጻሕፍቶችን እንዲሁም የደቂቀ እስጢፋኖስ ሰነዶች ሁሉ በማካተት የዳሰሰ አዲስ ክስተት የያዘ የምርምር መጽሐፍ ነው። 

* * *

መጽሓፉን ለማግኘት፦

አራት ኪሎ ገለን ሕንጻ (ከብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ግቢ ቀጥሎ)፥ ሦስተኛ ፎቅ፥ ቢሮ/ሱቅ ቁጥር 303

0978 21 22 23

ጌታቸው ረዳ

Ethiopian Semay ድረገጽ አዘጋጅ