Thursday, November 7, 2019

ለሯጩ ኃይሌ ገብረሥላሴ መልስ (ከጌታቸው ረዳ -ኢትዮ ሰማይ ድረገጽ አዘጋጅ) (Ethio Semay) (Nov. 7, 2019)


ለሯጩ ኃይሌ ገብረሥላሴ መልስ (ከጌታቸው ረዳ -ኢትዮ ሰማይ ድረገጽ አዘጋጅ)
(Ethio Semay) (Nov. 7, 2019)
Getachew Reda author and Editor Ethio Semay
ተፈጥሮ አድሎአቸው በብርና በዶላር ብዛት ስሜታቸውን መቆጣጠር አቅቶአቸው አላስኖር አላስቀምጥ ብሎአቸው ፖለቲካውን ሳይካኑበት ለኢትዮጵያ ጠ/ሚኒሰቴርነት እወዳደራለሁ ሲሉ ከነበሩት የፋሺስት ድርጅት መሪ አድናቂዎች ከነበሩት መካከል አንዱ ሯጩ ኃይሌ ገብስላሴ ነው። ዛሬም መፈትፈቱን አላቆመም።

ትዝ ይላችሁ እንደሆነ በራሴው መጽሐፍ “የትግራይ ብሔረተኞች በአማራ ላይ ያላቸው ጥላቻ ከምን የመነጨ ነው?” በሚለው መጽሐፌ ውስጥ ኃይሌ ገብረሥላሴ የተናገረውን በመግቢያየ ላይ ጠቅሼው ነበር እንዲህ ብሎ ስለ ዲሞክራሲ የተናገረውን፡

ልጥቀስ፤
““ በኔ እይታ ዲሞክራሲ  ለአፍሪካ ቅንጦት ነው!” ይላል እንግሊዙ ኃይለ ገብረሰላሴ እንዲህ በማለት “Everything we talk is about democracy, democracy. I know for me it is a little bit too luxurious. Democracy is too luxurious for Africa.”(ባለ ጊዜው  አትሌት ኃይለ ገብረስላሴ ሲሞላቀቅብን የተናገረው)  ምንጭ የጌታቸው ረዳ መጽሐፍ “የትግራይ ብሔረተኞች በአማራ ላይ ያላቸው ጥላቻ ከምን የመነጨ ነው? ገጽ 8

ሰሞኑን ፌስ ቡክ ልከስስ ነው ብሎ ይቦርቃል። እስኪ ምን እንዳለ እንመልከት፦እንዲህ ይላል
”ፌስ ቡክ (የማሕበራዊ ትስስር ገጾች)በኢትዮጵያ ውስጥ እያደረሱት ያለውን ጥፋት የኢትዮጵያ መንግሥት የማይከስ ከሆነ ጌስ ቡክ ፣ክሴ አይቀርም።ሐገር እየተጎዳ ሕዝብም እየሞተ ነው ብሎ ተናግሯል።.. ሌላ አገር የተፈጠሩ እዚህ አገር እንደተፈጠሩ፤ሌላ አገር የጠቆረጡ እጆችና እግሮች ምስሎች እዚህ አገር እንደተቆረጡ ፤ሌለ አገር የተቃጠሉ ቤቶችና ንብረቶች እዚህ አገር እንደተቃጡሉና እንደወደሙ እያስመሰሉ ለጣጠፍውና  አሰማምሮ ማቅረብ ዋጋ ያስከፍላል።”
ሲል ባለ ሃብቱ ፖለቲከኛ ሯጩ ሃይለ ግበረሥላሴ በማያውቀው ፖለቲካ ገብቶ ዛሬም መፈትፈቱን አላቆመም።    
መጀመሪያ አማራውን ማሕበረሰብ የጨፈጨፈው አንተ ስቅስቅ ብለህ ያለቀስክለት ያንተው ንጉሥ ፋሺስቱ መለስ ዜናዊን መክሰስ ሲኖርብህ ዛሬ አንተ ስለ “ሕዝብ ጭፍጨፋና ሰላም አሳቢ” ሆነህ ብቅ ማለትህ የሚመሰገን ቢሆንም የተደረገውን አልተደረገም እያልክ ከአብይ አሕመድ ውሸት ጋር መጣመርህ የሚገርም ዘመን ነው። ለመሆኑ እንዳንተው ያሉ ለነ መለስ ዜናዊ ለፋሺሰቶችና ለጸረ አማራዎች ስቅስቅ ብለው እምባቸውን የሚያፈስሱ አሞጋሾችን በየትኛው ፍርድ ቤት እንክሰሳችሁ?

 እናነት ሙዚቀኞች እና ራጮች ምናለ በማታውቁበት ፖለቲካ ባታቦኩና ነገር ባታበላሹብን? ዛሬ ደግሞ ፌስቡክን እከሳለሁ ብለህ ስትጮህ በጣም ነው የገረመኝ። ብርሃኑ ነጋም በሎሌዎቹ ዝቶ ነበር። አብይ አሕመድም ተነፋፍጦብን ነበር።
የሚገርመው እዛው አንተ ካለህበት አገር አዲስ አበባ ውስጥ ተቀምጠው ነፍጠኛን ሰበርነው፤አዲስ አባባ ኦሮሞ ተቆጣጥሮታል’ የሚሉ እነ ሽመልስ አብዲሳ አስከ አብይ አሕመድ ጀምሮ ለማ መገርሳ፤እና ጃዋር፤ አማርኛ ከሚናገር ጋር እንዳትጋቡ፤ የሚለው በቀለ ገርባ፤ እንዲሁም “በአዲስ አባባ ዙርያ ጎጃሜዎችን አምጥተው ካሰፈሩ በላ ሕገ ወጠው ቤቶችን እንዳይፈርሱ እያሉ ሲከላከሉ የነበሩ ነፍጠኞች ማንነታቸው በውል ስለተለየ፤ የነፍጠኛ ሥርዓት ባለቤቶች መሆናቸው ስለታወቀ ከዚህ በኋላ ሒሳብ እናወራርዳለን” ብሎ በግልጽ የተናገረ ታየ ደንዳአ የመሳሰሉ ጸረ አማራዎች ሃይለ ገብረስላሴ ለምን አልከሰስካቸውም? ወይንም ለምን አንተ መንግሥት ተብየው “ሥርዓተ አልባው መንግሥትህን” ፌስቡክ ካልከሰሰ እኔ ፌስቡክ እከሳለሁ የምትለውን መንግሥትህን ለምን የተጠቀሱትን ጽንፈኞች አልከሰስካቸውም ብለህ አልጠየቅክም?
ያውም ወንጀለኞቹ ጸረ አማራ ኦነጎች እነ ሌንጮ ለታ፤ እንዲሁም ከጥቂት ወራት በፊት 3000 አመት አማራውን እንገዘዋለን ብሎ በግልጽ የተናገረ ጭፍን ጠባብነትና ትምክሕረተኝነት የተናወጠው ‘ሌንጮ ባቲ’ (ባለፈው ሰሞን አብሮ ከአብይ ጋር ወደ ሩስያ የሄደው የዛሬው የአብይ አሕመድ አማካሪ) ፤ ከማል ገልቹ (ሰሞኑን ነፍጠኛ እያለ የተናገረው ሰምታችል) የመሳሰሉትን በጠቅላላ “ኦፒዲኦ” የተባለው የቄሮ ጽንፈኛ አንቀሳቃሽን ሳትከስ ለዝና ብለህ ወደ ፌስቡክ ማትኮር “የብብትዋን ትታ የቋጡን” ያሰኛል።

አንተ ባለህበት አዲስ አበባ ከተማ አብረውህ ባንድ ከተማ የሚኖሩትን ከላይ የጠቀስኳቸው ዘረኞች ምላሳቸው አሞርሙረው የሚናገሩት ተደብቀው ሳይሆን ወይንም  “ፒያሳ መሃሙድ ጋ ጠቢቂኝ!” ደራሲ ጋዜጠኛ ‘መሐመድ ሰልማን’ እንዳለው ሚስጢረኛ ተሳሳሚዎች የሚሳሳሙበት “ኢንትር ላንጋኖ” ፤ “ትሬይን ሃውስ” ፤ “ቢግ ትሪ” ፤”ጊቤ” ፤”ቬሮኒካ” በሚባሉ ፒያሳ ውስጥ የሚገኙ ድብቅ መሰሳሚያ ቤቶች ውስጥ ሆነው ሳይሆን ጸረ አማራ የሆነ  ሕዝብ ለሕዝብ የሚያፋጀውን ማኒፌስቶአቸውና ንግግራቸው ያሰራጩት ፤ ተደብቀው ሳይሆን “በግልጽ በአደባባይ” የኢትዮጵያ ሕዝብ ጀሮ እና ዓይን እያየ እየሰማ በጽሑፍና በንግግር ያሰራጩት አደገኛ መልዕክት አልሰማህም። ታዲያ ምነዋ ወንድም ኃይለ ግበረስላሴ እጉያህ ያሉትን እነ አብይ፤ እነ ለማ፤ እነ በቀለ ገርባ ሺመለስ እና ታየ ደንዳአ፤ጃዋር መሐመድ፤ በቀለ ገርባ እና መሰሎቹን ሳትከስ ወደ አሜሪካ አነጣጥረህ ፌስ ቡክን ለመክሰስ ምን አነሳሳህ?

ለመሆኑ  ፌስ ቡክ ያሉትን ዘረኞች እጅ እግር ሳይቆረጥ ከሌላ አገሮች የተፈጸመውን አጅና አንገት “በቆርጦ ቀጥል ቴክኒክ እያሰማመሩ” የተቆረጠውን የሌችን አገሮች ጭካኔ አገር ውስጥ እንደተደረገ አስመስለው እየለጠፉ ሕዝብን ለሕዝብ የሚያጋጩ የፌስ ቡክ  ኢትዮጵያውያንን እከሳቸዋለሁ የምትለው ቅዠት እውነት አንተ አገር ውስጥ ነው የምትኖሮው? የተደረገው አታውቅም?

 ለመሆኑ ሌላውን ልተወው እና “ሁለት ፕሮቴስታንቶች ሁለቱም እህትማማቾች ጡታቸው ተቆርጦ የሰውነት ክፍላቸው እንኳ በጽንፈኞች ሜንጫ ቁርጥርጥ ተደርገው መገደላቸውን ከዓይን ምስክሮችና ከሥፍራው የሸሹ እማኞች ሲናገሩ አልሰማህም? አከላቶቻቸው ተሰብስቦ በስንት መከራ ነብሳቸውን ሳያድኑ ለሞቱት ነብሳት ሲሉ ተሸሽገው ኦርቶዶክሶች አልቀበርዋቸውም? ጆሮህ እዛ ደርሶ ለምን ተደፈነ? የዓለም ኦሎምፒክ ሩጫ ስትመለከት ወይስ  የዓብይን ውሸት ስታዳምጥ አመለጠህ?   
ለፋሺስት መሪዎች የሚያለቅስና የሚያሞግስ ሕሊና የተሸከሙ፤ አገር ውስጥ የሚደረገውን አልተደረገም የሚሉ ሞራለ ቢስ ሁላ ገንዘብ ስላለው ብቻ እንዳመጣበት መፈትፋት ያስነውራል።  ጌታቸው ረዳ (ከኢትዮ ሰማይ ድረገጽ አዘጋጅ)