Monday, June 7, 2010

በኢትዮጵያ አስደንጋጩ የባሕል ወረርሽኝ

የወያኔ ገበና ማሕደር (ኢትዮጵያን ሰማይ ብሎግ) በኢትዮጵያ አስደንጋጩ የባሕል ወረርሽኝ ከቀድሞ የኢትኦጵ ጋዜጣ ባልደረባ

ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በአገራችን ኢትዮጵያ አስደንጋጭ ብሎም አሳሳቢ የባሕል “ወረርሽኝ” ስር እየሰደደ መጥቷል። ኢትዮጵያዊያን የምንኮራበትና ደረታችንን ወጥረን የምንናገርበት እንዲሁም ሌሎች ጠንቅቀዉ የሚያዉቁልን ኩሩ የባሕል እሴታችን ከወደ አናቱ መናድና በግልጽ መገንዘብ ጀምሯል። ክርስቲያን ይሁን ሙስሊም፤ባሁላ ሆነ ፕሮቴስታንት፤ካቶሊክ ይሁን ጆሆባ…ብቻ የፈለገዉ ሃይማኖት ተከታይ በእኩልነትና በመከባበር ተቻችለዉ በመኖር የምትታወቀዉ አገራችን የተደቀነባት “ምዕራብ” አመጣሽ የተጨማለቀ ወራዳ “ቆሻሻ” አድማሱን እየለጠጠ በከፍተኛ ደረጃ እየበከላት ይገኛል። በስልጣን ላይ ያለዉ ፈላጭ ቆራጩ የመለስ ዜናዊ አስተዳደር፤ ለአገር ክብር፤ ለዜጎች መብትና ነፃነት ለባሕልና ታሪክ የሚሰጠዉ ግምት የተንጠፈጠፈ ዝቃጭ ዓይነት በመሆኑ አሁን እየተንሰራፋ ላለዉ ወረርሽኝ ቅንጣት ታክል ይቆረቁረዋል ተብሎ በጭራሽ…በጭራሽ…በጭራሽ!... አይታሰብም። እንዲያዉም ለነዚህ የባሕል ወረርሽኝ አደጋዎች የእጅ አዙር ድጋፍ በተዘዋዋሪ መንገድ እየሰጠ ያለበት ተጨባጭ እዉነታ እንዳለ ታይቷል። የመለስ ዜናዊ መርሕ “ማንም ግለሰብና ቡድን በኢትዮጵያ ምድር ያሻዉን የዘረፋ ወይም ሙስና ስልት ማራመድ ይችላል። ያሻዉን እምነት ማራመድ በቡድን ተደራጅቶም መንቀሳቀስ ይችላል። ነገር ግን በአራት ኪሎ ቤተመንግሥት ዙርያ የተሰመረዉን ቀይ መስመር ማለፍ አይቻልም” የሚል ነዉ። የህ ማለት ማንም ግለሰብና ቡድን በመለስ መንበረ ስልጣን ዙርያ ከመጣና ፖለቲካዊ ይዘት ያለዉ የተቃዉሞ አቋም ሲያራምድ ከታየ አደጋ ሊከተለዉ እንደሚችል በማያሻማ መልኩ ደንግጓል። በገሃድ የሚታይ በመሆኑ ማስረጃዎች መዘርዘር የሚያስፈልገዉ አይመስለኝም። የመለስ የዘቀጠ “አቋም” ይህ ስለሆነ ነዉ አደጋዉ እየከፋ የመጣዉ “የባሕል ወረርሽኝ ምንድነዉ?’ ለምትሉ ዝርዝሩ ይኸዉላችሁ።በ ኢትዮጵያችን በተለይም በመዲናችን አዲስ አበባ ግብረ-ሰዶማዊነት ከሚታመነዉ በላይ እየተስፋፋና በአስደንጋጭ መልኩ በግልፅ አደባባይ መዉጣት ከጀመረ እነሆ አምስት አመታት ደፈኑ። በተለይ ከ1998 ዓ.ም. ወዲህ እየተስፋፋ የመጣዉ የግብረሰዶማዊያኑ ብዛት ከዕለት ወደዕለት መጥቷል። ከተጠቀሰዉ ጊዜ አንስቶ በአዲስ አበባ መሰማት የጀመረዉ ዜና “የ10፤9፤8…ዓመት ዕድሜ ያላቸዉ ታዳጊ ሕፃናት አንድ የካናዳ ዜግነት ባለዉ ግለሰብ (ነጭ) በደረሰባቸዉ መደፈር ለከፍተኛ የስነልቦና ኹከት እንደተዳረጉ የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነዉ። በተለያዩ የመደለያ ስልቶች በማባባል ታዳጊ ሕፃናቱን “አሜሪካና ዉጭ አገር እንወስዳችሗለሁ፤ገንዘብ እመድብላችሗላሁ…” እያለ ሃያ (20) ታዳጊ ሕፃናት እንደደፈረ የችግሩ ሰለባዎች በነፃዉ ፕሬሰ በሰጡት ጥቆማ በወቅቱ ተጋልጧል። ታዳጊዎቹ ከ10 እስከ 14 የዕድሜ ክልል ሲሆኑ፤የስነልቦና ቀዉስ የተፈጠረባቸዉ በዕድሜ ከፍ እያሉ ሲሔዱ ነበር። ያ ወንጀለኛ ለአንድ ወር ታስሮ በዋስ በመለቀቁ ከአገር መዉጣትና ማምለጥ እንደቻለ ወቅቱ ተገልጿል። የሚገርመዉ ስለሰለባዎቹ ታዳጊዎች ጉዳይ ሰምተዉ እንዳልሰሙ የሆኑት የመንግሥት መገናኛ አዉታሮች “ጅብ ከሔደ…” እንደሚባለዉ ዜናዉን እየተቀባበሉ ያሰራጩትና በባዶ ሜዳ ሲቦርቁ የታዩት ወንጀለኛዉ ከአገር ከወጣ በሗላ ነበር። ይህ ግለሰብ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ በኬኒያ ባንዳንድ የምስራቅ አፍሪካ አገራት ተመሳሳይ ወራዳ ወንጀል ሲፈፅም እንደቆየ ተደርሶበታል። አሁን ያለዉ ተጨባጭ እዉነታ ደግሞ ከተገለጸዉ በላይ አስጊ ሆኗል። ግብረሰዶማዊያን ማሕበር (ቡድን) እስከ መደራጀት ደርሰዋል። ከላይ እንደጠቀስኩት የመለስ አስተዳደር ምን አቋም እንዳለዉና እንደሚከተል ጠንቅቀዉ የተረዱ ግብረሰዶማዊያን የ2000ዓ.ም. ሚሊኒየም በማስታከክ “ሕጋዊ ዕዉቅና ይሰጠን” እስከማለትና የመለስ ዜናዊን በቀጥታ እስከመጠየቅ ደርሰዋል። ስለዚሁ ጉዳይ ወይም ጥያቄ “ሪፖርተር” ጋዜጣ የዜና ሽፋን በወቅቱ ሰጥቶታል። በዚህ ዙርያ ንዴት የተንጸባረቀበት ምላሽ የሰጡት ፓትርያሪክ አቡነ ጳዉሎስ “ይኸ ክቡር ባሕላችንን የሚበርዝ ቆሻሻ ጥያቄ ነዉ።ግብረሰዶምና ግበረሰዶማዉያን የፈጣሪን ሕግጋት የተላለፉ ናቸዉ። መዝቀት ጭምር ነዉ። ወራዳነት ነዉ>> ሲሉ አጣጥለዉታል። እንደ አቡኑ ባይሆንም የካቶሎክና የእስልምና ሃይማኖት መሪዎች የተለሳለሰ ተቃዉሞ በወቅቱ ሰንዝረዋል። ግብረሰዶማዉያኑ በዚህ ብቻ አልተገቱም። በአገር ዉስጥ ከሚታተሙ የኪነጥበብና ማሕበራዊ ነክ የግል መጽሔቶች ሳይቀር ሕብረተሰቡን የሚንቁ ጽሑፎችን ማዉጣት ይዘወል። አንድ “ቢኒያም” ነኝ ያለ ግበረሰዶማዊ ባወጣዉ መጣጥፍ- በአዲስ አበባ ብቻ 7 ሺሕ (ልብ በሉ ሰባት ሺሕ ነዉ!) ግብረሰዶማዉያን በአንድነት እንደተሰባሰቡና ማሕበር እንደመሰረቱ፤ለሚመለከተዉ የመንግሥት አካል ሕጋዊ ዕዉቅና እንዲሰጣቸዉ ጥረት እያደረጉ መሆኑን (ግብረሰዶማዉያንን (Gay) ገይ በሚገልጽ ሁኔታ በአዲስ አበባ ዕምብርት (በስማቸዉ መሆኑ ነዉ) ትልቅ ናይት ክለብ ለመክፈት አስፈላጊዉ ዝግጅት መጠናቀቁና ለዚህም የሚያስፈልገዉ ገንዘብ በበቂ ሁኔታ መመደቡን፤ አባላቱ ያቋቋሙት ማሕበር የፋይናንስ ችግር የሌለበት መሆኑን፤የበለጠ ለመደራጀት ሲሉ የአባላት ቁጥር በየፊናዉ እየመለመሉና እያበራከቱ መሆኑን እዉቅና ካገኙ በሗላ በስማቸዉ ጋብቻ የሚፈፅሙበት የሃይማኖት ተቋማት (ቸርች) እንደሚመሰርቱ፤ በ2000 ዓ.ም. ጀርመን ከሚገኝ ወንድ ጓደኛዉ ጋር የጋብቻ ስነስርኣት አከናዉኖ መምጣቱን…በሰፊዉ ከዘረዘረ በሗላ አያይዞም “ሕብረተሰቡን እያግለን፤ግብረሰዶማዉያንን ማግለል ይቁም” እያለ በጽሑፍ ዘላብዷል። ይኸዉ ግለሰብ በተደጋጋሚ ተመሳሳይ ይዘት ያለዉ መጣጥፍ በመጽሔት ያቀረበ ሲሆን በዛዉ ጽሑፍ ያካተተዉ ተጨማሪ ጉዳይ በአዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች የመዝናኛ ክለቦች ተከፍተዉ በስራ ላይ እንዳሉና ግብረሰዶማዉያን በአንድነት ተሰባስበዉ እንዲዝናኑ ሲባል ታስቦበት የተከፈቱ መሆናቸዉን አክሎ ገልጿል። በጽሑፉ የምሽት ክለቦቹን አድራሻ ያልገለጸ ቢሆንም “ዋና ዋና” በሚባሉ ስፍራዎች እንደተከፈቱና ቁጥራቸዉም የተወሰነ መሆኑን አመልክቷል። አስደንጋጩ የግብረሰዶማዉያኑ ተግባር ከላይ የተገለጸዉን ይመሰላል። እነ መለስ ዜናዊ ላገራችን ባሕል ትኩረት መስጠት፤ የአገራችንን ባሕል በመጥፎ ባሕሪዎች እንዳይበከል የመንከባከቡን ሃላፊነት መዉሰድ ግድ የላቸዉም። ይኸዉም በመረጃ አስደግፎ ቸልተኝነታቸዉን መጥቀስ ይቻላል። “7ሺሕ ግብረሰዶማዉያንን እወክላለሁ” ሲል የፃፈዉ ቢኒያም የተባለዉ ግለሰብም ሆነ ፅሑፉን ያተመዉ መጽሔት በመንግሥት የተጠየቁበት ሁኔታ የለም። የሃይማኖት መሪዎችም በዚህ ዙርያ ትንፍሽ አላሉም።መፅሔቱ አልተጠየቀም ስል ሃሳቦችን የማንሸራሸር መብቱ ይገፈፍ፤ይገደብ፤ይሰቀል…ማለቴ አይደለም። ነገር ግን እንዲህ ያለዉን ባሕል አርካሽ ጽሑፍ ይፋ ሲሆን እነ መለስ ወጣቱን ህብረተስብ ምን ያክል በቁም እየገደሉትና ለወራዳ ርካሽ ወረርሽኝ አሳልፈዉ እየሰጡት እንዳሉ የሚያስረዳዉ በሌላ ጋዜጣ ላይ የወሰዱት እርምጃ በቂ ማነፃፀርያ ነዉ። የኦሳማ ቢን ላዲንን ፎቶ በጋዜጣህ ላይ ልታትም ነበር” በሚል ከማተሚያ ቤት ጋዜጣዉ እንዲታፈን ያደረጉት እነ መለስ ዜናዊ አዘጋጁን የሁለት ዓመት እስራት አከናንበዉታል። እንግዲህ ይታያችሁ የአሜሪካ የሚዲያ ተቋማትን ጨምሮ በመላዉ ዓለም ያሉ መገናኛ ብዙሃን ስለ ቢን ላዲን ሳይዘግቡና ምስሉን ሳያሳዩ ወይም በጋዜጣ ሳያትሙ የቀሩበት ቀን ቢኖር በጣም ጥቂት ነዉ ቢባል አልተጋነነም። የመለስ የግል ይዞታ ተድረጎ የተወሰዱት የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ራዲዮና የፓርቲዉ ልሳናት አሁን ድረስ ቢንላዲንን የተመለከቱ ወቅታዊ ዘገባዎች ይፋ ከማድረግ የቀሩበት የለም። ሃቁ ይኸ ቢሆንም የቢን ላዲን ፎቶ ልታትም ነበር የተባለዉ ጋዜጠኛ አዘዲን የሁለት ዓመት እስራት ሲፈረድበት ባሕል ወረርሽኝ አደገኛ ነቀርሳ ግን ያሻዉን እየለቀለቀ ወጣቱን ራሱ እንዳለዉ በገንዘብ ሃይል እየደለለና እየበከለ አገራችንን ቆሻሻ አዘቅት ዉስጥ እየከተታት እየታየ “መንገዱን ጨርቅ ያድርግላችሁ” ዓይነት የተባባሪነት ምላሽ በነመለስ በኩል ተሰጥቷል። ሌላዉ ነጥብ “አታግልሉን” የምትለዉ አስገራሚ አባባል ትጠቀሳለች። የ ኤች አይ ቪ ኤድስ ሕሙማንና የስጋ ደዌ የአካል በሽተኞች… የመሳሰሉት “አታግልሉን፤መድልዎ ይቁም!” እያሉ በአጽንኦት ማሳሰባቸዉ አግባብ ነዉ። ነገር ግን በኢትዮጵያ ያልነበረና ትዉልድን የሚበክል ቆሻሻ የተሸከሙ የባህል ነቀርሶች ተመሳሳይ የመብት ጥያቄ ሲሰነዝሩ መታየታቸዉና በለየለት ድፍረት “አታግልሉን” ማለታቸዉ ሲታይ እነ መለስ ዜናዊ አባሪ ተባባሪ ሆነዉ በምን ደረጃ ሕዝብን በጅምላ እያዋረዱ እንደሆነ የሚያስገነዝብ ጭምር ነዉ። በሌላ ረገድ ግብረሰዶማዊዉ ግለሰብ በደፈናዉ የጠቀሰዉ የምሽት መዝናኛ ስፍራ በተመለከተ በግሌ ለማጣራት ጥረት አድርጌያለሁ። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በርካታ የሕብረተሰብ ክፍሎች ስለግብረሰዶማዊያኑ መሰባሰቢያ ባር እንዲሁም ስለ እንቅስቃሴያቸዉና ከጀርባ ስለሚደረግላቸዉ ዳጎስ ያለ ድጋፍ (ምንጭ) ለይተዉ እያወቁ ነዉ። አሽቃባጭ የሆነዉ “ሪፖርተር” ጋዜጣም አንድ ሁለቴ ባወጣዉ ወረርሽኙ ዋናዉ “አስኳል” የት ቦታ እንዳለ በደፈናዉ ገልጿል።ከባሕላችን ያፈነገጡ ርካሽ ተግባራት በሕብረተሰባችን እንዲስፋፋ እየተደረገ መሆኑን የጠቆመዉ ጋዜጣዉ፤ አክሎም በሸራተን ሆቴል በመሸጉ ቱጃሮች በሚለገስ ከፍ ያለ ገንዘብ አማካይነት አደገኛዉ እንቅስቃሴ እየተንሰራፋ መሄዱን አጋልጧል። በሸራተን ዋናዉ ርካሽ ተግባር እንደሚፈጸም አያይዞ የጠቀሰዉ ጋዜጣ ጉዳዩን በደፈናዉ “ርካሽ የወሲብ ተግባር” ከማለት ዉጭ የግብረሰዶማዊነት መሆኑን ያለመግለጽ ለትዝብት ያደረገዉ አነጋጋሪ ጉዳይ ሆኖ ነበር። እንደተገለጸዉ አስኳሉ ሸራተን የሆነዉ ወረርሺኝ በይፋ ከከፈታቸዉ የምሽት መዝናኛ መካከል የሚከተሉት ይገኛሉ። በአካል ጭምር ተገኝቼ ያረጋገጥኳቸዉ ቦሌ ቴሌ መድሃኒያለም ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ የሚገኘዉ “ሸገር“ ሕንፃ ሦስተኛ ፎቅ በሰፊ አዳራሽ (ሁለት ቦታ ተከፍሎ) ተከፈተዉ “ሻምፒዮን” ወይም በሌላኛዉ መጠሪያዉ “ዲቫይን” የተባለዉ የግብረ ሰዶማዉያን መዝናኛ በዋናነት ይገኛል። የባሩ ባለቤት በአሜሪካ ለረጂም ዓመት የኖረና በ1999ዓ.ም. እንግሊዝ-ለንደን ከተማ ከወንድ ጓደኛዉ ጋር “ጋብቻ” መስርቶ እንደተመለሰ ተረጋግጧል፡፤ ለጋዜጠኛነት ስራየ እንዲሁም ባሕላዊ ወረርሽኝ ለመከላከል ባለብኝ ግዴታ በመነሳት ወደተጠቀሰዉ ባር በእኩለ ሌሊት አመራሁ። የገጠመኝ ሁኔታ ከሰማሁት የበለጠ ነበር! በምሽት ደብዛዛ የብርሃን ጨረር የተሞላዉ ይህ ባር እንደነገሩ ሁለት ቦታ ተከፍሏል። እንደ ዊስኪና ሌሎች የአልኮሆል መጠጦች በዉድ ዋጋ የሚቸበቸቡበትና በዲጄ በሚለቀቁ የዉጭ ዘፈኖች ታጅበዉ የሚደነስበት ሲሆን፤ በሌላኛዉ ክፍል ደግሞ እጅግ ከደበዘዙና ብዙም የብርሃን ጨረር ከማይፈነጥቁ አምፑሎች በመታገዝ ግብረሰዶማዉያን የሚፈጽሙት የሚያቅለሸልሽ አፀያፊ ተግባር የሚፈፅሙበት ነዉ። ከሰኞ በቀር በሁሉም የሳምንት ቀናቶች ይህ ወራዳ ተግባር ይፈጸማል።በጣም የሚገርመዉ ፈረንጆች ወንድ ለወንድ ፤ሴት ለሴት ሆነዉ (ካፕል- ካፕል መሆኑ ነዉ) እየተላላሱ በሚያጠይፍ አኳሗን መመልከቴ ነበር። “ይሕች ያልታደለች፤ተቆርቋሪ መንግሥት ያጣች አገር… ድሕነት አሳሯን የሚያሳያት አልበቃ ብሎ፤ የነርሱ ቆሻሻ ባሕል ማራገፊያ መሆኗ ስታይ ያቃጥላል” አልኩ በወቅቱ ለራሴ ። የእኔን ሃሳብና ቁጭት የሚጋራ ድፍን ሙሉ አገር እንደሆነ አልጠራጠርም። በሌላ ቀን ጥቆማ ወደ ደረሰኝ መዝናኛ ስፍራ አመራሁ። ቦታዉ ከቦሌ ትምህርት ቤት ሽቅብ እንደተጓዘ “ቦሌ ኬክ ቤት”ን ያገኛሉ፡ ከኬክ ቤቱ በግምት 200 ሜትር ርቀት ላይ ከመንገዱ ግራና ቀኝ በመደዳ ከሚገኙ በርካታ ባር ቤቶች ከቀን በኩል ቅድሚያ የሚያገኙት “ላጌቶ” የተባለዉን የግብረሰዶማዉያን መናኻርያ ባር ነዉ። በሚታይ ጉልሕ ጽሑፍ የመዝናኛዉ ታፔላ ተሰቅሏል። በግራዉንዱ አልፈዉ ባሩ ወደ ሚገኝበት አንደኛ ፎቅ ይደርሳሉ። ከእነሱ በቀር ሌላ ተጨማሪ ሌላ ሕንጻ የለም። የባሩ ባለቤት አስመራ የቆየና “ላጌቶ” የሚል ተመሳሳይ መጠሪያ የሰጠዉ መዝናኛ ከፍቶ እስከ ዘጠናዎቹ አመታት አጋማሽ ሲሰራ እንደቆየ ከራሱና ከኤርትራዉያን ጭምር ማረጋገጥ ተችሏል። አስመራ ያለዉ መንግስት በግብረሰዶም ዙርያ ጠንካራ አቋም ያለዉ ሲሆን በዚህ ርካሽ ተግባር ተሰማርቶ የተገኘ ማንኛዉም ግለሰብ ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ በሞት እንዲቀጣ ይደረጋል። ይህ ግለሰብ ሻዕቢያ ሲደርስበት አምልጦ በየመን በኩል አዲስ አበባ ይገባል። አስመራም አዲስ አበባም የሚታወቅበት መጠሪያ ስሙ “ላጌቶ” በባሩ ስያሜ ነዉ። ይህ ማለት ( Gay-ጌይ) የሚለዉን ለማመላከት ነዉ የሚሉ አሉ። በየዕለቱ በዚህ ባር አካባቢ ፖሊሶች አይጠፉም። ግለሰቡ ኤርትራዊነቱን ሸሽጎ “ሻዕቢያ ሊገድለኝ ሲል ያመለጥኩ የትግራይ ተወላጅ ነኝ” እያለ ከማደናገሩ በተጨማሪ ሴት “ጥንዶች” ወይም ‘ሌዝቢያን’ በብዛት አይጠፉም። ለመግለጽ የሚቀፉ እንቅስቃሴ ሲያደርግ የሚታየዉ ኤርትራዊዉ እና ግብረሰዶማዉያኑ አባላቶቹ በሚለቀቀዉ ዘፈን (ዘፈኖቹም የነጭ እና የሻዕቢያ ናቸዉ)ጣልቃም ከ አየአቅጣጫዉ”አሞሬ”…አሞሬ” የሚሉት ቃላት ይወረዉራሉ። ትርጉሙን ስጠይቅ “ፍቅረኛየ” ማለት እንደሆነና የ“Gay”ዮቹ ቋንቋ እንደሆነ ተረዳሁ። ሽንት ቤት ሳመራ ባየሁት ነገር አስታወኩ! ወዴት ያመራን ይሆን? Published on www.Ethiopiansemay.blogspot.com questions email editor at getachre@aol.com