Monday, May 8, 2023

ኢትዮጵያን በብርሃን ፍጥነት የመደፈር ፈጣን ክስተት የኦሮሙማ እና የትግራዋይነት አጀንዳ ነው! ኦሮሙማ ጸያፍ ቃል ኣይደለም ለሚሉ መልስ ጌታቸው ረዳ Ethiopian Semay May 8, 2023

 ኢትዮጵያን በብርሃን ፍጥነት የመደፈር ፈጣን ክስተት የኦሮሙማ እና የትግራዋይነት አጀንዳ ነው!

ኦሮሙማ ጸያፍ ቃል ኣይደለም ለሚሉ መልስ
ጌታቸው ረዳ
Ethiopian Semay
May 8, 2023

ይህ ጽሑፍ ልጽፍ መነሻ የሆነኝገበታበተባለ አውስትራሊያ ውስጥ በመጎስ ዘውዱ ተሾመ የሚዘጋጅ መድረክ ላይ ከትግሬ ጽንፈኞች ጋዜጠኞች ተመርጦ የተጋበዘውሸዋ ጠልየሆነው ዓድዋዊው ጋዜጠኛዳዊት ከበደ ባህታ” (ሸዋ፤ሸዋ የሚያሰኘው መረን የለቀቀለሽዋ አማራያለው የጥላቻ በሽታው በአውድዮ የተደፈገፈ ማስረጃ ስላላኝ ነው) እና ኤርትራኖችን ደግሞከእባብ፤ ከጊንጥ፤ ከእንሽላሊት ጋር አብረው ያደጉክሬቸሮችናቸው ይልና የኤርትራ ሴቶችን ደግሞነፃ ላወጣናችሁ (ለትግሬዎች ማለቱ ነው) እንጂ እንደባርያ የሚያዩዋችሁ ባዕድ ገዢዎቻችሁ እማ (አማራ ማለቱ ይመስላል- ባዕድ የሚሉት ኣርትራዊያኖች አማራን ነው) ሴቶቻችሁ  እግራቸው ተሎ ባንዴ ነው ከፍተው አንስተው የሚሰጥዋቸው፤ ያውም እንኳን ሴቶች ወንዶቻችሁም ጭምር ትሰጥዋቸዋላችሁእያለ ካሁን በፊትም ሆነ ዛሬም ኤርትራኖችንእባብና አንሽላሊትጋር ያደጉ እያለ በዚህ መድረክ የተደመጠው ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ ባህታ ሲሆን፤ ሌላው ትግሬው ደግሞ  “መሃል ትግራይ በመወለዴ እኮራለሁ’’ የሚለን አዲሱ የትግራዋይነት ብሔረተኛ አቀንቃኙ ሁሉምየኛ የትግሬዎች ሥሪትና ድል ነውባዩ ምልምል ወያኔው የርዕዮቱቴድሮስ ጸጋዬየዓድዋ ድል የትግሬ፤አክሱም የትግሬ ሥልጣኔና ሃይማኖት ፈጣሪውና ሰሪው ዋናው ባለቤት ትግሬ፤መንጋው ምን ያድርግ ጨነቀው በቃ! ወደ ሗላ ሲመለከት ምንጩ አሉላ ሆነበት! ባሻይ አውዓሎም ሆኑበት! ዮሐንስ ሆነበት ወዘተ…. ችግር ሆነባቸው። ምክንያቱም ኢትዮጵያ ውስጥበኮር ስቴትነት” (በአገር ስኳልነት) ትግራይ ነች ወዘተ.. ወዘተ.. የሚለው ቴድሮስ ፀጋየ ተጋባዥ ነበር፤ ይህንን 2022 የተናገረውን ንግግሩ በማስረጃ የተቸሁበትን ለማንበብ   “አምባ ሰሎዳ ወሳኝ አልነበረም ወሳኞቹ የኢትዮጵያ አርበኞች እንጂ! መልስ ለቴድሮስ ጸጋዬ (ርዕዮት) ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay) 6/21/2022” የሚለውን መመለከት ነው።

ከነዚህ ሌላው ከኦሮሞ ጽንፈኞች ተመርጦ የተጋበዘው ደግሞ ግብጽ አገር የሚኖረውሃብታሙ ተስፋዬየተባለአድጎ ያላደገ የኦሮሞ ቄሮአንድ ነገር በተነገረ ቁጥር ከኦሮሞ ሕዝብ ጋር የማያያዝ አባዜ ያለው የኦሮሞ ወጣት በላቲን ፊደልና በኦሮሞ ቋንቋ ብቻ እንዲማር በመደረጉ በሰፊው ገበያ መግባብያ ስለሚያጥረው ከኦሮሞ ክልል ውጭ ሥራ ማግኘት ተቸግሯል’’ ብለው ማሕበራዊ አጥኚዎች ሃሳብ ሲያቀርቡ የኦሮሞ ወጣት ኦሮምኛ ስለተማረአማርኛ ተጎድቷልማለትዎ ነው? እያለ በግልጽ የተነገረው ንግግር ቃላትን የማጣመም አባዜ የተጠናወተው፤ አባቴ አማራዎች አስገድደውት ተገድዶ ነው ከኦሮሞ ስሙተስፋዬወደ እሚለው የአማርኛ ስም  እንዲጠራ የተገደደው ሲል በሚገርም ሁኔታ ግን እራሱ ሃብታሙ የተወለደው በወያኔ ጊዜ ከሆነ፡ ወይንም በደርግ ጊዜ ነው ብንልም እንኳ አንድ ኦሮሞ በነዚህ ጊዜያቶች ስምህ ወደ አማርኛ ለውጠው ባልተባለበት ዘመንሃብታሙየሚለው ስም ሲሰጠው ወላጅ አባቱስ ማን አስገድዶአቸው ነው አማርኛ ስም ሊሰጡት የቻሉት? የሚለው ጥያቄ ፌስቡኩ ላይ ጠይቄ ነበር፤ መልስ የለውም፡ ሆኖም ልጁ ፀረ አማራ መሆኑን በዚህ የተገታ አይደለም፤  ነፍጠኛየሚል ድምጽ በመግቢያ ፕሮግራሙ ላይበጥላቻ ድምፅየሚጀምረው ከግብጽ አገር የሚተላለፈውኩሽየሚባለው እርሱ ራሱ የሚያዘጋጀው ሚዲያ አዘጋጅ ሲሆን በዚህ ውይይት እነዚህ እና ሌሎች ምሁራንም የተጋበዙበት ‘’ዘላቂ ሰላም ምን፤ በማን እና እንዴት ይምጣ?’’ የሚል ውይይት ሲያደርጉ

ኦሮሙማየሚል ቃልፕሮፌሰር ግርማ ተፈራበመጠቀሙ አክራሪው የኩሽ ሚዲያ አዘጋጅሃብታሙ ተስፋዬ፡ኦሮሙማ ማለት እኔ እና ሌላው ሩቅ አገር የሚኖር የማንተዋወቅ ኦሮሞ በደም ትስስር የሚያገናኘን ማለት ነው፤ ምንድነው እርስዎ (ፕሮፌሰሩን ነው) ኦሮሙማን እንደ አውሬ አድርገው ሊያቀርቡት የፈለጉትይልና አዘጋጁ ሞገስ ተሾመ ደግሞኦሮሙማ ማለት ትግሬነት አማራነት ኢትዮጵያዊነት እንደማለት ማለትምኡማማለትነት”.. እንደማለት ነውበማለት ተርጉሞልናል። ጥሬ ትርጉሙ ሃቅ ነው ብለን እንቀበልና በቃላት ትርጉም እንድንረካ ሊነግሩን ይፈልጋሉ። ሆኖም ኦሮሙማ እና ትግራዋይነት የቃላት ትርጉም ሳይሆን ስያሜው ላይ ተተንተርሶ የሚደረገው ድርጊት ነው ወሳኙ አጀንዳ።

 ሁለቱ ትግራዋይነትናኦሮሙማ” ) (ኦሮሞ ኡማ) ስያሜዎች ወደ ሃይማኖትነት የተለወጡበት ዘመን ነው። ወደ ጸረ አማራነትና ጸረ አማርኛ ያቀና አጀንዳ ነው። የፈለገ ሰውኡማማለትነትማለት ነውነትማለት ሌላ ትርጉም ሳይሆንነትማለት ነው በሚል በቀላሉ እንደደጉ ዘመንሳይሆን ተሸምግለን የምንተረጉመው አይደለም።ኦሮሙማ እና ኦሮሚያየሚባሉ ቃላቶች ለጆሮኣችን አዲስ ስሞች ናቸው። ይህ ስያሜ ተከትሎ የመጣውሄጀመኒማለትምየመሬት፤ የሃይማኖት የቋንቋ፤ የሰው መፈናቀልና ጭፍጨፋ የላቲን ቋንቋ መስፋፋት ጋር የተከሰተው እነዚህ ቃላቶች ተንተርሰው ነው።   እነዚህ ወንድሞችኡማማለት ነት ማለት ነውኦሮሞ ኡማ” (ኦሮሙማ) ማለት ኦሮሞነት ማለት ነው ብለው በቀላሉ ልባችን እንዲረጋ ቢሞክሩም ውስጠ ምስጡሩ ግን አፍሪቃኖች አማርኛ እንደ መገናኛ ቋንቋ እንዲሆን ሲጥሩየዛሬኦሮሞዎችግን (ልሂቁም ሕዝቡም አምኖነውበትና ተቀብለውት) አማርኛን ከአፍሪቃ ምድር ውስጥ ተወግዶ የላቲን ቋንቋ እንዲስፋፋ ኦሮሞዎች እንዲጽፉበት ካደረጉት በፌርማና በስብሰባ ካጸደቁ 1000 የኦሮሞ ልሂቆች ስም ዝርዝር ውስጥ ግምባር ቀደም ኦሮሞ አክራሪ ምሁር የሆነው አሰፋ ጃለታ ስለ ኦሮሙማ ትርጉም ቁልጭ አድርጉ እንዲህ ይነግረናል።

The concept of Oromummaa and Identity formation in contemporary Oromo society (Asafa Jalata- The University of Tennessee Knoxville) ትርጉምበዘመናዊው የኦሮሞ ማህበረሰብ ውስጥ የኦሮምማ እና የማንነት ምስረታ ጽንሰ-ሀሳብ (አሰፋ ጃላታ - የቴኔሲ ዩኒቨርሲቲ ኖክስቪል)” የሚለውን ያንብቡ

የኦሮሙማ ጽንሰ ሓሳብ ኦሮሞ ያልሆኑ ነገዶችን ኦሮሞ ማድረጊያ፣ የኢትዮጵያ ነገዶችን ጨፍልቆ በኦሮሞ ባሕልና ቋንቋ መሰልቀጥና መዋጥ፣ የኦሮሞ የተባለውን ሃይማኖት ብቻ እንዲቀበሉ ማስገደድና ባጠቃላይ ሰማዩንም ምድሩንም ኦሮሞ የማድረጊያ ፕሮጀክት እንጂ ኦሮሞነት ወይም የኦሮሞ ማንነት ማለት አይደለም።  ይላል ተመራማሪው አቻምየለህ ታምሩ የአሰፋ ጃለታ ከላይ የተጠቀሰው ጽሑፍ ትርጉም ሲተረጉመው። ይህንን የኦሮሙማ ትርጉም የሚነግረን የርዕዮተ ዓለሙ ፈጣሪ የኦሮሞ ብሔርተኛው ፕሮፈሰር አሰፋ ጃለታ ነው። በሌላ አነጋገር ኦሮሙማ ከኦሮሞ ማንነት ጋር አንድ አይደለም። እንዴውም ኦሮሙማ ለአብዛኛው የኦሮሞ  ሕዝብጸረ ኦሮሞየሆነ ፕሮጀክት ነው። በኦሮሙማ ፕሮጀክት እሳቤ  መሰረት የክርስትና የእስልምና እምነት ተከታይ የሆነ  ኦሮሞ እንደ ኦሮሞ አይቆጠርም። የኦሮሙማ ፕሮጀክት አይዲዮሎጉ ፕሮፈሰር አሰፋ ጃለታ አንድ ኦሮሞ የክርስትናና የእስልምና እምነትን  ከዋቄ ፈታእምነት የሚመርጥ ከሆነ በፍቃዱኦሮሞነቱን እንደተወ ይቆጠራልይላል።  በኦሮሙማ እሳቤ አንድ ሰው ኦሮሞ የሚሆነውየዋቄፈታ እምነት ተከታይ ሲሆን ብቻ ነው ስለዚህ ኦሮሞማ የክርስትናና የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ የሆነውን የኦሮሞ ተወላጅ ጭምር የማጥፊያ ፕሮጀክት ነው።ኦሮሙማ ይኼው ነው። ከዚህ ውጭ ኦሮሙማ ሌላ ትርጉም የለውም!” ይላል አቻምየለህ ታምሩ

ምሁራኖቹ እንደምናውቃቸውና እንደለመዱት እርስ በርስ ሊሞዳመዱ መብታቸው ነው፡ መለሳለስ ልማዳቸው ነው፤ እኛ ግንማፏጨታችንንአናቆምም። ኦሮሙማ ከፍተኛ ሰልቃጭ አጀንዳ ነው።ለምሳሌ አዲስ አበባን ለኦሮሞየከተማዋ ህጋዊ ባለቤትእንዲሰጥ የሚወተውተው የኦሮሙማው ውትዋተውና ኢትዮጵያን በክልል አገሮችመንግስታትመቀየስ ኢትዮጵያን ለመበታተን ቀደም ብሎ እንዳየናት ሶማሊያ እና እንደተበተነቺው ኤስ ኤስ አርየተበታተኑ አገሮችን ለመፍጠር የሂደቱ አካል መሆኑን ስናስጠነቅቅ ዘመናት አልፎናል። ይህ ሁሉ የሆነው በእኛ የንቃተ ህሊና ጊዜ ውስጥ CIA ወኪሎች ማለትምበኦነግ/ኦፒዲኦ/ የኦሮሙማ ዘመን እና በህወሓት ትግራዋይነትዘመን ነው

ወያኔ በጊዜውኦሮሙማለሚባለው ‘’ኦሮሞችን በደም የሚያስተሳስረው (አሀብታሙ ተስፋዬ አንደሚለው) የማንነት አጀንዳ ለማጽደቅ ¾ ዩሆነው የሁሉም ኢትዮጵያዊያን ሰፊ መሬት ኦሮምያ ብሎ ለሰየመው ኦነግ እንዲቆጣጠር ሲፈቅድ ህወሓትለትግራይ ትግርኚ/ወይንም ለትግራይ ሪፑብሊክአጀንዳው የሚውል ሰፊ መሬት የወልቃይና የራያ ለም መሬት አግኝቷል (አሁን በጉለበት ተነጥቋል) ጠቅላላትግራዋይነትማለትበምእራብ እና በደቡብ በዚህ መልኩ ሄጂመኒው ተባብሶ የህወሓት ትግራይ 65,000 ካሬ ኪሎ ሜትር ስፋትና ከባህላዊው እና ከኦፊሴላዊው ቦታ ተነድፎ 102,000 ካሬ ኪሜ. ሙሉ በሙሉ ካርታው ውስጥ ነድፎ አስቀምጦታል። ይህ የኦሮሙማ እና የትግራዋይነት የስልቀጣ ውጤት ነው።

በተመሳሳይ መልኩ የወያኔ ትግራዋይነት ኢትዮጵያን የመበታተን አጀንዳውን ለማራመድ በመኮረበት ወቅት 350,000 ካሬ ኪሎ ሜትር ወይም (አሁንም ከዚህም በላይ) የኢትዮጵያን ግዛት ሙሉ በሙሉ ደቡብ ኢትዮጵያ የሚሸፍነውን በወያኔ ተተኪዎች ባኦነጎች (ኦፒዲኦ) በመሳሪያ ሃይል ተቀርጾ የሲአይኤ የወደፊት ዕጣ ፈንታ እንዲሆን ፈቅዷል።የኦሮሚያ ሪፐብሊክ"!! አሁን ያለውና የቆየው የሶማሊያና የሱዳን ሁኔታን አትርሱ። ንድፎቹንና ክስተቶችን ኣያይዝዋቸው።

ኦሮሙማ እና ትግራዋይነት፤ነትማለት ነው በሚል ሸንጋይ ትርጉም ተደልለን ይህንን አገራዊ ወንጀል እንደ ጥቃቅን እርምጃ ልንደራደር ወይም ልንቀበለው ወይም ዝም ብለን ልንመለከተው አንችልም። ይህ ኢትዮጵያን በቀን ብርሃንና በብርሃን ፍጥነት የመደፈር ክስተት የኦሮሙማ እና የትግራዋይነት ንድፍ ነው! ቢያንስ በአዲሱ የኢትዮጵያ ትውልድ አእምሮ ውስጥ እንዲህ ያለውን ሀገራዊ ወንጀል እና ከውስጥ እና ከውጪ ጠላቶች ሴራ ጋር መጋፈጥ እንዳለበት ላለፉት በርካታ አሰልቺ አመታት ስንጮህና ስናስጠነቅቅ እና ለወጣቶቹ ታሪክ ስንቀርጽላቸው ቆይተናል። በዚህ አምስት አመት አገር የማፍረሱ የኦሮሙማ እና የትግራዋይነት አጀንዳ አፍጥጦ የወጣበት ወቅት ነው።ሆን ተብሎ ኢትዮጵያና ሱዳን እንደ አገርፌይል እስቴቶችእንዲሆኑ ተደርገዋል። በእንደዚህ ዓይነት ወንጀል በማንኛውም ሁኔታ ምንም ዓይነት የፖለቲካ ስምምነት ሊኖር አይገባም። አሁን አይደለም ነገም አይደለም ወደፊትም አይገባም! ኢትዮጵያን ለመበታተን ምንም ስምምነት መደረግ የለበትም። በቃ! ማለት እንልመድ!

የትግራይ ተወላጆች በትግራዋይነት መፈክር በስልጣን ዘመናቸው ያስተጋቡት ትምክሕት የማይረሳ ነው። ባለፉት 27 አመታት ከባሕር በር መዝጋት ጀምሮ አንድ በአንድ እየወሰዱ የነበሩዋቸው እርምጃዎች ስታዩ፣ ኢትዮጵያ ልትበታተን የታሰበችበትን የመጨረሻ ገመደዋን እየበጠሱ (ሲአይኤ ከፕላኑ ጀርባ እንዳለበት አትዘንጉ) ሲጓዙ በመጨረሻ ትግራዋይነት በኦሮሙማ ተነጥቆ አሁን መልህቋ እንዲፈታ ተደርጎ ለመጨረሻ እርምጃ ጋዜጠኞችና ጠበቆችዋ አንድ ባንድ እና በጅምላ ወደ ሞት ገንዳ እየተወሰዱ ናቸው። ትግራዋይነትና ኦሮሙማ ማለት በትርጉም ሳይሆን በግብር ኢትዮጵያን በብርሃን ፍጥነት የመደፈር ፈጣን ክስተት ምክንያት የኦሮሙማ እና የትግራዋይነት አጀንዳ እንጂ ነትትርጉም የምናየው የቃላት ጨዋታ አይደለም።

አመሰግናለሁ

ጌታቸው ረዳ