Tuesday, March 10, 2026

የ1884 ዓመተ እግዚእ የበርሊን ኮንፈረንስ እና የ1882 ዓመተ ምሕረት የዲማ ኮንፈረንስ ተመሳሳይነት ጌታቸው ኃይሌ Ethiopian semay 3/10/26


1884 ዓመተ እግዚእ የበርሊን ኮንፈረንስ እና 1882 ዓመተ ምሕረት የዲማ ኮንፈረንስ ተመሳሳይነት

ጌታቸው ኃይሌ

Ethiopian semay

3/10/26


ፎቶ ቅንብር ከEthiopian Semay


ማሳሰቢያ ከEthiopian Semay ድረገጽ አዘጋጅ


ርዕሱን በሚመለከት፡ 3 ነገሮች እርማት ቢደረግባቸው እላለሁ።

“1882”“ዲማ” እና “ተሰነይ”

«የ1884 ዓመተ እግዚእ የበርሊን ኮንፈረንስ እና የ1882 ዓመተ ምሕረት የዲማ ኮንፈረንስ ተመሳሳይነት» የሚለው ርዕስ «1884 ዓመተ እግዚእ የበርሊን ኮንፈረንስ እና 1991 የሰንዓፈ ማንፌስቶ” ተመሳሳይነት» ተብሎ ቢነበብ የግል አስተያየቴ ለአንባቢ አቀርባለሁ። በ1882 ዓመተ መሕረት ዲማ ውስጥ ምን እንደተፈረመ አላወቅኩም (የ1991 ቅርጫ ግን አውቃለሁ)። (ዲማ ጎጃም ውስጥ ያለ ቦታ (ከተማ/ገጠር/ ይመስለኛል)። ምክንያቱም፤ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ “የተሰነይ ማኒፌስቶ አባባል ምናልባት «የሰንዓፈ ማኒፌስቶ» ለማለት ይሆናል። ምክንያቱም “የኦነጎቹ ወኪል ሌንጮ ለታእና “የወያኔዎቹ ወኪል መለስ ዜናዊ” ኢትዮጵያን ለቅርጫ መስዋዕት ያቀረቡዋት የስምምነት ፌርማ ተሰነይ ውስጥ ሳይሆን ሰንዓፈ (ኤርትራ ውሰጥ በአከለጉዛይ አዋራጃ ውስጥ የምትገኝ ከተማ ነች) ከተማ ውስጥ  እንደነበር ነው እራሱ ሌንጮ ለታ የነገረን።>>

አሁን ወደ ጽሑፉ እንግባ

1884 ዓመተ እግዚእ አፍሪካ ለቅርጫ መሥዋዕት ላይ የቀረበችበት ጉባኤ በርሊን ላይ ተካሂዶ ነበር። ጉባኤውን የጠራችው ፖርቱጋል ስትሆን፥ አዘጋጁ የጀርመኑ ካንስለር ኦቶ ፎን ቢስማርክ ነበር። የጉባኤው ዓላማ የአውሮፓ ቅኝ ገዢዎች አፍሪካን ሲሻሙ ግጪት እንዳይፈጠር የሺሚያ ሕግ ለማውጣት ነበር። ተስማምተው General Act of the Berlin Conference በሚል ስም የታወቀውን ውል አጸደቁ። ኮንፈረንሱ የጎሳ መሪዎች ንግድም፥ጉቦም እያሳዩ የያዙትን ውሉ አጸደቀላቸው፤ ያልያዙትንምሕግ አክብረውየሚይዙበትን ሥርዓት አወጣላቸው። አፍሪካውያን ሳይሰሙ አገራቸውን አውሮፓውያን ተከፋፈሉት፤ (ከኢትዮጵያና ከላይበሪያ በቀር የቀሩትን)

ጉባኤውን ታሪክ The Scramble for Africa “አፍሪካን ሽሚያበሚል ስም መዝግቦታል።

ኢትዮጵያም ተመሳሳይ ወንጀል ተፈጽሞባታል፤ ያውም በልጆቿ። እንዳነበብኩት ከሆነ ሰብሳቢዎቹ ወያኔዎች ሲሆኑ ተሰብሳቦዎቹ እነ ኦነጎች ነበሩ። ውሳኔውየተሰኔ ማንፌስቶበመባል ይታወቃል። አቶ ገብረ መድኅን አርአያ እንደሚለው፥

ፕሮግራሙን በመጻፍና በማሰራጨት ወሳኙን ኃላፊነት የወሰዱት አረጋዊ በርሄ፣ ሥብሃት ነጋ፣ ሥዩም መሥፍን፣ መለስ ዜናዊና ዐባይ ፀሐዬ ነበሩ። ይህ ፕሮግራም ኢትዮጵያን ለመበታተን የተዘጋጀ ቀመር ነበር። ሕዝቡን በዘርና በቋንቋ የከፋፈለ፣ ታላቁን ነገድ ዐማራውን በደመኛ ጠላትነት ፈርጆ እንዲጠፋ መጠነ ሠፊ ዘመቻ የከፈተ፣ የኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት ማጥፊያ ሰነድ፣ እነሆ! ዛሬ የአገሪቱ ሕገመንግሥት ለመሆን በቅቶ የአገሪቱን የጥፋት ጉዞ እያፋጠነ ይገኛል።

የፕሮግራሙ ውሳኔ ደርግ ሲወድቅ ባለቤት-አልባ ኢትዮጵያን ካርታዋን ዘርግቶ ቋንቋን መሠረት በማድረግ ለዜጎቿ ማካፈል ነበረ--ልጆች ከወላጆቻቸው የወረሱትን ርስት እንደሚከፋፈሉ። እግዚአብሔር ነፍሱን ይማራትና፥ የዚህ ወንጀል ቀንደኛው ጠንሳሽ መለስ ዜናዊ ነበረ፤ እንዲህ ሲል ጽፏል፤ ያለፈው የአማራው ትምክህተኛ አገዛዝ ኢትዮጵያዊነት ዘልቆ የተዋሃደውና ከደመ ነፍሱ ጋር የተሳሰረ ነው። ይህንን ከህዝቡ ስነአእምሮ ነቅለን ለመጣል፣ በዘር፣ በጎሳ፣ በቋንቋ ማደራጀትና በዚህ ዓላማ የሚመሩ ድርጅቶችን መፈጠር ነው።

አንደኛ ቊጥራችን ብዙ ነው፤ ሁለተኛ የገዳ ዲሞክራሲ ወራሲዎች ነንየሚሉ የኦሮሞ ፖለቲከኞች ይህ ሊያስታውካቸው የሚገባ ውሳኔ ተዋጠላቸው። አጅሬ ምናምንቴ ቀብቶ፥ ሰፊውን አገራቸውን ነጥቆ በክልል የሚያጉር ሕግ አጐረሳቸው። ዛሬ ካልሆነ አሉ እንጂ፥ ባለው ቢቀጥሉ ከጥቂት ጊዜ በኋላ መላ ኢትዮጵያን ማንም ሳይቈረቁረው ይቈጣጠሯት ነበር። በሰላም አብሮ ከመኖር ተከፋፍሎ መለያየት ለምን እንዳስፈለገ ምክንያቱን ለኋላ እናቆየውና ውሳኔውን የሚደግፉትን አንዳንድ ጥያቄዎች እንጠይቃቸው።

አንደኛ የተወሰኑ ሰዎች ተጠራርተው ሀገርን የሚያህል ነገር ሲያከፋፍሉ፥ኢትዮጵያ የምትባል አባቶቻችን ያወረሱን አኩሪ አገር አለንየሚሉትን በውስጧ የሚኖሩትን ዜጋዎች ድንገት ሀገር-አልባ አደረጓቸው። ውሳኔው ቢያስፈልግ እንኳን ሲሆን ሕዝቡ በውሳኔው መሳተፍ፥ ካልሆነም ማወቅ ነበረበት። ግን ሳይሰማ እንደ ከብት ነድተው ክልል ከሚባል በረት አስገቡት።

ሁለተኛ አከፋፋዮቹ (ወያኔዎቹና ኦነጎች) በወሰዱት አገር ድምበርተኞች ባለመሆናቸው፥ ስለማይጋጩ ለሌሎች ሊገባቸው ከሚችለው መሬት ላይ ድምበር እያለፉ የፈለጉትን ያህል ተሻሙ። ለሌሎች ክልሎች ሊሆን የሚገባውን መሬት የቀሙት ከነሕዝቡ ስለሆነ፥ ሕዝቡንም ማንነቱን እንዲለውጥ አስገድደውታል።

ሦስተኛ ሀገሪቷን ቋንቋን መሠረት አድርገው ተካፈሏት እንላለን እንጂ፥ የሆነው አይደለም። ቋንቋ አፍአዊ ምክንያት ነው። ዋናው ምክንያት ካሁን በፊት ያልነበረች ኦሮምያ የምትባል አዲስ አገር ለመፍጠርና በአውራጃ ደረጃ የነበረችውን ትግራይን አስፋፍቶ እሷንም ራሷን የቻለች አገር ለማድረግ ነው። ክፍፍሉ በቋንቋ ቢሆን ኖሮ፥ ደጋግሜ እንደሳፉትና እንደተናገርኩት፥ አገሪቱ ከሰማንያ ላይ ትከፋፈል ነበር። ውሳኔው በጉልበት ስለሆነ ቍጥረ-አናሳ አቅመ-አናሳ ጎሳዎች ተመሳሳይ መብት አይሰጣቸውም። እሱ ቀርቶ ከሌላው ክፍለ ሀገር የሚያገናኘውን ቋንቋ እንኳን እንዲማሩ ከማይፈቀድበት ሁኔታ እየተገፉ ነው።ዓዋጅ ዓዋጅ!! እናንተ ጥርቅም ጎሳዎች፥ ከዛሬ ጀምሮ ከኢትዮጵያዊነት ዜግነታችሁ ተራቁታችሁ ኦሮሚያዊነት ዜጋ ተጎናጽፋችኋልሊባሉ ነው።

የአባትህ ቤት ሲዘረፍ አብረህ ዝረፍየሚሉት ደርሶ፥ ከአማሮች ውስጥም ትኩረታቸውን ከ“ኢትዮጵያን እናድን” ላይ አንሥተው “ድርሻችን ተቀነሰ” ከሚል ቅሬታ ላይ ያሳረፉ አሉ። ተለያይቶ በጉርብትና መኖርን መርጠው ይሆን ወይስ ኢትዮጵያ ምንም ቢሆን አትፈርስም ብለው ነው? ሁለቱም አስተሳሰብ ስሕተቶች ናቸው።

ክፍያውን ለመግታት አይቻልምየሚሉ ሰዎች አሉን። አገሪቱ ፈርሳለች ማለታቸው መሆኑን ልብ አላሉትም። ውሀ ሲወስድ እያሣሣቀ ነው እንዲሉ፥ ኢትዮጵያም ቍርጡን ሳንረዳ እነሆ እየተበታተነች ነው። ተቀራማቾቹ ነፃነታቸውን ለማወጅና ትዳር ለመውጣት አመቺ ጊዜ ከመጠበቅ ሌላ የቀራቸው መሰናክል ብዙ አይደለም። ወያኔዎችም፥ ተመርምሮ እውነቱ ባልታወቀ ምክንያት እንደነሱ የተከፉና የብሶታቸው መፍትሔ ፍቺ መሆኑን ያመኑ ወገኖችን ይዘው ታሪካቸውን በዲሞክራሲ አንጋሺነት ከማስመዝገብ ይልቅ በአገር አፍራሽነት ማስመዝገብን መርጠዋል። ኢትዮጵያ ለነሱ እናትነቷ ቀርቶ የዓመፅ ንብረት ነች። የሚፈጽሙትም መጽሐፉበዓመፅ ንብረት ወዳጅ ግዛበትየሚለውን ነው። አገር ይገባናል ለሚሉት ሰዎች እነሆ ኢትዮጵያን ቈርሰውኦሮምያእንዲሉት ሰጧቸው። እነሱም አገራችን ነው የሚሉትን አውራጃ አስፋፉ፤ ሱዳንንም ወዳጅ ለማድረግ የጠየቀችውን ያህል መሬት አስታቀፏት።

ማንነት መሬት ላይ አይዘራምበሚለው ጽሑፌ ውስጥኦሮሚያ በተባለው ምድር ላይ በዓሥራ ስድስተኛው ምእት ዓመት በረይቱማና ቦረን እስኪወሩት ድረስ አንዳች ኦሮሞ ዝር አላለበትም ነበርስላልኩኦሮሞዎችን መጤ አደረግሃቸውየሚል ወቀሳ ደርሶብኛል። አሁን ለያዙት ምድር መጤ ያደረጋቸው ታሪካቸው እንጂ እኔ አይደለሁም። ግን መጤነታቸው ለዚያ ቦታና በዚያ ዘመን እንጂ፥

ከዚያ ዘመን በፊትና ከዚያ ዘመን በኋላ ለሆነው ታሪካቸው አይደለም። ለዘመኑ ቅርብ የነበሩት ሊቅ ታሪክ ጸሐፊ አባ ባሕርይ እንደመዘገቡት፥ በረይቱማና ቦረን በአፄ ወናግ ዘመን (1500-1533) ከምዕራብ ወጥቶ ገለና የሚሉትን የሀገሩን ወንዝ ወደባሌ ዳርቻ ተሻገረ።እስከዚያ ዘመን ድረስ ባሌ የሌሎች ኢትዮጵያውያን መኖሪያ ነበረች። ግን የተሻገሩት ከአንድ የኢትዮጵያ ምድር (ከባሕር ገሞ) ወደሌላው ምድር እንደሆነ መረጃዎች ስለሚመሰክሩ፥ በምንም ዘመን ኢትዮጵያውያንነታቸን የምንጠራጠርበት ምክንያት የለንም። ሆኖም፥ እነዚህ ነገዶች ለከብቶቻቸው ግጦሽ ፍለጋ የትውልድ ሀገራቸውን ትተው ማንነታቸውን ግን ይዘው ወደማህል ኢትዮጵያ መምጣታቸው እርግጥ ነው። ዛሬ ወራሲዎቻቸው ነን እንደሚሉት፥ ማንነት ከመሬት ላይ የሚዘራ፥ መሬቱንም ሲለቁ ባህላቸው ወደኋላ የሚቀር ቢሆን ኖሮ፥ በረይቱማና ቦረን ከትውልድ ሀገራቸው ልውሽ አይሉም ነበር።

ማንነት መሬት ላይ አይዘራምማለት አንድ ሰው ከትውልድ አገሩ ጋር ያለውን ትስስር መካድ አይደለም። ሁሉም ተወልዶ ላደገበት የማይፋቅ ፍቅር አለው። እርግጥ አንድ ሰው ሕይወቱን ለማሻሻል ከትውልድ ሀገሩ ወጥቶ ወደሌላ ቦታ መሄድ የተለመደ ነው። ቢሄድምየትውልድ አገሩንሲያመቸው እየተመላለሰ ይጐበኛል። ምናልባት ሲሞትምአገሬ ቅበሩኝብሎ ይናዘዝ ይሆናል። አሁንም በተመቸች አሜሪካ የምንኖር ኢትዮጵያውያን የተወለድንባት መንደር የምትናፍቀን ስለዚህ ነው። ከመሬት ጋር ትስስር ማለት ይህ ነው። የሰውን ልጅ ከዚህ ዓይነት ፍቅርና ትስስር ማለያየት ትልቅ ወንጀል ነው። ኦሮሞዎች ላይ እንደ ሕዝብ ይህ ግፍ አልተፈጸመባቸውም። ይህ ኦሮሞዎች ዛሬ በሺ በሚቆጠሩ አማሮች ላይ የሚፈጽሙት ወንጀል ነው። ነፍሰ ገዳዮች ናቸው።

የአባ ባሕርይ ስም ሲነሣ፥ የሚበሳጩ የኦሮሞ ፖለቲከኞች፥ በዚያው አንጻር ጆሯቸውን ጣል አድርገው የሚያዳምጡ የታሪክ ተመራማሪዎች አሉን። ብዙ የታወቁ የታሪክ ምሁራን (ኢትዮጵያውያን፥ኢጣልያኖች፥ ጀርመኖች፥ ወዘተ.) ስለ ኦሮሞች ጽፈዋል። ሁሉም ጥናታቸውን የመሠረቱት በአባ ባሕርይዜናሁ ለጋላላይ ነው። ዶክተር መሐመድ ሐሰን በዚህ ዓመተ ምሕረት ባሳተመው መጽሐፍ ውስጥ አባ ባሕርይንና ዜናሁ ለጋላን “Abba Bahrey’s Zenahu le Galla and its Impact on Emperor Za-Dengel’s War against the Oromo, 1603-1604” በሚል ርእስ በአንድ ሙሉ ምዕራፍ ተችቷቸዋል።

የበረይቱማና የቦረን ልጆች ወደማህል ኢትዮጵያ ከመፍለሳቸው በፊት የነበረውን ታሪካቸውን የሚናገር ተጨባጭ ማስረጃ የለንም። የነዚህ ጎሳዎች ኢኮኖሚ ከብት ማርባት ላይ የተመሠረተ ስለሆነ ከከብት አርቢነት የተለየ ታሪክ ያላቸው አይመስለኝም። ወደማህል ኢትዮጵያ ሲፈልሱ፥ የነባሩን የክርስቲያን ሕይወትና ቅርስ ገዳ በሚባለው የጂሃድ ሥርዓታቸው መንግሥቱን ስላናጉትና የሀገሪቱን የጥንት ቅርስ ስላወደሙት፥ ሊቃውንቱ የወረራ እርምጃቸውን በዝርዝር መዝግበውታል። ስለዚህ የበረይቱማና የቦረን ልጆች ታሪክ ከማናቸውም የኢትዮጵያ ነገድ ታሪክ ይበልጥ ተጽፏል። የኢትዮጵያ ታሪክ መጻፍ የተጀመረው ሌሎቹ ነገዶች አገሪቷን ከወረሱ በኋላ ሰለሆነ፥ የጥንቶቹ እንዴት እንደወረሷት የሚታወቅ ነገር የለም። ኦሮሞዎች ማህል ኢትዮጵያን የወረሱት፥ የነባሩን ሕዝብ ኢኮኖሚና የሀገሪቱን ቅርስ እየደመሰሱ ቢሆንም፥ በዘመነ መሳፍንት ተዳክማ የነበረችውን ኢትዮጵያ በማጠንከርና የሥነ ጽሑፍ ቅርሷን በማዳበር ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርገዋል። የደራሲዎቻችንን ማንነት በስማቸው ማወቅ

አይቻልም። ብቅል የገደለውን ብቅል ያነሣዋል ይባላል። ስጋታችን ብቅል የገደለውን ብቅል ይቀብረዋል እንዳይሆን።

 Ethiopian Semay