Tuesday, March 17, 2026

ወረበሎች፥ የሰነፎች፥የከሃዲዎችና የአድርባዮች መንጋ የሚፈነጩባት ኢትዮጵያን ለማስተካከል አፄ ቴድሮስ እና ሐቢብ ቡርጊባ ከየት እናግኛቸው? ጌታቸው ረዳ Ethiopian Semay 3/17/26

 

የወረበሎች፥ የሰነፎች፥የከሃዲዎችና የአድርባዮች መንጋ የሚፈነጩ ኢትዮጵያን ለማስተካከል

አፄ ቴድሮስ እና ሐቢብ ቡርጊባ ከየት እናግኛቸው?

ጌታቸው ረዳ

Ethiopian Semay  3/17/26

 

ትግራዊው-ወያነ ወደ ሥልጣን ከመጣበት አፓርታይዳዊ ባልካናይዘሺን "Apartheid balkanization” በሕገመንግሥት ካሰፈረበት ጀምሮ ያንን በነገድ ቋንቋ (በዘር) ከፋፍሎ የሚያስተዳድረውን የአፓርታይዱን ማኒፌስቶ በማስቀጠል ላይ ያለው እሰካሁኑ የኦሮሙማዊው ኦሆዲድ የአብይ አሕመድ ሥርዓት ድረስ ኢትዮጵያ የወረበሎች የሰነፎች የከሃዲዎች እና የአድርባዮች መንጋ የሚፈነጩባት አገር ሆናለች።

በዚህ ርዕስ ሊደፈሩ የማይችሉና ዋጋ የሚያስከፍሉ ግን ጠቀሜታ ያላቸው ለአገር ጠቀሜታ ተብሎ በድፍረት ሃቁን የዘረገፉ አገራቸው የወረበሎች፥ የሰነፎች፥የከሃዲዎችና የአድርባዮች መንጋ መፈንጫ ስትሆን በቸልተኝነት ያልተመለከቱ ፤ በቁርኛነታቸውና ለሃገር ፍቅር ራሳቸውን የሰጡ መሪዎች ፤ ተያይዞም፤ ከመሪዎች ጋር ሳይጣጣሙ ቆይተው ሃገር በጠላት እጅ ስትወድቅ ከተቃወሙዋቸው መሪዎች ጎን ሆነው ጠላትን መክተው መስዋዕት የከፈሉ ጀግኒት አንስቶች በታሪክ የሚታወሱ ጥቂት መሪዎችና የተራ ዜጎች ሚና እና ታሪክ እንመለከታለን

ዛሬ እነዚያን የሚመስሉ “ጥቂቶች” ፈልጎ ለማግኘት እያስቸገረ ነው።

ለአገር ሲባል የማይደፈርን ድፍርት ደፍረው ራሳቸውን ለአደጋ የጋረጡ መሪዎች እና ዜጎች፤ በየትውልዱ እየታወሰ የኖረ በዚህም ጎልተው በዓለም ታሪክ የተመዘገቡ ጥቂቶች ከሃገር መሪዎች «አፄ ቴድሮስ እና ሐቢብ ቡርጊባ» ከተራ ዜጎች ደግሞ የጎጃም ተወላጂትዋ ምንትዋብ የማነን እንመልከታለን።

ቱኒዚያ-ሐቪብ ቡርጊባ

ሃይማኖትን አመካኝቶ ስንፍናን ሲከተል የነበረው የቱኒዚያ እስላማዊ ሕዝብ ሊደፈር የማይቻል ደፍሮ የተጋፈጠው ቱኒዚያ ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ነፃ ሰትወጣ 1956 የመጀመሪያው የቱኒዚያ መሪን ስላስመዘገበው ድፍረት እንመልከት!

1956 . ነፃ የወጣችው የመጀመሪያው የቱኒዚያ መሪ የነበረውሓቢብ ቡርጊባይባላል። የእስልምና ተከታይ የሆነውን የቱኒዚያን ሕዝብ ያልተጠበቀቦልድፈጣጣ ውሳኔወስዶያደርገዋል ተብሎ ያልተጠበቀ አስገራሚ እርምጃበሕዝቡ ላይ ተቀባይነት አግኝቶ እስከዛሬ ድረስ ሲታወስ ይኖራል።

ምንድ ነው ያደረገው? ከገዛሁት አመት ሆኖኝ አንብቤ ሳልጨርሰው በመጀመር በማስቀመጥ ላይ ያለሁት መጽሐፍ Conflict, Culture, and History (regional Dimensions) የሚል በአምስት ደራሲያን የተጻፈ መጽሐፍ ሳነብ በእስልምና እምነት ተከታዮች ጭንቅላት ውስጥ የገባበትን አስተሳሰቦችን የመለወጥ ጥበቡ የሚገርም ነበር።

አገሪቷ በቅኝ አገዛዝ ስትማቅቅ ኖራለዘብ ያሉ እስላማዊ ሃይላትንያቀፈ አክራሪ እስላሞችን የተቃወመ መሪ ነበር። አስገራሚው ውሳኔው ቱኒዚያ ድህነት ስላጠቃትበሮመዳን ጾምበቴ/ቪዥን ቀርቦ የብርቱካን ጭማቂ የያዘ ብርጭቆ በመያዝፉትእያለ ለሰከንዶች ቃል ሳይተነፍስ አፍጥጦ ተመልካቾቹን ያይ ጀመር፤ ወቅቱየሮመዳን ጾምነበርና የብርቱካን ጭማቂ የመጠጣቱን ትዕይንት ተመልካቾቹበድንጋጤተውጠው ይመለከቱት ጀመር።

እንዲህም አለ፦

ወቅቱ ሮሞዳን መሆኑን አውቃለሁ። ብዙዎቻችሁ ስራ ከመስራት ተቆጥባችሁ በየመስጊዱም ሆነ በየቤቶቻችሁ አጥልላችሁ አርፋችሁ ተቀምጣችሁ አያለሁ። ሆኖም ሸሪዓ በሮማዳን ወቅትአትስሩ’ ‘እረፉአላለም ሸሪዓ ሥራን አይቃወምም የገባንበትን አስፈሪ ድህነትበጂሃድመመታት እንዳለበት ሸሪዓ ያዝዛል ሕዝባችን በድህነት እየማቀቀ አጋዥ አቅም ሳይኖሮው ድህነትን ማሸነፍ ከቶ አይቻለውም። ጂሃድ ሰይፍ አንስቶ በጦርነት መሳለፍ ብቻ አይደለምስራም ጂሃዳዊ ግዴታ ነውስለዚህም አቅም ሊሰጠን የሚችል አጋዥ ሃይልሳንኮንንየገባንበትን የምጣኔ ሃብት ግንባታ ተሎ ካላፋጠንን የባሰውን ጭንቅ ውስጥ መግባታችን አይቀሬ ነው!”

በማለት እዛው ቁጭ ብሎ የሚታየውን የሸሪዓውን እውነታ እንዲመለከቱት አዘናጊውን የአስተሳሰብ ዘይቤን በገንቢ አስተሳሰብ መዝዞ ለመለወጥ ወቅቱ የሚጠይቀውን ፈተና መጋፈጥ ምን ያህል ቆራጥ ድፍርት እንደሚጠይቅ ከሓቢብ ቡርጊባ ታሪክ ሳንብብ በጣም ተመሰጥኩ

ይህንን በማድረጉ በአክራሪ እስላሞች ምን ያህል አስጨናቂ ፈተና እንደሚደርሰው የውቃል። ሆኖም እውነታውን በድፍረት መጋፈጥ ያንድ መሪ የመርሕ ባሕሪ ነበርና ያንን አድረጓል።

ቡርጊባ ለማለት የፈለገው፤ በጂሃድ ጦርነት ውስጥመግደፍይቻላል ሳትበላ ከባዱ ጦርነት ላማካሄድ አቅም ያንሳሃል፡ ስለሆነም መግደፍ ይፈቅዳል ድህነት እና አገር ግናበታምሌላው ጂሃድ” (ጦርነት) ስለሆነ አቅም ሊሰጣችሁ የሚችለውን ሁሉ ሳትኮንኑ ሳታርፉ ድህንትን መዋጋት ሸሪዓ ይፈቅዳልና ድህነትን ተዋጉ ማለቱ ነው። ባጠቃላይ ሊደፈር የማይቻለውን ውነታ ደፍሮ በተግባር ማሳየት ካንድ መሪ የሚጠበቅ አስገራሚ ክስተት ነው። ያውም እስላማዊ አገር መሪ ሆኖ!

አፄ ቴድሮስን እንመልከት

ወረበሎችን (ሽፍቶችን) ፤ የቀሳውስት ሰነፎችን፤ አድርባዮችን፤ ሰለ አገር ክብር እና መልካም ዝናን ለማስጠበቅ ራስን መስዋዕት መሆንን በንጉሡ ዓይን እንመልከት።

አፄ ቴድሮስ አድርባዮችን አይወዱም ነበር።  ወዳጄ ደራሲ አማረ ብሻው «አጤ ቴዎድሮስ ለኢትዮጵያ ትናንትም ዛሬም ነገም» በሚለው መጽሐፉ በገጽ 121 ላይ ንጉሡ አድርባዮችን እንዴት ይጠየፉዋቸው እንደነበር ያብራራበትን እንይ፡

ደጃዝማች ካሣ (አፄ ቴድሮስ አፄ ከመባላቸው በፊት) ደጃዝማች ውቤ ለካሳ እጃቸው በሰላም እንዲያስረክቡ ቢጠይቁዋቸው አሻፈረኝ ሰላሉ በውግያ ከማረኩዋቸው በኋላ፤

ደራሲው እንዲህ ይላል፡

«በሰላም እጅዎን ይስጡ ብየዎት እምቢ በማለት እነሆ  ይህን ውርደት ተቀበሉ፤ አሁንም ያለዎትን ንብረት አስረክቡኝ» በማለት ጠየቅዋቸው ደጃዝማቹም «ወታደሬ በጁ የያዘው ካልሆነ በቀር ሌላ ንብረት የለኝም” አሉ። ደጃዝማች ካሣም የደጃዝማች ውቤን ንፉግነት ሰምተው ስለነበሩ፤ “ደጃዝማች እብክዎን ንብረትዎም  እርሰዎም በእጅ ስለሆኑ ቢያሥረክቡ ይሻላል» በማለት ቢጠይቅዋቸው ፤ «ወታደሬ በጁ የያዘው ካልሆነ በቀር ሌላ ንብረት የለኝም” አሉ። የደጃዝማች ካሣ ወታድሮች  በዋሻ የተደበቀው ንብረት ሲፈትሹ  ገንዝብ ብቻ ሳይሆን በጋን መርፌ ሞልቶ ተገኝ።

ደጃዝማች ካሣ ደጃዝማች ውቤን አስጠሩና “ንብረት የለኝም ብለውኝ ነበረ፤ ይህ የማን ነው?” ሲሉ ጠየቁዋቸው ደጃዝማች ውቤም « ለከፉ ቀን ይሆናል ብዬ ነው» ሲሉዋቸው  ደጃዝማች ካሣም ፤ «ቆፍጣጣ! ከዛሬ ወዲያ ምን ክፉ ቀን አለ፤ ለክፉ ቀን ያስቀመጡትን መጠቀም  ካልተቻለ ምን ክፉ ቀን አለ?” አሉዋቸው።

ያ እንዲያ እያለ ፤ የደጃዝማች ውቤ አሽከሮችም ወደ ደጃዝማች ካሣ መጡና እንዲህ ሲሉ ጠየቁ፡

« እኛ ልንሸለም ይገባናል ይህን ያደረግነው እርስዎን ለመርዳት ብለን ነው» አሉ።

ደጃዝማች ካሣም

«እኔ ጌታውን ከከዳ አሽከር ጋር አንድነት የለኝም! እሰረው! ከጌታው ጋር» ሲሉ አዋርደዋቸው። ፊታውራሪ ኮከቤ እንዳውም በደጅዛማች ካሣ “የቃሪያ ጥፊ” ቀመሱና ወደ እስር ቤት ተወረወሩ።

Wondering among the Falasha በሚለው መጽሐፍ ሳነብ የሚከተለው አየሁኝ፡

በታህሳስ 1860 ንጉሱ በደብረታቦር አቅራቢያ በጃን ሜዳ ሰፍረው በነበሩበት ወቅት በግብፅ ምክትል አለቃ በሴይድ ፓሻ የተላኩትን የኮፕት ፓትርያርክ ቄርሎስ ይዘውት የመጡትን መልእክት ተቀበሉ።

ንጉሡ ፓትርያሪኩን ሲያነጋገሩ ፤ ወደ አገሩ ከመጡ ጀምሮ በአቢሲኒያዎች ላይ ያሳዩት ከፍተኛ ኩራትና ንቀት በመታዘባቸው፣ንጉሡም በምጸት ዓይን  እየተመለከቱ “እርስዎ ሊቀ ጳጳሳት ነዎት ፤ ታዲያ እርሰዎ የመሐመድ ተወካይ ሆነው ሹመቱን መቀበልዎ አስገርሞኛል፡ እርስዎን የመሰለ ኩሩ እና ብልህ ፓትሪያሪክ ይህንን ውክልና መቀበልዎ ለክርስቶስ ፍቅር ወይስ ለሰይድ ፓሻ ፈቅር ያለዎትን እምነት ነው? ሲሉ  በአሽሙር ምጸታዊ ቃና ጠየቅዋቸው። ከዚያም አቡንን በንጉሣዊው ካምፕ ውስጥ እንዲታሰሩ አዘዙ።

ንጉሡ ወደ ሥልጣን ከመምጣታቸው በፊት አገሪቱ ውስጥ ቀምኛና ሽፍታ በየቦታው ሕዝቡን ያስጨነቀ ተዕይንት ነበር፡ ስርቆት እና ግድያ አሁን ባለው የግዛት ዘመን  በተሳካ ሁኔታ የታፈነ ሲሆን ፤ ቀማኞችና የተደራጁ ወረበላ ሽፍቶች በአሁኑ ጊዜ በአቢሲኒያ ደጋማ ቦታዎች ላይ እንደ ምርጥ የአውሮፓ ግዛቶች ሰላም የሰፈነበት ሆኖ እምብዛም ብዙ ወሮበላ አይታይም። ከዚዝያ በፊት ማራኪ በሆነው የገጠር መንደር ውስጥ፣ እንደ ብርጭቆ የሚያንጸባርቀው የጣና ሀይቅ ቅርብ የሆኑ መንደሮች ውስጥ ለብዙ አመታት ሕገ-ወጥ የሆነ ማጋጭ ወሮበላ እንደ አሸን ፈልቶ የነበረበት ማህበረሰቡን በሕገወጥ የሰው ዝውውርን ( ሰው መሸጥ...) ለብዙ አመታት ሲካሄድ የነበረበትን ሁኔታ ንጉሡ አስቆሙት።

የትደራጁ ሽፍቶችና ሰው አዝዋሪዎች ከሽፍትነት ለማስወጣት ንጉሡ የሚተዳደሩበት መተዳደርያ ሰጥተዋቸው ነበር።ሆኖም  እነዚህ አመላቸው መተው ያልቻሉ ሰዎች ፤ የምንንቀሳቀስባቸው አካባቢዎች ጭምር ይሰጠን በማለት ተደጋጋሚ ስሞታ በማሰማታቸው፤ ሲሰሙ ንጉሡም መደበኛ ቅሬታቸውን በሉዓላዊው የግዛት መሪው ፊት በአካል ቀርበው እንዲያስረዱና ለመዘዋወር ያሰቡበትን ወሰኖችና ቦታዎች ለማሳወቅ ተወካዮች ላኩ ብለው ላኩላቸው።

ንጉሡም ይህንን ስሞታ ለመስማት ተቀምጠው በጥሞና የተወካዮቹን ስሞታ አደመጡ። ካሁን በፊት በተደጋጋሚ አነጋግሬአችሁ ይህንን የሽፍትነት ሥራችሁን አቁማችሁ ወደ ግብርና በመግባት የምታርሱባቸው ማሳዎች ፥የኮርማዎችና የበርካታ ላሞችን እንዲሁም የምታርሱባቸ ሞፍር ቀምበሮች እንዲሰጣችሁ አድርጌ በዚህ ተስማመታችሁ ስታበቁ አሁን ግብርናውን እንደማትቀጥሉብትና ወደ ሽፍትነታችሁን  እንደምትመለሱበት ነው የተረዳሁት፡ ሲሉ በጥሞና ለማስረዳት ሲሞከሩ ፤ ተወካዮቹ ጮክ እያሉ ድፍረት በማሳየታቸው እንደነበርንበት እንጂ ግብርናው አልጣመንም፤ ሲሉ ራስ ዓሊን ያስፈራሩበት የነበርውን ባሕሪያቸው አፄ ቴዎድሮስ ላይም የሚሰራ መስሏቸው የቀማኛዎቹ ድፍረት የንጉሱን ቁጣ አባባሰው።

በመጀመሪያ፣ እያንዳንዳቸው የኮርማዎችና የበርካታ ላሞችን ተቀብላችሁ ሕዝቡን የምታስፈራሩበት አፈሙዝ በገበሬ ጅራፍ ለውጡት ብያችሁ ተስማምታችሁ ነበር ፣ ነገር ግን ከሽፍታነት ወደ ገበሬነት መቀየሩን ጣዕም አልሰጠንምና ሕዝቡን ሰላም እናውካለን ሰውን ማዘዋረችንን እንቀጥላለን ማለት ከዚህ ወዲያ አይቻልም! በማለት ተወካዮቹ በወታደሮች ታጅበው እንዲረሸኑ አዘዙ።

(......They had defied Ras Ali, and their prowess, they also thought, had intimidated the king Theodros, but, to their surprise, on presenting themselves a few days afterwards in a strong-armed band, they found, instead of good-humored monarch, a stern judge; and instead of civil courtiers, a formidable line of troops to lead them to execution.)

Henry Arron Stern በመቀጠል

ሄንሪ አሮን ስተርን “wandering among the Falashas” በፈላሻዎች መንደር (ዑደት) በተባለ መጽሐፉ ላይ ንጉሡን ሰላም ለማለት ወደ ግቢው ስንሄድ ንጉሡ የተቀመጡበት ቦታ ግርማ ሞገስ በጎደለው አኳኋን በተንጣለለ ግድግዳ በፈራረሱ ድንጋዮች ላይ ደብዛዛ ቦታ ላይ በሺዎች የሚቆጠሩ የቀድሞ ተዋጊዎችና አጃቢዎች በአንድነት ተሰብስበው ተቀምጠው አገኘናቸው።ወዲያውኑ ንጉሡ በግምባሩ ኑ ቅረቡ ብለው ምልክት በመስጠት ወደ እሳቸው እንድንጠጋ ጠሩን።

<<ልጆቼ እንኳን ደህና ጣችሁ>> በማለት ሰላም ካሉን   በኋላ፤ ካሁን በፊት በሌሎች ሥፍራዎች ያላየነውን ስለ መልካም አቀባበላቸው ተደስተን በአጸፋው እኛም

«ግርማዊነትዎ ሆይ!  በሀገራችን ልማድ መልካም የትዳር ትስስር የገቡትን ሳይቀር እንኳን ደስ ላችሁ’ ማለት የተለመደ በሀገራዊ ልምዳችን እራሳችንን በደስታ ለመግለጽ በግዛቱ ውስጥ ይህን የመሰለ ሁለንተናዊ እና ልባዊ ደስታን ያስገኘ ክስተት ላይ በማየትና በመገኘታችን እንኳን ደስ አለዎት ለማለት ያለንን ልባዊ ምኞት እና ጸሎታችንን ለእርስዎ ለማቅረብ እንወዳለን።» ስንል

ግርማዊነታቸው <<ወገኖቼ>> ለው ፈጥነው እንዲህ ሲሉ መለሱልን

- “<<ወገኖቼ ክፉዎች ናቸው ዓመፅን ይወዳሉ ሰላምንም ይጠላሉ፥ ሥራ ፈትነት ደስ ይላቸዋል፥ ኢንዱስትሪን ይጠላሉ፥ ነገር ግን እግዚአብሔር ሕይወቴን ቢቀጥልልኝ፣በማለት በሚያንጸባርቅ ግርማ ቀና እያሉ << ያን ሁሉ መጥፎ ነገር አጠፋለሁ፣ ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን መልካም የሆነውን ሁሉ አስተዋውቃለሁ።ከዚያም አገሬአሁን ካለበት የበሰበሰ የሞራል፣ የማህበራዊ እና የሃይማኖት ውድቀት ላላቅቃት እና ላሳድጋት ፍላጎት አለኝ።» በማለት እንዲህ ያለ ተስፋ ሰጪ ትንቢት ከንጉሡ ስንሰማ እኛም ተደስተንአሜን በማለት በድጋፍ ተነፈስን።ሲል ምስክርነቱን ጽፏል።

ንጉሡ ሥራ በማይወዱ አንዳንድ አውደልዳይ መነኮሳትና ቀሳውስት ላይ በጎ እይታ አልነበራቸውም። የፀሐይ ቆብ ደፍቶ ፥ መነኩሴ መስሎ ከገዳሙ እየለቀቀ ከተማ ገብቶ የቅንጦት ኑሮ በመጀምር ፡ የሚያምታታውን ቄስና መነኩሴ ደግሞ “ኩፌት ደፊ፤ ጢም ከፍካፊ፥ቀሚስ አንዘርፋፊ ሁሉ  ከፊቴ አጥፉልኝ» ይሉ ነበር። ( ቀሲስ አስተርአየ ጽጌ ‘ጠልሰም በዲሲ ደብተራ’ ከሚል መጣጥፋቸው አማረ አፈለ ብሻው በምጽሐፉ እንደጠቀሰው)፡~

የአፄ ቴድሮስን ሥምና አስተዳደር የሕበረተስቡ መድቦችና ነገዶች በራካቶች ቢኖሩም፣በግምባር ቀደም ተቃዋሚዎች ብዙዎቹ ቀሳውስቶች ነበሩ። ቴዎድሮስ የቤተክሕነት ዕውቀት በሚገባ እንዳጠኑ የጎበኙዋቸውፕሮተስታንቶች እንደመሰከሩላቸው ካነበብኩዋቸው የውጭ ጸሐፊዎች አይቻለሁ። ካገኙዋቸው የሀገር ቀሳውስቶችም ክርክር እንድሚገጥሙና ቀሳውስቱ ያላቸው ሃይማኖታዊ ዕውቀት ሲመዝኑ ታይተዋል።

አንዳንድ ፕሮተስታንት ምሺነሪዎች በዙዎቹ የኢትዮጵያ ቀሳውስት በቂ የመጽሕፍ ቅዱስን ጥናት በሚገባ ያላጠኑ ናቸው እያሉ እንድሚያሙዋቸው ስለሚሰሙ ማንኛቸውም መነኮሳትና ቀስውስቶች በቂ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምሕርትና ከነ መዕራፋቸው ብዛት ሳይቀር ዕውቀት እንዲኖራቸው ይወተወቱ ነበር

በዚህ የተነሳ መነኮሳቱና ቀሳውስቱ ማስተማራቸውን እየተው ከተማ ውስጥ በየመሸታው ስለሚወሉ እና በዓላት እያመካኙ ሳያርሱ ሳይጎለጉሉ ተወዝፈው ስለሚውሉ፤ ንጉሡ ይህንን ልማድ እንዲተው ሰለወተወቱዋቸው ፤ ንጉሡ አገር ለማሳደግ ሲነሡ ‘’ንጉሡ ፐሮተስታንት ነው’’ እያሉ ሃሜት እያሰራጩ ወታደሩ እንዳይዋጋ ባንዳንድ ቦታዎች ማውገዝም ጀመሩ።

አማረ አፈለ ብሻው በመጽሐፉ ላይ ቀሲስ ዘመነ አቡሐይ ደስታ «የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን አጭር ታሪክ በተባለው በገጽ 76 መጽሐፋቸው ላይ ይህንን አስመልክቶ እንደጠቀሰው እንዲህ ይላል፡

«ቤተክርስትያን ውስጥ አስተዳደራዊ ለውጥ ለማምጣት ካላቸው ፍላጎት የአገለጋይ ካሕናት ቁጥር እንዲወሰን ቀዳስያን 5 ብቻ እንዲሆኑ የቤተክርስትያን የመሬት ይዞታ እንዲቀነስ በማድረጋቸው ካሕናቱ ጋር እንዲጣሉ ምክንያት ሆኗል። በአጠቃላይ በጎ ራዕይ ያላቸው ለውጥ ፈላጊ የሀገር መሪ ከመሆናቸው የተነሳ ይከተሉት የነበረው የዘመናዊነት ፖሊሲ በሃገር ውስጥም ሆነ በውጭ አልተወደደላችወም» ሲሉ ጽፈዋል።

በዚህ የተነሳ ንጉሡ ከእንግሊዞች ጦርነት ገጥመው ራሳቸውን በጀግንነት ከሰው በኋላ ቄሶች ያድረጉት ጉድ አሳዛኝ ነበር።

ኢትዮጵ ጋዜጣ ግንቦት 18 ቀን 1996 ዓ.ም ገጽ 15 እንዲህ ይላል።

«ከኔ የሚቀጥሉት መሪዎች ያስተካክሏት ይሆናል ብለው ተከዙ። ጦርነቱ ግን አሁንም ተፋፍሟል። የጠላት ጦር ተራራውን እየቧጠጠ ወደ አምባው መውጣት ይዟል፤ ድንኳኖች በሚተኮሱ ጥይቶችና መድፎች በእሳት ይቀጣጠላሉ፤ እንዲሁም ቤቶች። አፄ ቴዎድሮስ አገራቸው በሲቃና በሰቀቀን  ከተሰናበቱ በኋላ እጃቸውን እንደ መስቀል  አድርገው አማተቡ፡ ወደ መቅደላ መድኃኔዓልም ፊታቸን አዙረው ሰገዱ፡ ተከታዮቻቸው ራሳቸውን ለማደን  አሰናበቱአቸው። የእቴጌ ጥሩ ወርቅ ለቅሶና ተማጽኖ ከዓላማቸው አላነቃነቃቸውምበዓለማዮሁ ሞት እጃችንን እንስጥ ቢሏቸው አልሰሙዋቸውም“ለዓለማየሁ የምተውለት ኑዛዜ “አንዲት ኢትዮጵያ በዓይኑ እንደዞረች ሞተ ብለሽ ሲያድግ ንገሪው ብቻ አሉ። ሽጉጣቸውን ወደ ራሳቸው አነጣጥሩና ተኮሱ ፤ራሳቸውን ገደሉ፡ የክበር ሞት ሞቱ።» ሲል ጋዜጣው ጽፏል።

አማረ አፈለ ብሻው እንዲሕ ሲል ያክልበታል፤

« ንጉሡ እሰከመጨረሻው ለመታገል ባደረጉት ትግል በትግላቸው ባስገኝዋቸው ድልና የክብር ሞት ሞቱ። በእንግሊዝ ጦር አለመማረካቸው ክብርንና ታሪክን ለሚወድ ለኢትዮጵያውያን ክብር አጎናጽፈውናል።» ይላል።

እዚህ ላይ የቀሳውስቱ መጥፎ ገመና ሳልገልጽ አላልፍም፤

ታስረው ከነበሩት ከፈረንጆች መጽሐፍት እንዳነበብኩት አፄ ቴዎድሮስ ራሳቸውን ከሰው በኋላ ልብሳቸው ተተልትሎ ግማሽ እርቃናቸው እንደነበሩ ይናገራሉ። ታዲያ ይህንን መልሶ በደራሲው በአማረ አፈለ ብሻው መጽሐፍም በድጋሚ አነበብኩና ይህንን ለማወቅ ሬሳቸው ተንጋሎ ልብሳቸውን ቀዳድዶ እርቃናቸው እንዲወጡ ያደረገው ማነው? ብየ ደራሲውን ስጠይቅ «ይህንን ያደረጉት ቂም ቋጥረውባቸውና ቀን ሲጠብቁ የነበሩት ቀሳውስቶቹ ናቸው» በማለት ነገረኝ።

ምንትዋብ የማነ

በስተመጨረሻም አገርና የግል ቂም ለያይታ ያየች ምንትዋብ የማነን ታሪክ አይተን ጽሑፌን ልቋጭ፡

ምንትዋብ የማነ ጎጃሜ ነች። በንጉሡ እስከ የመጨረሻዋ ሰዓት ድረስ አብራ ግቢው ውስጥ የኖረች ነች። የምንትዋብ እናትና አባት በንጉሡ ውሳኔ የተገደሉ ናቸው። እስዋም እዛው ግቢ አብራ ትኖር ነበር።ታዲያ እንግሊዞቹ የግቢውን በር በመውረር ተንጋሎ ሰላማዊ ፈገግታ በሚታይበት የደስታ ሳቅ (እንግሊዞቹ እንደጻፉት) በሚያሳየው ወደ ንጉሡ ሬሳ አንድ የእንግሊዝ ወታደር ተንደርድሮ በመምጣት ዘውዳቸውን ለመዝርፍ ሲሞክር፡ምንትዋብ የማነ የወላጆችዋን ገዳይ ንጉሡ መውደቃቸው ቂም ሳትይዝና ሳትበቀል፤ ለሀገር ክብር ስትል ተንደርድራ የእንግሊዙን ጉሮሮ አንቃ  እኑሮው እያለች ስታስጭንቀውና የማትለቀው ሲሆን ፤አንድ የእንግሊዝ ወታደር እስዋንም ጓደኛውንም  አንድ አድርጎ ጣላቸው

ለምጩ ይሚባለው መጽሔት መሰክረም 1991 ዓ.ም ገጽ 15 እንደዘገበው ይላል ደራሲ አማረ እንዲህ በማለት፤

«...አወዳደቃቸውም ከጀግናው አጤ ቴዎድሮስ ሬሳ ሥር ዝቅ ብሎ ነበር። በዚህ ጊዜ ለእንግሊዝ ታላቅ ኅፍረት ሆነ። ወዲያውኑ ጀግኒት ምንትዋብ የማነ እና እንግሊዙ እየተናነቁ በወደቁበት ቦታ ዘውዱን አንስተው የአጤ ቴዎድሮስ ሹሩባቸውን ቆርጠው በደም የጠለቀውን የሐር እጅ ጠብባቸውን አውልቀው ከነደሙ ወሰዱት....።»  

በማለት አገርና የግል ቂም ለያይተው የሚያዩ ሴት ጀግኒቶች ታሪክ እንዲህ ዘግቦአቸዋል። ታዲያ ዛሬ ድሃን የሚቀጠቅጡ ፖለሶች የማይጠየቁባት ፥ የዘረኞች፤ የወረበሎች ፥ የሰነፎች ፥ የቂመኞች ፥ የከሃዲዎችና የአድርባዮች መንጋ የሚፈነጩባት ኢትዮጵያን ለማስተካከል ምን ቢደረግ ይሻላል?

ጌታቸው ረዳ

Ethiopian Semay