የሰዎች ፍትሕ ሞከረቺው አልቀናትም ፥ ፈጣሪዋም ለመነች እሱም ዘገየባት ፥ ታዲያ ኢትዮጵያ ወደ ማን እጆችዋን ትዘርጋ?
ጌታቸው ረዳ
Ethiopian Semay
5/29/26
መጀምሪያ ይህንን እንመልከት የዚህ ወር Ethiopian Semay አንባቢዎች ቁጥር 630,677 ተዘግቧል
“እውነት እንደፀሐይ ናት፤ ፊት ለፊት በባዶ ዐይኖች አትታይም” ይላል ናማያራ የተባለ
ህንዳዊ ደራሲ በአንዲት አጭር ልቦለድ ትረካው፡፡ በጣም እውነት ነው፡፡ የኔ ነው የምትለውን እውነት ይዘህ ግትር ካልክና የሚቃወምህ
እንጂ የሚደግፍህ ካጣህ በርግጥም በቃላት ልትገልጸው የሚቸግርህ ህመም ጭንቅላትህን ሰንጎ ይይዝህና ትሰቃያለህ።” (አምባቸው ደጀኔ)።
በመቀጠል ወዳጄ አምባቸው ያንን
ሲያጠናክር አሁን ኢትዮጵያን ረግጦ እየተንፈላሰፈ እየገዛትና እየበዘበዛት ያለው ቡድን እና ማሕበርሰብ ማን እንደሆነም ይነግረናል፦
<....በአሁኑ ወቅት የሚሾሙ ሰዎችን ተመልከቱ፡፡ አብዛኞቹና ወሳኝ ቦታ ላይ የሚመደቡት ኦሮሞዎች ናቸው። በኦሮሞነታቸው ላይ ሃይማኖታቸው ፕሮቴስታንት ነው። ወይም ኢ-ሃይማኖታውያን (atheists)፡ ጥቂቶች ደግሞ ሙስሊሞች ናቸው፡፡ ተሹዋሚዎች በዕድሜ ፌዴራላዊያን ናቸው - ማለትም በዕድሜ ያልገፉ ወጣቶችና ጎልማሦች ናቸው - በፌዘኛ ፌዴራሊዝም ዘመን ተኮትኩተው ያደጉ። ብዙዎቹ አቢይ የሚያውቃቸውና አብረውት በካድሬነት ወያኔን ያገለገሉ ናቸው። ግለ ታሪካቸው ደግሞ በሹመታቸው ላይ አንድም ተፅዕኖ የለውም፣ ሙልጭ ያሉ ሌቦች ወይም ገዳዮች መሆናቸው ከሹመት አያግዳቸውም ፡ ብቻ የከይሲው ወዳጆችና ደንገጡሮች ይሁኑ። በዕድሜ በአማካይ ከ25 እስ 45 ግፋ ቢል እስከ 50 ይሆናሉ። ብዙዎቹ ሹመኞች ራስ ወዳድና ማኅደራቸው በ”ፋወል” የተሞላ አጭበርባሪዎች ናቸው - በሀሰት ዲግሪዎች የተምበሸበሹ
፥ ከርሳሞች ናቸው። የሚገርመው ደግሞ ሆዳምነቱንና ከሃዲነቱን በግልጽ ካላስመሰከረ በስተቀር ኦርቶዶክስና አማራ በምንም መንገድ አይሾምም። ባጨሩ በቅርብ የሚለይላት ገደል አፋፍ ላይ የምትገኘው የአቢይ ኢትዮጵያ ይህች ናት።» ይላል።
እኔ ድግሞ ይህንን ከላይ ያየነው እውነታ ‘የጸሐይ ጨረር ያልጋረደው ኮለል ብሎ ለመላ ኢትዮጵያ ሕዝብ በዓይን የሚታይ የአፓርታይዳዊው መዋቅር እውነታ ነው’ እላለሁ። ይህ እውነታ ደግሞ የአብይ
አሕመድ የኦሮሙማ ፖለቲካ ፈልሳፊ
እና የአብይ አሕመድ የፖለቲካ መምሕር የሆነው ”የኦነግ መሪ
እና የኦነግ ሸኔ መስራች አባል” ሌንጮ ለታ የሚከተለው እውነታ እንዲህ ሲል አረጋግጦልናል፡
ሌንጮ ለታ
ሰሞኑን
መጽሐፍ ጽፎ ቃለ መጠይቅ ሲደረግለት እንዲህ ይላል።
«ዛሬ ለመጀመሪያ ጊዜ ሥልጣን የተቆጣጠረው ኦሮሞ ነው። ለመጀምሪያ ጊዜ ዲሞክራሲ የማይፈራ
ነው ሥልጣን የተቆጣጠረው። ለምንድነው የማይፈራው? በሁለት ምክንያት ነው። 1ኛ ኦሮም ዲሞክራት ነው፤ ዲሞክራት ነኝ ብሎ ያምናል
ኦሮሞ፡ 2ኛ በብዛት ከሁሉም ሕዝቦች የበለጠ ነው። እሰከዛሬ ኢትዮጵያን የገዙ ሃይሎች የመነጩት የዲሞክራሲ ባሕል ከሌላቸው ሕብረተሰቦች
ነው የመጡት። ለመጀምሪያ ጊዜ ዲሞክራሲ ባሕሌ ነው ከሚል የመነጨ መሪ
(አብይ አሕምድን ነው መሪ እያለ ይሚለው) ኢትዮጵያን አሁን
ሥልጣን ተቆጣጥሯል።»
ሌላኛው ሌንጮ ባቲ ደግሞ
እንመልከት
ይህ
ደግሞ በአሜሪካ ሚኔሶታ ውስጥ ሲኖር የነበረ ፤ የአሜሪካ ዜግነት
ያለው ፤ አብይ ሥልጣን ሲይዝ ወደ አዲሰ አበባ ገብቶ የአብይ ልዩ ከፍተኛ አማካሪ ሆኖ የተሾመ፤ ከዚያም በአሜሪካ አምባሳደር ሆኖ ለሹመት ሲታጭ አሜሪካ
አልቀበለም አለቺው ተበሎ የተወራለት በኋላ ግን በለዋጩ ወደ ሳውዲ ዓረብያ አምባሳደር ሆኖ የተሾመ አሌላኛው እጀግ አከራሪ
የሆነ የኦነግ አመራር ነው።
እንዲህ
ይላል፤
« ኦሮሚያ የምትባል ሃገር ለማዋለድ ሥራ ላይ ነን። በወሊድ ጊዜ ደግሞ ደም መፍሰስ ግድ ነው።
እኛ “ለሚፈሰው ደም ሳይሆን የምንጨነቀው
ለሚወለደው ነው ትኩረት የምንሰጠው። ይህ መቼም የምናገኘው የመጨረሻ እድላችን ነው። ጊዜ ለመግዛት ግድያ ጭፍጨፋ
......... በየቀኑ አጀንዳ መፈጠር መስጠታችንን አጠናክረን መቀጠል አለብን። ከዚህ በላይ መጨከን አለብን። ደም ይፈሳል፤ ደም
ሳይፈስ የተመሰረተ ሃገር የለም። በመላ ሃገሪቱ የቀድሞ የተወረሱ ርስቶችንን በግድም በውድም ወደ ታላቅዋ ኦሮሚያ እያስመለስን ነው።
ሥልጣን ከሰሜኑ ፊውዳሎች እጅ ጠቅልለን ወደ ኦሮሚያ እጅ አስገብተናል። የሰሜኑን ፊውዳል ወገቡን ሰብረነዋል። ከዚህ በኋላም እድሜን
ልኩን.........”» በማለት ለኦሮሞዎች በኦሮምኛ የተናገረው ነው።
ልብ ማለት ያለባችሁ “ለሚፈሰው ደም ሳይሆን የምንጨነቀው ለሚወለደው ነው
ትኩረት የምንሰጠው የሚለው ሐርግ ምን ማለት እንደሆነ እና የሚፈሰው ደም የማን እንደሆነ እና ያንን ኦሮሚያ የምትባል
ምናባዊ ሃገር ለመመስረት የሚጨፈጨፈው ሕዝብ እና እያተፈናቀለ ያለው ሕዝብ በዋናነት ማን እንደሆነ ይገባችኋል።
አብይ አሕመድ
እንዲህ ሲል እየገዛን
ያለው ነገድ ማን እንደሆነ ነግሮናል
ኦሮሞ እሰኪነቃ ነው እንጂ ፤ እስኪነሳ ነው እንጂ ፤ ሲነሳ ሚዳቋ አትበላንም። እኛ ዝሆን ነን ፥ እንሰብራለን ፥ እንበላለን ፥ እንገዛለን፤።ንግግሩን በመቀጠል እንዲህ
ይላል፤«ትናንት ያዋረደንን
አዋርደን፤ ትናንት የሰበረንን ሰብረነዋል፤ ትናንት አትገቡም
፥ አትወጡም ብሎ አጥር ያጠረብንንን ፣ ዛሬ መውጣት መግባት አይችልም ከኛ ፈቃድ ውጭ» (February
4/ 2020 ባሌ ኦሮሚያ ክልል በሚባለው “ወልወል ግድብ” ምረቃ እመርቃለሁ ብሎ ሄዶ የተናገረው)
እነዚህን 4 ቃላቶች ልብ በሉ አደገኛነታቸውን እዩ፡ «እኛ ዝሆን ነን!” ፥”እንሰብራለን!”፥“እንበላለን!”፥”እንገዛለን!”
ስለ ታገቱ ተማሪዎች ሲጠይቅም፤ «የት እንዳሉ አላውቅም፤ የከተማ ከንቲባ ስላልሆንኩ። የለገጣፎ
ተፈናቃዮች መፈናቀል አልሰማሁም። እኔ ጠ/ሚንስትር እንጂ የሰፈር ሚሊሺያ አይደለሁም። (ሰላልሆንኩ የሃገሪቱ ጸጥታ አይመለከተኝም
እያለን ነው)፡ ሰለሆነም ጠ/ሚኒስትሩ ደግሞ የተሰጠውን ሃላፊነቱን በሚገባ እየተወጣ ነው (ሲል ራሱን ያሞካሻል)። ሰው ተገደለ
አትበሉ፤ ግድያው መቸ እንደሚቆም አላውቅም እንጂ ገና ይቀጥላል። ሞትን አታዳምቁ፤ ሞት ብርቅ አይደለም፤
አምሪካም እኮ ሰው ይገደላል።» እያለ የኦነግ ሸኔ ድብቅ ሥራው እያቀላጠፈ ነው።
አብይ የኦነግ ሸኔ መስራች አባል ነው። ኢትዮጵያን በተለይ አማራ እና ኦርቶዶክስን እየጨፈጨፈ
ያለው ኦነግ ሸኔ የተባለው አሸባሪ ቡድን 26 ባንኮችን እንዲዘርፍ፤ ዘመናዊ የኮማንዶ ወታደራዊ መኪኖች እና ዘመናዊ
መሳሪያዎች የሚረዳቸው የኦነግ ሸኔው አባል አብይ አሕመድ እንደሆነ የሚከተሉት አክራሪ የኦነግ ሸኔ እና የኦነግ አመራር አባሎች
ይህንን ያረጋገጥሉናል፡
ኃይሉ ጎንፋ እና አፈንዲ ሙጠቂ እንዲህ ይላሉ፡
«አብይ አሕመድ ኦነግ ሸኔ ነው» ሲመሰረትም አብረን ነው የመሰረትነው ሲል
«አፈንዲ ሙጠቂ»
ኃይሉ ጎንፋ ደግሞ በቪዲዮ እንዲህ ይላል፤
ዶ/ር አብይ አህመድ ኦነግ
ሽኔ (አባኦ ABO) ነው! እኔም (ኃይሉ ጎንፋ ) ኦነግ ሽኔ (አባኦ ABO) ነኝ! ለማ መገርሳም ኦነግ ሽኔ (አባኦ ABO) ነው!
ሁላችንም ኦነግ ሽኔ (OLF ABO) ነን!! (ኦሮሚያ መመስረት አለብን
ብሎ የሚጎተጉት አከራሪው የኦህዴድ ባለስልጣን ኃይሉ ጎንፋ)።
ይህ ቡድን የሩዋንዳ ውስጥ የቱትሲን ነገድ ለማጥፋት በ1981 ዓ.ም
የተመሰረተው “MRND” (ልክ እንደ የኦሮሞዎቹ Prosperity/
ብልጽግና” የነበረ ገዢ የፖለቲካ ፓርቲ እና በሩዋንዳ
ጦር ሃይሎች (ኤ.ኤፍ.አር AFR) ለአሸባሪው “ኢንተርሃምዌ” (እንደ ኦነግ ሽኔ (አባኦ ABO)’ ወታደራዊ ስልጠና፣ ሽጉጥ እና
ሜንጫ አስታጥቆ ቱትሲዎችን እንዳስፈጃቸው አብይ አሕመድም አማራን እና ኦርቶዶክስን ለማጥፋት “አባኦ” (ABO)
ኦነግ ሸኔም ሥልጠና እና ወታደራዊ ዕርዳታ የሚያገኘው ከአብይ አሕምድ ፓርቲ እና መንግሥት መሆኑን ከመስራቾቹ አንደበት ምሥክር
ሰምተናል (የሚክድ ሰው ካለ ቪድዮው አለኝ)።
ታስታውሱ እንደሆን ይህንን ጭፍጨፋ ለማጠናከር እንዲመቻቸው “ውጣልኝ!” የሚል የአብይ አሕመድ ኢንተርሃሙዌው የሙዚቃ ቡድን ያሰራጨው
አዋጅ የዚሁ የአብይ አሕመድ ቡድን ተልዕኮ መሆኑን አንርሳ ። ይህ ሁሉ ክንዋኔ የሚነግረን አመላካች ቀስት
“ሥልጣኑ በማን እጅ እንዳለ እና ይህ ሁሉ ሽብር ሲፈጸም ተሎ ያልቆመበት ምክንያት ሩዋንዳ ውስጥ ኢንትርሃሙዌው ቡድን ሽብር
ሲፈጽም የMRND እና የሩዋንዳው (ኤፍአር AFR) ፓርቲ እና የሰራዊት ጥምረት ከኋላ እንደነበረው ሁሉ በኢትዮጵያ ውስጥም
«በብልጽግና/ ኦፒዲኦ/ የኦሮሙማ ፓርቲ” እና »በኦሮሙማ አጀንዳ ትዕዛዝ የሚመራው የOromia Special Forces (OSF
/ ልዩ ሃይል)” ከኋላ ሰላለ ነው።
ይህ ኃይል በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ለኦነግ ሸኔ (አባኦ ABO) ሽፋን በመስጠት አማራዎች
እና ከርሰትያን መዕመናኖች እና ቀስውስት ሲታረዱ ከመታረድ የሚሸሹትን አስቁሞ እንዲገደሉ በማድረግ አንሸሽም ብለው ታጥቀው ራሳቸውን
ለመከላከል የሚደራጁትም ትጥቅ በማስፈታት እንዲገደሉ አድርጓል። ከዚህ ሌላ የራሱ ሚሊሽያ እና ልዩ ሃይሎች በጭፍጨፋው ላይ ተሳትፈዋል።
አብይ አሕመድ ያዘጋጃቸው ጨፍጫፊ ቡድኖች አማራን እና ክርስትያን አርደው ካንድ
ቦታ ወደ ሌላ ቦታ በመሄድ ጭፍጨፋ ለማካሄድ ትዕዛዝ ሲሰጣቸው “በOPDO እና በ(OSF / ልዩ ሃይል)” “አይ-ሲዙ” እና ልዩ ፣ ልዩ ወታደራዊ መኪኖችን በማዘጋጀት “የሞት
ድግስ ወደ ተደገሰባቸው ተረኛ መንደሮች” እንዲጓጓዙባቸው ድጋፍ የሰጣቸዋል። ይህ ደግሞ አማራሮቹ እና ልዩ ኃይሉ በዚህ ወንጀል
እንደሚሳተፉ እና ተከላካይ ኃይል ጣልቃ
እንዳይገባም የስልክ መገናኛዎችን በምዝጋት ጥቃት እንዲደርስ ለአሽባሪዎቹ ትብብር ይደረጋላቸው እንደነበር «ጀነራል ከማል ገልቹ» ሲናገር ሰምተናል
(ቪዲዮውም አለኝ)።
የአብይ አሕመድ የኦሮሙማ ፓወር ያዘጋጀው “አባኦ ABO” እና የጃዋር Ethiopia out of Oromia የ“ቄሮ” ቡድን እና የሩዋንዳው “ሁቱ ፓወር” በአስተሳሰብ እና በተግባር አንድ ናቸው።
በሚገርም ሁኔታ ይህ ሁሉ ጭፍጨፋ ሲደረግ “አብይ አሕመድ” ትንፍሽ
አይለም። ካለም “ለሞቱት ጥላ እንዲሆናቸው የባሕርዛፍ ችግኝ እንተክላቸዋለን” እያለ ያሾፋል። ሰለዚህ የኦሮሙማው “አብይ አሕመድ”
እና የሁቱ ሩዋንዳው መሪ “ሃቢአብሪማና” ወንጀሎች ተመሳሳይ ናቸው።
የአማራ ሕዝብ ከየክፍለሃገራቸው ለሥራ ወደ መዲናዋ በአብቶብስም ይሁን በጭነት ሲመጡ መዲናዋ
የኦሮሞ መናሃሪያ ለማድረግ እንዲመቻቸው እና ዳግም ሰው ወደ መዲናዋ እንዳይመጣ መኪኖችን መንገድ ላይ እያስቆሙ ተሳፍሪዎችን በማገትና
ከፍተኛ ማስለቀቂያ ገንዘብ በመጠየቅ ወይንም በከፋ መልኩ በተሳፋሪው ላይ የእሩምታ ቶክስ በመክፈት ሕዝብ ሲጨፈጭፉ አጥጋቢ እርምጃ አይወስድም።
የዛሬዎቹ ተተኪዎቹ ተረኞቹ “ኦሮሞዎች” በዚህ 8 አመት ብቻ (ሌላውን የ27 አመት የታየው
ወደ ኋላ ትተን ማለት ነው) ሰማዩም ምድሩም ያወቀው ስለሆነ ዝርዝር አልገባበትም። በአብይ አሕመድ ኦሮሙማ ፕላን 1፣ ፕላን 2፣ ፕላን 3 …እየተባለ እየተሰራ ያለው አማራ ላይ ያነጣጠረ ከወያኔዎች የቀጠለ የኢንተርሃሙዌው “ፕላን” ቀስ እያለ ሲሰራ ቆይቶ እነ ሌንጮ እነ ዶ/ር ዲማ ነገዎ እና አሰፋ ጃለታ
የመሳሰሉ የኦሮሙማ አጀንዳ አቀንቃኞች እንደተናገሩት ፥ እንዳቀዱትም ፥ እንደዛቱትም፤ በአብይ አሕመድ በኩል ተግባሪ በማድረግ አማራዎች
ወደ አዲስ አባባ እንዳይገቡ፤ የገቡም ቀስ በቀስ ከተከበቡ በኋላ እየተለቀሙ እስር ቤትና በየት/ቤት ማጎርያ ህንጻዎች እንዲታጎሩ
መደረጉን ታስታውሱ ይሆናል።
ይህንንም ዕቅድ የቆየ በጥናት ሲጠናበት የነበረ ኦሮሙማዊ አጀንዳ ነው። ይህን የዲማ ነገዎ
አጅንዳ እና ንግግር በዶ/ር አሰፋ ነጋሽ በEthiopian Semay የተለጠፈው ጽሑፍ እናስታውስ። በዚህ 8 አመት አማራ ምሁራን
እና ወጣቶች በየምክንያቱ ሰብስቦም ይሁን አንደ ባንድ እየለቀሙ ማጎር ፥ ቀደም ብለው ያቀዱት የኦሮሞ ፖሊተከኞች ንድፍ ነው።
አዲስ አበባና አካባቢው ውስጥ የሚኖሩ አማራዎች (‘ነፍጠኞች’) እየለቀምን ከሰበሰብናቸው በኋላ
የመውጫ ኮሪደር (በር) ከፍተን ወደ አገራቸው “እንዲወጡ” እናደርጋለን ብለው በተለያዩ ሰነዶቻቸውና ንግግሮቻቸው ባስቀመጡት መሰረት መጨረሻ አዲስ አባባ እንዳይገቡና የገቡትም እየተለቀሙ ተሰብስበው እንዲወጡና
“ኦሮሚያ” የተባለ አገር ለመመስረት እንዲያመቻቸው <<ወኪላቸው አብይ አሕመድ>>
ይህንን በአዋጅ ተግባራዊ እያደረገው ይገኛል።
ይህንን ንግግር ያደረገውም አብይ ወደ ሥልጣን ሲምጣ ከኔዘርላንድ (አወሮጳ) ወደ አገር በመግባት
አሁን በአብይ አሕመድ ፓርላማ አባል የሆነው <ዶ/ር ዲማ ነገዎ> የተባለ እጅግ አደገኛ የኦሮሙማ ቄሮ የኢንተርሃሙዌ ቡድኖች
ቀስቃሽና የኦነግ መሪ ነው።
ከ3 አመት በፊት ከላይ የጠቀስኩት “ውጣልኝ!” የሚል የአብይ አሕመድ ኢንተርሃሙዌው የሙዚቃ
ቡድን ቅስቀሳ እያታጀበ በየገጠሩ በአማራ ሕዝብ ላይ የዘር ጭፍጨፋና
ሲፈጸም፡ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ደግሞ “ኦነግ
ሸኔው ፖሊስ” አንገቱ ላይ የክርስትና ሃይማኖት ምልክት ያለው ኢትዮጵያዊ እና የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ የያዘና
የለበሰ ሰው አስቁመው እየነጠቁና እየደበደቡ እስርቤት በማስገባት ፤ ለቁጥር የሚያዳግት በሺዎቹ የተማረውና ያልተማረው አምሐራዊው
ክፍልም ተሰብስቦ እስር ቤት ታጉሮ እየተሰቃየ የምናይበት ምክንያት አብይ አሕምድ የተከናነበ ልዩ አጀንዳ
ሰላለው ነው።
የኦሮሞ 1ኛ ደረጃ ተማሪዎች መዝሙር
ይህ ሁሉ አጀንዳ እና ጭካኔ ካደረጉ በኋላ መጪዋን ኦሮሚያ ለመገንባትና ሕጻናቶቻቸውም በጥላቻ
አድገው አደገኛ ቂመኞች እንዲሆኑ “መገዳደል እንዲቀጥል” ለትምሕርት ቤት ሕጻናት የህንን የጥላቻ እና የውሸት መዝሙር አዘጋጅተው
የኦሮሚያ (አነግ) ባንዴራ ሲሰቅሉና ሲያወርዱ በ1ኛ ደረጃ ት/ቤቶች የሚከተለው መዝሙር እንዲዘምሩ ተደርጓል። (ማስታወሻ ነፈጠኛ
ማለት የምስጢር ስሙ (ኮድ) አማራ ማለት ነው፡
«ነፍጠኛ የሰራውን ማሰብ ያንገበግባል
ታሪክ ኖሮን እንደሌለን፥
እናት ኖሮን እንደሌለን
እንደ በግ ግልገል በየመንደሩ ታርደን ያንን ያንን ያሰብን ዕለት ምሽግ ያዝን
ሌላ
ማሰብ አንፈለግም ከኦሮሚያ በቀር» ይላል።
“ኦሮሙማዊው ኢንትርሃሙዌው አጀንዳ” ተግባራዊ ለማድረግም አዲስ አበባ ብቻ ሳይሆን የአማራ
ከተሞችና ገጠሮች የጦር ቀጣና ሆነው አማራዎች ሲፈጸምባቸው የነበረው
የ27 አመት ጭፍጨፋ አበቃለት ስንል “እንደገና ነብስ ዘርቶ” በከፋ መልኩ በመቀጠሉ የአማራ ወጣቶች የሞት ሽረት የጦርነት
ፍልሚያ በማድረግ ላይ ናቸው። እነሱም ሕዝቡን ነፃ ያወጡታል ተብሎ ተስፋ ሲጣልባቸው የሚከተለው ተስፋ አስቆራጭ የጫካ ባሕሪያቸው
እንድናይ አደረጉን።
ፋኖ
ፋኖን ስናነሳ በማን እንጀምር? የጎጃም አፈቀላጤ በመሆን
ሲሰራ በነበረው በማርሸት ፀሐዩ እንጀምር። ማርሸት ፀሐዩ ሰሞኑን ጎጃም ውስጥ ዝናቡ በተባለ የፋኖ የጎበዝ አለቃ ትዕዛዝ “ወፌ ላላ” ታስሮ እንደተገረፈ ያለፈው
ሁለት ሰሞን የሕዝቡ መነጋግረያ ሆኖ የሰነበተ ሰው ነው።
ማርሸት
ጸሐዩ
ባለፉት የሽምቅ ተዋጊ ድርጀቶች ታሪክ ስንመለከት አድማጭ የታዘበኛል” የማይሉ ሲዋሹ እጅግ እስከ-ጥግ ድረስ የሚቀደዱ፤ የተቃዋሚያቸውን ስም ለማጠፋት ሲፈልጉ ራሳቸውን ለትዝብት የሚጥሉ፤ ዓለም የዘገቡዋቸውን የሃገራችን ታሪኮችን የሚያጠለሹ “የወያነ ፤ የኦነግ/አብይ-ኦሮሙማ እና የሻዕቢያ መሪዎች” የውሸት ባሕሪዎች ምን እንደሚመስሉ ለብዙ አመት ታዝበናቸዋል። ዛሬ ደግሞ በጎበዝ አለቆች የሚመራ “ፋኖ” ብሎ ራሱን በውሸት የሚኮፈስ ሲዋሽም ዳርቻ የማያውቅ፥ያለፉት “የዋሾ ድርጅቶች ባሕሪ” የተላበሰው ባንድ ወቅት የጎጃሙ የፍሺስት ዱርየ ታጣቂዎች መሪ የሆነው የዘመነ ካሴ “አፈቀላጤ” የነበረው ሰው ነው።
ይህ ሰው አማራ አማርን እንዲገድል (ጫካ
የወጡትን ማለት ነው) በማወጅ የመገዳደል ጦርነት ሲናገር እንደነበር ታስታውሳላችሁ ብየ እገምታለሁ።
ይህ «ትንሽ ሰው» የመግደል አዋጅ ብቻ ሳይሆን ሲዋሽም
ዳርቻ አልነበረውም።ሽዋ ውስጥ ሲንቀሳቀሱ የነበሩት እስክንድርና
ጓዶቹ የሚመሩት “የአምሐራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት”
፤ “ስላዳከምነው የትጥቅ ዕርዳታ
የሚያገኘውም ከአብይ አሕመድ
ነው” ሲል “አድማጭና ታሪክ” ይታዘበኛል ሳይል ሃሰትን ለመቃወም ጫካ ገብቶ ሃሰትን መመሪያው ያድረገ ማርሸት ፀሐዩን ታስታውሳላችሁ።
እንቀጥል፦
አስረስ
ማረ
እና የድረጀቱ ምክትል የነበረው አሁን ቃል አቀባይ እና የፕሮፓጋንዳ/ የሕዝብ ግንኙነት ሆኖ የተሾመው አስረስ ማረ የተባለ ደም የጠማው ነብሰ ገዳይ እንመልከት።
ይህ ሰው አብረውት የአማራ ሕዝብ ነጻ ለማውጣት የወጡትን «የእነ እስክንድር ነጋ ድርጅት እና አመራርሮቹን የጠላት ድርጅት አድርጎ በመሳል፤ ለአምሐራ የቆምን ብቸኛ የሽምቅ ታጣቂዎች እኛ ጎጃሞቹ የመሰረትነው ፋኖ ብቻ ነው፡ስለሆነም “የተቀረ ፋኖ ነኝ የሚል ታጣቂ መደምሰስ አለበት፤ ጀምረናቸዋል፤ ጦርነት ገጥመናል፤ አዳከመነዋል፤ እናጠፋቸዋለን!” ሲል በፋሺት የብሔረተኛ ድንፍታ ሲጎረን ስመተን አፋችንን በአግራሞት አስያዘን። በዚህም ታዋቂ ታጣቂዎች ተገድለዋል፤ ተዋክበዋል (ወያን እና ሻዕቢያ በየት ዞሮው መጡም አስኘን)።
ዘመነ
ካሴ
የጎጃም ፋኖ መሪ ነኝ የሚል ዘመነ ካሴ አሁንም በድጋሚ የአምሐራን ሕልውና እጠብቃለሁ ብሎ “በሚያስቅ ጉጉት” ራሱን ለማንገሥ ሲል «እኔ አጥናፉ አባተ አይደለሁም ፥ “እኔ የፋኖ ንጉሥ ነኝ ፥ሳልወለድ ትንቢት የተነገረልኝ፥ከዘር የተላለፍልኝ አንጋሽና ነጋሽ ነኝ” እያለ ምሁራን ጀሌዎቹን የሚያስፈነድቅ ዘመነ ካሴ ፣ እስክንድርን ካላጠፋሁ “በሚል በማሃይምነትና ደም በጠማው አስተሳሰብ እየተመራ «የፖሊስና የሌባ» «ራሱን አዳኝ (አጥማጅ)” “እስክንድር ታዳኝ” አድርጎ በመሳል ጦርነት እንደገጠመ ሲናገር የነብረውን በሪኮርድ የያዝነውን ታሪኩን ታስታውሳላችሁ።
እንደምናውቀው ይህ ሰው መምሕራንና ተማሪዎች ሲያዋከብ፤ ሲጠልፍ፤ ሲያግት ፤ ሲያስር ፤ ሲረሽንና የፋኖ ታጣቂዎችን እኔ ካልመራሁ ብሎ (እያፈነ ሲያሰገድልና አስገድዶ ሲያታግል የጎጃሙ ኮ/ል ጌታሁንና በሥሩ የነበሩ በመቶዎች የሚቆጠሩ ታጣቂዎች ለምን ከእስክንድር ጋር ወገናችሁ በሚል ወደ ዘመነ ታጣቂ ታፍነው በአስረስ ማረ “ቃለ መሃላ” አስፈጻሚነት በግድ ከማሉ በኋላ ምን እንደደረሰባቸው እና የተቀሩትም እንዴት ወደ ዘመነ እንደተቀላቀሉ ታሰታውሳላችሁ ብየ እገምታለሁ።
በነዚህ ብቻ ሳይገደብ የጋዜጠኞች የዶክተሮች የመምሕራኖችና የተማሪዎች አፈና ግድያ እና እገታ በዚህ ሰው አመራር ስር ያስገረመን ክስተት ነበር። እውነተኛ አምሐራዎች መጠየቅ ያለባችሁ «በዚህ ቀውስ ውስጥ እንዴት ልንገኝ ቻልን?» ማለት አለባችሁ።
ብዙ አምሐራ ወጣቶች ፥ ምሑራን ደጋፊዎቻቸው ጭምር በብሔረተኛነት ስካር ሰክረው እያየናቸው ነው። አንዳንድ ምሑራኖቻቸው ወደ ፋኖ የሚቀላቀል ሰው 7 ትውልድ የአማራነቱን የደም ጥራት መረጋገጥ እንዳለበት ጠይቀዋል። እነኚህ ሰዎች ፋሺዝምና የብሔርተኛነት እንቀሰቃስዎች ባሕሪ ክፋቱ ምን እንደሚመስል ከወያኔ እና ከኦሮሞዎች የብሔርተኛነት ሰበብና ጠባሳ ትምሕርት ያስተዋሉት አይመስሉም።
በፋሺስታዊ እንቅስቃሴዎች መካከል የተለመዱ ጭብጦች የሚያጠቃልሉትን እንመልከት፡-
“ፈላጭ ቆራጭነት፣ ብሔርተኝነት (የዘር ብሔርተኝነት እና ሃይማኖታዊ ብሔርተኝነትን ጨምሮ) ፤ ወታደራዊ ድንፋታነትን ፤ የአካባቢ አጉራዘለል አለቃነት ስሜትና አልገዛም አልገብርም የሚለውንም ማንበረከክ የፋሺዝም ባሕሪያቶች ያጠቃለሉ ናቸው። ጎጃም ውስጥ አቆጥቁጦ እያየነው ያለውንም ይህንኑ ባሕሪ ነው። የዚህ ድርጅት ደጋፊ ምሑራኖች ይህንን ጭራሽ እንደማይታያቸው ይክዳሉ።
ለምን እንደሚክዱ ካሁን በፊት ምሑራን በዶግማቲክ (ችክተኛ ኢጎ) ራሳቸውን አንዴ ከተበተቡ ከገቡበት ስሕተት ተሎ ላለመውጣት የሚመርጡት ማምለጫ መንገድ “ከሕደት” ወይንም በ“ዲናያል” ጉዞ እንዴት እንደሚቀጥሉ ካሁን በፊት ገልጫለሁ።ሰለዚህም አምሐራ ምሑራንና ወጣቶች በዚህ ቀውስ ውስጥ እንዴት ልንገኝ ቻልን? ብለው ቢጠይቁና ቢመራመሩ ችግሩ ሊታያቸው ይችል ይሆናል እላለሁ።
እነሱ ብቻ ሳይሆኑ በዚህ ጥያቄ ውስጥ እንዴት ልንገኝ ቻልን? የሁላችን ጠያቄ መሆን ያለበት የመወያያ ርዕስ መሆን ያለበት ነው። ለጥያቄው መልስ ስጡ ብትባሉ ብዙዎቻችሁ የምትሰጡት የለመዳቸሁት መልስ ገና አዲስ ድርጅት እና አመራር ስለሆኑ ነው፡ ቢሆንም ከስሕተታቸው እየተማረ ይሻሻላሉ...” ፡ ትልላችሁ።
መምሀራን እና እግራቸው ያልጠና ልጃገረዶች በማን አህለኝነት ቢረሸኑ ፥ አያቶቻቸው የሚያክሉ አረጋዊያን ቢያንበረክኩ ፤ ቢገርፉም ፥ ይህ ድርጅት “ለመመስረት” ከባድ ዋጋ የከፈሉ ስለሆኑ ግድያና ግርፋት መፈጸማቸው እንደ ከባድ ወንጀል አናካብደው.......” የሚሉ ደጋፊዎቻቸው እንዳሉ አድምጣችኋል።
በአዳዲስ እና በነባር ታጣቂ ድርጅቶች የሚታየው የወንጀል ድርጊት ቀጣይነት የሕዝብ አያያዝና የአስተዳደር ልምድ ስላነሳቸው ሳይሆን ፤የምንከተላቸው መሪዎችና ድርጅቶች/ወይንም መንግስት እና ሚዲያ፤ “ስለሚዋሹንና ያለፉት ድርጀቶች እና የመንግሥት መሪዎች የፈጸሙዋቸው ወንጀሎች የክስ ተጠያቂነት ስላልተደረገባቸውና ሕዝቡም እኔን ስላልነኩኝ ምን አገባኝ እያለ በቸልተኝነት ሰልሚያልፈው ነው”
የፋኖ መሪዎች እየተከተሉት ያለው ማን የጠይቀኛል የወንጀል
እና የአጉራ ዘለል ባሕሪ ከላይ ያየነው ድግምግሞች (አዙሪት) ስለሆነ አዲስ መንፈስ ለምፈለግ ከባድ እየሆነ ነው።
መሪዎች (ጫካም ይኑሩ ከተማ) እንደ ዛሬው በዚህ 50 አመት ውስጥ ያሳዩት የውሸት ባሕሪ በታሪካችን አላየንም። ሕዝቡን እየዋሹ አስከፊ ዘመን አምጥተውለት እነሆ ‘ሲሰደድ፤ሲዋረድ፤ ሲንገላታ’ እንደዛሬ ስቃይ ደርሶበት አያውቅም።
ለዚህ ሁሉ መከራና መበጣበጥ “መሪዎች” ገደለው ሳይቀጡ፤ እንደገና ሥልጣን ሲሰጣቸው ፤ ሲዋሹ ድጋፍና ጭብጨባ ሲቸራቸው ፡ አምባገነኖችን እየካብን በአገራችን ውስጥ ቁቡል ሆኖ መታየቱ በማንወጣበት እሽክርክሪት ላይ ነን።
ከዚህ ዘልቀን መሰረታዊ መነሾውን መመርምር ያስፈልጋል። የሚጎመዝዙ ዋሾ መሪዎችና ነብሰ ገዳዮችና ወረበላ ታጣቂና መሪዎች በፋኖ ድርጅቶች ውስጥ በገፍ ተፈልፍለዋል። አሰገራሚ ያደረገው ደግሞ “የፋኖ መሪዎች በዋሹ ቁጥር፤ ምሑሩም ሕብረተሱም አብሮ ይዋሻል፡ ወይንም ሲዋሹ ይታገሳቸዋል፤ ወይንም ያምናቸዋል። ውሸት ሕብረተሰብን የሚገድል እና የሚያጋድል፤የሚያሳስት መሰረታዊ የሆነ ማሕበራዊ ነቀርሳ እንደመሆኑ መጠን ፤ ‘ዋሾ’ መሪዎች በዋሹ ቁጥር ሕብረተሰቡም አብሮ እየዋሸ ወይንም ‘እየታገሳቸው’ በሄደ ቁጥር የሚፈለገው ሰላማዊ የሆነ ፍትሕ የነገሰበትና ‘ተጠያቂነትን’ የሚያከብር ስርዓት እንዳይመጣ እንቅፋት ይሆናሉ። አሁን እየሰማነው ያለውና እያየን ያለው የፋኖ ክስተት ይህንኑ ነው።
“ውሸትና ዋሾ መሪዎች” የመቀበል ባሕል እያጎለበትን በመምጣታችን ለቀውሳችን ተጠያቂዎች መሪዎቹ ሳይሆኑ እኛ የመሆናችን ጉዳይ አስገራሚ ያደርገዋል። ይህ “እገሌን ካላጠፋሁ አላርፍምና ፤ ጥላሸት የመቀባት (የመዋሸት) ባሕሪና «ወንጀል ሠርቶ› ሳይጠየቁበት ተንደላቅቆ ያለሰቀቀን በነፃነት እንዲኖሩ አብረን ስንጨፍር ፥ውለን አድረን ሠለጠንን ባልንበት ዘመን ወደ አራዊት ባሕሪ ተለውጠን ፤ ይህ አምሐራን አምሐራን በመግደልና በመደብደብ ያየነው የወንጀል ክስተት እነሱ ሲያብዱ ባልታሰበ ድንገተኛ እምርታ እኛም እነሱ ጋር እየዋሸን እና እያበድን ቀስ በቀስ “ዕብድ ሕብረተሰብ” ወደ መሆን እየተሸጋገርን ነው፡ ይህንን እንመን። የፋኖ ታጋዮች፤ የሰው እጅ ቆርጠው አሳይተውናል፤ ኢትዮጰያዊ የአምሐራ ባሕሪያቸውን ጥለው ወደ አረመኔያዊ ባሕሪ ገብተዋል። ይህንን ጭካኔ ማጣጣል ቀጣይ ያደርገዋል።
ፋሺስታዊና አክራሪ የብሔረተኛነት በሸታ «ፋኖ ውስጥ ገብቶ»
ይፋ ሆኖ እየኮሩበት ነው። መሁራኖቻቸው ይህንን ሲነግራቸው “ፋኖ ሳይሆኑ ፋኖ እና አማራ መስለው የሚቀርቡ ወያኔዎች እና ኦነጎ
ናቸው”” እያሉ ከውነታው ርቀው ሲናገሩ ሰምቻለሁ። የብሔርተኛ ፖለቲካ መጨረሻው ስብእናን ነጥቆ የራሱ ያልሆነውን ነገድ በቻ ሳይሆን
አሁን እያየነው እንዳለው የጎጃም ፋኖ “ጀምረናቸዋል እንጨርሳቸዋለን” አምሓራን ለመጨፍጨፍ ዛቻ መጨረሻ የራሱንም ወገን እንደሚበላ
ሰሞኑ ብራሳችወ ሰው «በማርሸት ፀሐዩ» የደረሰው እያያችሁት ነው።
ማጠቃለያ
ተስፋ አድርገንበት የነበረው የከሸፈው የፋኖ ታጣቂ ቡድንም
ይሁን አሁን ሥርዓት የሚመራው ኢትዮጵያ ወስጥ ሕዝብን አሞኝቶ ወደ ሥልጣን በመግባት ለ27 አምት የቆየው አፓርታይዳዊ ሥርዓት እንዲቀጥል
ከውጭ ሃይሎች ጋር እየተመሳጠረ በትጋት እየሰራበት ያለው ኦሮሙማው የኦንግ ሽኔ (አባኦ ABO) መንግሥት
ሁለቱም “በውሸትና ወገንተኛነት” እየተመሩ ነፃነት እንዳትገኝ እሩቅ አድርገዋታል።
ሕዝቡ
ሃይማኖቱችም” “የዜና አውታሮችም” በውሸት የሰከሩ ሆነዋል። ዜጎችም ለ35 አመት ራሳቸው እንዳያውቁ በተለያዩ የማሰርያ ስንሰለቶች ተተብትቦ“ዞምቢ” (Zombie/Zombee) ሆኖ በግዝገዛው አጅንዳ ላይ ተስታፊ ሆኖ ራሱን እየበላ ሞቱን የሚያቀላጥፍ በሴረኞች ወጥመድ እየደነሰ እንደ “ዞምቢዋ ንብ” («ናላዋ እንደዞረባት ንብ”) ራሱን ስቷል።
የፈረንጁ ቃል “ዞምቢ” ማለት “ናላዋ የዞረባት ንብ ማለት ነው”። ንብዋ አፖሴፋለስ ቦሪያሊስ (Apo Cephalus borealis) በተባለ ባከትሪያ/ህዋስ/ የተበከለች ዝምብ (ፎሪድ ዝንብ) ንብዋን ስትነድፍ ፤ በጥገኛው “ፓራሳይት” ዝምብ” የተበከለች “የማር ንብ” ሆድ እቃዋ ውስጥ ይራባ እና እንቁላል ይጥላል። እንቁላሎቹ ከተፈለፈሉ በኋላ “እጮቹ” የንብዋን የውስጥ አካላት ይበላሉ። የተበከለቺው ንብ ከመሞቷ ጥቂት ቀደም ብሎ ናላዋ ስለሚዞር ሌሊት ላይ ቀፎውን ትታ ወደ ውጭ ትበራለች። በስሕትተ መብራት ወዳለበት በመብረር “በመብራቱ ዙርያ” ሽክርክሪት እየዞረች የሞትዋን ሰዓት ተጠባበቃለች። ለዚህ ነው የደነዘዘ ማሕበረሰብ ስናይ “ዞምቢ” ብለን የምንጠራው።
ውሸት አየር ነገር አይደለችም ፡ በማሕበረሰቡ ሕሊና ውስጥ የምትኖር ፥ ጠበቃዎችና ተከላካዮች ያሏት የሰዎች ባሕሪ ነች። ማሕበረስቡ በውሸት ዓለም እየዋዠቀ ነው፡ ማሕበረስቡ ወደ ዞምቢነት ተለውጦ ተነስ ብትለው አልነሳ አለ ፥ ማሕበረሰቡ ናላው ዞሮ ወደ ዞምቢነት ከተለወጠ ማን ይታደገው? ሰላማዊ ሰልፉም ቢሆን ዞምቢው የአዲሰ አበባ ኗሪ የሚያነሳሳና የሚቀሰቅስ እሰክንደር ነጋን የሚተካ ደፋር እምቢተኛ መሪ እና አዘጋጅ አጣ ፥ ታጣቂውም ገዳይ ሆነ ፥ መንግሥትም አፓርታይዳዊ ጨፍጫፊ ሆነ ፥ ወደ ፈጥሪዋም ለመነች እሱም ዘገየባት ፥ ታዲያ ከዞምቢነት ለመውጣት ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ ማን ትዘርጋ?
ጌታቸው ረዳ
Ethiopian Semay
