ገራፊዎች የሚመሩት የፋኖ ጎጠኛ ትርኪምርኪዎች እና እጅ የሚቆርጡ ብልት ቆርጠው ጠብሰው ተቃዋሚያቸውን ለማጉረስ በሚዝቱ የፋኖ ደጋፊዎች የሚመጣ የአማራ ሕዝብ ነፃነት
ጌታቸው ረዳ
Ethiopian Semay
5/16/2026
በአገራችን የብሔርተኞች ሽምቅ ተዋጊ ቡድኖች ታሪክ እንደሚያሳየው ታጣቂዎቹ የተነሱበት መፈክር (ዓላማ) ትተው በጫካ ሕግ እየተመሩ ከሳሽም ፈራጅም ፈጻሚም እነሱ ብቻ ሆነው የሚንቀሳቀሱበት በረሃ እና ሕዝብ “ናሺናላይዝ”
በማድረግ በማን አህለኝነት
ተነስተው ከመፈክራቸው እና ከሚያከብሩዋቸው በዓላትም ይሁኑ ስብሰባዎች ጋር የማይስማማ ቡደን/ሕዝብ/ግለሰብ
ከመግረፍ እስከ መረሸን ድረስ ሲፈጽሙ እንደነበር ማህደራቸው ያሳያል። ሰሞኑን እየሰማን ያለነው አስገራሚ ዜና ልክ ወያኔን ሲመሩት እንደነበሩት
የዓድዋ ልጆች፤ ፋኖ ተበሎ የሚጠራው በዘመነ ካሴ ፥ በአስረሰ እና ዝናቡ በተባሉ የጎጃም ልጆች የሚመራ ታጣቂ ቡድንም የራሳቸው የጎጃም
ተወላጅ የሆነውን «በሃሰት ሰማይ እና ምድር በማጣበቅ” የሚታወቀው አንድ ታዋቂ ጸሐፊ |*አር-ሸት* ብለው የሚጠሩት ዋሾው “ማርሸት
ጸሃዩን* አስረው ጭንቅላቱን ቁልቁል ዘቅዝቀው ወፌ-ላላ ቀጥቅጠው የገረፉትን “የእግር ባቱን” የሚያሳይ ‘ፎቶ’ በሚዲያ እየተዘዋወረ
እንደሆነ ሰምተናል።
ይህ እንደ አስደንጋጭ ዜና እየተዘገበ ያለው የጎጃም
ፋኖ መሪዎች ሰውን ማፈን፤ ማሳደድ፤ መረሽን፤ ሴቶችን መድፈር፤ ባንክ መዝረፍ የመሳሰሉ በታጋዮቻቸው እና በሰላማዊ ሰዎች ላይ ይፈጽሙ
እንደነበር ስንዘገበው የነበረ ምግባራቸው ነው። አሁን አዲሰ ዜና ሆኖ አስደንጋጭ የሆነበት ምክንያት በገዛ የአመራር አባላቸው ላይ
በሕዝብና በተራ ታጣቂዎቻቸው ላይ ሲፈጽሙት የነበረው የግርፋት ስራ «የገዛ ጓዳቸውን ልከ እንደ ጅብ ሲነክሱት» መስማት ነው ሕዝቡን
ያሰገረመ ድርጊት።
በሕዝቡ የሚፈጽሙትን ጭካኔ ውሎ አድሮ በአባሎቻቸው እና በአመራሮቹ ላይ ይፈጸም እንደነበር ከፋኖ በፊት የነበሩት
በሻዕቢያ፥ በኦነግ እና በትህነግ/ወያነ/ የግድያ፤ የዘረፋ፤ የግርፋት እና የፖለለቲካ ዝሙትነት ይፈጽሙ እንደነበር
የገመና ማሕደር ታሪካቸው አሳይቶናል።
አመራሩ በውጫዊ (በሕዝቡ ላይ) የሚፈጽማቸው የጭካኔ እርምጃዎች ውሎ አድሮ ወደ ውስጥ (ከሕዝብ
ወደ ድርጅቱ) የሚዞርበት ምክንያት ቀደም ብሎ እደተገለጸው አመራሮቹ በበሕሪያቸው ጨካኝ (አንስቲንክት) ገለሰቦች ከሆኑ “በሞራል ኮምፓስ” ስለማይመሩና “የራሳቸው ጥላ ሳይቀር የሚያባንናቸው
ተጠራጣሪዎች” ሰለሚሆኑ የሰሩት ወንጀልና ምስጢር ካለም በዙርያቸው ያሉትን ሰዎች ውሎ አድሮ ያጋልጡኛል በሚላቸው አባላቶቹ ላይ
“በትግሉ ስም” ለትግሉ አዛኝ በመመሰል ልክ እንደ ጅብ “በውስጣዊ ፓራኖያ” ቅጽበታዊ እርምጃ እንዲወስዱ ሰለሚያስገድዳቸው “ቀለበት ውስጥ ያስገቧቸው አመራሮቹ” ከጠላት ጋር ሲገናኙ ይዣቸዋለሁ በሚል ወደ “ማጽዳት ዕርምጃ” ውስጥ ይገባሉ።
ይህ በሚሆንበት ወቅት ድርጀቱ የሞራል ውደቅት
ውስጥ እየገባ መሆኑ አመላካች ምልክት እየሰጠ ቢሆንም፤ አባላቶቹ /ካልቶቹ/ (ለምሳሌ የፋኖ ደጋፊ የሆነው የ Wamera
media አዘጋጅ የሆነ ከነ ዘመነ ጋር እገናኛለሁ የሚል ግርማ ካሳ የተባለ Sycophant: (“Someone who acts subserviently
toward a powerful, tyrannical abuser, dangerous, or disreputable leader”) የተበለ አስገራሚ “ውትፍ ነቃይ” (አሳማሪ) የሆነ ይህ ሰው “ድበረ-ኤልያስ ውስጥ ከዕድሜ በታች የሆኑ 3 ልጃገረዶች ከነሱ ውስጥ አንድዋ
ጀሮዋ የማይሰማ (አካለ ጎዶሎ) ጨምሮ ሰላዮች ናቸው በሚል ውንጀላ ያስረሸናቸው አስረስ ማረ ይተባለ ይህ የሰው ደም ጥማት
ያለው “የፋኖ አምራረ አሸባሪ ሰው” እነዚህን ልጃገረዶች በማስረሸኑ “አስረስ ማረን” በጦር ወንጀል (war crime) ሲከሰው እና በጠቅላላ የድርጀቱ ሦስቱን መሪዎች (ዘመነ፥አስረስ እና ዝናቡ)
ሰዎችን በመረሸንና በመግረፍ ብቻ ሳይወሰኑ የራሳችወ ታጋይ የነበረች “አስካለ ደምሌ” የተባለች በመርማሪዎች መደፍርዋና የት እንዳለች
እንደማይታወቅ ወዘተ.. ወዘተ..ወዘተ የፋኖ አመራር ወንጀሎች እየዘረዘረ ያምን እና እነዚህ ወንጀሎች የጦር ወንጀሎች ሕግ የጣሱ
ወንጅሎች መሆናቸው “ለስሙልኝ” ይናገርና ትንሽ ሳይቆይ ወዲያውኑ እንዲህ ሲል ሕዝቡ እነዚህ ውንጀለኞች እንዲንከባከባቸው
ይማጸናል፡
« በማርሸት ብቻ እኮ አይደለም ይህንን የተፈጸመው
፥ ጎጃም ውስጥ እኮ እንዲህ ያለ (ወንጀልና ግርፋት ማለቱ ነው) ፓተርን (pattern) የተደጋገመ ክስተት ነው። ግን ወገኖቼ
“3 አመት ሙሉ ሕይወታቸውን ሰጥተው እንደው አንዴ ሁለቴ ተሳሳቱ
ብለን እንደ ትልቅ ወንጀል ይመስል ልንፈጠፍጣቸው
አይገባም ......”
“እነዚህ የሕዝብ ዕንቆች ናቸው፡ አንድ ሁለት ሦስት ስሕተት ሰሩ ብሎ መፈጥፈጥ አያስፈልግም።.....”
“ዝናቡም ዘመነም አስርስም” በተለይ አስረስ ኤለኩዋንት በሆነ (ማራኪ ንግግር) እየተናገረ እኮ ነው
ስሕተትም ቢሰራ ብዙ ሥራ የሰሩ ናቸው እኮ ወገኖቼ።..... “የተፈጠረው ነገረ ደግሞ ማይነር ነው።
እንደ ትልቅ ወንጀል ይመስል........”
እያለ የሰላማዊ ሰዎች ንብረትን መዝረፍ፤ ማሸበር ፥ የተማረኩ ሙርከኞች ርሸና እና የግርፋት ወንጀልን በተለይ “War crim እና torture” በGeneva Conventions ሕግ ተነድፎባቸው የተጠቀሱ ከባድ ወንጀሎችን ነው ግርማ ካሳ የተባለ የፋኖ አምራር ጫማ የሚልስ Bootlicker በነዚህ ወንጀለኞች የተፈጸሙ ወንበጀሎችን “ማይነር ነው” “እንደ ትልቅ ወንጀል ይመስል አትንጫጩ” “እነዚህ የሕዝብ ዕንቆች እንደው አንዴ ሁለቴ ተሳሳቱ ብለን እንደ ትልቅ ወንጀል ይመስል መፈጥፈጥ አይኖርብንም” እያለ ይህ ድርጊቱን የተቃወሙ አባሎችን ሲስብክ መስማት አስፈሪው የአገራችን ትልቁ ችግር ወንጀል ሲፈጸም እንደተፈጸ ማምን ግን የድርጅቱን ችግር እንዳይጋለጥ አሳነሶ በማየት ፥ ውርደትን ለመሸፈን ወዲያ ወዲህ በማመንታት ፥ አእምሮም በሚጋጩ ሁለት ሃሳቦች ተወጥሮ ምቾትን የማጣት ክስተት ቁልጭ ብሎ በግርማ ካሳ ያየንበት አጋጣሚ ቢሆንም፤ የግርማ ካሳ ክስተት በብዙ የአገራችን የፖለቲካ ካልቶች (አምላኪዎች) ያየነው ምፍትሄ ያልተገኘበት ከባድ የአገራችን psychological discomfort ችግር ነው።
አስገራሚው የግርማ ካሳ Cognitive
dissonance ክስተት ድርጀቱ የፈጸመው ከባድ ወንጀልን አሳንሶ
በማየት ብቻ ሳይገደብ ፤ ድርጅቱ እግርዋ እንደተሰበረች ኤሊ 3 አመት ሙሉ መላወስ አቅቶት በአሳፋሪ ሁኔታ እርስበርስ እየተጋደለ ሲንፏቀቅ
እያየ እና አሁን ደገሞ ያ “ፓተርን” በሎ እራሱ የሚጠራው የወንጀል ድግግሞሽ ባሕሪ እየቀጠለ መሆኑን እያመነም “ድረጀቱ ብጥሩ
ቁመና ነው ያለው፤ ስጋት አይግባችሁ” እያለ ሲስብክም አድምጨዋለሁ። የሞራል ኮማፓስ የተሰበረበት ድረጅት በዛው “ፓተርን” እንዲቀጥል መስበክ ለብዙ
አመታት ድርጅቶች የሚፈጽሙት ወንጀል እንዲቀጥሉበት ከሚያደርገው ካብዱ ችግር እንዲህ ያሉ ቅሰቀሳዎች ናቸው።
እንዲህ ያለ የመግረፍ እና የመረሸን ወንጀሎችን አሳንሶ ማየት እና ድርጀቱ በዛው የድግምግሞሽ (ፓተርን) መንገድ እንዳይቀጥል ስናወግዝ በነበርን ሰዎች ላይ በፋኖ አባሎች ዛቻ ደርሶብናል።
ለምሳሌ የጎጃም ፋኖ መሪዎች ብራሳችወ ታጋዮም ሆነ በሕዝብ ላይ እና በምርኮኞች ላይ የሚፈጽሙት ወንጅል መወገዝ እንዳለብተ እና አመራሮቹ ከመሪንተ እንዲነሱ ተደጋጋሚ ትችትና ምክር ስለግስ በነበረኩባችወ ወቅቶች የጎጃም ፋኖ የዲያስፖራ ደጋፊዎቻቸው ብዙ ዛቻ ካደረሱብኝ ሰዎች አንዱን ልጠቀስላችሁ፡
Yonas Andulem Abawa የተባለ የጎጃም ፋኖ ተከታይ እና የጎጃም ተወላጅ ምን ሲሉ እንደ ዛተብኝ ይህንን አንብቡ፤
«Yonas Andulem Abawa
አቶ ጌታቸው ብታርፍ መልካም ነው።በተደጋጋሚ ጊዜ በጎጃም ላይ የአለህ ጥላቻና ንቀት ከልክ የአለፈ ነው ።ተው! አንተና መሰሎችህ ስለዚህ ትግል ተንትኖ ማስረዳት አንደኛ አይጠበቅብንም ሲቀጥል አይገባችሁም።
ሌላው አንተን ቀኝ ጅህን በሚገባ ቆርጦ ማስቀመጥ ይቻላል መፍቴው ቀላል ነው።ዝርዝር አያስፈልገውም አንተም ታቀው አለህ ።ደርሰህ መሪአችንን አትዝለፍ እረፍ ።አልያ ግን ከላይ እንደነገርሁህ ነው!» ሲል
የምትከተለዋ ሌላዋ አሸባሪት ደግሞ ለተቃወማት አንድ ሰው ምን እንዳለቺው ተመለከቱ።
ቤተልሄም ዳኛቸው ትባላለች፡ የጎጃም ተወላጅ ነች። አውሮፓ ውስጥ ትኖራለች። የጎጃም ፋኖ ደጋፊ ብቻ ሳትሆን ልክ እንደ
እነ ዘመድኩን በቀለ ፥ እንደ ግርማ ካሳ እስዋም “ከእነ ዘመነ ካሴ እና አስረስ ማረ” ጋር ቀጥታዊ ግንኙነት ያላት የውጭ ፋኖ
“ዲያስፖራ ካድሬ” ነች። ይህች ልጅ ባንድ ወቅት “ዘፋኝ” እንደነበረች እራሰዋ ስትናገር ሰምቻታለሁ (ዩ ቱብ ላይም አልበምዋ ይገኛል)።
ታዲያ የዘመኑ ጭካኔ ካፈራቸው ዩቱብ እና የቲክ ቶክ ዕብዶች አንደዋ
ይህች ሴት ፡ ሕሊናዋ በሽብር የሞላ፥ የሚቃወሙዋትን ሰዎች ብልት ቆርጣ ጠብሳ እንደምታጎርስ እና ይህንንም “የምታወቅበት ስብዕናየ ነው” ስትል በሚዲያ ቀርባ በኩራት ላንድ ተከራካሪዋ ሰው እንዲህ ስትል
ዝታበታለች፡
«እኔ ቤተልሄም ዳኛቸው እንዳንተው ዓይነቱ ቆሻሻ ፣ ሽንታም፤ ስድብ ብቻ አይደለም እንዳንተው ዓይነቱ ሽንታም ባገኝህ “ብልትህን ጠብሸ” ነው የማጎርስህ። በዚህ ልክ ነው የኔ ስብዕና» በማለት ተከራካሪዋን አሸብረዋለች።
እንደ ቤተልሄም ዳኛቸው እና Yonas
Andulem Abawa የመሳሰሉ እጅ እና ብልት ቆራጭ የፋኖ ግብረ-አሸባሪ
(terrorist) ደጋፊዎች ሰላሉዋቸው ነው የጎጃም ፋኖ አመራሮች ለጃገርዶችን የሚረሽኑ፤ ቀሳውስትን አረጋዊያንን መመሕራንን የሚረሽኑ
እና ሴቶችን የሚደፍሩ እጅ ቆርጠው የሚያሳዩ፤ አሁን ደግሞ የራሳቸው አመራረ አባልን ጭንቅላቱን ዘቅዘቀው ቁልቁል ሰቅለው የእግር መዳፉን ገርፈው ደም በደም አድርገውት እርስበርስ ወደ መታኮስ ተቃርበው
እያየንበት ያለንው ምክንያት የፋኖ እንቀሰቃሴና አደረጃጀት የሽብር ባሕሪ
በተጠናወታቸው አመራሮች እና ደጋፊዎች ስለሚመራ ነው።
ለዚህ ነው አስቀድሜ ትግሉ በማይረቡ ኩታራዎች
ተጠልፎ የጫካ “በጋሚዶዎች” (አጉራ ዘለሎች) እየተመራ እና የወረበላዎች ማፈንጫ የጎጠኞች ታጣቂዎች መፎካከሪያ ሆኗል ስንል “እጅህን
እንቆርጣለን” ሲሉ እንዳንዱም ብልታችሁን ቆርጨ ጠብሸ አጎርሳችሃለሁ የሚሉ
ይህንን የሽብር ስነ-ትካት (እንሲቲንክት የሚታወቁበት ስብዕና
መሆኑን ነው ከአመራሩ ጋር ጥበቅ ግንኙነት ያላቸው የፋኖ ደጋፎች በኩራት ሲናገሩ መስማት የድረጀቱ አመራሮችም ስብዕና ማንነትም አብሮ የነግረናል።
ፋኖ የተባለው ታጣቂ ስበዕና የጎደለው ፤ አርቀው
የሚያስቡ የተማሩ ሰዎች የጎደሉበት የሞራል ኮምፓሳቸው በተበላሹ መሪዎችና Sycophant በሆኑ ደጋፊዎች ሰለተበከለ
ሌላ አመራር እና ስልት ቀይሱ እያልን ስንጮህ ሰሚ አጥተን እነሆ የገዛ ወንጀል ተባባሪያቸው እና የፋኖ አመራረ አባላቸው ማርሸት
ጸሐዩን ዝቅዝቅ ሰቅለው ገርፍውት ዕርስ በርስ እየተወነጃጀሉ ፍጥጫ ውስጥ ገበተዋል። ቅጣዩስ ማን ይሆን?
ሰላም እንሰንብት!
ጌታቸው ረዳ
Ethiopian
Semay
