Tuesday, March 3, 2026

ሉሲፈሩ ያዘጋጀው የ2018 የምርጫ ውድድር ተወዳዳሪዎች እና «የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ጌታቸው ረዳ Ethiopian Semay 3/3/26

 

ሉሲፈሩ ያዘጋጀው የ2018 የምርጫ ውድድር ተወዳዳሪዎች እና «የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን

ታቸው ረዳ

Ethiopian Semay 3/3/26


ከመጀመሬ በፊት በትናንት እና በዛሬው ቀን Ethiopian Semay “ድረገጽያነበቡ አንባቢዎች የሚከተለው አሃዝ ተዘግቧል

3/3/2026 11,948

3/2/2026 4,339

አሁን ወደ ጉዳያችን እንግባ እነሆ!

ትችቴን በዚህ ጥቅስ ልጀምር

“Cry my beloved country!” <<ዕርይ በይ ውዲትዋ አገሬ!>> በተባለው ደቡብ አፍሪካዊው ‘አላን ፓተን’ እንደፃፈው ፣ እንዲህ ይላል: -

 “የተወደድሽ ሀገሬ ሆይ ፣ ላልተወለደው ልጅ ፣ የፍርሃታችን ውርስ ወራሾች ሆኗልና ምድርን በጣም በጥልቀት አትውደድ በይው። በጣቶቹ ውስጥ ውሃ ሲንቆሮቆር በድስታ አይፈንድቅ፤ ወይም ፀይ ስትጠልቅ ዙርያዋ በሚንቀለቀል ቀይ እሳት ስትከበብ እያየ ዝም አይበ ….”

ይላል በኔ አተረጛጎም። መጽሐፉን እንደ ‹ማህበራዊ መዝገብ› የጻፈው በነጭ እና በአገሬው ደቡብ አፍሪካውያን መካከል የነበረውን የዘር ልዩነት እና የዘረኝነት መድልዎ ከመጀመሩ በፊት የነበረውን ማህበራዊ ግጭት ክስተቱን ካየ ወዲህ ‘አላን ፓተን’ ስጋቱን የገለጸበት መጽሐፍ የተረጎምኩት ጥቅስ ነው።

ይህንን ልል ያስገደደኝ አጋጣሚ ነበር። በ2019 በፈረንጅ አመት «በየዓለማቱ መዞር የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች ፈውሰ -ቢሱ ሱስ!» ጌታቸው ረዳ Ethio Semay 11/16/2019» በሚል ርዕስ

“ኢዜማ” ብሎ ራሱን ሚጠራው ባንዳው ብርሃኑ ነጋ እና ከወርቅ ዙፋን ወደ አፈር በመንከባለል ራሱን ያሳጣ የድርጅቱ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል የነበረው “አንዱአለም አራጌ “በMinnesota አሜሪካ ለሚኖሩ ለኖቮምበር 23/2019 “በውጭ አገር ስላሉ ዜጎች ዕጣ ፈንታ ለመወያየት” ይመጣሉ የሚል ማስታወቂያ ተለጥፎ ባየሁበት ወቅት የተቸሁበት ርዕስ ነበር።

 “በውጭ አገር ስላሉ ዜጎች ዕጣ ፈንታ ለመወያየት” ቀርቶ አገር ውስጥ እየተጨፈጨፈ እየተፈናቀለ የዘር ጭፍጨፋ- (ጀነሳይድ) እየተካሄደ ባለበት ወቅት ወስጥ አገር ሰላሉ ተጨፍጫፊዎች ዕጣ ፍንታ ማወቅ ያልቻሉ 27 አመት ዓለምን በመዞር በፖለቲካውና በሕዝቡ ሕልውና ሲቀልዱ የነበሩት በረካታዎቹ “የተደማሪ ተቃወሚዎች” ድፍረትና የፖለቲካ ድሃነታቸውን ስገረም፡አሁን ደግሞ በአብይ አሕመድ ዘመን በ2018 ዓ.ም (በኛ አቆጣጠር) ተቃዋሚ ፓርቲዎች ተብየዎቹ በደም የተጨማለቁ ልብሶች፥ የተበጣጠሱ የራስ ቅሎች፥ የተበላሹ ፊቶች፥ የተበላሹ ደረቶች፥ የተቦረቦሩ ሆድ እና የተቆረጡ አንገቶች እያዩ «6 አመት ሙሉ» ሕዝቡን ለአድማ ሳይቀሰቅሱ፤ በየከተማውና ገጠሩ የአፓርታይዱ ወታደሮችና ካድሬዎች እየተጋፈጡ ሕዝቡን ሳያነሳሱ ፤ ጀሮ ዳባ ብለው፤አፓርታይዱ ለቁንጣናቸው መዝናኛ በሰራላቸው «ፓርክ» ሲዝናኑና ሲጎበኙ ከርመው ፥ ድንገት ብቅ ብለው እነሆ «በ2018 ሉሲፈሩ ባዘጋጀላቸው የተደማሪ ተቃዋሚዎች የምርጫ ውድድር ትዕይንት ተሳትፈው» ስመለከት አገሪቱ መውጣት በማትችልበት ጥልቅ ገደል ውስጥ ገብታ ዛሬም የሚያወጣት እንዳጣች ነጋሪ ምልክት ነው።  

እነዚህ እና የመሳስሉት  ብቻ እኮ አይደሉም፤ አፓርታይዱ ባዘጋጀላቸው ምርጫ የገቡት፥ «ዕርቅ ኮሚሽን» (የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን) የሚባል በአፓርታይዱ ፓርላማ አባላት እና አፓርታይዱን በሚደገፉ አባላት የተገነባ ለድርድርና ለሰላማዊ መስተጋብር ተበየ የሚሰራ መሳቂያ ድርጅትም አለ።

ለትችቴ ማዳበሪያ ይረዳኝ ዘንድ ክርስቶስ ከሰይጣን ጋር ተደራድሮ ወይም ታርቆ ያውቃልን? ከሚል በላይነህ አባተ የተባሉ ከ10 አመት በፊት በእንግሊዝኛ ከጻፉት ዕርቅንና ሽምግልናን በሚመለከት ያቀረቡት ጽሑፍ ጠቃሚ ሆኖ ስላገኘሁት በዚህ ጽሑፌ በብዛት ወደ አማርኛ እየመለስኩ አስፈላጊ ሆኖ ባገኘሁዋቸው ቦታዎች በብዛት ተጠቅሜባቸዋለሁ።

ጸሐፊው የጻፉበት ወቅት በዘመነ ወያኔ የትግሬዎች ሥርዓተ መንግሥት ወቅት ነው።

እኔደግሞ ይህንን ጠቃሚ ጽሑፍ በወያኔ፤ ስሪት የታነጸው ለአፓርታይዱ ፋሺስት አብይ አሕመ።አንዳንዶቹን አባባሎች ለጽሑፉ እንዲመች የለወጥኳቸው አሉ።ጸሐፊው ጽሁፋቸው የጀመሩት በወቅቱ ስለ ሚዲያዎች፤ ፖለቲከኞች እና ከወያኔ መንግሥት ጋር ድርድር/ሽምግልና ሰለሚባለው ጉዳይ ነበር ያነሱት።

እንዲህ ይጀምራሉ፡

«አንዳንድ “ፓንዲስቶች” ፣ ፖለቲከኞች፣ የሀይማኖት መሪዎች እና አክቲቪስቶች ከልማዳዊ ኢትዮጵያዊ ነፍሰ ገዳዮች ጋር ስለ ድርድር እና እርቅ ይናገራሉ። እንደተለመደው እነዚህ ተደራዳሪዎች በተገደሉት ሰለባዎች ወጪ የሥልጣን ወንበሮችን እና አግዳሚ ወንበሮችን ከገዳዮች ጋር ለመጋራት ምራቃቸው ሲያዝረከረኩ ይታያሉ ። ከኢትዮጵያውያን ነፍሰ ገዳዮች ጋር መደራደር ከሰይጣን ጋር መደራደር ነው። በእግሩ ስር ተንበርክከህ የባህሪውን ለውጥ ብትጠይቅ ምንም ያህል ጊዜ ሰይጣን ሰይጣን ሆኖ ይቀራል። ድርድር እና እርቅ ሰይጣንን ወደ መልአክ አይለውጠውም ፤ ነገር ግን መልአክን ወደ ሰይጣን ሊለውጠው ይችላል

ሰይጣንን ህልውናውን ከተጠራጠሩ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) መሪሕ እዩ። እግዚአብሔርን ማንም እንዳላየው ሁሉ ሰይጣንንም ያየው ሰው የለም።

እግዚአብሔር በበጎ ፈቃዱ እንደሚታወቀው ሁሉ ሰይጣንም በክፉ ሥራው ይታወቃል። ቅዱሳት መጻሕፍት የሚሉን «ሰይጣን ይሰርቃል ፣ ያጭበረብራል፣ ይዋሻል እና ቃሉን ያፈርሳል» ። ሰይጣን «ገንዘብን ያመልካል፣ ጥላቻን ያስፋፋል እና በደም መፋሰስ ይደሰታል» ሰይጣን ማለት የዘመነ ወያነ ባሕሪዎች ናቸው>> ይላሉ ጸሐፊው።

ጸሓፊው ወያኔን በመሰሉበት ሰይጣናዊ ስም የወረሰው አሁን ደግሞ ያንን ሰይጣን ባሕሪ ተክቶ ፖሊሲውን በማስቀጠል ወደ ሥልጣን የመጣው አፓርታይዳዊው የኦሮሙማው የአብይ አሕመድ  ሥርዓት ያንን የአማራን ሕዝብ መጨፍጨፈና ማስጨፍጨፍ በመቀጠል ፣ ጭራሽ አማራ አዲሰ አበባ እንዳይገባም ትዕዛዝ በማስተላለፍ በየመፈተሻ ቦታዎች እየተፈተሹ ወደ መጡበት እንዲመለሱ በማድረግ ግፉ በባሰ መልኩ እየቀጠለበት ነው።ይህንን የተደረገው በኔ ዕውቅና ነው ሲል አብይ ሲናገር ሰምተናል (ፓርላምው ውስጥ)።

የወልቃይት ሄጂመኒ (የስልቀጣው) ማስተር ፕላን ዋና አርክቴክቶቹ ወያኔዎች በአማራዎች መቃብር ላይ የትግሬ ሪፓብሊክን ለመመስረት እንዲመቸው ከሱዳኖች ጋር ባደረገው የቆየ ምስጢራዊ ስምምነት የፖርት ሱዳንን ወደብ ለመጠቀም እንዲያመቸው ወደ ሱዳን የሚገናኝበት መውጫ በር ለመጠቀም ሲል በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የወልቃይት አማራዎችን ጨፍጭፎ ወልቃይትና አካባቢው ወደ ትግራይ አዋስኖታል (ይህ የሆነው ገና ጫካ እያለ ጀምሮ ነው)። አሁን አበይ አሕመድ ያንን የጠነጠኑት ደባ ለውጦ በጉልበት የተነጠቀው ወልቃይትና አካባቢው ወደ ነበረበት ወደ ጎንደር እመልሰዋለሁ እያለ ሲያሞኝ ከቆየ በኋላ ወልቃይትና አካባቢው ለትግራይም ለአማራም አይሰጥም በማለት ጢባ ጢቦ ጨዋታ በመጀመሩ ወያኔዎቹም ለጦርነት ተዘጋጅተናል እያሉ እያስፈራሩት ነው።

ይህ ሁሉ የደም ገምቦ ሞልቶ እየፈሰሰ ባለበት ወቅት ሉሲፈሩ አብይ አሕመድ ባዘጋጀው የምርጫ ጨዋታ ተጠቅመን የሉሲፈሩን ሥልን እንወርሳለን ብለው ጨዋታው ላይ የገቡ “ተደማሪዎች” 6 አመት ሙሉ ሕዝባችንን እንደ ጭድ እና እሳት እርሰበርስ እንዲቃጠሉ ቤንዚን ሲርከፈከፍባቸው አዳንዱም ሥራዓቱን ሲደግፉ ከርመው ዛሬ ለምርጫ ውድድር ምልክት ይዘው የድምፅ ማጉሊያ ጨብጠው የማያውቃቸውን ሕዝብ መረጡን እያሉት ነው።ይህን ሁሉ ሰይጣናዊ ተግባር አይተው

ፍትህን ወደ ጎን በመተው የስርዓቱን ዕድሜ ለማራዘም የሥርዓቱ ትወና አድማቂዎች በመሆን ከእድሜ ልክ ነፍሰ ገዳዮች ጋር ተጠያቂነትን ያላካተተ እርቅ እንዲወርድ ፥ ምርጫ እንዲደረግ ይጠይቃሉ።

ይህንን በሚመለከት አስቀድሜ የጠቀስኳቸው ጸሐፊ ወያነ ነካከቶት በነበረው የምክክርና ዕርቅ ማታለያም ይሁን ያንን ሲደገፉ የነበሩት ፖለቲከኞችን አስመልክቶ በእንግሊዝኛ ከጻፉት ወደ አማርኛ የተረጎምኩት አንድ ዘለላ ምክር እንዲህ ይላሉ

«የድርድርና የዕርቅ ሰባኪዎች እባካችሁ የኢትዮጵያን መንገድ፣ ወንዝ፣ ገደል፣ ተራራ፣ ጫካ፣ ሸለቆ፣ መስጊድ እና ገዳማት ላይ የተወረወሩትን የተጨፈጨፉ ሕጻናት እና ወላጆችን ሥዕሎች ተመልከቱ! በደም የተጨማለቀ ልብሶች፥ የተበጣጠሱ የራስ ቅሎች፥ የተበላሹ ፊቶች፥ የተበላሹ ደረቶች፥ የተቦረቦሩ ሆድ እና የተቆረጡ ጡቶች ላይ ትኩረት ስጡ።» ሲሉ ከ10 አመት በፊት በጻፉት ላይ ዋናው ትኩረት መሆን እንደነበረበት ያሳስቡ ነበር።

ዛሬም ያንን ግፍ ቀጥሎ ወለጋ ውስጥ <<ወላሂ ሁለተኛ አማራ አልሆንም አትግደሉኝ>> እያለች አማራ ስለሆነች በግፍ በጭካኔ የተረሸነችው ‘’ህጻን ሃንሻ ሰዒድ” ደም እየጮኸ ባለበት ወቅት ተቃዋሚ ተብየዎቹ ዳንኪራ ሲመቱ ከርመው ከእንደዚህ አይነት ነፍሰ ገዳዮችና አስገዳይ መንግሥት ባዘጋጀው የምርጫ መንበር ተቀምጠህ ጥገናዊ ለውጥ ነው የምናካሂደው እያሉ «ሕዝናዊ አመጽን እያወገዙ» ስለምርጫ ማሰብ ምን አይነት ሕሊና፣ ልብ እና አንጀት እንዳላቸው እየገረመኝ ነው።

አንዳንዶቹ ዕጩ ተወዳዳሪዎች የአብይ አህመድ ፓርላም የመረጣቸው የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከተባለው ጋር የሚሰሩ ናቸው።የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን (Ethiopian National Dialogue Commission) በተባለው የጉባኤ ተስታፊዎች በየከተማው በተደረገ የወጣት (የገዢው መደብ ወጣት ማሕበራት ማለት ነው) ፥ የሙያ ማሕብራት የፖለቲካ መሪዎች ፤ የሕዝብ ወኪሎችን ወዘተ  ለኮሚሽኑ ምክክር ዝግጅት ሲያሳትፍ ፥ ሆን ተብሎ “ሥርዓቱ የገደላቸውና ያለ ሕግ በግፍ የጨፈጨፋቸውና  በስርዓቱ ወታደሮችና ፖሊሶች እና በሃገር ገንጣይና እሰላማዊ ታጣቂዎች የተደፈሩ እንስቶች ፥ እንዲሁም በማንነታቸው እየተለቀሙ ከወለጋ ፥ ከሶማሊ ፥ ከጂማ ፥ ከጉምዝ ፥ በጅምላ የተባረሩ ፥ የታሰሩና የተገረፉ ፖለቲካ እስረኞችና ዘመድ አዝማድ ወኪሎቻቸው ያላሳተፈ፤ ንብረታቸው በሥርዓቱ ባለጊዜዎች የተነጠቁ፤ ከደሳሳ ጎጆአቸው በቡልደዘር እየተጠረጉ እንዲወጡ የተደረጉ በረንዳ አዳሪዎችን ያላሳተፈ ይህ «ሀገራዊ መክክር ለሀገራዊ መግባባት» (የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን) ተብየው አዋቃሪው <<የብዙ ነብሳት ደም ተጠያቂ የሆነው የአብይ አሕመድ ስርዓትና ፓርላማው>> ነው።

 አንዳንዶቹ በጭፍጨፋ ወንጀል የተሳተፉ የወያኔ እና የኦነግ መሪዎች አሉበት። ይህንን ስንመለከት ወንጀለኞቹ በራሳቸው ተጠያቂነት ላይ ፈትሕ እንዲመጣ ፍርድ ይሰጣሉ ብሎ ያዋቀረው አካል ብልጣ ብልጥና እራሱ የወንጀሉ ተሳታፊ ስለሆነ በራሱ እንደሚመቸው አድረጎ አዋቅሮታል።

በዚህ የአፓርታይዶቹ 7ኛው ዘመነ ምርጫ ተሳታፊዎች «የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን» ተብየው ደጋፊዎች ናቸው»። በዙዎቹ ከርስትያኖች ናቸው የሚል ግምት አለኝ።በክርሰቶስም የሚያምኑ ናቸው። አብይ አሕመድ ሰይጣን ነው።ሰለሆነም ክርስቶስ ሰይጣን ባዘጋጀለት መድረክ ከሰይጣን ጋር ተደራድሮ ወይም ታርቆ ነበር የሚል አንብበን አናውቅም።

የህወሓትም ይሁን የህወሓት ሥርዓት እያስቀጠለ ያለው አብይ አሕመድና አሽከሮቹ ሉሲፈሮች ሥርዓት አስቀጣዮች መሆናቸውን እያወቁ በ2018 ዓ.ም ሉሲፈሩ ባዘጋጀው የምርጫ ውድድር ተሳታፊ በመሆን ሉሲፈሩ አብይ አሕመድን ከሥልጣን እናስወግዳለን ማለታቸው በታሪክ ላይ ራሳቸውን በባንዳነት እና ስቃይ አስረዛሚነት እያስመዘገቡ መሆናቸውን እያወቁ ወይስ ሳያውቁ በየዋህነት?

አብይን በራሱ መድረክ እናሸንፈዋለን ሲሉ ካለፉት የ6 ጊዜ የምርጫ ታሪኮች መማር ለምን አልቻሉም? ያውም ከነሱ በፊት እሳት የላሱ እንደ ልደቱ አያሌው እና “አንዱአለም አራጌ” የመሳሰሉ መደርኩን መቆጣጠር የሚችሉ የሕዝቡን ቀልብ ያኖሆለሉ ትንታግ ተወዳዳሪዎች ባየንበት ዓይን እነዚህ ደባሪ አንደበቶች የሕዝብን ቀልብ እንስባለን ብለው መድረክ ላይ ደፍረው መውጣታቸው አንድ ነገር አስታወሰኝ።

 በድሮ ዘመን ዩኒቨርሲቲ ለመማር ወደ አዲስ አበባ የመጡ የክፍለሃገር ተማሪዎች አዲስ አበቤዎቹ ሲደንሱ አይተው እንደንስ ብለው የዳንኬራውን ምት ሳይከተሉ የወለሉን ግርማ በማበላሸት የደናሾች መሳለቂያ ሲሆኑ እንደነበሩት የድሮ የክፍለሃገሩ ልጆች ሁሉ ፣ የዘንድሮ የ2018 ዓ.ም የምርጫ ተወዳዳሪ ንግግራቸው ደባሪነት ሳይ አስቂኞች ከመሆናቸው ባሻገር አብይ አሕመድ ትንታጉን ልደቱ አያሌውን ከውጭ ወደ አገር እንዳይገባ ያገደበት የፍራቻው ምክንያት ለምን እንደሆን  አሁን ይገባቹሃል ብየ እገምታለሁ።

ምርጫ እየተባለ አሁን 7ኛው ጊዜው ነው፤ 6 ጊዜ ተቀልዶብናል፤ ዛሬ ለ7ኛ ጊዜ ሊቀለዱብን ዝግጁ ናቸው

«ቀልቀሎ ስልቻ ፤ ስልቻ ቀልቀሎ» በሚል  በጻፉት አንድ ጸሐፊ ብ1984 ዓ.ም  አእምሮ በሚባለው መጽሔት ላይ እንዲህ ብለው ባሉት ልሰናበታችሁ።

«አንድ የታሪክ ሰው እንዳስቀመጡት “ከአምባገነኑ ደርግ  *ሀ* ”  “ወደ ደርግ  *ለ* ተሸጋግረናል። የማክልበት ነገር ቢኖር ‹ደርግ ለ» የ «ደርግ ሀ» አስከፊ ገፅታ መሆኑን ነው”። ባሉት መሰረት አሁን ደግሞ «ከአፓርታይዱ ወያኔ ሀ» ወደ «አፓርታይዱ ወያኔ ለ» ተሸጋግረናል። የማክልበት ነገር ቢኖር «አፓርታይዱ ወያኔ ለ» ወደ «አፓርታይዳዊ ኦሮሙማ» የተሸጋገረ «የአፓርታይዱ ወያኔ ለ» አስከፊ ገጽታ መሸጋገራችንን እየገረመኝ በመርጫ ስም «ያልጣለውን ዕንቁላል እንደሚታቀፍ ወፍ» ሕዝባችን ሲጮህ ያልደረሱለት የማያውቃቸው ተወዳዳሪዎች እዲያቅፍ መገደዱ ለ7ኛ ጊዜ ማየት የኢትዮጵያ ገዢዎች ማብቂያቸው መች ይሆን?

ሰላም እንሰንብት

ጌታቸው ረዳ

Ethiopian Semay