በታላቅዋ ትግራዋይነት ድምፅ የሚጮህ የትግራይ “ናዚትራ” ርዕይዮተ ዓለም ‘የናዚ ጀርመን “ሊበንስራም”
ቀጥተኛ የመስፋፋት ቅጂ
ጌታቸው ረዳ
(ETHIOPIAN SEMAY)
02/03/2026
በሙሶሎኒ እና በጀርመን ናዚ ርዕዮተ ዓለም የሚመራው የወያነ
ትግራይ የመገንጠል ዕቅዱን ለማስፈጸም የቦታ ማስፋፋት ፍለጋ አያቆምም ብለን ጉንጫችን እሰኪደክም ድረስ
ተናግረናል።እነሆ ሰሞኑን ካደፈጠበት በመንቀሳቀስ አየሩን
“መጠነኛ” የባሩድ ሽታ አውዶታል።
ይህ እያነከሰ ያለ ዝግምተኛ ግን አይቀሬ የመስፋፋት ጦርነት
ሰሞኑን ወደ ጠለምት (ወልቃይት) እና ራያ አካባቢ የመንቀሳቀሱን ክስተት
ዋና የሚዲያዎች ትኩረት ሆኖ ስንብቷል። ለዚህ ሁሉ ለወያነ ሞቶ መነሳት ዋናው ተጠያቂ ደጋግሜ እንደጻፍኩት አፓርታይዱ የአብይ ኦሮሙማ ቡድን
ነው።
አብይ አሕመድም ደጋግሞ ባንደበቱ እንደገለጸው “ወያኔ እንዲጠፋ ፍላጎት የለኝም” ሲል ነግሮናል። ስለዚህም «ነካ ለቀቅ» እያደረገ በሞተች
አይጥ እንደምትጫወተው አይነት ድመት እየተጫወተ ያለው አብይ አሕመድ ለወያነ “ሞቶ መነሳት” ዋናው ተጠያቂው ሰው አብይ አሕመድ ነው።
በምስል የቀረቡ ሁለቱ ካርታዎች
የመጀመሪያው “የናዚትራ” መንጋዎች (የትግራይ ናዚ መንጋዎች) የፈጠሩት የትግራይ ነባር ካርታ ነው የሚሉት በ2014 ዓ.ም
(በ2022) “የተፈበረከ” ከላይ የለጠፍኩት ካሁን በፊት ያልተጨመሩ በጠቀስኩት ዓ.ም. የተጨመሩ አዲስ “የዓባይ ትግራይ”
ካርታ “አብርሃ
ጂራ” ፥ “አብደራፍዕ” ፥ “ራዕሲ ደጌና” (ራስ ደጌና) ፥ “ዓዲ አርቃይ” ፥ በነሱ አጠራር “ለማልሞ” (ለማሊሞ) ፥ “አለውሃ” ያጠቃለለ አዲሱ “የዓባይ ትግራይ” (የታላቅዋ ትግራይ) ካርታ ሲሆን (ምንጭ Ethiopian Semay)
ሁለተኛውና በክብ የተመለከተው የትግራይ አውራጃዎችና ወሰኖች
በነባሩዋ ትግራይ
የነበሩ አውራጃዎችን እና ይዞታዎች ከመጽሐፈ አከሱም የተገኘ የካርታ
ማስረጃ ነው (ምንጭ አቻምየለህ ታምሩ) ።
ነባር የሚለው ካርታ በነባርነት የሚታወቀው “ትግራይ” በክብ
“መልክኣምድርዋ” የተመለከተው በ8 አቅጣጫዎች/መዓዝኖች/ የተጎራበተና ወሰኖችዋንም ማመሰከሪያ የቀረበ “ነባር” የትግራይ ይዞታ
ነው።
የትግራይ ተስፋፊ ናዚዎች የፈጠሩት መልክአምድር እና የቦታ
ስሞች በነባሩ የትግራይ ካርታ ከሚለው ብምዕራቡም ሆነ ደቡባዊ ከሚሏቸው ቦታዎች “አንዳቸውም” ለማስረጃ አይገኙም።
ከፎቶዎች መጨረሻ ያለው የ1 ሚሊዮን ብር “ቸክ” ምንነት
ልግለጽላችሁ።
በኮረና ወረርሺኝ ምክንያት በመላ አገሪቱ እንዳይደረግ
የታገደው የምርጫ ሂደት በመጣስ ትግራይ ውስጥ በ2020 እሁድ ነሐሴ የተካሄደው የትግራይ ፖለቲካ ምርጫ ተወዳዳሪዎች ቀርበው ለነበሩ «ትግራይ ሃገር ሆና እንድትመሰረተት» የሚታገሉት 4ቱ ተገንጣይ ፓርቲዎች
፤ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት)
ባይቶና ዓባይ ትግራይ (ባይቶና)
፤ ሳልሳይ ወያነ ትግራይ (ሳውት)፤
ውድብ ናፅነት ትግራይ (ውናት)
በመላው ሃገሪቱ የሚገኙ የትግራይ ነጋዴዎች ማሕበር 4 ቱ ድርጅቶች «የግንጠላ አጀንዳ በማራመዳቸው» ለ 4 ቱ ሃገር ገንጣይ
ድርጅቶች እያንዳንዱ 1,000,000.00 ብር እና የየራሳቸው አርማ ያሉባቸው የግድግዳ ሰዓቶች፤ በጠቅላላ 4,000,000.00
ብር በሽልማት ያበረከቱላቸው ቸክ ነው።
የሽልማቱ አስረካቢ የምርጫው “ኮሚሽነር” ተደረጎ የተመረጠው ዶ/ር
ሙሉወርቅ ኪዳነማርያም ነው።
የትግራይ ንግድ ማሕበረሰብ ያደረጉት ልክ የኢጣሊያ የንግድ
ማህበረሰብን ጨምሮ የኢንዱስትሪ ግዙፍ ኩባንያዎች እና የባንክ ባለሙያዎች እንዳደረጉት ለቤኒቶ ሙሶሎኒ እና ለፋሽስት ፓርቲያቸው
በተለይም በ1920ዎቹ መጀመሪያ ላይ ሥልጣን ላይ በወጡበት ወቅት እና አገዛዙ በተጠናከረበት ወቅት ወሳኝ የገንዘብ፣
የሎጂስቲክስና የፖለቲካ ድጋፍ ያደርጉ የነበሩት እነዚህ ማሕበረሰብ ክፍሎች ናቸው። ይህ ድጋፍ በአብዛኛው ያነሳሳው ምክንያት
አክራሪ ብሔርተኝነት ያነሳሳው ድጋፍ ነው።
ለወደፊቱ በዚህ ድንኳን በተተከለበት የሽልማት ወቅት
በተደረገው መስከረም አንድ ቀን (ቅዱስ ዮሐንስ ዕለት) የተከበረው ሃይማኖታዊ በዓል ላይ መላው የመቀሌ ሕዝብ በተሰበሰበበት
ከመድረኩ ምን ይነገር እንደነበር ሌላ ቀን አቀርባለሁ።
አንድ ነገር ሳልጠቅስ የማላልፈው ግን ከተጠቀሱት ፓርቲዎች
ውጭ የመገንጠል አጅንዳ የማያራምደው “ዓሲምባ” የተባለው ፓርቲ ሳይሸለም ቀርቷል (!!)።
ይህ ካልኩ ዘንድ ወደ ርዕሱ ልግባ።
የመስፋፋት ውትወታው ምክንያታቸው ፣
በተጠቀሱት ቦታዎች የሚኖሩ ትግሬዎች ብዛት ሰላላቸው (ማጆሪቲ) ሆኖው ሳይሆን እነዚህ ቦታዎች በሁለት መንገድ
ጠቀሜታዎች ስላላቸው ነው።
1ኛው- ትግራይ ወደ ሃገርነት ለመመስረት ባላቸው ዕቅድ “የተጠቀሱት የውልቃይትና የመተማ ወዘተ. . . ልክ እንደ ባሕር ወደብ” መሸጋገርያ በማድረግ ወደ ውጭ አገር
መውጪያ በር ስለሚሆንላቸው፡
2ኛ- የተጠቀሱት አካባቢዎች ለም መሬት ስለሆኑ ለሚመሰርቱት “ሃገር” ሕዝባቸውን ለመመገብ ስለሚያስችላቸው ነው።
3ኛ- ትምክሕት የወጠረው ያልሆኑትን “ለመሆን” ያመጣው ተስፋፊ ባሕሪ ነው።
ይህንን የመስፋፋት አጀንዳ
ቀጣይ ለማድረግና ሃገር ለመመስረት እንዲያመቻቸው፤ በማንነት ቀውስ የሚሰቃዩት፤ ያልሆኑትን “ለመሆን” ከሚከጅላቸው ፤ እንደ
“ሰው ሳይሆን እንደ ጎሰኛ” የማስብ ባሕሪ ከፉኛ የተጠናውታቸው ናቸው።
ይህንን በቀጣይነት
የምናየው በሰው ልጅነት ማሰብ ያቆሙ ብዙ ትግራይ ምሁራን እና “ወያኔዎች የወለዱዋቸው አዲስ ውልደት የሆኑ የግንጠላ “መርህ”
(አጀንዳ) የሚያራምዱ በርካታ የናዚትራ (የትግራይ ናዚ) ድርጅቶች ተፈጥረዋል።
ከነዚህ
ውስጥ እላይ በጨረፍታ ስማቸው የጠቀስኳቸው ህዝባዊ
ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህ ወ ሓ ት) ባይቶና ዓባይ ትግራይ (ባይቶና) ፤ ሳልሳይ ወያነ ትግራይ (ሳውት)፤ ውድብ ናፅነት
ትግራይ (ውናት)... እና 99.999% የትግራይ ምሁራን የዚህ የግንጠላ እና የመስፋፋት አጀንዳ አራማጆች ናቸው።
እንደሚታወሰው በኮረና
ቫይረስ ወረርሺን በሽታ ወቅት በነሓሴ 23/2020 ትግራይ ውስጥ “መረጻ ትግራይ” (የትግራይ ምርጫ) እናካሂዳለን ብለው
ከተሳተፉት 6 ፓርቲዎች ውስጥ ልፍስፍሱ «ዓረና ለዲሞክራሲና ሉዓላዊነት
ፓርቲ» (ዓረና) ፤ እና “ዓሲምባ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ (ዓዴፓ) (ተገንጣይ
ስላልሆነ ከላይ አልጠቀስኩትም) በስተቀር ከላይ የተጠቀስኳቸው 4 ድርጅቶች ስለ ትግራይ ሃገርነት ፕሮግራም አዘጋጅተው
እርስበርስ ሲከራከሩ “በትግራይ ቲቪ” አድምጠናቸዋል።
ሁሉም የሚያቀርቧቸው መከራከሪያዎች ስለ መጪዋ ታላቅዋ ትግራይ የሚያሳይ እኔ እበልጥ እኔ ልመረጥ የትግራይ
መልክአ-ምድር ከዚህ ጽሁፍ ጋር የተለጠፈው ምስል ነው።
ይህ “የናዚትራው” ቡድን
መከራከሪያቸው “ትግሬ
በተፈጥሮ ከአማራ ጋር አትዋሰንም” በማለት ያንን እውን
ለማድረግ እንደ የርዕዮተ
ዓለም አባቶቹ እንደ “ናዚ ጀርመኖች እና የጣሊያን ፋሺስቶች” እንደ ቡልኮ ከዚህም ከዚያም ያጣቀሱዋቸው የተለያዩ የቦታ ስሞችን ቀለሞች ቀባብተው “ትግሬ
በተፈጥሮ ከአማራ ጋር አትዋሰንም” የሚሉባቸው ሦስት ነጥቦች ከትግርኛ ወደ አማርኛ ልተርጉምላችሁ።
እንዲህ ይላል፦
በተፈጥሮ ትግራይ ከአማራ ጋር
አትዋሰንም። ከአማራ ጋር እንድትዋሰን ያደረጋት ዋነኛዎቹ ምክንያቶች ሦስት ናቸው።
1-ትግሬ ሆኖ
በአማራ አስተሳሰብ የተጠመቀ
2-አማራዎች እራሳቸው
ታላቅዋ አምሐራን
ለመፍጠር ያቀዱት ስትራተጂ በመቀዳጀታቸው ምክንያት
3- በተራ ቁጥር 1 የተጠቀሱ ትግሬዎች (የትግሬ ገበሬና የአማራ ገበሬ
አንድ ናቸው፡ ሁሉም ብሄረሰቦች እኩል ናቸው፤ ሕዝብ ከሕዝብ አይለይም፤ሁሉም ሕዝቦች አንድ ናቸው…ወዘተ) የሚሉ “የአማራ አስተሳሰብ” ተሸክመው በተራ ቁጥር 2 ጋር
ከተጠቀሱት ከአማራዎች ጋር ግምባር በመፍጠር ያጸደቁት ፀረ ትግሬ የሆነ የኢትዮጵያ ሕገ-መንግሥት ማለትም “ሽጉጥ
የምትመስል ምጢጢዋ ትግራይ በመፍጠር (ባይቶና የተባለው ፓርቲ እዚህ ላይ እነ መለስን እየወቀስ ነው) የጥንታዊ ነባርዋ የትግሬን ድምበሮች ቆራርሰው ታላቅዋን አምሓራ በመፍጠር ስለተቀዳጁ ነው።” ይላሉ።
የዚህ ሰነድ ግምባር ቀደም አቀንቃኝ ደግሞ የባይቶና ትግራይ መሪ የሆነው
“ናዚትራዊው ቲኦሪሰት” እንደ ጀርመናዊው “Alfred Rosenberg” የሌሎች አጎራባች ሕዝብ መኖርያ ቦታዎችን በመውረር
(ስፔስ ፍለጋ) (ቦታ ፍለጋ) መዋዠቅን ያማረው “ሕልመኛ ተስፋፊ” አማራን በመውቀስና በመዝለፍ የሚቀናው “ኪዳነ አመነ” ነው።
“ቦታን
ማስፋፋትና ሁሉም የኛ” የሚለው ስግብግብ የናዚ ልክፍት የተጠናወታቸው ይትግራይ ምሁራን
ከፈጠሩት አዲስ ካርታ እና የትግራይ ድምበርና ካርታ ለማሳየት የትግራይ “ነባር” ድምበሮች ስሞች እና አካባቢዎች ከስዕሉ
ያቀረብኩት ከመጽሐፈ አከሱም የተገኘ መጽሐፍ በማስረጃ ስታነጻጽሩት “ወያነ ሰራሽ” ካርታ ውሃ አይቋጥርም ።
ትግሬዎች ለምን የመስፋፋት ፍላጎት እንዳደረባቸው በሁለተኛው
ዓለም ጦርነት ወቅት ያነበበናቸው ሰነዶችን ስንመረምር ድርጊታቸው ከናዚ
ፍልስፍና ጋር ተመሳሳይነት እናይባቸዋለን።
ይህንን እንመልከት።
ሂትለር በ1933 ሥልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ
Lebensraum (ሊበንስራም) በተባለው መርሃግብር የአካባቢ ጎረቤት አገሮችን መሬት በማግበስበስ ላይ ያተኮረ የናዚ ዕቅድ
ሲሆን፡ በዚህ መርሃ ግብር “ቦታን የመፈለግና የመውረር ዘመቻ” ብዙ ስራ ተሰርቷል።
መርሃ ግብሩ በአንደኛ የዓለም ጦርነት(1914–1918) መጀመሪያ ላይ ሌበንስራም የኢምፔሪያል
ጀርመን የጂኦፖለቲካ (የቀጠና አሰላለፈና የፖለቲካ-ግንዛቤ ክንውን) ግብ ቀዳሚ ቢሆንም ፤ መሬትን (ስፔስ) የማስፋፋት ዕቅድ
እጅግ የተደገፈው ደግሞ (ኤን ኤስ ዲ ኤ ፒ- National Socialist German Workers' Party -) ፓርቲ እና
የጀርመን ናዚ ፓርቲ እስከ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ማብቂያ ድረስ ተግባራዊ ሆኖ ሲገፉበት ነበር።
አዶልፍ ሂትለር ወደ ሥልጣን ከመምጣቱ በፊት አዳዲስ
የማስፈሪያ ቦታዎችን በቅኝ/ በጉልበት/ የማስፋፋት መርሃ-ግብሩን የጀርመን ግዛት ወደ
መካከለኛው እና ምስራቅ አውሮፓ እንዲስፋፋ የሊበንስራም ዕቅድ ተግባራዊ ለማድረግ (1914–1918) መንቀሳቀሱ ይታወሳል።
የናዚ አጠቃላይ ‘ማስተር ፕላኑ’ በመሠረታዊ ሥርዓቱ ላይ
ሌሎችን ሕዝቦች ከቦታቸው በማስለቀቅ (ወያኔ ለ27 አመት ሲያደርግ እንደነበረውና አሁንም በከፋ መልኩ ለማስፋፋት በወያኔዎቹ
“ከላይ በጠቀስኳቸው” ድርጅቶች እና በመሳሰሉት «የትግራይ ፋሺስትና ናዚ ምሁራን» በመሪ ድርጅታቸው በ’ህወሓት’ እና ባዘጋጃቸው ታጣቂዎቹ በኩል እንደታቀደው
ሁሉ ጦርነት ከፍተው ለሃገረ ትግራይ
ህልውናችን ያስፈልገናል ብለው ባሰመርዋቸው አጎራባች ድምበሮች የጎረቤት ነባር ኗሪዎችን ከቦታቸው በማስለቀቅ።ጀርመኖች እንዳደረጉት ሁሉ
ትግሬዎችም ያንን ተግባራዊ አድርገዋል
ትግሬዎች በወልቃይትና በመሳሰሉ የወሎ ግዛቶች ወርረው ነባሩን
ሕዝብ አማርኛ እንዳይናገር በማድረግ አብዛኛዎቹንም በመግደልና በማስወጣት፤ሴቶችንም በትግሬዎች እየታመጹ ትግሬዎች እንዲባዙ
በማድረግ እና አማራ በሚበሉት መሬቶችም “ሴቶች የአማራ ትውልዶች እንዳይወልዱ በወሊድ መቆጣጠሪያ መርዞችን ወደ ማህጸናቸው በማስገባትና በመውጋትና እንዲሁም በዘር ፍጅት እና በመሳሰሉ የአማራ ዘር በሚሊዮኖች
አንደተሰወረ/እንደቀነሰ (በወያነ ፓርላማም ጭምር ባመነው ዘገባ) ብዙ ሺሕ
ታጋዮቻቸው በሃይል በተነጠቁ ለም መሬቶችና ከተሞች አስፍረው እንዲበለጽጉ እንዳደረጉት ሁሉ ጀርመንም “በሊበንስራም አቅድ”
የጀርመን ዝርያዎች (ኖርዲኮች) ያለምንም ስጋት በምቾት ለመኖርና ለመመገብ ለራሳቸው የእርሻ ትርፍ እንዲያገኙ ሞክሯል።
ይህ የሂትለር ስልታዊ ስግብግነት መርሃግብር የአለም
የበላይነትን ለመቀዳጀት “ቦታዎችን/ስፔስ” በማግበስበስ ብቻ የተወሰነ ሳይሆን በተያዙ ቦታዎች “አሃዳዊ ብቸኛ የዘር ወጥነት” የላቀ የጀርመን
ማህበረሰብ ለማሳደግ ሲባል “በሊበንስራም ዘመቻ የተነጠቁ አገሮችና ጎረቤቶች ውስጥ” ፣ “አሪያን ያልሆኑ ዘሮች”
የጀርመን ማሕበረሰብ አካል እንደሆኑ የሚታሰቡ ቦታዎችን በመለየት የአርያን ዝርያ ያልሆኑትን
እየለቀሙ ማባረር ወይም የአካል የንብረት ውድመት እንዲደርሳበቸው በማድረግ (ወያኔዎች በጉልበት በያዝዋቸው ቦታዎች እንዳደረጉት) በዓለም ውስጥ racially superior society የአርያን ዝርያዎች ልቀው ብብዛትና
በሃያልነት እንዲወጡ የሚረዳ የናዚዎችና የፋሺሰት ጣሊያኖች “የቦታ ፍለጋና መስፋፋት” መርሃ ግብር ታቅዶ በተግባር እንደዋለ ታሪክ
ይነግረናል።
ሲጠቃለል የመርሃግብሩ ሁለት ገጽታዎች የሚከተሉት ናቸው።
(1) ናዚዎች በሚይዙት ቦታዎች ሁሉ ትላልቅ የግብርና እና ኢንዳስትረያል ንጠረ ዕቃዎችን ለጀርመን ህዝብ ፍጆታ ማዋልናዚዎችና/ፋሺስቶች በሚይዝዋቸው ቦታዎች የዘር ማጽዳት በማድረግ የተደላደለ ኑሮ ለአርያን ዘሮች መፍጠር።
(2) የሊበንስራም ሁለተኛው መርሃ ግብር ደግሞ የሌሎች ሕዝቦችን ቦታዎች “የኛ ነበሩ” በሚል ትርክት በወረራ ቦታዎችን በመያዝ በዛው ቦታ የነበሩ “ነባር ተወላጅ ሕዝቦችን” በደምና (በዘራቸው) አርያን ያልሆኑትን እየለቀሙ ማጽዳት ወይንም ከቦታው በማባረር፡ በምትካቸው በሚያዙ ቦታዎች ሁሉ አርያኖችን እንዲባዙ በማድረግ የአርያን ዘር እንዲባዙና ሃያልነታቸው በዓለም መጥቆ እንዲወጣ ማድርግ ላይ የተመሰረተ ዕቅድ ነበር።
(3) በዚያም አስታክኮ ናዚዎች Nordicism (ኖርዲክ/ጀርመኒክ) በቆሸሹ ዘሮች እየተዋጠ ከምድረገጽ እየጠፋ ያለ የዓለም ምርጥ ዘር በመጥፋት ያለ ነው የሚሉት ናዚዎች እና ትግሬዎች “በጉርዲ” (የትግራይ ዘፋኞችና ገጣሚዎች ቃል) በቆሻሻ ዘሮች በተለይ ከአማራ ጋር የተዳቀሉ ትግሬዎች “ትግራዋይነትን” እያቆሸሱት ስለሆኑ ከጉርዲ (ከገለባ) የጸዳ ትግራዋይነት “የተባለ “አዲስ የትግራይ ሃይማኖት በመፍጠር እንደሚንቀሳቀሱት ሁሉ፥
(ፋኖ ውስጥም ተፈራ ማሞ የተባለው “የብአዴን ባህላዊ ጀነራል” ዛሬ “የአማራ ፋኖ ታጣቂ አዋጊ የሆነው «ኢትዮጵያዊያኖች የአማራ ስም ሰለያዙ ስማችንን ስላቆሸሹብን ለባለቤቶቹ ለኛ ለንጹሃን ለአማራዎች መልሰው በራሳቸው ስም ይጠቀሙ’ ብሎ እንዳለው ማለት ነው። በዚህ ጉዳይ ራሱ የቻለ ርዕስ እያዘጋጀሁ ነው በሚቀጥለው ጊዜ እመለስበታለሁ)።
እነሆ የትግራይ ምሁራን እና በርካታ
ድርጅቶቻቸው የማስፋፋት መዝሙር በማስተጋባት ለብዙ አመታት የሕዝብ እልቂት ምክንያት እንደሆኑት
ሁሉ ከዚያ ሳይማሩ ሰሞኑን ደግሞ አድፍጦ
የነበረው ወያነ ወደ እሚያልማቸው ቦታዎች እየተንቀሳቀሰ ነው።
ጥጋብ አላስቀምጥ በሎት ራሱ በለኮሰው
ጦርነት ጫካ እያለ ጀምሮ በጉልበት የያዛቸው የነ ጠለምት እና የመሳሰሉ ወደ በባለቤቶቹ በመግባታቸው ያንን እንደገና ለማስመለስ
ጦሩን ወደ ተጠቀሱት ቦታዎች (ጠለምት....) በማንቀሳቀስ ቶክስ ክፍቶ አልሆን ሲለው ተመልሶ ወደ ትግራይ አፈግፍጓል ይባላል።
ጫካ እያለ የዘር ማጽዳትና ማጥፋት ወንጀል እየፈጸመ ይዟቸው የነበሩት ቦታዎች ተነጥቅኩ በማለት ተደጋጋሚ
የማጥቃት ሙከራ እያደረገ ያለው ምክንያት ያንን ኢትዮጵያን የማዳከመና
የማፍረስ «የታላቅዋ ሃገረ ትግራይ ምስረታ ዕቅዱ» እውን
ለማድረግ ነው።
አስገራሚ ትረካቸው ከነጭራሹ “ጎጃም ጎንደር ሽዋ እና ወሎ እንጂ “አማራ”
የሚባል ዘር የለም “አማራ” ብሎ የፈጠረው “ወያኔ’ እንጂ አማራ የሚባል ሥፍራ/ማሕበረሰብ በታሪክ ተሰምቶ አይታወቅም፡
‘አማራ” የተፈጠረው በ27 አመት ውስጥ ነው፤ ያውም “በወያኔ ዘመን ይላሉ። ስለዚህ አመራ ከትግሬ ጋር ተካልሎ አያውቅም
የምንለው ለዚህ ነው ይላሉ።
ይህ የሚያሳየን ምንድነው? ስንል ከላይ የጠቀስኩት የናዚው ሊሂቅ “Alfred Rosenberg” እንደሚለው
አይሁዶች ሰው
ሳይሆኑ ከአርያን/ ከኖርዲክ ሕዝብ እኩል እንደ ሰው ወይንም እንደ ሕዝብ መጠራት
አይቻልም” ባይ ሲሆን እንደ ጀረመኖቹ ከኖርዲክ ዝርያ ውጭ ወይንም እንደ ተስፋፊዎችና ተገጣዮቹ
ትርክት «ከትግራይ ውጭ
ያለው ሕዝብ እኩል እንደ ትግራይ “ሰው” ሰው ነው ማለት አይቻልም” ይላሉ።
እነዚህን
ሰው ያልሆኑትን ሰዎች ለማንበርከክ “Total alienation እና “Total humiliation” ማድረግ ነው። የላሉ ። ይህንን
ከሚሉት የትግራይ ናዚ ድርጀት መሪዎቹ አንዱ የሆነው ባይቶና የተባለው ተስፋፊና ተገንጣይ ቡድን መሪ «ኪዳነ አመነ እና ድርጀቱ»
ነው።
የትግራይ ተስፋፊ ምሑራን
እና ድርጅቶቻቸው ይህ አዲስ ካርታቸው እውን ለማድረግ ያቀዱት መንገድም “በጦርነት” ነው። ይህንን ለማከናወን
በሱዳን ውስጥ እያሰለጠኑዋቸው ያሉት ከ3 አመት በፊት የከፈቱት ጦርነት ወልቃይት ውስጥ ጀነሳይድ ፈጽሞ ወደ ሱዳን የሸሸው «ሳምረ» የተባለው የትግራይ-«ኢንተርሃሙውዌ»-ቡድን» ከሱዳን
ድምበር እያሾለከ በማስገባት ከውስጥም “ቲ
ዲ ኤ ፍ” በሚል አዲስ ሰም የሚጠራው “የህ ወ ሓ ት” ታጣቂ ጦር በማዘጋጀት ነው።
ይህ “ጦርነት” ደግሞ የሚያየው እንደ ቦታ ማስገኚያ እና ከተሰመሩ አዲስ ካርታዎችና ድመበሮች “አማራን የማጽጂያ/የማጥፊያ” ምቹ መንገድ መሆኑን የትግራይ ተስፋፊ ምሑራን እና ድርጅቶቻቸው ልሳኖች የሚስተጋባ ነው።
በመጨረጻም ይህንን ልበልና ልደምድም፡
ናዚ ከተሸነፈ በኋላ የ “Alfred Rosenberg ጠረጴዛ ሲፈተሽ በጠረጴዛው ውስጥ የተገኘው የእጅ ጽሑፉ እንዲህ ይላል።
“I welcome the war. It is necessary to
exterminate directly all those racially inferior germs of Jewry and its
bastards as a final solution to the problem unsolved for ever two thousand
years …”
“(Alfred Rosenberg- by Fritz Nova P-120 published 1986)
ትርጉም
“ጦርነቱን በደስታ እቀበላለሁ። ለሁለት ሺህ
ዓመታት ላልተፈታው ችግር የመጨረሻ መፍትሄ ሆኖ እነዚያን በዘር ዝቅተኛ የሆኑ የአይሁድ “ጀርሞችን/ትል/” እና መናኛ ፍጡራን
ሁሉ በቀጥታ ለማጥፋት ጦርነት አስፈላጊነት ነው…።” (Alfred Rosenberg- ደራሲ Fritz Nova ገጽ-120 ሕትመት
1986) ይላል የተገኘው ጽሑፍ።
እንግዲህ የትግራይ ነባር ደቡባዊና ምዕራባዊ የትግራይ መሬትና ድምበር ብሎ የፈጠረው ካርታ እውን ለማድረግና አማራን ለማጥፋት ጦርነት አስፈላጊነቱን በግሃድ ሲናገሩና ሲጽፉ እያየን ነው።ይህንንም
እውን ለማድረግ
“ድል ለታሪካዊና ሕጋዊ መሬታችን!”
“ድል ለታላቅዋ ትግራይ!”
የሚለው ድምፅ የትግራይ “ናዚዎች” ርዕይዮተ ዓለም ‘የናዚ ጀርመን “ሊበንስራም” ቀጥተኛ የመስፋፋት ቅጂ ነው።
ሰላም እንሰንብት
ጌታቸው ረዳ (ETHIOPIAN SEMAY)
