Tuesday, June 16, 2026

የገዳዮችን ስም እና መለያ መለውጥ ለአብይ እና ለኦነጎች አዲስ ታክቲክ አይደለም ጌታቸው ረዳ Ethiopian Semay 6/16/2026

 

የገዳዮችን ስም እና መለያ መለውጥ ለአብይ እና ለኦነጎች አዲስ ታክቲክ አይደለም

ታቸው ረዳ

Ethiopian Semay

 6/16/2026

ሰሞኑንን አርሲ ላይ የተፈጸመው ጭፍጨፋ አድራጊዎቹ አይ ሲስ እና የሶማሊያው አልሸባብ ነው እያሉ ዜና ሲያሰራጩ እየስማን ነው (እነሱ የሚፈጽሙት ጥቃት ቢኖርም ፤ ዋና ተዋናዮች አይደሉም፡ ተዋናዩ የኦሮሞዎች መንግሥትሰለፊው እና ኦነግ  ናቸው)። አብይ ከመጣ 8 አመት ውስጥ ወያኔ ከነበረበት 27 አመት የጭለማ ጊዜ ለአማራው፤ ላጋሞው ለጉራጌውና ለኦርቶዶክስ ክርስትያኖች እጅግ የከፋ የዘር ጭፍጫፋ የተፈጸመበት ወቅት ነው አብይን ከዚህ ነጻ ለማውጣት ከአብይ ጎን ተሰልፈው እኛኑን ሲሞግቱን እና ሲከላከሉለት ከርመው አሁን ተቃዋሚው የሆኑት ከፉዎቹ እነሱ ነበሩ። ላደረጉለት ድጋፍ ይቅርታም አይጠይቁም (ሐፍረት የሚባል የለም) በይፋ በሚዲያ ይቅርታ የጠየቀ አንድ ሰው ብቻ ነው የማውቀው እሱም ፕሮፌሰር መሳይ ከበደ ብቻ ነው (ምስጋና ይገባዋል)።

አንድ ወንጀል በተፈጸመ ቁጥር “ዝም ማለት” ወይንም “የገዳዮችን ስም እና መለያ መለውጥ”  አማራን እና አምርኛን ፥ ኦርቶዶክስን እና ስንደቅ አላማን በጥርሱም በጥፍሩም እየቦጫጨቃቸው ያለው አፓርታይዳዊው የኦሮሞዎቹ ሥርዓት የተካነበት ተንኮል ነው።

ከ1983 ጀመሮ ሥርዓቱ የተዋቀረው አማራን ያገለለ ነበር፡ አሁንም ሶበታል አማራን ቅድሚያ በጠላትነት የፈረጀ ነው ስንል በማስረጃ ነው አንድ  ሥር ነቀል መፍትሄ እሰካለተደረገ ስርዓቱና የሥርዓቱ መሪዎች ሥልጣን ላይ እስካሉ ድረስ አማራ እና ኦርቶዶክስ በዘሩ እልቂትን መፈናቀል እየተደረገበት መቀጠሉ ነው። አማራን በማፈናቀልና በመፍጀት የተዋቀረውን ሥርዓት በስንት ደምና በትግላችን የመጣ ስለሆነ በደማችን እናስቀጥለዋለን፡ ይህንን ሕገመንግሥት የማይቀበል ከምርጫ ውጭ መሆን አለበትብሎ አብይ አሕመድ በማያወላዳ ግልጽ ንግግር መናገሩን እኮ ታሪክ የተዘገበው ንግግሩ ነው። ሥርዓቱ አምሐራን ነጥሎ ግምባር ቀደም ተጠቂ ያደረገ አፓርታይድ ስለሆነ አንቀበለውም የሚል አምሓራ አብይ እንደተናገረው ለጀነሳይድ የተጋለጠ፡ነው። የሩዋንዳው ሁቱው ፕረዚዳንት ሃቢአሪማናም ልክ እንደ አብይ አሕመድ ቃል በቃል ደግሞት ነበር

አማራው በረሰብ ምሬቱን እየገለጸ ያለውይህ ሥርዓት ማንነታችን እየለየ እየገደለን ነው እና ሥርዓቱ ይወገድልንሲሉ አብይ ደግሞ14 አመቴ ወደ ጫካ ሄጄ በደሜና በላቤ ታግየ የገነባሁት ሥርዓት ስለሆነ አስቀጥለዋለሁ እናንተም መጨፍጨፋችሁ ይቀጥላል ነውየመልእክቱ ቀጥተኛ አቋሙ።ያ ትክክለኛ ንግግሩ ደግሞ ከሥር ቃል በቃል አቀርባለሁ።

ስለዚህ አማራን እያስገደለ ያለው ሥርዓት በመሪነት የተኮፈሰው አብይ አሕመድ እና ከየጫካው እና ከአወሮጳ እና አሜሪካ ሰብሰቦ ባለሥለጣኖች ያደረጋቸው የኦነግ መሪዎች እና አባሎች ተባብሶ ለቀጠለው ለዘር ጭፍጨፋው ወንጀል ተጠያቂዎች ናቸው

 ክርስትያን አማራ እና እሰላም አማራ  በየቀኑ እየተባረረ፤ መጨፍጨፉ ጨፍጫፊዎችም እነማን እንደሆኑ በተለያየ መልካቸው ሰለፊ (አክራሪው ውሃቢያ) ፤ አይሲስ ወዘተ ይባል እንጂ ያው ከላይ በተጠቀሰው ድርጅትና አመራሮች ማኒፌስቶ (አይዲኦሎጂ) የታጠቡ ከፍሎች ናቸው። ኦርቶኦክስን ላምጥፋተ እና የጀግኖች ሃውልቶችን በማፍረስ አማራን በመጥላትና አማራን በማስጨፍጨፍም ይሁን አማርኛ ቋንቋን ለማጥፋት ስኬታማ ናቸው ብሎ የሹመት እውቅና ሰጥቶ፤ ግድያና ጥላቻ የሚያስፈጽሙበት ዕድሎች ፣ (መኪኖች፥ መሳሪያዎች፥ የባንክ ዘረፋ..) መርቆ በሩን የከፈተላቸውና ወደ አገር እንዲገቡ የፈቀደላቸው ነብሰ ገዳዮች እና ወንጀለኞች አብይ አሕመድ ነው። 3000 አመት እንገዛችሗለን ብሎ አዲስ አባባ ውስጥ በቴ/ቪዥን ቀርቦ የተናገረው ሌንጮ ባቲ የአብይ ከፈተኛ ታማኝ ሰው ነው አደለም እንዴ?

እነ ታየ ደንዳኣ አማራው ቡራዩ ላይ ምን ይሰራል በጭነት መኪና ተጭኖ ወደ ጎጃም ይሂድብሎ የተናገረው አሁን የታሰረው ታየ ደንዳአ ነው፣ አደለም እንዴ? ከረሳችሁት ሙሉውን ንግግሩን እነሆ፡

«በአዲስ አበባ ዙርያ ጎጃሜ አምጥተው ካስፈሩ በኋላ “ሕገ ወጥ ቤቶች እንዳይፈርሱ ሲከላከሉ የነበሩ ነፍጠኞች ማንነታቸው በውል ስለታወቀ የነፍጠኛ ባለቤት መሆናቸው ሰልታወቀ ከዚህ  በኋላ ሂሳብ እናወራረዳለን”።

(ታየ ደንዳአ የኦሮሞ ዲሞክራቲክ ፓርቲ ኦደፓ OPDO አመራር)

 የኦሮሞ ቄሮ ኢንተርሃሙዌው ካድሬ «ሽመልስ አብዲሳ “ነፍጠኛን በቀበረን ቀብረነዋል፤አማራን ሸውደንም ሆነ አሳምነን በቁጥጥራችን አድርገን መቸም ቢሆን እንደማይነሳ አድርገን ቋንቋውን አጥፍተነዋል፡ ላሚትዋንም ወተትዋንም እጃችን ውስጥ ገብታለች…..”

እያለ ኢንተርሃሙዌው ቡድን በግልጽ አዋጁን ለተከታዮቹ ያበሰረው ሽመልስ አብዲሳ ማን ነው የሾ? እሰካሁንስ ለምን ሥልጣኑ ላይ ቆየ? ይህ ሁሉ ፍጅት የዘር ጥቃት አዋጅ ነው ተብሎ አቤቱታ ሲቀርብለትም አብይ አሕመድ ለምን በንግግሩ አልተከፋም? ምክንያቱም ፍላጎቱ እየፈጸሙለት ስለሆነ ነው። ለዚህ ነው አልሸባብ ምንትስ እየተባለ ድብብቆሽ እይተደረገ ያለው።

የባሌ ሮቢ የጀነሳይድ አዋጅ እስኪ ላስታውሳችሁ።

የባሌ ሮቤ ቅድመ ጭፍጫፋ ከጀርመን EHRC ጽ/ቤት ለኦነጋዊው የአብይ አሕመድ መንግሥት ያስጠነቀቀው ደብዳቤ መጀመሪያ ለስነብባችሁና ከዚያም ወደ የኦሮሞ ኢነትርሃሙዌው ቡድን እንመለከታለን።

ስለ ባሌ ሮቤ ዘርና ሃይማኖት ተኮር ቅድመ ጭፍጨፋ ማስጠንቀቂያ EHRC (Ethiopian Human Rights Committee) ከጀርመን 

<<አስቸኳይ መግለጫ

 27 October 2019

አስቀድሞ ማስጠንቀቅ የዜጎችን ህይወት ለመታደግ” EHRC (Ethiopian Human Rights Committee)

በባሌ ሮቤ ባለፈው አርብ ዕለት በግልጽ በጥቃት አድራሾቹ ማስጠንቀቂያ የተሰጠበት ከሰኞ ጀምሮ ሊያካሂዱት ያስታወቁት የጅምላ ጭፍጨፋ እንዳይፈጸም መንግሥት የዜጎችን ህይወት የመጠበቅ ሃለፊነት አለበት።

በዛሬው ቀን ዕሁድ ጭምር ዜጎች ከሃይማኖት እና ዘር ተኮር መሰረት ያደረገን በህይወት ላይ ያነጣጠረን ጥቃት በመፍራት በቤተክርስትያን ተጠልለው ይገኛሉ።

የተቀሩት ቤታቸውን ቆልፈው በጭንቀት እያሳለፉ ነው። ስልካቸውን ለድረሱልን የስልክ ግንኙነት ለማድረግ ለመደወል ስለካቸው ካርድ መሙላት አልቻለም። ሱቆች ዝግ ናቸው።

ይልና በዚያ ባለፈው ሳምንት ዘርና ሃይማኖት ላይ ያነጣጣረ ጭፍጨፋ እንደተካሄደ እንደገና ያ መሰል ጭፍጨፋ እንዳይደገም በድጋሚ መንግሥትን ሲያስጠነቅቅ እንዲህ ይላል፤

“በአካባቢው የገባው የጥቃት ሃይል በቁጥር ከጥቃት አድራሾቹ በትጥቅም በቁጥርም በጣም ስለሚያንስ ስጋት ጨምሯል። ይህንን በባሌ ሮቢ በጥቃት አድራሾች አርብ ዕለት ማስጠንቀቂያ የተሰጠበትን የ “ሰኞ እንመለሳለን” ቀጣይ ዘር እና ሃይማኖት ተኮር ጭፍጨፋ እንዳይካሄድ የዜጎች ህይወት እንዳይጠፋ የኢትዮጵያ መንግሥት ይህንን አስቀድሞ ማስጠንቀቂያ ተቀብሎ ከግምት በማስገባት የዘጎችን ህይወት ለመታደግ እርምጃ እንዲወስድ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚቴ ይጠይቃል፤

(ስዩም ሀብተማርያም ጀርመን) >>

ድምቀትና ሰረዝ የተጨመረ።

አሁን ደግሞ ወደ ኦሮሞው ኢንተር ሃሙዌው ጨፍጫፊው ቡድን አዋጅ እነሆ!

በባሌ /ሃገር (ክልል) በሮቤ ከተማ ደግሞ የከተማው ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ በመሃል ሜዳ ቆሞ በብዙ ሺሕ ሰው ፊት

 

ከባሌ አባ ገዳዎች፤ከሃይማኖት አባቶች፤ከአገር ሽማግሌዎች እና ከቄሮዎች የአቋም መግለጫ ከተንጣለለው የገበያ አደባባይ በቪዲዮና በድምጽ የተቀረጻ አዋጅ ከድምጽ ወደ ጽሑፍ የገለበጥኩትን ላስነብባችሁ እንዲህ ይላል፦

 

ዶርዜና ነፍጠኛ ከሚባል ማንም ሰው ግንኙነት አድርጎ የተገኘ ሰው ፈጣሪ መአት እንዲያወርበት በሼኮች የተረገመ ሲሆን ይህንን ትዕዛዝ ተላልፎ የተገኘ ከነፍጠኛ እና ከጠላት ለይተን አናየውም። ይህን በተመለከተ

1) ከዛሬ ቀን ከዚች ሰዓት ጀምሮ ከነፍጠኛ እና ከዶርዜ ንግድ አንገዛም አንሸጥም።

2) ከዛሬ ጀምሮ መግብ መጠጥ ልብስ ሲገበያይ የተገኘ ሰው የተረገመ ይሁን።

3) ከነፍጠኛ እና ከዶርዜ በልተህ ብትገኝ ፈጣሪ በሽታ ያድርግብህ፤

4) ይህ ድርጊት ፈጽሞ በሃይማኖት በሸኮች የተወገዘ ነው።

5) የኪራይ ቤት ወይንም ሱቅ በረንዳ ይህንን የመሳሰሉትን ከዛሬ ጀምራችሁ ካሁንኑ ሰዓት አከራይታችሗቸው ከሆነ እንድትነጥቁዋቸው።ያላከራያችሗቸው ከሆነም እንዳታከራይዋቸው። እንጠይቃችሗለን፡

6) መሬት እና ቤት እንዳትሸጡላቸው። አሁንም ለመውጣት ተዘጋጅተው ለመሸጥ ከፈለጉም እንዳትገዝዋቸው። መሬቱ የናንተ ነው፤ቤቱም የናንተ ነው።

7) የእህል ወፍጮ ቤት የንግድ ተቋማትም እንዲሁ የመኪና አገልግሎት የመሳሰሉትን አገልግሎቶች ለነዚህ ሰዎች አትፍቀዱ፤ እናንተም እንዳትጠቀሙ። ይህንን አድርጎ የተገኘ ነፍጠኛ ነው ማለት ነው።

8) ዛሬ ሰልፍ የወጣነው ጀግናችን የቄሮ አባት የሆነውኦቦ ጃዋር መሓመድላይ ጠላት ለመግደል ሙከራ ስላደረገበት ድምጽ ሆነንለት ነው። ጃዋርን የሚቃወም መቼም ቢሆን የባሌ ሕዝብ ጠላት ነው።

9) የልጆቻችን ህይወት ያጠፉ የመንግሥት አካል የሆኑ፤ ደሞዝ የሚከፈላቸው መስተዳደሮች፤ ትናንት ልጆቻችንን የገደሉ፤ለፍረድ ይቅረቡልን።

 ይላል።

እንግዲህ ይህንን የዘር ማጥፋት ጥሪ ከተላለፈ በኋላ የኢትዮጵያ የሰብኣዊ መብት ድርጅት /ቤት የዘር ማጥፋት አዋጁ ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት አደጋውን ለማስቆም ለአብይ አሕመድ ያስተላለፈው አስቸኳይ ጥሪአስቀድሞ ማስጠንቀቅ የዜጎችን ህይወት መታደግየሚል የባሌ ሮቤ አክራሪዎቹ እና አባ ገዳዎቹ እንዲሁም ሼኮች እና ቄሮዎች ከሰኞ ጀምሮ ሊወስዱት የተዘጋጀውየዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ አዋጅ/ጀነሳይድመግለጫ በጽሑፍ አስታውቆታል።

 የተፈራው እልቂትም ደረሰ። በዛው ዓርብ ዕለት አዋጅ ታውጆ ለሰኞ እንመለሳለን ያሉ ታጣቂዎች ዓርብ ጥቂት ቀናት በፊት በአማራ ብቻ ሳይሆን በጋሞ ነገዶች ላይም ጥቃት ፈጽመው ነበር። መንግሥት ይህንን ያውቃል። የጋሞ ነገዶችም አርባ ምንጭ ውስጥ ለዜጎቻቸው ስጋትና ደህንነት ሲሉ መንግሥት ጣልቃ እንዲገባ ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ። ሰሚ አልነበረም። 

ይሁንና እነዚህ በሃይማኖታቸው እና በነገዳቸው ተነጥለው ለግድያ የታጩ በሺዎች የሚቆጠሩ ዶርዜዎች እና አማራዎች እንዲሁም ክርስትያኖች በቤተክርስትያን ተጠልለው በፍርሃት ቆፈን እየተንቀጠቀጡ፤ የአብይ አሕመድ መንግሥት እንዲያድናቸው የመንግሥት ያለህ/የአብይ ያለህ/ ሲማጸኑ ነበር። ይህ ደግሞ አበይ በደምብ መረጃውም ጥሪውም ደርሶታል።

 ጋሞዎች ምን የሚል መልእክት ለአብይ አስተላለፈው ነበር? እንዲህ ይላል

መንግሥት ሕግን ማስከበር የሚችል ከሆነ ያስከብር የማይችል ከሆነም እራስችንን ለመከላከል የምንጠብቅበት መንገድ ሁሉ ለመጠበቅ እንገደዳለን”።ብለው ነበር፡ 

ሆኖም አብይ ይህንን አቤቱታ እና ማስጠንቀቂያ ቢሰጠውምግድያው ይቀጥላል፤ ከዚያ ይሰክናልእያለ ነበር። በዚያው አዋጅ መአት ጋሞዎችና አማራዎች በሚያሳዝን አገዳደል ተጨፈጨፉ። ይህ የሆነው ጥቅምት በፈረንጅ ኦክተበር መጨረሻ ገደማ 2019 ነው።

ኢትዮጵያዊ ኢትዮጵያዊውን አርዶ በላው ሲባልእርዱ ይቀጥላል፤ እስኪሰክን ግን ዝም በሉ፤ እኛ ከሠልጣን ከወረድን በመቶ ሺዎቹ ይታረዳሉስለዚም እርዳን አትበሉ ይልቅኑስ አመስግኑኝ! ሲል እርዱ ሕጋዊ አድርጎታል እኮ አብይ አሕመድ

አማራ እየተገደልን ነን ብለው አቤቱታ ሲያመለክቱም አብይ ለሚታረዱ እና ለተፈናቀሉ አማራዎች /ክርስትያነ እና እሰላም አማራዎች/ “አልቃሾችሲል ሰድቧቸዋል።

ቃል በቃሉ ልጥቀስላችሁ፡_

 እንዲህ ሲል፤

አንድም ሰው እሚያመሰግን የለም። ከእስላም አፍአልሓምዱላህንተነጥቋል። ክርስትያናትም ማመስገን የለምማልቀስ ብቻነው። አልቃሽ ሕዝብ ደግሞ አይሻገርም። ችግር ብቻ ነው የምሰማው።እናንተን እያረጋጋሁ ስራየን ልሰራ አልቻልኩም ሕዝቡ ሰላሙን ካልጠበቀ ይህ አሁን የሰማችሁት ልቅሶ ትናንትናም ብዙ ልቅሶ ነበር፤ አሁንም እናንተንም ሸኝቼ አዲስ አልቃሽ ይመጣል፤ የኔ ሥራ እምባ መጥረጊያሶፍት ይዞ መቅረብ ብቻ ሆኖ ቀረ። ሁላችንም እየተጋፋፋን እንዴት እንዲህ ሊሆን ይችላል? አደራችሁን በሚቀጥለው አመትም እንደዚሁመሃረምይዛችሁ ኑ፤ እንዳትረሱ። ወንድሙን ወንድሙን መንገድ የሚዘጋ ከሆነእኔ ምን አድርጌ እፈታዋለሁ?’ ሃይማኖታችሁ እንኳ የማይገዛችሁ ከሆነ? ምን አደርጋችሗለሁ እኔ! በልቅሶ ብዛት አገር አይገነባም እና ትንሽ እንኳን ብትሆን እያመሰገንን እንኑር።

ሲል አንገ በካራ የታረደባት ሚስት ህጻናት በካራ የታረዱባ እናት፤ ሰውን ሰው በልቷል ብሎ ‘አቤቱ ሆይ! አድነን ፤ወታደር ላክልን፤ በክልልህ የሾምካቸው መሪዎች እየገደሉን ነው፤ እነሱን አስወግደህ ጤነኛ መሪዎችን አምጣልን አብያተ ጸሎታችን ተቃጠለብን፤ ብለው አቤት ለሚሉ የሃይማኖት መሪዎች እና ምእመናንእኔ ምን አድርጌ እፈታዋለሁ?’ለምን አታመሰግኑኝም ማልቀስ ብቻአልቃሾችእያለ ጉልበት የሌላቸው እናቶች እና ደከማ ተጠቂውን የሚሳደብ፤ ለሚቀጥለው ዙርም 'መሃረም አትርሱ' የኔ ስራሶፍት ይዞ አልቃሹን እንምባ ማበስ ሆኖ ቀረእያለ እራሳቸውን መከላከል የማይችሉ ነብሰጡሮች እና አረጋዊያን እና እናቶች ከመኖርያ ቤቶቻቸው እየተጎተቱ ወደ በረንዳና ጫካ ሲጣሉ፤ አብይ ደግሞ አቤት ስላሉ «ማመስገን የለም “ማልቀስ ብቻ” ነውአልቃሾች እና ምስጋና ቢሶችእያለ ያሾፍባቸዋል

ሰሞኑን ደግሞ አርሲ ውስጥ ከርስትያኖችን ያረደ ቡድን አይ ሲ ስ እና አልሸባብ ነው ማለት ጀምረዋል ። አይ ሲ ስ እና አልሸባብ ከሆኑ ድረሱልን ብለው አቤቱታ ስላቀረቡ ቀሳውስቱን ወደ ጣቢያ ውሰዶ ያሰራቸው  “አልሸባብ” ነው? ታዲያ አርሲ ውስጥ አልሸባብ የራሱ ፖሊሶች እና እስርቤቶች ካለው አብይ ምን እያደረገ ነው?

ብው16ኛው ክ/ዘመን የተደረገው አንዳንድ ጎሳዎች ከዚህ ዓለም የመደምሰስና የመዋጥ ወንጀል፥ የጾታ መደፈር ፥የንበረት ዝርፊያ ፥ ነባር ሕዝቦችን ባርያ (ገባሮ) የማድረግ ፥ የቋንቋዎች መጥፋትና መከለስ  ፥ የከተሞችና የገጠሮች የትራሮችና ውነዞች ሥም መለወጥ ፥ የቅርስ እና የታሪክ ዘረፋ እና እልቂት ሲደረግ “ብዙዎቹ የኦሮሞ ሊሂቃን” በዛው ዘመን ተፈጸመውን ግልጽ የሆነ የራሳቸው ታሪክ ጸሐፍት ድርጊቱን ሳያዛቡ የዘገቡት የሕዝብ ዕልቂት እና ወረራ  ጥያቄ ስንመለከት፤ የዛሬ ኦሮሞ ምሑራን  ጋ” ላ የሚል ቃል ‘ኦሮሞ’ በሚል መለወጥ አለበት በማለት ሥልጣን ከያዙ በኋላ ለውጠውታል። ይህ የታሪካ መበረዝ ሆን ተብሎ ላንድ ምስጢር የተደረገ ተልዕኮ ነው። የኦነግ መሪዎች ፍላጎት ግልጽ ነው (አንድም ወረራውን አያምኑበትም፤  ሌላው ደግሞ የተፈጸመው የዘር ማጥፋት ወንጀልና ወረራ በዛኛው  በሚታወቁበት ስም ስለነበር ያንን ስም ማስቀጠል ወንጀሉን ይፋ ማድረግ ሆኖ ስለተሰማቸው አዲስ የስም ለውጥ ያደረገላቸው “ዮሀን ከራፍት  የተባለ ጀርመናዊ ፓስተር” ተለዋጭ ስም በመቀበል  ያንን የማመለጫ እና መደበቂያ ስልት ተጠቅመውበታል።

  እውነትን መጣስ ነውር ነውና ነገሩን ማድበስበስ እስከ መቸ?  ታሪክ የዘገበው እውነታ በኢትዮጵያ የሶስት መቶ አመት ጥፋት የፈፀሙ ጋ” ላ  ይባላሉ እንጂ ኦሮሞ አይደሉም። የኢትዮጵያ ታሪክ ነውና የሞቱትን፣ የተዘረፉትን ሀብቶቻችንን፣ የተቃጠሉትን ቅርሶቻችንን መታሰቢያ ማቆየት የእኛ ኃላፊነት ነው። ከአክሱም መጥፋትና ውድቀት ጋር የተፈጠረውን ባዶነት ማስረዳት ባለመቻላችን የፈጠረውን ክፍተት እንዴት እንደምንገልጸው የምታውቁት ታሪክ ነው።

ያለፈውን ታሪክ ለመርሳት ሰዎች ራሳቸውን በሌላ ስም እንዲሸሽጉ መፍቀድ አይገባም። በተለይ ደግሞ ኦነግ በፈለሰፈው  "ኦሮሞ" የሚል የነገድ ስም "ኦሮሚያ" በሚባል ያለነበረ አዲስ አካባቢና ስም ሊጨፈጨፉን የጀመሩ እና ወደፊትም ሊጨፈጭፉን ቃል የገቡ ሰዎች ገና ከጅምሩ ጭፍጨፋን ሀ ብለው ሲጀምሩ ሀረር ውስጥ አማራዎችን ወደ ገደል ወርውረው ጨፍጭፈዋል፣ እንደ አርሲ አርባ ጉጉ አካባቢዎች “ሰው አቃጥለው” ፈጅተዋል።

በግልጽ እና በይፋ አማራን ብቻ ሳይሆን የተቀረው ኢትዮጵያዊያኖችን ከማስፈራራት በጭራሽ ቦዝነው አያውቁም። የኦነግን የፖለቲካ ፕሮግራም አንብቡ። አቢይ እና ሽመልስ አብዲሳ እንዲሁም በውስጥም ሆነ በዲያስፖራ የሚኖሩ የኦነግ ተከታዮች በሙሉ (እንደ ፀጋዬ አራርሳ - እጅግ በጣም የበታችነት ስሜት የተላበሱ ግለሰቦች) አማራን (ነፍጠኛን) እና ኢትዮጵያን ለማንም የማትሆን ብትንትን ያለች ሀገር እንድትሆን ይዝታሉ፥ የጀግኖችና የሀገር ስም ሲያጠፉና ሲሳደቡ ሰምተናል።

የ"ኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ሽመልስ አብዲሳ" ታሪካችንን የነፍጠኛ ታሪክ ብሎ ሲናገር እና ሁላችንንም ከጫማው በታች እንደሚረግጠንና ሃገሪቱ አማርኛ አጥፍታ ኦሮምኛ እንድትናገር እንድሚያደርጉ ነግሮናል።

አስገራሚው ነገር ሊሂቃኖቹ እራሳቸው ሲጠሩበት የነበረ ስም እና  የኦነግ ራዲዮ ከሶማሊያ ምድር «ይህ የጋ’’ላ ነፃ አውጪ ራዲዮ ጣቢያ ነው” እያሉ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በጆሮየ ሰስማችወ የነበርውን ወቅት አስታውሳለሁ። ለምን ይዋሻሉ? እራሳቸውን ጋ;ላ ብለው ይጠሩ ነበር። እስከ ዛሬ ድረስ በኬንያ እና በሶማሊያ ጋ;ላ የሚል የጎሳ መጠሪያ አለ (አምስረጃውን ካሁን በፊት ለጥፌዋለሁ)።  ብታሪክ መጽሐፍት እሰከዚቺው ደቂቃ ድረስ “ኦሮሞ” የሚል የተጻፈ የኢትዮጵያ ምንጭ የለም – ዜና መዋዕል ወይም ጂኦግራፊያዊ ምንጮች፣ ወይንም በወቅቱ የነበሩት ሊቅ “አባ ባሕሪ” መጽሐፍቶችም ይሁን  የውጭ ምንጮች  ጋ፤ላዎች ሰለተባሉ የተለያዩ ጎሳዎች እንጂ “ኦሮሞ”  የሚል ስም የጠቀሱት የለም። እያወራን ያለነው እውነተኛ ታሪክ እንጂ የፈጠራ ስም አይደለም።ያለፈውን ታሪክ ለመርሳት ሰዎች ራሳቸውን በሌላ ስም ሊሸሽጉ ቢምክሩም ታሪክ አይፈቅድላቸውም። ቢሞከርም እየሾለከ ይወጣል። ታሪክን አፍነዋለሁ፤ ለጨብጠው ነው ማለት  ሜሪኩሪን ለመጨበጥ መሞክር ነው

አሁን ሰሞኑ እየሆነ ያለው ያንን ሽሸጋ ነው። አርሲ የተፈጸምው ጭፍጨፋ የሶማሊያ አልሸባብ እና አይ ሲስ በተባሉ የውጭ ሃይሎች እንጂ በሀገር ውስጥ ገዳዮች አልተፈጸመም ይሚል በስፋት እይተሰራጨ ነው። ያለፈውም ይሁን አሁን እይተፈጸመ ያለው ወንጀል ላለመርሳት ሰዎች ራሳቸውን በሌላ ስም እንዲሸሽጉ መፍቀድ አይገባም።የገዳዮችን ስም እና መለያ መለውጥ ለአብይ እና ለኦነጎች አዲስ ታክቲክ አይደለም

Ethiopian Semay