Friday, September 18, 2026

በሕዝብ ትኩረት ስር የመኖር እውነታ ጌታቸው ረዳ 9/18/2026 Ethiopian Semay

 

ዝብ ትኩረት ስር የመኖር እውነታ

ጌታቸው ረዳ

9/18/2026

Ethiopian Semay


ህዝቡ ብዙውን ጊዜ የሚያየው አንጸባራቂውን ገጽታ ብቻ ቢሆንም፣ በሰፊው የህዝብ ትኩረት ስር የመኖር እውነታ ግን እጅግ ውስብስብ ነው። "የዝና ውበት" ጊዜያዊ ነው፤ በህዝብ የመገምገም ወይም የመፈረጅ ጫና ደግሞ ልዩ የሆነ የብቸኝነት ስሜትን ይፈጥራል።

በዓሉን እንዴት አሳለፋችሁት? እንግዲህ ከእልቂት ወደ  እልቂት ከተሸጋገርን እነሆ 53 አመት ሆኖናል። እኔ እንደ ገባኝ በኢትዮጵያ አጽናፈ ዓለም በ53 አመት ውስጥ የታዩ ምሁራን (አብዛኛዎቹ) «ፍትህ ደካማ የሰው ልጅ ግንባታ ነው» ብለው ሰላመኑ የኢትዮጵያን ልጅ እንደታራጅ በግ ያለስጋት ፈጁት፤ አስፈጁት።

እሰካሁን ያየቸው ሥልጣን ላይ የወጡ ቡድኖች ይዘዋቸው የሚመጡ ፖሊሲዎቻቸው ለሀገርም ይሁን ለሕዝብ ጎጂ መሆናቸውን እያዩ ያለገደብ ሲተገብርዋቸው አይተናል። ሥልጣን ሲወጡ ሕዝቡን ይረሱታል። ሥልጣን አልኮሆል ነው።

 ልክ እንደ ሥካር ሁሉ፣ ስልጣንም የግለሰቡን ራስን የመቆጣጠር አቅምና ባሕሪ ያዳክማል፤ በዚህም የተነሳ፣ መሪው ራሱን መግታትና መቆጠብ በሚገባው ወሳኝ ወቅት፣ ለተለያዩ ድርጊቶች የሚከፍተው በር ከወትሮው በሰፊው ይከፈታል። በዚህ ጊዜ እራሱንም ሀገርም ለውጭም ለውስጥ ጠላትና ተቃዋሚ ያጋልጣል። ይህ ባሕሪ በጫካም ይሁን በመንበረ መንግሥት ሲተገበር እያየን ነው።

በሥልጣን የመባለጉ ሥካር ሕዝባችንን ለጭፍጨፋ፤ለስደትና ጥላቻ ተድርጓል። እዚህ ላይ በ53 አመት ውስጥ የጥላቻ መሑራኖቹ ያነጣጠሩበት የጥቃት ዒላማቸው ባብዛኛው በአምሐራ ማሕበረሰብ ላይ ነው። ይህ ማሕበርሰብ በደረሰበት ጥቃት ምክንያት እንዲገለል ተደርጓል። ከማህበረሰብ የተገለለ ሰው የሚያጣው ነገር ስለሌለ፣ ተስፋ መቁረጥ የመጨረሻውንና እጅግ አደገኛውን እርምጃ እንዲወስድ ሊያነሳሳው ይችላል።

በዚህ ማሕበርሰብ ሕይወት ከቤት መፈናቀል፣ እስራት፣ ስደት እና ግድያ፤ ስለደረሰበት በነዚህ ራሳቸውን እንደተጨቆኑ በሚቆጥሩ ሰዎች ልብ ውስጥ እሳት ስለተቀጣጠለ፤ ይህ እሳት “በስሜታቸው ጥልቀት ውስጥ” እየነደደ ቆይቶ አሁን ባለበት የጠመንጃ አምጽ ተሸጋግሯል።ለማዳፈንም ሆነ ለማጥፋት አስቸጋሪ ነው።

አሳሳቢው ግን ፤ ይህ አመጽ የፈራነው ተተኪ አምባገነን ቡድን እየተከሰተ መምጣቱ አሳሳቢ ሆኖ እያየሁት ነው። ትግሉ በስሜት በሚጋልቡ ወጣቶች ሰለተነጠቀ፤ ክፉኛ የመንደርተኞች ቡድን እየፈለፈለ እና በሃሳብ የተለያቸውን የገዛ ታጋያቸውን ማጥላላት እና  መረሽን የተለመደ ክስተት ሆኖ እያየሁ ነው።

 በዚህ ላይ መሪዎቹ ጠላት እና ወዳጅ የመለየት ጥልቅ እውቀት ስለሌላቸው ትግሉ ለተለያዩ የቡድን አንጃዎች መፈንጫ ሆኖ የገዢውን መደብ ሸክም አቃልለውለታል። ነፃ እናወጣዋለን የሚሉለት ማሕበርሰብም በገፍ አልደገፋቸውም፤ ከማጡ ሊያወጡትም አልቻሉም።

ጨቋኝ ገዢዎችን በመቃወም የሚያምፁ ሰዎች ጠመንጃ እና መሪነትን ሲይዙ ብዙውን ጊዜ ያንኑ የተበደሉበትን ዓይነት በደል ጫካ ውስጥ ሲደግሙት ማየት ልብ ይሰብራል። ከ53 አመት የመከራ ዘመን አልፈን በዚህ በ2019 አዲስ አመትስ ወዴት እየተጓዝን ይሆን?

ጌታቸው ረዳ