ሞት ለዘላለም ይኑር! እያሉ የሞት ቅድስና እና ማራኪነት እየሰበከ ወጣቶችን ያስፈጀ የትግራይ ነፃ አውጭ ግምባር
ጌታቸው ረዳ
Ethiopian Semay
7/20/26
ወያኔ ልክ እንደ የጀርመን
ናዚዎች ልብ ያላዳበሩ ወጣቶች ቀዳሚው የትኩርቶቹ ኢላማዎች ነበሩ። የወያኔዎች እና የሻዕቢያ ተዋጊዎች ከመሪዎቹ በስተቀር 99%
ወደ ጫካ ሲቀላቀሉ ከ12 እሰክ 15 ዕድሜ ያላቸው ነበሩ።
በወጣቶች ላይ ያነጣጠረ ቀዳሚው የኢላማው ግብ፣ የመሪዎቹ የወደፊት ዕጣ ፈንታ ለማረጋገጥ ሲባል፤ በልጆች ላይ ያለ ምንም ጥያቄ “ታማኝ” መሆንን፣ የአካል ብርታትን እና ጽንፈኛ የዘር ርዕዮተ-ዓለምን መምሪያቸው
በማድረግ ታዳጊ ወጣቶችን ፣ ለራሱ ወታደራዊ እና ፖለቲካዊ ግቦች እንደ መገልገያ መሳሪያዎች በማድረግ ከመሪዎቹ በፊት እኛ እንሞታለን እያሉ እነሆ ሞትና የአካል ጉዳተኞች በገፍ ትግራይ እና
ኤርትራ ውስጥ ለማየት ችለናል።
ሂትለር ሰለ ወጣቶች
ሲናገር እንዲህ ይላል፤
"አካላዊ እና ርዕዮተ-ዓለማዊ ተስማሚነት፡ 'ህመምን መቋቋም የሚችሉ ወጣት ወንዶችንና ሴቶችን እፈልጋለሁ። አንድ ወጣት ጀርመናዊ እንደ ግሬይሀውንድ (greyhound) እንደ “አዳኝ ውሻ” ፈጣን፣ እንደ ቆዳ ጠንካራ እና እንደ እማይታጠፍ ብረት ጠንካራ መሆን አለባችህ።” ይላል፤
ይህ ንግግሩ በኑረምበርግ በተደረገ ስብሰባ ላይ ሲሆን ዋናው ትኩረት ያደረገው “ከትምህርታዊ ዕውቀት ይልቅ ለወታደራዊ ብቃት ቅድሚያ በመስጠት”፣ ከናዚ ወጣቶች ይጠበቁ የነበሩትን አካላዊ እና ስነ-ልቦናዊ ባህሪያት የሚገልጽ ዋና ቅስቀሳ ነበር። ይላሉ ተንታኞች።
ወጣቶችን ለወታደራዊ አገልግሎት ለማዘጋጀት ሲባል፤ አገዛዙ ውጊያን፣ ግዴታን እና ለድርጅቱ ሲባል የሚከፈልን መስዋዕትነት (ሞትን) እንዴት ማራኪና ክቡር አድርጎ ያቀርብ እንደነበር ያየነው ነው።
በዚህ ጭፍን እና ዘረኛ የድርጅት ፍቅር የወደቁ ታጣቂ ወጣቶች ድርጅቱ ዕድሜው ጨርሶ መበታተን ሲመጣ ታጣቂ የነበሩት በጭፍን አምልኮ የድርጅቱን ተልዕኮ ለመፈጸም ሲሉ በርካታ አሰቃቂ ወንጀሎች ይፈጽሙ ስለነበር እነኚህ ባንድ የድርጅት ዕዝ ሰንሰለት የነበሩት ወጣቶች ከድርጅቱ መበታተን ቀን ጀምሮ ቀጥታ የሚገቡት ወደ ለመዱበት ወደ ወንጀል ተግባር ነው። ይህ ድርጊት ትግራይ ውስጥ እንደ ባሕል የተለመደው “ዝርፍያ”፤ “ግድያ” “ሰው ማገት” የምሳሰሉ ወንጀሎች አይተናል። ብዙዎቹ ደግሞ ታጣቂ የነበሩ ናቸው። ይህም ሞት ለነሱ ብርቅ አይደለም እና እየዘፍኑም ሆነ እይታገሉ Viva la Muerte “ቪቫ ላ ሙወርተ” ሞት ለዘላለም ይኑር! እያሉ የሰው ሕይወትና የራሳቸው ሕይወት ይዘው ይጠፋሉ።
ወንጀል በባህል ላይ ተጽእኖ
ያሳድራል፤ ባህል ደግሞ በወንጀል ላይ ተጽዕኖ ያሳድራል ይላሉ በወንጀል ጥናት ያደረጉ ምሁራን። ይህ ማለት ማሕበረሰቡ እንደሚከተለው
የባሕል ዓይነት ፤ ያንድ “ማሕበረሰብ ደህንነት ጠባቂ” የሚሆንበት ወይንም ‘’የደህንነት አስጊ’’ ሆኖ የሚከሰትበት ወቅቶች አሉት
ማለት ነው
እዚህ ላይ “ወቅት” ብየ
የጠቀስኩት ልብ እንድትሉት የምፈልገው “ባሕል የማሕበረሰቡ ደህንነት ጠባቂ ሆኖ ለዘመናት ከቆየ በኋላ ፤ ባንድ ወቅት ፤ የባሕል ብረዛ
(ለውጥ) ሲደረግበት፤ ያ ጠባቂ ባሕል (ነባር) በአዲስ አስጊ ባሕል ይተካና ማሕበረሰቡ ልክ ትግራይ ውስጥና ኦሮሞ አካባቢ እየታዩ
እንዳሉት አሰቃቂ የወንጀል ከስተቶች ምክንያት ማሕበረሰቡ አዝጋሚ ወይንም ፈጣን ሥጋት ውስጥ የገባል
አምና ትግራይ ውስጥ መነጋገርያ
ሆኖ የሰነበተው ያንዲት 12 አመት ዕድሜ ያላት ታዳጊ ወጣት ታክሲ ሲያመላልሳት በነበረው ባንድ ጎረብትዋ ጎረምሳ ወጣት ተጠልፋ ተገድላ ከተሰወረች በ3ኛው ወርዋ
ሬሳዋ መገኘቱ ይታወሳል፡፡ በዚህም መላው ሕዝብ በሁኔታው መደናገጡና እንዴት ሊሆን ቻለ? የሚል ጠያቄ ሲጭር ሰንብቷል
ኢትዮጵያ ወስጥ በተለይም
ሰሜኑ ክፍል አብዛኛው በጥንታዊው የክርስትና መጻሕፍትና ቁርአን መመሪያ የሚከተል ማሕበረሰብ ስለነበር ከንጉሡ (ክ1966 ዓብዮት)
ሞትና ክ63 ምኒሰትሮቹ ርሸና ብኋላ ከዚያም ትግራይ ወስጥ የተከሰተው የ1967 የዳግማይ ወያኔ አብዮት ያሰክተለው የባሕል ለውጥ ማሕበረሰቡ በወንጀልና በሃገር ክሕደት እንዲዋኝ አድርጎታል
የካቶሊክ ፤ የፕሮተሰታንት፤
የኦረቶዶክስና እስልምና መሪዎች በሙሉ በወያኔ የፋሺስት ፖለቲካ አስተምህሮ (ዶክትሪን) የተቀኙ በመሆናቸው፤
ፈሪሃ ወያኔ እንጂ ፈሪሃ ፈጣሪ ሆኖ እንዳይቀረጽ ሆኖ ተሰብከዋል፡፡ ይህ በትግራይ ብቻ የታየ ክስተት ሳይሆን በተለይም ወንጀል እና ጥላቻ እንደ
ዋና የሥርዓቱ መገለጫና መጋበያ (መሳርያ) ሆኖ ጣራ የነካበት ባሁኑ የኦሮሙማው የአብይ አሕመድ አገዛዝ በመላው ኢትዮጵያ ውስጥ እየታየ ያለ አስደንጋጭ ክስተት ነው።
(ሰሞኑን በሐምሌ 2018 (ጁላይ 2026) አብይ አሕመድ ባሕር ዳር ከተማ ሆኖ ሰለ አፄ ዮሐንስ በጎጃም ላይ የፈጸሙት ጭፍጨፋ
እያነሳ ጎጃም እና ጎንደር ፤ጎጃምና ትግራይ ወዘተ....እንዲተላለቁ በስልትና በግሃድ የሰበከው አጋጪ ንግግሩ ሚነግረን ፤ ግጭቶችና
ወንጀሎች ሥርዓቱ የሚፈልጋቸው መሳሪያዎቹ እንደሆነ ማስርጃ ነው)
አትግደል የሚለው የፈጣሪ መመሪያን በመጣስ መግደል እንደባሕል ተወስዶ ወንድም እህቱን ሲገድል የጀብድ ምልክት ሆኖ እንዲታይ ፤ ልጅ የአባቱን ገዳይ እያሞገሰ መቀሌ ከተማ አዳራሽ ሲነገር አውድዮውን አስደምጨአችሁ እንደነበርና የሃየማኖት መሪዎችም ነን የሚሉ እዛው ተቀምጠው ልጁን በጭብጨባ ሲያጅቡት መኖራቸው ትችት መጻፌን አሰታወሳለሁ።
ወያኔ ጫካ እያለና መንግሥት ከሆነ በኋላ ማሕበረሰቡ ገድያና ሞት ቅቡል
ሆኖ እናት 3 ልጆችዋን ወደ ጫካ
ልካ እስዋም ተዋጊ ሆና ልጆችዋ በማለቃቸው ምንም ቅር እንደማይላትና እንደገና ቢወለዱ መልሳ ወደ ጦርነት እንደምትልካቸው በኩራት
ስትናገር መስማት፤ ከምናውቀው የእናት ሆድ ቡቡነት እጅግ የተለየ የልጆቻቸውን ሞት ደጋግመው ቢያዩ ልዩ ኩራትና ደስታ እንደሚሰማቸው የሚገልጹ
የትግራይ እናቶች በርካቶች ናቸው
እንዲሀ ያሉት እናቶችና
አባቶች ሞት ኩራት መሆኑን የሚያመኑ “ኡር ፋሺዝም” (Ur
Fascism) የሜከተል ማሕበረሰብ መሆኑን ካሁን በፊት Ur Fascism ኡር ፋሺዝም የወያኔ ታጋዮች እውነተኛ መገለጫ በሚል አንድ መጣጥፍ መለጠፌ የታወሳል፡፡
የኡር
ፋሺዝም (Ur Fascism) ባሕሪ ምንነት የነገረን ጣሊያናዊው
“ኡምቤርቶ ኤኮ” ነው። በትርጉም ካልተሳሳትኩ
“ኡር ፋሺዝም” ዘላለማዊ ሺዝም ማለት ይመስለኛል፡፡ አንግሊዞች cult of tradition የሚሉት።ኡምቤርቶ
ኤኮ << ህይወት>> ለኡር-ፋሺዝም <<የህይወት ትግል የለም>> ይልቁንም << ህይወት ለትግል ነው የምትኖረው>> ይላል።
<< ህይወት ዘላቂ ጦርነት ስለሆነ በጸጋ ይቀበለዋል። ይህ ግን የአርማጌዶን ስብስቦችን ያመጣል። ጠላቶች መሸነፍ ስላለባቸው የመጨረሻው ጦርነት ሊኖር ይገባል ስለሚል፤ በዛው ቦግ እልም እያለ ያልተቋረጠ የጸብና የጦርነት ጫሪነት የእንቅስቃሴው ሂደት ዓለምን በመቆጣጠር ወርቃማ ሰላምን ማምጣት ይቻላል የሚል ባህሪ አለው>> ይላል። ነገር ግን እንዲህ ያለው ሁሉንም ተቆጣጥሮ ሰላም የሚያመጣ
ተስፈኝነት የተሳካለት ፋሽስት መሪ የለም>>
በማለት የኡር ፋሺዝም ባሕሪ
ርቀት ይገልጽና መጽሐፉን ሳነበው፤ ከጠቀሳቸው የኡር ፋሺዝም 14 ባሕሪያቶች ውስጥ ቀልቤን የሳበው ከርዕሴ መግቢያ የለጠፍኩት በመጀመሪያው
የ17 አመት የወያኔ የጫካ ጦርነት ዘመን “አማረ
ታረቀ” የተባለ የወያኔ ታጋይ በውግያው ውስጥ ግራ እግሩ በከባድ የጥይት አሎሎ ተመትቶ ተቆርጦ በመውደቁ የተቆረጠው ቀኝ እግሩ አንስቶ ወደ
ሰማይ በመቀሰር የሞት ብስራቱን በጸጋ በመቀበል ወዲያውኑ ህይወቱ አልፏል።
እንዲህ ያለ ሞት ኡምቤርቶ
ኤኮ አንዲህ ሲል ይገልጸዋል።
<< … በእንደዚህ ዓይነት አመለካከት ሁሉም ሰው ጀግና ለመሆን ይማራል፡ በእያንዳንዱ አፈ ታሪክ ውስጥ ጀግና ልዩ ፍጡር ነው። ነገር ግን በኡር-ፋሺስት ርዕዮተ ዓለም ውስጥ ጀግንነት “ብርቅ” አይደለም የተለመደ ነው። ይህ የጀግንነት አምልኮ “ከሞት አምልኮ” ጋር በጥብቅ “የተያያዘ” ነው። የፈላንግስቶች መሪ መፈክር “Viva la Muerte “ቪቫ ላ ሙወርተ”” ("ሞት ለዘላለም ይኑር!") ይላሉ። ይህ የሞት አምልኮ ባሕሪ በአጋጣሚ አይደለም፡ ፋሺስት “ባልሆኑ” ማህበረሰቦች ውስጥ ምእመናን “ሞት ደስ የማይል” አንደሆነ ይነገራቸዋል። አማኞች ከተፈጥሮ በላይ የሆነ ደስታ ላይ ለመድረስ “አሳማሚው መንገድ” እንደሆነ ይነገራቸዋል። በአንፃሩ የኡር-ፋሽስት ጀግና “የጀግንነት ሞትን” ይመኛል፣ ለጀግንነቱ “ሞት” “ምርጥ ሽልማት” ተብሎ ይታወጃል። የኡር-ፋሽስት ጀግና “ለመሞት ትዕግስት የለውም”” ። ትዕግስት በማጣቱም “ሌሎች ሰዎችን” ወደ “ሞት” ይልካል። >>
በማለት የ ኡር ፋሺሰቶች “ቪቫ ላ ሙርቴ” - "ሞት ለዘላለም
ይኑር!" እያሉ የሞት ቅድስና
በመስበክ በጦርነት ወቅት እኔ ልሙት እኔ ልሙት እየተሽቀዳደሙ ወደ ጦርነት እሳት በመግባት ይሰዋሉ። ይህ የኡር ፋሺዝም ከ14
ቱ ባሕርያቶች አንዱ ሞትን በቅድስና እንዴት እንደሚያመልኩት ስንመለከት የወያኔ እና የሻዕቢያ ተዋጊዎች ባሕርይ “የ ኡር ፋሺዝም” ባሕሪ እንደተላበሱ ከሚዘግብዋቸው
የታሪክ ማሕደሮቻቸው ለማወቅ ችለናል።ለዝሀ ነው የትግራይ እናቶቸና አባቶች
ልጆቻቸውን እና እራሳቸው ወያኔ
በሚያደረግላቸው የሞት ጥሪ ሁሉ “ሞትን” የምርጥ ትግሬዎች “ምርጥ ሽልማት” ነውና በቅደስና ተቀበለውት እነሆ <<ኡር ፋሺዝ>> ትግራይ
ውስጥ ከነገሠ ውዲህ ሞገደኛ ማሕበረሰብ ተፈጥሯል፡፡ ሰለሆነም ወጣቱ በታነጸበት “ሞገደኛ ባሕል” ምክንያት ራሱን ወንጀል
ፈጻሚና ጉዳተኛ ሆኖ የምናየው ለዚህ ነው፡፡
ባሕልና ሕግ የኛን “ድምበር” (ባውንድሪ) ይወስናሉ፡፡ተፈጠሮ የራሰዋ ሕግ እንዳላት ሁሉ
ማሕበረሰቦች የሚከተሉዋቸው ባሕሎችም ጎልተው የተሰምሩ የቆዩ ሕጎች
መጣስ ከጀመሩ፡ መጣስ የሌለባቸው የተሰመሩ ባሕላዊ ወሰኖች ከጣስን ዋጋ እንደሚያሰከትል ትግራይ ውስጥ ያለው ክስተት አመላካች ነው፡፡ ፋሺስቶች ይህንን
ሃቅ አይቀበሉትም፡፡
የትግራይ ስትከተላቸውና
ሰታከበራቸው የነበሩ ሃይማኖቶች፤ ሕግ፤ አገርና ሰንደቅ አላማ፤ ክ1967 ጀመሮ ተንቀው ተጥለዋል፡፡ትግራይ ውስጥ አመጽ ቅቡል ሆኖ
፤ <<እያባረርክ ግደለው ያንን ሞኝ አማራ>>
ክሚለው አመጸኛ ዘመቻና ዘፈን ጀመሮ የራሱን ጎረቤትና አብሮ አደግ ወንም ወንድምና እህት
በጥይት ወይንም በስለት አርዶ መግደል ንቡር ሆኖ “ኡር ፋሺዝም” ቁቡል ባሕል ከሆነ ወዲህ የማሕበረሰቡን ሰላምና ደህንነት የሚጠበቁባቸው
ነባር ባሕሎች በፋሺስት ፖለቲካ ተተክተው አነሆ ትግራይም መላው ኢትዮዮጵያም
“ባሕል በመታመሙ” ምከንያት ሕዝቡ ችግር ውሰጥ ይገኛል፡፡ አመታዊ በዓላትና ሃየማኖታዊ ስብሰባዎች
የሚሰበኩት ፡ ስለ “ግደለው
አፍነው፤አንተ ሞት አይፈሬ ድንጋይ አናጋሪ ፤ተራራን አንቀጥቃጭ ባለ ልዩ ዲ ኤን ኤ” የሚሉ ዘፈኖችና መፈከሮች የምታስተጋባ ትግራይ ጤነኛ ልትሆን አትችልም፡፡ ሁሌም ሐዘንና ሞት ይከብዋታል፡፡
ታስታውሱ እንደሆነ ትግራይ
ውስጥ ተገደለች የተባለቺው የ12 አመት ታዳጊ ውጣት ብዙ ሰዎች እንዴት ወደዚህ አስነዋሪ የግድያና የእገታ ባሕል ገባን? ሲሉ ከጠየቁት ካሰገረመኝ አንዱ <<ገነጠላና መከፋፈል፤
ጸብ ፤ ጠላቻ፤ ሞትና አመጽ ቅቡል እንዲሆን ከሚቀሰቀሱ <<የፋሺስት ቀሳወስትና ጳጳሳት>> አንዱ “የትግራዩ
አባ ሰረቀበረሃን” ነው፡፡
“ይህ ነብሰ ገዳይ ከየት
ነው የተላለፈብን? እውነት የትግራይ ሰው ነው ይህንን ወንጀል የፈጸመው? እንዴት ወደዚህ ክስተት ገባን? እያለ ተገርሞ
ተከታዮቹን ይጠይቃል፡፡
ትግራይ ውስጥ ሰረቀ በረሃን
የሚያመልከው “ወያኔ” እነ አቶ ገዛኢ ረዳ እና የኔ ዘመድ የሆኑት አቶ ገብረሊባኖስ መዘገቦ የመሳሰሉ አረጋውያንን
እስከ እነ ሕይወታቸው እሳት ወሰጥ እየጨመሩ እንዳላሰቃዩዋቸውና እንዳልገደልዋቸው፤
ሰረቀ ብረሃን ያንን ወንጀል ስመቶ እንዳልሰማ (ራስ መንገሻ ወንድም አይደለህም ብለው የካዱት) ከደጅ የተወለደ ኢሕጋዊ የሆነ የራሥ
ሥዩም ልጅ አታኸልቲ ሥዩም መቀበሪያውን ጉድጓድ አሰቆፈርው ከነ ሕይወቱ ጉደጋድ ውስጥ ገብቶ እንዲቀበር ያደርገ የአባ ሰረቀበረሃን ብቸኛ ሿሚ እና መሪ የሆነው የወያኔ ወንጀል ሸሸጎ ተከታዮቹን ሰብሰቦ ያችን ታዳጊ ህጻን የገደለ ለመሆኑ ትግራዋይ ነው? እኛ ውስጥ ነው የበቀለው? እውነት የኛ ሰው ነው? እያለ እጆቹን እያወራጨ ተከታዮቹን ሲጠይቅና
የትግራይ ሰው ንጹህነት ሲመጻደቅ መስማት “ከአባ
ሰረቀበረሃን” የምሳስሉ አመጽና
ጠላቻ ሰባኪ ፋሺስቶች
ሲነገር በመሰማቴ ብገረምም በዙም አልገረመኝም፤
(fascism had profound archaic roots. it
represented the crude transformation of Christian doctrine into slogans of
political violence) (Theodor Adorno- Anti Semitism and Fascist Propaganda- (A
Brief history of Fascist lies (Federico Finchelstein p/88)
<<(አመጽን አሰመለከቶ)ፋሺዝም ጥልቅ የሰደደ ነባር ሥር አለው፡፡ ነጹሁን የክርስትና አስተምህሮ ወደ ፖለቲካዊ መፈክሮች በመቀየር የፖለቲካ አመጽ ያበረታታል፡፡>> (A Brief history of Fascist lies (Federico Finchelstein p/88) ከሚለው መጽሐፍ ለዚህ ረዕስ ስዘጋጅ ሰሞኑን ካነበብኩት መጽሐፍ፡፡
ትግራይ ውስጥ የመናየው አምጽ ማሕበርሰቡ የፋሺስት ተከታይ ሰለሆነ አመጽ በመለመዱ ሐዘን በመከሰቱ ለሳምንት ያጉረመርምና ክዚያ ወደ ወትሮው ይመለሳል፡፡ የትግራይ ወጣቶች በሙሉ በሚያስብል አሃዝ የፋሲስት ታጋዮች ናቸው፡፤ ለወያኔ መሪዎቸና ባንዴራ ይሰዋሉ፤ ተሰወተዋልም፡፡ ዛሬም በኩራት፤ለመሞት ትዕግስት የላቸውም”። ሌሎች ሰዎችን በመረሸንም ሆነ ወደ ሞት ለመላክ ግድ የሌላቸው ገራፊዎችና ጨካኞች በበዛት የተበራከቱበት አክባቢ ነው፡፡
በሁለመናዊ መልካቸው ከኡር ፋሺዝም ገንዳ የተቀዱት የትግራይ ወጣቶችና
ምሁራኖቻቸው ሞትን ቅዱስ ባሕል አድርገው አሁንም እገፉበት ነው፡፡ ሞትን በማቆለጳጰስ “መስዋእት” የሉታል፡፡
ይፈክሩበታል፤ የጨፈሩበታል፤ይደሰቱበታል፡፡ ሰውን ድበደቦ አሰቃይቶ ገድሎ ቆሻሻ መጣያ ላይ መጣል በአመጽ ተወለዶ በአምጽ ያደገ
ወጣት ሰለሆን መግደልና መሞት ምኑም ማለት አየደለም፡፡
ሞት ተወዳሽ በሆነበት ማሕበረሰብ
የተወለደ ወጣት እንኳን
ለጎረቤቱ
ሕይወት ሊያዝን ቀርቶ ለራሱ ሕይወትም የማየጨነቅ ትግራይ ወስጥ
በሺዎቹ አሉ፡፡
ከላይ የጠቀሰኩትና የምታዩት
ፎቶገራፍ በ17 አመት የወያኔ የጫካ ጦርነት ዘመን “አማረ ታረቀ” የተባለ የወያኔ ታጋይ
በውግያው ውስጥ ግራ እግሩ በከባድ የጥይት
አሎሎ ተመትቶ ተቆርጦ በመውደቁ የተቆረጠው ቀኝ እግሩ አንስቶ ወደ ሰማይ በመቀሰር የሞት ብስራቱን በጸጋ በመቀበል ወዲያውኑ ህይወቱ
እንዳለፈ ወያንዎች በኩራት ሲተርኩለትና ቅዱሰ ሞት መሆኑን ለተቀረው የትግራይ ወጣት በፈለጉ እንዲከተል ይሰብካሉ (ለሞተውም ሆነ
ለቆሰሉት ቤተሰቦቻቸው ግን አይረዱም፟ የንን ቤተሰብ ለመሳሌ)። እንዲሀ ሞትን የሚንቅ እንዲገደልና እንዲሞት ሲሰበክ ሞትን የማይፈራ ሞገደኛ ማሕበረሰብ በተለይ “ሲገድልና
ሲደፍር ፤ እየደበደበ ሲመረምር የቆየ ከጦርነትና ከጫካ ወደ ከተማና ገጠር (ማሕበረሰብ) የተመለሰ የፖለቲካም ሆነ የጦር አዋጊም
ሆነ ተራ ተዋጊ ሕሊናው በደም የተነከረ እንቅልፍ ሲተኛ የሚያባንነው “ድንጉጥ (ሲፍሮዘኒክ) የቀውሰ ሰለሚሆን የሕሊና ጭንቀቱ ለመወጣት መጠጥ አልያም ያልታከመ “ነበሰ ገዳይ”
ሆኖ የጎረቤቱ ለጃገርዶችና ወዳጅ ዘመድ ቢደፍርና ቢገድል በአእእሮ
ሐኪሞች የሚጠበቅ ከሰትተ ነው፡፡
በግፍ ሰለተገደለቺው ምስኪን ታዳጊ ወጣት፤ ባጭር መቀጨትዋ ቢያሳዝንም ትንሽ ብትቆይ ኖሮ እስዋም የዚያ ያልታከመ የወያኔ ታጣቂ ወጣት ማሕበረሰብ አባል ትሆን እንደነበር የሚያጠራጥር አይሆንም ነበር፡፡
ትግራይ ውስጥ የተለመደ ከሰተት
አለ፡፡ሰው ሲገደልና ሲታገት፤ ሴቶች
ሲደፈሩ ውጤት
በማያስገኘው በሰላማዊ ሰልፍ ከመቃወም ይልቅ ሰከን ብሎ ትግራይ ወሰጥ ከ48 አመት በላይ እንክብካቤ ተደረጎለት በቅሎ ሥር የሰደደው
<<የአመጽ ሁሉ እናት>> የሆነው “ኡር ፋሺዝም”
እንዲወገድና ወያኔ የሚባል ድርጅት ከፖለቲካ እንዲታገድ ካልተደረገ
ችግሩ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገረ ሞት ቅዱስ ሆኖ “ቪቫ ላ ሞርቴ”
("ሞት ለዘላለም ይኑር!") እያለች ትግራይ
በማትወጣበት ከባድ ማእበልና ጸጸት ትገባለች፡፡
ጌታቸው ረዳ
