Monday, February 7, 2011

በስሜት ፈረስ መጋለብ አቅጣጫን ያስታል።

ድረስ ለጎጠኛው መምህር (አማርኛ) $25.00 እና ሓይካማ (this is diffrent book/story that is defferent than the Amharic indicated) (ትግርኛ) $15.00 መጽሐፌን ለመግዛት ዕድሉን ያላገኛችሁ ካላችሁ በሚከተለው አድራሻ ደውላችሁማግኘት ትችላላችሁ Telephone (408) 561 4836 (Getachew Reda P.O.Box 2219 San Jose, CA 95109) getachre@aol.com www.ethiopiansemay.blogspot.com

በስሜት ፈረስ መጋለብ አቅጣጫን ያስታልጌታቸው ረዳ ካረንት አፈይርስ የተባለው የትግራይ ሕዝብ ጠላቶች የተደራጁበት “የኢንቴርኔት/የጠጅ ቤት” ቡድን (ፓል ቶክ ይሉታል መሰለኝ ፈረንጆቹ) ትናንት ማታ  እንዳያችሁት በስዕለ ድምፁ ላይ ያስተላለፈው ዘገባ እና ኢሳት የተባለው የስዕለ ድምፅ የዜና ማሰራጫም (መነፅር ያጠለቀ እዚህ በግራ በኩል ስዕሉ የሚታየው ሰውየ፤ የራዲዮኑ መልክት ማስተላለፊያ ድምፅ በእጁ ይዞ የኦጋዴን ነፃ አውጪ “ጣሊባኒሰት/ሙጃሃዲን ባንዴራ” የፎቶ ቁራጭ/ ክሊፕ ደረቱ ላይ computer screen ተለጥፎበት የሚታየው የኢሳት ዘጋቢ ከሆነ) መለስ ዜናዊን ለመቃወም ጀርመን ምዩኒክ ከተማ ድረስ በመሰባሰብ የመጡትን ሰልፈኞች ወደ ኢትዩጵያ ያስተላለፈው መልዕክት ከወንጀለኞቹ ሌላ የከፋው ወንጀል የሚፈጽም የራሱን ዘመን ብቻ ሳይሆን የመጪው ትውልድ ዕድል የሚያበላሹ፤ ከብሔራዊ ወንጀል ፈፃሚዎች ጋር የሚዳራ/የሚተሻሽ ስለሚያስመስለው በሚዲያው ላይ ግልጽ ዘመቻ ከመጀመራችን በፊት እርምጃውን በጥንቃቄ መመርመር ይኖርበታል እንላለን። ይህ ማሳሰቢያም ቸል ሳይለው ለሚዲያቸው ክብርና ህልውና ሲል እንዲቀበለው ከወዲሁ አሳስባለሁ። ደረቱ አጠገብ በክፕ ፎቶ ተለጥፎ የሚታየው የሙጃሃዲኖቹ ባንዴራ “ክሊፕ” ከ ኢሳት ጣቢያ ተላልፎ ከሆነ ጅግ አሳፋሪ ነው።
በተለይ “ካረንት አፈይርስ” ብሎ ራሱን የሚጠራው የትግራይ ሕዝብ ሲሳደቡ የሚውሉ እና የሚያድሩ ጠላቶች የተከማቹበት የፓልቶክ “ሽምቅ ተዋጊዎች” ስበስብ ከኢትዮጵያን ሰንደቃላማ ጋር የኦጋዴን እና በኦሮሚያ ነፃ አውጪ አልቃኢዳዎች የሚውለበለበው የጠላት “ባንዴራ” ጋር በማጋራት ሰንደቃላማችንን ሲያቆሽሹብን በስዕለ ድምፅ ቀርፆ
{“የካረንት አፈይርስ ልጆች- - በተለይም ከኦሮሞ ብሐረስብ (በኔ አገላለጽ ማሕበረሰብ) ወንድሞቻችንና እንዲሁም የኦጋዴን ብሄረሰቦች (ማሕበረሰብ) የተውጣጡ ህዝባችንን ነፃ ለማውጣት ባሁኑ ጊዜ የወያኔን አገዛዝ ሥርዓት ለመጣል የሚያስችለው የጋራ አንድነት እንደፈጠረ ነው የሚያሳየን”}
በማለት ያስተላለፈው የፓል ቶኩ ሽምቅ ተዋጊ ዘጋቢ፤- ኢሳትም እንዲያ አይነት ወራዳ ዘገባ አስተላልፎ ከሆነ ከጥንት 640 ዓ.ም ጀምሮ ኢትዮጵያን ለመደምሰስ የተጠነጠነው ሴራ ከሚያድሱት ጂሃዲስቶች ጋራ ዓለማ ያነገቡ ጠላቶችን መደገፍ መሆኑን ከወዲሁ ሕዝቡ እንዲገነዘብ አሳስባለሁ። ኢነኚህ ጂሃዲስቶች ከጥንት ጀምረው ከዘርአያቆብ አምደፅዩን ወዘተ….ከዚየም በሗላ በተለያዩ የኢትዩጵያ አምበሳ ጦሮች ሲደከሩ የቆዩ ክረስትናን እና እስልምናን የሚያንኳስሱ፤ህግን ሚፃረሩ ተራ ወረበሎች ከጌዜና ከስልጣኔ ጋር የማይሄዱ ጣሊባኖች ጠላት መሆናቸውን አሁንም አሁንም ደጋግመን የፓልቶክ የሽምቅ ተዋጊ ቡድኖችና እንሱን የሚያሰክሩ በያገሩ እየዞሩ ድምፅ ማጉልያ ጨብጠው የሚየሳብዷቸው ዋሾችና ደላሎች አሁንም ደጋግምን እንመክራችሗለን። ተገንጣዩችና ጂሃዲሰቶች ኢትየጵያውያን አይደለንም ስለሚሉ የግድ “ወብድሞቻችን፤ ቅብጥርጥስ ..”የምትሉትን ቂልነት አሁኑኑ አቁሙ!ራሳችሁን አበላሽታችሁ ሌላውን አዲስ ትውልድ አታደንዝዙ አትሞዳሞዱ ማለት “አትሞዳሞዱ” ማለት ነው! ያለፈው ይበቃል! ሌላ ጉድ አታ ምጡብን! የወላጆቻችሁን ታሪክና ባሕል አታርክሱ!ጂሃዲሰቶቹ እና ኦኖጊያኖቹ አቅም ቢኖራቸው የ ኦርቶዶክስ እና ያማራ ገበሬዎች ሴትና እመጫት አርደው በደም እንደታጠቡት ሁሉ ድሮ ኢትዮጵያን በትነው እናንተውን አርደው በጨረሷችሁ ነበር፤ ነገር ግን ዕድሜ ላንዳንድ ኢትዩጵያዊያን ቆራጥ ዜጎች ዛሬም ገትረው ይዘዋቸው አቅማቸው ተመናምኖ ፈረንጅ አገር ለፈረንጅ እየሰገዱ ጌቶቻቸው ያሰፉላቸውን ጨርቅ እያውለበለቡ አገር ከመበተን ርቀው እራሳቸው ስደት ከትተው ከሩቅ እሳቱን ለማቀጣጠል “እፍ…እፍ..”ሲሉ መከራቸውን ሲያዩ እናንተ ደግሞ ጭዱንና ማገዶውን እያቀበላችሁ ማፈሪያ ትውልዶች ሆናችሁ እነሱ ጋር “እፍፍ እፍፍ..” አትበሉ!!!!
እነኚህ በስሜት ፈረስ የሚጋልቡ የትግራይ ህዝብ ጠላቶች የተከማቹበት “?ካረንት አፈይርስ”የተባለው የፓልቶክ ሽምቅ ተዋጊ ቡድን፤ -ቀን በብርሃን ቁርኣን በእጃቸው የያዙ ሲጨልም ደግሞ ሰይፍን የሚያውለበልቡ ጂሃዲሰት ሽብርተኞችን “ውንድሞቻችን”እያላችሁ የማንቋለጫ ስም በመስጠት አልፎም “ከነሱ ጋር የጋራ አንድነት በመፍጠር ወያኔን በመጣል ሕዝባችንን ነፃ እናወጣለን” እያላችሁ ከፀረ አንድነት ከፀረ አገርና ከሽብርተኞች ጋር አንድነትን አበጅተናል በማለት ባደባባይ የሚትለፍፉ “የስሜት ፈረሶች” ዊኪ ሊኪ የተባለው “ምስጢር አውጪ”ድረገጽ እንዳለው እውነትም ተቃዋሚው “ከአብዛኛው ኢትዮጵያ ሕዝብ ልቦና የጎበጠ/ያፈነገጠ’/ያልተጣመረ”ሊለን የበቃውም እንደናንተው ያሉትን የስሜት ፈረሶች ግልቢያ እና ጥድፍያ ግምገማ በመነሳት እንደሆነ ይመስለኛል።
አንባቢ ሆይ!
እነኚህ የስሜት ፈረሶች የት እንደሚጋልቡ እና ከማን ጋር እየጋለቡ እንዳሉ ካላወቁት መለስ ዜናዊና ቡዱኑ ብታምኑም ባታምኑም ብዙ ጌዜ ሊገዛን ነው።የነኚህ ጂሃዲስቶችና ጣሊባን ከሃዲዎች ባንዴራ ያለ ማፈር ሰንደቃላማ ተብሎ- ለዘመናት የብዙዎቹ አፍሪካ መመኪያ ሆና በክብርና በተምሳሌነትዋ በየአፍሪካ አገሮች የምትውለበለብዋ በአረንጓዴ ቢጫና ቀይ ቀለም ያሸበረቀቺው ሰንደቃላማችን ጋር ዕኩል እያጎዳኙ ሲያቆሽሿት ያየነው እንዳይበቃ:-
“ኢትዮጵያዊነታችን ለነፃነታችን ለማስከበር በጋራ እንሰለፋለን ይህ የጋራ አንድነት ሰላማዊ ሰልፍ የመጀመርያው ትልቁ ምልክት ነው ነው…. ምንም እንኳ አንዳንድ ጥራዝ ነጠቆችን ቢደመጡም ያንኑን ከቁም ነገር ሳንቆጥር በጋራ ተሰልፈናል”
ሲል ዘጋቢው ያስደመጠን ዘገባ ምን ማለት ነው? ጥራዝ ነጠቅ ማለት ምን ማለት ነው? ኢትዮጵያ ትውደም! ኢትዮጵያ አውት ኦፍ ኦጋዴን! ሲሉ ጂሃዲስቶቹ እንደ ቀላል ቃላት “ጥራዝ ነጠቅ” እያሉ ቸል ብሎ ህዝቡ ለማንንቱ ነቅቶ እንዳይከራከር ሕዝብን ማዘናጋት ምን የሚሉት ኢትዩጵያዊነት “ወንድማዊ አንድነት” የቱ ጋር እንደሆነ ሊገባኝ አይችልም።
“ህዝባችን ባሁኑ ጊዜ ወያኔን አገዛዝ ለመጣል የሚያስችለው የጋራ አንድነትን እንደፈጠረ ነው የሚያሳየን” ማለት ምን ማለት ነው”? የጋራ አንድነት ከ “ኦኖግያ”፤ ከኦጋዴንያ ሙጃሃዲኖችና ጣሊባን ጂሃዲስቶች? በምን ስሌት ነው “የጋራ ግምባር” እና “አንድነት” ፈጥራችሁ እኛኑን ከወያኔ አገዛዝ ነፃ አውጥታችሁ የኢትዮጵያን አንድነት የምታስከብሩት?ወይስ የነሱ ፈረሶች ሆናችሁ ሊጋልቧችሁ ሲመጡ አለጥልጣችሁ ወገባችሁን በማዘጋጀት ጀብሃዎችና ሻዕቢያዎች በተማሪዎች ማህበር ጊዜ የተጫወቱትን ሚና ዛሬም በነ ብርሃኑ እና በነ ኦነግያ ቡድኖች እየተቀነባበረ ያለው እከከኝ ልከክህ አስቂኝ ‘/የፖለቲካ ኮሞዲ ሴራ ለመድገም ነው”? በጣም አስገራሚ ጊዜ!!!!!
አንድ አገር እንደ አገር ለመቀጠል ከሆነ ቤትህን እና አገርህን ለማፍረስ መጥቻለሁ እያለ በግልፅ ሳይደባብቅ የሚወጋህን ጠላት “ወንድምየ! ጋሽየ” ስላሉት ጠላት ካሰበው ማዘናጋት አይቻልም። ተሞክሮአችን ያንኑ አይቶታል/አልፈታል። ወይስ ኦኖጊያኖቹ እና ኦጋዴኒያኖቹ በረሃውን ሊያለማምዷችሁ ፤ኮሪደር ሊሰጧችሁ ነው ያ ሁሉ “ማንቋለጥ”እያደመጥናችሁ ያለው? ያ ከሆኑ ሕልማቸሁ ደካማ ነው፡ ለራሳቸው ኮሪደሩ ጠቧቸው “ሻ …ዓ…ቢ .. ያ” ጓዳ ውስጥ ከብርዱ ተጠልለው ተጣበው መርሃ ግባቸው አልሰራም ብሏቸው ተቸገርዋል! ወንድሞቼ ልንገራችሁ (የትግሬ ወንድመ የለንም ካላላችሁኝ -ሁሌም በየፓኢልቶካችሁ ትግሬ ትግሬ እያላችሁእንደምትለፋደዱት) ብዙ ተሞዳሟጆች ጠላትን ሲለሳለሱ ኢትዮጵያን አሁን ላለንበት አድርሰውናል። ኤርትራን ከኢትዮጵያ የሚያስገነጡሉበትን ዘዴ አጥብቀው ጣሩ፡ ምሁራን ጠላቶችን እየተለሳለሱ ነፃ አውጪዎቹ ጋር በየአዳራሹና አውሮጳ አሜሪካ “ወንድሞቻችን ናቸው”፤ “ላንደነት በጋራ ቆመናል ፤በጋራ ደርግን ነፃ ከጣልን በሗላ እንነጋገራለን”እያሉ ሲተሻሹ ገንጣዮቹ ግን ኢትዮጵያን የሚያፈርስ ሴራ ሲጎነጉኑ ነበሩ። እንደናንተው ዓይነቶቹ የፈረስ ስሜቶችም ወገባቸውን ለተገንጣዩች እያለጠለጡ ጋልበው ጋልበው ጋልበው አስመራ እና አዲስ አበባ አደረሷቸው። መጨረሻው የሆነው መዘርዘር አያስፈልግም፡ የምታውቁት መሰለኝ። በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ “ኦኖግያም”ሀኑ “የኦጋዴን ጣሊባን ሙጃሃዲኖች”የሚፈልጉት እና የሚመኙት “የኢትዮጵያ ሞት” ነው!! አራት ነጥብ። የጋራ አንድነት የጋራ ንገግር ፤ጋራ ትስስር፤ የጋራ ሰላማዊ ሰልፍ፤የጋራ ጥምረት…ወዘተ…የሚሉት የማታለያ ዝባዝንኬ ጌዜው ያለፈበት ተሞክሮ የከሸፈበት የስሜት ግልቢያና ማዘናጊያ መሽቀንጠር አለበት። ጠላት የሚሞዳሞደው በቂ ሃይል ሲያይልህ እንጂ ውጭ አገር ፓል ቶክ ተወሽቆ ወይንም ዳላስ ቴክሳስ እና ካናዳ አዳራሽ ባንድነት ቁጭ ብሎ ስለለፈለፉና እራት ስለበሉ “ኦነጊያም ሆኑ ሙጃሃዲኒያ” በደማቸው ያደረው የኢትዮጵያ ሞት ከመመኘት ከቶ አይቦዝኑም። የኸን ማወቅ ይኖረባችሗል። እንደገና ልድገመው፤ ኢትዩጵያን የመጥላት አባዜ ደማቸው ውስጥ ስለተሰራጨ “ለ ኢትዩጵ ያ ሞት ከመመኘት” አይቦዝኑም ። ይኸነን ማወቅ ይኖርባችል!!!!!
ከተሰው ጀግኖቻችን ምክር አንድ ነገር ልስጣችሁ። በጠላቶች “አትሞኙ፤ ጠላት ምንም ቢሆን ጠላት ነው!” ብለው ምፅዋ ላይ የቴዎድሮስ ፅዋ አንስቶ የተሰዋው ጀግና ቃል በመዘከር ልሰናበታችሁ። ያ ጀግና ጀርመን ላይ ተውለበለቡ የጠላቶቻችን ባንዴራዎች ኩፉኛ የተፋለማቸው መሆኑን በዚህ አጋጣሚ የስሜት ፈረስ ጋላቢዎች እንዲያውቁት እነሆ። “አንድ ሰው ቤት ሲሰራ የሚሰራው ቤት በርና መስኮቶች አሉት። አንድ ሰው ደግሞ ሞተ እንበል፤መቃብሩ በርና መስኮት የለውም። በርና መስኮት የሕይወት ምልክቶች ናቸው። በመሆኑም ያለ ባህር ብልፅግና ስለሌለ የ ኢትዮጵያ ሕዝብ ባህር ተነጥቆ የሚኖር ሕዝብ አይደለም። ከሻዕቢያ ጀርባ ሆነው ቀይ ባህር የኢትዮጵ ያ አይደለም የሚሉ አገሮች ጋሻ ጃግሬዎቻቸው ሁሉ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ፍላጎታቸው የ ኢትዮ ጵያ ሞት ነው። የባሕር በር የሌላት ሀገር ሞቶ ከተቀበረ ሰው የምተለየው በትንሹ ነው። ምክንያቱም የባህር ሀብት ከማጣቷም በላይ ምርቷን ወደ ውጭ የግዴታ ወደብ ስለምትከራይ ለወደብ ክፍያ የምትከፍለው የገንዘብ ውጭ ዜጎቿን ያደኸያል። በአኳያው ጠላቶቿንና ባለወደቦቹን ብቻ ያበለፅጋል። ይህ ዕድል ለኢትዮጵያ እንዳይደርስባት ቀይ ባሕርን የኢትዮ ያ ትውልድ ይፋረድ”ሲሉ እንደጨረሱ ፊታቸውን ወደ ቀይ ባሕር አድርገው ወታደሩ እያያቸው እንደ ቴዎድሮስ ራሳቸውን ገድለው ወደ ባሕሩ ወደቁና ሞቱ። " ጀኔራል ተሰማ ይባላሉ!
ያ ጀግና ጀኔራል ከመሞቱ በፊት በህይወቱ እያለ በበርካታ አጋጣሚዎች የተፋለማቸው የጠላት ባንዴራዎች በሙሉ ጀርመን ውስጥ በዛ ሰላማዊ ሰልፍ ውስጥ ሲውለበለቡ አይተናል። ቅጥረኛውን ፀረ ኢትዩጵያ መለስ ዜናዊን ለመቃወም ሲባል ብቻ ጀኔራሉ ከተፋለማቸው የለየላቸው የኢትዮያ ጠላቶች ጋር እየተሞዳሞዱ “የጋራ አንድነት” ፈጥረን መለስ ዜናዊን ለመጣል ሰልፍ አደረግን በማለት የኢትዮጵያ ዳር ድምበር እና በከርሰ ማህጸኗ ውስጥ የተካለሉና የታቀፉ ሃብቶች ሁሉ ለማውደም እና ለመቆራረስ ከሚጣጣሩ ጠላቶች ጋራ አንድነት መግጠም ማለት ያለ መብሰልና ያለፉት ትግሎች ያለ ማጠን የተነሳ ችግር ነው። በኤሊባቡር በጂማ በሓረር በባሌ…ክርስትያኖችና አማራዎች በገጃራ አንገታቸው እየተቀላ ጀርመን ውስጥ ለገጀራ መግዢያ ከሚያቀብሉ ጋር የጋራ ግምባር ፈጠርን ማለት የወንጀል ተባባሪነትና አሳፋሪ አንድነት ስለሆነ ለወደፊቱ ከ እንዲህ ዓይነት ዘገባ ከማተላለፍ መቆጠብ ያስፈልጋል። በስሜት ፈረስ መጋለብ አቅጣጫን ያስታል። ሰላማዊ ሰልፉን ማስተባበሩ ጥሩ እያለ መለስ ዜናዊን ለመጣለ፤ኢ ሲባል መጨረሻ ላይ ከጠላቶች ጋር አንድነት ፈጠርን ስትሉ ነገረ ስራችሁ “ወጡን በሚየስጎመጅ መልክ ከሽና ስታበቃ መጨረሻ ላይ ውሃ ሞላቺው የሚባል ትግርኛ ምሳሌን አስታወሰን።በስሜት ፈረስ መጋለብ አቅጣጫን ያስታል።
ኢትዩጵያን ሰማይ አርታኢ ጌታቸው ረዳ my advice to those untrained Horses is “stop flirting with Ethiopian Mujahedeen and Talibanist terrorists” Editor www.ethiopiansemay.blogspot.com or simply Google it (Ethiopian Semay.)