Saturday, December 25, 2021

ስር የሰደደ የበታችነት ስሜት የወለደው የትግሬ ፋሽስታዊ ልዕልና የቪዲዮ ማስረጃ ጌታቸው ረዳ ETHIO SEMAY 12/26/2021

                                     ስር የሰደደ የበታችነት ስሜት የወለደው

የትግሬ ፋሽስታዊ ልዕልና የቪዲዮ ማስረጃ

ጌታቸው ረዳ

ETHIO SEMAY

12/26/2021

ዛሬ በዚህ በለጠፍኩት በስዕለ ድምፁ የምታደምጡት የወያኔ ወረበላ “ታጣቂ” “በኢትዮጵያዊያን የጦር ሙርከኞች ሕሊና” ላይ የፈጸመው ነውረኛ ስነመግባር እንመለከታለን። ቪዲዮውን ስትመለከቱት ሙርከኞቹ ከውስጥ የተሰማቸው ቅሬታና ንዴት፤ መፈክሩን የማስተጋባቱን ውስጣዊ ልግመተኛነት ማየት ትችላለችሁ።

 ወያኔ ድሮም ሆነ በቅርቡ በወረራቸው የአማራ “ክልሎች” የተከተለው የፋሺሰቶች ፖለቲካ ደጋግሞ ያሳየን አስነዋሪነቱ በ ከዓለም አቀፍ ሕግ ውጭ በሆነ አያያዝ የሰው ልጆች ልዕልና እና ክብር በሚነካ የሙርከኞችን ሕሊና በሚጎዳ መልኩ “ጠመንጃ” ደግኖ በማስፈራራርት “የእራሳቸውን እና ወላጆቻቸውን” ሰብአዊ ክብር የሚነካ “መፈክር” እንዲያስተጋቡ ወረበላው የሚያስተጋባውን መፈክር ተገድደው እየደጋገሙ እንዲያስተጋቡ በኢትዮጵያዊያን ነውር የሚባለውን ነውር ለጀሮአችን የሚቀፍ እንግዳ ነገር አይተናል።

 ይህ ድርጊት በስነ ሕሊና ምሁራን ትርጉም አለው።ድርጊቱን ስትመለከቱት ወያኔ በሚገርም ባሕሪ የበታችነት ስለሚያጠቃው “የበታችነቱን ስሜት ለመደበቅ” ሲል “ልዕልናውን እንዲአስተጋቡለት” ሙርከኞቹን እንዲጨነቁ አድርጓል።

እኔ እንደገባኝ በትምክሕት የተወጠረው የበላይነት እና የበታችነት ስሜት ሁለቱ በውስብስብነት ተጋምደው አንዱ አንዱን ለመሸፈን የሚደረገው የሕሊና አለመረጋጋት የሚታዩ የስነልቦና ክስተት ነው። ሁለቱም እርስ በርሳቸው ተመሳሳይ ናቸው። በዚህ ሙያ የሚያስተምሩ ሊቃውንት እንደሚሉት “ልዕልናን ለማሳየት መሞከር የበታችነትን ስሜት ለማካካስ የሚያገለግል “የመከላከያ ዘዴ” ነው ይላሉ።

 

የበላይነትን ለማጎናጸፍ የሚዞሩ የወያኔ የበታች ስሜት “በሽተኞች” እራሳቸው በአሸናፊነት ረድፍ በማስቀመጥ የበታችነት ስሜታቸው እየተባባሰ በሄደ ቁጥር ለበታችነታቸው ስሜት “ምክንያታችን” ነው ብለው ለሚወነጅሉት ማሕበረሰብ አጋጣሚውን አግኝተው “በቁጥጥራቸው ሥር ሲገባ” ከዛው ማሕበረሰብ በመጣ “ሙርከኛ” ላይ እራሳቸው የሚሰቃዩበትን “የበታችነታቸውን ስሜት” ይጭኑበታል። ይህንን ሲያደርጉ በበታችነት የሚሰቃዩበት የሕሊና ጭንቀታቸው እንደ መውጫ መስኮት ይጠቀሙበታልታል። በዚህ ቪዲዮ ላይ ወያኔዎች በማረኩዋቸው ወታደሮች ላይ የፈጸሙት አስነዋሪ ስነምግባር እያየነው ያለው ዓይነተኛው መነሻ ከላይ ከጠቀስኩት እውነታነት የተነሳ ነው።

ድርጊቱ እጅግ መረን የለቀቀ ነው። “እራሳቸውንና በጦርነቱ ውስጥ የሌሉትን የሙርከኞቹ ወላጆች” በዓለም አቀፍም ሆነ ሃይማኖታዊ ሕግ “injurious to dignity” የሚባለው “ክብረ ነክ” የሆነ የትግሬዎች ፋሺሰታዊ የስነ ልቦና ሲመረመር “የሞራል መበስበስ” ብቻ ሳይሆን ወንጀልም ነው። ኢትዮጵያዊያን ለታሪክ ማስረጃ ሊዘግቡት የሚገባ ቪዲዮ ነው።

ቪዲዮው ዛሬ አንድ ወዳጄ ልኮልኝ ነው ያየሁት። ቪድዮው በተመለከትኩበት ዓይን እራሴን መልሼ የምጠይቅበት አጋጣሚ ነበር። ወደ ሱዳን ስሄድ ከወያኔዎች በተለይ ከነ አባይ ጋር “ትግራይን ከጫፍ እስከ ጫፍ” እየተዘዋወርኩ ወደ 4 ወር ሰንብቼአለሁ። አያያዛቸው ከሌሎች ትግሬዎች እጅግ የሚገርም ወንድማዊ መስተናግዶና አያያዝ ነበር። ለደግነታቸው ከመሪዎቹ አብሮ አደግነት መስሎ ብገምተውም ‘እኔን ወደ ድርጅታቸው ላማስቀረት የጣሩበት ምክንያት’ ዋነኛው ነበር ብየ እገምታለሁ። ሆኖም አልተሳካላቸውም።

በወቅቱ ከላይ እስከታች ያሉትን መሪዎች የፖለቲካ ንትርክ ገጥሜ አብረውኝ የነበሩ ጓዶኞቼ “እባክህ እራስን አስገድለህ እኛንም እንዳታስረሽነን” ባታምንበትም የሚሉትን ፖለተካ እመንላቸው እስኪሉ ድረስ ስከራከራቸው ነበር።  አሁን አሁን እራሴን ስፈትሽ “እውነታዊ ተፈጥሮ” ወይንም “ጠበብ አልባ ግትረነት” ስለነበረኝ ይሆን እንዲያ ከነዚህ አረመኔዎች ጋር ፖለቲካው በግትርነት ሳልፈራቸው ስከራከራቸው የነበረው? ብየ አሁንም እራሴን እጠይቃለሁ።

ክርክራችን ከብሔር ፖለቲካ እስከ አማራና ትግሬ እስከ ምኒልክ እና ዮሐንስ እስከ የሌቦች ቅጣት ፤እስከ ዘርኣያዕቆብ ወዘተ…ወዘተ… ነበር።

 

አጋጣሚ ይህ ቪዲዮ ስመለከት በትንሽነቴ ወዳደግኩበት “ሰመማ” ወደ እሚባል ገጠር የሚወስድ “ማይ አድራሻ|” ከሚባል ሽሬ እንዳስላሴ እና ሰለኽለኻ መካክል አቋርጠን ከወያኔ ተጋዮች ጋር ስንጓዝ፤ “ስሙን የማላስታውሰው” ነገር ግን መልከመልካም እና ለግላጋ ረዢም የሆነ የታጋዮቹ ዋና መሪ ጋር እያወራን እንጓዝ ነበር። በእዛች ቦታ ስንደርስ የሆነ የራዲዮ መልእክት ጥሪ ደረሰውና መነጋገር ጀመረ። በንግግሩ ውስጥ ከዚህ ቪዲዮ ጋር ተመሳሳይ የሆነ ንግግር ከተጣራው የራዲዮ ሞገድ ላይ “ወላጆቻቸውን ማርከን ልጆቻቸውንም እየማረክን ነው!” …“ተቀበልከኝ” ለማለት ይመስለኛል የሆነ “ኮድ” ነገረው: እርሱም “አዎ! አዎ!” እንደማለት ይመስለኛል በፈገግታ እርሱም “በኮድ” መልስ ሰጠውና “ግንኙነቱን” በዛው ተቋጨ።

ስናወራው የነበረው ጥሞታል መሰለኝ ልጁ ወደ እኔ መለስ ብሎ “አካባቢያችን” ውግያ ነገር ስላለ ፤ ቃኚ እስኪያጣራልን ድረስ ትንሽ እዚህ እንቆያለን ብሎኝ ከኔ ራቅ ብሎ ሄዶ ጥቂት እንደቆየን “ጉዞአችን እንድንቀጥል ሆነ” ፤

ዛሬ ያየሁት ቪዲዮና ያደመጥኩት መፈክር ተመሳሳይነቱ ሳነጻጽረው ይህ የስነሉባና ትምክሕታዊ የበታችነት ስሜት ቀደም ብሎ በረሃ ላይ እያሉ የነበረ መሆኑን ራሴን የማስታውስበት አጋጣሚ ሆኖ ሳገኘው፤ እጅግ ገርሞኛል።

እናንተስ ምን ትላላችሁ? ተቀባበሉት “ሼር” አድርጉት፤ ሕዝቡ ይመስግበው።የስነሉባና ትምክሕታዊ የበታችነት ስሜት ቀደም ብሎ በረሃ ላይ እያሉ የነበረ መሆኑን ራሴን የማስታውስበት አጋጣሚ ሆኖ ሳገኘው፤ እጅግ ገርሞኛል።

እናንተስ ምን ትላላችሁ? ተቀባበሉትሼርአድርጉት፤ ሕዝቡ ይመስግበው።



  እናንተስ ምን ትላላችሁ? ተቀባበሉት “ሼር” አድርጉት፤ ሕዝቡ ይመስግበው።

Tigrean fascist magnanimity humiliating captives out of war rules

https://youtu.be/MeauhEGT_cs

 

ጌታቸው ረዳ

ETHIO SEMAY