Wednesday, July 6, 2022

ክፉ ህልም ስታይ የመጀመሪያ አማራጭ መፍትሔ ከእንቅልፍ መንቃት ነው!! ዳግማዊ ጉዱ ካሣ (ma74085@gmail.com) Ethiopian Semay 7/6/22

 

ክፉ ህልም ስታይ የመጀመሪያ አማራጭ መፍትሔ ከእንቅልፍ መንቃት ነው!! 

ዳግማዊ ጉዱ ካሣ

 (ma74085@gmail.com)

Ethiopian Semay

7/6/22

ሰላም ውድ አንባቢያን-

ከጽሑፍ ውስጥ እንደጥቅስ የተገኘ

…..ታሪክን እናጣቅስ፡፡ ያኔ ዱሮ በኛ የልጅነት ዘመን ሰባት ወጣቶች በረሃ ገቡ፡፡ በረሃ ገቡናም ሕዝባችን ለሚሉት “ወዲ ትግራይ! “አምሓራይ ዝባሃል “ጨቋናይ ተግራይ” ቀቲልካ ዓድኻ ትግራይ ናፃ ክትገብር ኣለካ…” አሉና ቀሰቀሱት፤ አእምሮው እስኪዝል በ“ላም አለኝ በሰማይ፣ ወተቷንም አላይ” ተረት ተረት ወዘወዙት፡፡ በዚያ ስብከት ከጎናቸው ያሰለፉት የሕዝብ ቁጥር ቀላል አልነበረም፡፡ በዚያም አጋጣሚ ትግራይና ትግሬነትን ተንተርሶ ከዚያ ዘመን በፊት ይኖራል ተብሎ ከሚገመተው በላይ ቋንቋና ዘውግን መሠረት ያደረገ የብሔር ፖለቲካ ኢትዮጵያ ውስጥ ተተከለ፡፡ ተተክሎም ዛፉ ለመለመና ይሄውና አገር ምድሩን አዳረሰ፡፡…….የአማራ መለያየትና ወደዘውገኝነት የዘቀጠ ደረጃ አለመውረድ አማራን ሲጎዳ ጠላቶቹን ግን በእጅጉ ጠቀመ፡፡ ይህ አስቀያሚ ትዕይንት አይገለበጥም ተብሎ በእርግጠኝነት መከራከር አይቻልም፡፡……..አማራ ተያይዞ ማበድን ቢለማመድ ኖሮ አንድም ጠላት አጠገቡ ድርሽ አይልም ነበር፡፡

አውላላ ሜዳ ላይ የተኛውን በሬ፤

ነካክተው ነካክተው አደረጉት ዐውሬ፡፡ የሚለው የአበው ገጠመኝ ልብ ይለዋልና!

አዎ፣ አርፎ መተኛትም ተከለከለ፡፡ አማራ “ሥልጣን አልፈልግም፣ ወንርበር አይሻኝም፣ ስትፈልጉ ቀቅላችሁ ብሉት፤ ነገር ግን በሀገሬ የትኛውም ክፍል ተዘዋውሬ በላቤና በወዜ ሠርቼ ልኑር” ብሎ ጫካ መንጥሮ፣ ገደል ቆፍሮ በልፋት ድካሙ በኖረ ይሄውና በዚህም ቀንተውበት በያለበት ቦታ እየሄዱ በየትም ሀገር ባልታዬ ጭካኔ ይጨፈጭፉታል፤ ያስጨፈጭፉታል፡፡ እነዚህ ጨፍጫፊዎች ከትግሬና ከኦሮሞ የወጡ ፀረ አማራ ኃይሎች ናቸው፡፡ እንወክለዋለን የሚሉትንም ወገን የፕሮፓጋንዳቸው ሰለባ አድርገውት ብዙው ዜጋ ፀረ አማራ ሆኗል፡፡ ፀረ አማራነት ከፌዴራል መንግሥት እስከ ክልሎች የወቅቱ ፋሽን ነው፡፡

ከአባቶቹ ወያኔዎች በተማረው መሠረት ሸመልስ አብዲሣ የኦሮሞ ልሂቃንን በደረቅ ሌሊት ሰብስቦ እንዲህ ሲል የነገራቸው ምድረ ሾርት ሜሞሪያም ሁላ ረስቶታል፡፡ “አማራንና አማርኛን ከኢትዮጵያ በማጥፋት በኦሮሞና ኦሮሚፋ እየተካን ነው፡፡ ጥቂት ታገሱን፤ ሥራችንን በሚገባ እየሠራን ነው፡፡ ቁማሩን በልተነዋል፡፡ አባይን ተሻግረን የሠራነውን እናንተም ታውቃላችሁ፡፡፡ አምስት ቋንቋዎችን የፌዴራል የሥራ ቋንቋ ያደረግነው ለብሔሮቹ አዝነን ሳይሆን ለዘዴያችን ነው፡፡ አማራን ከኦሮሚያ ብቻ ሳይሆን ከራሱ ከአማራው ክልልም ጭምር እናጠፋዋለን፡፡ ይህን ለኛ ተውት፡፡ ነፍጠኛን ሳናጠፋ እንልቅፍ የሚባል አይወስደንም፡፡…”

ተመልከት - አቢይና ሸመልስ ያቺን ንግግር ተግባራዊ ለማድረግ ከቡድናቸው ቆራጥ አባላት ጋር ላለፉት አራት ዓመታት ሌት ከቀን ለፍተዋል፤ አሁንም ከምንጊዜውም በበለጠ እየለፉ ናቸው፡፡ ሞኙ አማራውና የአማራ ዕጣ ሊደርሰው ወረፋውን በመጠባበቅ ላይ ያለው ወገን ነው፡፡ ፈጣሪ ይቅር ይበለኝና ነገረ ሥራው ጉማሬ የሚመስለኝ ሽመልስ አብዲሣ የተማረ ነው፤ እንደነገሩም ቢሆን የዘመናዊነትን ባህል እያዬ ያደገ ነው፡፡ አሁን ግን ዋና ሥራው ሲታይ ሰውን ማሳረድ ነው፡፡

ቢሮ ውስጥ ሆኖ በስልክና በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች በየቦታው አሰማርቶ በሚያዛቸው ኦነግ-ሸኔዎች አማካይነት አማሮችን ሲያሳርድ ከዋለ በኋላ እቤቱ ሄዶ ሣሎን በር ላይ የሚያገኛቸውን ሕጻናት ልጆቹን ጉንጫቸውን ሳም አድርጎ ሶፋው ላይ መጋደሙ አይቀርም፡፡ ሲያሳርዳቸው የዋለው የአማራ ሕጻናት ደም ባጨቀየው ከንፈሩ ልጆቹን መሳም ምን ያህል እርካታ እንደሚሰጠው እሱና አንድዬ ብቻ ያውቃሉ፡፡ ከዚያም ወደ መኝታ ቤቱ ሲገባ የአማራን ደምና ሥጋ ሲጠጣበትና ሲያመነዥክበት በዋለው ክርፋታም አፉ ሚስቱን መሳሙ አይቀርም፡፡ ያኔ ያቺ የፈረደባት ሚስት በዚህ በላዔሰብ አፍ ስትሳም ምን ደስታ እንደሚሰጣት አንድዬ ብቻ ነው የሚያውቀው፡፡

አቢይም ሆነ ሽመልስ ደግመው በማይኖሩባት አጭር የምድር ዕድሜ ውስጥ ለሚገኝ ሥልጣንና ሀብት ብለው የሚሠሩት ወንጀልና ኃጢኣት ሰማይና ምድር አይችሉትም፡፡ የሆነው ሆኖ ግን አማራው ለነዚህ ጭራቆች እስካሁን የሚሰጠው ምላሽ አነስተኛ ወይንም ምንም ስለነበር ያ የልብ ልብ እየሰጣቸው የፈለጉትን ሲያደርጉ ቆይተዋል፤ አሁንም በአማራና በኢትዮጵያ ላይ ያሻቸውን እያደረጉ ናቸው፡፡ በዚህ መሀል አማራው የሚያደርገው ጠፍቶት የሚወርድበትን የመከራ ዶፍ ሁሉ ዝም ብሎ ሲቀበል ነበር፡፡ አሁን አሁን ግን ትከሻው በመሳሳቱ እርሱም እንደጓደኞቹ ለማበድና ዕብደትን በዕብደት ለመመለስ ዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ ይህም የቀን ጉዳይ እንጂ ተያይዞ ማበድ እስከዚህ የሚጠቅም ከሆነ አማራም ቢያብድ አይፈረድበትምና ዘሩ ጨርሶ ከመጥፋቱ በፊት ኅልውናውን ወደማስጠበቁ የመጨረሻ እርምጃ መግባቱ አይቀሬ ነው፡፡ ያኔ ማቄን ጨርቄን አይሠራም፡፡

አማራ በይሉኝታና በባህል፣ በሃይማኖታዊ ቀኖናና በአስተዳደጋዊ የጨዋ ወግ ልማድ የተነሣ ለሚደርስበት ግፍና መከራ ሁሉ ተመጣጣኝ ምላሽ ሳይሰጥ ቆይቷል፡፡ ጠላቶቹ ከዛሬ ነገ ይሻሻላሉ ወይ ይለወጣሉ ብሎ ለዘመናት ቢጠብቃቸውም ያንገቱን ገመድ ይብስ ሲያጠብቁበት እንጂ ሲያላሉለት አልታዩም፡፡ ስለሆነም አንድን ችግር ለመፍታት አንዳንዴ ችግሩ በመጣበት መንገድ ገፍቶ መሄድም ጠቀሜታ አለውና አማራው የነሱን መንገድ ለመከተል መገደዱ የሚጠበቅ ነው (ጭካኔው ሳይሆን ተገቢው የመልስ ምት)፡፡ ያን ሲያደርግም በቅድሚያ የቤቱን እሾህና አሜከላ ማጥፋት እንደሚጠበቅበት ሳይታለም የተፈታ ነው (ዋናው ሊሰመርበት የሚገባ ትኩረት እዚህ ላይ ነው!) ፡፡

 እቤትህ ውስጥ ቀያጅና የጠላት ሎሌ ካለ ልፋትህ ሁሉ የዜሮ ብዜት ነው፡፡ ምንም ዓይነት ጥረት በዜሮ ሲባዛ ውጤቱ ያው ዜሮ ነውና፡፡ ይህንንም ቀኑ ሲደርስ የምናየው ይሆናል፡፡ ብአዲን እንዲህ አማራን እንዳስፈጀ አይቀርም፤ የርሱ ጉድጓድ ከሌሎቹም በበለጠ እጅግ ጥልቅ ነው፡፡ ክርስቶስን የሸጠው ይሁዳና አማራን የሸጠው ብአዲን መጨረሻቸው አንድ ነው፡፡

በአጭር አገላለጽ ይህን በትክክል ቢቆጠር ከ50 ሚሊዮን የማያንስ ሰፊ የአማራ ሕዝብ ከሁሉም ይበልጥ የጎዳውና እየጎዳው ያለው በእስካሁኑ ሁኔታ ተያይዞ ማበድን መጠየፉ ብቻ ነው፡፡ እንደሌሎች ነባርና አዳዲስ ተያይዞ አባጆች ራሱን ለመንጋ ማኅበረሰብኣዊ ዕብደት ቢያመቻች ኖሮ በአሁኑ ወቅት አማራ ከየትኛውም ማኅበረሰብ ባልተናነሰ ምናልባትም በበለጠ የራሱን ኅልውና ባስጠበቀ ነበር፤ ኧረ ከራሱም አልፎ የሌሎች ወገኖቹን ሕይወትም ከአቢይና ሽመልስ መሰል ሰብኣዊ ጭራቆች በታደገ ነበር፡፡ ክፉ ህልም ስታይ የመጀመሪያ አማራጭ መፍትሔ ከእንቅልፍ መንቃት ነው - አማራ ግን ያለፈው የወያኔና የአሁኑ የኦነግ/ኦህዲድ/ብአዴን የበደል ደለል እየወረደበት መንቃት አልቻለም፤ ሲነቃ የሚታየውን መዓት ደግሞ እንኳን ለወዳጅ ለጠላት አልመኝም፡፡ በኢትዮጵያ ሰማይ የተረገዘውን ጉድ ከፈጣሪ በቀር ማንም አያውቀውም፤ እንደተነገረው ከሆነ ግን ብዙ ነገር በግምባር ይጠብቀናል፡፡ ለነገሩ እነእንቶኔ እንዲህ ተጨማልቀው በነፃ ሊሰናበቱ አይችሉም፡፡

ታሪክን እናጣቅስ፡፡ ያኔ ዱሮ በኛ የልጅነት ዘመን ሰባት ወጣቶች በረሃ ገቡ፡፡ በረሃ ገቡናም ሕዝባችን ለሚሉት “ወዲ ትግራይ! “አምሓራይ ዝባሃል “ጨቋናይ ተግራይ” ቀቲልካ ዓድኻ ትግራይ ናፃ ክትገብር አሎካ…” አሉና ቀሰቀሱት፤ አእምሮው እስኪዝል በ“ላም አለኝ በሰማይ፣ ወተቷንም አላይ” ተረት ተረት ወዘወዙት፡፡ በዚያ ስብከት ከጎናቸው ያሰለፉት የሕዝብ ቁጥር ቀላል አልነበረም፡፡ በዚያም አጋጣሚ ትግራይና ትግሬነትን ተንተርሶ ከዚያ ዘመን በፊት ይኖራል ተብሎ ከሚገመተው በላይ ቋንቋና ዘውግን መሠረት ያደረገ የብሔር ፖለቲካ ኢትዮጵያ ውስጥ ተተከለ፡፡ ተተክሎም ዛፉ ለመለመና ይሄውና አገር ምድሩን አዳረሰ፡፡

ከዚያ በኋላማ ምኑን እነግርሃለሁ፡፡ ከስድስት ሚሊዮን ገደማ ሕዝብ የወጡ በመቶዎችና በጥቂት ሽዎች የሚገመቱ ወየንቲ ተጋሩ የትግራይን ሕዝብ በ“እምበር ተጋዳላይ” ያምሱት ያዙ፡፡ ዓመታት ተቆጠሩ፡፡ ቀንም ሆነ ማታም ሆነ በ17 ዓመታቸው በለስ ቀናቸውና በእውን ቀርቶ በህልም የማያገኙትን የአራት ኪሎ ቤተ መንግሥት ወረሱ፡፡ ባዶውን ተጥሎ ሜዳ ላይ የሚገኝን ነገር ውሻም ጅብም አይምሩትም መቼም፡፡  

የተያይዞ ዕብደቱ ውጤት የመንግሥትን ሥልጣን እስከመቆጣጠር አደረሰና ያኔ ሁሉም የኢትዮጵያ ሕዝብ በሚሆነው ሁሉ ፈዞና ደንግዞ ለነዚያ ወያኔዎች አለውድ በግዱ እንዲገዛ ታሪክና ፈጣሪ ፈረዱበት፡፡

የዘፈኑ ሁሉ ቅኝት “ትግራይ አደይ፤ ወዲ ትግራይ፤ ትግራይ ትስዕር፤ ሕወሓተይ ማኣረይ ሸንኮሪናይ…” ሆነና ብሔራዊ ስሜት ጠፍቶ የጎሣና የነገድ መሳሳብ የወቅቱ ፋሽን ሆነ፡፡ ያ ፋሽን ለጥቂቶች የሀብትና የሥልጣን ምንጭ ሲሆን ለብዙኃን ግን የሰቆቃና የመከራ ባሕር ሊሆን በቃ፡፡ ኢትዮጵያም የገዛ ሕዝቧ እሥር ቤት ሆና ወደምድራዊ ሲዖልነት ተለወጠች፡፡ ሲዖሉ ደግሞ የሌት እንቅልፍና የቀን ዕረፍት በማያውቁ የፖለቲካና የንግድ ትሎች የተሞላ ሆነ፡፡ ሰው ከዕውቀትና ከጥበብ ማዕድ ሲወጣ ምን እንደሚመስልም አየን፡፡ ምድረ ሥራ ፈትና ሥራ አጥ የፖለቲካውን መርከብ እየተሣፈረ ያቺን የመሰለች ውብ ሀገር ገደላት፡፡ እስክትነሳም አሳራችንን ለማየት ተገደድን፤ ግን መነሳቷ የጊዜ ጉዳይ እንጂ አይቀርም፡፡

ተያይዞ ዕብደት ማለት ፈረንጆቹ “ሶሻል ሣይኮሎጂ” ከሚሉት የወል መታወቂያ የሚቀነጨብና አንድ ማኅበረሰብ ሊጋራቸው የሚችሉ የአስተሳሰብና የአመለካከት ተመሳስሎዎችን ይመለከታል፡፡ እንደውነቱ አንድ ነገድ ወይንም ዘውግ ተለይቶ የሚታወቅባቸው የጋራ ባሕርያት አሉት - አብሮ ከመኖርም ብዙ ነገርን መለዋወጥ ይቻላልና ይህ ነገር እንግዳ አይደለም፡፡ ከነዚህ ውስጥ ቋንቋው አንዱ ሆኖ የአመጋገብና የባህልና ወግ ተዛምዶዎቹ ይጠቀሳሉ፡፡ ከዚህ ወጣ ባለ ሁኔታ ግን የሚታዩ ከእውነት ሣይሆን ከስሜት የሚፈልቁ መሳሳቦችና ትስስሮችም አሉ፡፡ እነዚያን ትስስሮች የሚፈጥሩም የማኅበረሰብ አባላት አሉ፤ ልክ እንደወያኔዎችና ኦነግ/ኦህዲዳውያን ጭፍሮቻቸው - ዞምቤው ብአዲንም ሳይዘነጋ ታዲያ፡፡

ጥቂት ሆነው ሳሉ ብዙዎችን የሚያንበረክኩ ኃይላት በየትኛውም ዘመንና በየትኛውም ሥፍራ አሉ፡፡ በጣት የሚቆጠሩ የዚያ ማኅበረሰብ አባላት በተለይ ወጣቱን በበሬ ወለደ ፕሮፓጋንዳ ሥልታቸው የሃሰት ትርክት እየፈጠሩ ሌት ተቀን ይግቱታል፤ በዘረኝነት በተቃኘ የፈጠራ ወሬ ያሰክሩታል፡፡ ጠላት ብለው የፈጠሩለትን ማኅበረሰብ ሲያሸንፍ የዓለም ቀጭን ጌታ እንደሚሆን ያሳምኑታል፡፡ ያኔ በጠላትነት የፈረጁለትን ማኅበረሰብ እንደዝምብና ትንኝም ባለመቁጠር ባገኘው ዘዴ ሁሉ ከምድረ ገጽ ለማጥፋት የማያደርገው የለም፡፡

የአማራ ሕዝብ ማኅበረሰብኣዊ ሥነ ልቦናው እንዳብዛኛው የትግራይና ኦሮሞ ሕዝብ በቡድናዊና በድርጅታዊ ስሜት የተጠለፈ አይደለም - ሁለቴ ማሰብ የባሕርይ ገንዘቡ ነው፡፡ አማራ የመንጋ አስተሳሰብን ይጠየፋል፡፡ “ና በአማራነታችን እንደራጅና ጠላታችንን እናሳፍር፤ በዚያውም ኅልውናችንን እናስጠብቅ” ብትለው ይስቅብሃል - ቢያንስ እስከቅርብ ጊዜና አሁንም ድረስ፡፡ ይህንን ጠባዩንም ጠላቶቹ አሳምረው ያውቃሉ፡፡ ስለሚያውቁም በደምብ ይጠቀሙበታል፡፡ እንጂ አማራ ተያይዞ ማበድን ቢለማመድ ኖሮ አንድም ጠላት አጠገቡ ድርሽ አይልም ነበር፡፡ አማራ ተያይዞ የማበድን ጥቅም ቢገነዘብ ኖሮ በአንድ መንደር ከ3000 በላይ ወገኖቹ በዐውሬዎች እንደቅጠል መርገፍ ይቅሩና ገና የአማራ ስም ሲነሳ የትም ቦታ የሚገኙ ጠላቶቹ እግር አውጪኛቸውን በፈረጠጡ ነበር፡፡ የአማራ መለያየትና ወደዘውገኝነት የዘቀጠ ደረጃ አለመውረድ አማራን ሲጎዳ ጠላቶቹን ግን በእጅጉ ጠቀመ፡፡ ይህ አስቀያሚ ትዕይንት አይገለበጥም ብለህ ግን አታስብ፡፡

አማራን የግድያ መለማመጃ ያደረገው፣ አማራን ያስናቀው፣ አማራን ለዚህ አሰቃቂ ዕልቂት የዳረገው የሃይማኖትና የሞራል ሰው መሆኑ ነው ብያለሁ፡፡ አማራን ለጭፍጨፋ ያጋለጠው እንደሌሎቹ ከሰውነት በታች ወርዶ የክፉ ክፉ ዐውሬ ለመሆን ሰብኣዊነቱ፣ የነቃ ኅሊናውና አስተዳደጉ ስላልፈቀዱለት ነው፡፡ አማራን ለዚህ የውርደትና የሰቆቃ ደረጃ ያበቃው “ማተቤን አልበጥስም” ማለቱ ነው፡፡ ማተቡ ደግሞ “ግራ ጉንጭህን ለሚመታህ ቀኝህን አዙርለት” የሚል ያያት የቅድመ አያቶቹ ክርስቲያናዊ አስተምህሮ ነው፡፡

አማራ በዚህ ትግስቱና ሞራላዊ አቋሙ ይቀጥላል ወይንስ አይቀጥልም የሚለው ጥያቄ ጊዜ የሚመልሰው ቢሆንም አንዳንዴ “ሮም ውስጥ ስትሆን እንደሮማውያን ሁን” የሚልም ብሂል አለና ጠባዩን መለወጡ አይቀርም፡፡ ዝንታለሙን በጥፊ እየተጠፈጠፈ የሚኖር በርግጥም ጅል ነውና ከነዘር ማንዘሩም ሊጠፋ ይችላል፡፡ ስለሆነም ቆም ብሎ የሚያስብበት ጊዜ መምጣቱ ቢዘገይም የሚጠበቅ ነው፡፡ ለአማራ ደግሞ በተለይ የሰሞኑ የወለጋ ዕልቂት ቆም ብሎ እንዲያስብ ዕድል የሰጠው ይመስላል፡፡ ምንም ያላጠፉ ሕጻናትና አሮጊቶች፣ ከአድማስ ወዲያ ማዶ አገር መኖሩን እንኳን የማያውቁና አማራነታቸውን ሣይቀር የማይረዱ፣ ስለዘርና ጎሣ ምደባ ምንም ዕውቀትና ግንዛቤ የሌላቸው በነገዳቸው ብቻ አማራ እንደሆኑ ኦነግ/ኦህዲድ የፈረጃቸው ዜጎች በዚያ መልክ ሲጨፈጨፉ ለጎጃምና ለጎንደር፣ ለወሎና ለሸዋ እንዲሁም በየታላላቅ ከተሞች ለሚኖረው ሰፊው የአማራ ሕዝብ የሚያስተላልፈው መልእክት እጅግ የከረረና የመረረም ነው፡፡

ተያይዞ ማበድን በተጋሩና ከነሱ በተማሩ በአክራሪ ኦሮሞዎች እስኪያንገሸግሸን አየነው፡፡ እንደወገናዊ ምክር ይህ ተያይዞ ዕብደት ካልቆመ ተጋቦታዊ ትልልፉ የሚያመጣው ሌላ አዙሪት መኖሩ እውነት ነውና ሁሉም ቆም ብሎ ሊያስብ ይገባል፡፡ በበኩሌ ሌላ አዙሪት እንዲመጣ አልፈልግም፡፡ በዘረኝነት ልክፍት ያበዱት ወንድሞቼና እህቶቼ እጃቸውና እግራቸው እየታሰረ ወደሚቀርባቸው ጠበል ሄደው ቢጠመቁ ደስ ይለኛል፡፡ እነሱ ጃዝ ብለው የለቀቁት ዕብድ ሀገራችንን ጨርሶ እስኪያፈራርሳት መጠበቅ የለብንም፡፡ በተለይ ሽመልስ አብዲሣና አቢይ አህመድ በቅርብ ተይዘው ወደ አእምሮ ህክምና ማዕከል ወይንም እነሱና ገዢው ፓርቲ ባያምኑበትም ወደጠበል መወሰድ ይገባቸዋል፡፡ አለበለዚያ ይህ ተያይዞ ማበድ በተሟላ ክብርና ሞገሱ ወደሌሎች ነገዶችና ዘውጎች ከተላለፈ ማጣሪያው ያጥረናል፤ የአባይንና የጋንጀስን ወንዞች የሚስተካከል የደም ጎርፍ በኢትዮጵያ ይፈሳል፡፡ በተለይ የመከራ ገፈት ዋናው ቀማሽ አማራው ወደዚህ ዕብደት ከመግባቱ በፊት ቀድመው ያበዱ ወንድም እህቶቻችንን በማከሙ ረገድ የምንችል አሁኑኑ እንድረስላቸው፡፡

ፈሪ መጥፎ ነው፡፡ የፈሪ ዱላ አያድርስ ይባላል፡፡ በሥነ ልቦና የተጎዱ ሰዎች ጥቃታቸው እጅግ ዘግናኝ ነው፡፡ እነዚህን መሰል ሰዎች የመንግሥትን ሥልጣን ሲይዙ ደግሞ የጥቃታቸው ደረጃና የቦታ ሽፋን ምን ያህል ሊሆን እንደሚችል እያየን ነው፡፡ ጥቂትነት የሚፈጥረው ትንሽነት ደግሞ ዕዳው ተከፍሎ የማያልቅ ኪሣራ ያስከትላል፡፡ ዓለማችን ፍዳዋን እያየች የምትገኘው ጠቅላላ ብዛታቸው 20 ሚሊዮን ከማይደርስ ጠርጣራና የገለልተኛነት ስሜት የሚያጠቃው ዘውግ የፈለቁ ጥቂት አሰለጦች በፈጠሩት ችግር ነው፡፡ እነዚያ ምሥጢራውያን አሰለጦች የዓለምን ሀብትና ሥልጣን በመቆጣጠር ወደ ስምንት ቢሊዮን የሚጠጋውን የዓለማችንን ሕዝብ በነሱ ፍላጎት አሽመድምዶ ለመግዛት ያቀዱት ከብዙ መቶዎች ዓመታት በፊት ነው፡፡ እነሆ ዕቅዳቸው ተሣክቶ የዐውሬውን ቁጥር በየግምባራችን ወይንም በየመዳፋችን በመሰካት ለመገበያየትና ሁላችንንም ለማሰይጠን ተቃርበዋል፡፡ በሙከራ ደረጃ ብዙ ገፍተዋል፡፡ የኞቹ ደናቁርት ዘረኞችም የነሱን ፈለግ በመከተል ብዙኃኑን የኢትዮጵያ ሕዝብ አፀፋውን በማይችሉት የበቀልና የጥላቻ ምሪት እየተነዱ አሣሩን ማብላታቸውን ተያይዘውታል፡፡ እነሱ የፈጠሩት የተያይዞ ዕብደት በሽታ ወደሌሎች በተለይም ወደአማራው ማኅበረሰብ ሲገባ ግን እነሱን አያድርገኝ፡፡ ያም ቀን በንፋሰ ፍጥነት እየመጣ ነው፡፡ ለዚያ ያብቃን አይባል ነገር፡፡ ተናግረናል!! “እንደሠራ አይገድልም”ና ምንም ያልተፈጠረ መስሏችሁ በየከተሞች የምትፈነጥዙና የምትምነሸነሹ ወገኖች ዙሪያ ገባችሁን ቃኙ፤ አዲስ አበባ ላይ ሕይወት ያለች ብትመስልም ከአዲስ አበባ ውጪ ግን ጨለማው እየበረታ ነውና በምናባችሁም ቢሆን ወጣ ብላችሁ አገራችሁን ጎብኙ፡፡ ሁሌ ቸበር ቻቻ የለም፤ ሁሌ ሣቅና ሆታ የለም፤ አቢይ እያንዳንድህ የሲዖል ጓደኛው ሳያደርግህ አይለቅህምና ወገኔ ሆይ ብዙም ሳይረፍድብህ አሁኑኑ ንቃ!!

  ዳግማዊ ጉዱ ካሣ

Ethiopian Semay