Thursday, October 27, 2022

የመስከረምና የልደቱ ውይይት የሞገስ አብሻቂ ጣልቃ ገብነት ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay) 10/27/22


የመስከረምና የልደቱ ውይይት የሞገስ አብሻቂ ጣልቃ ገብነት

ጌታቸው ረዳ

(Ethiopian Semay)

10/27/22

በልደቱ ላይ እንደምታውቁት ብዙም ትችት አላበዛም ነበር። የተቸሁት ጊዜ ከብዙ አማታት በፊት ወያኔ የደርግ ባለሥልጣናትን ስያስር እኩል ፍትሕ ለመስጠት ኢህአፓንም ማሰር ነበረበት ሲል በመናገሩ፤ ወቅሼዋለሁ። ለመውቀሴ መነሻ ለምን ኢሕአፓ አይታሰርም አለ በሚል ሳይሆን፤ ወያኔ ታሰሪ መሆን የነበረበት እንጂ ፍትሓዊ የሆነ ፍትሕ አስፋኝ አድርጎ በማየቱ እጅግ ተገርሜ ተችቼዋለሁ። ወያኔ ደርግ ብሎ ያለ ሃጥያታቸው አስሮ ብዙ አመት ካሰቃያቸው በኋ ላ በነፃ የለቀቃቸው ስላሉ ፍትሕ የተመረኮዘ አልነበረምና ልደቱን ወያኔን አሳሪና ፍትሕ አንጋሽ አስመሰሎ በማቅረቡ ወያኔነት ነው ብየ ተችቼዋለሁ። 

በተረፈ በድጋፍም እንዲሁ እንግሊዝ አገር ለስብሳባ ሄዶ ተቃዋሚዎቹ አላናገር ብለው ሲንጫጩበት ክፉኛ ወቅሼአቸዋለሁ ። ምክንያቱም ልደቱ “ሃሳብ ካላችሁ በሃሳብ እንወያይ እና አናግሩኝ እያለ በጨዋ መልክ ሲለምናቸው ጨርቃቸው ጥለው አብደው አላናገር ስላሉት የመናገር እና መልስ የመስጠት መብቱን መጣስ የራሳቸው ድንቁርና ማንጸባረቃቸው አልወደድኩተምና ልደቱን ደግፌ ተችቼአቸዋለሁ።

በሌላ ትችቴም ልደቱ እንግሊዝ አገር ለትምህርት ይሁን ለፖለቲካ “ኦሬንተሽን/ኮርስ (?)” ተጋብዞ ሄዶ እያለ፤ ድንገት መለስ ዜናዊ በሞት ሲለይ፤ ልደቱ ኩፉኛ አዝኖ ባደረገው የቃለ መጠይቅ ይሁን ያስተላለፈው የሃዘን መግለጫ  ልክ ያሬድ ጥበቡ እንዳለው አይነት “ኢትዮጵያ/አገሪቷ ታላቅ ሰው አጣች” ሲል ሰምቼው ክፉኛ ተችቼዋለሁ። ኢትዮጵያን ለዘላለሙ የባሕር በር ያሳጣት፤ በዚህ ምክንያት በእስላማዊ አገር ጎረቤቶች ቢሊዮኖች ብር እየከፈለች “ወደብ ክራይ  ልመና” በጠላቶችዋ እጅ እንድትወድቅ ያደረገ ሰውና “የባንቱስታ’ አፓርታይድ አስተዳደር የመሰረተልን አደገኛ “የሙሶሎኒ ተግባር አስፈጻሚው ትንሹ ሰው መለስ ዜናዊ” እንደ ታላቅ ሰው ፈርጆ ለሕዝብ ማስተማሩ ክፉኛ ተችቼዋለሁ።

በቅርቡም እሱን በመደገፍ ደግሞ በዘመነ ኦሮሙማው መሪ በአብይ አሕመድ በግፍ ሲታሰር እዚህ ፌስቡክ እና በድረገጼ ላይ፤

<< በኢሳያስ አፈወርቂ  ትዕዛዝ በኢትዮጵያ ውስጥ የኤርትራ የውጭ ጉዳይ ተወካይ በሆነው በአብይ አሕመድ ዓሊ ተባባሪነት ኢትዮጵያዊ ትንታጉን ልደቱ አያሌውን አስሮ እያሰቃየው ነው! ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay) Saturday, July 25, 2020>>

በሚል ርዕስ መታሰሩን ተቃውሜአለሁ።

ይህ ካልኩኝ ዘንድ በቅርቡ ስለ ትግራይ አስመልክቶ እየሰጠው ያለው ትንታኔ አልወደድከለትም። ትናንት የመስከረም እና የልደቱን ውይይት አደምጥኩ። ልደቱ የሰጣቸው ክርክሮች ከተቻለ ሌላ ቀን እመለሳለሁ። በዛው ላይ ጊዜ አልፈጅም። ምክንያቱም መስከረም በሚያስደንቅ በቂ መልስ ሰለሰጠችበት። ልደቱ ያልጠበቀው ትንታግ ተከራካሪ ስለገጠመው “ፍራስትሬትድ መሆኑን” በቁጣውና በገጽታው ያስታወቅበታል።

የመስከረም አበራ እና የልደቱ አያሌው ክርክር የተካሄደበት የውይይታቸው ቦታ “የሃሳብ ገበታ” በሚባል (Buffet of ideas) የሕግ ምሁር በሆነው የኢሳቱ ሞገስ ዘውዱ ተሾመ ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ነው።

አንድ ቀን ሲያመች ይህንን አስመልክቶ ስለ ልደቱ የምመለስበት ብሆንም፤ እጅግ የገረመኝ የልደቱ አብሻቂ ንግግሩን እና የመስከረም አበራ መልስ አንዲት ነጥብ ላስታውሳችሁ እና ወደ ሞገስ እገባለሁ።

ልደቱ ስለ ኤርትራ ተዋጊ ሃይሎች ወደ ትግራይ ስለመግባት ካነሳቸው ነጥቦች አንዱ እንዲህ  ይላል።

“ከውዝ የለውም” “ንብረት ለመዝረፍ የትግራይ ሴቶችን ለመድፈር ብሎ ነው የገባው” ሲል ይከራከራትና መስከረም ደግሞ “ሻዕቢያ ወደ ጦርነቱ የገባው “የራሱ ስጋት/ከውዝ/ ስለነበረው እንጂ የትግራይን ሕዝብ እጎዳለሁ የትግራይ ሴት እደፍራለሁ ብሎ ከመነሻው እንደ አላማ አልመጣም ብየ እገምታለሁ።” ስትል በማከልም፤ “አለመታደል ሆኖ ስለ ሴቶች መደፈር ደግሞ በጦርነት ላይ የሚከሰት ክስተት ነው” ብላ በማለትዋም  ልደቱ ደግሞ “የትግራይ ሴቶች የተደፈሩት የትግራይን ሕዝብ ላለመጉዳት ስለተፈለገ ነው?” እያለ “የጀነሳይድ ደጋፊ እንደሆነችና የሴቶችን መደፈር ግድ አንደማይላት ለማሳየት አጉል ሲባትል “እንድትሸማቀቅ” ሲዳክር  መስማቴ ገርሞኛል።

ወደ መጎስ ከመሄዴ በፊት ላንባቢዎች ይህንን ላጥራላችሁ።

ጦርነት ሲካሄድ እንደ ናዚ እና እንደ ወያኔ መሪዎች ዓላማ ተይዞ በጽሑፍ በሰነድ የተደገፈ የዘር ማጥፋት ውግያ ሲካሄድ “ሆን ተብሎ ነው” የሚል ክርክር ማካሄድ ይቻላል። ወያኔ በአማራ ላይ ያደረሰው የሴቶችና የንብረት ዝርፊያ በሰነድ አስደግፎ አገሪቷን አፈርሳለሁ ብሎ አማራን ሰላም እነሳዋለሁ ብሎ በተደጋጋሚ የቆዩ ያልተሰረዙ ዛሬም ህያው የሆኑ ሰነዶቹ ይመሰክራሉ።

በቅርቡም "የአማራ አገር እና ስሪት" የሚላትን "ኢትዮጵያ" በከርሰ መቃብር

 ላይ ብርሃን የሞላባት ያደገች ሃገረ ትግራይ እመሰርታለሁ ብሎ  በመስከረም 30 በ2013 ዓ.ም ወያኔ ከመቀሌ ጽ/ቤቱ የዘረጋው ባለ 86 ገጽ ሰነድ ባለፈው ሰሞን የለጠፍኩላችሁን የጦርነት ሰነድና አላማው አንብቡት። 

በተጨማሪም ተዋጊዎቹ በመመሪያ የተሰጣቸው የድርጅታቸው አማራን እያሳደድክ አጥፋው የሚለውን ይፋ የሆነው በለጠፍኩት “እባቦቹ የሚተፉት ምራቅ! ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay) 10/13/22 የሚለውን አስታውሱ።

እንዲህ ይላል፤

ትግርኛው ግጥም

 <<“ጎበዝ ተዓወት ተጋዳለይ ትግራይ

 አርኪብካ በሎ ነዚ ዓሻ አምሓራይ “>>

አማርኛው ትርጉም፡

<<ጎበዙ የትግራይ ታጋይ ሆይ

ድሉ ያንተው ይሁን እያንበረርክ በለው ያንን ሞኝ አማሃራ (ይ)>>

የሚለው ተዋጊዎቹ እየጨፈሩ የሚያሳየው ቪዲዮና እንዲሁም ፤

<<አማራውን “በእናታችሁ በቃኝ” አሰኘነው! ይላል የትግሬው ሩዋንዳ ሁታዊው  ኢንተርሃሙዌው የሙዚቃ ቡድን! ጌታቸው ረዳ ( Ethiopian Semay) 9/19/22 >>

የሚለውን የለጠፍኩትን በዚህ በጦርነቱ መሃል እየጨፈሩ በፖሊሲ ደረጃ አማራን ለማጥፋትና ለመጉዳት እንደተነሱ በርዕሱ የጠቀስኳቸውን ቪዲዮ የሁለት ሳምንት ማስረጃዎችን መልሳችሁ ጎብኝዋቸው።

የወያኔ ሙርከኞች የሚናገሩት ዘራፊዎች፤ሴት ደፋሪዎች፤ ቤት አቃጣዮች፤ ረሻኞች በየምድብ በመሪዎች ትዕዛዝ እንደተመደቡ ተናግረዋል። አንዱ ደፋሪም እኔ አንዱ ደፋሪ ነበርኩ ሲል ኑዛዜውን ይናገራል። ባይናገሩም ቪዲዮዎቻቸውን ማየት ነው።

ከዚህ አያይዤ ብዙ ሰዎች ልደቱ አያሌውን ጨምሮ ስለ ተረሸኑት የትግራይ ወጣቶች እያለ የሚከራከረው ክርክር (“በእርግጠኛነት እንደተደረገ ያምንና ፤ እንደገና በገለልተኛ እስኪጣራ እያለ ጥርጣሬ እንዳለው ደግሞ ያማላክታል) እንመልከት።

የልደቱ እና የቴድሮስ ጸጋዬ ክርክር ኢሳያስ ወደ ትግራይ የገባው “ፖለቲካዊ አጠባ ለማካሄድ ወደ ትግራይ እዘምታለሁ” ባለው መሰረት ነው የገባው ሲሉ ያልተባለውን ትርጉም ተርጉመው እንደተከራከሩበት ባለፈው ለቴድሮስ ጸጋዬ (ርዕዮት) በሰጠሁት ትችት የኢሳያስ ትክከለኛ ቅጂ ትርጉም የለጠፍኩትን ሰነድ በዚህ ፌስቡክ ፈልጋችሁ ተመለክቱ (በቅርብ ነው የተለጠፍኩት) እንዲህ ይላል  << ቴድሮስ ፀጋዬ መስከረም አበራን ለመሞገት የኢሳያስ አፈወርቂን የትግርኛ ንግግር ለምን ማጣመም አስፈለገው?

ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay) 10/9/2022። የሚል አንብቡት

ልደቱ ትግርኛ አያውቅም፤ ቴድሮስ ጸጋየም እንዲሁ ይናገራል እንጂ ጥልቅ የትግረኛ ትርጉም አቅም የለውም። በስማ በለው የሰሙትን ተርጉመው ሲከራከሩ መስማት ልደቱ ምን ያህል እንደታጠበ አመላካች ነው። ያንን ልተውና፡

ለምሳሌ ወያኔ የኢትዮጵያ ወታደሮች ትግራይ ውስጥ ገብተው “ማህበረ ዴጎይ” (የአክሱም ገጠር ወረዳ) ውስጥ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ወጣቶች እየተረሸኑ ወደ ገደል ሲጣሉ በቪዲዮ ሲያሳይ፤ ግድያወን የፈጸሙ ወታደሮች የተባሉት በወያኔ እጅ ሲወድቁ ከመቀሌ  እስር ቤት ያደረጉት ቃለ መጠይቅ እዚህ ፌስቡኬ ላይ ለጥፌዋለሁ <<፡አክሱም ማሕበረ ዴጎይ የተፈጸመውምንድነው? ጌታቸው ረዳ Ethiopian Semay 9/30/2022>>፡የሚለውን እሱንም በዚህ ፌስቡክ ላይ ደግማችሁ ተመልከቱት 

ወታደሮቹ ሲረሽኑ ከመንግሥት የተሰጣቸው ትእዛዝ ሳይሆን ይልቁኑ አንድ ሰው እንዳታንገላቱ እንዳትረሽኑ” ተብለው ከመአከላዊ መንግሥት ጦር ማዘዣ ስምሪት ለያንዳንዱ ሰራዊት የተላላፈውን የደብዳቤ መልእክት ወደ ጎን በመተው የበታች አዛዦች ያደረጉት ወንጀል እንደሆነ እራሳቸው ወያኔዎች ባስተላለፉት የቃለ መጠይቅ የቪዲዮ ያሳያል።

አምሳለቃ (ሳርጀንት) ኢብሳ ተረፋ ይባላል፡ በመግደል የተሳተፈና አዛዥና ታዛዥም የነበረ ነው። እንዲህ ይላል፡_

<< ንፁሃን ዜጎችን እንዳትገድሉ። ሰላማዊ ንጹህ ዜጎችን መግደል የለባችሁም፡ እንዳትገድሉ” የሚል መመሪያ ከበላይ በራሪ በደብዳቤዎች በየክፍለ ጦሩ ተላልፏል። ሆኖም በቅርብ አዛዦቻችን ምክንያት ተግባራዊ አልሆነም። እኔ ሦስት ሰዎች እንዲገደሉ አዝዣለሁ፤ እኔ እራሴም ሁለት ሰዎች ገድያለሁ።”

 በማለት ሰው በመግደልና ቤቶችን በማቃጠል የተሳተፉት እነዚህ ወታደሮች ከላይ የተላለፈውን የደብዳቤ ትዕዛዝና መመሪያ በመጣስ በሕዝብ ላይ ወንጀል ፈጽመዋል። ስለዚህ በፍርድ ስንመለከተው በመንግሥት የተላለፈ ትዕዛዝ ሳይሆን ከታች ያሉት ወንጀል ሰሪዎች ሃላፊነትን ይወስዳሉ።

ስለዚህ መስከረም የተከራከረቺበት መንገድ “አንድ አገር ወደ ጦርነት ሲገባ ኮውዝ (ስጋት) ይዞ እንጂ በመመሪያ ሴቶችን ልደፍር ነው ብሎ አይገባም” “ሴቶች ሲደፈሩ ደግሞ አለመታደል ሆኖ ጦርነት ውስጥ የሚከሰት የጦርነት አንዱ ባህሪ ነው” የምትለው የጦርነት ምንነት ከገባው ተመራማሪ ሰው የሚነገር ትክክለኛ ክርክር ነው። ልደቱ ግን “በመስከረም ላይ ጠባሳ ለመጣል ጎል ሊያስቆጥርና  በመጥፎ እንድትታይ መሞከሩ ብልህ ብየ ስቆጥረው ከነበረ ፖለቲከኛ ወደ ታች ወርዶ ሳየው ያልጠበቅኩት ነበር።

አሁን ወደ ሞገስ ልግባ።

አወያዩ ወደ ኋላ ተሻለው እንጂ መጀመሪያ አካባቢ በመስከረም አበራ ላይ ያሳየው ጣልቃ ገብነት/አደናቃፊነት/ ጭራሽ ነበር ያበሳጨኝ። ስለዚህም በማግስቱ ትችት ለመጻፍ ፈለግኩና እስኪ ለዛሬ ልልፈው ብየ ተውኩት። ግን ደግሜ ሳደምጠው በዚህ ቪዲዮ የምትመለከቱት አጭር የመስከረም አበራ “ደጋግማ የምሬት ብስጭት” ያሳየቺው የሁለቱ ልደቱና የሞገስ አላናግር ብለዋት ሊረባረቡባት ሲሞክሩ “የምታሰማው ቅሬታ” ሳደምጥ አላስችል አለኝና በሁለቱም ላይ “ብልጭ የሚል የንዴት ስሜት ተሰማኝ። እነሆ ቀርብኩ።

በኦነግና በወያኔ የተደረገው የስምምነት ውል አማራን ለመጨፍጨፍ እንደሆነ እየታወቀ የሕግ አዋቂውና ተንታኝ አቶ ሞገስ ጣልቃ ገብቶ፤ ሃሳብዋን ሲያደናቅፍ መልሶ በሌላው ወቅት “ፋክችዋል ኤረር” በሚል ሰበብ  ሃሳቦችዋን ሁሉ እንዲሰናከል አድርጓል። መስከረም ደግሞ “አረ እባካችሁ ይህ አሁን ፋክችዋል ኤረር ነው? እሺ በናንተው መንገድ ለመሄድ “እሺ” ፋክችዋል ኤረር ነው ልበልና “እሺ” ካልኩ በኋላ ለምን አታቆሙም/ ስትል ማን ትዝ አለቺኝ “አስቴር በዳኔ” ። ኑ ገበያ በተባለው ሰለሞን ሹምየ በሚያወያው መድረክ ላይ አንድ ሴት አስቴር ብቻ ነበረችና እማሃል ወንዶች ሆና  "ብሄርሽ ምንድነው?" የሚል ጥያቄ ሲያቀርቡላት እስዋም ጥያቄውን ለማብራራት ስትሞክር ከግራም ከቀኝም እያዋከቡ አላናግር ሲልዋት “እንዴ እናንተ ወንዶች ስትባሉ ሴትን አላናግር የሚለው አመላችሁ ምነው አታቆሙም አናግሩኝ እንጂ..?” እያለች ምርር ብላ ስትናገር ዛሬ ደግሞ የመሲ ምሬት አስቴር በዳኔን አስታወሰኝ።

አወያይው ማድረግ የነበረበት፤ ጠያቂዎች ለመጠየቅ በሰሌዳው ላይ ከሚጽፍዋቸው ጥያቄች መርጦ አጭር የድምጽ ጥያቄ አቅርቡ ብሎ ዕድል ከመስጠት ይልቅ  ሞገስ ጣልቃ እየገባ ለማደናቀፉ የሰጠው ምክንያት ደግሞ ሰዎች ሲናገሩ ያልሰማነው << ሰዎች የጠየቁት ነው>> እያለ ማምለጫ መፈለጉ አትኩራ ሃሳብዋን እንዳትሰጥ ማደናቀፍ አልነበረበትም (የጠያቂዎች መሆኑን በምን እናረጋግጥ?)።  “ኦነግና የወያኔ የስምመንት ውል” አማራን ለማጥፋት እንደሆነ እየታወቀ ነገር ግን “ወጣት ሞገስ በጸጉር ስንጠቃ ሊሞግታት” መሞከሩ አልወደድኩትም።

መስከረም “እሺ” ስላችሁ ለምን አታናግሩኝም እያለች ሁለቱንም ስትማጸናቸው በሚገርም ሁኔታ እንደገና አዋያዩ አቶ ሞጎስ ዘውዱ  ተመልሶ ይመጣና፤ ስለ ኦነግ ሰራዊትና ስለ ወያኔ ስምምነት ጥልቅ ትንታኔ ለመስጠት ስትሄድ ጣልቃ ገብቶ የሕግ ባለሞያነት ነገር ሆኖበት መሰለኝ፤ ስለ ኦነግና ወያኔ ሰምምነት “ጸጉር ስንጠቃ” ገብቶ ሲያደናግራት ይደመጣል።

<< እኔም ጣልቃ ልግባና..” ሲል መስከረም ድግሞ “ሁለታችሁም ጣልቃ እየገባችሁ እየረበሻሁኝ ነው” እያለች ምሬትዋን ስትገልጽ “መጎስ ወደ መጨረሻ አካባቢ ከሕዝብ የሚቀርቡ ጥያቄዎችን አቀርባለሁ ያለውን ረስቶ  የራሱን ሕግ በመጣስ እመሃል ንግግረዋ ላይ እንዲህ ይላል፤-

“የእኔ ሃሳብ እኮ መስኪ! ፤ መስኪ! የሕዝብ ጥያቄ ነው እየጠየቅኩሽ ያለሁት ፤የሕዝብ ጥያቄ ነው እያቀረብኩ ያለሁት፤ “ኢምፓክቱ……እያለ” ትንተና ውስጥ በመግባት ወደ መጨረሻ የሕዝብ ጥያቄዎችን አቀርባለሁ ያለውን ንግግሩን ዘንግቶ (ባለመዋቅ ነው እላለሁ) ሲያበሳጫት የልደቱን እንዳይበቃት የመጎስ አደናጋሪነት ተጨምሮበት “ጉንፋን በያዛት የሰውነት ድካም” ላይ ሲጨመርበት ለመቋቋም ያሳየቺው ጥንካሬዋን አደነቅኩ።

ፅሑፉን ሌላውን ለማሳወቅ መቀባበል “ሼር” ማድረግ ትችላላችሁ

ጨርሻለሁ

አመሰግናለሁ

ጌታቸው ረዳ  Ethiopian semay