Tuesday, December 24, 2019

የኢትዮጵያ ታሪክ ወይስ የኦሮሞ ተረት? ሰመረዲን ሰይፈ (POSTED AT ETHIO SEMAY)


ኢትዮጵያ ታሪክ ወይስ የኦሮሞ ተረት?
ሰመረዲን ሰይፈ (POSTED AT ETHIO SEMAY)

ፋሺሰቱና ኦነግ ኩሊው አበይ አሕመድ በኦሮሞ ተረኛነቱ እያተራመሳት ያለቺውን አገራችን በታሪካችን ላይ ከወያኔና ኦነግ የተማረውን ታሪክ የማጠልሸትን ሴራ የኢትዮጵያ ታሪክ ለማበላሸት በዩኒቨርሲቲ ውስጥ  ምን እየተደረገ እንዳለ ይህንን አንብቡ። ይባስ ብሎ ብአዴን/አዴፓ/ብልፅግና (የፀረ አማራ ካምፕ) በዚህ የታሪክ ማጠልሸት ሴራ እንዴት እየተባበረ እንዳለ በዚህ ሰነድ ታገኙታላችሁ። መቃወም ቀርቶ ታባበሪነቱን ታያላችሁ። ዘገባ ሰመረዲን ሰይፈ፡ (posted Ethio Semay)
መልካም ንባብ፦

የኢትዮጵያ ታሪክ ወይስ የኦሮሞ ተረት?
ሰመረዲን ሰይፈ
..
ተረኞቹ የራሳቸውን የተረት ተረት ጫዎታ "አዲሱ የታሪክ ሰነድ " በሚል የኢትዮጵያ ታሪክ በዩኒቨርሲቲ ውስጥ እንደ "ኮመን ኮርስ" ለሁሉም ተማሪ ይሰጥ ተብሎ ሰነድ አዘጋጅተው እንደነበር ሁሉም ሰው ሲቀባበለው ነበር።
..
ብአዴን/አዴፓ የሚባለውም የአቅመቢሶች ጥርቅም ለስሙ ትምህርት ሚኒስተሩን የሚመራው ራሱ ነው። ነገር ግን አሁንም አማራውን የእነ ተስፋዬ ገብረ አብ የፈጠራ ትርክት ወደ ትምህርት ሲቀየር እና ለትውልዱ የፈጠራ ታሪክ እንደ እውነተኛ ታሪክ ተስሎ ሲዘጋጅ አብሮ ሲያዘጋጅ ነበር። ብአዴን/አዴፓ/ብልፅግና የፀረ አማራ ካምፕ መሆኑን ዛሬም አስመስክሯል፣
...
ልብ በሉ ለኮርሱ ማስተማርያ ሰነድ የሚያዘጋጁ ምሁራን ተብለው የተመረጡት የአንድ አካባቢ የሆኑ ብሄርተኞች እንጅ የታሪክ ዘርፍ ተመራርማሪዎችና ታዋቂ ሰዎች አልነበሩም። ከታች እንደምትመለከቱት 3 PhD ያላቸው የኦሮሞ ብሄርተኞች እና 1 ጀማሪ የደብረ ታቦር ዩንቨርስቲ የማስተርስ መምህር ናቸው።
..
እውነት የኢትዮጵያን የእውነት ታሪክ ለትውልድ ማሳወቅ እና ማስተማር ከተፈለገ የኢትዮጵያን ታሪክ በውል የተረዱ እና ለብዙ አመት የተመራመሩበት ምሁራን የሉምን፣ በታሪክ ከፍተኛ ዕውቀትና ምርምር ያላቸው ፕሮፌሰሮች የሉንም (እንደ ባህሩ ዘውዴ፣ ኃይሌ ላሬቦ፣ ወዘተ)...
ለምን ስማቸውን በውጤታማ የታሪክ ምርምር ስራ ሰምተናቸው የማናውቃቸው የሰፈር ሰዎች ተመረጡ? ለምን ከአንድ ሰፈር ተመራርጦ መምጣት አስፈለገ!?
ከአማራ ምሁራንስ የታሪክ ተመራርማሪዎች እና ፕሮፌሰሮች የሉምን፣...!?

እንግዲህ ታሪክ ማዛባት ከአባታቸው ከህወሓት የተማሩት ትክቁ እውቀታቸው መሆኑ ነው።
........

ከዚህ ቀጥሎ የተፃፈው ትዝብት ሰነዱን ከአነበበ ሰው ነው፤

የስራቸው አለማማር እና ከጅምሩ የከሸፈ የታሪክ ማዛባት እና ሴራ መሆኑ የሚገለጥልን ይህን ሰነድ ገልጠን ስነበው ነው። ሰነዱ አጠቃላይ ኢትዮጵያን የሚያዋርድ ኦሮሞን በሀሰት ትርክት ሰማይ የሚሰቅል ሆኖ ይገኛል ነው።
...
==>እንደ አክሱም፣ ዛግዌ፣ ዳማትና የሰሎሞናዊ ስርወ መንግስታትን "ፖሊቲስ" በሚል ርዕስ ስር አስፍሮ ተራ የጎሳ አደረጃጀት አስመስሏቸዋል። ራሳቸውን ችለው በምዕራፍ መቀመጥ ሲገባቸው አንድ ገፅ ተኩል እየሰጠ ያልፋል።
=>ለአክሱም ሁለት ገፅ ያልሞላ ሽፋን የማይሰጠው ሠነድ ለገዳ ግን ዘጠኝ ገፆችን ይሸልማል፣የኦሮሞ ገዳ ስርዓት 9 ዓመቱ ነው ሲል ማስረጃ የለሽ ተረቱን ይዘበዝባል።
=>እነ ቢዛሞን እና እነርያን ኦሮሞ እንዳጠፋቸው እያወቀ ክርስትያን ኪንግደም አወደማቸው ይላል።

=>እንደ ኽምራ ያሉ ህዝቦችን ታምታንጋ የሚል የፈጠራ ስም ይሰጣል። ባጭሩ የኦሮሞን ተረት በኢትዮጵያ ላይ ለመጫን ያደረገውን ጥረት በሚከተለው ቁጥር መግለፅ ይቻላል፦
በሠነዱ የተጠቀሱ ስሞች ብዛት፦
-->ኦሮሞ 122 ጊዜ ተጠቅሷል
-->ሶማሊ 56 " "
-->ትግራይ 33 " "
-->ሲዳማ 20 " "
-->አማራ 16 " "
አማራ እና የአማራ ምሁራን በፍፁም ይህን መቀበል የለባቸውም፣እውነት ይህንን ታረኬ(የኢትዮጵያ) ብሎ የሚያስተምሩ ምሁራኑ ባርነት ቢመርጡ እንኳ ተማሪ በጭራሽ ሊቀበለው አይገባም።
....
የአማራ ዩኒቨርሲቲዎች ፎረም በዚህ ጉዳይ ስብሰባ ጠርቷል። ውሳኔው ይህን ሰነድ ውድቅ የሚያደርግ እንደሚሆን እንጠብቃለን። ካልሆነ ህዝባዊ ትግል ይጠራል፣ወይ ሰነዱ ይስተካከል፤ አልያ ይቀራል። አፄ ቴዎድሮስ ራሳቸውን ማጥፋታቸው እንኳ የማይቀበል ሰነድ አንድም አማራ ታሪኬ ብሎ አይቀበልም። ጭራሽ የምንሊክ፣ የዮሀንስና የቴድሮስ ምስል እንኳ እንዲታይ አይፈቅዱም፣ ድሬ ሸክ ሁሴን ብለው የባሌውን ቅርስ ፎቶ ለጥፈው የትግራዩን አልነጃሽና ፋሲል ግንብ አልያ ላሊበላን ማሳየት አይሹም።