Sunday, July 28, 2024

ከኤርትራዊው ብሔረተኛ “መነሻችን አማራ መዳረሻችን አማራ” ጋር የወገነው ትልቁ ሰው አቻምየለህ ታምሩ ሊጥ ሆኖ ተገኘ ከጌታቸው ረዳ አዘጋጅ Ethiopian Semay 7/28/24

 

ርትራዊው ረተኛ መነሻን አማራ መዳረሻችን አማራ ጋር የወገነው ትልቁ ሰው አቻምየለህ ታምሩ ሊጥ ሆኖ ተገኘ

ከጌታቸው ረዳ

አዘጋጅ Ethiopian Semay

7/28/24

አቻምየለህን ያክል አዋቂና በሳላ የትግል ወንድ በሕልም በውም በተቃራኒው ቆ እተቸዋለሁ ብየ አስ አላውቅም፡፡ ወዳጅነታችን እስከመደዋወል የደረሰ ነበር፡፡ ባንድ ወቅት (አመት ይሆነዋል)  ምክንያቱ ባላወቅኩት ነገር ስልክ ብደውል፤ ኢመይል ባደርግ ፤ ስ ቡኩ ላይም መሰንጀር ባደርግ፤ ዘጋኝ፡፡ እሱን የሚያወቁት ጋር ደውየ ሰለ ደህንነቱ ለማረጋገጥ ባነጋገራቸውም “እሱ ለበዙ ሰው እንዲያ ነው፤ ትንሽ የመለዋወጥ ትዕቢት ያጠቃዋል፡ ወዘተ... ይሉኛል፡፡  እንዲያም ሆኖ እስክንድርን “ያለቦታው ነው የገባው እዚህ ውጭ አገር መጠቶ ገንዘብ እያሰባሰብ ትግሉን ቢረዳ ይሻላል” ሲል “ቅር አለኝና ምክንያት ይኖሮው ይሆናል ብየ ብዘገይም ቆይቸ አጭር ትችት ጻፍኩበት፡ ለና እንዳልሆነም ተሰማኝ” ከዚያም ድምጹን አጠፋና የእስክንድርን ስም ለመፍጨትና ማስረጃ ሳያቀርብ ለመወንጀል ብቅ ብሎ ወደ መድረክ መጣ፡፡

ርቀውን ከነበሩበት እንን ብቅ አሉ አቶ አቻምየለህ እላለሁ!!

ኦነጋዊው ያዲሰ አበባ ፖሊስ የለበሰውን ኢትዮጵያዊ ሰንደቅ ከገላው ሲገፈውና ማተቡን ሲበጥስበት በዱላ እየነተረ ሲያራሩጠው ቆመህ ታገለው እያለ ፤ ጫት ቃሚውን ሽቅርቅሩና ልፍሰፍሱ ያዲሰ አበባ የአማራ ወጣት ከምርቃናው ነቅቶ ጠላቱን እንዲጋፈጥ በተግባር ያሳያቸው፡ የአማራ ዘር ጭፍጨፋ ኒውዮርክ ፤ ዋሺንግቶን ድረስና አውሮጳ ድረሰ ተገኝቶ ለዓለም ተወካዮች ያስረዳ ታላቁ እስክንድርን ባማቃለል (ከ disparage አልፎ በመወንጀል) “መነሻም መዳረሻውም አማራነት” ለሚለው ኤርትራዊው ዘመነ ካሴን የወገነው አቻምየለህ ታመሩ በድረገጹ የለጠፈው ትችት አንብባችሁ ይሆናል ብየ እገምታለሁ፡፡

“Nationalism is infantile disease. It is the measles of mankind” (Scientist Albert Einstein)  “ብሔርተኝነት የጩጬነት ሕሊና በሽታ ነው። ባጨሩ “የሰው ልጅ የኩፍኝ በሽታ ነው” ይላል ሳይንቲስቱ አልበርት አንስታይን፡፡ አቻምየለህ ባልጠበቅኩት መንገድ “መነሻችን አማራ መዳረሻችን አማራ” ከሚለው ጠባብ “አምሐራይ”ሔረተኛው ባሕርዳር የተወለድኩ ኤርትራዊ ነኝ ከሚል ፓስፖርት የያዘ ዘመነ ካሴ ጋር በመወገን እስክንድርን ወንጅሎታል፤ ስሙንም በጥቁር ጥላሸት ቀብቶታል፡፡ እነ ዘመነን ጦም አደር ፤ እስክንድር ቅቤና ማር ተመጋቢ ዳገት ቁልቁል የማይወርድ የማይወጣ የጫካ ሚሊዮነር አድርጎ በመይገብ ላሸት ሲቀባው ማየት አስገርሞኛል፡፡

እስክንድርን አላግባብ በቃላት ሲፈጨው፤ ማርሸት የተባለው ጸረ ዲሞከራሲ አጉራዘለልና አለቃው ዘመነ ካሴም ሆነ ጡጦ እንደሚጠባ ህጻን ከዘመነ ጉያ የማይጠፋ  እግሩ ሥር ሆኖ ‘ኩት ኩት’ የሚለው አስረስ ማረ የተባለው ጠበቃ  “ቢ ቢ ሲ አማርኛ” ተጠይቆ መልስ ላለመስጠት ሲሸሽ”

<<ንጽኋን አማራዎች መረሸናችንና በእምብርክክ እንዲዱ ማድረጋችንን በማሕበራዊ ሚዲያ ነው የሰማሁት “እናጣራለን”>> በሎ እያሾፈ፤ ለፋሲል የኔዓለም ቃለ መጠይቅ የሰጠ አስረስ ማረ የመሳሰሉት የዘመነ አሽከሮች ግን አቻምየለህ አንዲት ፍሬ ቃል ሰንዝር አልወነጀላቸውም ፤ አልወቀሳቸውም አልወረፋቸውም፡፡

አቻም ወገንተኛ ሆኖ ለአውራጃው ልጆቹ በሚያዳላ መልኩ ማስረጃ ማቅረብ በማይችልበት ውንጀላው እስክንድርን ብቻ ለይቶ ጥላሸት ቀብቶታል፡

እንዲህ እያለ፡

(ቀደም ብሎ እስክንድር ነጋ ላይ አንድ ነገር ቢሰራ ኖሮ ) በአርበኛ አሰግድ መኮንን ላይ የደረሰው መከራ ላይደርስ ይችል ነበር” በማለት ምስኪኑን እስክንድርን ይወነጅለዋል፡፡ አንድ ነገረ ቢሰራ ኖሮ የሚለው በሞት ወይስ  ከትግሉ ማስወገድ? አልገባኝም!

የሚገርመው አሰግድ መኮንን እጅ ስጥ ሲባል እንደ የጦር መሪነቱ ራሱን በሳይኖይድ ወይንም ሽጉጡን ጠጥቶ መስዋእት ላለመሆን ፈቅዶ ለአብይ አሕመድ አሽከሮች እጁና መሳሪያውን ያሰረከበን የአሰግድ መኮንን  እጅ መስጠት ምርጫ “እስክንድርን ዋና ተጠያቂ አድረጎ መወንጀል” እናቴ ቀሚስ አደናቀፈኝ አይነቱ የነ አቻመየለህ መሸፈኛ ‘’አርቲ ቡርቲ” የቀረበበት ዋና ምክንያት አቻምየለህና መሰሎቹ እስክድር ላይ የሚዘባበኑበት ምክንያት አላቸው፡፡

ይኸውም የአሰግድ መኮንን ሽንፈት መደበቅ ነው፡፡ አሰቀደሞ ጥንቃቄ ያላደረገ ራስን ለመከላከል ፤ ጠላት እጅ ቢወድቅ ፤ አንድ መሪ ቢያዝ ምስጢር እንዳያወጣ ሽጉጡን መጠጣት ባይችል እንኳ ቅጽበታዊ መስዋእትነት ለመቀበል “በኪሱ ምን አማራጭ (እንደ የሳዮናይድ ከኒን መርዝ የመሳሰሉ) መያዝ እንዳለበት የመጀመሪያው “ሀ ሁ” የሽምቅ ጦር አዋጊና ሃላፊ’ ትምሕርት የመሰውያ ሕግ ማወቅ/መማር ነበረበት፡፡ ይህንን “ሀሁ” የማያውቅ የሽምቅ ተዋጊ መሪ የሆነው አሰግድ ልምድሥልጠና” ያልነበረው ሰለነበር ሰተት በሎ እጁን ለጠላት ሲያሰረክብ ፤ እነ አቻምየለህ ያቺን ድክመቱን ላለማጋለጥ ፤ ደክመቱና ተጠያቂነቱ ለእስክንድር ጭነውበታል፡፡

ትግ <<ገሪሙኒ አነ፤ ናይዞም ሸማነ>> ይላል <<የሸማኔ ነገር እኔኑም አስገረመኝ>> ይላል፡፡  ነገረ ሰሪዎችም “የሰው ስም ለማጠልሸት” እንደ ሸማኔው ‘’የሥም ማጥፊያ መወርወርያቸውን’’ ከግራ ቀኝ፤ ከቀኝ ወደ ግራ እየተቀባበሉ ነገር ይጠነጥናሉ፡፡

 በመቀጠል እስክንድርን ጸረ አማራ አደረጎ በመወንጀል፤የጀርባ ታሪኩን በጸረ አማራነት አድርጎ ሲከሰው ታያላችሁ፡

እንዲህ የላል፡-

 <<የኋላ ታሪኩና በአማራው የኅልውና ተጋድሎ ውስጥ ሊያራምደው በሚሞክረው ጸረ አማራ እሳቤው>>

በማለት ይወነጅለዋል፡፡

እስክንድር ጸረ አማራ የኅልውየኋላ ታሪኩ አቻምየለህ ማስረጃ አላቀረበም፡፡ አቻምየለህ የአማራ ተቆርቋሪ እስክንድር  ግን ጸረ አማራ የሚሆነበት በታአምርም መባል ያልነበረበት ጮርቃነት ነው፡፡ አቻምየለህ ከትልቁ ኢትዮጵያዊ ማማ ወርዶ ወደ <<አማራ እ ነኝ ፤ የአማራ አሳቢና ተከላካይ እኔና የተቀረነው ነን >>  በሚል ውስጠ ገለጻ  የአማራ ሕልውና ለማጥፋት አስቦበት የመጣ  በማለት ይወነጅለዋል፡፡

አቻም ከላይ እንደተመለከታችሁት አማራ ማለት እኛ እንጂ እስክንድር የአማራን ሕልውና በመጻረር የሚታወቅ <<የኋላ ታሪኩ>> ሳይመረመር የተቀላቀለን የሚለው የአቻምየለህ ጽሑፍ የሚያሳየን ትምክሕተኛ ወደ ሆነው ወደ ማፈሪያ ካምፕ ተፈጥፍጦ ሊወድቅ እንጥልጥል ላይ ነው (if not already) ያሳዝናል፡፡ካልሆነማ የእስክንድር <<የኋላ ታሪኩ>> አማራ የዘር ማጥፋት እየተፈጸመበት ነው እያለ ዓለም ሙሉ እየዞረ ሲታገል፤ “የግራኝ አሕመዱ” አብይ አሕመድ ጉግ ማንጉግ ፖሊሶችና ገራፊ ሰላዮች ፤ እንዲሁም አዲሰ አበባ ውስጥ በጸረ አማራ የተቀረጹ የወሃቢያ ኦሮሞ እስላማዊ ዱርየዎች ሽጉጥ ይዘው በሞተር ሳይክል ሲፍልጉትና ቁምስቅሉን ሲያሳዩት ፤ ሲታሰር ሲፈታ ፤ አቻምየለህ ግን እዚህ እኛ ጋር ትምሕርቱን ሲያጎለብት ነበር፡፡

ያ ሁሉ የእስክንድር <<የኋላ ታሪኩ>> ለአማራ የከፈለው ታሪካዊ መስዋዕት ነው፡፡ ታዲያ ምን ያደርጋል አለመታደል ብዙዎቹ አማራዎች የሞተላቸውን ፤ የተሰደበላቸውንና የታሰረላቸውን  የሚሰድቡና የሚያግሉ፤ ኤርትራ እንጂ ኢትዮጵያ አይደለሁም የሚልን የሚያሞግሱ የኤርትራ ባንራ የሚያውለበልቡ ማፈርያዎች ናቸው፡፡

“መነሻችን አማራ መድረሻችን ኢትዮጵያ” የሚለው የእስክንድር የትግል ቅስቀሳ “አቻምየለህ ታመሩ” ቅራቅምቦ እያለ አሹፎበታል፡፡

እንደተገነዘበኩት ከሆነ አቻምየለህ ታምሩ ከጎጃሜ ብሄርተኞቹ (ሌሎችም ሰምቻቸዋለሁ) "መነሻቺን አማራ፣መድረሻቺን አማራ" ጋር ፍቅር የያዘው ይመስላል። እንደዚህ ዓይነት ጎበዝ ወገኔ ከኢትዮጵያ ኮረብታ ላይ ሳይታሰብ ወደ ጽንፈኛው የብሄር ብሄረተኛ አማራ ሰፈር ተወርውሮ ሊወድቅ  መቃረቡ ማየት ያሳዝናል።

አቻምየለህ መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ የሚለው የናዚ አይነት ‘ኩፍኝ’ ተለክፎ ካልሆነ እስክንድርን እንዲወገድ መምከር ይበልጥ ትግሉ ያኮላሸዋል እንጂ አያጠናክረውም፡፡

እንዲህም ይላል፡-

<<እስክንድር ራሱ መሪ አድርጎ ሲሾም የሚታየው ድል ለዲሞክራሲ የሚለው ሕዝባዊ መዋቅር በተዘረጋበት አገር የሚታሰብ መፈክሩ እንጂ የአማራ የኅልውና ተጋድሎ አይደለም።>>

የሚገርም ነው!!!! ድል ለዲሞክራሲ ሕዝባዊ መዋቅር በተዘረጋበት አገር የሚታሰብ መፈክር እንጂ በአማራ የኅልውና ተጋድሎ ወቅት አይደለም ሲል ፤ ሕዝባዊ መዋቅር ያልዘረጋው በዲሞከራሲ የማያምነው አማራ መነሻና መዳረሻችን ባዩ በሃሳብ የተለዩትን ሰዎች ዘመነ የገነባው የጉደጋድ ድብቅ እስርቤት ታፍነው የታሰሩት

1 ዶ/ር እንዳለማው

2 ዶ/ር መዝገቡ

3 ጊራወርቅ ወርቁ

4 ጋዜጠኛ ወግደረስ

5 ወግደረስ ጤናው

 6 የአብስራ ሞላልኝ

 7 ዶ/ር ዳዊት ፍስሃ

 8 አንሙት አምሬ

 9 ልዑል ያሳብ

 10 አብርሃም ጎደፋው

የመሳሰሉት አማራዎች ታስረው 1ኛ እና 2ኛ ታሳሪዎች ለመፈታት በሚልዮኖች ብር ተጠይቆባቸው አሁን ጨለማ ውስጥ ያሉት እና 4 ሰዎች “ገርጨጭ” በተባለ ገጠራማ ከተማ ውስጥ በዘመነ ካሴ ታጣቂዎች ጥይት ያለ ምንም ወንጀልና ፍርድ ቤት ቢ ቢ ሲ ዜና የሰራባቸው ተረሻኞች ውስጥ

1) የወረዳው ቤተ ክሕነት ሥራ አስኪያጅ የነበሩት  መሪጌታ ግሩም

2)  አቶ አዘነ ደምሴ

3)  አቶ  አስማማው አቤ

4)  ወ/ሮ ላይን አየሁ ዳኛው   (የጤናኤክስተንሺን ሰራተኛ) ሲረሸኑ  13 ሰዎች በእምብርክክ እንዲንፏቀቁ የተደረገው ሕዝባዊ መዋቅር እስኪደራጅ በዲሞከራሲ እንቀልድ የሚሉት እነ ዘመነና አሁን ደግሞ አሁናዊው  የአማራ ሕልውና የሚረጋገጠው ያለ ዲሞከራሲ በእውር ድምብሩ ሲራመድ ነው  ይለናል አቻምየለህ ታምሩ!

ሳደንቀው የነበረው “ትንታጉ” የአቻምየለህ መመራመርና ማስተዋል ምን ጅብ ነጠቀው?   

አቻምየለህ በሚገርም ጥበት እንዲህ ይላል፡

<<መነሻችን አማራ፤ መድረሻችን ኢትዮጵያ” የሚል ጸረ አማራ ዝባዝንኬ ማዘውተራቸው ለምን ይሆን ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል። ሲጀመር “መነሻችን አማራ፤ መድረሻችን ኢትዮጵያ” የሚለው ጸረ አማራ ማጭበርበሪያ የተፈለሰመው በእስክንድር ነጋም አይደለም። ማጭበርበሪያውን የፈለሰሙት የፋኖን ተጋድሎ ለመጥለፍ የተሰለፉ አሜሪካን አገር የሚኖሩ የምናውቃቸው የግንቦት ሰባት ጉግ ማንጉጎች ናቸው።>> ይላል፡፡

በአቻምየለህ አባባል “መነሻችን አማራ፤ መድረሻችን ኢትዮጵያ” ማጭበረበሪያና  ጸረ አማራ መፈክር ሲሆን “ኢትዮጵያ” የሚል ቃልና መድረሻ  የሚጠቅሱ ሰዎች አማራ ሳይሆኑ ኢትዮጵያዉያን ናቸው ወደ ማለት ይዳዳዋል፡፡

“መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ” የሚለው ትርጉሙ (አቻምየለህ እስካላስረዳን ድረስና ዘመነ ‘አብይ አሕመድ ሥልጣኑ ለአማራ በቻ” ‘ያሰረከብ’ ከሚለው ውጭ ሌላ ትርጉም ከሌለው በቀር ) ትርጉሙ ልከ እንደ ትግራይ በሔረተኞች በ80ዎቹ ጦርነቱ ወቅት ትግራይ ነፃ ካወጡ በ ከዚህ ወዲያ አገራችን አይደለም፤ ኢትዮጵያ ነው፤ << መበገሲትና ትግራይ መዕለቢና ትግራይ>> (መነሻችን ትግራይ መዳረሻችን ትግራይ) ከሚለው መመሪያችን ውጭ) አንንቀሳቀስም! በማለት በርካታ ታጋዮች ወደየ ቤታቸው ከነ ትጥቃቸው በመሄዳቸው አዲሰ አበባ መዝልቅ ሰላለተቻለ በስንት ልመና እነ ሳሞራ የኑስና አመራሩ ወራት የፈጀ ልመና ተደርጎ ነበር አዲሰ አበባ የገቡት ( አድማው “ደውታ” ይሉታል “ባለህበት መቆም” ማለት ነው)፡፡ ካሁን በፊት ይህንን በሚመለከት ሳሞራ የሰጥው ቃለ መጠይቅ አቅርቤ ነበር፡፡

የአማራ ብሔረተኞች፤ ትግራይና ኦሮሞ ብሔረተኞች ኢትዮጵያ የሚል ሐረግ በጆራቸውና በትግላቸው ሊደመጥ አይሹም፡፡ ስለሆነም አዲሱ ወጣት የፋኖ ታጋይ አማራ “አማራዊነት” እንጂ “ኢትዮጵያ” የሚል ቃል በነበር ትውስታ ሕሊናቸው ውስጥ ቀሰ በቀስ እየተቀረጸ ከነ አካቲው “ኢትዮጵያ” አሁን እንዳለው የትግራይ ወጣት ያው አማራው ወጣትና ታጋይ ፋኖው የዚያ ባሕሪ ይይዛል፡፡ እመኑኝ !!! የአማራ ወጣቶች ከሚለቁት የማሕበራዊ ሚዲያ ንግግራቸው አድመጡና ሥጋቱን ታያላችሁ፡፡

የነ አቻምና ዘመነ ትምሕርት “ዲሞከራሲ፤ ኢትዮጵያና አማራ” የሚባል የሚደባልቅ ትግልና ቃል በፋኖ ውሰጥ መፈቀድ የለበትም ነው፡፡“ኢትዮጵያ ለዜጎችዋ አራት ኪሎ ደግሞ ለአማራው” ነው ዘመነ እንደሚለው፡፡ ትግሬና አሮሞ ገዘተውን አሁን ደግሞ በዘመነ ይሚመራ አማራ ሊገዛን አራት ኪሎን አስረክበን እያሉት ነው፡፡

ለመሆኑ የግንቦት 7 መፈክር ስለሆነ ኢትዮጵያ የሚባል መዳረሻ ያለው ጠላት ነውና መወገድ አለበት ብሎ ማስተማር ምን እሚሉት ዝቅጠት ነው? ለመሆኑ አማራን ነጻ ካወጣህ መዳረሻህ ወዴት ነው? ነው ውይስ መነሻችን አማራ መድረሻችን አማራ ያንተው ዘመነ <<ገድለን ከቀበርነው ማን ይደራደራል፤ ሥልጣኑን ሙሉ ለሙሉ ለአማራ አስረከቦ ኢትዮጵያ ደግሞ ለዜጎቻ ያስረክብ” ሲል ዘመነ በዚህ መልክ እስክንድርን “በኢትዮጵያ ካድሬነት ከስሦታል’’፡፡ ኣቻም ይህንን ሰመቶ ትንፍሽ አላለም፡፡

 እግዚሐር ይስጠው ሳይደብቅ የጎጃም አማራ ፋኖ  ብረት ያነሳበት መነሻው <<አራት ኪሎን በሙሉ ለአማራ እንዲረከበው>> መሆኑን መነሻውም መደረሻው ሳይሸሽግ ነግሮናል፡፡ ይህንን ነው አቻምየለህ ያለማፈር ደግፎ እስክንድር ኢትዮጵያ ሰላለ ጸረ አማራ ሕልውና ነው እያለው ያለው፡፡   

አቻመየለህ እወነትነት ቢኖሮው ኖሮ እስክንድርን “የችግሩ መነሻና መጨረሻ ኣድርጎ” መወገድ አለበት ብሎ ከመቃዠት ይልቅ አቻምየለህ የሚደግፈውን “መአት ጉድ ያለው” “መነሻችን አማራ መዳረሻችን አማራ የሚለው የኤርትራ ፓስፖርት የያዘው “የጎጃሙ ዲገላውን ቡድን”  ትንፍሽ ሳይል እስክንድር ላይ መረባረቡን ስመለከት አቻምየለህ አድፈጦ በነበረበት ቦታ ቢቆይ የሻል ነበር እላለሁ፡፡

ይህንን ልበልና ላቁም፡-

ባልተጠበቁ ሁለት ወቅት የማከበራቸውና የምወዳቸው ወዳጆች አጥቻለሁ (1) አብይ ሲመጣ እና (2፟) በእስክንድርና በዘመነ መካከል የተከሰተው ጸብ፡ አሁን በ2ኛው ወቅት ወዳጄ የነበረው አቻምየለህ ጋር ተለያየን፡፡ ከተለያየን የቆየን ቢሆንም (ከተለያየን በእርሱ ትእቢት ቢሆንም)፡፡ አሁን ጎራ ለይተን <<መነሻውና መዳረሻው አማራ ያደረገው> “ጩጬ” ብሔረተኛው ቡደን ጋር ለበጎ ፖለቲካዊ ፍልሚያ ተለያይተናል፡፡

ጌታቸው ረዳ    

አዘጋጅ Ethiopian Semay