Wednesday, June 14, 2023

ብዙ አካለ ስንኩል ወጣት የያዘቺው ትግራይና በባዶ ካዝና እየተራመደ ያለው አፓርታይዱ ኦሮሙማው መንግሥት ጌታቸው ረዳ (EEthiopian Semay 6/14/2023

 

ብዙ አካለ ስንኩል ወጣት የያዘቺው ትግራይና በባዶ ካዝና እየተራመደ ያለው አፓርታይዱ ኦሮሙማው መንግሥት

ጌታቸው ረዳ

(EEthiopian Semay

6/14/2023

ኢትዮጵያ እንደሃገር ሳይሆን የከሸፈች ሃገር (ፈይልድ ስቴት) ሆናለች። ከሆነችም ቆይታለች (በዚህ ርዕስ ብዙ፤ብዙ ብለናል) በዚያ ምክንያትም ነበር የአማራው ወጣትና ምሁር ክፍል ሕዝባቸውና እራሳቸውን ከተነጣጠረባቸው የዘር ማጥፋት ዘመቻ ለመከላከልና ብሎም ለማስቆም ራሳቸውን ቶሎ ነፃ ማውጣት አለባቸው ስንል የነበርነው።

በከፊልወድዶ ሳይሆንመሆን እንዳለበት የጠበቅነው ሕዝባዊ ማዕበል እንኳ ባይሆንም ተገድዶ የአልሞት ባይ ተጋዳይ በትንሹም ቢሆን የሽምቅ ውግያውብሎ ጀምሮታል፡ እንዲበረታበትም እንመክራለን።

አገርን ማስተዳዳር ችሎታ የሌለው በባዶ ካዝና እየተንከላወሰ የዕርዳታ ስንዴ እየሸጠ በመተዳዳር ላይ ያለው ማፈሪያው አብይ አሕመድ ኢትዮጵያን በማፍረስ ሂደት የአምበሳው ድርሻ በመውሰድ ከወያኔ ትግሬዎች ጋር ወዳጀነት ግምባር ገጥመው አማራን ለማጥፋት በተናጠልና በጋራ ዛሬም ተቀናጅተው ቀጥለውበታል።

በዘርና አገር በማፍረስ ተጠያቂ የሆነው መለስ ዜናዊን የተካ ሚሳይል ወደ ተተኮሰባት ምድር ባሕርዳር እንዲጎበኝና ፡እንዲሁም የኦሮሙማ አህዮችን የሚሸከመውቂሉ ማሞንየተካው ይልቃል የተባለውጌኞመቀሌን እንዲገበኝ በአለቃቸው አብይ አሕመድ ትዕዛዝ በታዘዙት መሰረት ሁለቱም ስለ ወልቃይትና ራያ ወደ ትግራይ የማዋሃድ ስምምነት አውን ለማድረግ በሁለት አቅጣጫ ጦርነት የመከፍት ጥናት ለመነጋጋር እንደሆነ ግልጽ ነው።

ስለ አብይ አሕመድ ሁላችሁም ስለምታውቁት ብዙ አልሄድበትም። ይልቅኑ ውስጥ ለውስጥ ምን እየተካሄደ እንዳለ ትግርኛ ለማታደምጡ ወገኖች እንድታውቁ ባጭሩ ላብራራ፡

ትግሬዎች ለመገንጠል ሦስት ሂደቶችን እያሳኩ ነው።

1- ሊሂቃን ስለመገንጠል ተከታታይ ስብሰባ እያደረጉ ይገኛሉ

2- የወያኔ ጳጳሳትና ቀሳውስት ተዋህዶ ቤተክርሰትያንን በማፍረስ ከማኣከላዊው ሲኖዶስ በመነጠል  የትግራይ ሪፑብሊክ ሃገረ ስብከትበይፋዊ አዋጅ ተነጥለው መስረተዋል።አዲስ አባባ ውስጥ የተቀመጡት በጳጳስነት ወንበር የተሾሙት አባ ማትያስ በዚህ ሴራ ላይ በግላቸውም ሆነ በሲኖዶሱ በኩል ያሉት ነገር እንደሌለ ነው እስካሁንዋ ደቂቃ ድረስ የማውቀው።

3- ጌታቸው ረዳ፤ በሚመራው መንግሥትፈራ ተባእያለ ለትጥቅ ትግል በመጠባበቅ ላይ ያለውውስጥ ለውስጥበመደራጀት ላይ ላለው ለአንጃው የሽምቅ ፓርቲ የውስጥ እገዛ ለመስጠት ያለው ገጽታ ሦስቱን እንመለከታለን።

“Undoubtedly, war is the greatest source of the evils which oppress civilized nations. Not so much actually war, but rather the never-ceasing and indeed ever increasing preparation for a future war.” Page 66 (Kant on History) published by the Library of Liberal arts) ይላል ፈላስፋውካንትይህንን በራሴ ልተርጉመው፡ እንዲህ ይላል።

"ጦርነት የሰለጠኑ ሀገራትን የሚያወድም የክፋት ምንጭ መሆኑ አያጠያይቅም። ክፋቱጦርነትሳይሆን የማያቋርጥ እና ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ላለው የጦርነት ዝግጅት ይበልጥኑ አሳሳቢነቱ የላቀ ያደርገዋል።" ገጽ 66 (ካንት  በታሪክ ላይ”) በሊበራል አርትስ ቤተ መጻሕፍት የታተመ ትንሽየ መጽሐፍ)

ጦርነት የክፋቶቹ ሁሉ የክፋት ምንጭ ነው ሲል አውዳሚነቱን እየገለጸ ነው። የወያኔ ትግሬዎች በከፈቱት ጦርነትና አብይ አህመድ በሴራ በተባባራቸው የጦርነት አውድ ላይ ባለፈው ሁለት አማታት ውስጥ በሚሊዮኖች ወጣት ትግሬዎችና ኢትዮጵያዊያን አካለስንኩል እና ሙት ወይንም መፈናቀልና የሕሊና በሽተኛ እንዲሆን አድርገዋል። ለዚያ ሁሉ ወንጀል ዛሬም ተጠያቂ የለም። ስለሆነም ዛሬም ሁለቱ በሴራ ተስማምተው ያልጨረሱትን አማራን የማጥፋት አጀንዳቸው ዛሬም ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ናዚዎች በአውሮጳ አይሁዶች ላይ እንዳወጁትየፋይናል ሶሊሽንየዘር ማጥፋት ዘመቻቸው ጀምረውታል።

 ብዙ አካለ ስንኩል ወጣት የያዘቺው ትግራይ ክፍለሃገር ወዴት እየተጓዘች ነው? የሚለውን ላወያያችሁ። ከላይ የጠቀስኳቸው ሦሰት ነጥቦች እንመልከት።

የጌታቸው ረዳና የይልቃል ወደ ባሕርዳርና መቀሌ የመጎብኘት ትዕይንትን በሚመለከት፡

ሚሳይል የተኮሰባት ባሕርዳርን እያስተዳደሩ ያሉት የኦሮሙማ እልፍ አስከልካይብአዴኖችወልቃይትና ራያን ወደ ትግራይ ለማስረከብ በሁለቱ አቅጣጫ የሚካሄድ የጦርነት ሰልት ለመንደፍ እንደሆነ የውስጥ አዋቂ ምንጭ አያስፈልግም (ግልጽ ነው)

ምክንያቱም እነ ጌታቸው ረዳ በጉጉት እየጠበቁት ያሉት ወልቃይት የውጭ አገር መውጫ በር ካገኙ ሳይውሉ ሳያድሩ በፕሪቶርያው ስምምነቱ መሰረት (ማሃይምዋ አበበች አዳኔ እንዳለቺው መገንጠልን የሚከለክላቸው ስለማይኖር)  ሕዝብ ሰብስበው የመገንጠል ሪፈረንደም የማካሄድ መብት እንዳለቸው ተፈራርመው ስላሉ ያንን ለማካሄድ ከአብይ አሕመድየገዳይነት የምሰክር ወረቀትተሸላሚ የሆኑትን ቡዱኖች ይዞ ባሕርዳር ላይ ይገኛል።

የትግራይ ሊሂቃኖችም ሰሞኑን በተከታታይትግራይ የት ላይ ቆማለች? እያሉ ከሕልማቸው በድንገት የተሰወረችባቸውን ትግራይበዳሰሳላይ ናቸው።

ሰሞኑን መቀሌ ውስጥ ሁለት ትዕይነቶች ታዝቤአለሁ።

1ኛው ስብሰባ ከህጻንነተቻው ዕድሜ ጀምሮ ኢትዮጵያንና አማራን በመጥላት በየትምህርት ቤቶቻቸው የጥላቻ ትምህርት እየተጋቱ 27 አመት ያደጉ ጎረምሶችና እንዲሁም የድሮ የወያኔ ታጋዮች ትግራይ ከኤርትራ ወይስ ኢትዮጵያ ጋር መዋሃድ የሚልቅዠትውስጥ ገብተው መቀሌ ባንድ አዳራሽ ውስጥ በመሰብሰብ አገር በማፍረስሴራላይ ሲተነትኑ ቱብላይ አድመጠናል።

ይህ ቡድን ማሕበረሰቡን በፕሮፓጋንዳ እያጠበ ለማይቀረው የግንጣላ ጦርነት ለዳግም የሕሊና ዝግጅት በማካሄድ ላይ ነው።

2ኛው ሴራ የትግራይ የወያኔ ጳጳሳትና ቀሳውስት ውሳኔ ነው።

ሰሞኑን ከሕግ ውጭ ከዋናው ሲኖዶስ በመነጠል ኢትዮጵያ የምትባል አገር የትግራይ ቅኝ ገዢ ነችና አናውቃትም ብለው አዋጅ በማስነገር ከወሰኑዋቸው ውሳኔዎች ውስጥኢትዮጵያየሚል ቃል ከእምነት ማሕደሮችና ቤተክርትያን ተቋማት እንዲሰረዝ በማድረግ በመጽሐፍ ቅዱስም ሆኑ ሃይማኖታዊ መጻሕፍት እንደገና እየተጣሉ ወይንም እየተሰረዙ በምትኩትግራይበሚል ቃል ተተክተው ለአዲስ ሕትመት እንደሚዘጋጁ ሳያመነታ ገልጸዋል፡ (ይህ የታሪክ፤የቅርስ፤ የጽሑፎች፤የሃውልት፤የመንገዶች ስም ስረዛና ድለዛ በወያኔዎች የተጀመረ ቢሆንም ሃይማኖት መሪዎች ነን የሚሉ ካድሬ ቀሳውስት እየሰሩት ያለው ግን ከፍተኛ ወንጀል መሆኑን በዓለም ውስጥ በታሪክ አዋቂነቱና መምህርነቱ የታወቀው ሟቹ Eric Hobsbawm “The Age of Extremes 1914-1991”  በተባለው መጽሐፉ ወንጀል መሆኑን ይገልጻል። የኛ የሃይማኖትና የፖለቲካ ወንበዴዎች ግን ነባር ቅሪቶችንና ስሞችን በመለወጥ ወንጀል በመስራት ማሃይምነታዊ ድፍረታቸውን ሲገልጹ እናያቸዋለን።

 አማርኛ የሚባል ቋንቋና ኢትዮጵያ የሚል ቃል ጭራሽ እንዳይደመጥ በሙሉ ተስማምተዋል። የትግራይ ሪፑብሊክ ተዋህዶ ቤተክርስትያን በሚል እየተዘጋጀ ያለው ኢሕጋዊ አገራዊ ግንጠላየወያኔ ፖለቲካዊ የሃይማኖት ክንፍ በመሆን 1968 . ጀምሮ  በወያኔዎች የሚታዘዝበእነ ደብረጽዮን እና በእነ ጌታቸው  ረዳበውስጥ አበራታችነት እየተከናወነ ያለሁለተኛው ረድፍአገር የማፍረስ ሴራ ነው።

እነዚህ የትግራይ ጳጳሳትና ቀሳውስት ኢትዮጵያን ስያስወግዱ ኢትዮጵያ የምታቀርበው የባንክ፤የስልክ፤ የገንዘብ፤ የሸቀጥ፤የመብራትና መድሃኖቶችና ሆስፒታሎች፤ የመገናኛ አውታሮች፤ ነዳጆች እንዳይታገዱ የመጠቀም መብት እንዲኖራቸው፤ በእነ ጌታቸው ረዳና በአብይ አሕመድ ፈቃጅነት ዛሬም ኢትዮጵያን እየጠሉ ምርትዋን እንዲጠቀሙ እየተደረገ ነው (አገር ወዳድ ተጋሩ የኔን ዘመቻ ሰምታችሁ እገዳ እንዲደረግባቸው ተቃውሞአችሁን እንዳተስተጋቡ ጥሪ አቀርባለሁ፤መንግስት ቢኖር ነው ግን!!”)

አሁን ያለው መሪ አገር ወዳድ ቢሆን ኖሮ ወይንም እኔ መሪ ብሆን ኖሮ  አገልግሎት እንዳያገኙ በሕግ እንዲታገዱ አደርግ ነበር። (እናንተ ምን እንደምትሉ ባላውቅም እውነታው ግን እየሆነ ያለው አሁንም የኢትዮጵያ ምርትና አገልግሎት ልክ እንደ ሕዝቡ  እኩል አግልገሎት እያገኙ ነው።)

3ኛው በዚህ ጽሑፌን ልደምድም።

ጌታቸው ረዳና አንጃው ጦረኛ የድብቅ ሴራቸው፡

ጌታቸው ረዳ፤ በሚመራው መንግሥትፈራ ተባእያለ በመጠባበቅ ላይ ያለውውስጥ ለውስጥበመደራጀት ላይ ላለው ለአንጃው የሽምቅ ፓርቲ የውስጥ እገዛ ለመስጠት ያለው ገጽታ ገልጬ ልደምድም።

ሰዎች ይህንን ሴራ አያውቁም የሚል ግምት አለኝ። ታስታውሱ ከሆነ ካሁን በፊት November 16, 2022 

የትግሬዎች ፎኒክሲዝምበጻፍኩት ሐተታ ላይ እንዲህ ጽፌ ነበር።

ትግርኛውን ልጀምር << ሞይትና ዘይንሞት ሓመድ ልሒስና ዝተሳእና

ዓለም ዘገረምና

መስተንክር አፋጣጥራና >>

ሞተን እንደገና በዳግም ልደት አመድ ልሰን የተነሳን!

ዓለምን ያስገረመ መስተንክር ስነ አፈጣጠራችን!

ትናንትም ዛሬም አስገራሚ ልዩ ፍጡሮች ነን!!

እያሉ በንግግራቸውም ሆነ በሙዚቃዎቻቸው የሚያስተጋቡት የፎኒክስዋ ታሪክ 99% ትግሬዎች የፎኒክስዋ ዳግም ልደትና የትግሬዎች ዳግምአመድ ልሰን የተነሳንቅቡልነት የመፈክራቸው ተመሳሳይነት በዚህ 3 አመት በጆሯችሁና በዓይናችሁ ያያችሁትና ያደመጣችሁት አጋጣሚ ነው።ብየ ነበር።

 በመቀጠልም የፕሪቶሪያ ስምምነት ተብየው ከተፈራረሙ ማግስት ብዙ ሰውሲደሰትእኔ ተቃውሜ ነበር። በዚህም ጽሑፍ November 2, 2022

<< ከዚህ በኋላስ ወዴት? ከዚህ በኋላ ወያኔ ውስጥ ለውስጥ ተዋጊ አንጃ ይፈጥራል>> በማለት በጻፍኩት ጽሑፍ ላይም:-

ሁለቱም ፋሺስቶች መጨረሻ ሕዝብ አስፈጅተውና ፈጅተው አርስበርሳቸው ተቃቅፈው ያለ ምንም ተጠያቂነት ጦርነቱ ይቋጫል ብየ ደጋግሜ ከነሓሴ ጀምሮ ጽፌአለሁ፡ ስንት ሰው እንዳነበበው ባለውቅም እውነታው ይኼው ዛሬ ተፈራረሙ። ሆኖም ችግሩ እስካልተፈታ ድረስ የሁለቱ የፋሺስት ሰላም እንጂ የማሕበረሰባችን ሰላም ሊፈታ አይችልም።በማለት ስጽፍ፡ አስደግፌም እንዲህ ብየ ነበር፡

እንድታውቁልኝ የምፈልገው ወያኔ የሰላም ስምምነት ያድርግ እንጂ ትግራይ ውስጥየትግራይ ሪፑብሊክዓላማ ለማስቀጠል በውጭም በውስጥም ፍላጎት ያላቸው ትግሬዎች ስላሉ ወያኔዎች ቦታውን (ትግራይ ውስጥ) አስተዳደሩን ከተቆጣጠሩት በሗላ አንጃ ለሚፈጠረው ድጋፍ ሰጪ ሆነው ይቀርባሉ ብየ ነበር። ይህንን ዛሬ እውን እየሆነ አዝማሚያው እያየሁ ነው። ያንን ላብራራ።

ከዚያ በፊት ግን ስለ ጌታቸው ረዳ የጻፍኩት April 19, 2022

መቀሌ ዩኒቨርሲቲ የተነገረ የወያኔ ትልቁ ንድፍ

ነፋስ ላይ በአእዋፍ የተሠራች ዩቶፒያ ከተማጌታቻው ረዳ Ethiopian Semay) በሚል የጻፍኩት ላይ የጌታቸው ረዳ ንግግር ልጥቀስ፡

ጌታቸው ረዳ ለግንጣላ ከሚያሴሩት አንዱ ነው፡ በጣም ደብቅ ሴረኛነትና ጮካነት ከወያኔ የቀሰመው ትምህርት ተሎ ቀስሞ ተግባራዊ ካደርጉት አንድ ጌታቸው ነው። መቀሌ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ጋብዘውት የተናገረውን በድጋሚ ላስታውሳችሁ እሻለሁ።

እንዲህ ይላል

ብዙ ወዳጆች አሉን፤ ብዙ ነገሮች ውስጥ ለውስጥ ለማምጣት እየሞከርን ነው። እነሱ ይህንን የሚያደርጉልንመለስን ስለሚወዱ እኔን ሰለሚወዱ ወይንም ትግራይን ሕዝብ ስለሚወዱ እንዳይመስላችሁ የትግራይ አገርነት ፍላጎት በመደገፍ የነሱን ፍላጎት ይጠቅመናል ከሚሉት ጋር በማገናዘብ ሊደግፉን እየተንቀሳቀሱ ነው። ለምሳሌ ተከብበናል ስንል በድንገት … (?) ብሎ (ድሮን ?) ለማለትአግኝተናልለማለት ይመስላል::

ሶርያ አግኝታለች” “የመኖች አግኝተዋልበማለት በደፈና ስለ የውጭ ዕርዳታ ምን እንደተሰጣቸው ፍንጭ ሳይሰጥ ስለ የመኖች ሲያወራድሮንእንደተሰጣቸው የሚመስል  ፍንጭንግግር ሲናገር ይደመጣል። (ተረክበናል ከሚላቸው መሳሪያዎች አሁን በርክክብ አልታየም- ምክንያቱም አግኝተናል የሚላቸው ዘመናዊ መሳሪያዎች ደብቀዋቸዋል)

በመቀጥል እንዲህ ይላል፤

ትግራይ እንደ አገር ዓለም እንዲያውቋት የሚገደድበት ስራ መስራት አለብን። ያንን ማድረግ ከቻልንኢን ኤቭሪ እስቴፕ ኦፍ ወይ” (በያንዳንዱ ዘርፍ)ተፈላጊዎች እንሆናለን ማለት ነው። መጀመሪያብሔረ ሃገረ ትግራይለመመስረት አስፈላጊኢንስትቱሽንመስራት አለብን።ሠራዊታችንየዚህ አካባቢጎብለልእንዲሆን ካደረግነው ራሳቸው ይፈልጉናል። Red Sea/ የቀይ ባሕር/ ሃያሎች መሆናችን አሁን እያመኑ ነው። የዚህ አካባቢእስታብሊቲ” (የሰላም ምሰሶዎች) መሆናችን ማየት ጀምረዋል።

ሲል ጌታቸው ረዳ የግንጣለው ሴራ የውጭ ሃይላት እየገፉበትና ወያኔዎችም በዚህ ሴራ እየገፉት እንዳሉ ሳይደብቅ የተናገረውን አስነብቤአችሁ እንደነበር ይታወሳል።

ስለ ሃይማኖቶኞቹ መገንጠል ገልጫለሁ፤ ስለ ሊሂቃኖቹ ገልጫለሁ፤ አሁን ድግሞ ጌታቸው ረዳ እና መሰሎቹ አስተዳዳሩን የተቆጣጠሩበት ዋናው ምክንያት፤ዛሬ በየአዳራሹ ስለ ግንጣላ የሚሰብኩ በርካታ የትግራይ ምሁራን ቅስቀሳው እያካሄዱ ወጣቱን በሕሊና ዝግጅት ለዳግም ጦርነት እያዘጋጁት ሲሆን፤ ከውስጥ እነ ጀነራል ምግበይ እና የመሳሰሉ በወንጀል የተጨማለቁ ወንጀለኞች በየገጠሩ እና አውራጃው እየሄዱ የቆየው ድብቅ የጥርናፈ (የማደራጀት) ስራ በመካሄድ በሰላም ሰበካ ስም እየሄዱ ገጠሬውና ከተሜው እንዲሁም ታጣቂው ውስጥ ለውስጥ ሲሰብኩት ጌታቸው ረዳ ደግሞበሰላም ጡሩምባውአገራዊ ኢትዮጵያዊነት እየሰበከባንኩን ስልኩንና ሸቀጣ ሸቀጦችን ወደ ነበሩበት ደረጃ እንዲያድጉ ካደረገ በኋላ፤፤ እነ ደብረጽዮን እነ መንጆሪኖ እና የመሳሰሉ መሰሪ ወያኔዎችንኣንጃእንዲያዘጋጁ በማድረግ ከጌታቸው ረዳ ወይንም ከመጪው ወያኔዊ አስተዳዳር ጋርበዲሞክራሲ ስምጸብ የፈጠሩ መስለው በረሃ በመውጣት አገራዊ ግንጠላ ለማካሄድ እየተዘአጋጁ ነው።በውስጥ የሽኩቻ ባሕሪ የለም ማለት ግን አይደለም፤ አብሮም ወያኔን ከሚቃወሙ እኔን መሳይ ጥቂቶችም ግፍትና ፍትግያ እንዳለበትም አትዘንጉ። በዛው ላይ አካለ ሰንኩላን ሆነው ባለሰቡት ህይወት የወደቁት እሮሮ ሲጨመር ውጥረቱ የት የሌለ ያደርገውና ምናልባትም ትግራይ በብርት የሚጨራረሱ ሥርኣተ አልባየአናርኪጋንጎች ምድርም ልትሆን ትችል ይሆናል። በተለይ ኤርትራ ኢሳያስ ሞት በኋላ እነዚህ ቡዱኖች የሚኖራቸው ሚና አካባቢው ለውጥርት ይዳርጋል። ይህ የሚሆነው ሁነኛ አገራዊ መንግሥት እንዳሁን ካጣች ሁኔታው ይባባሳል።

ከኢትዮጵያ ሳይገነጠሉ አገሪቷ ለትግራይ ሕዝብ  የምታቀርበውን ሸቀጥና ገንዘብ ትግራይ ውስጥ በውስጥ አባሎችና እራሳቸውም በመዝረፍ 17 አመት ሽምቅ ተዋጊያቸውን እየቀለቡ ለድል ደርሰው እንደነበር ይታወሳል።ግንጠላ ለማካሄድም ዕደል ነበራቸው፡ ምቹ ነበር።

ያኔ ምቹ ሆኖ በድል ሲገቡ ዛሬ ሁሉ ጥንካሬና ብረት ይዘው ለምን ተሸነፉ ብንል፤ ዛሬ ከመአከላዊ መንግሥት ጠቅላላ የባንክ ፤የንግድ የስልክ የገንዘብ ጠቅላላየኑሮ ቧንቧዎችሁሉ ዝግ ስለተደረገ እንኳን ተዋጊው ሕዝቡ ችግር ውስጥ በመግባቱ ተዋጊዎቻቸው የሚቀልቡበት መንገድ ስላልነበራቸው በቀላሉ ተከብበው ተሸነፈዋል።

በለመሳካቱ ምክንያቱን  ወደ በመፈተሽ በመግባት ለመሸነፋቸው ዋናው ምክንያትየምጣኔ አቅም ዝግ ስለነበርና ሕዝቡ ሊቀልባቸው ባለመቻሉየስምምነቱን ዕድል በመጠቀም አስተዳደሩን ከተረከቡ በኋላ ትግራይ አስፈላጊውንፋሲሊቲና ጥቅማጥቅምካገኘች በኋላ ትግራይ የኢትዮጵያ አካል ሆና እንደነበረቺው በክልል ደረጃ እንድትቆይ እያደረጉ የምታገኘው ጥቅም በሕዝቡ በኩል እያገኙ ልክ እንደ 17 አመቱ ትግል በመጀመርአንጃቸውንወደ በረሃ በመላክ የተጣሉ አስመስለው የሽምቅ ውግያ ከፍተው አገራዊ ግንጠላውን በቀላሉ ላማሳካት እንዲመቻቻው እየሰሩ ነው።

ያንን ከማድረጋቸው በፊት መጀመሪያ የወልቃይትና የራያን ነገር እልባት ማወቅ ይኖርባቸዋል። ወልቃይትን ካገኙ የሽምቅ ተዋጊ መስርተው ወደ ሱዳን መውጫ በር ከፍተው ካሁን በፊት ያሳየሁዋችሁ የፖርትሱዳን እና የወያኔ ዕቅድ በመቀጠል ምናባዊዋንዓባይ ትግራይ” (ታላቅዋን ትግራይ) ይመሰርታሉ። ሆኖም

በዳመና ውስጥ በአእዋፍ የተሠራች ምናባዊ ከተማመጪው ህይወትዋ ምን ይመስል ይሆን? የሚለው ትልቁ ጥያቄ መልስ ሊገኝለት የማይቻል ጥያቄ ነው።

ጽሑፉን ብትቀባበሉት ምሁራንና ሌሎቹ እንዲያዩት ይረዳል።

ጌታቻው ረዳ

Ethiopian Semay