Monday, February 14, 2011

ቀን ሲደርስ አምባ ሲፈርስ

>ለጎጠኛው መምህር (አማርኛ) $25.00 እና ሓይካማ (this is diffrent book/story that is defferent than the Amharic indicated) (ትግርኛ) $15.00 መጽሐፌን ለመግዛት ዕድሉን ያላገኛችሁ ካላችሁ በሚከተለው አድራሻ ደውላችሁማግኘት ትችላላችሁ Telephone (408) 561 4836 (Getachew Reda P.O.Box 2219 San Jose, CA 95109) getachre@aol.com www.ethiopiansemay.blogspot.com

ቀን ሲደርስ አምባ ሲፈርስ

ከዲዳክ

ተክለ ጻድቅ መኩርያ በጻፉት ዐፄ ቴዎድሮስ እና የኢትዮጵያ አንድነት በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ ዐፄ ቴዎድሮስ አንቱ የተባሉ ጉምቱ ጉምቱ መሳፍንትን እየረቱ ከቋራ ጎንደር የደረሱበትን ምክንያት ሲገልጡት «መኳንንቱ እና መሳፍንቱ የተጠናወታቸው መጠን ያለፈ ንቀት ነው» ይላሉ፡፡ እነርሱ የሚያውቁት ይህ ነው የተባለ የሚጠቀስ የነጋሢ ዘር የሌለው፣ «የኮሶ ሻጭ ልጅ»፣ ካሣ የተባለ ሽፍታ፣ አንድ አሥር ጀሌ አስከትሎ የት ይደርሳል? የሚል ንቀት ነበራቸው፡፡ ካሣ እቴጌ መነንን ድል ነሥተው እንኳን መሳፍንቱን ሊያስደነግጣቸው አልቻለም፡፡ ለውጡን ከጎንደር፣ ከመቀሌ እና ከጎጃም አብያተ መንግሥታት ነበር የሚጠብቁት፡፡ እነ ደጃች ውቤ፣ እነ ራስ ዐሊ፣ እነ ደጃች ጎሹ፣ እነ ደጃች ክንፉ፣ እነ ደጃች ወንድ ይራድ፣ አንዳቸው ሌላቸውን እንጂ ካሣን ለአልጋው አይጠረጥሩም ነበር፡፡

ሁሉም ምክንያታቸውን በአንድ ቃል ነበር የሚገልጡት «ይህ የኮሶ ሻጭ ልጅ የት ይደርሳል?» እያሉ፡፡ ከጎንደሯ ንግሥት ከእቴጌ መነን መኳንንት አንዱ የነበረው ደጃች ወንድይራድ «ይህን የኮሶ ሻጭ ልጅ አንገቱን እንደ ሙጭልጭላ አንቄ አመጣልሻለሁ» ብሎ ፎክሮ ነበር ጭልጋ ጫቆ ወረደ፡፡ ነገር ግን ያሰበው ከሽፎ በጦር ተወግቶ በካሣ እጅ ተማረከ፡፡ ካሣም «እናቴ ከገበያ ኮሶ ሳይሸጥላት የቀረ አለ፤ እህል ጠፍቷልና ይህንን ተመገብ» ብለው ደጃች ወንድይራድን የኮሶ ሻጭ ልጅ ብለው በተሳደበበት አፉ ኮሶ አጠጡት ይባላል፡፡

እቴጌ መነንም በሰኔ 1840 ዓም ካሣን ለመውጋት ሰባት ነጋሪት አገር አስከትተው ወደ ቋራ ሲጓዙ ከንቀታቸው ብዛት «ይህ ቆለኛ ወዴት አባቱ ሊገባ ነው ይሆን?» እያሉ የትዕቢት ቃል ተናገሩ ይባላል፡፡

ይህንን ክፉ ቃል የተናገሩትን እቴጌ መነንን ለመበቀል ካሣ ከማረኳቸው በኋላ በዋሻ ውስጥ አስገብተው ባቄላ አስፈጯቸው ይባላል፡፡

ይህ ሁሉ ሆኖ መሳፍንቱ እና መኳንንቱ ስለ ራሳቸው ኑሮ እና ሥልጣን ይጨነቁ ነበር እንጂ እየመጣ ያለው ነገር ሊታያቸው አልቻለም፡፡ አንድ ካሣ የሚባል ሰው ከቋራ ተነሥቶ ታሪክ እየሠራ መሆኑን ለማየት የሚችል ዓይነ ልቡና አልነበራቸውም፡፡

እንዲያውም ደጃች ጎሹ ዲ አባዲ ለሚባል ፈረንሳዊ በጻፉት ደብዳቤ «ተካሣ ጋር የተዋጋን እንደሆነ ጎንደር እገባለሁ፤ እንገናኛለን፡፡ ወደ ቆላ የሸሸ እንደሆነ ሰው ባገኝ እሰድልሃለሁ ፈረሱን» ብለው ጽፈው ነበር፡፡ ደጃች ጎሹ ካሣ እንደሚሸነፉ እንዲያውም ወደ ጫካ እንደሚሸሹ ነበር የሚያስቡት፡፡

ራስ ዐሊም ከደጃች ካሣ ጋር ታርቀው እናታቸውን እቴጌ መነንን ካስመለሱ በኋላ ካሣን ንቀው ተዋቸው፡፡ ካሣ ጎንደር ቤተ መንግሥት ደጅ ጥናት መርሯቸው ሀገራቸው ቋራ ሲሸፍቱ ቀድሞ የተሾሙበትን ርስት ደንቢያን ለደጃች ጎሹ ሰጧቸው፡፡

ሁሉም መሳፍንት እና መኳንንት የካሣን ጀግንነት እና ታሪክ ሠሪነት ለማየት የቻሉት ሊመለስ በማይችል አጋጣሚ ውስጥ ሆነው ነበር፡፡ ደጃች ጎሹ ጉር አምባ ላይ በኅዳር 19 ቀን 1845 ዓም በካሣ ሠራዊት ድል ከመሆናቸው ከቀናት በፊት

አያችሁት ብያ ይህንን ዕብድ

አምስት ጋሞች ይዞ ጉር አምባ ሲወርድ

ያንጓብባል እንጂ መች ይዋጋል ካሣ

ወርደህ ጥመድበት በሽንብራው ማሳ

እያሉ ያዘፍኑ እንደ ነበር የቴዎድሮስን ታሪክ የጻፉት አለቃ ወልደ ማርያም ይነግሩናል፡፡ ጎሹ እንደ ፎከሩት የሽንብራ ማሳ አልነበረም የገጠማቸው፤ እንደ አንበሳ የሚደቁስ የካሣ ክንድ እንጂ፡፡ በጦርነቱ ቆስለው ወዲያው ነበር ጎሹ የሞቱት፡፡

ይህንን የሰሙት ራስ ዐሊ አሁንም ንቀት አልለቀቃቸውም፡፡ ካሣ የሚባል ጀግና ሊዋጥላቸው አልቻለም፡፡ ከእውኑ ዓለም ይልቅ የሕልሙን ዓለም መርጠው «እኔ ለካሣ ጦር አልጭንም» ብለው በሦስት መኳንንት የተመራ ጦር ጎርጎራ ሰደዱ፡፡ ሚያዝያ 5 ቀን 1853 እኤአ ይህ ጦር በካሣ ሠራዊት ድባቅ ተመታ፡፡ ራስ ዐሊም ጭንቅ ውስጥ ገቡ፡፡ «ጦር አልጭንም» ማለት ትተው ካሣን አይቀጡ ቅጣት ሊቀጡ ሰኔ 23 ቀን 1845 ዓም አንድ መቶ ሺ ጦር ይዘው ጎርጎራ ወረዱ፡፡ የካሣን ጦር በመነጥራቸው አዩና «ሠርገኛ እንዳንለው በዛ፣ ጦረኛ እንዳንለው አነሰ» ብለው ዘበቱ፡፡

አይሻል ላይ የተደረገው ውጊያ እሳት እና ጭድ ሆኖ መቶ ሺው የዐሊ ሠራዊት በካሣ እጅ ተደቆሰ፡፡ ዐሊ ያልጠረጠሩት ሆነ፣ ያልገመቱት ደረሰ፤ ሊቀበሉት ያልፈለጉትን መራራ እውነት መዋጥ ጀመሩ፡፡ በመጨረሻዋ ሰዓት «ይህ በትር የእግዚአብሔር ነው እንጂ የሰው አይደለም» ብለው ራስ ዐሊ በየጁ አልፈው ራያ ወሰን ገብተው በዚያው ሞቱ፡፡

በመጨረሻ የቀሩት ደጃዝማች ውቤ «ቀን ደርሷል አምባ ፈርሷል» ይግቡ የሚል መልእክት ከካሣ መጣላቸው፡፡ ለአንድ የኮሶ ሻጭ ልጅ መግባት መደፈር ነው፡፡ ደጃች ውቤ «ምንኛ የጠገበ ነው አያ» ብለው ጦር አስከተቱ፡፡ ካሣን ገድለው ወይንም ማርከው ደረስጌ ላይ ሲነግሡ እየታያቸው ውቤ ገሠገሡ፡፡

የካቲት 3 ቀን 1847 ዓም ደረስጌ አጠገብ በተደረገው ውጊያ ውቤ ቆስለው ተማረኩ፡፡ በቴዎድሮስ እጅም ገቡ፡፡ መሳፍንቱ ሳይጠረጥሩ ዘመነ መሳፍንት አለቀ፡፡ መሳፍንቱ ሁሉ ዘመነ መሳፍንት ማለቁን የተረዱት ሁሉም ሲቆስሉ እና ሲማረኩ ነበር፡፡

«ቀን ሲደርስ አምባ ሲፈርስ መመለሻ የለውም» እንዲሉ በናቋቸው ካሣ ሁሉም ተረትተው ታሪክ ሆነው ቀሩ፡፡

ሆስኒ ሙባረክ የዛሬ ሃያ ቀን አካባቢ ግብፃውያን ወደ ጣሂር አደባባይ ሲወጡ ከጩኸት ያለፈ ነገር ይመጣል ብለው አልጠበቁም ነበር፡፡ ብርዱ ሲለበልበው፣ ሆዱ ሲሞረሙረው ወደ ቤቱ ይገባል ብለው ሕዝቡን ንቀውት ነበር፡፡ ቀን መድረሱን አምባ መፍረሱን መጠርጠር አልቻሉም፡፡

ውኃ በመርጨት፣ አንዳንዶቹን በማሠር፣ ትዊተር እና ፌስ ቡክ በመዝጋት፣ የሳተላይት ቴሌቭዥኖችን በማስተጓጎል፣ ጋዜጠኞችን በማንገላታት፣ ደጋፊዎቻቸውን በኃይል በማሠማራት ችግሩን በቀላሉ እፈታዋለሁ ብለው ገመቱ፡፡ እልፍ ሲልም የጉልቻ መለዋወጥ የመሰለ የሥልጣን ለውጥ አምጥተው ያላችሁትን ፈጽሜያለሁ ለማለት ሞከሩ፡፡ ሕዝቡ እርሳቸውን እየተቃወመ «የካቢኔ አባላቱ ስለ በደሉት እንጂ እኔንማ ሕዝቡ ይወደኛል» ይሉ ነበር፡፡

ያ ጣሂር አደባባይ የወጣ በሚሊዮን የሚቆጠር ሕዝብ ለእርሳቸው መወድስ ሊያቀርብ፣ ለዋሉለት ውለታም ሊያመሰግን፣ ለአመራራቸው ያለውንም አክብሮት ሊገልጥ የወጣ መሰላቸው፡፡ ሕዝቡ ማምረሩን፣ አንጀቱ መቃጠሉን፣ ቋቅ ብሎት አንገሽግሾት መውጣቱን መገመት አልቻሉም፡፡

ሕዝቡ «ይውረዱ» ሲላቸው እርሳቸው ስለ ልጃቸው ያወራሉ፡፡ ሕዝቡ «ይውረዱ» ሲላቸው እርሳቸው ስለ መስከረም ምርጫ ይደሰኩራሉ፤ ሕዝቡ «ይውረዱ» ሲላቸው እርሳቸው በቴሌቭዥን ቀርበው ምዕራባውያንን ይሳደባሉ፤ ጋዜጠኞችን ይኮንናሉ፡፡ ሕዝቡ «ይውረዱ» እያላቸው እርሳቸው «እኔ ከወረድኩማ ግብፅ አበቃላት» ይላሉ፡፡ ቀን መድረሱን አምባ መፍረሱን ማየት አልቻሉም፡፡

እርሳቸው በጦር ኃይል ነው የመጡት፤ ራሳቸውም ወታደር ናቸው፡፡ አገዛዛቸውም ወታደራዊ ነው፡፡ ጦር የሌለው ሕዝብ አደባባይ ቢውል ቢያድር፣ ቢራብ ቢበላ፣ ቢጮኽ ቢያቅራራ፣ ዳስ ቢጥል መፈክር ቢሰቅል፤ ቢሰለፍ ቢለፈልፍ ምን ያመጣል? ደግሞ ከመቼ ወዲህ በጩኸት መንግሥት ተቀይሮ ያውቃል? ሙባረክ ያነበቡት መጽሐፍ እንዲህ አይልም፡፡

እንዲያውም በመጨረሻ «እኔኮ እወድዳችኋለሁ» ብለው የዓመቱን ታላቅ ቀልድ ቀለዱ፡፡ ምክትላቸውም ብቅ ብለው «የሳተላይት ቴሌቭዥን አትዩ፤ እነርሱ ናቸው የሚያታልሏችሁ» ብለው በአሥር ዓመታት ውስጥ ተገኝቶ የማያውቅ ምክር ሕዝቡን መከሩ፡፡

«አልወርድም» አሉ ሙባረክ፡፡ ስዕለት ያለባቸው ይመስል ከመስከረም ወዲህ ወይ ፍንክች አሉ፡፡ ሕዝቡ ደግሞ ከጣሂር አደባባይ ወይ ፍንክች አለ፡፡ የሚያዩት ነገር እውነት ሳይመስላቸው፤ የናቁት ሕዝብ እየገነገነ መምጣቱ ሳይገለጥላቸው፤ ሰባት ወር የቀረውን መስከረም ሕዝቡ አሳጠረውና ሙባረክ ወረዱ፡፡

እኔ እንጃ፤ አሁን ራሱ ሲያስቡት «በሕልሜ ነው፣ ወይስ በውኔ፣ ወይስ በቴሌቭዥን» እያሉ ሳይቃዡ አይቀሩም፡፡ ከሳምንት በፊት እንኳን አሁን የሆነው ነገር ሊሆን ይችላል ብለው ቅንጣት ያህል ጥርጣሬ አልነበራቸውም፡፡ ጦር ጭነው ያገኙትን መንበር ጦር ያልጫነ ያስለቅቀኛል ብለው እንኳን በታሪክ በተረት አስበውት አያውቁም፡፡ ግን

መናቅን የመሰለ የመሪዎች ክፉ በሽታ የለም፡፡ ቀን ከደረሰ፣ አምባ ከፈረሰ የተናቀው ተነሥቶ መሳፍንቱን ሁሉ ነድቶ ጎንደር ቤተ መንግሥት ይገባል፡፡ ቀን ከደረሰ፣ አምባ ከፈረሰ፣ የበጎች እረኛ ሙሴ እሥራኤልን እየመራ የኤርትራን ባሕር ያሻግራል፡፡ ቀን ከደረሰ፣ አምባ ከፈረሰ አገር ያንቀጠቀጠ ፈርዖን ባሕር ውስጥ ይወድቃል፡፡ ቀን ከደረሰ፣ አምባ ከፈረሰ ትንኝ ዝሆንን፣ ቁንጫም አንበሳን ትረታለች፡፡

ቀን ሲደርስ፣ አምባ ሲፈርስ በፈቃድ ያልሆነ በግዳጅ ይሆናል፤ እንደ ደጃች ወንድይራድ ኮሶ ያስጠጣል፤ እንደ እቴጌ መነን ባቄላ ያስፈጫል፤ እንደ ሙባረክ የሠላሳ ዓመት ቤት ጥሎ ያስኬዳል፡፡

ምናለ የአፍሪካ እና የዓረቡ ዓለም መሪዎች ዛሬ እንኳን ቢነቁ፡፡ ቀን እየደረሰ አምባ እየፈረሰ እኮ ነው፡፡

8 comments:

Anonymous said...

SO WHAT EXACTEDLY WOULD BE THE STEPS YOU WOULD LIKE TO SEE THE PEOPLE TAKE ANY SMALL CHANGE THAT THE AVERAGE READE COULD DO.???? "p"

Anonymous said...

From the Editor
Remember the reason why TPLF is still murdering, torturing citizens and ruining and repressing press rights and selling vast lands of the country to Arabs, Indians, Chinese, Americans … political opposition leaders have reached their decadent stage (Besbisewal) and they stink. You get sick when you smell the stink for 19 years. The opposition press in Addis namely Awramba and the like still are promoting the stinking leaders to the mass by highlighting under the title “who said what as if they are Jesus of Ethiopia”. The very first think readers should take steps is to throw out these stinks from their leadership and refuse to give them media coverage so that they will not spoiled the air with their decadent stink. Debridement is the medical word to clean the stink and the useless dead dry part of the body. Africa experienced decadent political leadership after colonialists left the continent (though they are still there even worst under TPLF’s Ethiopia) and still Africa experienced the decadent political leadership even worse than ever. The decadent political leadership is an amoeba in the opposition, and in the government. Both stinks! Let me give you one example that how the opposition stinks and what each of you need to do first before talking big issue. Let me give you one simple example how educated individuals like Roble Ababiya (who is regular contributor on Ethio Media/Ethio Forum’/ECADEF, Abugida….. and the prominent economist Seid Hassan and their likes write about young Oromiya Republic advocate Jawar Mohamed- some of them calls him “Patriotic Ethiopian” some of them like Robele Ababiya explanation to praise Jawar refer like this “ a young politician with considerable potential to tackle problems logically on the basis of true history of our ancient country, Ethiopia.” I have explained to all of you why I can’t accept such silly stinking praising anti Ethiopian elements (Read the Tricky Smile of Jawar Mohammed by Getachew Reda). Unless the opposition know their enemy and know with whom they are sleeping- they can) t change the politics of our country if they continue sleeping with enemies. The first thing to do is avoid flirting and sleeping with enemies. The rest will go on from there. The current politics going on by the opposition is multiple deficiencies. The so called free press in the country still stinks the same as the opposition. They too need to wake up and stay away from praising and giving propaganda to the failed and toothless opposition depicting them as Tigers and lions.The avarage reader could do is cahalange the dealers inside politics before any thing (before they stink). Getachew Reda editor Ethiopian Semay

Anonymous said...

Really but Dictators are blined
mind & dormant, they can't learn from the envirnmont.
just feeding like grasshopers

Anonymous said...

which dictators and how do you address them. who is tO start the revolution. how many can reaD AND TAKE ACTION.

Anonymous said...

which dictators and how do you address them. who is tO start the revolution. how many can reaD AND TAKE ACTION.

Anonymous said...

which dictators and how do you address them. who is tO start the revolution. how many can reaD AND TAKE ACTION.

Anonymous said...

From Getachew
The robbed, oppressed and stripped. Who do you think started the revolution of 1974? Who do you think strated the revolution in 1997 that resulted with the killing of over 200 protesters by the TPLF dead Squad on which TPLF leader said “ we did it because our soldiers are not trained how to handle demonstrators and lack tools or gas tears to handle it easily without murdering”. Here you got a dictator. Can you see who the dictator? You must be in hell heaven if you can’t see a dictator in Ethiopia. Denial is what most of the puppets’ sickness. Once a puppet is set to deny events- he/she is set not to see or hear. This remind me a puppet called w/o or w/it SHASHU HABTU and BERHANU (Aba Mela TPLF’s given nick name) both chair woman and vice chairman of the Woyane net work for Peace and Development group (infect I have mentioned both of them o my upcoming new book). If you think there is no oppressed you are out of your mind, if you think there is no abused society you are out of your mind. If there is then there is a tyrant/dictator. When will your dictator remove out of power- it has its own day of chasing. Nothing stays strong as its youth. When it gets decadent the tooth comes loose and fall with little shake. Then will the Visa and the Passport buyers will have long line in a hurry as Meles and his crony were hiding in DebreZeit. Remember that? I don’t know if Azeb will also have time to take her expensive fashioned closes with here when that rush comes to reality. Above all we don’t expect the set minded puppets to change. every minute of our life change takes place, even though it is complex mater for our mind and eye to understand it. Getachew Reda

Anonymous said...

Mr Getachew, what does it mean 'ከዲዳክ', who is he. I think you have to give credit for the writer of this Article, only posting is not good. You should give us the sources correctly, and what does those highlighted words by you. what do you went to convey to us? if you want to make a critic, please let us know. Otherwise, i completely lost about what you did!