Saturday, July 26, 2014

አንዳርጋቸው/ግንቦት 7/ ባንዳ ነው አይደለም? አንዳርጋቸው/ግንቦት 7/ ባንዳ ነው አይደለም?



አንዳርጋቸው/ግንቦት 7/ ባንዳ ነው አይደለም?


አንዳርጋቸው/ግንቦት 7/ ባንዳ ነው አይደለም?


ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያን ሰማይ አዘጋጅ)

አቶ ተድላ ትናንት ማታ Where is Ethiopian Character, Andargatchew Tsige is not Banda !!!” በሚል ርዐስ በስሞታ ተቃውሞውን ለEthiopatriots.com አዘጋጅ ወቀሳውን ሲገልጽ፤ ለኔም ሁኔታው ባይገባኝም በግልባጭ “ፎርወርድ” ያደረገልኝን ተመለክቼዋለሁ። እንዲህ ይላል፦

(“For sometimes I did challenge the editor of "ethiopatriot" to remove "Bekumu Yemote" photo of  Dr.Birhanu carrying a donkey on his shoulder. Ethiopatriots as the name attests  should be a "patriot" website not "anti Ethiopian".

Ethiopians are known all over the world by their fairness towards humanity. We have Ethiopian value. We even go to the burial of our mortal enemy. When someone is in trouble we are not going to add more trouble. We have a saying, "LeWedeke Zaf Misar Yebezabetale"………. I am really troubled by www.ethiopatriots.com Andargatchew and Birhanu "Banda T Shirt" still posted to welcome readers. Where is the Ethiopian character ???........ You do not need to support the G7 Movement but you need to hear the voice of Ethiopians all over the word. Andargatchew Tsige for whatever flaws he might have is not Banda. ) ይላል።

የግንቦት 7 አመራሮች እና የፓልቶክ/ድረገጽ ጀሌዎቻቸው፤ አንዲሁም ኢሳት የተባለው የግንቦት 7 የፕሮፓጋንዳ ማሰራጫው ክፍል “ኤርትራን እና ስርዓቷ፤ መሪዋን እና ስብእናውን እያሞገሱ፤” ኢትዮጵያን በሚያንኳስስ መልኩ ለኤርትራኖች በመወከል፤ ፀረ ኢትዮጵያ ፕሮፓጋንዳ ሲያስተጋቡ በዩቱብ ተቀርፆ የተዘገበ ማሕደር ነው። ስለዚህም “ሳይልኳቸው ወዴት፤ሳይጠሯቸው አቤት” የሆኑ ስለ ጠላቶቻችን የሚሳሱ “ቡት ሊኪንግ” ስብስቦች ናቸው።


ኤርትራ ለኛ (ለኔ ልበል) እጅግ አደገኛ ጠላት አንጂ “ወዳጅ” የሚል ቃል የሚጠቀሙት የግንቦት 7 መሪዎች እና የኦነጐች ማጃጃያ ቃል በኔ ዘንድ ቦታ አንደሌለው ግልጽ ልሆንላችሁ እፈልጋለሁ። ለወደፊቱም ቢሆን ኤርትራኖች እኛ ያቀረብነውን “ዴማንድ/የይገባኛል/ ሉአላዊ ጥያቄዎቻችን ካላከበሩ “ኢትዮ -ኤርትራ” በሚል የየዋሃን “ወንድማማች” ስብስብ ማሕበሮች ወይንም  የግንቦት 7 መሪዎች እና “ጸረ ትግሬ” የፓልቶክ ጀሌ ወጣቶቻቸው ወይንም “የፖለቲካ ተቃዋሚ ነን በሚሉ ዛሬ የምናያቸው አዲስ አበባ ያሉትን “ዲፕሎማት ተቃዋሚዎች” ሳይሆን ፤ “በጉዞ ሂደት” በሚወለዱ በቆራጥ ጀግኖች ኢትዮጵያዊያን ወጣቶች መሪነት በሚቋቋም “ኢትዮጵያዊ መንግሥት” “አዲስ ጦሪነት”  በመክፈት ኤርትራን “በማንበርከክ” አስገድዶ’ “የይገበኛል ሉአላዊ ጥያቄአችንን” እንደሚያስከብሩ ባንዳዎች አንዲያውቁት፤ ይህ ትንቢት በልቦናቸው እንደይዙት “ከሻዕቢያ እና መሰል ኤርትራኖቹ” ጋር ሆነው የሚያፌዙብን ባንዳዎች ሁሉ ተዋጊው ብዕራችን አንደማይተኛላቸው፤ በዚህ አጋጣሚ ይወቁት። ስለ ኤርትራ የሚሳሳ አንጀት ላላቸው ኢትዮጵያዊያን ጀሌዎቻቸው መምከር የምፈልገው ነገር፤ ከእኛ በላይ ስለማታውቋቸው፤ በማታውቁት ሥራ ገብታችሁ እያዳመጥናችሁ ካለው “ሳይጠሯችሁ አቤት፤ ሳይልኩዋችሁ ወዴት” ባሕሪያችሁ ተቆጠቡ። ከባለቤቱ ያወቀ ቡዳ አትሁኑ። ተረጋጉ!

ለኤርትራ ባንዳዎች የሚራሩ ቃላቶች ከሻዕቢያ እና ከወያኔ እየተቀበሉ “ወዳጆች ነን፤ጎረቤታሞች ነን” የሚሉ “ኤርትራኖች እና  ወያኔዎች ሲያሾሩብን” የፈጠሯቸው ስልታዊ ቃላቶች ኢትዮጵያዊያን ነን የምትሉ ወገኖች አነኚህ ቃላቶች ከጠቀም አንዲቆጠቡ ኣሳስባለሁ። ኤርትራኖች እና ወያኔዎች አነኚህ ቃላቶች ለምን አንደሚጠቀሙባቸው እና ‘ኢትዮጵያዊያንም አነዚህ ቃለቶች አንዲለማመዱዋቸው” በማድረግ ላይ የሚያደርጉት ይህ የረቀቀ ተንኮል፡ “ከአርበኞች እና አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን ወጣቶች” ለወደፊቱ ወደ ኤርትራ ለመነጣጠር አድብቶ እየጠበቃቸው ያለው “ቀስት” አደገኛ መሆኑን ስለሚያውቁ (ኢሳያስ ይህንን ቀስት ይፈራዋል፤ለዚህ ነው ወጣቱ ሳዋ እየወሰደ እያሰለቻቸው የሚገኘው) እነኚህ የ “ማጃጃያ” የጠላት ስልታዊ ቃላቶች “ኢትዮጵያዊያን” ከመጠቀም አንዲርቁ አሳስባለሁ። ብዙ ያልተወራረደ ሂሳብ ስላለን ፤ ሂሳባችን እስክናወራርድ፤ድረስ የኤርትራ ጨው እንደለመደች ወደል ላም ምላሳችሁ ከመዘልዘል ተቆጠቡ።

ከላይ “ሊያልፍ ኰት ለብሶ ቆሞ የሚታየው ወጣት ኢትዮጵያን ለማጥፋት ኮሚኒስት ቻይና ለስልጣና በሄደበት ወቅት ነው”ድሮም አሁንም በጠላትነት ቆሟል።።

አሁን ወደ አቶ ተድላ አስፋው አስተያየት።

ወንድም አቶ ተድላ አስፋው ለኢትዮፓትርዮትስ. ካም አዘጋጆች  በሚመለከት፤ አዘጋጆቹ ስለ አንዳርጋቸው እና ስለ ብርሃኑ ነጋ አህያ በጀርባቸው ተሸክመው ‘ባንዳ’/በቁሙ የሞተ…. የለጠፉላቸው “ፓለቲካል ካርቱን” ቅሬታውን ለመግለጽ ዋናውን አቤቱታ ለነሱ ሲልክ ለምን በግልባጭ ለኔ አንደላከልኝ ባይገባኝም፤ ብርሃኑ አህያ በጀርባው ተሸክሞ መታየቱ የፖለቲካ ካርቱኒስቶቹ ለምን በዚያ ሁኔታ ሊያሳዩት አንደፈለጉ የፖለቲካ ካረቱኒሰቶች መነሻ ስለሚኖራቸው ተድላ አስፋው ትርጉሙ ካልገባው ማብራሪያ ይሰጡት ይሆናል። ስለ አንዳርጋቸው ጽጌ ባንዳነት እና ስለ ኢትዮጵያ ጨዋነት አንስቶ ስለሚያሰማው አቤቱታ ሃሳብ አንዳለኝ ለማወቅ ከሆነ፤ ትንሽ ልበል።በዚህ አረፍተ ነገር ልጅምር።

Ethiopians are known all over the world by their fairness towards humanity. We have Ethiopian value. We even go to the burial of our mortal enemy. Where is Ethiopian Character?” አቶ ተድላ ለመለስ ዜናዊ የሙት መታሰቢያ ፀሎት ለማድረግ ወዳጆቹ አሜሪካኖች፤እና የመሳሰሉ ትልልቅ የውጭ አምባሳደሮች በተገኙበት በአቢሲኒያ ዋሺንግተን ቤ/ክርስትያን ቅጥር ግቢ ሲታሰብ፤ አቶ ተድላ ደጅ ሆነው ፀሎቱ ተገቢ እንዳልሆነ መቃወማቸው አቶ ተድላ አይስቱትም። እኔ ለምን ተቃወሙ አልልም፤ መቃወም አይደለም መለስ በመሞቱ ምን እንደዘገብኩ ሁሉም የሚያውቀው ስለሆነ ለመስ አዛኝ እንዳልሆንኩ የዘገብኩትን መለስ ብሎ ፋይሉን ማንበብ ነው። ሆኖም፤ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት አስመልክተው ኢትዮፓትርዮትን “Ethiopians are known all over the world by their fairness towards humanity. We have Ethiopian value. We even go to the burial of our mortal enemy.” ብለው “ኢትዮጵያን ቫሊዩ” የሚሉትን ኢትዮጵያዊ ወደ ጠላቱ የቀብርም የፀሎትም ቦታ ሄዶ ሀዘኑን የሚገልጽ ሕብረተሰብ መሆኑን ካወቁ አቶ ተድላ አስፋው እንደ “ጠላት እና ባንዳ” የሚመለከቱትን የመለስ ዜናዊ የሙት ጸሎት ስነስርዓት በተከበረበት ኢቢሲኒያ ቤተክርስትያን ድረስ ሄደው “ለዚህ እርኩስ “የማማለጃ- ፀሎት” አያስፈልገውም” ብለው ለምን ተቃዉሞ እና ጩሆትዎን አሰሙ? We even go to the burial of our mortal enemy.” ብለው ኢትዮጵያዊ “ቫሊዩ” የሚሉትን እርስዎ ሲያከብሩት አላየንም። ታዲያ በኢትዮፓትርዮትስ ጀርባ ላይ ሚዛን ያጣ አለንጋዎን ለማስጮህ ለምን ከጀሉ?  

 እስኪ ከእርስዎ ወደ አንዳርጋቸው ልመልሰዎት። ይሄ ጥያቄ አስቀድሞ መጠየቅ የነበረበት በኢትዮጵያዊ ጨዋነት እና ሰብአዊነት ልብ ለተሞላው “ኢትዮጵያዊ ቫሊዩ” ያውቅ ነበር ብለው ለሚከራከሩለት (ኢትዮጵያዊ ስነምግባር/ቫልዩ ከሚያከብሩት ኢትዮጵያዊ ነበር ብለው ከሆነ መላት ነው) ለአንዳርጋቸው ጽጌ መቅረብ የነበረበት ጥያቄ ነበር። ወደ እራሱ አንደበት ልውሰደዎት፦ አንዳርጋቸው ጽጌ ተድላ አስፋው የሚያደንቀውን የአንዳርጋቸው ኢትጵያዊ ጨዋነት እና ሰብአዊነት አንዳርጋቸው በራሱ አንደበት በድሮ ወዳጁ የሗላ ጠላቱ በመለስ ዜናዊ ላይ ምን ሲል ነበር? ፦

“መለስ ሚባል ሰው፤ከተቀበረበት ሥላሴ ቤተክርስትያን ወጥቶ፤መንገድ ላይ አንዲወረወር ነው ያደረገው የኢትዮጵያ ሕዝብ” ይላል አንዳርጋቸው ጽጌ ለሕዝብ ያስሰማው የቀድሞ በዩቱብ የተለጠፈው ንግግሩ። አቶ ተድላ አስፋው በኢትዮፓትርዮትስ ድረገጽ ስለ አንዳርጋቸው የተለጠፈውን ካርቱን አለመደሰቱን ሲገልጽ፤ አንዳርጋቸው “የኢትዮጵያ ሕዝብ ከጨዋነቱ ወጥቶ ሬሳን ከሥላሴ ቤተክረስትያን መቃብር ቆፍሮ አውጥቶ መንገድ ላይ እስከመጣል የደረሰ ሕዝብ ነው”  እያለ የኢትዮጵያን ሕዝብ  “የሕዝብ ሞራላዊ ስነ ምግባር” በዓለም ፊት ሬሳ ከመቃብር ቆፍሮ መንገድ ላይ የሚጥል አረመኔ ሕዝብ ነው እያለ በሃሰት ሲያጎድፍ እና ሲዳፈር አቶ ተድላ ምን አሉ? አቶ ተድላ! ምነዋ ለዚያ ሕዝባዊ ኤቲከስ የሚያጎድፍ ጽያፍ ንግግር ሲሰነዝር ያኔ ምነዋ ዝም አሉት? የኢትዮጵያን ሕዝባዊ ቫሊዩ በአረመኔነት የሚከስ ሰው እና ቡድን የሰማሁ በኢሳያስ አፈወርቂ እና በጽንፈኛ ኤርትራኖች ምላስ ካልሆነ እንዲህ ያለ ድፍርት ሰምቼ አላውቅም።ምናልባትም እንዲያ ያለ አንደበት እዛው ኤርትራኖች ጋር እያለ የቀሰመው ተላላፊ የምላስ ባሕሪ ሊሆን ይችላል። ሕዝቡ ለመለስም አልቅሷል፤ ውጭ ያለው ተቃዋሚም ለአንዳርጋቸው አልቅሷል። ድንጉጥ ባሕል/ቫለዩ ይሁን ወይንም ለሁለቱም ወግኖ ይሁን ፤ ብቻ ሕዝቡ አዝኗል፤ “ለሁለቱም አልቅሷል፤አዝኗል!” ጉደኛ አንጀት! “ለአራጁም ለአሳሪውም ለሚዋሸውም፤ ለሚየስገነጥለውም፤ ለሚዶልትለትም፤ ለሚያጃጅለውም- ለሁሉም የማንጨበጭብ ልምድ እና አዛኝ እጅ! ለሁሉም የሚያለቅስ አንጀት ያለው ወርቅ ሕዝብ የት ይገኛል?! ነገ ኢሳያስ ወይንም አቦይ ስብሓት፤ ወይ በረከት ስሞን ቢሞቱ ያለቅስ ይሆን? ማን ያውቃል፡ ለመስ ካለቀሰ ለምን ለኢሳያስ አያለቅስም። ሁሉም ጠላቶቹ ናቸው። ለትርጉም የማያበጅ “ብሽቅ አንጀት!”

አቶ ተድላ አስፋው “We have Ethiopian value. We even go to the burial of our mortal enemy. Where is Ethiopian Character?” ብለው መጠየቅ የነበረበዎት ግየንቦት 7 አመራሩን ነው። ይህነን ለማድመጥ The Two Faces of Andargachew Tsige http://youtu.be/0VrFHs4GPvg ያድምጡ። እስኪ የተናገረው “ቫሊዩ” ወደ አንግሊዝኛ ይተርጉመት፡ ለፈረንጅ አድማጩ ምን ስሜት አንደሚሰጥ ንገሩን። እንዴት ነው ሞኞች እያረጋችሁን ለመቀጠል የምትፈልጉት? ፖለቲካውን ያለ እናንተ እኛ አንከታተልም እየመሰላችሁ ነው? አንደ ቂሉ ማሞ ብርሃኑ ትከሻ ላይ የተሰቀለው ወደል አህያ አይተው አንዲህ ያንጣጣዎ ምንድ ነው? ከሰይጣንም ፤ ከአልሸባብም ቢሆን ዕርዳታ ከሰጠን አንቀበላለን የሚሉት ግንቦት 7 መሪዎች “አህያ በትከሻቸው ላይ መጫኑ” ምን ያስከፋቸዋል?


አቶ ተድላ አስፋው፤ በመቀጠል፦ “Andargatchew Tsige for whatever flaws he might have is not Banda.” ይላል። ጽቡቕ! እስኪ ገፋ አድርገን ወደ ሗላ የገዛ እራስዎን ጽሑፍ አንዴ ጎራ ብለን አንቃኘው? Ginbot 7 has been on news recently after Dr.Birhanu’s leaked “embarrassing” audio and the interview Ato Andargatchew gave on ESAT this month. (Dr. Birhanu should apologize for the public (Tedla Asfaw) September 19, 2013 ) ብለው በጻፉት እንጀምር። “ኤምባረሲንግ” ብለው የሰየሙት የብርሃኑ ምስጢራዊ አውድዮ የስልክ ንግግር ተጠልፎ ለሕዝብ ይፋ የሆነውን ምስጢራዊው ሰነድን ነው። ለምንድነው ኢምባረሲነግ ብለው አቶ ተድላ የሰየሙት? መቸም ፖለቲካ ውስጥ የሚያሳፍር ነገር የባንዳ ስራ ነው እና የባንዳ ሥራ ነው ማለታቸው አንደሆነ እገምታለሁ ! አቶ ተድላ ይህንን አሳፋሪ ገበና ያሉትን እንዲህ ሲሉ አብራርተውት ነበር፤-

Dr. Birhanu has a budget of 500,000 dollar from bankrupt Eritrea. The budget is used for Ginbot 7 and also for ESAT. Most of us believed that ESAT has nothing to do with Ginbot 7, that is now history, Ginbot 7 owns ESAT.” እስኪ ይህነን ዘርዘር እናድርገው.
አንዳርጋቸው ችግር ውስጥ እያለ ለምን ይህንን ታሪኩን ትናገራላችሁ ካልተባልን በቀር ፤ መሪ ነበር እና ታሪኩን መነገር ያስፈልጋል። በጐ ጎኑን እናንተ ንገሩን (ደሞ ከሚገባ በላይ እየተተረከ ነው)፤ ሸካራ ጐኑ ደግሞ እኛ እንናገርለት። ሸካራ ጐን ከቤተሰብ እና ከወዳጅ አይጠበቅም። ከታዛቢ እንጂ። አንዳርጋቸው በመያዙ ግን ስለ ተደሰትን ሆኖ መተርጎመ የለበትም። እያወራን ያለነው “ፖለቲካ/ትግል ነው”። አፋችሁ ክደኑ “ሃሽ ሃሽ” ከሆነማ ፖቲካ ሳይሆን እየታገልን ያለነው የእግር ኳስ ጨዋታ ነው ማለት ነው። አንዳርጋቸው ድሮ የወያኔ  ሗላ ደግሞ የሻዕቢያ “ሳይለኩት ወዴት፤ ሳይጠሩት ምን ልናገር  አቤት!”  ነው የምንልበት ብዙ ምክንያቶች አሉ። አብዛኛዎቹ ለማወቅ በብዙ ጸሐፍት ስለተዘረዘሩ አልደግመውም። የቅርቡ እንኳ ብንመለከት፤ አንዳርጋቸው ከሚያደንቀው እና ከሚያሞግሰው
ከሻዕቢያው መሪ ኢሳያስ እና ተስፋዬ ገብራብ ጋር አስመራ በነበረበት ወቅት (ለግንቦት 7 እና ኢሳቶች ኢሳያስ ወዳጃችን ነው የሚሉን። አንደ ዜና ማዕከልም በኢሳያስ የሚዶጐም ስለሆነ፤ ስለ ኢሳያስ መጥፎ ሥርዓት አንዲት ቃል ማውራት የተከለከለ ነው! ይኼ ደግሞ አንደ ሚዲያ ሃላፊነቱን ዘነግቶ ለግለሰብ/ላንድ ንጉሥ አሽከርነት ከማደር የተለየ አያደርገውም።)  በአፍሪቃ ውስጥ ያልታዬ ድንቅ መሪ ሲል ፤ በኢሳያስ ዱጐማ የሚተዳዳረው የግንቦት 7 በኢሳት ቲቪ ቀርቦ ምን እንዳለ ማስታወሱ ጠቃሚ ነው። የጥቁሮች መሪ ነበረው  “ማልካም ኤከስ”  እንደሚለው “በሃውስ ኔገር“ አንደበት በወረደ መልኩ አንዲህ ይላል፡

“የፕረዚዳንቱ ልጆች ዩኒቨርሲቲ ፈተና መግባት አቅቷቸው በቂ ውጤት ስላላገኙ፤አንደ ማንኛውም ኤርትራዊ $10.00 (አስር ዶላር) በወር እያገኙ ነው አገልግሎት የሚሰጡት።” ሲሳይ አገና እንዲህ ሲል አንዳርጋቸውን መልሶ ይጠይቃል፦
“ልጆቹ ውጭ አገር ሄደው ተምረው አያውቁም”? አንድም ልጅ አንኳን ፈረንጅ አገር ሄዶ ለመማር ቀርቶ ሱዳንንም አያውቅም”።”ሦስቱም ሳዋ በረሃ ሳዋ ነው የተማሩት….”
አንዳርጋቸው ስለ ኤርትራ ቅንጣት ነገር አያውቅም። አብርሃም የተባለው ትልቁ ልጁ “የኤርትራን አየር ሃይሉ ክፍል ባይነ ጥላ መስርያቤት ተሰጥቶት ባቱን ወክሎ የሚከታተለው እሱ ነው። በአባቱ ላይ ክጀላ እየተደረገ ስለመጣ፤ እሱን እዛው መድቦታል።” አንዳርጋቸው አንዳለው ልጁ $10.00 ዶላር ወይንም 30 ዶላር ወይንም 500.00 ናቕፋ የሚያገኝ ሳይሆን ልጁ ጥጋበኛ እና የፋብሪካዎች ሃላፊ ሆኖ በየቦታው በመዞር የአባቱን ሥርዓት እንዴት አንደሚረከብ በልምምድ ላይ ነው (አስተዳደሩምንም ሳይቀር በመቆጣጠር ሥርዓቱን እየተለማመደው ነው።። ታሪኩ ባጭሩ ላቅርብ፡ 
ልጁ አንኳን አውሮጳ ሱዳንም አያውቀውም ሲል አንዳርጋቸው በእርግጠኛነት እንደ አሳዳጊው ተከራክሯል። አንኳን የኢሳያስ ልጅ፤ የሥርዓቱ አገልጋይ ባለሥልጣኖች ልጆች ዓለምን ዞረዋል። አንዳንዱ ውጭ ይማራሉ። ቀልድ ነው።፡ የየማነ ማንኪ ባለቤት እና ልጆች ሁሉ የሚኖሩት ካናዳ ውስጥ ነው። (ያውም እኾ የኤርትራ ባለሥልጣኖች መቀመጫው ከተቀዳደደ ባረጀ የድሮ ፊያት ነው የሚጓዙት ብሎ ሲል እማ ያስቃል። ረንጅ ሮቨር፤ቢኤም እና መርሰዲስ አንደሚነዱ ከነፎቶግራፋቸው አንድ ቀን እለጥፍላችሗለሁ። ዝገርም እዩ! )።

በእግረመንገዳችን ስለ አብርሃም ኢሳያስ ስለ ልጁ ከተነሳ ይህንን እንፈትሽ።

ኤርትራ ውስጥ፤  ቀጽሪ ኤክስፖ” እየተባለ በሚጠራ የስርዓቱ አሽከሮች ማጃጃያ፤ እስክስታ ማውረጃ፤ የገንዘብ ማመንጫ የሆነ፤ ውጭ አገር የሚኖሩ ደጋፊዎች በየአመቱ የሚፈነጥዙበት ፈስቲቫል አለ። ታዲያ በሐምሌ 2013 (በፈረንጆቹ በኤርትራኖች የዘመን አቆጣጠር)  ማዝናኛዎች እና የከተማ መጠጥ ቤቶች ለፀጥታ እንዲያመች በጊዜ አንዲዘጉ በተደረገበት እና ከተማዋ ጭር ባለችበት ሌሊት ኢሳያስ እና ልጁ አንዲሁም የስርዓቱ አሽከሮች ልጆች እና አንጨብጫቢ ሃብታሞች ብቻ በኤክስፖው እና በመሳሰሉ ትልልቅ ሆቴሎች እየጨፈሩ እየበሉ እየጠጡ በነበረበት በኤክስፖው ቅጥር ግቢ ውስጥ ድንገት  የቶከስ ድምፅ ተሰማ። የፀጥታ ክፍሎቹ ተደናግጡ፡፡ ባካባቢው የነበሩ የሚዝናኑት ወጣቶች በመሰብሰብ ጥያቄ አጥብቀው ማን አንደተኰሰ ካልተናገሩ ችግር አንደሚገጥማቸው ተነገራቸው፡፡ አንድ ከነዛው ወጣቶች በድፍርት “ይህ እማ ካላችሁ  ኣብርሃም ኢሳያስ (የኢሳያስ አፈወርቂ ልጅ) ሽጉጥ አውጥቶ  ወደ ሰማይ ከተኰሰ በሗላ መኪና አስነስቶ ከግቢው ወጥቷል።  ሲል ነገራቸው፡፡ በማግስቱ ወሬው ወደ ከተማው ተዳረሰ። ሕዝቡም ስለ ዜናው በመገረም፤ የመሪዎቻችን ጥጋብ ወደ ልጆቻቸው መተላለፉ ማሳያ አሳዛኝ አጋጣሚ ማየታችን በጣም ይገርማል፡ አንሱን ማን ያስራል?  ኤርትራ አንዲህ የጠገቡ የመሪዎች ልጆች ታፈራለች የሚል ግምት አልነበረንም፤ በማለት በከተማው ውስጥ በሃሜት ውስጥ ለውስጥ መታማት ጀምሮ ነበር። 

 አብርሃም ኢሳያስ የተባለው ይህ በህር ልጁ ባለ ትዳር ነው (የ31 ኣመት ዕድሜ ጎልማሳ ነው)። ማይ ነፍሒ በተባለው ኮለጅ ትምህርቱን በማቋረጥ  አባቱ ወደ በየኩባንያ ህንጻ ሄዶ አስተዳደራዊ ልምድ እንዲቀስም በማድረግ ፤ ለምሳሌ  ሆርን ኮንስትራክሽን (Horn Construction Company) አንዲሰራ ተደርጓል፡፡ ኩባኒያው የሻዕቢያ ሲሆን  በጀነራል ዳሪክቶር ብርጋዴር ጀነራል ጣዓመ ጎይቶም ክንፉመቐለበተባለው ልክስክስ/ኮራፕት የኢሳያስ ቀኝ እጅ የሚመራ ነው። እንዲሁም  የመሳሪያ ተተኳሽ የጥገና ሥራ ሁሉ ልምድ እንዲወስድ ተደርጛል። “አባቱ ድንገት በሞት ወይንም በሕመም /በአደጋ ክፍተት ከታየ፤ የአባቱን ቦታ አንደሚተካ ቦታው እተመቻቸለት እንደሆነ እየተነገረ ነው።

ስለዚህ አቶ አንዳረጋቸው የኢያስ ልጆች ሳዋ ሄደው በ30 ናቕፋ እና በ500.00 ናቕፋ ደሞዝ እያገኙ አንደማንኛውም ድሃ ኤርትራዊ ይኖራሉ ብሎ ማለት “አሳፋሪ ውክልናዊ ንግግር ነው”። ይኼ “ሳይጠሩት አቤት ሳይልኩት ወዴት” የምንለው ወይንም በጣሊያኖቹ አነጋገር “ባንዳነት/ውክልና” ነው። ለመሆኑ አንዳርጋቸው ስለ ኢሳያስ ልጆች፤ ስለ ባለስልጣኖቹ መኪና ረዢም ጊዜ ወስዶ ማውራት ምን ይጠቅማል? እስኪ ስለሚያወራው የሳዋ የትምህርት ተቋም ምን ይመስላል? ቋንቋውን ለማይገባችሁ ለማትከታተሉ የሩቅ ሰዎች፤ “ሳዋ” የሚያፈራቸው ልጆች (YPFDJ የሚላቸው የሥርዓቱ ደጋፊ ወጣቶች) እነኚህን ይመስላሉ። ሁለቱም ግበረሰዶማዊ ሴቶች ናቸው።
YPFDJ Patriotism in Action
 እነህ ግበረሰዶማዊ ሴቶች ነው “ወጣቶች፤ወጣቶች፤ እያለ በመመጻደቅ ሊያቀርብልን የሞከረው”።

 ሌላው ስለ አቶ አንዳርጋቸው “ሳይጠሩት አቤት፤ ሳይልኩት ወዴት” ገላጭነት፦ ስለ ኢሳያስ ተክለ ሰውነት ደግሞ አንዲህ ይላል፡ “በማንኛውም አፍሪካ ውስጥ (በሞተር ሳይክል) ያለአጃቢ የማይሄድ፤ ያለጠባቂ የሚሄድ ፕረዚዳንት የማይታይበት አገር እኔ የማውቀው ኤርትራ ውስጥ ነው።” መንገድ ለመዞር “ፍሬቻ” እያሳየ እንደማንኛውም መንገደኛ ትራፊክ መብራቱን ጠብቆ ነው የሚጓዘው።” ይለናል።
ሲሳይ አገና፤ “ፕረዚዳንቱ መኪና ይዘው እየነዱ መንገድ ላይ ይሄዳሉ?
አንዳርጋቸው፤- “አዎ መኪና ይዘው እየነዱ ይሄዳሉ ።ዛሬ ፤አሁን። በመቶ ሰው የሚቆጠር አቅፎ ያለምንም መሣሪያ ያለ ምንም ጠባቂ ሽማግሌዎቹ ጋራ ተቃቅፎ… መንገድ ላይ ይሄዳል። መሳርያ የያዘ ፖሊስ ወይንም ሰው የማይታይበት ከተማ (አፍሪቃ ውስጥ) አስመራ ብቻ ናት። ” ብሏል እውነታውን በጨው ዓይኑን አጥቦ ልክ አንደ ሻዓብያ ካድሬ በሚመስል መልኩ ሲያስተባባል።
እውነታው ግን እንዲህ ይነበባል
Last year, a plethora of defections of high-ranking military and government officials hit the headlines. The most high-profile defection was that of Ali Abdu in November 2012. Ali held a key post as Minister of Information and had very intimate personal and political ties with Issayas, whom he never challenged. Another notable defection was that of two trustworthy Air Force pilots, Captain Yonas Woldeab and Captain Mekonnen Debesai. In early October 2012, they flew in Eritrea’s only presidential plane to Saudi Arabia and asked for political asylum.” ዓሊ ዓብዶ ማን እንደሆነ ታውቃላችሁ፤ ይህ ነው፤
ዓሊ ዓብዶ (እጁ እኪሱ ላይ ከትቶ ያለው ነው። ሁለቱ ኤሊያስ ክፍሌ እና ስለሺ ጥላሁን ናቸው። ከዚያ ከሕሊናችን ከማይፋቅ፤በጣም ዘግናኝ ከሆነው የኢሳያስ የዘር ማጽዳት ወንጀሉ ወዲያ ኢትየጵያዊያን ወደ እዚህ ጭራቅ አጅ ይነሳሉ ሚል ግምት አልነበረኝም። አጅ መንሳት ብቻ ሳይሆን - የአመቱ ምስጉን ሰብአዊ ሰው ተብሎ በኛ ሰዎች ይሞገሳል የሚል ሕልም አድሮባችሁ ያውቃል? ባንዳ የሚባል ቃል ምን አንደምትተረጉሙት ባላውቅም “ባንዳ” ማለት ይህ ክፉ ባሕሪ ካልገለጸው ምን አንደሚገልጽ አላውቅም። ዓሊ ዓብዶ የኢሳያስ የማስታወቂያ/የዜና ሚኒስትሪ/ሓላፊ እና የሥርዓቱ አፈ ቀላጤ  የነበረ ዛሬ ከድቶተት  “አውስትራሊያ” ጥገኝነት እየጠየቀ ነው። የግንቦት 7 ምስጢር እና የሌሎቹ ጉዶች  በደምብ ስለሚያውቅ- እሱን አግኝቼ ለማነጋገር  እሞክራለሁ (አሁን ባለበት ሁኔታ መረጋጋት ስላላበት እና ፖለቲካውም አስጠልቶኛል ብሎ ለአውስትራሊያ መንግሥት ስላመለከተ በቅርቡ ማግኘት ዕደሉ ቢጠብም  ለወደፊቱ የማግኘት ዕደል ይኖራል የሚል ግምት አለኝ።) በዚህ መልክ፤ ኢሳያስ እና ሕዝቡ ፤ኢሳያስ እና የሥርዓቱ ባለሟሎች አንዳርጋቸው ሊያቆነጃቸው ከሞከረው ስዕል ሰማይ እና ምድር ናቸው። 

ሲሳይ አገና ነገሩ እጅግ ስለሰቀጠጠው እና አውነታው እየተጋጨበት አንደሆነ ስለሚያውቅ፤ አንዲህ ሲል አንዳርጋቸውን ለማረም ይጠይቀዋል፦

“ግን አቶ አንዳርጋቸው፤ ከ…(እውነታው) አንዳይጋጭ። ባለፈው ጊዜ መሳሪያ የያዙ ማስታወቂያ ሚኒስትሩን (ሥርዓቱን ለመቃወም) ይዘውት ነበር። እሱ የተወሰነ የኩርፊያ ምልክት ነው። ያ ……(እንዲህ ባለ) ወታደር ባለበት ከተማ ወስጥ …..

አንዳርጋቸው ሲሳይን በማቋረጥ በጣም አሳፋሪ በሆነ የሥርዓቱን አፈቃላጤነት በሚያስብል  እንዲህ ይላል፡

“ዌል ሁኔታውን እናንተ ይህንን በተመለከተ የደረሳችሁበት ጥናት ምን ያህል እንደሆነ አላውቅም፤ ግን እዛ ላይ የመጡ ወታደሮች ፤የመጡበትን ምክንያት ተነግሯቸዋል።መንግሥት ወድቋል ተብለው ያመጧቸው ወታደሮች ናቸው።….”

ሲሳይ አገና አንዳርጋቸውን በማቋረጥ፤

“መንግሥትን ለመጠበቅ?!”

አንዳርጋቸው “ አዎ! አንደዚያ ብሎ ነው ሐላፊያቸው ያመጣቸው። (ወደ አስመራ ሲጓዙም) ሲያልፉም፤ ባለፉበት ቦታ ሌላ ታንከኛ ብርጌድ እያያቸው ነው ያለፉት፤ “ለሥራ ተፈልገው ይሆናል” እየተባለ ነው ያለፉት። ማስታወቂያ ሚኒስቴር ሲደርሱ የተጠየቀው እና የተነገራቸው ነገር ምን አንደሆነ በተነገራቸው ሰዓት ላይ ምንም ለማድረግ ፈቃደኛ ያለመሆናቸው…ወደ መጡበት ቦታ በሰላም ተመልሰው ሄደዋል።”  ሲል  ዋሽቷል።  (በነገራችን ላይ ኢሳያስ የሰጠው ቃለ መጠይቅ ደግሞ “ወዴት እያቀኑ እንደሆነ አስቀድመን ነቅተንባቸው ነበር። አንዲያቆሟቸው ያላደረግንበት ምክንያት “ሁኔታው አስቀድምን ተነግሮን ስለነበረ ‘ይበልጥ አንዲበላሹ” ነበር ዝም ብልን አንዲያሳሉፏቸው ስንከታተላቸው የነበረው። አኔ ሰብሰባ ላይ አለሁ፡ አውቀነዋል። ስብሰባችን እስክንፈጽም እነሱ ተከታታዮች አድርገንላቸው ነበር።” ሲል ገልጿል። አንዳርጋቸው የተናገረው ግን የሻዕቢያ ራዲዮን ያሰራጨው የውሸት ፕሮፓጋንዳ ነው። ሆኖም ኢሳያስ እንደጠበቀው በቀላሉ (መልዕክታቸው ለሕዘብ በቲቪ ከማስተላለፍ ሊቀጨው አልተቻለውም) አልሆነለትም፤ ሰዎቹ “መልዕክታቸው በቲቪ አንዲተላለፍ አድርገዋል።” በሗላ ግን የውስጥ ሰላዮች አንደከዷቸው ስላላወቁ፤ በሽምግልና ድርድር በመግባታቸው ምክንያት ተኰላሸባቸው።

ለውጥ ፈላጊው ቡድን፤- የሥርዓት ለውጥ ለማድረግ ሕዝባዊ ምርጫ እንዲደረግ፤ እስረኞች እንዲፈቱ እና ኢሳያስ ሥልጣኑ ለሕዝብ እንዲያሰረክብ፤ ማድረግ ያለበት ቅድመ ሁኔታ የተጻፈ “አዋጅ” በአክሱማዊው የሻዕቢያ ቡችላ በሆነው የዜናው ክፍል ሃላፊ ገረዝጊሔር (ቅድመ ሁኔታውን በጠመንጃ አንዲያነብ ተገድዶ) አንዳነበበው የታወቀ ሆኖ ሳለ፤ያውም  መፈንቅለ ሙከራው በትላልቅ የኢሳያስ ጀነራሎች የገቡበት ፕላን ሆኖ- ነገር ግን በሗላ ቆይተው፤ ፈርተው ሃሳባቸውን በመለወጥ ፕላኑ እንዲኰላሽ ያደረጉት አብረው የመከሩ ጀነራሎች አንደሆነ የተዘገበ ነው (ልክ መንግሥቱ ሃይለማርያም መፈንቅለ መንግሥት ሙከራ አንዴት አንደከሸፈ ተመሳሳይነት)። “የሳይጠሩት ወዴት፤ሳይልኩት አቤት አለሁ ወዴት” የአንዳርጋቸው አፈ ቀላጤነት ግን የሻዕቢያ ዜና ማሰራጫ የተናገረውን በመድገም ውጥረቱን ሊያጣጥለው ሞክሯል።

በሕዝብ የተተፋው ጭራቁ ኢሳያስ በወጣቱ እና በሽማግሌው የታቀፈ ተወዳጅ መሪ ነው ይለናል። “ድጋፍ ስላደረገልን ብዬ አይደለም። በዓይን የሚታይ ነው” ሲል  የሻዕቢያን ዜና ደግሞልናል። የኢሳያስ ቀኝ እጅ አንደ እነ ዓብደላ ጃቢር የመሳሰሉ ሰዎች ‘በሚዩትኒው’ ሰበብ ተይዘው ደብዛቸው ጠፍቷል። የኤርትራ ሥርዓት ለአፍሪካ አርአያነት እና ለኢትዮጵያ የሚመኝላት “ኢሳያሳዊ አስተዳዳር” ነው የሚለን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ፤  በዓይን የሚታየው፤ የኢሳያስ አፈወርቂ አውነታ ግን “ኢሳያስ” አያቶቹ የሚያክሉ ሽማግሌዎችን ቀይ ጃዊ እያስለበሰ የሚያስር ናዚያዊ ሥርዓትን ነው አንዳርጋቸው እያደነቀው ያለው። - ይህንን ይመስላል”


አንዳርጋቸው የሚመኝልን መጻኢት ኢትዮጵያ በኤርትራ ቅጅ ይህንን ኢምፖርት ላመድረግ ነው ( ወፌ ላላም እዛው በአንዳርጋቸው ታጋዮች ላይ የተፈጸመ አሁንም እየተፈጸመ አንዳለ ሰለባዎቹ በቃላቸው ነግረውናል)። አንዳርጋቸው እንደገና ይቀጥል እና “እዛ ላይ የታየው ትልቁ ችግር፤ ኤርትራ ውስጥ ያለው የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ድክመት ነው። ነገ ጥዋት እኛ ሥራ መሥራት ብያቅተን ችግሩ እዛ ቦታ የተሰበሰብነው እኛ መሆናችን ነው የማውቀው። ድክመቱ የኤርትራ መንግሥት አይደለም።የኤርትራ መንግሥት መስዋዕትነት እየከፈለም፤ በዓለም ዓቀፍ ደረጃም፤”ጋንግ አፕ” እየተደረገበት፤የተለያዩ መዋቅሮች እየተደረጉበት፤በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ተቃዋሚዎች በእግራቸው ቆመው፤አገራቸው ውስጥ ያለውን አስከፊ ሥርዓት አንዲያስወግዱ የቻለውን ሁሉ እያደረገ ነው ያለው። ነገር ግን ይህነን ድጋፍ በሚገባ መጠቀም የሚችል የሰው ሃይል መመደብ የሚችል ቀርቶ የነሱን ድጋፍ ፤የነሱን ድካም ከንቱ ያደረገው “የኢትዮጵያ ተቃዋሚ እራሱ ነው”።በነሱ (ኤርታራኖች ድጋፍ )በኩል በዚህ ጉዳይ ላይ ምንም ዓይነት ችግር የሌለበት ነው።

ሲሳይ አገና -

 “በተቃዋሚዎች በኩል ያለው ችግርስ ተቀርፏል አሁን?”

 ቅድም የተናገርኩት እሱ ነው። የነበረው ትጥቅ ትግል በመፍታት የሚሰጠው ድጋፍ፤በሚገባ በመጠቀም በአገር ውስጥ ስፋት ያለው እንቅስቃሴ ማድረግ ወደ እሚችልበት ሁኔታ ማሸጋጋር የኛ ነው። በነሱ በኩል ከሚገባው በላይ ነው የሚደግፉት ያለው። ታይቶ በማይታወቅ! ካሁን በፊትም እኰ ትግል አይቼ አውቃለሁ። በኤርትራ በኩል የሚደረገው ድጋፍ ስመለከት ባሁኑ ሰዓት ላይ 4 ኮከብ እና 5 ኮከብ ሆቴሎች ውስጥ ሆኖ የሚደረግ ዓይነት ትግል አድርጌ ነው የማየው። የምትበላውም የምትጠጣውም ለሰራዊቱ በሚገባ የሚለብሰውን፤ ምን የሚለውን…….፤ ሌላ ቦታ እኮ ሻዕቢያ እራሱ (ትግል ሲያደርግ) ከምን አንደተነሳ እናውቃለን፦ ኢቭን ወያኔ።በዛ ደረጃ ኢሕአፓ (በሻዕቢያ) ሲደረግለት የነበረው ድጋፍ- በዛ ዘመን ስታወዳድረው፤ ከሚገባ በላይ የበዛ ነው ጭራሹ።

ሲሳይ አገና፡

 “ ኤርትራን በተለያዩ ሁኔታዎች ስንመለከት ከዓለም የተነጠለች አገር ነች፡እንኳን ከራሷ አልፋ ተቃዋሚን የምትደግፍበት ሁኔታ ….”

አንዳርጋቸው፦

“እርሾ እኮ ነው የሚያስፈልገው ለድጋፍ።(ድሮ) ስድት እና ሰባት ሰዎች እኰ መረረ እና የቆረጠ ነገር……፤ የተወሰ ሥልጠና እና የበሰበሰ ካርባይን እና ጓንዴ ይዘው እኰ ነው ሜዳ የተገባው። አሁን ኤርትራ ያሉት ተቃዋሚዎች ትጥቅ (የት የሌለ ነው)። ኤርትራ እኮ አንተን በቋሚነት መሳርያ አንድትሰጥህ ፤ምግብ አንድትሰጥህ ግዴታ የለባትም፤ መሆንም የለበትም።”

ሲሳይ አገና፤-

ኤርትራ ምን ልታገኝ ነው እናንተን የምትደግፈው? በናንተ በኩል ምን ልትሰጡ ነው?

አንዳርጋቸው ጽጌ፤-

ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር ያደረግሁት ንገግር ሲገልጽልኝ “ እዚህ  የምትመጡት በኤርትራ መንግሥት ጭንቅላት አመለካካት እና በኤርትራ ሕዝብ ጭንቅላት እምነት እና አመለካካት ኤርትራ ኢትዮጵያን ፤ ኢትዮጵያ ኤርትራን በጣላትነት አንዱ ኣንዱን ፈርጆ ወያኔን ለማዳከም እዚህ ቦታ ላይ የምትመጡ ከሆነ፤ ወይንም ደግሞ የኤርትራ መንግሥት ተቃዋሚዎችን የሚፈልጋቸው፤ ወያኔን አንዲያደክሙለት ነው የሚል እምነት ከሆነ እዚህ የምትመጡት፤ሁላችሁም ተሰብስባችሁ ወደ እምትፈልጉበት ቦታ መሄድ ትችላላችሁ።” (አንባቢ ሆይ! ኢሳያስ ምን ማለቱ አንደሆነ ተረዱለት።)

 “ኤርትራኖች አናንተን ሲረዱ ከናንተ ምን ያገኛሉ? ብልህ ለጠየቅከው.. (ሻዕቢያ) የአገር እና የሕዝብ ክብር የማንነት ክብር አለው (ከሻዕቢያ ጋር፡) ” ይላል አንዳርጋቸው ያልተባለውን ለማስተዋወቅ የምናውቀውን አሳፋሪ የሻዕቢያ ማንነትና ኩራት ምን መሆኑንን አንደማናውቅ”።

አውንታው ግን የተቃዋሚዎች ኤርትራ መደራጀት የሚፈልገው “ለኛ ብለው ሳይሆን ለነሱ ጥቅም ብለው እንደሆነ በምስጢር የተጠለፈው የብርሃኑ ነጋ ንግግር አድምጠነዋል። እሱ ከሚለው በጣም በራቀ መልኩ እውነታው እስኪ እንመልከት። ቲፒዲ ኤም/ዲምሕት የተባለው በኢትዮጵያ ሰንደቃላማ መሃል ላይ በጉልበቱ “የአክሱም ሃውልት” የለጠፈው የትግሬ ተዋጊ ለምሳሌ እንፈትሽ። አንዳርጋቸው ተቃዋሚውን ደካማ የሚላቸው ምን እንዲሰሩ በኢሳያስ እየታዘዙ እንደሆነ እንመልከት፤-
ማሕደራቸው አንዲህ ይቃኛል፦The Tigray People’s Democratic Movement (TPDM, known by its Tigrinya accornym De.M.H.T.) is one of half a dozen Ethiopian opposition groups stationed in Eritrea whose mission statement appears to have changed from bringing change to Ethiopia to fighting change in Eritrea by being President Isaias Afwerki’s last enforcement unit.
Over the weekend, TPDM was dispatched to Asmara to conduct routine roundup of Eritrean youth who have to be mobilized for military enlistment.  In previous dispatches, only TPDM members with passable Eritrean Tigrinya accents were recruited to conduct the roundup.  In this patricular mission, there appears to have been a breakdown and TPDM members with noticeable Tigrayan accents were roaming the Merkato neighborhood of Asmara and asking for “metawekia” and “mewasawesi“–Ethiopian words for “moving permit”– whose Eritrean version is “tessera” and “menkesakesi” respectively.In the ensuing altercation among Asmara residents and TPDM, shots were fired near Hamasien Restaurant.A TPDM soldier who was wounded by stone-throwing Eritreans was treated in Orota Hospital. When asked for his identification, he disclosed that he is an Ethiopian national and gave his address as Alla (near Dekemhare) and gave the name of his Eritrean handler.
Since the incident, the Isaias Afwerki regime has gone on full information-management campaign:

“መሬት ላይ ወርደህ ስትመለከተው የሚገርም ነገር ነው። ከኤርትራ በላይ ለኢትዮጵያ ወዳጅ መሆን የሚችል ማን ነው? አንደ ኤርትራ ለኢትዮጵያ የሚመሳሰል አካባቢ የለም። ኢትዮጵያ ከኬኒያ ጋር አትመሳሰለም፤ ከሱዳን፤ከጅቡቲ ጋር አትመሳሰልም። እነዚህ ወዳጅ አድርጐ ኤርትራን ጠላት አድርጎ የሚያይ የፖለቲካ ሃይል፤ ከድንቁርና የተላቀቀ አይደለም ብዬ አስባለሁ።በኤርትራም በኩል ካለ አንዲሁ።” (ሲል አንዳርጋቸው /የግንቦት 7 ፖሊሲ “ኤርትራን” አንደ ወዳጅ እንጂ አንደ ኢትዮጵያ አካል እንደነበረች እና እንደ አንድ ሕዝብ አድርጐ አንደማይመለከት ልሳኑ ከላይ ያረጋግጣል።)። ኤፍሩም ማዴቦ የተባለው የግንቦት 7 የሕዝብ ግንኙነት (ሦስተኛው ባለስልጣን) ሃላፊ የሆነው ሌላው የሻዕቢያ ባንዳም “ነግሮናል” ያውም ለነሱ ወክሎ “ነፍጠኞች እያለ እተሳደበን” (Do you know NEftENga? Yes, we have NefTeNgOch from the old system here inside us with in the opposition who wants your Assab…..!እያለ። ኦክላንድ ከተማ አሜሪካ ውስጥ በሻዕቢያ ሰብሰባ አዳራሽ ተገኝቶ! ወገኖቹን የሚዘልፍ ማን ነው? አዎ! ግንቦት 7ን የሚመሩት ባንዳዎች ናቸው! በመረጃ ከምላሳቸው የተገኘውን መረጃ እኮ ነው እያሳየናችሁ ያለነው! ፓልቶክ ላይ የስሜትና የጎሰኛ ዉሃ የሚጐነጭ ተሎ የሚጨፈለቀው “ፈዛዛ ቲማቲም” ሂዳችሁ ስለ ግንቦት አርበኞች እና ስለ ኤርትራ አገርነት እና ወዳጅ መሆን አውሩለት፡ ያደምጣችሗል። ብሽቅ ተቃወሚ!

አንዳርጋቸው ስለ ዓረቦች ፤ኤርትራና ኢትዮጵያ ሲተነትን ይገርማል። ኢሳያስ አፈወርቂ ኢትዮጵያዊ ሆኖ አማርኛ አጣርቶ የሚናገር ሰው መሆኑን እያወቅን “አማርኛን” የጠላት ቋንቋ ነው ብሎ በዓረብኛ እና በእንግሊዝኛ ሲናገር ምን ማለት አንደሆነ እያወቅን በዓረቦች የሚጣላ “የኢትዮጵያ ወዳጅ” ነው ይለናል። ዓረቦች በጠላትነት ያዩታል” ይለናል፤ ሲዋሸን። ኢሳያስ “አንጀራ መብላት አንኳ ከፓስታ ስልጣኔ” ጋር ያወዳደረ ደንቆሮ ናዚ_( ይህንን ለማንበብ በኔው ብሎግ ከሁለት ዓመት በፊት ተለጥፏል ፈልጋችሁ አርካኢቭ ላይ አንብቡት) “ዓረባዊ ስሜት የለውም፡ ኢትዮጵያዊ ወዳጅነት ይፈልጋል” ይለናል አንዳርጋቸው ስራው እየሰራለት በነበረበት ወቅት። ታሪኩን የምታውቁት ሁሉ እና የኤርትራ ታሪክ ያነባችሁ ከአንዳርጋቸው ጋር እንደማትስማሙ የታወቀ ነው። ብቻ ዘርዝሩ አልገባም።

አቶ ተድላ አስፋው  ወንድሜ ስለ ግንቦት 7 መሪዎች ለምሳሌ እነ ንአምን ዘለቀ እነ ኤፍሬም ማዴቦ (ከሻዕቢያ ጋር ቃል ኪዳን ሲገባ ያለው ፎቶ) አና የፓልቶክ ክፍሎቻቸው
ስለ ኤርትራ እየተወከሉ በባንዳነት ሥራ አፈቀላጤ እየሆኑ እኛ ጠላት ስንለው እነሱ “ጠላታችን አይደለም፤ ያውም የአመቱ ሰው መባል ሲያንሰው ነው” ፡ እያሉ እኛን “ነፍጠኞች/የድሮ ርዝራዦች/ትምክሕተኞች” እያሉ ከጠላቶቻችን ከሻዕቢያ ጀሌዎች እና መሪ ጋር እየተሻሹ የሚያደርጉት ስነ ምግባር ከማየታችን በፊት፤ እስኪ ያንን አንድበት አንደገና የግንቦት 7 ሚዲያው ኢሳት ባንተው ሸጋ አገላለጽ አንመልከት፦

“We all remember when Tamagne Beyne of ESAT fundraiser/Activist answered this question long time ago by saying if ESAT is a Ginbot 7 media let it be, “Behonese”. Dr. Birhanu backed Tamagne positively thanks to the leaked audio that ESAT is financed by Ginbot 7. It is no more “Behonese”, ESAT is a media wing of Ginbot 7.” ግርም!

ይኸ ከሆነ ግንቦት 7 ደግሞ በሻዕቢያ የሚደገፍ ነው። ሻዕቢያ ላንዳንዶቻችሁ ወዳጅ ከሆነ አላውቅም ለኔ ግን ከወያኔ እኩል የማየው የኢትዮጵያን ሕልውና ለማጥፋት ዕድሜውን ሙሉ የሰራ ጠላት ነው። ከ9 ሚሊዮን ብር/$500፣000 (ያውም በስድት ወር ውስጥ ብቻ) በሻዕቢያ ለግንቦት 7 ሲሰጥ እሩብ የሚሆን ገንዘብ ለግንቦት 7 የፕሮፓጋንዳ ክንፉ ለኢሳት ራዲዮ እና ተቪ የተሰጠ ነው።ይህ ባንዳነት ነው። ኢሳት ለኢትዮጵያ ሕዝብ እያስተላለፈ ያለው የወያኔ ገበና የሚደነቅ ነው የሚሉ ሰዎች- መልስ አለኝ።  ከኢሳት ይልቅ ሻዕቢያ ከአስመራ በራሱ ጣቢያዎች የወያኔ ገበና ያጋልጣል። ታዲያ ያንን ስለሰራ ሻዕቢያም የኢትዮጵያ ሕዝብ  ዓይን እና ጀሮ ነው” ማለት ይቻላል? ኢሳት ስለ ወያኔ መጥፎነት ሲያሰራጭ አንደም ቀን ስለ ሻዕቢያ መጥፎ እና ወንጀል መዘገብ አይፈቀድለትም። ከዘገበ ግን ድጐማው ይቋረጣል ደሞዝተኞቹ ችግር ውስጥ ይወድቃሉ። ታዲያ “ባንዳ” ማለት ጠላት ስለ እምንለው የሻዕቢያ ወንጀል ማውራት ካልቻለ፤ ስለ ጠላት ደግነት  ካሰራጨ ከዚህ ወዲያ ለጠላት ማደር ምን አለ? ለዚህ ነው ስለ ሻዕቢያ መጥፎነት በኢሳት መነገር የማይፈቀድ።ስለ ድግነቱ እና ዲሞክራትነቱ፤ሰብአዊነቱ/አፍሪካዊ አርአያነቱ…… ግን በወኪላቸው በአንዳርጋቸው በኩል አንዲነገር ተፈቅዷል። አንዲህ ያለ ለጠላት የወገነ ሚዲያ “ባንዳ” ካልተባለ ሌላ ስም ምን ይስማማዋል?

ስለሆነም ነው ካንተው ከወንድም አቶ ተድላ አስፋው ጋር እንዲህ ስላልክበት ጉዳይ የምስማማው “Dr. Birhanu should be asked this coming Sunday why does he need to “Deceive” the public for almost three years. He should apologize for the public. ……One thing ESAT can not do is to criticize its financiers, Isaias Afeworki and Ginbot 7. As long as it does that it will be on air. The Diaspora fundraising has to go on because Isaias Afeworki is not a reliable partner.”

Ato Andargatchew is working hard to make sure Isaias finance is coming. That was the reason he came strongly to sell Isaias as “a man of the year of 2006″. Lionizing a dictator as a model for Africa “self rule and reliance”. If Ginbot 7 has such leadership in mind for future Ethiopia after Woyane it will not win any free and fair election.” ይህ ነው እኔም ባንዳዎች የኢሳያስ አስተዳዳራዊ ሞዴል ተመስጠው ለአፍሪአካ እና ለመጪዋ ኢትዮጵያ ምን እያለሙላት አንደሆነ ለመንገር ከሁሉም ጋር እየተጋጨሁ እውነቱን ለመንግር እየጣርኩ ያለሁ። ሰሚ ጀሮ ካለ! ከዚህ ወዲያ ባንዳናት አለ? ኤፍሬም ማዴቦም ልክ አንዳርጋቸው እንደሚለው ነው እየሰበከ ያለው። ለዚህ ነው ግንቦት 7 አመራሮች በተማሩ አደገኛ ባንዳዎች የተሞላ ነው የምለው። ስለ ኤፍሬም ማዴቦ እና ስለ የግንቦት አመራር አባል እና የኢሳቱ መሪ ንአምን ዘለቀ የኢሳያስን ስርዓት በማሞገስ እና ፖለቲካቸው ለማካሄድ ሲሉ በመላ የዓለም መንግሥታት ማሕበር የተወሰነው “ኢሳያስን የሚያወግዝ” ውሳኔ ያስተላለፈው መቀጮ (ውሳኔው ዋጋ ቢስ ቢሆንም) ከኤርትራኖች ጋር ሆነው በየአደባባዩ የተናገሩትን ከዚህ በታች ያለውን ማሕደር አድምጡ/እዩ።

Ephrem Madebo of Ginbot 7 Ethiopian opposition movement at Eritrean Festival in Oakland http://youtu.be/pW1mopFgf2k

Ephrem Madebo of Ginbot 7 and Aklilu Wondaferew of Shengo with Addis Dimts radio Host Abebe Belew http://youtu.be/M72Khe9NrdU

ከዚህ በታች ያለው በጥሞና የቪኦ እና የግንቦት 7 ጋዜጠኛው ፋሲል የኔአለም የተባለው የግንቦት 7 እና የ ኢሳት ጋዜጠኛ (የብርሃኑ ነጋ አምላኪ)  የሻዕቢያው ወዳጅ ለሆነው የኢሳቱ አቶ ንአምን ዘለቀ የሰጠው ቃል አድመጡት። በጣም ታፍራላችሁ፤ ያባሳጫቹሗልም። ግንቦት 7 ባንዳ ነው የምንለው ከዚህ ወዲያ ሌላ ባንዳነት የባሰ ጥብቅና ካለ ንገሩን። ንአምን አንዲህ ይላል ተጠይቆ ሲመልስ፤-

“ኢትዮጵያዊያኖች በሰልፍ መገኘት ብቻ ሳይሆን ‘ ሰልፉ ድጋፍ አንዲያገኝ፤ በሰሜን አሜሪካ  እና አውሮጳ በሚገኙ ሬዲዮኖች፤ ድሕረገጸች ሰልፉ ድጋፍ እንዲኖረው፤ ብዙ የማስተባባር ብዙ ጥረት ተደርጛል። ስለዚህም ብዙ ኢትዮጵያዊያኖች ሰንደቃላማዎች አሸብርቀው፤ይዘው ብዙ ተገኝቷል።…ወጣት ኢትዮጵያዊያን በተለይ!” ይላል ንአምን።

ይህ ባንዳነት የዲያስፖራ ራዲዮኖቻቸው፤ ቲቪ፤ ድረገፆች በዚህ የባንዳነት ሥራ መሰማራታቸው ያለ ምንም ሐፍረት አንደ ጀብዱ  የኢሳት ጣቢያ ዋና ደይሬክተር ነግሮናል። ቃለ መጠይቁ ተከታተሉት፡(አሳፋሪ ፎቶዎችም ታያለችሁ)። Ethiopians Participation on Eritreans Demonstration http://youtu.be/caF_F0aSsXA
Shameless Ethiopians Participating at Shaabiya YPJDF Demonstration
Niamin Zeleke coordinator of the Shaabia Ethiopian Demonstration

 ለዚህም ነው አቶ ተድላ አስፋው ካሁን በፊት ““Ethiopians should ask how could Ginbot 7 leadership defend working closely with Isaias Afewroki?” ብልህ ስትጠይቅ፤ ከዚያ ጠላት ጋር አገራችን ከሚያጥላላ እርኩስ ጋር መስራት ብቻ ሳይሆን ስለ እሱ ተክለ ሰውንት ጥብቅና ቆመው “የ2006 ኣ.ም የአመቱ ሰው’ ብለው እነ አንዳርጋቸው እና እነ ….የመሳሰሉ ሰዎች ሲሟገቱ መስማት “የባንዳነት ስራ” ከዚህ ሌላ ካለ አስረዱን ብለን የምንሟገተው። ያውም አቶ ንአምን ዘለቀ በቃለ መጠይቁ ምን እንዳለ አድምጣችሁ ፍረዱ። (በዚህ ሁኔታ እኔ እና እሱ በኢመይል ተመላልስናል። የኤርትራን ሕዝብ ያለ ማዕቀብ እያጠፋ ያለው ኢሳያስ አፈወርቂን ሳይቃወም፤ በኢሳያስ እና አለቆቹ ተደረገ የተባለው የውሸት/የይስሙላ ማዕቀብ “የኤርትራን ሕዝብ ይጐዳል” ብለው ለባንዳዎች ውክልና መጮህ  አሳስቦአቸው ከነ ኦ ኤል አፍ እና ኦብነግ ባንዴራ ሰንደቃላማችንን አጎራብተው ጎን ለጎን እስያቆሸሹብን የባንዳ ስራ ሲሰሩ እና ስለ የማይረባ “የዩ ኤን  ማዕቀብ” መጮህ ከዚህ ወዲያ “ለጠላት ውክልና የለም። እነ ንአምን ሁሉ የግንቦት 7 መሪዎች እና አባሎች ናቸው። እነዚህ ሁሉ!

ወንድሞቼ ይህ ሁሉ የኤሊት ጋንግ ብልጣብልጥ ስብስብ ሕዝባችን አንዴት ለጠላት መንበርከክ አንዳለበት የሚሰሩት “የሳብ ቨርሲቭ” አንቅስቃሴ በሚዛናችሁ ፍረዱ! ይህ ብሽቅ፤ ቅጥረኛ ተቃዋሚ ሥራው ሁሉ ስታዘበው “ያበግናል፤ ያበሽቃል!”

ወንድሜ አቶ ተድላ አስፋው- አንተ ልበልህ እና   “Ethiopians should ask how could Ginbot 7 leadership defend working closely with Isaias Afewroki?” ብለህ ስትጠይቅ አንደገረምህ፤ እኛም ገርሞን የጠየቅከውን ነው ደግምን ድሮም፤ አሁንም ደግመን ስለ ኤርትራ መሪም ሆነ ፖሊሲያቸውን አንዲፈትሹ የምናሳስባቸው። ስሜት አደገኛ ፈረስ ነው እና “አልቦት አልቦት” “ጋልቦ፤ጋልቦ” እራሱ እስኪቆም ድረስ አንጠብቃለን።  በሚቀጥለው ጽሑፌ “Isayas  lapdog in Ze-Habesha website- training “rubbish Eritrean and Ethiopian nationalism” to the Ginbot7 Pets! በሚል ዶ/ር ፀጋዘአብ የተባለው የለንደን ኗሪ የሆነው የታወቀ ሻዕቢያ ቱልቱላ እና ጸረ ኢትዮጵያ ስለ ወሻከተው ጉድፍ እተነትናለሁ። ጠብቁኝ።  አመሰግናለሁ ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያን ሰማይ አዘጋጅ) Ethiopian Semay  ኢመይል ለማድረግ (getachre@aol.com) ይፃፉ።



Monday, July 14, 2014

‘የቀራንዮው እየሱስን’ ስም የተቸረው የአንዳርጋቸው ጽጌ ገበና ማሕደር፤ ኤርትራ እና ኢትዮጵያ ታጋዮች ጉዳይ!




 

ይህ ፎቶግራፍ በኢትዮጵያዊነት ስም በሴራ ተጨፍለቀው እነ አርበኞች ግምባር እነ ቤንሻንጉል ወዘተ…በጥምት ስም ለሻዕቪያ ተወርዋሪ ሃይል/ፈጥኖ ደራሽ ተብሎ ለሚጠራው “ለትህዴን” (ቲ ፒ ዲኦ ኤም) ተሰጥተው በስሩ እንዲንቀሳቀሱ የተደረገ ሻዕብያ ያዘጋጀው የጥምረት መሪዎች ምስል ነው።


ሻዕብያ ያዘጋጀው የጥምረቱ የ “ኢጥዴለ” መግለጫ ማንፌስቶ ነው
‘የቀራንዮው እየሱስን’ ስም የተቸረው የአንዳርጋቸው ጽጌ ገበና ማሕደር፤ ኤርትራ እና ኢትዮጵያ ታጋዮች ጉዳይ!


ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያን ሰማይ አዘጋጅ)
ከፍል  -2-


በአንድ ጠረጴዛዬ ላይ ቁጭ ብየ ሳስብ አማካሪዬ እና ተሟጋቼ የሆነው ሕሊናዬ አንዲህ አለኝ፦

“እኔ እና አንተ የምናርስበት የእርሻ ቦታ ታሪክ  ይባላል።በእርሻው ላይ ጊንጦች፤ እባቦች እና አመኬላዎች ይጋሩናል። ምርታችን “ፍትሕ ነው”። ፍትሕን አንዘራለን፤አንኮተኩታለን፤እናሳድጋለን። አጭደን ከምረን ፈጭተን የምንመገበውም ምግብ ከፍትሕ ሌላ ምግብ አናውቅም ። የሰዎች ልጆች ሁሉ የላቀ ምርት ነውና ፤እየተነደፍንም ሆነ ከሥር እየተወጋን  ፍትሕን ከመከላከል  የማንቦዝን በታሪክ እርሻ የምንገኝ የፍትሕ ሰብል አምራች ገበሬዎች ነን አለኝ” (ጌታቸው ረዳ ኢትዮጵያን ሰማይ ብሎግ አዘጋጅ)          


ይህ ሐተታ፤ ፍትሕን እየረገጡ፤ስለ ፍትሕ መጮሕ ልማድ ለሆነባቸው አንዳንድ የዲያስፖራ ጸሐፊዎች፤የሕግ ምሁራን፤ ተቃዋሚዎች እና ሚዲያዎቻቸው የዳሰሰ ሐተታ ነው። ባለፈው ሰሞን የሕዝባዊ ሃይል/ግንቦት 7 አባል የነበረው አንተነህ ጌትነት  ጋዜጤኞችን "ጠያቂዎች ብቻ መሆናችሁን አታስቡ ተጠያቂዎችም እንደሆናችሁ አትዘንጉ።" በማለት ለአንዳረጋቸው ጽጌ በመወገን ፤ኤርትራ ውስጥ  በሕዝባዊ ሃይል ታጋዮች ላይ አንዳርጋቸው ጽጌ የፈጸመባቸው “ሰብአዊ ጥሰት” ለተቃዋሚ ሚዲያዎች ቢያሳውቁም፤ የአንዳርጋቸውን ገበና ላለማጋለጥ በወገንተኛነት ለግንቦት 7 ወግነው እሮሮአቸውን “አፍነው” ፤ ወተኞች በመሆን የተቃዋሚ ሚዲያዎች እና ጸሐፊዎቻቸው ላይ አባሪ ተባባሪነታቸውን በቅሬታ የገለጸበት በእኔ ብሎግ ላይ ከተለጠፈው ካለፈው የተወሰደ ሚዲያዎችን የወጠረ ጥቅስ ነበር። ዘሬም ሌላው የአንዳርጋቸው ጽጌ ሰለባ የሆነው ወጣት ሽታው ሽፈራውን እና ኤርትራ ውስጥ ለ10 አመት መሽገው ወያኔነን ለመጣል ሲንቀሳቀሱ ከነበሩት የሻዕብያ መሰሪ ገበና በአካል የሚያወቁ ሰዎች የሰጡንን መረጃ በጥልቀት አንቃኛለን።


የተቃዋሚ ፖለቲካ ድርጅት ተከታዮች ‘አጭበርባሪ መሪዎቻቸውን’ ወደ ማንዴላ፤ወደ ጋንዲ እና ወደ ረቂቅ መንፈስነት በመለወጥ፤ የሰው ልጅ መብት ሲረግጡ፤አገር ሲሸጡና ሲክዱ ከሚገኙት “ጲላጦሶች” ጋር ሆነው ሲተሻሹ፤ዊስኪ ሲጫለጡ፤ ፖለቲካቸውን ሲያሻሽጡ ፤ሕዝብ ሲያተራምሱ፤በግድያ እና በሰይል (ቶርች) ዜጎችን ሲያቃዩ የነበሩትን፤ የኢትዮጵያ ጠላቶች የሆኑትን የምናውቃቸው የኤርትራ እባቦችን “ወደ እርግብነት” ለውጠው ሊሸጡልን የከጀሉ፤ ፍትሕ ረጋጮችን ሁሉ ወደ ፖለቲካ ገበያ አውርደው “የቀራንዮው ክስቶስ” አስመስለው በተካኑበት የጽሑፍ ችሎታቸው ቀባብተው በማስዋብ  የፈዘዘው እና የደነነዘው ማሕበረሰብ አንደገና ለማጃጃል፤ የቀራንዮ ክርስቶሳቸውን አንድንገዛላቸው፤ አንዳርጋቸው ጽጌ የተባለ ፖለቲካዊ  ሸቀጣቸውን መሸጥ የጀመሩት አሁን አይደለም።

ወደ ሗላ ተጉዘን ብንኝ፦ በፍትሕ ረጋጭነት እና በብሔራዊ ወንጀሎች በመሳተፍ እና በመምራት መጠየቅ የሚገባቸው ለገበነኞቹ ለእነ ስዬ አበርሃ፤ ኢሳያስ አፈወርቂ፤ ለእነ ቡልቻ ደመቅሳ፤ ለእነ ብርሀኑ ነጋ ፤ነጋሶ ጊዳዳ፤ ለሸኽ አብደል ከሪም (ጃራ)፤ለእነ ሌንጮ እና በያን አሶባ፤ከማል ገልቹ; እነ ጃዋር መሓመድን …. ወዘተ…ወዘተ… የቀራንዮውን እየሱስ፤የማንዴላ እና የጋንዲ የረቀቀ መንፈስነትን እና የፍትሕ አርበኞች የሚል ስም እየተቸራቸው የፖለቲካ ሸቀጣቸውን እንድንገዛቸው፤ ተሞክሯል።

የወያኔው ታምራት ላይኔም በአሜሪካኖች “የሃይማኖት ኔት ወርክ” በኩል እየታገዘ ተከታዮች አግኝቶ እንደ የቀራንየው እየስ እግሩ ላይ እየተደፉ የሚያለቅሱለት ተከታዮችን አይተናል። ታምራትም ከቀራኒዩው እየሱስ ጋር ኢትዮጵያ እስር ቤት ውስጥ ነጭ ልብስ ለብሶ በብርሃን ታጅቦ በሞስኮቱ ብቅ ብሎ እንዳገኘው እና እንዳየው፤ ለተከታዮች እያለቀሰ ሲያስለቅሳቸው አይተናል። ይህች ጉደኛ ዓለም ስንት ሸቀጥ በዱሩጇ አሽጋ ይዛለች።


የዲያስፖራውን ጭንቅላት በሃሰት ፖለቲካ እያጃጃሉ በየፓልቶኩ እና በድረገጾች ተሰግስገው ንባ እያፈሰሱ ስቅስቅ ብለው በማልቀስ አንዳርጋቸውን ወደ መለኰትነት እየለወጡት የሚገኙት የግንቦት 7 ጓዶች እና ጀሌዎች መለስ ብዬ ወደ ሗላ ስቃኛቸው፤ የወያኔ ጀሌዎች አምና ነሐሴ ውስጥ መሪያቸው መለስ ዜናዊ በድንገት ሲሰወርባቸው “ገዛ ተጋሩ” በሚባል የትግሬዎች ፓልቶክ የሰማሁት ልቅሶ፤ ምግብ አልበላም ባይነት፤ ዋይታ፤ ድንጋጤ እና ባዶነት ሳመዛዝነው፤ የግንቦት 7 ጀሌዎች ሊህቃን እና ሚዲያዎች፤ የገዛ ተጋሩ የመለስ ዜናዊ “ካልቶችን” ቦታ ተክተዋል።

በዚህ “የማይንድ ኰንትሮል ቢዝነስ” የማሻሻጥ ስለት ስንፈትሽ  ሊሂቃን የሚባሉ አብዛኞዎቹ የዲያስፖራ የተቃዋሚ ‘ኤሊቶች’ ግምባር ቀደም ተዋናዮች ሆነው ተገኝተዋል። የለመድናቸው ሸቋጮች፤ በፖለቲካው ብቻ ሳይወሰኑ በስፖርት ሴክተር ውስጥ ሳይቀር ተሰግስገው በታራ ዜግነት ሽፋን ፖለቲካ ሸቀጣቸው እና የገንዘብ ምንጫቸው ለማድረግ ሆን ብለው በረቀቀ ዘዴ የተንጠላጠሉባቸው ምልከቶች ተዛቤአለሁ።

የሓፈረት ትርጉም የማያወቁ አንዳንድ ምሁራን ተብየዎችም የንቀታቸው ብዛት “የኦሮሞ ነፃነት ግምባር” ብሎ ራሱን የሰየመ የሽብር ድርጅት “ኢትዮጵያን በቅኝ ገዢነት አልከሰሰም፡ ከኢትዮጵያ የመገንጠል ጥያቄ አቅርቦ አያውቅም” ብለው ከኦነጐች እና ከነብርሃኑ ነጋ ጋር በየአለማቱ እየዞሩ እንደ እነ ዶ/ር ጌታቸው በጋሻው (ዶ/ር ዜሮ/0) የመሳሰሉ በአደባባይ ለሐሰት ጥብቅና ቆመው ሐሰትን ሲሸጡ እና ሲያሻሽጡ አንደነበር እና ዛሬም ከዛው ምግባራቸው የተቆጠቡ አይመስሉም ። ሐሰትን ለመከላከል አንዲያመቻቸው፤ “የፖቲካው ሸካራነት ለማስወገድ ሲሉ ነው አንዲያ ያሉት” የሚሉ የዋሃንም ገጥመውኛል። ኦነጎች “To fully exercise the rights of self - determination of the Oromo people” .  All Urban lands inside Oromia is part and parcel of the Oromia state that they will be controlled  by the Oromian government. The state of Oromia will have its own policy to these urban lands” የሚሉትን እስካሁን ደረስ የሚነበብ አንደ አዲስ የተጻፈው ይህ ፕሮግራማቸው ተዘርግቶ እያነበብነው “ደላሎቹ” ከነሱ በባሰ አሁንም “ወደ ኢትዮጵያዊነት መንገድ ተሞርደዋል” እያሉ  እየዋሹን ነው።

ህ ማኒፌስቶ “ኦነጐች ወደ ኢትዮጵያዊነት መጥተዋል” እያሉ እነ ብርሃኑ ነጋ ከሚዋሹን “የተሞረዱ ኦኖጎች” (የተሻሻሉ) ከሚባሉት ኦነጐች ያገኘሁት ፕሮግራም ነው።

እነሱ በግልጽ እየነገሩን እያሉ፤ኦኖጎች መገንጠልን ትተዋል የሚሉ በርከታ የተጃጃሉ አዋቂዎች እና አሻሻጮች ዛሬም አሉ። ኦነጐች ብልጠት እየተማሩ በመምጣታቸው፤ አብረዋቸው ከኢሳት ጋር ፤ከግንቦት7 ጋር ከጥምረት ፤ምናምን ምናምን ከሚባሉት፤  አሿሿጮች ጋር አብረው አሁንም በየእስቴቱ፤ በየገንዘብ ቅራማቱ አብረው “ኢትዮጵያዊያን” ተመስለው  ቄሶች እና ሼኮችን ጭምር ሁሉ ሳይቀሩ ይዘዋቸው ይዞራሉ።  ኦኖጐች “ነፍጥ” አንደማያዋጣቸው 40 አመት ስላዩት፤ አዲስ ስልት በመቀየስ “መርሲናሪ ሴልስ ሜን/ሴልስ ወመን/’ “አሻሻጮች” በማግኘታቸው ከማንም ጊዜ በበለጠ የተካኑ/better smarter /better intelligent ሆነዋል።  

ኦነግ የተባለው ከስልጣኔ እጅግ ፤እጅግ በጣም የራቀ ጀሌ የሚያስከትል ቡድን “አውስትራሊያ- ፐረዝ” ከተማ የሞረሹ አቶ ተክሌ የሻውን ሕይወት ላይ አደጋ ለመጣል በመዶለት “አሲድ” ወደ ፊታቸው ደፍተው አደጋ ለመጣል ዶልተው አንደነበር ተዘግቧል። ይህ ነው “ኦነግ ወደ ልቦናው ተመልሷል፤ በሰለጠነ ፖለቲካ እየተራመደ ነው” እያሉ ደላላዎቻቸው እኛኑን ለማጃጃል እየሞከሩ ያሉት

ሬ ደግሞ የሽምቅ ተዋጊ መሪነት እና የተጠራጣሪነት ስልት ስልጣና እና ልምድ ሳይላበስ፤ የኤርትራ ሰዎች ምንነት ሳያጠና፤ እነሱን አምኖ፤ ያለ ምንም ጥርጣሬ በእየ ዓረብ መዲናው እና በየ አውሮጳ እና አሜሪካ ከወዲያ ወዲህ ሲዘልል፤ ጠላት እጅ ውስጥ የገባው አንዳርጋቸው ጽጌ፤ በጠላት ሲያዝ  “ደጋፊዎቹ”  ወያኔን  ማውገዝ ሲገባቸው፤ ከላይ እንደጠቀስኩት ስብእናውን ወደ “ክርስቶስ ፤ ወደ ረቂቅ መንፈስነት፤ ከዚያም ወደ ማንዴላነት እና ወደ ጋንዲነት፤ እና የፍትሕ  ጠበቃ ” እያሉ  መቀባባቱን ስንመለከት፤ አንዳርጋቸው ኤርትራ ውስጥ እያለ “በአድርባይ ባሕሪው” ለሻዕቢያዎች አድሮ የገፋቸው ኢትዮጵያዊያን ማሕደር ስንፈትሽ፤ “አድማቂዎቹ አንደሚቀባቡት “የቀራንዮ ክርስቶስ፤ ረቂቅ መንፈስ” ሳይሆን፤ እሱን አምነው ኤርትራ ድረስ ሄደው በሰይል ላሰቃያቸው እና ለሻዕቢያ አስረክቦ ለሞት እና ለድብዳባ፤ አንዲሁም ለሻዕቢያ እርሻ አምራቾች እንዲሆኑ ለባርነት ላስረከባቸው ኢትዮጵያዊያን ሰለባዎቹ ግን “የሃሬና መጻጉእ” ነው። ፍትሕ እና አንዳርጋቸው አይገናኙም። ከቶውንም  አይጣጣሙም። 

ሕሊናን በመቦወዝ ስራ የተሰማሩ የግንቦት 7 “የማይንድ ኮንትሮል ፍሪክስ ግሩፕ” ደጋፊዎች፤ገጣሚዎች እና ጸሐፊዎች ማወቅ ያለባቸው፤ አንዳርጋቸው ጽጌ ይመራው ነበር የተባለው የግንቦት 7 ሽምቅ ተብዬው “ኤርትራ ውስጥ ኢትዮጵያዊ መንፈስም ሆነ ራእይ ያለው እንቅስቃሴ የለም።” ሲል የሕዝባዊ ሃይል የፋይናንስ እና  የአስተዳደር ክፍል ሓላፊ የነበረው በአንዳርጋቸው ጭካኔ እና ውሳኔ ለሻዕቢያ ደብዳቢዎች ተላልፎ “ሄልኰፕተር” ተብሎ በሚጠራው የሻዕቢያ ድብደባ /ቶርቸር/ በገመድ ቁልቁል ተዘቅዝቆ ታስሮ ሰውነቱ በሰይል የተዳከመው ከሞት አፋፍ ያመለጠው ወጣት “ሽታው ሺፈራው” ነግሮናል።

ወጣት ሽታው ሺፈራው በየ እንተርኔቱ የሚዘላብዱትን ፤ የግንቦት 7 ጉድ እና የአንዳርጋቸው ጽጌ ስብእና እና ምንነት፤ ኤርትራ በረሃ ሄደው በቅርብ በቅጡ፤ ያላዩት ጉዱን ያልተረዱ፤ ደጋፊዎች እና ያለቦታቸው የሚለቀለቁ ቃላቶችን እና ለቅላቂዎችን እጅግ ስላስገረሙት “የወረቀት ላይ ደፋሮች” ይላቸዋል።


አንዳርጋቸው ነበረበት በተባለው ሃረና መስልጠኛ ጣቢያ እና በረሃ የነበረው የሸምቅ ተዋጊው ሃይል ከፍተኛ ሃላፊነት የነበረው ሽታው “ኤርትራ ወስጥ” ስለሚንቀሳቀሱ ኢትዮጵያ ድርጅቶች ጉዳይ አንስቶ አንዲህ ይላል። 

“እነዚህን ሻቢያ አቡክቶ የጠፈጠፋቸውን ድርጅቶችንም ሆነ ለግል የእኩይ ተግባር ሲባል ሻቢያ የኛ ሆነውን አላማ ተሰማምቶ የገቡ ድርጅቶችን ተስፋ ማድረግ በራሱ ላም ባልዋለበት ኩበት ለመልቀም ያክል ራስን ማዘጋጀትና መሸንገል ነው።” ይላል።

ተስፈኞቹ “የሚያከብሩት የቀራኒዮ  ክርስቶስ” ጭምር ድንገት ከሰማዬ ሰማያት ወርዶ ሽታው ሺፈራው የነገረንን፤ አውነታ ቢደግምላቸውም የሚያምኑ አይሆኑም። እስኪ ከሽታው በተለየ ሌላ የደርጅት መሪ “ከኤርትራኖች ጋር የቀረበ ግንኙነት መስርቶ የነበረ” ፤በትግሉ ለብዙ አመት እዛው ኤርትራ ለአስር አመት የቆየ፤ ልክ ሽታው እንደነገረን በሰፊው እና በጥልቀት ከነመረጃው የገለጸልንን “ፕሮፌሰር ሙሴ ተገኝን” እናዳምጥ። አንዲህ ይላል፦

“ይህ ሁሉ መረጃ በቪዲዮ የማሳያችሁ በኤርትራ ውስጥ ብዙ አመት በከንቱ ያሳለፍነው ኢትዮጵያ ወንድሞቻችን ከእኛው ትምህርት አንዲማሩ እና ተሳስተው ወደ እዛው አንዳይሄዱ ነው።”  ይላል ፕሮፌሰር ሙሴ ተገኝ በዩቱብ ስለቀቀው መግለጫው ምክንያት ሲናገር።

ባጠናቀረው “የስእለ ደምፅ” መረጃው ላይ አንዲህ ይላል። “ኑ ወደ ኤርትራ እርዳታ እንሰጣችሗለን” ብሎ ሻዕቢያ የስልጠና የገንዘብ፤ የምግብ እና  የመረጃ እርዳታ ከሰጠን በሗላ “ተዋጊው ሃይል “በራሱ አስተዳዳር፤ በራሱ መሪነት፤ የድርጅት መግለጫ እና ፕሮግራም ሳይቀር ቀርጾ የሚሰጠን እሱ ነው። የኢትዮጵያዊነት ጥንካሬ ካየ ሆን ብሎ፤ አመራሩን በማናከስ ፤በመለዋወጥ በማጨቃጨቅ ስራ ጣልቃ ገብቶ ያምሰናል።

አርበኞች ግምብርን “አጋሮ” ውሰጥ ስንመሰርት ሁለት በሬ አርደን እንዳንካካድ “ደም” አፍስሰን ተማምለን ነው አርበኞች ግምባርን መሰረትነው። የረባ ስራ አንኳ ሳንሰራ፤ ለምሳሌ  ከ2000 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 2005 ዓ.ም ድረስ ለአምስት አመት ሙሉ በጭቅጭቅ ሻዕቢያ መሪ ሲቀይርልን አንዱ ካንዱ ሲያሳብቅ፤ እርስ በርስ ስንናከስ፤ በከንቱ ጊዜ አለፈ። ይህ ሁሉ ሲሆን በቅርብ የሚቈጣጠን የሻዕቢያው ትልቁ  ሰው ኮለኔል ፍጹም ይባላል። ከላይ ሆኖ የማናከስ ሴራ የሚመራው እሱ ነው።  የእኛ ጽ/ቤት እና የኮለኔሉ ጽ/ቤት ፊት ለፊት ነው (በረሃ ውስጥ)።


ከዚያ ጠቅላላ ኤርትራ ውስጥ  ያሉትን ኢትዮጵያ የሚላቸውን ተዋጊዎችን ብቻ ሰብስቦ በኤርትራዊው ኰለኔል ፍጹም ቁጥጥር ሥር “ፕሮግራም ቀርጾ” እኛ ያላጸደቅነው ያልነደፍነው፤ ያለወቅነውን ፕሮግራም በመንደፍ  “ወህደት/ጥምረት” ብሎ ፤ ሁላችን ሰብስቦ “በትፕዲኤም”  በትግሬ ተዋጊው ሃይል ስር አንድንጠቃለል አድርጎ ፤ የወያኔ ተጋይ እና የስለላ ኦፊሰር የነበረው  ከኰለኔል ፍጹም ቢሮ ደርሶ ሲመለስ መንገድ ላይ አብሮት ሲጓዝ የነበረው ጥይት አርከፍክፎበት ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው ሟቹ የ“ትፕዲኤም’ ፍስሃ ሃይለማርያም መሪያችን አደረጉት። በዚህ በጣም ተበሳጨን ፤ብዙ ንትርክ ተደረገ።

እዛው (ኢትዮጵያ) ውስጥ ያለምንም ዲሞክራሲ ወያኔ ከትግሬ መጥቶ እየገዛን ፤ አሁንደ ደግሞ እዚህ በረሃ ዲሞክራሲ ፍለጋ ስንመጣ ሌላ ትግሬ “ያለ ምርጫ እና ያለ የኛ እውቅና በጎ ፈቃድ አንዴት ይመራናል? እንዴትስ የኛ ድርጅት በትግራይ ቁጥጥር መሪነት አንዲውል አንፈቅዳለን!” በማለት ንትርክ ተፈጠረ ፤ በጣም ከፍተኛ ሁከት። …”።   ይላል ፕሮፌሰር ሙሴ ተገኝ።

 ኮለኔል ፍፁም እና ኢሳያስ አፈወርቂን አንድንወዳቸው እና እንድናመሰግናቸው ሲሰብከን የነበረው አንዳርጋቸው ጽጌ፤- ፕሮፌሰር ሙሴ ተገኝ የሻዕቢያ ምንነት በሚገባ ገልፆልናል።

ያውም ይላል፤- ፕሮፈሰር ሙሴ ተገኝ “ሻዕቢያ አርበኞች ግምባር የሚለውን መጠሪያችንን ቀይሮ ፤ አንዲሁም የሌሎችን ስም ቀይሮ በትግራይ ተዋጊዎች እና መሪዎች ስር አንደንመራ በማድረግ “ኢጥዴል” (EADC)
የኢትዮጵያዊያን ጥምረት ለዲሞክራሲያዊ ለውጥ) በማለት ትህዴን አንዲመራው ተነገረን። በሻዕቢያ ትእዛዝ የአዋጁ እና መተዳደሪያ ረቂቅ አንዲሁም ያዋጁ ሰንደቃላማ እና የጥምረቱ ዲዛይን  ሻዕቢያ አዘጋጅቶ ተግባር ላይ አንዲውል ተደረገ።  ብዙ ጭቅጭቅ አስነሳ። 

ቡድኖችም የሚከተሉት ሲሆኑ ሁሉም በ “ኢጥዴል” የተጨፈለቁ። አነሱም (1)ትህዴን (TPDM) “ብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት” ምናምን እያለ የወያኔዎች ቶን የሚመስል የሚዘላብድ ድርጅት ነው። ዛሬ አንደሚታወቀው (ዛሬ የሻዕቢያ ልዩ ተወርዋሪ ሃይል ተብሎ በኤርትራኖች የሚነገርለት እና ‘የትህዴን’ ባንዴራም የኢትዮጵያ ሆኖ እመሃሉ ላይ የአክሱም ሃውልት ያለበት ነው። (2)ኢሕአግ (EEPPF) (3) ቤህነን (BPFM) (ቤንሻንጉል)  (4) ደኢሕፍግ SEPJEF (ደቡብ ሕዝቦች)ናቸው። ይላል።


ፕሮፌሰር ሙሴ ተገኝ እየነገረን ያለው፤

የሻዕቢያ ዋና አላማ አራቱን ድርጅቶች አሰባስቦ፤ በአንድ ጨፍልቆ፤ ሻዕቢያ እያጠናከረልን ያለው ዘዴ/ሰትራተጂ የሚከተለው ነው ይላል። ‘ሌላው የሻዕቢያ ተላላኪ የሆነው በትግሬ ተዋጊ ሃይል ስር በትሀዴን ስር በመሆን በሂደት ተውጠን ‘አጀንዳ አስፈጻሚዎች” እንድንሆን፤ ሻዕቢያ ለወደፊቱ ሌላ ሁለተኛ የወያኔ ትግሬዎች አሻንጉሊት በማጠናከር ኢትዮጵያን ለመቆጣጠር እንዲያመቸው የራሱን ስልት እና አጋር ቡድን ለማጐልበት የጠነጠነው ስተራተጂካዊ  ስልት ነው።’ ይላል። እውነቱ ነው ፕሮፌሰር ሙሴ።


አርበኞች ግምባር ከኤርትራ ለመውጣቱ ዋናው ምክንያት የሆነው ይላል ፕሮፌሰር ሙሴ “ቢረባም ባይረባም 10 አመት ሙሉ ራሳችንን ችለን የኖርነውን ኢትዮጵያዊያኖች፤ በትግሬዎች ድርጅት ገብትን ተውጠን “ትህዴን” አንዲመራን መደረጉ ነው”። “ይህ ያደረገው ደግሞ እኛ ሳናወቀው ማእከላዊ አመራሩ ሳይሰበሰብ “ማአዛው” የተባለው መስከረም አታላይን የተካው የሻዕቢያ አስፈጻሚ ሆኖ የነበረው የግማባራችን ሃላፊ ተብሎ ሻዕቢያ የሾመው ሰው፤ የሻዕቢያ “ሪሞርክዮ” (ተሳቢ/ተጐታች መኪና) ተብሎ ቅጽል ስም የተሰጠው ማአዛው ነው።” ይላል።   

ስለ ኦነጐችም አንዲህ ይላል። ኦኖጎችም ሆኑ ኦጋዴን ነፃ አውጪዎች አብረን ተሰባስበን ነን ያለነው።  እና የኛ መስርያቤት ከአስመራ ከከተማው ትንሽ ወጣ ብሎ ያለው ስፍራ ነው፤ እኛ እና ኦነጐች ያለነው መስርያቤት “አንድ ቦታ ነን” አንጫወታለን ፤እንገናኛለን። እነሱ የሚደረስባቸው በደል በጣም ብዙ ነው፤ ከእኔ ይልቅ እነሱ ራሳቸው ቢነግሯችሁ የተሻለለ ነው።”ይላል።


(ታስታውሱ እንደሆነ ከጥቂት ወራቶች በፊት ብርሃኑ ነጋ  በቃለመጠይቁ ላይ “አርበኞች ግምባርን” አንስቶ “አርበኞች ግምባር የተባለ ተዋጊ ኤርትራ ውስጥ የለም። ካሁን ወዲህ ስለ እነሱ “ኢሳት” ምንም ዜና አንዳያነሳ ያነገረዋል!” ማለቱን ትዝ ይላችሗል?)። ለምን ይመስላችሗል? ሻዕቢያ ልክ የድሮው አርበኞች ግምባር በ “ትጥዴ” ለመጨፍለቅ አንደሞከረው ሁሉ፤ ዛሬም ግንቦት 7 እንዲመራው ያንኑ ስልት በአንዳርጋቸው እና በብርሃኑ ነጋ ተሞክሮ “አምቢ” ስላሉት እንደሆነ ምንም አያጠራጥርም። “ኤርትራዊ/ዐዘቦታይ(?)” ነው እያሉ አንዳንድ ሰዎች የሚጠረጥሩትን  በሞላ አስገዶም የሚመራው የሻዕቢያው ተወርዋሪ ሃይል “የትህዴን”  ቡድን አመራር እና ሰራዊት ለመቆጣጠር አንዲያመቸው “ግንቦት 7” ግምባር ፈጥረናል እያለ የነሱን መዝሙር እና ሰልፍ ሲያሳይ በግንቦት 7 ቱለቱላ ሚዲያው በኢሳት እየደጋገመ ሲያሳየን የነበረው ልብ ይለዋል። ለዚህም ነበር ሞላን እየደጋገመ በቃለ መጠይቅ ኳኩሎ “ሊሸጥልን” የሞከረው።  

ፕሮፌሰር ይህነን አስመልክቶ ገለጻው ይቀጥላል።

"ኤርትራ ውስጥ ሄደን በኢትዮጵያዊነት የተደራጀን ሁሉ የድምበር ጠባቂ ነው ያደረገን። ለምሳሌ “ወያኔ እና ሻዕቢያ” ዘወትር የሚፈላለጉበት አደገኛ የድምበር ቀጣናዎች “አይተርፍ” “ኩርባ ዲዳ”፤ “አንቶረ” “ማይ ጠብ” ወዘተ…በሚባሉ ፤ አደገኛ የድምበር ቀጠናዎች እኛን ሳያማክር በስልጣኑ፤ በጉልበቱ፤ ሻዕቢያ ሆን ብሎ እኛን እዛው ‘ወታደራዊ ካምፕ/ ቤዝ/ጣቢያ” መስርተን ፤ አንድንሰፍር አድርጎናል። ምን ለማድረግ? ደምበሩን ለመጠበቅ እና የመጀመሪያ ጥይት ቀማሾች እና “አብሪዎች” ሆነን አንድንሰዋለት እና አንድንከላከልለት ሆን ብሎ እዛው በሳተላይትነት/በአብሪነት መድቦን ነበር። አስር አመት ሙሉ ደምበር ጠባቂ አድርጎ ሲጫወትብን ኖሯል።” ይላል፡፤ ኤርትራ መሄድ የሚታየው እውነታ ሲያስረዳን።


አርበኞች ግምባር ተበሳጭቶ ግማሹ ሸሽቶ  እየጠፋ ብትንትኑ ከወጣ በሗላ የኢፒፒኤፍ ሰራዊቱ ባዶ ቀረ ። እነ አቶ ዘወድ አለም እና ስለሺ ጥላሁን ፤ግሩም ዘገዬ ከለንደን አርበኞች ግምባር ለመጎብኘት በመጡበት ጊዜ፤ ባዶ ስለነበር፤ ሻዕቢያ አጭር “ማልያ” (ከናቲራ) የለበሱ ከቲፒዲኤም/ ከትግሬዎቹ/ ሰራዊት ተበድሮ አርበኞች ግምባር በማሰመሰል፤ አቀረበ። በተንኰል ሰንደቃላማ እየተውለበለበ፤ ቀረርቶው ሁሉ እንዲያሰሙ ተደረገ። ያኔ ትግሬዎቹ ወደ 5 ሺሕ ተዋጊዎች ነበሩዋቸው። እኛ ግን በዛው ሁሉ አመት ኖረን፤ ሁለት/ሦስት መቶ ግፋ ከዚያ በላይ መውጣት አልቻልንም። ሆን ብሎ የሚመጡትን ተዋጊዎቻችን ወደ ሻዕቢያ እርሻ እያላከ “አዳክሞ” በኤርትራ ጠባቂዎች  አክላሽንኮቭ እየተጠበቁ በቀን 30 ናቅፋ እየተከፈላቸው አንዳንዱም በነፃ የሰቲት እርሻ እያሳረሰ
አዳከማቸው።

የሆኖ ሆኖ ሻዕቢያ የሚፈልገው፤ እኛም ሆነ ትህዴን በብዛት አሰልጥኖ ወያኔ ድምበር ለመጣስ ሲሞክር መጀመሪያ የሚዋጋለት ሰራዊት ትህዴን እና እኛ ነን። እዛው ድምበር በራሱ ትዕዛዝ የሚመድበንም ደምብሩ አንድንጠብቅለት ነው። ምክንያቱም ሻዕቢያ ተዋጊ ሰራዊት የለውም፤ አጅግ ተዳከሟል፤ ወኔ ያለው፤የጠነከረ ተዋጊ የለውም። ስለዚህም እነሱን በትህዴን እየተካ ይገኛል”።  ይለናል ፕሮፌሰር ሙሴ ተገኝ። "ስለዚህ ለኛ ሲል ያደረገው በጎ ነገር የለም። ሻዕቢያ እርግማን እና ውግዘት እንጂ ምስጋና የሚገባውም አይደለም"  ይላል ፕሮፌሰሩ።


ይህንን አስመለክቶ በተመሳሳይ በቅርቡ ከሕዝባዊ ሃይል ከሞት ያመለጠው የአንዳርጋቸው ጽጌ ሰለባ ወጣት ሽታው ሺፈራውም አንዳርጋቸው ጽጌ አሜሪካ ድረስ መጥቶ “ስለ ሻዕቢያ ምጋና አንደሚገባው እና እስካሁን ድረስ ነጻነታችን የዘገየው በኤርትራ በኩል መሽገው ለአመታት የተቀመጡ ፈዛዛ ተዋጊ ሃይሎች ስንፍና እና ዳተኛነት አንጂ  ሻዕቢያ “ፋይፍ/5 ስታር” ኰከብ በሚባል ለነፃነት ኢትግላችን ለምናደርገው ምቾት እና ድጋፍ ውስጥ እያስተናገደን ስለሚገኝ  “ሻዕቢያን አንውደድ፤እናክብረው፤ ‘ሻዕቢያ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ምስጋና” ይገባዋል። በማለት አንዳርጋቸው ጽጌ ስለ ሻዕቢያ አዛኝነት እና በጐ ስራ ሰሪነት አንድናመሰግን ሲማጸነን፤ የአንዳርጋቸው ጽጌ ሰለባ የሆነው ወጣት ሽታው ሺፈራው ግን በበኩሉ አንዲህ ይላል።


“በተለይ ደግሞ ትልቅ ፌዝ የሚሆነው ለዚህ የሻቢያ እኩይ ተግባር ምስጋናይ ገባዋል ሲባል ነው። ከፌዝም የሞኝ ፌዝ ማለት ይህ ነው። የገዛ መንግስታቸው ኤርትራኖች አንኳ ሳይቀር ያልወደዱት እኛ የምንወድበት ምን በወጣን? ሻዕቢያ ምንድ ነው የሰራልን?"  ይላል ወጣት ሽታው ሺፈራው።

ህዝባዊ ሃይሉ ከሌሎች ድርጅቶች በተለየ የሻቢያ ቸርነትን አግኝቶ የተመሰረተ እንዳልሆነ አንዳንድ ሃቆችን ማስቀመጥ ይቻላል። በተለይ ለአመታት በመዋጮ ተማሮ ቅሬታውን አምርሮ መግለጽ የጀመረውን በውጭ በስደት የሚኖረውን ዲያስፖራ የፖለቲካ ኪሳራ እና ተችሮት የተቋቋመ ለመሆኑ እና ከቸነፈሩ ለመዳን የተደረገ የተሎ ተሎ ይድረስ፤ የትግል ምስረታ እንደሆነ የቅርብ ግዜ ትዝታችን ነው።

ስለዚህ የግል ጥቅም ታሳቢ ያደረገ ካልሆነ በቀር የሻቢያ አቋም እየታወቀ ወደ ኤርትራ ለመሄድ የሚያስደፍር የሌሎች ድርጅቶች ተሞክሮም ሆነ የራስ ፖለቲካዊ ስብእና እንዳልነበረ በወቅቱ ውሳኔው ሲወስን በአንድ ሰው የበላይነት (በአንዳርጋቸው) የጸደቀውን በሌሎች ለይ ምሰል በተሰየሙት የስራ አስፈጻሚዎች ውድቅ የሆነውን ነገር ግን ተግባራዊ የሆነውን ውሳኔ ያስታውሷል።” ይላል ሽታው።

እንዲያውም “ህዝባዊ ሃይሉ ከተመሰረተ በኋላም ይታዩ የነበሩ ችግሮች የዚህ አይነት የድርድር ችግር ውጤት ለመሆናቸው ምንም አይነት ጥርጥር የለኝም።” ይላል ወጣት ሽታው ሺፈራው የሕዝባዊ ሃይሉሉ የአስተዳደር ክፍል ሃላፊ የነበረው።

ሽታው ስለ አንዳርጋቸው ምንነት ሰሞኑ የግንቦት 7 አድናቂ እና ደጋፊ ሚዲዎች የሆኑት. “ኢሳት፤ዘሓበሻ፤ ኢትዮሚዲያ….” አንደሚለቀልቁት ሳይሆን አንዳርጋቸውን በቅርብ ያወቀ እና አብሮ ባሕሪውን የተከታታለ ሽታው አንዲህ ሲል ይነግረናል።

በሻቢያ መርህ መሰረት መንቀሳቀስ ለይስሙላ የተዘጋጀው ድርጅታዊ ህገ ደንብ ተግባራዊ ያለመሆን፤አባላት በሻቢያ የጉልበት ስራ ላይ መጠመድ፤ለትግል ቆራጥ አላማ የነበራቸው አባላት በሆነ ባልሆነው ሰበብ እየተፈለገላቸው ብቻ መታሰር፤የተለመደ ክስተት ነው።….

…..በተለይ በአንዳርጋቸው በኩል ከፎቶ ግራፍ እና ከቪዲዮ ቀረጻ የዘለለ ስራ ለመስራት ያለመፈለግ፤ወደ አውሮፓ ለገንዘብ ስብሰባ ሲሄድ የሚለብሰውን ኮንጎ ጫማ ተሸክሞ ለመሄድ ጉጉት ያለበትን ያህል ሲመለስ ደግሞ ጠላት እንዳየች ጃርት የሸበተ ጸጉሩን እንጨፍርሮ ለሻቢያ ነው የማስረክባችሁ በሚል ስሜት ሁል ግዜም የሚገልጽ መሆኑ እና ሌሎችም ከሻቢያ ምድር ላይ የግድ ሊታጨዱ የሚገቡ ውጤቶች ሆነው ተገኝተዋል። በመሪዎች በኩል ያለውን ከወረቀትያልዘለለ የትግል ሞራል በማንሳት ትግሉ ከግለስቦች ጥቅም እና ከሻቢያ ፍጆታ የዘለለ ትርጉም የሌለው መሆኑን በተጨባጭ ስላየነው ድርጅቱ በፈጣን ኪሳራ ከመውደቅ አይድንም። ይህነን  ማስቀመጥም ይቻላል።”…

….ትንፋሽ ለትንፋሽ የመጠጋጋትን ያህል የሚጠይቅ ሆኖ ሳለ በሪሞት ኮንትሮል ትግል መምራት እና በገንዘብ ፍለጋ ሽፋን እያመካኙ በየውጭ እና አረብ አገሮች ኮንጐ ጫማ ተጫምተው ለማሳያ አገሩ ሁሉ ሊዞሩ  መፈለጋቸው፤ አንዳንዶቹ  ያውም በትርፍ ጊዜ ትግልን አሜሪካ እና አውሮጳ ተቀምጠው ለመምራት ሲከጅሉ ማየት የዋህ ታጋዮችን ከንቱ ጽዋ እና መከራ አንዲቀበሉ ከማድረግ አይዘልም።”


ስለ ሕዝባዊ ሓይሉ ያለበት ሁኔታም አንዲህ ያብራራል።

“የሻቢያ አቋም እና የሰዎችን ድብቅ አጀንዳ በአሳዛኝ ሁኔታ በቅጡ መረዳት የቻለው የሃይሉ አባላት ያለበትን ሁኔታ መግለጽ ተገቢ ነው የሚል እምነት አለ። አንድም ሆነ ሁለት የመልቀቂያ ደብዳቤ ያላስገባ ያለመኖሩ ቀዳዳውን ተጠቅሞ መውጣት የማይፈልግ አንድም አባል (ከአንዳርጋቸው ውጭ) ያለመኖሩ ነው።

ባለፈው ሁለት ወር አካባቢ እንኳን 16ሰዎች ጥበቃውን ሰብረው ማምለጥ መቻላቸው፤በዚህም አጠቃላይ የሰው ሃይሉ ወደ ግማሽ እንዲወርድ ማድረጉ ሌሎችም ቢሆኑ አንድም ሊያመልጡ ሲል ስላልተሳካላቸው እስርቤት የሚገኙ፤አለበለዚያም ሊያመጣ የሚችለው የፖለቲካ ኪሳራ ተፈርቶ በቁም እስር ላይ የሚገኙ መሆናቸው እና የመሳሰሉት በቦታው ተገኝተው የእነ አንዳርጋቸውን መሰሪነት ጠንቅቀው የተረዱ ውድ የኢትዮጵያ ጅግኖች እያስተናገዱ የሚገኟቸው ትይንቶች ናቸው።”
ይላል የአንዳርጋቸው ሰለባ ሽታው ሺፈራው።

ለማጠቃለል ያህል ዛሬ አንዳርጋቸው በወያኔ እጅ የመውደቁን ድንገተኛ ክስተት ተከትሎ ምሁራን ተብየዎች እና ጀሌ ሚዲያዎቹ አንዲሁም ተቃዋሚ ጻሀፊዎች እና አንዳንድ የፖለቲካ እና የስቪክ ድርጅቶች አልፎም “አክቲቪስቶች” እያስተጋቡ ያሉትን አንዳርጋቸውን በማዋብ ዘመቻቸው  የሚጠቀሙባቸው አስገራሚ ቃላቶች ስመለከት እነዚህ ሁሉ “ፍትሕን የሚረግጥ አንቃወማለን” እያሉ ሲለፍፉ፦ ፍትሕን ረግጦ ሻዕቢያን ተማምኖ ኢትዮጵያዊያን ለሰይል (ቶርቸር) እና ለግድያ፤ አንዲሁም ለጉልበት ሥራ ለሻዕቢያ ጨካኝ ገራፊዎች መጫወቻ አድርጎ አሳልፎ፤ ሲሰጣቸው የነበሩትን የአንዳርጋቸው ጽጌ ሰለባዎች ያስሰሙት የድረሱልን ዋይታ እሮሮ፤እምባ እና አቤቱታ ጀሮ ዳባ ብለው፤ ስለ ፍትሕ ምንንት ሲጮሁ መስማት አጅግ ይዘገንናል።


ይህንን አስመልክቶ፤ ከግንቦት 7 እና የሻዕቢያ አፈናና ግድያ በመከራ አምልጠው ከወጡት የህዝባዊ ኃይል አመራሮች አባስ/ ማስረሻ (የስልጠና ከፍል ኃላፊ) አና ኮስሞስ (የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ) ቴዎድሮስ ስዩም (ምኒሊክ) (የምልመላ ክፍል ላፊ) ሽታው (አስተዳደር እና ፈይናንስ ሃላፊ)፤ዳኒኤል፤አንተነህ፤ ወዘተ ወዘተ… የመሳሰሉ ታጋዮች አንዳረጋቸው ጽጌ ከሻዕቢያ ጋር በጠበቀ ሴራ እየተመሳጠረ፤ ጨካኝነት እና ጸረ ኢትዮጵያ እና ጸረ ሰብአዊነት ስብእናውን ያዩትን “በእኛ ይብቃ” በሚል
ፈው ያሰራ ትን መግለጫ፤ ሕሊና ላለን ሰዎች ያስደመመንን ሰነድ አስነብበውናል።


ሽታው ሽፈራው ለሦስት ወር ከዛፍ ጋር እየታሰረ ከጥዋት እሰከ ምሽት ለ 12 ሰዓታት አንድ ጊዜ ብቻ ውሃ እንዲጎነጭ እየተደረገ ሄሎኮፕተር/ወፌ ላላ እየተገረፈ ያሳለፈው መከራ በዝርዝር እንባ እየተናነቀው በቪዲዩ እና በድምጽ ገልልናል።

ይህንን የተመለከተ

 ለግንቦት 7 ሆነ ለሌሎች ተቃዋሚዎች ያለመተቸትን ከለላ ማን ሰጠ? የእነ “… ወይም ሞትፖለቲካ  (ያሬድ  ኃይለማሪያም) 

በሚል ትችት ከወደ አውሮጳ አካባቢ የሚኖር የሰብአዊ መብት ተሟጋች የሆነው ወጣት ያሬድ ኃይለማሪያም በፌብርዋሪ 2014 አንዲህ በማለት ያሰመረበትን ልጥቀስ እና ትችቴን ልደምድም።

“ከ1960ዎቹ የተማሪዎች ንቅናቄ ጀምሮ የአገራችንን ፖለቲካ የተጠናወተው “…. ወይም ሞትአስተሳሰብ ከአስርት አመታት በኋላም አለቅ ብሎን ዛሬም እኔ ከምደግፈው ፓርቲ ወይም የፖለቲካ ቡድን ወይም አስተሳሰብ ውጭ ያለው መንገድ ወይም አማራጭ ሁሉ ገደልና ሞት ነው ብለው የሚያስቡ ፖለቲከኞችና ዓጃቢዎችን ቁጥር በብዙ እጥፍ አባዝቶ ቀጥሏል። ደርግ ወይም ሞትየጀመረው የኼው የተወላገደ እና ጸረ-ዲሞክራቲክ የሆነው አስተሳሰብ ሳንወጣ ዛሬምወያኔ ወይም ሞትግንቦት 7 ወይም ሞትኦነግ ወይም ሞት ‘… ወይም ሞትበሚሉ ካድሬዎችና ስሜታዊ የድርጅት አምላኪዎች ተተክቶ እያደናበረን ይገኛል።  … ያለመታደል ሆኖ ከሃገር መሪዎች አንስቶ የፖለቲካ ተሿሚዎች፣ ካድሬዎችና ደጋፊዎች ለዚህ አይነቱ ኃላነፊት ብዙም ሳይጨነቁ ባደባባይ ያሻቸውን ይናገራሉ፣ የዘላብዳሉ፣ ይሳደባሉ፤ የሚጠይቃቸውም የለም። …

,…. ያጎለበትነው የፖለቲካ ባህል ቁጥራቸው ቀላል ለማይባሉ እጃቸው በንጹሃን ደም ለጨቀየ፣ በርሃብና በድህነት በሚሰቃየው ሕዝባችን ውድቀት ሞስነው ለጠበደሉ፣ በግል ህይወታቸውም ሆነ በሙያቸው ላልተሳካላቸው አዳዲስ እና ነባር ፖለቲከኞች መደበቂያ ጫካ ሆኗል። … 

ይልና ያሬድ 

" ከግንቦት 7 ሕዝባዊ ሃይል ታጋዮች እና መስራቾች የነበሩ ከኤርትራ ካንዳረጋቸው የሞት ገመድ ሸሽተው በየቦታው ተደብቀው ሕይወታቸው በስጋት አሁንም የሚኖሩ ዜጎቻቻን እሮሮ እና አቤቱታ አስመልክቶ በጻፈው ከላይ በተጠቀሰው ርዕስ ከአንባቢዎች ያገኘው አስተያየት በሦስት ከፍሎ አንዲህ ሲል ይገመግማቸዋል።

 “…  በዚህ ርዕስ እንድጽፍ ምክንያት የሆነኝ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይበእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ፤ የወያኔ ሳያንስ የነፃ አውጪዎቻችን (የግንቦት 7) የግፍ ተግባር እና የመገናኛ ብዙሃን ዝምታበሚል ርዕስ (ለጻፍኩት )ከአንባቢዎች የተሰነዘሩ አስተያየቶች ናቸው። …..”ሦስት አይነት ነቀፌታ አዘል አስተያየቶች ጽሑፌን አትመው ባወጡ ድኅረ-ገጾችና በማኅበረሰብ የመወያያ መድረኮች ላይ ተነበዋል።  ”…..በሦስቱ ጎራ ላሉት አስተያየቶች ምላሽ ልስጥ።” ይል እና በሦሰት አይነት የተከፈሉ አስተያየት ሰጪዎች ከዘረዘረ በሗላ ባስገረመው በአንደኛ ክፍል የመደባቸው የሰዎች ነጸብራቅ የታዘባቸውን አንዲህ ይገልጻቸዋል፤-

 “የመጀመሪያው አስተያየት ባነሳሁት ፍሬ ጉዳይ ላይ ያተኮረ ሳይሆን ብስጭትና ንዴት በተቀላቀለበት ስሜት ዝልፊያናዋናው የአገር ጠላት ወያኔ እያለ እንዴት ግንቦት 7 ትተቻለ ግንቦት 7 የነቀፈ ሁሉወያኔነው፣ ተቃዋሚዎችን መተቸትትግሉንያዳክማል፣ ተቃዋሚዎች ከነሃጢያታቸው መደገፍ ብቻ ነው ያለባቸው፣ ገፋ ብሎም ወንጀልም ቢሰሩ እንኳን ሊጠየቁ አይገባም ወያኔን እስከታገሉልን ድረስ የሚሉ ሃሳቦች የታጨቁበት ነው። እውነት ለመናገር ከእንደነዚህ አይነት ግራ ከተጋቡ ሰዎች ጋር ለመወያየት ያስቸግራል። ስለፖለቲካም ያላቸው ግንዛቤ ጥያቄ ውስጥ ይወድቃል። ከዚህ በፊት በሌሎች ጽሑፎቼም እንዳልኩት እነኚህ ሰዎች ገሚሱ በቅን ልቦና ለውጥን ብቻ ከመናፈቅ፣ ገሚሱም አዕምሯቸው በቂምና በበቀል ስሜት ተወጥሮ ፖለቲካውን መሳሪያ ያደረጉ፣ ገሚሶቹም ስለ ዴሞክራሲያዊ የፖለቲካ ባህል ያላቸው ግንዛቤ ውሱን ወይም የተዛባ በመሆኑ መፈክራቸው ሁሉግንቦት 7 ወይም ሞትኢሳት ወይም ሞት ወዘተ የሚል ነው። እነዚህ ሰዎች አዕምሮዋቸውን ከፈት አድርገው በፃነት እንዲያስቡ እና ከካድሬነትና ጭፍን ድጋፍ ወደ ሰላና በእውቀት ላይ ወደተመሰረተ የፖለቲካ ደጋፊነት እራሳቸውን እንዲያሳድጉ እመክራለሁ።”

ካለ በሗላ በሦስተኛ ደረጃ የመደባቸው አስተያየት ሰጪዎች (ሁለተኛ የመደባቸው ‘ወያኔ ነህ ብለውታል) ደግሞ እንዲህ ይገልጻቸዋል፡

“ሦስተኛው አስተያየት ኃላፊነት ከሚሰማቸውና የጉዳዩን ክብደት በቅጡ ከተረዱ ወገኖች የተሰነዘረ ነው። ይህውም ጉዳዩ የሰብአዊ መብትን የሚለለከት ስለሆነ በተበዳዮቹ ላይ ደረሱ ለተባሉት ጥቃቶች በቂ ማስረጃ አለህ ወይ? የሚል ነው። በመጀመሪያ እንኳን ለፍትሕ፣ ለዲሞክራሲና ለነጻነት እንታገላለን ያሉትን የፖለቲካ ኃይሎች ይቅርና አለም በሰብአዊ መብቶች እረጋጭነት ያወቀወን አንባገነናዊ የወያኔ ሥርዓት ለመተቸትም ሆነ ለመንቀፍ የሁል ጊዜ መነሻዬ ማስረጃዎች ናቸው። እንደ አንድ የሰብአዊ መብት ተሟጋች መረጃና ማስረጃዎች ያላቸውን ልዩነትም ሆነ ጠቀሜታ ጠንቅቄ ስለማውቅ ያለመረጃም ሆን ያለ ማስረጃ ማንንም ባደባባይ ለመውቀስም ሆነ ለመተቸት አልደፍርም። በተነሳው ጉዳይ ላይም በቂ ብቻ ሳይሆን ከበቂ በላይም ማስረጃዎችን መዘርዘር ይቻላል።” ሲል የግንቦት 7 የአንዳርጋቸው ሰለባዎች ክስ በበቂ ማስረዳት እና መረጃ አንዳለው መልሶላቸዋል።


በመጨረሻ የሕዝባዊ ሃይል ተዋጊዎች የነበሩ የአንዳርጋቸው ሰለባዎች እሮሮአቸውን እና በግንቦት 7 አመራር ላይ እያሰስሙት ያሉትን ክስ አንዳይደመጥ ሆን ብለው በማገድ (አሳት፤ዘሐበሻ ኢትዮ ሚዲያ፤ቋጠሮ… የመሳሰሉ የግንቦት 7 ስብስቦች )የሚባሉ ሚዲያዎች  የኔንም ጽሑፎች እና ምርምሮች ጭምር እንዳይነበቡ ከወያኔ በባሰ መልኩ እያገዱኝ ያሉትን የተቃዋሚ ሚዲያዎችን ላንዳድዶቹ እትችቱን እና ምሬቱን እንዲህ ሲል  ያጠቃልላል፦


“የፍረጃ ፖለቲካውን ፈርታችሁ ወይም እናንተም ’… ወይም ሞትየፖለቲካ አዙሪት ውስጥ ገብታችሁ አቋም ለያዛችሁትም ሁሉ እግዚያብሄር ለእውነት የምትቆሙበትን ልቦና እና መንፈሳዊ ወኔ ይስጣቸሁ በሚል ልሰናበት።” በማለት አንዳርጋቸውን ወደ ማንዴላነት፤ጋንዲነት፤ ክርስቶስነት እና ረቂቅ መንፈስነት እየለወጡብን ያሉትን ሚዲያዎች እና ጸሐፊዎቻቸው  ስለተቸበት  በሰፊው ስለ ሰብአዊ መብት ጉዳይ ጥልቅ አውቀቱን እና መረጃወን ለመመልከት ለግንቦት 7 ሆነ ለሌሎች ተቃዋሚዎች ያለመተቸትን ከለላ ማን ሰጠ? የእነ “… ወይም ሞትፖለቲካ  (ያሬድ  ኃይለማሪያም)  በሚከተለው አድራሻ ጐብኝቶ የወጣቱን ስራዎች ማየት ይቻላል።(http://humanrightsinethiopia.wordpress.com/) 

ተቃዋሚው እና ሚዲየዎቻቸው ከነጻሐፊዎቻቸው ጭምር የፖለቲካ አጭበርባሪዎችን ፤በክርስቶስ ተክለ ሰውነት መለወጥ እና ቀባብቶ ለመሸጥ የሞሞከር ልምዳቸውን ካላቆሙ ፤እኛም የንጹሓን እሮሮ እና ጩኸት ክስ ማስተጋባት ቀዳሚ ትግላችን ከማድረግ አንቆጠብም።

ያሬድ ሃይለማርያም እንዳለው፤  ደርግ ወይም ሞትየጀመረው የኼው የተወላገደ እና ጸረ-ዲሞክራቲክ የሆነው አስተሳሰብ ሳንወጣ ዛሬምወያኔ ወይም ሞትግንቦት 7 ወይም ሞትኦነግ ወይም ሞት ‘… ወይም ሞትበሚሉ ካድሬዎችና ስሜታዊ የድርጅት አምላኪዎች ተተክቶ እያደናበረን የሚገኘው መቆም አለበት።  … ያለመታደል ሆኖ ከሃገር መሪዎች አንስቶ የፖለቲካ ተሿሚዎች፣ ካድሬዎችና ደጋፊዎች ለዚህ አይነቱ ኃላፊነት ብዙም ሳይጨነቁ ባደባባይ ያሻቸውን ይናገራሉ፣ ይዘላብዳሉ፣ ይሳደባሉ፤ የሚጠይቃቸውም የለም። …

,…. ያጎለበትነው የፖለቲካ ባህል ቁጥራቸው ቀላል ለማይባሉ እጃቸው በንጹሃን ደም ለጨቀየ፣ በርሃብና በድህነት በሚሰቃየው ሕዝባችን ውድቀት ሞስነው ለጠበደሉ፣ በግል ህይወታቸውም ሆነ በሙያቸው ላልተሳካላቸው አዳዲስ እና ነባር ፖለቲከኞች መደበቂያ ጫካ ሆኗል..." እና ምሁራን ተብየዎች እና ጀሌ ሚዲያዎ አንዲሁም ተቃዋሚ ጻሀፊዎች እና አንዳንድ የፖለቲካ እና የስቪክ ድርጅቶች አልፎም “አክቲቪስቶች” መንገዳቸውን ያስተካክሉ። እንላለን። አመሰግናለሁ። ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያን ሰማይ ብሎግ አዘጋጅ) Google it “Ethiopian Semay”.  Email  getachre@aol.com