Sunday, May 30, 2010

ተቃዋሚዎቹ የሚፈተኑበት ፈተና የመፈተኛዉ ወቅት አሁን ነዉ

An electoral official removes campaign posters pasted on the iron sheet fence outside a polling centre in the capital Addis Ababa, May 22, 2010. Ethiopians vote on Sunday in the first elections since a disputed 2005 poll. Voters in sub-Saharan Africa's second most populous nation will be electing 547 parliamentarians. REUTERS

ተቃዋሚዎቹ የሚፈተኑበት ፈተና የመፈተኛዉ ወቅት አሁን ነዉ

ጌታቸዉ ረዳ www.Ethiopiansemay.blogspot.com

June 30, 2010

ዉጭ አገር ያለን ተቃዋሚ ክፍሎች አገር ዉስጥ የሚኖሩት የወያነ ተቃዋሚዎች በምርጫ 2002 (ግንቦት ወር) መሳተፍ አለባቸዉ መሳተፍ የለባቸዉም በሚሉ ንትርኮች ገብተን በተቃዋሚ መሪዎች ላይ ዘላፋዎች ተካሂደዋል። በሁኔታዉ ንትርክ ገብተን አቋማቸንን መግለጻችን ይታወሳል።

እንደሚታወቀዉ ምርጫዉ በወያኔ አጭበርባሪነት ተገባድዶ የሕዝብ ድምፅ ተዘርፎ በወያኔ የዉሸት ምርጫ አሸናፊነት ተደምድሟል። ምርጫዉ በወያኔ አጭበርባሪነት ሲደመደም ትግሉ አልተደመደመም። የምርጫዉ አጭበርባሪነት የሚያመለክተዉ ለመራራ ወሳኝ የመጨረሻ የሞትና የሽረት ትግል ጥሪ ነዉ ማለት ነዉ። ከምርጫዉ በፊት ተቃዋሚዎች ሁለት ዓይነት ተቃዋሚ እና ደጋፊ ነበርዋቸዉ። ወደ ምርጫ በመሳተፋቸዉ አንዱ ክፍል ደጋፊያቸዉ ነበር ምርጫ መሳተፍ የለባቸዉም የሚሉ ደግሞ ተቃዋሚያቸዉ እና ዘላፊአቸዉ ነበር። አሁን ግን አገር ዉስጥ ያሉት ተቃዋሚዎች የምርጫዉ ዉጤት በሚያስተጋባዉ ጥሪ ምክንያት በሚወስዱት እርምጃ ለነሱ በድጋፍ የቆሙት የተቃዋሚዎቹ ደጋፊዎች ሊያጧቸዉ ወይንም ደጋፊዎቻቸዉ ሆነዉ የሚቀጥሉበትን ሁኔታ ተፈጥሯል። ግልፅ ለማድረግ፦ ምርጫዉ በወያኔ አጭበርባሪነት እንዲደመደም ካደረገ ድምጽቻዉ የተነጠቁ ተቃዋሚዎች ከባድ ፈተና ያለባቸዉ መሆኑና ፈተና የመፈተኛ ወረፋቸዉ አሁን ሆኖ ፈተናዉን በሚገባ ለማለፍ ዝግጁነታቸዉ በተግባር የሚያሳዩበት ወጣሪ የመፈተኛ ዓዉድማ ተንጣሎ እየጠበቃቸዉ ስለሆነ ሲደጉፏቸዉና ጥብቅና ቆመዉ ሲደግፏቸዉ የነበሩት ደጋፊዎቻቸዉ እንዳያጡ በብርታት ፈተናዉን ማለፍ ይጠበቅባቸዋል።

ከፊታቸዉ ተንጣሎ እየጠበቃቸዉ ያለዉ ከባድ ፈተና ካላለፉት ለታሪካቸዉ እና ለዝናቸዉ መጥፎ ስዕል ትቶ የሚያልፍ መሆኑን መረዳት ይገባቸዋል። ምርጫዉ እንዲጭበረበር መሪዎችም እኛም እናዉቅ ነበር። ሆኖም ወደ ሚጭበረበር ምርጫ እንዲገቡ የገፋፋናቸዉ ዓይነተኛ ምክንያት፤ የተጭበረበረን ምርጫ መረጃ እና ምክንያት ተጠቅሞ ሕዝቡን ለፍትሕ ጥያቄ በማነሳሳት ወያኔ ለመጨረሻ ጊዜ ከስልጣን የሚሰናበትብትን ሕዝባዊ አመጽ/ሰላማዊ አመጽ እንዲቀሰቅሱ በር ይከፍትላቸዋል በሚል ነዉ። ወቅቱ ደግሞ አሁን ነዉ። የተጭበረዉን ምርጫ ትግራይን ለምሳሌ ብንመለከት፦ ትግራይን ከሚገዙ የወያኔ ፊዉዳላዊ ቡርዧ /ተወልጄዎችና የከበርቴ ተናብልት (የከበርቴ መኳንንት) ተወካይ የሆነዉ ሃለቃ ጸጋይ በርሄ ስለምርጫዉ አንስቶ ራሳቸዉን ላሞኙት ዉጭ አገር ላሉ ገለባዎቹን ባዘጋጁለት “የ ኢንተረኔት-ፓል ቶክ” ምርጫዉን አስመልከቶ ስለ ሰጠዉ ቃለ መጠይቅ ለምርጫ የተመዘገበዉ የመራጩ ሕዝብ ብዛት 2, 017,695 (ሁለት ሚሊዬን አስራ ሰባት ሺህ ስድስት መቶ ዘጠና አምስት) ሲሆን ከዚህ ዉስጥ 1,098218 (አንድ ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ሰማንያ ሁለት ሺሕ አስራ ስምንት) ሕዝብ ድምፅ የሰጠ ሲሆን ከነዚህ ዉስጥ 98.6% (99%) በመለስ ዜናዊ የሚመራዉ የወያነ ትግራይ ድርጅት ድምፅ አግኝቷል ሲል በክፍለ ሃገሩ ዉስጥ 6 ድርጅቶች እና አንድ በግል የቀረበ ተወዳዳሪ በድምሩ 7 ተቃዋሚዎች ያገኙት ድምፅ 30,000 (1%) እንደሆነ ያለ ምንም ሃፍረት በመኩራራት ገልጿል። ከ7 ተቃዋሚዎች ዉስጥ 5ስቱ ያክል ምርጫዉ ያለ ምንም ማጭበርበር ሕጋዊ እና ሰላማዊ ሆኖ እንደተከናዋነ ፌርማቸዉን እንዳኖሩ ገልጿል። እነ ስየ እነ ገብሩ በዚህ ፌርማ ይኑሩበት አይኑሩበት የታወቀ ነገር የለም። የመ ኢአድ ተወካይ ወ/ሮ መሰሉ ረዳ ግን ከምርጫዉ በፊትም በምርጫዉ ወቅትም የምርቻዉ ስርዓት ሕግ የጣሰ እና ማስፈራራት እና በማጭበርብር የተከናወነ እንደነበር ከትናንት በስቲአ ማለትም በዓርብ ዕለት ከየአሜሪካ ድምፅ ራዲዬ የ አማርኛዉ ክፍል ከጋዜጠኛዋ ከ/ወ/ሮ አዳነች ፍስሃየ ጋር ባደረገቺዉ ቃለ መጠይቅ ከሰጠቺዉ መረጃ ለማረጋገጥ ይቻላል። እነ ስየ አልተጭበረበረም ብለዉ ፈርመዉ ከሆነ ምንም ማለት አይቻልምና ሂሱ ለደጋፊወፐቻቸዉ መተዉ ነዉ። ተጭበርብሯል በማለት ፀጋይ በርሄ እንዳረጋገጠዉ አሃዝ በማጭበርብር የተገኘ አሃዝ ነዉ የሚሉ ከሆነ ደግሞ ፡ ይህ አሳፋሪ በስርቆትና በማስፈራራት የተከናወነ የድምፅ ዉጠት መፈጸሙ ካመኑ ደግሞ እነ ገብሩም ሆኑ እነ ስየ ከሌሎቹ ተቃዋሚዎች ጋር የሚጠበቅባቸዉ ቀጣዩ ፈተና በምን ሁኔታ ይወጡት ይሆን የሚለዉ ወጣሪ ሁኔታ ከሚከተሉት የትግል ስልት የምናየዉ ይሆናል።

መንም እንኳ 99.9% የሕዝብ ድምጽ አገኘሁ እያለ የራሱን ሞኞቹን ቢያሞኝም ያጭበረበረ መሆኑን ዉስጡ ስለሚያዉቅና በተለይም 18 ዓመት ሙሉ በስልጣን ሲቆይ ለሕዝቡ ባዕድ በመሆኑ ፡ ራሱን በቴ/ቪዢን መስኮት ብቅ አድርጎ ከመታየት ሌላ ከሕዝቡ ጋር ወዳጅነት ስላልመሰረተ እገደላለሁ ብሎ ሰለሰጋ “ጥይት የማይበሳዉ” የነብስ መከላከያ የመስተዋት ማማ (Booth) ባደባባይ አስተክሎ በብዙ ሺህ ብር ወጪ በተሰራችለት መስተዋቷ ዉስጥ በመግባት እንደ ጥንቸል ተቆልፎበት ስለ ዘረፈዉ የህዝብ ድምፅ ለማብራራት ያዘጋጀዉን ጽሁፍ ሲያነብብ የተመለከቱ ተቃዋሚዎች የሕዝቡን መብት ለማስከበር ሕዝቡን ለሰላማዊ አመጽ በማነሳሳት መለስ ዜናዊ መስተዋት ዉስጥ ራሱን ከመሸሸግ አልፎ ሌላ ያላየነዉ አስቂኝ እና አስገራሚ የድንጉጦች እዉነተኛ ባሕሪይ በድጋሚ ተደናብሮ እንዲሸሸግ ለዓለም ሕዝብ የሚያሳዩበት ወደ ከባዱ ፈታኝ አዉድማ አሁኑኑ ዘለዉ መግባት ይህ ጸረ ኢትዬጵያ ግለሰሰብ ከተሸሸገበት መስተዋት እንዲወጣ እና ለፍትሕ እንዲያቀርቡት ይመች ዘንድ የተቃዋሚዎች ጥራት እና የትንካሬ ማንነት የሚገልጹበት ተቃዋሚዎች የሚፈተኑበት የፈተና ወቅት አሁን ነዉና ፈተናዉን በልበ ሙሉነት በመጋፈጥ በኩራት ተወጥተዉ ታሪክ በመልካም ስም እንዲያነሳቸዉ ያድርጉ። ይህ በሚያከናዉኑበት ወቅት ቅማችንን ሁሉ በመለገስ ከጎናቸዉ የምንቆም መሆናችንን በድጋሜ ቃል እንገባለን።

ገሥጾሙ፤ ለአራዊተ ሃለት።ማሕበረ አልሕምት ዉስተ ዕጓላተ፤ሕዝብ። ከመ ኢትዐጸዉ፤ እለ ፍቱናን ከመ ብሩር።ዝርወሙ፤ለአሕዛብ፤እለ ይፈቅዱ፤ቅትለ፤ ይምጽኡ ተናብልት፤ እምግብጽ። አትዮጵያ ታበጽሕ እደዊሃ ሃበ እግዚአብሔር።

(በሸንበቆ ዉስጥ ያሉትን አራዊት ፤ በአሕዛብ ዉስጥ ያሉትን የበሬዎችንና የወይፈኖችን ጉባኤ ገሥጽ። እንደ ብር የተፈተኑትን አሕዛብ እንዳይዘጉ፤ ሰልፍን የሚወዱትን አሕዛብን በትናቸዉ። መኳንንት ከግብጽ ይመጣሉ፤ ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች።) የኢትዮጵያ ሰማይ ድረ ገጽ አዘጋጅ ጌታቸዉ ረዳ www. Ethiopiansemay.blogspot.com

Wednesday, May 26, 2010

ወያነ ትግራይ የሞት ሞቱ ያየበት የዲሞክራሲ ፌስታ! ጌታቸዉ ረዳ (ግንቦት17/2002) June 26/2010 http://www.ethiopiansemay.blogspot.com/

የወያነ ትግራይ ወንጀል ፋይሎች ክፍት ናቸዉ። ትንንትም ዛሬም ለነገም ክፍት ናቸዉ። ሞልቷል፤ተትረፍርፏል። ወያኔ ዘንድሮም በለመደበት ዉሸት እና ወንጀል በተካነበት ዘራፊ ባህሪዉ ስልቱን በመዘርጋት የዘንድሮዉንም ምርጫ ሳያሸንፍ አሸንፍኩ በማለት “የጠላቶቻችን ተቀጣሪ”-የሆነዉ መለስ ዜናዊ በመስቀል አደባባይ/አብዬት አደባባይ ተብሎ በሚጠራዉ በአዲስ አበባ የሕዝብ መሰብሰብያ ሜዳ ዉሸቱን ባደባባይ ሲዘላብድ በጆሮቸዉና በዓይናቸዉ ለማየት የተገኙና እንዲሁም “ለእሱ ያደሩ ታጋዬች እና ቤተሰቦቻቸዉ፤ከያቅጣጫዉ ያሰባሰባቸዉ በጎሳ ፤ባምቻ ጋብቻ በቋንቋ ፤በቆዳና በክልል መተዳደር የመረጡ ጠባብ ብሄረተኞች ፤ እና በተለያዩ ዘርፎች ያደሩለት አገልጋዬቹና እንዲሁም ሲያስነጥሰዉ መሃረም የሚያቀብሉት አፍረተ ቢሶች በመሰብሰብ” የዘላበደዉን የአሸነፍኩ ዉሸቱን ለማዳመጥ በተጠራዉ የዉሸት መድረክ በተናገራቸዉ ነገሮች ላይ በተከታታይ ሰሞኑን ስለምንሄድበት ለዛሬ አንድ የምላችሁ አግራሞቴን የሳበዉ በሚቀጥለዉ የምንመለከታቸዉ ንግግሮቹ ላይ ይሆናል።የዚህ ሰዉ ሕይወት ስገመግም ሰዉ ከሚገባዉ በላይ ረዢም ዕድሜ ይኖራል ያለዉ የጁልየስ ቄሳር አባባል ያስታዉሰኛል ።በትግርኛዉ “እግዜሔር ዝፈንፈኖ” (እግዚአብሔር አልወስድህም /አልገድልህም ብሎ ለመሬት ስቃይ የተወዉ” እንደሚሉት ነገር። ዕባብ አከላቱ ተቆራርጦ ወገቡ ተቆርጦም ቢሆን ሲንቀሳቀሱ እናያለን፤፡ አዎን እኛ አበሾች ወይንም ማን እንዳለዉ አላዉቅም በዛሬዉ አነጋገራችን “አምባገነኖች እንደ ድመት ዘጠኝ ህይወት አላቸዉ”የምንለዉ ነዉ ሮማዊዉ ጁልየስ ሴዛር “ሰዉ ከሚገባዉ በላይ ረዢም ዕድሜ ይኖራል” ለማለት የፈለገዉ። ሰዎች ከወንጀላቸዉ ብዛት (በስልጣን ከለላ ፤በጉልበት፤በሕዝብ ስም ተጠልለዉ ለሰሩት ወንጀል ሳይጠየቁበት)ወይንም ከሚበዛባቸዉ ስቃይ ምክንያት መኖር የሚገባቸዉን ህይወት መቀጨት ሲኖርባት (የአልጋ ቁራኛ ሆነዉ በድን አካል ይዘዉ ትንፋሻቸዉ ብቻ መተንፈስ የቻለች)የምታቃስት ህይወት መሞት ሲገባት ከሚገባት በላይ ትኖራለች ማለቱ ነዉ። የወያኔ መሪዉ ትናንት በዛዉ አደባባይ የተናገረዉ የቱልቱላ /ፕሮፓጋንዳ ንግግሩ ላዳመጠ “ጤነኛ ሕሊና”ላለዉ አድማጭ የሚደርስበት ግምገማዉ ቢኖር “ይህ ሰዉ ለሰራዉ ቅጥፈት እና ወንጀል ዉስጣዊ ሕዋሳቱ ምንኛ እየተፈታተነዉ እና እየተሰቃየ እንደሆነ ካዘጋጀዉ ጽሁፍ ከሚያንብባቸዉ የዉሸቶች ዓረፍተነገሮች፤መዋሸት ከሚገባዉ በላይ እየዋሸ በድን አካላቱ ተወጥራ መኖር ከሚገባዉ በላይ እየኖረ እንደሆነ ከአንደበቱ ከሚያ’ሰማዉ ሲቃ መገመት ይቻላል”።መለስ ዜናዊ በእንዲህ ዓይነት ዉሸት ተከብቦ ሲደመጥ የምንደመድመዉ አጠቃላይ ግምገማ ምንድ ነዉ? መለስ ዜናዊ ከሚገባዉ በላይ እየዋሸ እንደ “ሞሶሎኒ”በትምክህት ተወጥሮ በቆለለዉ ዉሸት መዳከሩ የሚያመላክተን ነገር “ሕይወትን ስለወደዳት ሳይሆን፡ ከእዉነት እየሸሸ “ሞትን/ቅጣትን”መፍራቱን ያመላክታል”። ትናንት ከአነበበዉ ወረቀት የተደመጠዉን እስኪ እንመልከት፦ “ይሁንታችሁን ያልሰጣችሁን ዜጎች ቅር ያሰኘንበት ምክንያት አጥንተን ለማስተካከል እንደምንረባረብ፤ በሚቀጥለዉ ጊዜ ይሁንታችሁን ለማግኘት ሌት ተቀን እንደምንጣጣር እስከዛዉ ድረስ ደግሞ የምናቋቁመዉ መንግሥት የመረጠንን ህዝብ ብቻ ሳይሆን እናንተንም በእኩልነት እንደሚያገልግል በድርጅታችን መላ አባልት እና ሰማዕታት ስም ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ።” (መለስ ዜናዊ ከተናገረዉ ያደባባይ ዉሸቱ “ከአዲስ አበባ የቀጥታ ስርጭት”በሚል በወያኔ ጋዜጠኞች የተላለፈዉ የድምፅ ቅጅ ምርጫ ግንቦት 17 2002/ በፈረንጅ May 25/2010)።ይህ ዉሸት መለስ ዜናዊ የሚዋሸዉ ዉሸት ብቻ ሳይሆን ከሱ ጋር የነበሩት የወንጀል ድርጊት ተጋሪ ግበረ አበሮቹ ዛሬ በአንዳንድ ምስኪኖች “መሪዎች እና ተቃዋሚ” የሚል ስም የተሰጣቸዉ እነ ስየ አብርሃ፤ገብሩ አስራት፤አረጋሽ አዳነ፤ ነጋሶ ጊዳዳ፤ እና ወዘተ…ሰልጣን ላይ በነበሩበት ወቅት ሲለፍፉት የነበረዉን የዉሸት ባህሪ ነበር የደገመዉ። ሁሉም በጭንቀት በጭንቀት ዓለም ተወጥረዉ እንደሚኖሩ እናዉቃለን። ይህ በድርጊት የማየተረጎም “እኩል እናገለገልሃልን” ቱልትላ የሚያሳየን ባህሪ እነ መለስም ሆኑ ከላይ የተጠቀሱት የድሮ የመለስ ጃንደረባዎቹ የፈጸሙትን የወንጀል ድርጊት ከባድ በመሆኑ “በይፋ ተገልጦ እንዳይወጣ እጅግ ይጠነቀቃሉ”፤ ይፈራሉንም። እነኚህ ሰዎች ቅጣንና ሞትን የሚፈርዋት መሆናቸዉ በዉስጣቸዉ ፍርሃትን ያነገሰበት አንደበት ከሚሰነዝሩት የንግገር አንደበት ማወቅ ይቻላል።በጣም የለሰለሰ፤ ለሕዝቡ አክብሮት ያለዉ የሚመስል ግን “በድርጊት የማይፈጸሙት” እንደሆነ በተደጋጋሚ የታየ ጉዳይ ነዉ። መለስ በተቃዋሚዎች ላይ ያስሰማዉ ንቀት፤ማንቋሸሽ፤የተጠቀመበትን “ከዚህ ተማሩ፤ ኑ እናስተምራችሁ…”ፍጸማዊነት እና የትምክህት አንደበት የሚያመለክተዉ ነገር ዉስጣዊ መንፈሱ የተረበሸ አንደሆነ ይጠቁማል። ሁሉም ማለት ይቻላል (እነ ስየ፤ እነ ብርሃነ ፤እነ ገብሩ..ጨምሮ ) በዛች አገር ሕዝብ እና ሉዓላዊነት ለሰሩት ወንጀል ዘርዝሮ ላለመናገር፤ላለመናዘዝ፤ያዩትን ወንጀል ላለመጠቆም በስልጣናቸዉ ቀንብር ስር “ማን ምን”-ግፍ እንደደረሰበት እና እንደተከናወነ፤ለፈጸሙትና ላስፈጸሙት ላለመግለጽ “ ይከሱናል ፤የቀዋሙናል፤በሕግ ይፋረዱናል”የሚሏቸዉን ክፍሎች ዝናቸዉን በማጥፋት/በማንኳሰስ ታጥረዉ የራሳቸዉን ስዕል ላለመግለጽ እጅግ ይጠነቀቃሉ። እያድበሰበሱ ለመሸሽ ይጥራሉ። ለነሱ ያደሩ፤በመንገዳቸዉ የተጓዙ ወይንም ህልናቸዉ በቀላሉ በሰሜት ተገዝቶ የሚታሉ ግለሰቦችን በመሰብሰብ/በማደራጀት ከሚፈርዋት ሞትና ቅጣት ይሸሻሉ። በእንደዚህ ያለ ስልት የመጓዙ ችሎታ ያወቀበት መለስ ዜናዊ ብቻ ሳይሆን መድረክ ዉስጥ የታቀፉት ጃንደረባዎቹም ጭምር “ብዙ የዋህ፤ብዙ ተላላ ኢትዬጵያዊ”-በየዓለማቱ ተስፋ ቆርጦ መሪ አጥቶ የሚያንቀራፋ ማሕበረሰብ እንዳለ እና እንደሚከተላቸዉ ከትግሉ በፊት ጀምሮ የሕዝቡን ደካማ ብልቱን ስላጠኑት በሕልም እያቃዠ ከሚያባርራቸዉ ከሕሊናቸዉ ብቻ “እየሸሹ”በጋሃድ ግን “እዉነትን እየተከተሏት”እንዳሉ እያታለሉ የሞት ሞታቸዉን ሲሞቱ በቁም እየታዘብናቸዉ ነዉ።ከላይ የታዘብነዉ የመለስ ዜናዊ ዉሸት እና ቃል ኪዳን እዉነትን ምንኛ በዉሸት ቢላዉ እየቆራረጠ እየጣላት እንደሆነ ነዉ። ያልመረጠዉ ሕዝብ እንዳለ አዉቋል። ቅር የተሰኘ ሕዘብ ደግሞ በራሱ የድምጽ ማጭበርበርያ ሰንጠረዡ ከመቶ ሕዝብ ምናልባት “ነጥብ አንድ”-እንበለዉ “አንድ-ብቻ”-ነዉ ቅር የተሰኘዉ እና ያልመረጠኝ ብሎናል (.1%)። እንግዲህ ከመቶ ሰዎች አንድ ሰዉ ብቻ በወያኔ የክህደት እና የወንጀል የገበና ማህደር ቅር ከተሰኘ “መለስ ዜናዊ ልጆቻቸንን ከበረሃ ጀምረህ ከግብራበሮችህ ጋር አሁን አስካለህበት ጊዜ ድረስ ገድለሃል፤ አሰገድለሃል፤ብሔራዊ ወንጀል ፈጽመሃል፤በስልጣን ባልገሃል፤ገንዘብ መዝብረሃል፤እንዲመዘበር አስደርገሃል፤ፈጽመሃል፤አስፈጽመሃል፤በሌላ ፍጡር ጉዳት እንዲደርስ አስደርገሃል፤አገሪቷን ለጠላት ክፍት በማድረግ ብዙ ሕይወት እንዲያልቅ ምክንያት ሆነሃል፤ብዙ እናቶች ባንተ ትዕዛዝ እንባቸዉ አቅርረዋል፤….እና ተጠየቅ!.”የሚሉ ክሶች እንድንመሰርት እንችል ዘንድ ተደጋግሞ ለ18ዓመት የጠየቅነዉን “አንተ እና መሰል ባልደረቦችህ ተከሳሾች መንግስትህና ድርጅትህ የማይቆጣጠሩት “ልዩ” ገበና ፈታሽ እና የፍርድ መድረክ፡ እንዲቋቋም ፈቀደኛነትህ አረጋግጥልን”ቢባል መልሱ ምን እንደሚሆን ለናንተ ግልጽ ይመስለኛል። እንኳንና መለስ ዜናዊ ስልጣን ላይ ያለዉ ቀርቶ ከወያኔ ስልጣን የተለዩት እነ ስየ እነ ገብሩ ደም በታጠበዉ እጃቸዉ እና ገበናቸዉ “እየሰጡት ያለዉን የመሸሽያ መልሳቸዉን”መገንዘብ ትችላላችሁ።
ዓለም በዉሸት ጎዳና መራመድ ለምዷታልና ምድሪቱ በዕዉነት ጎዳና እንዳትጓዝ ብዙ “ዉሸተኞች” መድረኩን በመቆጣጠር ሕዝቡ ከዉሸት ጎዳና እየሸሸ” ጉዞዉን ቀይሮ “በዕዉነት ጎዳና”-እንዳያደርግ ብቻቸዉን እንዳይቀሩና እንዳይጋለጡ በዉስጣቸዉ ፍርሃት ያነገሰዉን ዉሸት አየዋሹ ዛሬም በዛዉ የዉሸት ጎዳና ሲሮጡ ልባቸዉ አስሬ ሲመታ ይደመጣል። ለዚህም ነዉ መለስ ዜናዊ በዛዉ ፍርሃት ባነገሰዉ ዉስጣዊ ፍርሃቱ በአገርና በሕዝብ ላይ በፈጸማቸዉ እጅግ ከባድ፤ ከባድ ወንጀሎች እሱ እና በተቃዋሚ ጎራ የተሰለፉት ጃንደረባዎቹ አንድ ቀን ለፍርድ መቅረቡ እንደማይቀርለት ስለሚያዉቅ “አሁንም ሕዝባችንን ቅር የሚያሰኙ በርካታ መሠረታዊ ጉድለቶች እንዳሉብን በጥልቀት እንገነዘባለን”-ሲል ጃንደረባዎቹ በተቃዋሚ ጎራ ሆነዉ እየተናገረዉ ያለዉን የድላ ቃላት በቃል ብቻ እነሱም እንደሚደሉሉን ሁሉ እሱም ያንኑ መደለያ “ሕዝብችንን ቅር ያሰኙ በርካታ ጉድለቶች. እንደፈጸመን በጥልቀት እንገነዘባለን” ሲል ተጠያቂነት የሌለዉ የድለላ ቃል ትንናት “የዲሞክራሲ ፌስታ”-ብሎ በሚወዳቸዉ የልብ አማካሪዎቹ በጣልያኖቹ ቋንቋ በሰየመዉ “ፌስታ” *መሠረታዊሲ ወንጀሎች* እንደፈጸመና “ጉድለት ብሎ የጠራዉ ወንጀሉን *በጥልቅ እንደተገነዘበዉም* በኑዛዜ መልክ የተናዘዘዉን አስደምጦናል።ሕዝባችንን ቅር የሚያሰኙ በርካታ መሠረታዊ ጉድለቶች እንዳለበት በጥልቀት ከተገነዘበ ማድረግ ያለበት “የሕዝቡን ቅሬታ ለማጥናት እና ቅሬታዉን ለማዳመጥ በሰማዕታት ስም ቃል ገብቻለሁ” በማለት በለመደበትን የወያነ የዉሽት ባህሪ “ትሬድ ማርክ/መለያ” ከመፏከት መጀመርያ ማድረግ ያለበት “ይህ ይህ ወንጀል እኔ እና ጓዶቼ እንዲፈጸም አድርገናል፤ ዛሬ ተምረናል፤ ለዚህ ደግሞ ተገቢዉ ቅጣታችን ለማግኘት በደል ያደረስንባት አገር እና ሕዝብ፤ሰዎች እና ድርጅቶች በሚፈቅዱት ፍትሕ ሰጪ አካል ተምርምረን ቅጣታችንን ለማግኘት ዝግጁነታችን በሰማእታት ስም ቃል የገባንበትን ዉል ይሄዉ ሕይወታችን በናንተ ላይ ጥለናታልና ኑ ፍረዱን”፡ -ማለት ነበረበት። ነገር ግን እሱም ሆነ ግብረ አበሮቹ በወንጀል፤ የሺሕ ነብሳት ሕይወት እንድትጮህ ያደረጉ ፤ ነብሰ ገዳዬች እና እርኩስ መናፍስት ናቸዉና፤ ሞትና ቅጣትን ስለሚፈሩ “ዛሬ ወይንም ነገ ባጭር ለምታልፈዉ ሕይወት”ለእዉነት ሲል “ሞትና ቅጣትን”የማይፈራ ፍጡር አንድም (አስገደ ገብረስላሴ እና ገብረመድህን አርአያን ሳይጨምር)ከማሃላቸዉ ስለሌላቸዉ ትናንትም ዛሬም ነገም ዉስጣቸዉ ፍርሃት ባነገሰዉ ዉሸት መዋሸትን መምረጣቸዉ የሚያመላክተዉ ቢኖር ዛሬ መለስ ዜናዊ በ99.9%ድምፅ ተመርጫለሁ ሲለን ወያነ ትግራይ የሞት ሞቱ ያየበት ይህ የመጨረሻዉ የፍርሃት ጠርዝ የነካበት ወቅት መሆኑን ላሰምርበትእፈልጋለሁ።/_/-/-/http://www.ethiopiansemay.blogspot.com/ getachre@aol.com

Saturday, May 22, 2010

የቀይ ሽብር ወንጀለኛዋ የመለስ ካቢኔ ፀሓፊ

የቀይ ሽብር ወንጀለኛዋ የመለስ ካቢኔ ፀሓፊ ከኢየሩሳሌም አርአያ

የኢሕአፓ አንጋፋ አባላትአሸናፊ ለማወይንም በቅጽል ስሙአሸናፊ ጐላ ጠንቅቀዉ የዉቃሉ።ታሪኩን ጠንቅቀዉ ያስታዉሱታል የሚል እምነት አለኝ። ኢሕአፓ ታዋቂ አባል እንደነበረ በስፋት የሚነገርለት አሸናፊጐላተወልዶ ባደገበት አዲስ አበባ ልዩ ስሙ ቤላ ወረዳ 12 ቀበሌ 18 ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ በ1970 ዓ.ም ከመኖርያዉ አቅራቢያ በግምት በመቶ ሜትር ርቀት በደርጎች በጥይት በግፍ ተደብድቦ ነበር የተገደለዉ። በማሃል ኣናቱ በጥይት ተቦድሶና በሚዘገንን ሁኔታ አንጎሉ ተዘርግፎ በአፍ ጢሙ ተደፍቶ

የአካባቢዉ ሕዝብ ቀኑን በሙሉ እንዲያየዉ የተደረገዉ ታጋይ አሸናፊ በእስር ላይ እያለ ከፍተኛ ድብደባ (ቶርቸር) እንደተፈጸመበት በተዘረጋዉ ሬሳዉ ያለመጫሚያ ይታዩ የነበሩ የዉስጥ መዳፍ እግሮቹ ይመሰክሩ ነበር። መዳፎቹ በግርፋት ብዛት ቆስለዉ ከመገርጠታቸዉ ብዛት ኩፉኛ ተላልጠዉና ተቀራርፈዉ እንደነገሩ ተጣብቀዉ ተንጠልጥለዋል። በቅርብ የሚያዉቁት ጓደኞቹ እና የትግል አጋሮቹ “ጎላ” እያሉ የሚያወሱት ይህ ታጋይ ለሦስት ወራት አሰቃቂ ድብደባ እና ስቃይ ሲፈጸምበት አንድም ምስጢር ሳይተነፍስ እንደተገደለ የሚጠቁሙ እነዚህ ወገኖች ከዚህም ባለፈ በወቅቱ አብረዉት ታስረዉ በርካታ ወጣቶች “ከኢሕአፓ ጋር ምንም ግንኙነት የላቸዉም” ሲል እንደተናገረ እና ብዙዎቹ በሕይወት ሊተርፉ እንደቻሉ አያይዘዉ ይገልጻሉ።

በተጠቀሰዉ አካባቢ የነበረዉ የኢሕአፓ እንቅስቃሴ አሸናፊ ብቻዉን ያከናዉን እንደነበረ ለሰዉ በላዎቹ ደርጎች በመግለጽ ስቃዩን እና ሞቱን ለብቻዉ ተጎንጭቶ ማለፉን የመረጠ ጀግና ነዉ ሲሉ ያክላሉ። ድንቅ እና ብሩህ ኣእምሮ ለተቸረዉ አሸናፊ ለወላጆቹ ብቸኛ ልጅ ሲሆን፤ አባቱ አቶ ለማ የልጃቸዉን ሬሳ (አሟሟት) ካዩ በሗላ ጤና በማጣታቸዉ ለረዥም ጊዜ የአልጋ ቁራኛ ሆነዉ በዛ በደርግ ስርዓት አሸልበዋል። እናቱም ተመሳሳይ የጤና መቃወስ ገጥሟቸዉ እየተሰቃዩ እና አብዛኛዉን ጊዜ በሓዘን “እህህ” እያሉ እየተብሰለሰሉ ደርግ ስርዓት ሲገረሰስ ለማየት ቻሉ። ሁለት ሴት ልጆቻቸዉ አብረዋቸዉ ይኖራሉ ።

በዘመነ ደርግ ሕዝብ ሲጨፈጭፉ የነበሩ ተጠራርገዉ እስር ቤት መግባታቸዉን ተከትሎ- በ1984 ዓ.ም አነጋጋሪ የሆነዉ የኢሕአዴግ “ድራማ” ይገለጥ ጀመረ። “ማጋለጥ” የሚል ርዕስ የተሰጠዉ ይህ ተዉኔት በየአቅጣጫዉ ሲቀጣጠል ኢላማ ያደረገዉ በደርግ ስርዓት ሲገድሉና ሲያስገድሉ የቆዩ ሹመኞች በየመድረኩ ማብጠልጠል ነበር። በተጠቀሰዉ ዓመት ጥቅምት ወር በፈረንሳይ ለጋሲዬን በሚገኘዉ በከፍተኛ 12 ት/ቤት ቅጥር ግቢ የተካሄደዉ “ማጋለጥ” አንዱ ነበር። እስከ አምስት ሺህ የሚጠጋ የአካባቢዉ ኗሪ ተገኝቷል። ከቀይ ሽብር ወንጀል ጋር በተያያዘ 40 ወረዳ እና የቀበሌ ሹመኞች (አብዬት ጠባቂ የሚባሉትን ጨምሮ) በወንጀለኛነት ተጠርጥረዉ ከታሰሩ በሗላ -ሁሉም በዛኑ ዕለት ለታዳሚ ከሚታይ መልኩ ተደርድረዉ ተቀምጠዋል፡ በስርዓቱ የተረሸኑ እና የደረሱበት ያልታወቀ የኢሕአፓ አባላት (ታጋዬች) ከመድረኩ ግርጌ ተደርድሯል። ደረት እየደለቁ (ልጄን..ልጄን..” የሚሉ ሐዘን የደቆሳቸዉ ወላጆች ከወዲያ ወዲህ እያሉ ሲያለቅሱ ይታያሉ።

መድረኩን እንዲመሩ ተመደቡት የኢህአዴግ ወኪሎች ካድሬ ሃ/ስላሴ፤ መዓሾ፤ መ/አለቃ ታደሰ ሲጠቀሱ፤ ከቀይ ሽብር ሰለባዎች ተፋራጅ ኮሚቴን በመወከል የአሁኑ የ ኢቲቪ ጋዜጠኛ በቀለ መንገሻ ተገኝቷል። ወንጀሉ ሲፈጸም ያዉቁ የነበሩ የተገረፉና ያዉቁ የነበሩ የኢሕአፓ አባላት ተራ በተራ እየተነሱ ስላዩትና እናዉቃለን ስለሚሉት ይናገሩ ያዙ። ከኢሕአፓዎች ለድረግ አድሮ የገዛ የልብ ጓደኛዉን እስከማስገደል ደረሰ ምስጢሮች አዉጥቷል የተባለና እንዳጋጣሚ ሲሰራበት ከነበረዉ የአርባ ምንጭ ክልል መጥቶ ከታዳሚዉ ጋር ተቀላቅሎ ፕሮግራሙን ይከታተል የነበረዉ ከበደ ማኦ የተባለ ግለሰብ ወዲያዉኑ በቁጥጥር ስር ዉሎ ታሳሪዎቹን እንዲቀላቀል ተደረገ። ደርግ ከፍተኛ 12 ሊቀመንበር ሆኖ ያገለግል የነበረዉ ሰለሞን ይመስገን “ የአንድም የኢሕአፓ አባል፤ አንድም ወጣት አላስገደልኩም፡የፈረምኩት ወረቀትም የለም። “አለ” ከተባለ እዚሁ ልረሸን። አንድ ሰዉ እከካም ስትለዉ እከኩን ልታሳየዉ ይገባል።” በማለት የሰዉን ቀልብ በሚችል ገለፃ ተናገረ።

እዚህ ላይ የነበረ አስደንጋጩ የማጋለጥ ክስተት የተፈጠረዉ። በቀበሌ 18 የሚኖረዉ መምህር ቢሻዉ አበጋዝ በተደበላለቀ ስሜት ተወጥሮ ወደ መድረኩ አመራ። ማይክሮፎን ጨብጦ ሲያበቃ በተረጋጋ አንደበት እንዲህ ሲል ጀመረ። “ሰለሞን በሚገባ ታዉቀኛለህ፤ታስታዉሰኛል፤የድርጅት አባል መሆን ከወንጀል ተቆጥሮ በኢሕአፓ አባለነታችን ባንተ እና አጠገብህ ባሉ ጨካኞች የቁም ስቃይ ፍዳ ከቆጠርነዉ አንዱ ነኝ። በ1969-70 ዓ.ም በከፍተኛ 12 እና በሗላም በአንደኛ ፖሊስ ጣቢያ የእስር ቤቶች ግፍ ስትፈጽሙ ነበር። አስታዉሳለሁ ጋሸ ማሞ የሚባሉ አህያ ነጂ ቀን እንጨት ጭነዉ ማታ ጠጅ ቀማምሰዉ ጫካ ወደ ሚገኝ ቤታቸዉ ሲያመሩ የአንተ አብዬት ጥበቃዎች ይዘዉ እየደበደቡ እና ወዳለንበት እስር ቤት አመጧቸዉ በግምት 55 ዓመት ይሆናቸዋል። አዛዉንቱ በሚፈጸምባቸዉ ግርፋት ሳቢያ ሕይወታቸዉ አለፈች። ጭካኔዉ የት ድረስ እንደሆነ ይሄ በቂ ምልክት ነዉ።”

መምህሩ ቢሻዉ ቆፍጠን ባለ ድምፅ ወደ ዋናዉ ነጥብ ሲያመራ አንዲህ አለ “ ታጋይ አባላችን አሸናፊ ለማ ወይንም አሸናፊ ጎላ ያ ሁሉ ስቃይ እንዲፈጸምበት ያደረግከዉ አንተ ነህ። በመጀመርያ እህቱን ንግዴ ለማን እንድትታሰር አደርግክ። ከእስር ቤት በድቅድቅ ጨለማ ንግዴንና ዓይናለም የተባለቺዉ ሌላኛዋ ወጣት ልጃገረድ እስረኛ በአንድነት በአንድ አልጋ ላይ ይዘህ አደርክ። ወሲባዊ ግንኙነትም ከሁለቱም ጋር ፈጸምክ። ለአሸናፊ እሕት ማለትም ለንግዴ ለማ ቃል በገባህላት መሰረት ወንወድሟን ጠቁማ እንድታስይዝ አደረግክ። ይህችን ማፈርያ አንስት ወንድሟን አስይዛ በእርሱ ስቃይ እና ሞት አሁን ድረስ ያለችበትን የኢትዬጵያ የፖስታ አገልግሎት ድርጅት መ/ቤት በቋሚ መቆናጠጥ ችላለች።” ንግግሩን ገታ አድርጎ ታዳሚዉን እየቃኘ “… እዚህ ሕዝብ መሃል ንግዴ ለማ አለች። ቅድም ስትገባ አይቻታለሁ።” ብሎ ከማለቱ “ተነሽ!.. ዉጪ.. ዉጪ” የሚል ድምፅ ከተሰብሳቢዉ አስተጋባ። አብዛኛዉ ግን ለይቶ አያዉቃትም። ከመድረኩ በተሰጠ ትዕዛዝ መሰረት እንደመሸጎጥ ብላ በፀጥታ ሃይሎች ተይዛ ወጣች።

ከወንጀለኞቹ አጠገብ እንድትቆም ሲደረግ ታዳሚዉ በአንድ ድምፅ “መነፀርሺን አዉልቂ! …አዉሊቂ” እያለ የዉግዘትና የስድብ ናዳ ያወርደባት ያዘ። በዛ ቅጽበት ግን አብዛኛዉ ታዳሚ ያስተዋለዉ አሳዛኙ ሁኔታ እዛዉ መድረክ ስር የታይ ነበር። የዛች አንስት አንዲሁም የሟቹ አሸናፊ “ጐላ” ወላጅ እናት የልጃቸዉን ፎቶ በደረት ጉያቸዉ ሽጉጥ እቅፍ እንዳደረጉ በሰሙትና በሚያዩት ተደናግጠዉ ክዉ እንዳሉ፤ምንም ቃል ሳይተነፍሱ ሕሊናቸዉ ስተዉ በጀርባቸዉ ተንጋለዉ ወድቀዉ ነበር። ግዙፍ ሰዉነት አላቸዉ በመሆኑ በጥቂት ሰዎች ዕርዳታ ማንሳት አልተቻለም ነበር። ዉሃ ቢፈስባቸዉም አልነቁም። “ጉዴን ያላወቅሁ! ምነዉ ለማ (ባለቤታቸዉን) አንተን ባደረገኝ!? ልጄ የተባለዉ በገዛ ልጄ ኖሯል!” በለሆሳስ ይለፈልፋ ነበር። ለተከታታይ ሕሊናቸዉን እንደሳቱ ቆዩ።

ወንድሟን እንዳስገደለች ፊት ለፊት የተነገረላት ንግዴ ለማ ከመድረኩ መሪዎች የእምነት ክሕደት ቃል እንድትሰጥ ተጠየቀች። አንገቷን እንዳቀረቀረች ዝም አለች። እንደገና ብትጠየቅም እንዳቀረቀረች ዝም አለች። እንደገና ብትጠየቅም ከማቀርቀር በቀር የተነፈሰቺዉ አልነበረም። “ዝምታ በራሱ ማመን ስለሆነ -ወንጀሉን ስለመፈሟ ያስረዳል። ይህ በሬከርድነት ተይዟል። ዉሳኔ እስኪሰጣት ድረስ ማረፊያ ቤት ትቆያለች።” አለ ካድሬ ሃ/ስላሴ። ማጋለጡም በሌሎቹ ቀጥሎ ሲካሄድ ዋለ። ለአንድ ወር ገደማ እስር ቤት ቆይታ በዋስ የተለቀቀችዉ ንግዴ እስር ላይ እያለች ለዞኑ ካድሬዎች እና ተፋራጅ ለተባሉ ወገኖች በቢሮ በሰጠቺዉ ቃል ወንድሟን በሚስጢር ይኖርበት የነበረዉን አድራሻ በመጠቆም መርታ እንዳስያዘቺዉ፤ እሱን በማስያዝ የእርሷንና የቀሪ ቤተሰቧን ሕይወት እንደታደገች መነገሯን ጋዜኛ በቀለ እና ካድሬዉ አጫዉተዉኛል።

ሌላዉ የተረጋገጠበት ጉዳይ ሰለሞን ይመስገን ከወሲብ በሗላ ወንድሟን አሳልፋ በመስጠቷ ምክንያት ሰለሞን በወቅቱ በዋና ስራ አስኪያጅነት ይመራዉ በነበረዉ የፖስታ አገልግሎት በቋሚ ሰራተኛነት መቀጠር እንደቻለች ነዉ የተመለከተዉ።

በዚህ ወደ ዋናዉ የፅሑፌ ጭብጥ ልሻገር። በ2000 ዓ.ም በአዲስ አበባ በተካሔደዉ አስቂኝ “ማሟያ ምርጫ” ተብዮዉ የመለስ ዜናዊ የ ኢሕአዴግን በመወከል በወረዳ 12/13 ምርጫ ክልል ለክልሉ ም/ቤት እንድትወዳደር የታጨቺዉ ንግዴ ለማ ከዛ ባለፈ የአዲስ አበባን ሕዝብ እንዲመራ በተደራጀዉ አዲሱ የኩማ ደመቅሳ ካቢኔ ዉስጥ የዋና ፀሃፊነቱን መንበር እንድትቆናጠጥ ተደረገ። በ97 ምርጫና በተፈጠረዉ ሁኔታ ቆሽቱ እርር ድብን ያለዉ የአካባቢዉ ሕዝብ ንግዴ ኢሕአዴግን ወክላ ስለመወዳደሯ ሊያዉቅና ሊከታተል ቀርቶ “ማጣሪያ” ተብዬዉም የሚሰማበት ጀሮ አልነበረዉም። የታወቀዉ ሚያዚያ 2000 ዓ.ም የክልሉ ካቢኔ ሲያሰማና የዚህ ስነ ስርዓት በቲቪ ቀጥታ ሲተላለፍ ነበር። በንዴት የጦፉ የቀድሞ የኢሕአፓ አባልትና የአሸናፊ ጐላ የቅርብ ጓደኞች “አቤት” ለማለት ተሯሯጡ። የሚያሳዝነዉ ይህቺ ወንጀለኛ ሴት በወንድሟ የፈፀመቺዉ ወንጀል አልበቃ ብሎ በወላጅ እናትዋ ላይም በደል መፈፀምዋ ነበር።

ይህም በ1989 ዓ.ም ታስራ ከተፈታች በሗላ “ልጄን አስገደልሽ” እያሉ በቁጭት ሐዘን ይናገርዋት የነበሩ እናትዋን በተኙበት አልጋ ትጨቀጭቃቸዉ እንደነበር በተደጋጋሚ ጊዜያት በዓይናቸዉ የተመለከቱ የጎረቤት እማኞች ይናገሩ ነበር። “አድኑኝ!”…ቀጥቅጣ ገደለቺኝ! የወንድሟ አልበቃ ብሎ” የሚሉ ድምፆች የአካባቢዉ ኗሪ ያሰለቹ ነበሩ። በዛ ድርብር ሐዘንና ስቃይ እንደተከበቡ ያልጋ ቁራኛ እንደሆኑ በ1993 ዓ.ም በሞት ያሸለቡት ወላጅ እናት ከሳቸዉ ሞት በሗላ የሰፈሩ ኗሪ ንግዴ ለማ በአካባቢዉ ባሉ እድር እና መሰል ማሕበራዊ መስኮች እንዳትታቀፍ (እንዳታገለገል) ቆፍጠን ያለ አቋም እስከመያዝ የደረሰበት ተጨባጭ እዉነታ ነዉ የታየዉ። ሌላ ቀርቶ የቀበሌ 18 ሕዝብ የእግዚአብሔር ሰላምታ እንዲነፍጋት ተስማምቷል።

ይህችን ሴት ነዉ እነ መለስ የአአዲስ አበባን ሕዝብ እንድትመራ ስልጣን “ያጎናጸፋት”። የዚህ ጽሑፍ አቅራቢ ግንቦት 2000 ዓ.ም በአዉራምባ ታይምስ ጋዜጣ ላይ “ከአሸናፊ ጐላ” በሚል ብዕር ስም “ኢሕአዴግ ለየለት ማለት ነዉ? በሚል ርዕስ ከላይ የተገጸዉን ጭብጥ በመጭመቅ ለመጋለጥ ተሞክሯል።” በድጋሚ በዛዉ ጋዜጣ “ሰሚ ያጣዉ የሕዝብ እሮሮ” በሚል ተፅፏል። የመጀመርያዉ ጽሑፍ እንደወጣ የፓርቲዉ የ አ/አ ፕሮፖጋንዳ ሃላፊ ሕላዌ ዬሴፍ ‘እንዴት” በሚል አጣሪ እስከመሰየም ደረሱ። የገዢዉ ፓርቲ ዩበኩር ልጅ የሆነዉ ተለጣፊዉ የክልሉ ወጣቶች ማሕበር አስቸኳይ ስብሰባ በወቅቱ ጠራ። የጋዜጠዉን ፅሑፍ (ጥቆማ) መነሻ በማድረግ ሰባቱ አመራር አባላት (ግልገል ኢሕአዴጎችን ወይንም ግንቦቴዎች የሚባሉ) በጉዳዩ ለአራት ቀናት ተወያዩ። በነገራችን ላይ አምስቱ አባላት ተደራቢ ስራ ይከዉናሉ። እንደ ደህንነት የስለላ ተግባር በማካሄድ ጠ/ሚ/ሩ ድረስ ዘልቀዉ መረጃ ያቀብላሉ። ከባሊስትራ ወርቅ ጋር በተያያዘ ያስያዝዋቸዉ አሉ። አንዱ አፍቃሬ ኢሕአዴግ አመራር በስብሰባዉ ከቁጥጥር ዉጭ ሆኖ “ኢሕአዴግ እንደ ሽንፍላ ነዉ ታጥቦ አይጠራም። አንዴት ወንጀለኛ ሴት…” ብሎ መነገሩንና በሗላም ስሜታዊ ንግግሩ እንዳስበረገገዉ አንዱ አባል አጫወቶኝ ነበር። በጠ/ሚ/ት/ሩ ቢሮ ስለሚወጣ እና ስለሚገባ ሌሎች ይፈሩታል። “አዉቆስ ቢሆን!?” እያሉ።

የሆኖ ሆኖ የተለጣፊዉ ማሕበር ተወካዬች ሕላዌ ዬሴፍ ጋር ተቀምጠዉ በ1984 ዓ.ም የተቀረፀዉንና በፈረንአይ ለጋሰዬን አካባቢ የተካሄደዉንና በፈረንሳይ ለጋስዬን አካባቢ የተካሄደዉን ማጋለጥ በዝርዝር የሚያሳየዉን በቪድዬ ምስል የተደገፈ ማስረጃ ከኢትዬጵያ ቴሌቪዥን ምስል ክምችት በማስወጣት ተመልከቱ። እዛ ደረጃ ቢደርሱም የመጣ ለዉጥ አልነበረም።ወንጀለኛዋም በስልጣኗ እንድትቀጥል የአዲስ አበባም ሕዝብ በነብስ በላ እንድትተዳደር ፈርደዉ ቁጭ አሉ። የነመለስ ተዉኔት በዚህ አላበቃም። አሸናፊ “ጐላ”ን ጨምሮ በርካታ ወጣቶችን በማስረሸንና በግፍ በማሰቃየት ወንጀል ተከሶ የቆየዉ ሰለሞን ተመስገን (የወሲቡን ጉዳይ ልብ ይለዋል!) በሞት እንዲቀጣ የተበየነበት በዛሬዉ ዓመት ነበር። ንግዴ ለማ በገዢዉ በታጨች ማለትም ህዳር 2000 ዓ.ም ነበር የሞት ብይኑ የተደመጠዉ። ምን ዓይነት አሳፋሪና አሸማቃቂ ተግባር እነ መለስ እየፈጸሙ እንዳሉ ይህ ጉዳይ አመላካች ነዉ።

የሚገርመዉ እነሱ የሚሾሙትና የሚሸልሙት ወንጀለኛ/ኢሰፓ “የታጠበ ንጹሕ አድርገዉ ለማሳየት መዳዳታቸዉ ነዉ። በአንፃሩ ወንጀል የሌለበት በስመ ደርግ ኢሰፓ የነበረ የተቃዋሚን አባል በመንቀስ የታቀፈበትን ድርጅት በጅምላ ሲያብለጠልጡና በአደንቋሪ ስድብ ሲያላዝኑ ጭምር መታየታቸዉ ነዉ። ጉዳዩ ግን ደርግ፤ኢሕአፓ፤ቅንጅት፤መድረክ ወዘተ…..የመሆንና ያለመሆን አይደለም ቁም ነገሩ። የትኛዉን አባልና ሹመኛ ባገኘዉ አጋጣሚ በማሕበረሰቡ ላይ ወንጀል ሰርቷል?ወይስ አልሰራም? የሚለዉ ነዉ አንገብጋቢዉ ነጥብ። ወንጀለኛ ከሆነ ባግባቡ ፍርዱ ሊቀበል ይገባል። በዚህ መነጽር ከታየ “የንግዴ” ለማ ቦታ “የካቢኔ ፀሃፊነት” አልነበረም። የክልሉን ሕዝብ ነገ ጥዋት በጅምላ ላለማስፈጀቷ ምንም ማረጋገጫ የለም። “የታጋይ ድምፅ ይጮሃል! ይጮሃል ከመቃብር!”

በነገራችን ላይ ንግዴ ለማ በ84 ዓ.ም ስትጋለጥ መድረክ ይመሩ የነበሩት ካድሬዎች ከቦታዉ የተገለሉት ብዙ ሳየቆዩ ነበር። ቀደም ሲል በዚህ ጋዜጣ የተገለጸዉ ሃ/ስላሴ የተባለዉ ከአርቲስት ኪሮስ አለማየሁ ጋር በመርዝ ሲጠፋ ፤መቶ አለቃ ታደሰ የተባለዉ “የኢዴመን” አባል ያለ አንዳች ጥፋት በ86 ዓ.ም እስር ቤት ተወርዉሯል።የት እንደደረስም አይታቀወቅም።ማዓሾ የተባለዉ የህወሓት አባልና ካድሬ “40 ሺሕ ብር ሙስና ፈጽሟል” በሚል ባልተጨበጠና ማስረጃ በሌለዉ የፈጠራ ክስ ሆለታ እስር ቤት ተወርዉሮ ሲያበቃ በዚያዉ ሕይወቱ እንዳለፈ ማረጋገጥ ተችሏል። ኢሕአፓዎች ምን ይላሉ? ለዛሬ በዚህ አበቃሁ። //-// www.ethiopiansemay.blogspot.com getachre@aol.com May 22, 2010