Sunday, January 29, 2012

Al Mariam’s Contradictory approach to the Right of Free Speech


የሚታየው የወያኔ ገበና ማህደር አዲሱ መጽሐፍ ለመግዛት $30.00 ዶላር ሲሆን ይድረስ ለጎጠኛው መምህር መጽሐፍ ደግሞ $25.00 ሓይካማ የሚለው የትግርኛ መጽሐፌ ደግሞ $15.00 ዶላር ብትልኩ መጽሐፎቹን ማግኘት ትችላላችሁ።Getachew Reda P. O.Box 2219 San Jose, CA 95109 getachre@aol.com Phone (408) 561- 4636



Al Mariam’s Contradictory approach to the Right of  Free Speech

           Getachew Reda getachre@aol.com www.ethiopiansemay.blogspot.com


I have tow topics for you today.

 1-Al Mariam

2= Tesfaye GebreAb

As you have been following lately different critiques against EPRP and EPRP personalities accused of scanning /duplicating the new Mengistu Hailemariam’s book intent to distribute it via online free for readers is been the talk of some individuals.

The critiques were using such opportunity to attack EPRP personalities for their own personal reasons. Some of those are Derg personalities involved in the killing and torturing of EPRP members during the Derg era, where they still showed  rumors nor taken to court  for their crime.

The second critiques are from group members of OLF/Ginbot 7 (The Pal Talk guerrilla fighters) and EPLF agents wearing Ethiopian opposition garb to cover themselves assigned from EPLF for different agendas.

The EPLF agent I am talking is obviously whom many of us knew is Tesfaye GebreAb (the hero of the Tigray hater Pal Talk room ECADEF), involved in the business of actively attacking EPRP lately. I will come back later on this matter.

What made me wonder most from the group of critique is not those little minds mentioned above with missions of their own. But, Professor Al Mariam a University Professor and a Prominent Attorney who is furiously critique against the issue of EPRP’s action in regard to Mengistu’s book.

 As I explained it earlier, I have no problem if one showed sympathy or concern for Tsehay Publisher who took the contract to publish Mengistu Hailemariam’s book.
But, the issue I don’t like is when I reacted to some of Al Mariam’s irrational commentary, some of the Ginbot 7 cults were crying why I react against Al Mariam’s on which he vowed himself to defend any terrorist, any dictator including Mengistu Hailemariam , Benladen or Meles Zenawi, based on the principle philosophy of law on which even dictators have the right to address their case/grievances/ agenda to the public/audience/court …. Without restriction.

At the same time Al Mariam forgot and contradicted himself when he insulted us as “a Dog-like” (cynics) in support to his hero “Seye Abraha” of TPLF stating Seye has the right to express his view without any one to criticize  him or to oppose him.,

When we similarly exercised our freedom of speech to criticize in reaction to Seye’s arrogant responses when we asked him to release hidden information and crime that he knew or participated while he was as one of the leaders of TPLF as Gebremedhin or Asgede exposed TPLF’s secrets, Professor Al Mariam a popular Attorney and a professor of Law insulted us with intent to “shut our mouth”.


 when we the family victims of TPLF referred by Al as cynics for exercising using America’s freedom of speech with the right to react/write/ talk/complain/oppose/ condemned Seye Abraha during his tour to the United States to address the injustice he faced by the system he himself established, surely Al got it messed up the meaning of freedom of speech when it comes to the victims right to react.  

Al Mariam defended Seye’s the right to complain /condemned TPLF/Meles Zenawi’s injustice exercised against him as JUST, and stood with him and advocated for Seye Abraha  the right to speak, while ridiculed us as “cynic” is not only fair and a balance advocate of law, but ignorance of the meaning of the term VICTIMS’ Right to also react against their present or x- abusers and torturers. Al clearly showed to us his BUDINTENGA/WEGENTENGA/pick and choose discriminatory defense.

If I and Al Mariam could have debate in court or anywhere for this matter, what could have been Al’s  response to this inclination of siding with one party while telling the victims to shut their mouth contradictory to his preaching of “Speech of Rights” just because there is no established court where we can try Seye for his past crime? Abusers and their defense attorney always have this escape goat mechanism hiding behind the IRON FENCE called “everyone is innocent until proven guilty in the eye of the law unless proven guilty in a established court” their likes argue with us by telling us do not be critique of abusers/tortures/mercenaries/Meles Zenai/… until they are taken to court.  All torturers, abusers and tyrants, racists use this excuse as escape goat to shut us up! Al is one of them who use this none sense fence to protect abusers and tyrants. If we do we are ‘cynic’

I asked him on my previous articles in reaction to his support for Seye saying:- “Al Mariam, I have a great respect so far for you. But, you need to watch out the words you
used in defense of  Siye.
ou said :- “I am sure there are many cynics who would rather
condemn him for his past acts and omissions, and just as soon ignore his
manifest of transformation and commitment to do the right thing”.  

(Now, we saw where Seye’s transformation ended- Harvard University?! Isn’t it?)
I  responded:-

“Mr Al, cynic means “a sneering dog”, “a dog like”, “selfish”, “faultfinder” . Mr.Al, we are none of that. We are not looking for faults, it is there, and it was there for 17 years in the jungle and 10 years as one of the powerful government figure for anyone to see .So what, if we the people ignore /doubt his manifestation? Don’t we too have the right to reject his transformation after he failed to answer our concern, the injustice, the secret and the ingenuity of  his organization, the crime he hide from us with a full knowledge knowing what took place while he was in power?

I asked Al -What is wrong with asking him to tell us what went wrong, and where our beloved once disappear?  Mr. Al, Most of all, you vowed to defend his Speech of Rights, while you described us as cynic to shut our mouth by disrespecting our Speech of Rights is a total bias and discriminatory on your side…….”
This was some of the responses I did years back to Al Mariam, and still updating this issue of the Right to Speak he used it when he needed it as long as it fits him.

Here again this week, he is sick to his stomach Mengistu’s victim’s react the way they chose to react. When victims lost hope with justice in this world, Al Mariam forgot that victims have also the right to revenge when justice failed to serve. Why do the protesters of  “Occupy Wall Street” Occupy Oakland” Occupy Oklahoma City Hall” Occupy…..Museum” Occupy abandoned for closer houses” “occupy Free Ways” ….campaigners are doing?  People started to react that way because victims get frustrated while bourgeoisie are living comfort with the blood and sweat of the victim and poor? Will AlMariam defense the Wall Street, because the protestors are also blocking accesses to other business owners located nearby from customers coming to their business? Will Al Mariam stand in defense to Wall Street or nearby business owners against protesters if business owners file a law suit against protesters for causing the business broke or for causing havoc in the business area ?

Professor Alemayohu seemed to forget that victims felt hurt.  we are just victims as Seye with felt hurt by his comrades in power. We have no one to defend our patriots, friends, brothers and sisters disappearance. Our family was tortured with fire. Shot dead with bullet while asleep in the jungle prison, suffering just as Siye suffered and even worst.”

We expected you as a lawyer to see this side of the issue as the Right to Complain in our side also. ?  Where is Tsegaye Debteraw? I asked one day to Guru and his friends while they were  touring the US. NONE of them gave it a value. Why? We have Layers who defended them day in day out with disregard to victims cry. The time is now; the promise and transformation starts answering question as the public too has the right to know secrets of Seye and TPLF.

It is a shame that no one including Al Mariam the champ of Human Rights price winner advocated for those victims. Berhanu Negga was dedicated his book for Seye not for his former party leader Tssegaye and his friends or to Asefa Maru, Mekonnen Dori, Abera Yemaneab, Bahtawi Fekadeselasie!  
Check the following what Al Mariam In his latest topic “Copyrights and Copy Crimes” had to say :-
 “One can disagree deeply with Mengistu and the facts or lies contained in his memoir. Having read the book, I am critical of the accuracy and selective recollection of many of his “facts”; and disagree with his attempt to avoid personal and regime accountability for his gross violations of human rights. But that is the way of all dictators. They always try to tell their stories in heroic terms and attempt to justify their crimes as patriotic acts.”
 Did you hear him? I will repeat it for you

“…But that is the way of all dictators. They always try to tell their stories in heroic terms and attempt to justify their crimes as patriotic acts.”
That is exactly how we explained Seye and the rest of the liars when they tried to tell us only their side of the story without telling us the crime they committed. Our demand to Al’s hero Seye and his other groups was similar. We asked them to tell us secrets, disappearances before we trusted them as one of our own or a genuine opposition to Meles Zenawi. But, instead “They always try to tell their stories in heroic terms and attempt to justify their crimes as patriotic acts” or if they do they acknowledge there were wrongs done without detailing the wrongs.”
Al Mariam continues,


Although I disagree with Mengistu on numerous facts and unreservedly condemn his human rights record, I will be the first one to stand up and defend his right to write a book and publish it.”

Why then, Professor Al Mariam called those who complained about Seye as “cynic/ Sneering Dogs” or provocateurs, with their mild reaction if  Mengistu has the right  to write his book defended by Al Mariam? To me this a joke and discriminatory that failed to apply fairness of defense in equal footage to all. Note- I declined many media interviews and and invitation to be a guest speaker, but now I will offer myself to debate Professor AlMariam publicly on this matter at any media he wanted,if he disagree with my argument. Part 2 topic about Tesfaye GebreAb will continue next week. Stay tune.






Sunday, January 22, 2012

ጠላ ቤቶች ብቻ ነው የቀሩት!

ጠላ ቤቶች ብቻ ነው የቀሩት!


የወያኔ ገበና ማህደር $30.00  (ደራሲ ጌታቸው ረዳ)
ይድረስ ለጎጠኛው መምህር $25.00 (ደራሲ ጌታቸው ረዳ)
ሓይካማ (ትግርኛ) $20.00  (ደራሲ ጌታቸው ረዳ)

በመላክ መጽሐፍቶቹን ማግኘት ይቻላል። ወደ አዲስ የሕትመት ዙር ካልገባሁ በስተቀር (የአንባቢው መጠን የሚወስነው ይሆናል) አሁን የቀሩት ጥቂት ቅጅ ካላገኛችሁ መጽሐፍቶቹ እንደልብ አይገኙም።አሁን እንደ ዋዛ የምናያቸው መጽሐፍቶች እንደተቀሩት የኢትዮጵያ መጽሐፍቶች ለትውልድ ሲተላለፉ እንደመርፌ በመከራ ይፈለጋሉ።
Getachew Redda
P.O.Box 2219
San Jose California
95109 
(408) 561-4836

 To view the fonts/pictures (page) bigger or smaller press your keyboard (Ctrl and + sign) (Ctrl and –sign)
ጠላ ቤቶች ብቻ ነው የቀሩት!
ጌታቸው ረዳ
የኢትዮጵያን ሰማይ ድረገጽ አንባቢዎች፤ እንደምን አላችሁ? ዛሬ የማቀርብላችሁ ርዕስ በኢትዮጵያ ውስጥ በዘመነ ወያነ እየታየ ያለው አሳፋሪ የባህል ወረርሺኝን በሚመለከት ነው፡፤ ወያኔዎች በረሃ ሲወጡ አንደኛው ምክንያታቸው “አማራ የብሔረሰቦችን ቋንቋ አማርኛ እንዲሆን በመጫን ንግድ ቤቶች እና ተቋማቶችን፤የፍትህ እና የመሳሰሉ የሥራ መገናኛዎች በአማርኛ እንዲሆን “አማራዎች” ለብዙ ሺህ ዓመታት ተጽእኖ አድርገውብናል” በሚል ነበር ሁሌም ዛሬም ሲለፈልፉ የነበሩት(ዛሬም አለማፈር ያንኑ ሲደግሙት ታነባላችሁ/ታደምጣላችሁ)።
ሆኖም ዛሬ የሚታየው ባህል ወረርሺኝ ለምሳሌ በቅርቡ ትግራይ ድረስ ለጉብኝት የሄዱ ሰዎች ሲነግሩኝ “ጌሾ” ተብሎ የሚታወቀው የጠላ እና የጠጅ ቅመም ተክል ምትክ ከፍ ያለ ገንዘብ ለማግኘት ሲሉ ማለትም ገዳማቱ እና ቤተክርስትያናቱ (ገጠር ሁሉ) የተለያዩ ደረጃ ያላቸው “ጫት”በማብቀል ለገበያ በማቅረብ በጌሾው ምትክ ብዙ ገንዘብ  እያገኙበት አንደሆነ እና፤ሲጃራ ማጨስ እንደ ነውር ሲቆጠር በነበሩባቸው ከተሞች ሁሉ ሳይቀሩ የጫት መሸጫ ሱቆች እና “መመርቀኛ” ቦታ ተከፍተው ሰዎች ማታ ከስራ ወዲህ የሚዝናኑባቸው ቦታዎች በብዛት ተስፋፈተዋል። መንገድ ላይ ስታልፍ “የሓሺሽ” ጭስ እንደሚሸታቸው የታዘቡ ሰዎች ነግረውኛል። በዚህ ጫት እና በመሳሰሉት ዕጾች ሰበብ “ብዙ ትዳር” እንደፈረሱ ነግረውኛል። የወያኔ ራዲዮ ጣቢያ “ድምፂ ወያኔ ትግራይም” በተከታታይ ሁኔታውን ዘግቦት እንደነበረ ትዝ ይለኛል።
የወያኔን “ቦሶሮ” ሰነፍ አስተዳደርን በማሕበራዊ ባህል ጉዳዮች ያስከተለው  ጥቃት ስትመለከቱ ለምሳሌ ትግራይ ውስጥ መቀሌ ከተማ በሦሰት ማዕዝኖች ተዋቅረው በምስጢር ስም የሚጠሩ “ጋንጎች” /የከተማ ወረበሎች/ ከመንግሥት የፍትህ እና የፓሊስ አካላት በመመሳጠር  ከተማዋን በማወክ “በዝርፍያ፤እና ሰው በመደብደብ” እንዲሁም ለመቆጣጠር በሚሞክቸው ፖሊሶቹንም ሳይቀር በቀን ፀሐይ በድፍረት እንደሚደበዱቧቸው እንደሚያስፈራሩዋቸው መረጃዎች ያስረዳሉ። ባንድ ወቅት (አምና) የከተማዋ ፖሊስ አዛዥ/ኮሚሽነር
በጋንጎች ተደብድቦ ገደላማ ስፍራ ውስጥ ጥለውት ከነሽጉጡ እንደተገኘ መዘገቡ ታስታውሳላችሁ። የወያኔ አስተዳደራዊ ጉብዝና ሲመዘን አሳፋሪነቱ በግልጽ ማየት የሚያስቸላችሁ መረጃ ከዚህ ወዲያ ሌላ አያስፈልግም።
በሌላ በኩል ደግሞ የወያኔ የባህል እና የቋንቋ አብዮት የሚከተለው አሳፋሪ ወረርሺኝ ለኢትዮጵያ አስገኝቶላታል። ንባቡን ይከታተሉ።ዘገባው የተዘገበው ሁኔታው ያሳሰባቸው በወያኔ የዜና ማሰራጫ አውታሮች ተቀጥረው  በጋዜጠኝነት የሚተዳደሩ ዘጋቢዎች ያጠናከሩት ነው። የወያኔ የቋንቋ እና የባህል አብዮት ለኢትዮጵያ ያስገኘላት ዕድገት ይህ አሳፋሪ እርምጃ አንብቡ።
ዘገባውን ያጠናከረው ጋዜጠኛ እንዲህ ሲል ዘገባው ይጀምራል፡-
"ተጨባጭ ሁኔታው  ትናንት ወደ ጎን እንቃኛቸው የነበሩ ቤቶች ወደ እላይ ተመንጥቀው ቀና ብላችሁ ካላያችሁን የሚሉ ይመስላሉ።ይኼ እንግዲህ በታላላቅ ከተሞቻችን የምናስተውለው አስደሳች ሁኔታ ነው።ታዲያ ቀና ብለን ካስተዋልናቸው ግዙፍ ህንፃዎች ላይ ዓይናችን ሳይነቀል እይታውን ከቀጠለ፤ “ትኩረትን የሚስብ ሌላ ነገር አለ”፡ እዚህም እዚያም የተሰቀለ የተለያየ ስያሜ በደማቅ ቀለማት ያሸበረቁ አብዛኛዎቹ የንግድ ድርጅቶችና የሌሎቹ ስያሜዎች ከሌሎች በእርግጥም እይታ ይጠራሉ።ችግሩ ግን ከአገሩ ሰው ይልቅ የውጭ አንባቢ የሚሹ ይመስላሉ።
በባሕር ማዶ የሚገኙ ከተሞች ስም የተሰየሙ ባዕድ ሃገር ዝነኛ ሰዎችን ስም ስያሜ የተዋሱና ከኢትዮጵያዊ ባህል ይልቅ የውጩን ልምድ የተላበሱ በብዛት ይታያሉ።ነገሩ ዘመናዊ በሚባሉ አካባቢዎች የከፋ ይሁን እንጂ የውጭ ስያሜ ወረርሺኝ ግን የከተሞችን ጥጋ ጥግ በፍጥነት እያዳረሰ ነው። አንዳንዶች የሚሉት ከሆነ ደግሞ ከውጪው ስያሜ ይልቅ ሃገራዊ ስያሜዎችን ፈልጎ ማግኘት አዳጋች እየሆንም ነው።"
በባዕድ የባሕል እና የቋንቋ ወረረሺኝ ኩፉኛ እየተጠቁ የመጡት ከተሞችን አስመልክተው አስተያየታቸውን ተጠይቀው የመለሱት መምህር እና ደራሲ የሆኑት አቶ ኃይለመለኮት መዋዕል እንዲህ ይላሉ፡
“ከባዕድ የሚመጣ ስም ዓለም አቀፍ ስም ካልሆነ በስተቀር እኛ ላይ መጥቶ የሚለጠፍ ስም የኛ አይደለም።ራዲዮ ልንል እንችላለን ሳተላይት ልንል እንችላለን ዓለም የተቀበለው ነው። ካሜራ -አሁን ፊት ለፊቴ እንዳለው፡ ይኼ ዓለም በሙሉ የሚጠቀምበት ነው። ነገር ግን የትምህርት ቤቶችን፤አጸደ ህፃናትን፤አንደኛ ደረጃ፤ሁለተኛ ደረጃ ፤ከዚህ አልፈህ ደግሞ ለመዝናናት የምንኼድበት ቦታ “ቡና ቤቱ፤ሆቴል ቤቱ፤ካፍቴሪያው፤ሻይ ቤቱ ምኑ ቀረ? ጠላ በቶቹ ብቻ ናቸው የቀሩት። እነሱም ሳይጀምሩ አይቀሩም።
ለምሳሌ አንድ ጸጉር ማስተካከያ ቤት (ስሙን አላነሳውም) በአማርኛ ቢተረጉመው የተሻለ ስም ሊሆን የሚችል በእንግሊዝኛ ተጽፏል፤ ወደ ሰፈሬ ስኼድ መንገድ ሳልፍ የማየው ነው። ይኼነን አሁን በአማርኛ ቢጠራው የበለጠ ያምር ነበር።”
አንድ ታዛቢ መንገደኛ ቃለ መጠይቅ የተደረገለት ደግሞ አስተያየቱን እንዲህ ሲል ይገልጻል።
“እኔ እንጃ “ቴድሮስ””አራአያ” “ዘርአይ ደረስ”..የሚባል ስያሜ አይቼ አላቅም እስካሁን ድረስ ፤በእውነት ነው የምልህ።”
አዘጋጁ እንዲህ ሲል ትችቱን ይቀጥላል፡
“ያለንበት “የብሔር ብሔረሰቦች የጋራ ቤት በሆነቺው ኢትዮጵያ ውስጥ ነን። የተለያዩ ቋንቋዎች እና የባህል ስብጥር ደምቆ የሚታይባት ድንቅ ምድር። የረጂም ዘመን አኩሪ ታሪካችንም ቢሆን ሌላው መለያችን ነው። ታዲያ ምኑ ቸግሮን ይሆን የውጭ ስያሜ የምንዋሰው? ሲል ከጠየቀ በላ ፡ አንድ ወጣት መንገደኛ አሁንም አስተያየቱን እንዲሰጥ አቁሞ ይጠይቀዋል። ወጣቱ እንዲህ ይላል።
“ኢትዮጵያ ተዝቆ የማያልቅ ሰፍር ቁጥር የሌለው ታላላቅ ነገሮችን የሰሩ የጀግኖች አገርና ብዙ ታሪክ ያላት አገር ናት። ስለዚህ ከነዚያ ጀግኖች እና የታሪክ ስፍራዎች ስም በመጠቀም መሰየም ይቻላል ብየ አስባለሁ።”
አሁንም ደራሲ እና መምህር የሆኑት አቶ ኃይለመለኮት መዋዕል  አሁንም ከላይ ካቆሙት አስተያየታቸው በመቀጠል እንዲህ ይላሉ፡
“በወረራ ያልተያዝነው፡ለቅኝ ግዛት ያልተንበረከክን ሕዝቦች፤በሰላሙ ዘመን በደህናው ጊዜ “ቅድመ ግሎባላይዘሽን ነው- አሁን ነው 16 እና 20 ኣመት ውስጥ የመጣው” በመምጣቱ ሰበብ የተነሳ “አውሮጳ ውስጥ የሚገኙ ስሞች፤ላቲን አሜሪካ ውስጥ የሚገኙ ስሞች፤ ሰሜን አሜሪካኖች ውስጥ የሚገኙ ስሞች ካናዳ ትላልህ … የቀረ የለም  …የሚገኙ ስሞች፤ አልፎ ተርፎም እስከ ሩቅ ምስራቅ እስከ ጃፓን፤ጃፓን እና ቻይና ድረስ ኼዶ እዛ ድረስ ያለው ስም፤ወደ አገራችን እየገባ፤ ብሔራዊ ማንነታችንን በባህል ደረጃ ሊያጠፋ ወይንም ሊሸፍነው “ምንም ያህል አልቀረውም”።
የውጭ አገር ስያሜ ኢትዮጵያ ውስጥ መገልገል የስልጣኔ ምልክት እና አልፎም እንግሊዝኛ ቋንቋን ተሎ እንዲገባህ ይረዳል ሲል የባህል ወረርሺኙን እንደበጎ ነገር የተመለከተው አንድ “ምስኪን-ገራገር” አስተያየት ሲሰጥ እንዲህ ሲል ባለው ላይ ተጨማሪ ድንጋጤ ሲጨምርብን ታደምጡታላች ; እንዲህ ይላል፡
“እኔ እንዳውም በእንግሊዝኛ ቋንቋ ሳያቸው ደስ ይለኛል።ለምን? አፍ መፍቻ ቋንቋችን አማርኛ ስለሆነ እንግዘሊዝኛ ቋንቛዎችን ደግሞ እያወቅን እና ብዙ እየተማርን አንዳንድ የውጭ አገር ሰዎች ሲመጡ በእንግሊዝኛ ለማናገር ያፍ መፍቻ ይሆናል ብየ አስባለሁ።”
አሁንም መምህር እና ደራሲ የሆኑት አቶ ኃይለመለኮት እንዲህ ሲሉ ይቃወሙታል።
“እርግጥ አንግሊዝኛ አለም አቀፍ ቋንቋ ነው። ፈረንሳይኛ፤ዓረብኛ እነኚህ የትም ኼደህ በዓለም አቀፍ ደረጃ የትም ኼደህ የምትነጋገርባቸው ቋንቋዎች ናቸው። እነሱ ዓለም አቀፍ ቋንቋዎች ሆነዋል እና የኔን አማርኛ፤ የኔን ኦሮምኛ የኔን ትግረኛ እና አፋርኛ…ወዘተረፈ.. እንዲያንኳስስብኝ እና ለቅራኔ እንዲለውጣቸው መፍቀድ የለብኝም። በምን ምክንያት? በተለይም እኛ - ትምክህት አይደለም ፤በተለይም እኛ ከቅኝ ግዛት አገዛዝ  የወረስነው ድሪቶ መልበስ የለብንም! አዲስ የባህል ድሪቶ እያመጣን የነሱን እየተሸከምን ነው። የራሳችን ጸጋ ለምን እናጣለን ነው ትልቁ ነገር።
ስለዚህ ቋንቋ ግንኙነቱ አይደለም ዋናው አሳሳቢው ፍሬ ነገሩ፡በዓለም አቀፍ ቋንቋ መገናኘት ባሕሪያዊ ነው፤ አግባብም ነው።  ዓለም በሚሰማህ ቋንቋ ስትናገር ልትደመጥ ትችላለህ፡ነገር ግን እኔና አንተ በምንገናኝበት ጊዜ ካልቸገረ በስተቀር ለምንድነው በባዕድ ቋንቋ የምንነጋገረው? ወይንም ደግሞ ሃሳቤን ለመግለጽ ካስፈለገ አስቸጋሪ ሆኖብኝ ካልሆነ በስተቀር፤ ለምን የገዛ ቋንቋየን የሌላ ቋንቋ የምሰነቅረው?
እንግሊዝኛ የራሱ አገር አለው። ዓለም አቀፍ ቋንቋ ሆኗል።በታሪክ ምክንያት። እኔ ግን እንግሊዝኛን የምጠቀምበት አንድ ቃል እንኳ የምወስደው ከራሴ ቋንቋ የምተካበት ቃል ሳጣ እና የማናግረው ሰው ያቺን ቃል ብጠቀም ያቺ ቃል ትጠቅመዋለች ስል ነው። ዛሬ፤ዛሬ በውጭ ስያሜ ያልተሰየሙ፤የንግድ መስኮች ለማግኘት የሚያዳግት ነው። እንደፋሺንም የተያያዘም ነው የሚመስለው።በተለይ ደግሞ በግል የትምህርት ተቋማት አካባቢ ነገሩ የከፋ ነው።ከአጸደ ህፃናት ጀምሮ፤ኮሌጆች እና ዩኒቨርሲቲዎች ድረስ አዳርሶታል።...'
አሁንም ዳረሲ እና መምህር የሆኑት አቶ ኃይለ መለኮት እንዲህ ይቀጥላሉ።
“በጣም ጎጂው እና እጅግ አደገኛ የሆነው፤ ከስር ጀምሮ  የሚገኘውን ትውልድ የሚያበላሽብንና ቅኝ የተገዙ አገሮች አንኳ (ካገሬ ወጥቼ አላውቅም)ያደርጉታል ብየ ያልጠበቅኩትን ነገር እያየን ነው።የአጸደ ህጻናት ት/ቤቶች በሙሉ በመቶኛ መናገር አይቻልም እንጂ “በባዕድ ስም ሆኗል” ስማቸው መጥቀስ ይቻላል፡ አስፈላጊ አይደለም እንጂ፤ምክንያቱም እራሳቸው ያውቁታል፤ በፈረንጅ ስያሜ የሰጡ። ለመሆኑ ትምህርት ቤቶች በፈረንጅ ስም ካልተሰየሙ ትምህርት ቤቱ ትምህርት ቤት መሆን አይችልም ማለት ነው?” የፈረንጅ ስም ካላቸው ት/ቤቶች ውስጥ (ሙን ላይት ስኩል ) በዕድሜአቸው ወጣት የሆኑ ርዕሰ መምህር የሆኑት አቶ ፈንታሁን ሀሰን የተባሉ እንዲህ ብለዋል፤፡
“የትምህርት ቤታችን ስያሜ ‘ሙን ላይት ኢንተርናሽናል አካዳሚ ነው።” ኢንተርናሺናል ከመሆኑ አንጻር፤ በዚህ ትምህርት ቤት ውስጥ ይማራሉ ብለን የምንጠብቃቸው፡የተለያዩ የኢንተርናሽናል አገር ዜጎች ለኖሩ ይችላላሉ። እና አንደ ኢንተርናሽናል ተቋምነቱ ለሌላው ተደራሽ እንዲሆን ከሚል አንጻር ነው እንግሊዘኛ እንዲሆን ያደረግንበት ስያሜ ምክንያት። እንደሚመስለኝ ቅድም ያልኩህ አንድ ነገር አለ።አንዳንድ ድርጅቶች/የትምህርት ተቋማት፤የሚሰቷቸው ስያሜዎች የራሳቸው የሆኑ የፍልስፍና ይዘቶች ይኖራቸዋል።ሁለተኛ የግሎባላይዘሽን ተጽዕኖ ይመስለኛል።ሌላው ደግሞ በት/ቤቱ እይታ በወላጅ ዘንድ በተጠቃሚው የበለጠ ለማስረጽ እና ት/ቤቱ የተሻለ ጥራት/ሲስተም አለው ለማስባልም የሚጠቀሙ ይመስለኛል የእንግሊዝኛው ስያሜ የሚጠቀሙት።
የወላጆች “አንፍልዌንስ” ያለው ይመስለኛል። የተጠቃሚው የትምህርት ቤቱ ወላጆች ከስያሜው የተነሳ የሚሰጡት ግምት ብዙ ባለ ሃብቶች ወይንም የትምህርት ተቋሞቹ ባለቤቶች ስያሜው ወደዛው እንዲሆን የመራቸው ይመስለኛል።”
አቶ ኃይለመለኮት መዋዕል
“አማርኛው ትግርኛው ወላይትኛው ከምባትኛው ዓፋርኛው ኦሮሚኛ ሶማሊኛ በለው ሁሉም ውብ የሆኑ ቃላቶች አሏቸው። በፈረንጅኛ የሚገለፁትን እንዳውም አሳምረው ሊገልፁ የሚችሉ።
ለምሳሌ “ቀጤማን” እንውሰድ ውብ ነው አደለ? ቀጤማ ካፈተርያ ቢለው ገና ስሙ ሲጠራ አያስደስትህም? ዘምባባ ምግብ ቤት ብሎ ቢሰይመው አያስደስትህም? …ዋርካ! ዋርካ ትልቅ ነገር ነው አደለም? ዋርካ ሆቴል! ብሎ ቢል አይታይህም ትልቅነቱ  ከነ ግርማ ሞገሱ!..ሾላ ሻይ ቤት! ከነተረቱ ሾላ አርግፍ፤እርግፍ እያልን ነው የምንጠራው፡ ከዚህ የበለጠ ስም የት አለ?
ሴዳር ካፍተርያ ከምትል፤ የኛው አይበልጥብህም፤ ፓልም ሆቴል ከምትል “ዘምባባ” አይመረጥም? እንደገና ደግሞ ትልልቅ የውጭ አገር ሰዎች በሚሰየሙት ላይ ለምሳሌ የነሱን ሰዎች ስም ስያሜ እዚህ አምጥተው ይሰይማሉ፡ የእኛ ትላልቅ ሰዎች መቸ አጣን እና ነው? ሞልቶናል ሰው! ፈልጎ ጠይቆ ማምጣት ይቻላል።”
የሙን ላይት ርዕሰ መምህር ፈንታሁን ሃሰን እንዲህ ሲሉ ይከራከራሉ።
“ከስያሜው በስተጀርባ ሃገራዊ የሆኑትን ነገሮችን የመስራት ስራ ነው ትልቁ ትኩረት መሆን ያለበት። ተማሪዎች ለአገራቸው ለወገናቸው አፍቃሪና አዛኝ እንዲሆኑ የማድረግ ስራ ከውስጥ መስራት ይጠበቅብናል ማለት ነው ከስያሜው በስተጀርባ። ብዙ ት/ቤቶች ሊኖሩ ይችላሉ ኢትዮጵያዊ ስያሜ የያዙ። የሚሰሩዋቸው ስራዎች ግን “almost” ከኢትዮጵያውያን ባህል የማይሄዱ “systemሞች” ሊኖሩ ይችላሉ። ስለዚህ ከውጭ ከምትሰይማቸው ስያሜዎች  ይልቅ ከውስጥ የምትሰራቸው ስራዎችን ትኩረት ብናደረግ የተሻለ ነው እላለሁ።”
ጋዜጠኛው፡
“ ዕድሜ ለተረጋገጠው የመረጃ መረብ እያልን ዓለምን በየቤታችን ሆነን መዳሰስ ከጀመርን አመታት ተቆጥሯል።አሁን ባለንበት የጉለባላይዘሽን ደግሞ ምድራችን ይበልጡ የጠበበች መስላለች። ታዲያ በጎ ጎን እንዳለው ሁሉ ጣጣውም የከፋ ነው።በተለይም ለታዳጊ ሃገሮች። በተሌይም  ግን ስንቶቻችን ነን “ችግሩን” ያስተዋልነው?
ምንም ችግር አያመጣም የሚለው አንድ አስቀድሜ የጠቀስኩት “ምስኪን-ገራገር” አስተያየት ሰጪ ደግሞ ጋዜጠኛው ሲጠይቀው እንዲህ ብሏል።
ምንም የሚያሳስበኝ ነገር እኔ አይኖርም። የሚጠፋኝ ነገር አይኖርም ፤የሚያሳስበኝ ነገር ደግሞ ብዙም አይኖርም።”
ደራሲና መምህር አቶ ኃይለመለኮት መዋዕል ደግሞ “ብዙ የሚያሳስብ ነገር አለብን እንጂ! በማለት እንዲህ ይገልጹታል።
“እልፍ ኣእላፍ ቴሌቪዥን ጣብያዎች ከፍተው፤ ወጣቶቻችን አፋቸውን ከፍተው ቀኑን ሙሉ እነሱ ላይ አፍጠው እንዲመለከቱ አድርገዋቸዋል። እንዳይሰሩ እንዳይማሩ፤እንዳይመራመሩ፤ ሃገራዊ ማንነታቸው እንዳይረዱ ያደርጓቸዋል። ይህ ሲሆን ደግሞ “ወደ ላ ትቀራለህ። ወደ ላ በቀረህ ቁጥር ደግሞ “ሰብአዊ ጉልበትህንና ኣእምሮህን ይመዘብሩሃል”፡ ወይም በእነሱ እንድታመልክ ያደርጉል።በነሱ ካለመለክ ደግሞ “ለመገዛት ትሄዳለህ”። “ጠርተው ይገዙል፤ እዚህም ሆነህ ይገዙል”። ስለዚህ ከዚህ ለመውጣት የባህላዊ ነፃነት ትግል ያስፈልግሃል። ይህንን ደግሞ በአዋጅ አይደለም፡፤ ራሳችን ይህ ልክ አይደለም ብለን መውጣት አለብን! ሁልግዜ ምንም አይደል እያልክ የምትቀበለው ነገር፤እንደሚገነደስ ትልቅ ቅርንጫፍ “እላይህ ላይ ይወድቃል”።
ጋዜጠኛው፦
“በሃገራችን ስያሜ ምትክ ቦታው የውጭ ቃላት እየተረከቡ መምምጣታቸውን ጉዳይ በስፋት የቀጠለ ሲሆን፤የተለያዩ አስተያየቶችንም የሚያጭር ሆኗል። በርግጥ ሃገራዊ እሴታችን ለምን ይገፋል የሚለው የቁጭት አመለካከት ያመዘነ ቢሆንም፤ ምክንያታዊ መነሻ በተለያየ መልኩ ይገለጻል። የቋንቋ ፍቅር አንስቶ ከማንነት ጋር እስከተያየዘ ድረስ……ብሎ ጋዜጠኛው ወደ አንዲት ወጣት ሴት ልጅ አስተያየት በመዞር የሚከተለውን አስተያየቷን እንዲህ ትላለች።”
“አገርህን ስትወድ እኮ “ሁሉንም ነገር መውደድ አለብህ”። ሰለ እማናውቀው ነገር ከምንጽፍ የራሳችን የሆነ ብናስተዋውቅ የተሻለ ምጥቀት አለው።”
አንድ ወጣት ደግሞ እንዲህ ይላል፦
“በርካታ የንግድ ስቆች እና ተቋማት ስያሜዎቻቸው በእንግሊዝኛ ብቻ የምታስተዋውቅ ከሆነ የኛ መገለጫችን ምንድ ነው? ኢትዮጵያዊነታችን ታዲያ ምንድ ነው?”
መምህር እና ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል ደግሞ እንዲህ ያጠቃልሉታል።
“የራሱን ክብርና ባህል ያልጠበቀ ዜጋ የሌላ ቀላዋጭ ነው የሚሆነው።ከመቀላወጥ ደግሞ የባሰ አፀያፊ ነገር የለም። ልመና ማለት ነው! የኢኮኖሚ ለማኞች ልንሆን እንችላለን። ሰርተን እስኪያልፍልን ድረስ።የባህል ለማኞች መሆን ግን የለብንም። ሲሆን ከኛ ነው መውሰድ ያለባቸው እየለመኑ።  ሃገሩን መንጠቅ ሲያቅታቸው “የባህል ቅን ተገዢዎች ያደርጉሃል”። የባህል ቅኝ ተገዥ መሆን ደግሞ ከዋናው ቅኝ ተገዢነት የበለጠ ይጎዳል። ያኛው “ኮተቱን ጭኖ ይሄዳል” በትጥቅ ትግልም በብሔራዊ ወኔም ታግለህ ሰንደቃላማህን ልትሰቅል ትችላለህ። “ሰንደቃላማ የማትሰቅልበት እንደወራሪ ጠላት የማታስወግድበት ወረራ የባህል ወረራ ትልቁ አደጋ ነው። ስለዚህ ይህ ችግር በመንግሥትም በሕዝብም ታስቦበት ሊታረም ይገባል።”http://www.ethiotube.net/video/17458/Must-Watch-Documentary--Ethiopian-Business-and-their-Foreign-Names-in-Ethiopia   ኢትዮጵያ ሰማይ ድረገጽ -ጌታቸው ረዳ www.ethiopiansemay.blogspot.com getachre@aol.com


Wednesday, January 18, 2012

አዲሱ ኦነግና ነባሩ ኦነግ ያልለቀቃቸው በሽታ


አዲሱ ኦነግና ነባሩ ኦነግ  ያልለቀቃቸው በሽታ

ጌታቸው ረዳ


በዚህ ልጀምር። የአዲሱ ኦነግ ጅማሮ የሚያበረታታ ቢሆንም መላቀቅ ያለባቸው ያልለቀቃቸው የድሮው በሽታ ስላለ እሱንም እንዲያርሙ አሁንም ከመተቸት አንቦዝንም። ለብዙ ዓመት ስለተቸናቸው “መሻሻል አሳይተዋል”። ትችታችን አሁን ላሳዩት ውጤት መንገድ መርቶ አሳይተዋቸዋል። “አጀንዳቸው የማይሰራ መሆኑን ስናስረዳ “በኦነጎች ቀርቶ” “የኦሮሞ ሕዝብ ጠላቶች” ተብለን  “ስማቸው በማልጠራቸው ኢትዮጵያውያን ሳይቀር ለአመታት ተዘልፈናል። እኛም እነሱም እየተተቻቸን የቀራቸው ጉዞ እንዲጓዙ ትችታችን ጠቃሚነቱን ማናናቅ አይኖርባቸውም። እና በርቱ፡ ይህ ካልኩ ዘንዳ ኦነጎች የምትወዱት/የምትጠሉት ትችቴን እነሆ ከጠቀማችሁ ተበራቱበት።ዛሬ አልዋጥ ቢላችሁ ከመረራችሁም እርግጣና ነኝ አንድ ቀን ሲዋጥላችሁ ይጣፍጣችል። ዛሬ ብዙ ነጥቦች ስላነሳሁ፤ ከደከማችሁም ሳይሰለቻችሁ እየተመላለሳችሁም ቢሆን ጊዜ ወስዳችሁ ትችቴን አንብቡት።
እንደሚታወቀው በፈረንጆች አዲስ ዘመን ዓመት አቆጣጠር በከማል ገልቹ የሚመራው “ኦነግ” ከመገንጠል ወጥቶ ኢትዮጵያዊነቱን አውጇል ብለው የድርጅቱ መሪዎች ተናግረው ብዙ ሰው ደስታውን በመግለጽ ላይ ሲገኝ አንዳንድ ወገኖች ደግሞ “እስኪ ረጋ በሉ” ሲሉ የሁለቱም “ኦነጎች” መርሃ ግብር/መመሪያ እንፈትሽ ብለዋል።
አንፈትሽ ያሉት እኔን መሰል ግለሰቦች እና እንዲሁም ኢሕአፓዎች ናቸው ተብሏል። ኩፉኛ ሲወገዙ አልፎም “ይህንን ረጋ ብላችሁ እስቲ ፈትሹ ያሉት በፈረደባቸው ‘ኢሕአፓዎች’ ላይ ወዳጄ ቀድቶ የላከልኝ “ካረንት አፈይረስ/ኦካዴፍ” የተባለው ፓል ቶክ ውስጥ “ምንም ቢሆን ኢሕአፓዎች በሙሉ ካልተገደሉ የኢትዮጵያ ፖለቲካ አይጠራም’ ያሉትን በነሱ ላይ የታወጀውን ሳዳምጥ “ከመሳቀቅ በላይ” “በኢሕአፓ ላይ የቀይ ሽብር ይፋፋም!” ስትል ኢሕአፓዎችን እና ደጋፊዎቻቸውን ያስደነገጠች የዛው ክፍል ሴትዮ፤ “ቀለቤቴን ስጧት” በሚለው በብዕር አጣጣሉ ሕሊናን የሚያነሆልል ብዕርተኛው በልጅግ አሊ በጻፈው መጽሐፍ ላይ ከኮምፒዩተር በስተጀርባ ሆና በኢሕፓዎች ላይ ቀይ ሽብር ይፋፋም” ስትል እንደ አውሬ ስትጮህ አብረዋት “በርቺ ፤አይዞሽ” የሚሏትን ከገፅ 43 ጀምሮ “ራስኮልኒኮቭ ሰዎቹን ከገደለ በላ ለምን ተጨነቀ?” ብሎ የጠየቀውን አስታወሰኝና መጽሐፉን እንደገና አንስቼ እንዚህ ሰዎች አሁንም ግድያ ለምን እንዲፋፋም እንደሚወዱ መከለስ ነበረብኝ እና መልሱን አገኘሁት። መጽሐፉን ገዝታችሁ ብታነቡ ካሁን በፊት ያላወቃችሁትን ምንነታችሁ ታገኙታላችሁ Beljig.ali@gmail.com ያ ፓልቶክ ብዙ ችግር አለበት፤ለወደፊቱ እንዴት እንደሚደመደም እግዚሔር ይቀው እንጂ “ያልበሰሉ አደገኛ ሰዎች” ያሉበት ክፍል ነውና ምሕረቱን ይስጣቸው።
ዛሬም ቀይ ሽብር በኢሕአፓ የሚሉት “የአዲሱ ኦነግ” መርሕ ካልተቀበላችሁ “ለሞት ተፈርዳችል የሚሉት እነማን እንደሆኑ ሁላችሁም የምታውቁት ይመስለኛል። እኔኑን ግራ የገባኝ ግን የሚከተለው የከማል ገልቹም ሆነ የኑሮ ደዶፋ እና የአሚን ጃንዳይ ቡድን በግንጠላው ላይ ያላቸው መልስ ነው።
ምንድነው ሲሉን የነበረው? ታስታውሳላችሁ? ካሁን በፊት ኦነግ የመገንጠል ጥያቄ ጠይቆ አያወቅም! ሲሉ ብዙ አነጋግሮናል። የኢትዬ-ሚዲያ ድረገጽ አዘጋጅ ወዳጄ አቶ አብርሃ በላይም ኦነግ የመገንጠል ጥያቄ ጠይቆ አያውቅም የሚለውን አነጋገራቸው በማድመቅ ድጋፉን በድረገጹ የመሪዎቹ ውሸት “ብሪሊያንት/አሳማኝ” ሲል ሲከተሉት የነበረውን የመገንጠል ጥያቄ አቋማቸው “በኢትዮጵያውያን ሃይሎች” የተዋሸ እንጂ የኦነግ ጥያቄ እንዳልነበረ አስነብቦናል። እኛ እንደዋሾች ተቆጠርን ማለት ነው። በዚህ ላይ ጽፌአለሁ። ታስታውሱታላችሁ? ብዙ እርግማንም ደርሶኛል።
አሁን ዋሾው እኔ ወይንም መሰሎቼ ሳንሆን የእነሱን ውሸት ያደመቁላቸው እና የከማል ገልቹ ወገኖች እና እራሳቸው መሪዎቹ እንደነበሩ “ከማል እራሱ እና በፕሮግራሙ “መገንጠልን እንዳስቀረ ተናገሯል።ሌሎቹንም የተናገሩትን አስደምጣችለሁ/ታነባላችሁ።
ለምሳሌ ኢሳት ከተባለው ስዕለ ድምፅ አዘጋጅ ከወዳጄ ሲሳይ አገና ጋር በቅርቡ ኮሎኔል ሃይሉ ጎንፋ ከተባሉ የአዲሱ ኦነግ አመራር አባል እና የአቅም ግምባታ ሃላፊ ከሆኑት ጋር  ቃለ መጠይቅ አድርጎ ነበር። ሃይሉ ጎንፋ አስመራ ውስጥ ሆነው በስልክ የሰጡትን የስልክ ቃለ መጠይቅ እነሆ።
ኢቲቪ- ሲሳይ አገና፡- “…አንግዲህ ደጋግሜ የማነሳው እንደሚታወቀው አርስዎም ሆኑ ጀኔራል ከማል ገልቹ በኢትዬጵያ ሠራዊት ውስጥ ከፍተኛ አመራር ቦታ የነበራችሁ ናችሁ። እንግዲህ በብዙ ሰው ውስጥ የሚነሳው ጥያቄ ኦነግ የኦሮምን ሕዝብ ስም ይዞ የተነሳ ነው፡ ግን ድርጅቱ ወደ 40 ዓመታት እንዳስቆጠረ ይታወቃል.. (የድርጅቱ አቋም) የኦሮሞ ኢትዬጵያዊነት ወይንም ኦሮሞ ኢትዮጵያዊ አይደለም የሚል ለመገንጠል የሚደረግ እንቅስቃሴ ስለሆነ በሌላ ኢትዬጵያዊም ዘንድ ጥቂት በማይባሉ ኦሮሞዎችም ጭምር የኦሮሞን ሕዝብ ለማስገንጠል ነው በሚል ረገድ የሚነሳ ጥያቄ አለ። ኢትዮጵያ ሠራዊት የነበራችሁ በአመራር ስትመሩ የነበራችሁ ሰዎች አሁን ተመልሳችሁ ኦሮሞን ከኢትዮጵያ ለመገንጠል ከሚንቀሳቀስ ቡድን ውስጥ ነው የገባችሁት እና አንዴት ነው ቢያብራሩልኝ?” 
ኮለኔል ሃይሉ ጎንፋ፤- “አሁን ከመነሻው ጥያቄ ያለው ስሕተት ምንድነው፤ ገዢዎች ሁልጊዜ ሕዝቦች እንዲጠራጠሩ እንዳይተማመኑ በፍርሃት እንዲኖሩ ከሚያደርጉ አንዱ የቀን ቅዠታቸው ይቃዡና ቅዠታቸው እንዲያስተጋባ ያደርጉታል።…ኦሮሞ ነፃነት ግምባር የመገንጠል ዋና አላማው አይደለም። ተገነጠለ የሚል ስም የሚለጥፉበት ሌሎች ሃይሎች ናቸው፤ገዢዎች ናቸው።…(የመገንጠል ጥያቄ) የኦሮሞ ነፃነት ግምባር አጀንዳም አይደለም።…ገዢዎች አንደዚህ ሲሉ እኛም (እነርሱ ጋር)ማስተጋባት ትከክል አይደለም። ሲሉ መገንጠል የጥቆ አያውቅም በማለት ክደዋል። (ይኼ በጣም በቅርብ ገዚ ነው።)
ካሁን በፊት ኑሮ ደዴፎና አሚን ጃንዳይ የተባሉት የአዲሱ ኦነግ አመራሮች “ኦነግ የመገንጠል ጥያቄ ጠይቆ አያውቅም” ሲሉ መልሰው ነበር። አሁንም ደግሞ ኢሳት “ትኩረት” በተባለው መደቡ ላይ “አዲሱ ኦነግ” ሜነሶታ ላይ አዲስ ራዕይ/አጀንዳ ይዤ ብቅ ብያለሁ ሲል በስልክ ዶ/ር ኑሮ ደዴፎን በስብሰባው ጠርቶ ቃለ መጥይቅ ሲያደርግላቸው፤ ዶ/ር ኑሮ ደዴፎ የሚከተለው ብለው ነበር።
ጠያቂ” ፦ ቀደም ሲል ከነበረው አቋም በምን ይለያል?በግልፅ አድማጮች እንዲረዱት ፈልጌ ነው ዶ/ር ኑሮ፡
ዶ/ር ኑሮ መልስ፦”ዌል፤-ከዚህ በፊት የነበረው (አጀንዳ) እንደሚታወቀው አብዛኛው የሚለው “የኦሮሞ ሕዝብ የገዛ ራሱን አገር የማቋቋም አላማዎች አሉት” (ነበሩበት)። ያሁኑ ጊዜ ግልጽ አድርጎ ከሌሎች ኢትዮጵያ ሕዝቦች ጋር (ለመኖር) አንድ አገር መስርቶ (ኢትዮጵያ) አሁን አንዳለው እንደ ወያኔው የውሸት ፌደራል ሳይሆን (ዓለማችን) “በፌዴራል ዲሞክራቲክ”  ለመኖር ነው።(አሁን ይዞ የመጣው (መርህ) ካለፈው የሚያሳየው ልዩነት ካለ ያሁኑ አንድ አገር (ኢትዮጵያ) የመቀበል ጉዳይ ነው።
የኢሳቱ አበበ ገላውም አንዲህ ሲል አረጋግጧል፦“Washington DC (ESAT) – The Oromo Liberation Front has announced its historic decision to drop its long-held secessionist agenda and to embrace the unity of Ethiopia under a genuine federal arrangement that must guarantee the rights, equality and liberty of all Ethiopians.” January 2nd, 2012)
እንግዲህ በዚህ መልክ አዲሱን ኦነግ ለሚመሩ የምጠይቀው ጥያቄ “ኦነግ የመገንጠልን ጥያቄ አጀንዳ የለውም” የሚለውን አንመን ወይስ “ኦነግ የመገንጠል አጀንዳውን አንስቷልን” እንመን? በዚህ ውዥምብር ስንሰደብ ለውሸታቸው “ይቅርታ አንዲጠይቁን” ማንን እንጠይቅ? ወሸታሞቹ እነሱ ወይንስ እኛ? በዚህ የውሸት ባሕሪ ተነስተን አዲሱን የኦነግ አማራር አሁንም ለወደፊተም ከዚህ ልማዳቸው ተነስተን ብንጠራጠር እንዴት ልያስወቅሰን ይችላል?
እንቀጥል፦
ፕሮግራማቸውም ብትመለከቱት ለኔ ወያኔአዊ እንጂ ምንም ልዩነት የለውም። አማርኛ ስለሚጠሉ መግለጫቸው “በእንግሊዝኛቸው” ነው የተጠቀሙት እና እኔው ራሴ ፕሮግራማቸው ወደ አማርኛችን ስለውጠው አሁንም የተጠቀሙበት የነገዶች አገላለጽ ወያኔ የነደፈው/የተከተለው “ብሔር፤ብሐረሰቦች እና ሕዝቦች” የሚለው ነው። ሕዘብን በቋንቋም እንደ ወያኔ ተንትነውታል። ይህ ትምህርት ኮሚኒስታዊ፤ሲከፋም ጣሊያኖች አገራችን ሲወሩን የተጠቀሙበት የትንታኔ ፋሸስታዊ ንድፍ ነው። እነኚህም በዛው ፈለግ ተከትለዋል።
በመሰረቱ እነዚህም የኮሚኒስቱ የዋለልኝ መኮንን ደቀመዛሙርቶች ናቸው እና ዋለልኝ የተጠቀመበትን አገላለጽ ተጠቅመውበታል። ላገራችንም አደገኛነቱ አሁንም በነዚህ የፖለቲካ ገልቱዎች መቀጠሉ ያሳዝናል።
የዋለልኝ ኢትዮጵያ አገላለጽ አስተምህሮ ምን ብሎ ነበር? እነሆ፦“Ethiopia is not really one nation. It is made up of a dozen nationalities with their own languages, ways of dressing, history, social organization and territorial entity. . . . I conclude that in Ethiopia there is the Oromo Nation, the Tigrai Nation, the Amhara Nation, the Gurage Nation, the Sidama Nation, the Wellamo Nation, the Adhere Nation, and however much you may not like it the Somali Nation.” Wallelign. ዋለልኝ መኮንን ይህ አገላለጽ ከማን አገኘው? ከኮሚኒስቶች። ኮሚኒስቶች ብቻ ሳይሆኑ ጣሊያኖችም ጭምር ነው። ለመሆኑ ዋለልኝ ይህ በጻፈ ከብዙ ዓመት በላ ኢትዮጵያ የአማራዎች አገር እንጂ እሱ የጠቀሳቸው “የኢትዮጵያ እስረኞች” ብሎ የሚላቸው (በኔ አጠራር) “ነገዶች” በሱ አገላለጽ “ራሳቸው የቻሉ አገሮች/መንግሥታት” አንዳልሆነች ከገለጸበት እና የኮሚኒስቶቹ ፖለቲካ ኪሳራ ካጋጠመው ወዲህ ዛሬ “Wallelign misunderstood his country and its people as much as the people misunderstood him”. (ዘውገ ፋንታ) ዋለልኝ በቅርብ ከሚያውቁት አብሮ አደጎችና ጓደኞቹ መካከል። ተብሏል።
ዋለልኝ ያስተማራቸው ተ.ሓ.ህ.ት እና ኦነጎች ዛሬም በዛው በከሰረው ኮሚኒስታዊ እና ፋሺስታዊ ጎዳና ሲራመዱ አጀንዳቸውን ዛሬም እንደ ተገንጣ ወያኔ እና ሌላኛው ኦነግ አስተዳደራዊ ቅርጽ አስነብበውናል። ከዛው የተነሳም ዕድሜ ለዋለልኝ የየመንገሥታቶቹ ባንዴራዎች ተሰፍተው ዋለልኝ “አሳሪ” ከሚላት ወህኔ ቤት ውስጥ ነፃ ወጥተው ባንዴራቸው ያውለበልባሉ። አገር ውስጥ የሌሉም ኢንተርኔት ድረገጽ ላይ የፈለጉትን ጨርቅና የቀለም ዓይነት መርጠው ያውለበልቡታል።
ይህ የሕሊና በሽታ መነሻው ከየት ነው? ተብሎ መመርመር አስፈላጊ ነው።መለስ ብለን (ባክ ግራውንድ የሚሉት ተንታኞች) ፋሺስቶች እና ኮሚኒስቶች በየወቅታቸው ያሴሩብንን የሴራው መነሻው ጊዜ ከናዚዎች ኢትዮጵያን ዓይናቸው ውስጥ አስገብተዋታል።
ከሚከተለው መነሾ እንመልከት፡-“The Nazis of Austro Hungary had already in the 1930's targeted Ethiopia as a threat against white supremacy, and white colonialism in Africa, in much the same way as the Bush administration talks about Iraq's "weapons of mass destruction" and threat to "Western Civilization." In the case of Ethiopia, the classic work on the subject, which we have repeatedly introduced to the Ethiopian public, myself and the Ethiopian patriotic Diaspora in Germany, was , of course, the book by the Austrian Nazi, Baron Roman Prochazka's "Abyssinia the Powder Barrel" (Vienna 1935), translated in all the major Western languages (including American English, as the following text shows) before the Italian invasion in 1936. Baron Roman Prochazka was posted for two years as Austrian Consul in Addis Ababa until his expulsion in February 1934, as we say now for activities not compatible with his job of a diplomat. The Italian translation of Prochazka's book entitled ABISSINIA PERICOLO NERO meaning “Abyssinia the Black Threat or Danger” was published in 1935, which is a year before the Fascist invasion .Starting from the first page, Prochazka alerts his white public by stating that since four years that Emperor Haile Selassie's Ethiopia, in "close co-operation with Japan," was engaged "on a life and death struggle with the white race, the consequences of which are incalculable. The targets are the colonial powers in Africa without exception. It is hardly possible to imagine a more unhappy situation of a white man than to have to live under the oppression of an Abyssinian grandee. The prevalence of this contemptuous invective is characteristic of the mentality and attitude of the natives who imagine themselves to be infinitely superior to the white race."
Strikingly, the solution proposed by Prochazka is, and that is where he brings us to to the subject under discussion, is the tribalisation of Ethiopian politics for the purpose of divide and destroy. Prochazka was the first ever to have spoken of "self determination "as the most handy instrument for the dismantlement of the Ethiopian State. Here in brief are the highlights of Prochazka's strategy:
"The numerous peoples and tribes who inhabit the territory of the Ethiopian state, and which differ in race, language, culture and religion from the ruling minority of the Abyssinians proper, would long ago have thrown off the Abyssinian yoke if they had been given the right of self-determination. Instead, they are being forcibly kept cut off from European influences and from the advantages that progressive colonization could confer upon the country.” (Origin of Tribalisation of Ethiopian Politics: From Fascism to Fascism Aleme Eshete) www.ethiopiansemay,blogspot.com Or http://www.tecolahagos.com/origin_tribal.htm
ከላይ የተመለከታችሁት ኦነጎች እና ወያኔዎች የመሳሰሉት የተከተሉት ትምህርት ከዋለልኝ ብቻ ሳይሆን ከነዚ ፋሺስቱ ከሮማን ፕሮቻስካ እንደሆነ ያመላክታል። “ኢትዮጵያ የብሔር ብሔረሶቦች እና ሕዝቦች እስር ቤት ነች” ሲሉ የአዲሱ ኦነግ አማራር አባል ከአስመራ ባለፈው ሰሞን ያስተላለፉትም ከዚህ በመነሳት ነው። የታሰሩበት ምክንያት ከአስተማሪዎቻቸው አንዱ (ፕሮቻስካ) ሲገልጽ “they are being forcibly kept cut off from European influences and from the advantages that progressive colonization could confer upon the country.” ኦነጎች (ሁለቱም) ከወያኔ ጋር የሚያምኑት ላቲን ለኦሮሞ ሕዝብ የጽሐፈት መጠቀሚያ ቋንቋ የተመረጠበት መደረጉ ምክንያት በፕሮግራማቸው እንደሚነበበው እና ካሁን በፊት 1000 ኦሮሞ ምሁራን ከወዳጃቸው ወያኔ ጋር ፓርላማ ሆነው ሲያጽድቁት የተናገሩትም “ላቲን መጠቀም በቀላሉ ከስልጣኔ ጋር ያገናኘናል፤ ምክንያቱም ላቲን የሰለጠነ የስልጡኖች መነጋገርያ ቋንቋ ስለሆነ ነው።’ በማለት ነበር ያጸደቁት። ፕሮቻስካም እንዲሁ “ከአውሮጳውያን እኩል እንዳይሰለጥኑ ብሔሮች የመገንጠል መብት ተነፍገው ታስረዋል” ብሏል።



በዚህ መልክ የፋሺስቶችና የኮሚኒስቶች መመሪያ አፅም እና ቅረቶቻቸው ዛሬም በኢትዮጵያ የጎሳ አቀንቃኞች ውስጥ ህያው ሆነው እየታዩ ነው።
ለመሆኑ ከማል ገልቹ በሳምነቱ ስለ የላቲን ቋንቋ በቪኦኤ ተጠይቀው ሲያብራሩ “በአባባላቸው የተለየ አነጋገር ይጠቀሙ እንጂ” ከአቻቸው የሚለይ አመለካከት የላቸውም። ለምን እንደተገለጸ ሲገልጹም የላቲን ምቹነትን አብራርተዋል።
ለመሆኑ ግዕዝ ላለማለት “ሳባ” የሚል ቋንቋ ጀኔራሉ ተጠቅመዋል፡ ለምን? ሳባ እና ግዕዝ ልዩነት እንዳለው አላወቁም? ወይስ ብቸኛው የአፍሪቃ ፊደል “ግዕዝ ፊደል” “የኢትዮጵያውያን ፊደል” ማለት አቀበት ሆኗቸው? እኔ እየጻፍኩ ያለሁት አሁን የምታነብቡት ፊደል ሳባ ነው? ይገርማል። ለነገሩ ግዕዝ (ግዕዝና አማርኛ ኦነጎች የደብተራዎች ቋንቋ የሚሉት) ከ“ላቲን” በተሻለ ኦሮምኛን ለማገልገል እንደሚችል በመጽሐፌ የተገለጸው መረጃ ሰጥቼ ልሰናበታችሁ። ‘ቁቤ’የተባለው ኦነጎች የፈለሰፉት ሳይሆን ጸረ ኢትዮጵያ ክፍሎች የፈጠሩላቸው አንደሆነ ከኦኖጎቹ ፀሓፊዎች መረጃው እነሆ “. The early writing in the Oromo language began almost two centuries ago. It is the conquest of Oromiyaa by Abyssinia that interrupted its development into full-fledged writing instrument. Of the earliest writing was vocabulary of Oromo language in 1842 in Latin script by J. Ludwig Krapf, a German national.”
ክራፕፍ የተባለው ማን እንደሆነ የኦነጎችን ታሪከ የተከታተላችሁ እና የሚስዮናውያን ጣልቃ ገብነት ያነባበችሁ ሰዎች የምታውቁት ሰው ነው። ክራፕፍ ከራሴ ው መፅሐፍ ውስጥ የተወሰደ ጥቅስ ምን ብሎ እንደነበር ክራፕፍ  እነሆ “በሸዋ ቆይታየ ለጋሎች የተለየ ትኩረት ያደረግሁት በእግዚአብሔር ፀጋ ፕሮቴስታንትነትን ከተቀበሉ በኋላ የሠራዊት ጌታ ለጀርመኖች በአውሮጳ ላሳየው የተልእኮ መሳካትን የተመረጡ እንደሚሆኑ በመገመት ነው።"(J.Lewis Krapf; Travels, Researches and Missionary Labour During an eighteen years Residence... (London :1968), 2nd ed. p. 72)" (የወያኔ ገበና ማህደር -ገጽ 215)ብሏል።
ግን እውን ላቲን ከግዕዝ የተሻለ ነው?
አንድም የጋላ ቋንቋ ድምፅ በእንግሊዝኛ/ላቲን ፊደል የማይገለጽ የለም እንዲያውም ከኢትዮጵያዊ ፊደል ይበልጥ በተሻለ ረገድ ሊገለጽ የማይቻል የለም።"(J.Krapf: Journal of Rev. Mess Issenberg and Krapf etc. London 1843 and An Imperfect outline of the elements of the Galla -Language by Rev. J.L Krapf.
London 1840) ከሚለው የተተረጎመ።
“አንድም የጋላ ቋንቋ ድምፅ በእንግሊዝኛ ፊደል የማይገለጽ የለም እንዲያውም ከኢትዮጵያዊ ፊደል ይበልጥ በተሻለ ረገድ ሊገለጽ የማይቻል የለም።” ያለውን የኦነጎቹ አስተማሪ ሌላው ሐቀኛ ጀርመናዊ ቻርለስ ቱትሸክ የጋልኛ መዝገበ ቃላት አዘጋጅ የክራፍን ትክክለኛ ያልሆነ ሐሳብ ተቃውሞ 30 ሆሂያት ያሉት ፊደል አዘጋጅቷል። የላቲን ጐዶሎ ፊደል ለጋልኛ ይሆናል ማለቱ ምን ያህል ውሸታም እንደሆነ ያሳያል። ለመሆኑ የእንግሊዝኛ ፊደል እንደ ጰ፤ ጨ፤ ጠ፤ ኘ፡ ዠ፤ ቀ፤ ፀ፤. ወዘተረፈ፤ የመሳሰሉት ድምፆች እንደ ኦሮምኛ አሉት? ከዘረኝነት ነፃ አስተዋይ ሕሊና ያላቸው የቋንቋ ሊቃውንት ሁሉ እንደሚያረጋግጡት የኢትዮጵያ ቋንቋዎች በመሠረታዊ ድምፅ አወጣጣቸው ዓይነት ብዛት ተመሳሳይ ናቸው። ለምሳሌ አማርኛ አና ኦሮሚኛ ብንወስድ በአማርኛ ውስጥ ከሚገኙት 27 ተነባቢ ድምፆች ውስጥ 23 በኦሮሚኛም ይገኛሉ። እንደዚሁም 24 የጋሊኛ ተነባቢዎች 23 በአማርኛ ያሉ ናቸው። ይህ ዓይነት ተቀራራቢነት በቋንቋዎች መካከል ካለ አንደኛው ቋንቋ በሚጽፍበት ፊደል ሌላውን መጻፍ የሚቻል መሆኑን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቋንቋ መምህር ባዩ ይማም፤ ባቀረቡት ጥናታዊ ጽሑፍ ሥርዓተ ጽሕፈት ውይይት 3 ቅጽ 1 ቁጥር 1 መጋቢት (1984) ገጽ 17-38 ያመለክታል። ኦሮሚኛ ከላቲን ይልቅ ከኢትዮጵያ ፊደል ተስማሚ ድምጾች (ጰ፤ ጠ፤ ጨ፤ ) እና አጻጻፍ እንደሚቻለውአየለ በክሬ (Ethiopic An African Writing System, (Canada: 1997) ገጽ 95). (ምንጭ ይደረስ ለጎጠኛው መምህር- ደራሲ ጌታቸው ረዳ -ገጽ 228)
በተጨማሪም  በአዲሱ እና በቆየው ኦነጎች መካካል በድረገጻቸው አጀንዳ የፖለቲካ ኦሮሚያ እና ኢትዮጵያ የሚሉት አገላለጽ ኤምፓየር/አማራ የሚሉት የሁለቱ ኦነጎች ውሸት እኔ የተከራከርኩበት (ቆየት ቢልም) አንድ አገር ዋዳድ ምሁር ኢትዮጵያዊ የገለፁትን ጭምር አንብቡ OLF & It’s Group: - How Many More Raids Do Ethiopians Tolerate? by Engeda Kassa “This article is an extracted version of my 15 pages commentary article posted on the then Ethiopian Unity website in 2004, to an argument made between Mr. Getachew Redda and an OLF official Mr. Dumesaa Diimmaa on OLF’s Mission issues.” አመሰግናለሁ። ጌታቸው ረዳ www.ethiopiansemay.blogspot.com getachre@aol.com



.







1-