ክፍል 2
ሕዝባችን ለጠላቶቹ ሸብረክ ብሎ እንዲገዛና ገዢዎቹን ማስወገድ ያልቻለበት ምክንያቱ ምንድነው?
መልስ
ለዶ/ር ዮናስ ብሩ፡
ጌታቸው ረዳ
Ethiopian Semay
9/1/1953
ባለፈው ከፍል 1 ላይ ይህንን
በሚል ነበር ያቆምነው ፦ «Because፣ this is
the minimum number of years required to educate one generation of students in
the country of your enemy exposed to the ideology of [their] enemy.” ለምን ያንን ሁሉ አመት ይፈጃል? ይላል “ቤዝሜኖቭ” እራሱን በመጠየቅ። ምክንያቱም ይላል ሲመልስ፡ ለማጥቃት የፈለግከውን አገር የተማሪዎቿን
(ያንድ ተረካቢ ትውልድ) ሕሊና ለመለወጥ፤ የራስክን አስተሳሰብ በሕሊናቸው ለማስረጽ የሚፈጀው ጊዜ ያንን ያህል አመት እየተጓዘ መጠናቀቅ ስላለበት ነው።” ይላል። በሚል ነበር በይደር ያቆየነው።
ይህንን በምሳሌ ለማየት ከፈለጋችሁ በጣሊያን ፋሺስቶች ጊዜ ፤ በደርግ ጊዜ በወያኔ ጊዜ ፤ በኦሮሙማው ባሁኑ በአብይ ጊዜ የተከሰቱ የሕሊና ጥምዘዛዎች/ጥቃቶችን ስንመለከት፤ዝርዝሩ
በውጭ ሀገር ርዕዮት የተበከለው የ60ዎቹ የተማሪዎች አብዮት ለደርግ ያቀበለው የማኦ፤ማርከሲዝም ሌኒኒዝም አስተሳሰብ ማለትም “የሶቭየቶች/ የቻይናዎች/ ፍልስፍና በማስገባት የማሕበረሰቡን ባሕላዊ ክሮች በመበጣጠስ "ወንድም በወንድሙ ልጅ በአባቱ ጎረቤት በጎረቤት "የግደል ተገዳደል" የጨካኔ ሕሊና እንዲኖሮው በማድረግ ለቀወስ የዳረገውን ሁኔታ ስንመለከት ፤
ወይንም በወያኔ በኦሮሙማው ባሁኑ በአብይ ጊዜ የከፋፍለህ ግዛ፤ አክራሪ የጎሳ ብሔረተኛነት ማለትም “ከደቡብ አፍሪካው’ ክልላዊው ዘረኛ አስተዳዳር የማይተናነሰው የቋንቋ አስተዳደር ተግባራዊ በማድረግ ጐሳዎችን በተለይ አማራውን በግፍ ለጥቃት የተጋለጠበት ሁኔታ ስናይ፤
ወይንም የፋሺስት ጣሊያኖች ሴራ” በወያኔዎች ፈጻሚነት “በኤትኒክ ፌደራሊዝም” አገርን የማፍረስ ሴራ ተግባራዊ እንዲሆን በዝግታ ከ17 እስከ 22 አመት ፈጅቷል። ይህንን ስታዩ ፤ ይህ ሁሉ ጥቃት በአገር በቀል መሪዎች በሕገመንግሥት
ተደንግጎ ለምን እንደ ፈራረሱ ሕዝቦች ተሎ አልፈራረሰም? ትሉ ይሆናል። ምክንያቱም፤ ለሺዎች ዘመናት እንደ ሙጫ የዞት የነበረው
የማሕበረሰቡ መስተጋብር ተሎ ለማላቀቅ ከባድ ሰለሆነ ሲንገዳገድ እሰካሁን ደረስ መንምኖም ቢሆን ላለመውደቅ እየተንገዳገደ ነው። ሌላ አገር ቢሆን ግን የኸኔ ፈርሶ ነበር። ሆኖም መጠነ ሰፊ የሆነ ጥቃት ደርሷል። ሁኔታውም አሳሳቢ ነው።
ይህ ሳብቨርዥን/ግዝገዛ ሲፈጸም ያለ ምንም ጠንካራ ሀገራዊ ወይንም “ፓትርዮቲክ/ሀርበኛ” የተቃውሚ አጥር ሳይገጥመው የተከናወነ ነው። እርግጥ መጠነኛ ተቃውሞች ተደርገዋል፤እየተደረጉም ነው፡ ግን በቸልተኛነት ስለተለቀቀ “ዲሞራላይዘሺኑ/የሞራል ዝቅጠቱ እና ለሃይማኖታዊ ሕግጋትና ለሞራላዊ ድንጋጌ እንዳይገዛ ጥልቅ ግዝገዛ በመደረጉ” በውስጥ ተዋናዮች “በጠመንጃና በሕሊና አጠባ” ስለተከናወነ “በሦስት ትውልዶች እድሜ ሂደት” ውስጥ ተከናውኗል ማለት ነው፡ (ደርግን በልዩ ቦታ አስቀምጣችሁ)፤በዋናዎቹ የውጭ ተላላኪዎች “በወያኔ እና በአሁኑ በአብይ አሕመድ "የኦነጋዊው ኦሮሙማ" አገዛዝ ወቅት ከፍተኛ ግዝገዛ ተከናውናል።
ከፋሺስት ጣሊያን የቋንቋ/የነገድ ቅየሳ ለ 60ዎቹ ተማሪዎች ተላለፎ ፤ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢትዮጵያ ውስጥ በገዛ ልጆቿ የተቀየሰው አደገኛው “ኤትኒክ ፌደራሊዝምን /የቋንቋ/” አስተዳዳር ተዋውቋል ማለት ነው። ሁለቱንም ‘ርዕዮት’ በውጭ አገር የአይዲዮሎጂካል ሳብቨርዢን ተዋናዮች የተሰነዘሩበት የሕሊና አጠባዎች ናቸው ማለት ነው።
የዲሞራላይዘሺኑን ዝቅጠት ባጭሩ በ15 እስከ 20 አመት ሲጠናቀቅ፤ አሁን ያለው ሕብረተሰብም ይሁን በመወለድ ላይ ያሉ አዳዲስ ትውልዶች፤ያስተሳሰባቸው ሕሊና ከተቀየረ አገራዊ ፍቅር ስለማይኖራቸው ሁለተኛውን ደረጃ ማለትም “ዲስታብላይዘሽን” አገርን የማናገቱ ሂደት በቀላላሉ እንዲከናወን ይረዳል ማለት ነው (ስለተከናወነም በትግራይ፤ በኦሮሚያ ፤ ሶማሊ ፤ ወዘተ...የምናየው ሐላፊነት የጎደለው ጀብደኛውና አደገኛው ሀገር የማፍረስ ግዝገዛ በቀላሉ ማየት ትችላላችሁ።
2ኛው የ Destabilization አገርን የማናጋት ሂደትና ወጥመድ
የዚህ ሂደት ወጥመድ ደግሞ ምን አንደያዘ እንመልከተው፡
የሕብረተሰቡን የተረጋጋ ሕይወት (የተረጋጋ ሀገር) ለማናጋት የሕዝቡን አቅጣጫ/ቀልብን በማሳት የሚከናውን ብቻ ሳይሆን በሀገሪቱ ውስጥ ያሉት አርበኞቿ፤አገር ወዳዶቿ ፤ ምሁራኖቿን በዝግታ ማስወገድ ለመናጋቱ ከፍተኛ ክፍተት ስለሚኖሮው በነዚህ ላይ ጥቃት መከናወን ስለነበረበት ጥቃት ተፈጽሟል። ከሕሊና አጠባ የተሸጋጋረው የዲስታቢላይዘሽን ሂደት በጣም አስፈሪ እና የአገሪቱን ማሰርያ /መልሕቅ የሚበጠስበት ወቅት ነው ማለት ነው።አገር ሲናጋ ማሰሪያ፤ሉጓም የሌለው ፈረስ ይሆናል ማለት ነው።
ሊቃውንቶች፤ምሁራኖች፤አገር ወዳዶች እና አርበኞች የአገሪቱ መሪዎች እና ሉጓሞች ናቸው።እነዚህ “እሴቶች” ናቸው። ማለትም “ዋናው የአገሪቱ አንጡራ ሃብት ናቸው”። ካፒታል /አሴት የሌለው ባንክ “ባንክራፕት እንደሚሆነው ሁሉ” አገሪቱም ምሁራኖቿ ስታጣ “አገሪቱ ትናጋለች” ማለት ነው።እነዚህ በሰበብ አስባቡ በውጭ እና በውስጥ ተዋናያች አጥቂነት እየተጠቁ ከስራ እንዲፈናቀሉ፤ እንዲታሰሩ፤እንዲሰደዱ፤ አካላቸው አንዲጎድል፤ አንዳንዶቹም እንዲነቅዙ፤ ዱለት እንዲያምራቸው ሆዳሞችና አድርባዮች እንዲሆኑ ከተደረገ፡ አገሪቷ ጠባቂ፤ጠበቃ፤ተሟጋች፤ተዋጊ፤ተከራካሪ፤አስተማሪ፡ ስለማይኖራት “አገሪቱን ለማናጋት” ለአጥቂዎቹ ስለሚቀል፤ የወጠኑትን የማናጋት፤የማፍረስ ሂደት በቀላሉ ይጠናቀቃል ማለት ነው።
የሕብረተሰቡ “ኤክሶዳስ” ስደት፤ሞት፤ባርነት፤ውርደት፤ ባይተዋርነት ውስጥ ይገባል ማለት ነው። እዚህ ደረጃ ሲደርስ “አገርን የማናጋት” ሴራው ተከናውኗል ማለት ነው።
እኛ ከአገራችን ወጥተን እዚህ ያለንበት ዋና ምክንያት የማናጋቱ ሂደት ሰለባዎች ስለሆንን ነው።
ይህ ሲጠናቀቅ ተጫዋቾች አሉ። ተጫዋቾቹ በማወቅም ባለማውቅም በማናጋቱ ሴራ ውስጥ የየራሳቸው መጥረቢያ ይዘው በማናጋቱ ሂደት የሚተውኑ ተዋናዮች አሉ።
እነማን ናቸው?
የሃይማኖት ድርጅቶች፤ ነጋዴዎች፤ ሚዲያዎች፤ የሴት/ የወጣት/የምሁራን፤ እና የፖቲካ ድርጅቶች ወዘተ ወዘተ…. ይጨምራል። አነዚህ ተዋናዮች የአገሪቱ ዜጎች ስለሆኑ፤ የያራሳቸው ዓላማ/ አጀንዳ ግብ ለማድረስ የሚጓዙበት መንገድ አቀበቱን በጥንቃቄ ካልተጓዙት እራሳቸውን በማናጋቱ ሂደት ጠልፈው የማናጋቱ ሴራ ተጫዋቾች የሚሆኑበት ጊዜ አለ።
ባጭሩ እንመልከት።
ሕዝቡ/ድርጅቶች/ አጥቂዎቹ በሚሰጡት የፖለቲካ ጫዋታ/ካርድ እየተጠቀመ እርስ በርሱ በጣላትነት እየተፈራረጀ ፤እየገዛው ያለን ሥርዓት “ትቶ” የየራሱን ባንዴራ እያሰራ በማውለብለብ “ኢትዮጵያን” ማአከላዊ የጋራ ጠላት በማድረግ የተሰጣቸው የማናጋት ሴራ የየራሳቸው መጥረቢያ ይዘው በመገዝገዝ ላይ ናቸው።
ዶ/ር ዮናስ ብሩ ያልተረዳው ነገር ይህ ነው።
በፋሺስቶቹ የተሰጣቸው “የኤትኒክ ፌደራሊዝም አስተዳዳር” አገርን የማናጋትና ሕዝቡን የማምበርከክ ሴራ ለማከናወን “ጎሳዎች” የጋራ ጠላት እንዲፈጥሩ ተደረጉና የተነገራቸው የጋራ ጠላት የተባሉት ደግሞ “ኢትዮጵያ፤ አማርኛ፤ አምሐራ እና ኦርቶዶክስ” የሚባሉ እስቶች (ተቋማት) ወይንም ማሕበረሰቦች በጠላትነት ተፈርጀው ከፍተኛ “ጥቃት” ተፈጽሞባቸዋል። ይህ ሴራ በጣሊያን እና ከዚያም በፊት የተሰነዘረ የጥቃት ዘመቻ ስለሆነ “ጥቃቱ” አሁን በወያኔና ኦሮሙማ አብይ አሕመድ ጊዜ ደንዳና መሰረት ጥሎ አገሪቱን በማናጋት ሂደት ላይ ይገኛል ማለት ነው።
የወስጥ ተዋናዮቹ ማዕከላዊ የቅስቀሳ መርሆዎቻቸው ዒላማ ኢትዮጵያ ስትሆን ፤ ‘የነፍጠኛ፤የጡት ቆራጭ አገር፤ ኋላ ቀር አገር፤የመቶ አመት አገር’ በማለት ኢትዮጵያን ‘በማዋረድ፣በማንኳሰስ’ የማናጋቱ ሂደት “ስሎው ፕሮሰሱ” (በዝግታ) እንዲከናወን እየተደረገ ነው። የብከላው ቅጥ ማጣት “አጥቂም ተጠቂም” አብረው ባንድ መድረክ ቁጭ ብለው ምንም እዳልተፈጸመ ሲተሻሹ ይታያሉ።....
ክፍል
3 ይቀጥላል
ጌታቸው ረዳ
Ethiopian Semay
No comments:
Post a Comment