Friday, May 29, 2026

የሰዎች ፍትሕ ሞከረቺው አልቀናትም ፥ ፈጣሪዋም ለመነች እሱም ዘገየባት ፥ ታዲያ ኢትዮጵያ ወደ ማን እጆችዋን ትዘርጋ? ጌታቸው ረዳ Ethiopian Semay 5/29/26


የሰዎች ፍትሕ ሞከረቺው አልቀናትም ፥ ፈጣሪዋም ለመነች እሱም ዘገየባት ፥ ታዲያ ኢትዮጵያ ወደ ማን እጆችዋን ትዘርጋ?

ጌታቸው ረዳ

Ethiopian Semay

5/29/26

መጀምሪያ ይህንን እንመልከት የዚህ ወር (May) Ethiopian Semay አንባቢዎች ቁጥር566,117ተዘግቧል

“እውነት እንደፀሐይ ናት፤ ፊት ለፊት በባዶ ዐይኖች አትታይም” ይላል ናማያራ የተባለ ህንዳዊ ደራሲ በአንዲት አጭር ልቦለድ ትረካው፡፡ በጣም እውነት ነው፡፡ የኔ ነው የምትለውን እውነት ይዘህ ግትር ካልክና የሚቃወምህ እንጂ የሚደግፍህ ካጣህ በርግጥም በቃላት ልትገልጸው የሚቸግርህ ህመም ጭንቅላትህን ሰንጎ ይይዝህና ትሰቃያለህ።” (አምባቸው ደጀኔ)።

በመቀጠል ወዳጄ  አምባቸው ያንን ሲያጠናክር አሁን ኢትዮጵያን ረግጦ እየተንፈላሰፈ እየገዛትና እየበዘበዛት ያለው ቡድን እና ማሕበርሰብ ማን እንደሆነም ይነግረናል፦

<....በአሁኑ ወቅት የሚሾሙ ሰዎችን ተመልከቱ፡፡ አብዛኞቹና ወሳኝ ቦታ ላይ የሚመደቡት ኦሮሞዎች ናቸው። በኦሮሞነታቸው ላይ ሃይማኖታቸው ፕሮቴስታንት ነው። ወይም -ሃይማኖታውያን (atheists) ጥቂቶች ደግሞ ሙስሊሞች ናቸው፡፡ ተሹዋሚዎች በዕድሜ ፌዴራላዊያን ናቸው - ማለትም በዕድሜ ያልገፉ ወጣቶችና ጎልማሦች ናቸው - በፌዘኛ ፌዴራሊዝም ዘመን ተኮትኩተው ያደጉ። ብዙዎቹ አቢይ የሚያውቃቸውና አብረውት በካድሬነት ወያኔን ያገለገሉ ናቸውግለ ታሪካቸው ደግሞ በሹመታቸው ላይ አንድም ተፅዕኖ የለውምሙልጭ ያሉ ሌቦች ወይም ገዳዮች መሆናቸው ከሹመት አያግዳቸውምብቻ የከይሲው ወዳጆችና ደንገጡሮች ይሁኑበዕድሜ በአማካይ 25 እስ 45 ግፋ ቢል እስከ 50 ይሆናሉ። ብዙዎቹ ሹመኞች ራስ ወዳድና ማኅደራቸው ፋወልየተሞላ አጭበርባሪዎች ናቸው - በሀሰት ዲግሪዎች የተምበሸበሹ ፥  ከርሳሞች ናቸው። የሚገርመው ደግሞ ሆዳምነቱንና ከሃዲነቱን በግልጽ ካላስመሰከረ በስተቀር ኦርቶዶክስና አማራ በምንም መንገድ አይሾምም። ባጨሩ በቅርብ የሚለይላት ገደል አፋፍ ላይ የምትገኘው የአቢይ ኢትዮጵያ ይህች ናት።» ይላል።

እኔ ድግሞ ይህንን ከላይ ያየነው እውነታ ‘የጸሐይ ጨረር ያልጋረደው ኮለል ብሎ ለመላ ኢትዮጵያ ሕዝብ በዓይን የሚታይ  የአፓርታይዳዊው መዋቅር እውነታ ነው’ እላለሁ። ይህ እውነታ ደግሞ የአብይ አሕመድ የኦሮሙማ ፖለቲካ ፈልሳፊ እና የአብይ አሕመድ የፖለቲካ መምሕር የሆነው ”የኦነግ መሪ እና የኦነግ ሸኔ መስራች አባል” ሌንጮ ለታ የሚከተለው እውነታ እንዲህ ሲል አረጋግጦልናል፡

 

ሌንጮ ለታ

ሰሞኑን መጽሐፍ ጽፎ ቃለ መጠይቅ ሲደረግለት እንዲህ ይላል።

«ዛሬ ለመጀመሪያ ጊዜ ሥልጣን የተቆጣጠረው ኦሮሞ ነው። ለመጀምሪያ ጊዜ ዲሞክራሲ የማይፈራ ነው ሥልጣን የተቆጣጠረው። ለምንድነው የማይፈራው? በሁለት ምክንያት ነው። 1ኛ ኦሮም ዲሞክራት ነው፤ ዲሞክራት ነኝ ብሎ ያምናል ኦሮሞ፡ 2ኛ በብዛት ከሁሉም ሕዝቦች የበለጠ ነው። እሰከዛሬ ኢትዮጵያን የገዙ ሃይሎች የመነጩት የዲሞክራሲ ባሕል ከሌላቸው ሕብረተሰቦች ነው የመጡት። ለመጀምሪያ ጊዜ ዲሞክራሲ ባሕሌ ነው ከሚል የመነጨ መሪ  (አብይ አሕምድን ነው መሪ እያለ ሚለው) ኢትዮጵያን አሁን  ሥልጣን ተቆጣጥሯል።»

 

ሌላኛው ሌንጮ ባቲ ደግሞ እንመልከት

ይህ ደግሞ በአሜሪካ ሚኔሶታ ውስጥ ሲኖር የነበረ ፤ የአሜሪካ  ዜግነት ያለው ፤ አብይ ሥልጣን ሲይዝ ወደ አዲሰ አበባ ገብቶ የአብይ ልዩ ከፍተኛ  አማካሪ ሆኖ የተሾመ፤ ከዚያም በአሜሪካ አምባሳደር ሆኖ ለሹመት ሲታጭ አሜሪካ አልቀበለም አለቺው ተበሎ የተወራለት በኋላ ግን በዋጩ ወደ ሳውዲ ዓረብያ አምባሳደር ሆኖ የተሾመ ሌላኛው እጀግ አከራሪ የሆነ የኦነግ አመራር ነው።

እንዲህ ይላል፤

« ኦሮሚያ የምትባል ሃገር ለማዋለድ ሥራ ላይ ነን። በወሊድ ጊዜ ደግሞ ደም መፍሰስ ግድ ነው። እኛ “ለሚፈሰው ደም ሳይሆን የምንጨነቀው ለሚወለደው ነው ትኩረት የምንሰጠው። ይህ መቼም የምናገኘው የመጨረሻ እድላችን ነው። ጊዜ ለመግዛት ግድያ ጭፍጨፋ ......... በየቀኑ .. አጀንዳ መፈጠር መስጠታችንን አጠናክረን መቀጠል አለብን። ከዚህ በላይ መጨከን አለብን። ደም ይፈሳል፤ ደም ሳይፈስ የተመሰረተ ሃገር የለም።በመላ ሃገሪቱ የቀድሞ የተወረሱ ርስቶችንን በግድም በውድም ወደ ታላቅዋ ኦሮሚያ እያስመለስን ነው። ሥልጣን ከሰሜኑ ፊውዳሎች እጅ ጠቅልለን ወደ ኦሮሚያ እጅ አስገብተናል። የሰሜኑን ፊውዳል ወገቡን ሰብረነዋል። ከዚህ በኋላም እድሜ ልኩን.........”»  በማለት ለኦሮሞዎች በኦሮምኛ የተናገረው ነው።

  ልብ ማለት ያለባችሁ “ለሚፈሰው ደም ሳይሆን የምንጨነቀው ለሚወለደው ነው ትኩረት የምንሰጠው" የሚለው ሐርግ ምን ማለት እንደሆነ እና የሚፈሰው ደም የማን እንደሆነ እና ያንን ኦሮሚያ የምትባል ምናባዊ ሃገር ለመመስረት የሚጨፈጨፈው ሕዝብ እና እያተፈናቀለ ያለው ሕዝብ በዋናነት ማን እንደሆነ ይገባችኋል።

አብይ አሕመድ

 እንዲህ ሲል እየገዛን ያለው ነገድ ማን እንደሆነ ነግሮናል

ኦሮሞ እሰኪነቃ ነው እንጂ ፤ እስኪነሳ ነው እንጂ ፤ ሲነሳ ሚዳቋ አትበላንም። እኛ ዝሆን ነንእንሰብራለንእንበላለንእንገዛለን፤።ንግግሩን በመቀጠል እንዲህ ይላል፤«ትናንት ያዋረደንን አዋርደን፤ ትናንት የሰበረንን ሰብረነዋል፤ ትናንት አትገቡም ፥ አትወጡም ብሎ አጥር ያጠረብንንንዛሬ መውጣት መግባት አይችልም ከኛ ፈቃድ ውጭ» (February 4/ 2020 ባሌ ኦሮሚያ ክልል በሚባለው “ወልወል ግድብ” ምረቃ እመርቃለሁ ብሎ ሄዶ የተናገረው)

እነዚህን 4 ቃላቶች ልብ በሉ አደገኛነታቸውን እዩ፡ «እኛ ዝሆን ነን!” ፥”እንሰብራለን!”፥“እንበላለን!”፥”እንገዛለን!

ስለ ታገቱ ተማሪዎች ሲጠይቅም፤ «የት እንዳሉ አላውቅም፤ የከተማ ከንቲባ ስላልሆንኩ። የለገጣፎ ተፈናቃዮች መፈናቀል አልሰማሁም። እኔ ጠ/ሚንስትር እንጂ የሰፈር ሚሊሺያ አይደለሁም። (ሰላልሆንኩ የሃገሪቱ ጸጥታ አይመለከተኝም እያለን ነው)፡ ሰለሆነም ጠ/ሚኒስትሩ ደግሞ የተሰጠውን ሃላፊነቱን በሚገባ እየተወጣ ነው (ሲል ራሱን ያሞካሻል)። ሰው ተገደለ አትበሉ፤ ግድያው መቸ እንደሚቆም አላውቅም እንጂ ገና ይቀጥላል። ሞትን አታዳምቁሞት ብርቅ አይደለም፤ አምሪካም እኮ ሰው ይገደላል።» እያለ የኦነግ ሸኔ ድብቅ ሥራው እያቀላጠፈ ነው።

አብይ የኦነግ ሸኔ መስራች አባል ነው። ኢትዮጵያን በተለይ አማራ እና ኦርቶዶክስን እየጨፈጨፈ ያለው ኦነግ ሸኔ የተባለው አሸባሪ ቡድን 26 ባንኮችን እንዲዘርፍ፤ ዘመናዊ የኮማንዶ ወታደራዊ መኪኖች እና ዘመናዊ መሳሪያዎች የሚረዳቸው የኦነግ ሸኔው አባል አብይ አሕመድ እንደሆነ የሚከተሉት አክራሪ የኦነግ ሸኔ እና የኦነግ አመራር አባሎች ይህንን ያረጋገጥሉናል፡

ኃይሉ ጎንፋ እና አፈንዲ ሙጠቂ እንዲህ ይላሉ፡

  «አብይ አሕመድ ኦነግ ሸኔ ነው» ሲመሰረትም አብረን ነው የመሰረትነው ሲል «አፈንዲ ሙጠቂ»

ኃይሉ ጎንፋ ደግሞ በቪዲዮ እንዲህ ይላል፤

  ዶ/ር አብይ አህመድ ኦነግ ሽኔ (አባኦ ABO) ነው! እኔም (ኃይሉ ጎንፋ) ኦነግ ሽኔ (አባኦ ABO) ነኝ! ለማ መገርሳም ኦነግ ሽኔ (አባኦ ABO) ነው! ሁላችንም ኦነግ ሽኔ (OLF ABO) ነን!! (ል; ኦሮሚያ  መመስረት አለብን ብሎ የሚጎተጉት አከራሪው የኦህዴድ ባለስልጣን ኃይሉ ጎንፋ)።

ይህ ቡድን ሩዋንዳ ውስጥ የቱትሲን ነገድ ለማጥፋት በ1981 ዓ.ም የተመሰረተው  MRND” (ልክ እንደ የኦሮሞዎቹ Prosperity/ ብልጽግና” የነበረ ገዢ የፖለቲካ ፓርቲ እና  በሩዋንዳ ጦር ሃይሎች (ኤ.ኤፍ.አር AFR) ለአሸባሪው “ኢንተርሃምዌ” (እንደ ኦነግ ሽኔ (አባኦ ABO)’ ወታደራዊ ስልጠና፣ ሽጉጥ እና ሜንጫ አስታጥቆ ቱትሲዎችን እንዳስፈጃቸው አብይ አሕመድም አማራን እና ኦርቶዶክስን ለማጥፋት “አባኦ” (ABO) ኦነግ ሸኔም ሥልጠና እና ወታደራዊ ዕርዳታ የሚያገኘው ከአብይ አሕምድ ፓርቲ እና መንግሥት መሆኑን ከመስራቾቹ አንደበት ምሥክር ሰምተናል (የሚክድ ሰው ካለ ቪድዮው አለኝ)።

ታስታውሱ እንደሆን ይህንን ጭፍጨፋ ለማጠናከር እንዲመቻቸው “ውጣልኝ!” የሚል የአብይ አሕመድ ኢንተርሃሙዌው የሙዚቃ ቡድን ያሰራጨው አዋጅ የዚሁ የአብይ አሕመድ ቡድን ተልዕኮ መሆኑን አንርሳ ። ይህ ሁሉ ክንዋኔ የሚነግረን አመላካች ቀስት “ሥልጣኑ በማን እጅ እንዳለ እና ይህ ሁሉ ሽብር ሲፈጸም ተሎ ያልቆመበት ምክንያት ሩዋንዳ ውስጥ ኢንትርሃሙዌው ቡድን ሽብር ሲፈጽም የMRND እና የሩዋንዳው (ኤፍአር AFR) ፓርቲ እና የሰራዊት ጥምረት ከኋላ እንደነበረው ሁሉ በኢትዮጵያ ውስጥም «በብልጽግና/ ኦፒዲኦ/ የኦሮሙማ ፓርቲ” እና »በኦሮሙማ አጀንዳ ትዕዛዝ የሚመራው የOromia Special Forces (OSF / ልዩ ሃይል)” ከኋላ ሰላለ ነው።

ይህ ኃይል በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ለኦነግ ሸኔ (አባኦ ABO) ሽፋን በመስጠት አማራዎች እና ከርሰትያን መዕመናኖች እና ቀስውስት ሲታረዱ ከመታረድ የሚሸሹትን አስቁሞ እንዲገደሉ በማድረግ አንሸሽም ብለው ታጥቀው ራሳቸውን ለመከላከል የሚደራጁትም ትጥቅ በማስፈታት እንዲገደሉ አድርጓል። ከዚህ ሌላ የራሱ ሚሊሽያ እና ልዩ ሃይሎች በጭፍጨፋው ላይ ተሳትፈዋል።

አብይ አሕመድ ያዘጋጃቸው ጨፍጫፊ ቡድኖች አማራን እና ክርስትያን አርደው ካንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ በመሄድ ጭፍጨፋ ለማካሄድ ትዕዛዝ ሲሰጣቸው “በOPDO እና በ(OSF / ልዩ ሃይል)”  “አይ-ሲዙ” እና ልዩ ፣ ልዩ ወታደራዊ መኪኖችን በማዘጋጀት “የሞት ድግስ ወደ ተደገሰባቸው ተረኛ መንደሮች” እንዲጓጓዙባቸው ድጋፍ ሰጣቸዋል። ይህ ደግሞ አማራሮቹ እና ልዩ ኃይሉ በዚህ ወንጀል እንደሚሳተፉ እና ተከላካይ ኃይል ጣልቃ እንዳይገባም የስልክ መገናኛዎችን በዝጋት ጥቃት እንዲደርስ ለአሽባሪዎቹ ትብብር ይደረጋላቸው እንደነበር «ጀነራል ከማል ገልቹ» ሲናገር ሰምተናል (ቪዲዮውም አለኝ)።

የአብይ አሕመድ የኦሮሙማ ፓወር ያዘጋጀው “አባኦ ABO”  እና የጃዋር Ethiopia out of Oromia  የ“ቄሮ” ቡድን እና የሩዋንዳው “ሁቱ ፓወር” በአስተሳሰብ እና በተግባር አንድ ናቸው በሚገርም ሁኔታ ይህ ሁሉ ጭፍጨፋ ሲደረግ “አብይ አሕመድ” ትንፍሽ አይለም። ካለም “ለሞቱት ጥላ እንዲሆናቸው የባሕርዛፍ ችግኝ እንተክላቸዋለን” እያለ ያሾፋል። ሰለዚህ የኦሮሙማው “አብይ አሕመድ” እና የሁቱ ሩዋንዳው መሪ “ሃቢአብሪማና” ወንጀሎች ተመሳሳይ ናቸው።

የአማራ ሕዝብ ከየክፍለሃገራቸው ለሥራ ወደ መዲናዋ በአብቶብስም ይሁን በጭነት ሲመጡ መዲናዋ የኦሮሞ መናሃሪያ ለማድረግ እንዲመቻቸው እና ዳግም ሰው ወደ መዲናዋ እንዳይመጣ መኪኖችን መንገድ ላይ እያስቆሙ ተሳፍሪዎችን በማገትና ከፍተኛ ማስለቀቂያ ገንዘብ በመጠየቅ ወይንም በከፋ መልኩ በተሳፋሪው ላይ የእሩምታ ቶክስ በመክፈት ሕዝብ ሲጨፈጭፉ አጥጋቢ እርምጃ  አይወስድም።

የዛሬዎቹ ተተኪዎቹ ተረኞቹ “ኦሮሞዎች” በዚህ 8 አመት ብቻ (ሌላውን የ27 አመት የታየው ወደ ኋላ ትተን ማለት ነው) ሰማዩም ምድሩም ያወቀው ስለሆነ ዝርዝር አልገባበትም።  በአብይ አሕመድ ኦሮሙማ ፕላን 1፣ ፕላን 2፣ ፕላን 3 …እየተባለ እየተሰራ ያለው አማራ ላይ ያነጣጠረ ከወያኔዎች የቀጠለ የኢንተርሃሙዌው “ፕላን”  ቀስ እያለ ሲሰራ ቆይቶ እነ ሌንጮ እነ ዶ/ር ዲማ ነገዎ እና አሰፋ ጃለታ የመሳሰሉ የኦሮሙማ አጀንዳ አቀንቃኞች እንደተናገሩት ፥ እንዳቀዱትም ፥ እንደዛቱትም፤ በአብይ አሕመድ በኩል ተግባሪ በማድረግ አማራዎች ወደ አዲስ አባባ እንዳይገቡ፤ የገቡም ቀስ በቀስ ከተከበቡ በኋላ እየተለቀሙ እስር ቤትና በየት/ቤት ማጎርያ ህንጻዎች እንዲታጎሩ መደረጉን ታስታውሱ ይሆናል።

ይህንንም ዕቅድ የቆየ በጥናት ሲጠናበት የነበረ ኦሮሙማዊ አጀንዳ ነው ይህን የዲማ ነገዎ አጅንዳ እና ንግግር በዶ/ር አሰፋ ነጋሽ በEthiopian Semay የተለጠፈው ጽሑፍ እናስታውስ። በዚህ 8 አመት አማራ ምሁራን እና ወጣቶች በየምክንያቱ ሰብስቦም ይሁን አን ባንድ እየለቀሙ ማጎር ፥ ቀደም ብለው ያቀዱት የኦሮሞ ፖሊተከኞች ንድፍ ነው።

አዲስ አበባና አካባቢው ውስጥ የሚኖሩ አማራዎች (‘ነፍጠኞች’) እየለቀምን ከሰበሰብናቸው በኋላ የመውጫ ኮሪደር (በር) ከፍተን ወደ አገራቸው “እንዲወጡ” እናደርጋለን ብለው በተለያዩ ሰነዶቻቸውና ንግግሮቻቸው ባስቀመጡት መሰረት  መጨረሻ አዲስ አባባ እንዳይገቡና የገቡትም እየተለቀሙ ተሰብስበው እንዲወጡና “ኦሮሚያ” የተባለ አገር ለመመስረት  እንዲያመቻቸው <<ወኪላቸው አብይ አሕመድ>> ይህንን በአዋጅ ተግባራዊ እያደረገው ይገኛል።

ይህንን ንግግር ያደረገውም አብይ ወደ ሥልጣን ሲምጣ ከኔዘርላንድ (አወሮጳ) ወደ አገር በመግባት አሁን በአብይ አሕመድ ፓርላማ አባል የሆነው <ዶ/ር ዲማ ነገዎ> የተባለ እጅግ አደገኛ የኦሮሙማ ቄሮ የኢንተርሃሙዌ ቡድኖች ቀስቃሽና የኦነግ መሪ ነው።

ከ3 አመት በፊት ከላይ የጠቀስኩት “ውጣልኝ!” የሚል የአብይ አሕመድ ኢንተርሃሙዌው የሙዚቃ ቡድን ቅስቀሳ  እያታጀበ በየገጠሩ በአማራ ሕዝብ ላይ የዘር ጭፍጨፋና ሲፈጸም፡ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ደግሞ “ኦነግ ሸኔው ፖሊስአንገቱ ላይ የክርስትና ሃይማኖት ምልክት ያለው ኢትዮጵያዊ እና የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ የያዘና የለበሰ ሰው አስቁመው እየነጠቁና እየደበደቡ እስርቤት በማስገባት ለቁጥር የሚያዳግት በሺዎቹ የተማረውና ያልተማረው አምሐራዊው ክፍልም ተሰብስቦ እስር ቤት ታጉሮ እየተሰቃየ የምናይበት ምክንያት አብይ አሕምድ  የተከናነበ ልዩ አጀንዳ ሰላለው ነው

የኦሮሞ 1ኛ ደረጃ ተማሪዎች መዝሙር

ይህ ሁሉ አጀንዳ እና ጭካኔ ካደረጉ በኋላ መጪዋን ኦሮሚያ ለመገንባትና ሕጻናቶቻቸውም በጥላቻ አድገው አደገኛ ቂመኞች እንዲሆኑ “መገዳደል እንዲቀጥል” ለትምሕርት ቤት ሕጻናት የህንን የጥላቻ እና የውሸት መዝሙር አዘጋጅተው የኦሮሚያ (አነግ) ባንዴራ ሲሰቅሉና ሲያወርዱ በ1ኛ ደረጃ ት/ቤቶች የሚከተለው መዝሙር እንዲዘምሩ ተደርጓል። (ማስታወሻ ነፈጠኛ ማለት የምስጢር ስሙ (ኮድ) አማራ ማለት ነው፡

«ነፍጠኛ የሰራውን ማሰብ ያንገበግባል

ታሪክ ኖሮን እንደሌለን፥

እናት ኖሮን እንደሌለን

እንደ በግ ግልገል በየመንደሩ ታርደን ያንን ያንን ያሰብን ዕለት ምሽግ ያዝን

ሌላ ማሰብ አንፈለግም ከኦሮሚያ በቀር» ይላል።

“ኦሮሙማዊው ኢንትርሃሙዌው አጀንዳ” ተግባራዊ ለማድረግም አዲስ አበባ ብቻ ሳይሆን የአማራ ከተሞችና ገጠሮች የጦር ቀጣና ሆነው  አማራዎች ሲፈጸምባቸው የነበረው የ27 አመት ጭፍጨፋ አበቃለት ስንል “እንደገና ነብስ ዘርቶ” በከፋ መልኩ በመቀጠሉ የአማራ ወጣቶች የሞት ሽረት የጦርነት ፍልሚያ በማድረግ ላይ ናቸው። እነሱም ሕዝቡን ነፃ ያወጡታል ተብሎ ተስፋ ሲጣልባቸው የሚከተለው ተስፋ አስቆራጭ የጫካ ባሕሪያቸው እንድናይ አደረጉን

ፋኖ

ፋኖን ስናነሳ በማን እንጀምር? የጎጃም አፈቀላጤ በመሆን ሲሰራ በነበረው በማርሸት ፀሐዩ እንጀምር። ማርሸት ፀሐዩ ሰሞኑን  ጎጃም ውስጥ ዝናቡ በተባለ የፋኖ የጎበዝ አለቃ ትዕዛዝ “ወፌ ላላ” ታስሮ እንደተገረፈ ያለፈው ሁለት ሰሞን የሕዝቡ መነጋያ ሆኖ የሰነበተ ሰው ነው።

ማርሸት ጸሐዩ

   ባለፉት የሽምቅ ተዋጊ ድርጀቶች ታሪክ ስንመለከት አድማጭ ታዘበኛል” የማይሉ ሲዋሹ እጅግ እስከ-ጥግ ድረስ የሚቀደዱ፤ የተቃዋሚያቸውን ስም ለማፋት ሲፈልጉ  ራሳቸውን ለትዝብት የሚጥሉ፤ ዓለም የዘገቡዋቸውን የሃገራችን ታሪኮችን የሚያጠለሹ “የወያነ ፤ የኦነግ/አብይ-ኦሮሙማ እና የሻዕቢያ መሪዎች” የውሸት ባሕሪዎች ምን እንደሚመስሉ ለብዙ አመት ታዝበናቸዋል። ዛሬ ደግሞ በጎበዝ አለቆች የሚመራ “ፋኖ” ብሎ ራሱን በውሸት የሚኮፈስ ሲዋሽም ዳርቻ የማያውቅ፥ያለፉት “የዋሾ ድርጅቶች ባሕሪ” የተላበሰው ባንድ ወቅት የጎጃሙ የፍሺስት ዱርየ ታጣቂዎች መሪ የሆነው የዘመነ ካሴ “አፈቀላጤ” የነበረው ሰው ነው።

ይህ ሰው አማራ አማን እንዲገድል (ጫካ የወጡትን ማለት ነው) በማወጅ የመገዳደል ጦርነት ሲናገር እንደነበር ታስታውሳላችሁ ብየ እገምታለሁ።

ይህ «ትንሽ ሰው» የመግደል አዋጅ ብቻ ሳይሆን ሲዋሽም ዳርቻ አልነበረውም።ሽዋ ውስጥ ሲንቀሳቀሱ የነበሩት  እስክንድርና ጓዶቹ የሚመሩት “የአምሐራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት” ፤ “ስላዳከምነው የትጥቅ ዕርዳታ የሚያገኘውም ከአብይ አሕመድ ነው” ሲል “አድማጭና ታሪክ” ይታዘበኛል ሳይል ሃሰትን ለመቃወም ጫካ ገብቶ ሃሰትን መመሪያው ያድረገ ማርሸት ፀሐዩን ታስታውሳላች

 እንቀጥል፦

አስረስ ማረ

 እና የድረጀቱ ምክትል የነበረው አሁን ቃል አቀባይ እና የፕሮፓጋንዳ/ የሕዝብ ግንኙነት ሆኖ የተሾመው አስረስ ማረ የተባለ ደም የጠማው ነብሰ ገዳይ እንመልከት።

ይህ ሰው አብረውት የአማራ ሕዝብ ነጻ ለማውጣት የወጡትን «የእነ እስክንድር ነጋ ድርጅት እና አመራርሮቹን የጠላት ድርጅት አድርጎ በመሳል፤ ለአምሐራ የቆምን ብቸኛ የሽምቅ ታጣቂዎች እኛ ጎጃሞቹ የመሰረትነው ፋኖ ብቻ ነው፡ስለሆነም “የተቀረ ፋኖ ነኝ የሚል ታጣቂ መደምሰስ አለበት፤ ጀምረናቸዋል፤ ጦርነት ገጥመናል፤ አዳከመነዋል፤ እናጠፋቸዋለን!” ሲል በፋሺት የብሔረተኛ ድንፍታ ሲጎረን ስመተን አፋችንን በአግራሞት አስያዘን። በዚህም ታዋቂ ታጣቂዎች ተገድለዋል፤ ተዋክበዋል (ወያን እና ሻዕቢያ በየት ዞሮው መጡም አስኘን)።

ዘመነ ካሴ

የጎጃም ፋኖ መሪ ነኝ የሚል ዘመነ ካሴ አሁንም በድጋሚ የአምሐራን ሕልውና እጠብቃለሁ ብሎ “በሚያስቅ ጉጉት” ራሱን ለማንገሥ ሲል «እኔ አጥናፉ አባተ አይደለሁም“እኔ የፋኖ ንጉሥ ነኝ ሳልወለድ ትንቢት የተነገረልኝከዘር የተላለፍልኝ አንጋሽና ነጋሽ ነኝ” እያለ ምሁራን ጀሌዎቹን የሚያስፈነድቅ ዘመነ ካሴ ፣ እስክንድርን ካላጠፋሁ “በሚል በማሃይምነትና ደም በጠማው አስተሳሰብ እየተመራ «የፖሊስና የሌባ» «ራሱን አዳኝ (አጥማጅ)” “እስክንድር ታዳኝ” አድርጎ በመሳል ጦርነት እንደገጠመ ሲናገር የነብረውን በሪኮርድ የያዝነውን ታሪኩን ታስታውሳላችሁ።

እንደምናውቀው ይህ ሰው መምሕራንና ተማሪዎች ሲያዋከብ፤ ሲጠልፍ፤ ሲያግት ፤ ሲያስር ፤ ሲረሽንና የፋኖ ታጣቂዎችን እኔ ካልመራሁ ብሎ (እያፈነ ሲያሰገድልና አስገድዶ ሲያታግል የጎጃሙ ኮ/ል ጌታሁንና በሥሩ የነበሩ በመቶዎች የሚቆጠሩ ታጣቂዎች ለምን ከእስክንድር ጋር ወገናችሁ በሚል ወደ ዘመነ ታጣቂ ታፍነው በአስረስ ማረ “ቃለ መሃላ” አስፈጻሚነት በግድ ከማሉ በኋላ ምን እንደደረሰባቸው እና የተቀሩትም እንዴት ወደ ዘመነ እንደተቀላቀሉ ታሰታውሳላችሁ ብየ እገምታለሁ።

በነዚህ ብቻ ሳይገደብ የጋዜጠኞች የዶክተሮች የመምሕራኖችና የተማሪዎች አፈና ግድያ እና እገታ በዚህ ሰው አመራር ስር ያስገረመን ክስተት ነበር። እውነተኛ አምሐራዎች መጠየቅ ያለባችሁ «በዚህ ቀውስ ውስጥ እንዴት ልንገኝ ቻልን?» ማለት አለባችሁ።

ብዙ አምሐራ ወጣቶች ፥ ምሑራን ደጋፊዎቻቸው ጭምር በብሔረተኛነት ስካር ሰክረው እያየናቸው ነው። አንዳንድ ምሑራኖቻቸው ወደ ፋኖ የሚቀላቀል ሰው 7 ትውልድ የአማራነቱን  የደም ጥራት መረጋገጥ እንዳለበት ጠይቀዋል። እነኚህ ሰዎች ፋሺዝምና የብሔርተኛነት እንቀሰቃስዎች ባሕሪ  ክፋቱ ምን እንደሚመስል ከወያኔ እና ከኦሮሞዎች የብሔርተኛነት ሰበብና ጠባሳ ትምሕርት ያስተዋሉት አይመስሉም።

በፋሺስታዊ እንቅስቃሴዎች መካከል የተለመዱ ጭብጦች የሚያጠቃልሉትን እንመልከት፡-

“ፈላጭ ቆራጭነት፣ ብሔርተኝነት (የዘር ብሔርተኝነት እና ሃይማኖታዊ ብሔርተኝነትን ጨምሮ) ፤ ወታደራዊ ድንፋታነትን ፤ የአካባቢ አጉራዘለል አለቃነት ስሜትና አልገዛም አልገብርም የሚለውንም ማንበረከክ ፤ የደም ጥራት (blood purity) የፋሺዝም ባሕሪያቶች ያጠቃለሉ ናቸው። ጎጃም ውስጥ አቆጥቁጦ እያየነው ያለውንም ይህንኑ ባሕሪ ነው። የዚህ ድርጅት ደጋፊ ምሑራኖች ይህንን ጭራሽ እንደማይታያቸው ይክዳሉ/ጥቂቶችም የዚህ አይነት ቅስቀሳ ተሳታፊዎች ናቸው

ለምን እንደሚክዱ ካሁን በፊት ምሑራን በዶግማቲክ (ችክተኛ ኢጎ) ራሳቸውን አንዴ  ከተበተቡ ከገቡበት ስሕተት ተሎ ላለመውጣት የሚመርጡት ማምለጫ መንገድ “ከሕደት” ወይንም በ“ዲናያል” ጉዞ እንዴት እንደሚቀጥሉ ካሁን በፊት ገልጫለሁ።ሰለዚህም አምሐራ ምሑራንና ወጣቶች በዚህ ቀውስ ውስጥ እንዴት ልንገኝ ቻልን? ብለው ቢጠይቁና ቢመራመሩ ችግሩ ሊታያቸው ይችል ይሆናል እላለሁ።

እነሱ ብቻ ሳይሆኑ በዚህ ጥያቄ ውስጥ እንዴት ልንገኝ ቻልን? የሁላችን ጠያ መሆን ያለበት የመወያያ ርዕስ መሆን ያለበት ነው። ለጥያቄው መልስ ስጡ ብትባሉ ብዙዎቻችሁ የምትሰጡት የለመዳቸሁት መልስ ገና አዲስ ድርጅት እና አመራር ስለሆኑ ነው፡  ቢሆንም ከስሕተታቸው እየተማረ ይሻሻላሉ...” ፡ ትልላችሁ።

መምሀራን እና እግራቸው ያልጠና ልጃገረዶች በማን አህለኝነት ቢረሸኑ ፥ አያቶቻቸው የሚያክሉ አረጋዊያን ቢያንበረክኩ ፤ ቢገርፉም ፥ ይህ ድርጅት “ለመመስረት” ከባድ ዋጋ የከፈሉ ስለሆኑ ግድያና ግርፋት መፈጸማቸው እንደ ከባድ ወንጀል አናካብደው.......”የሚሉ ደጋፊዎቻቸው እንዳሉ አድምጣችኋል።

በአዳዲስ እና በነባር ታጣቂ ድርጅቶች የሚታየው የወንጀል ድርጊት ቀጣይነት  የሕዝብ አያያዝና የአስተዳደር ልምድ ስላነሳቸው ሳይሆን ፤የምንከተላቸው መሪዎችና ድርጅቶች/ወይንም መንግስት እና ሚዲያ፤ “ስለሚዋሹንና ያለፉት ድርጀቶች እና የመንግሥት መሪዎች የፈጸሙዋቸው ወንጀሎች የክስ ተጠያቂነት ስላልተደረገባቸውና ሕዝቡም እኔን ስላልነኩኝ ምን አገባኝ እያለ በቸልተኝነት ሰልሚያልፈው ነው

የፋኖ መሪዎች እየተከተሉት ያለው ማን የጠይቀኛል የወንጀል እና የአጉራ ዘለል ባሕሪ ከላይ ያየነው ድግምግሞች (አዙሪት) ስለሆነ አዲስ መንፈስ ለፈለግ ከባድ እየሆነ ነው።

መሪዎች (ጫካም ይኑሩ ከተማ) እንደ ዛው በዚህ 50 አመት ውስጥ ያሳዩት የውሸት ባሕሪ በታሪካችን አላየንም። ሕዝቡን እየዋሹ አስከፊ ዘመን አምጥተውለት እነሆ ‘ሲሰደድ፤ሲዋረድ፤ ሲንገላታ’ እንደዛሬ ስቃይ ደርሶበት አያውቅም። 

ለዚህ ሁሉ መከራና መበጣበጥ “መሪዎች” ገለው ሳይቀጡ፤ እንደገና ሥልጣን ሲሰጣቸው ፤ ሲዋሹ ድጋፍና ጭብጨባ ሲቸራቸው ፡ አምባገነኖችን እየካብን በአገራችን ውስጥ ቁቡል ሆኖ መታየቱ በማንወጣበት እሽክርክሪት ላይ ነን

ከዚህ ዘልቀን መሰረታዊ መነሾውን መመርምር ያስፈልጋል። የሚጎመዝዙ ዋሾ መሪዎችና ነብሰ ገዳዮችና ወረበላ ታጣቂና መሪዎች በፋኖ ድርጅቶች ውስጥ በገፍ ተፈልፍለዋል። አሰገራሚ ያደረገው ደግሞ “የፋኖ መሪዎች በዋሹ ቁጥር፤ ምሑሩም ሕብረተሱም አብሮ ይዋሻል፡ ወይንም ሲዋሹ ይታገሳቸዋል፤ ወይንም ያምናቸዋል። ውሸት ሕብረተሰብን የሚገድል እና የሚያጋድል፤የሚያሳስት መሰረታዊ የሆነ ማሕበራዊ ነቀርሳ እንደመሆኑ መጠን ፤ ‘ዋሾ’ መሪዎች በዋሹ ቁጥር ሕብረተሰቡም አብሮ እየዋሸ ወይንም ‘እየታገሳቸው’ በሄደ ቁጥር የሚፈለገው ሰላማዊ የሆነ ፍትሕ የነገሰበትና ‘ተጠያቂነትን’ የሚያከብር ስርዓት እንዳይመጣ እንቅፋት ይሆናሉ። አሁን እየሰማነው ያለውና እያየን ያለው የፋኖ ክስተት ይህንኑ ነው።

 ውሸትና ዋሾ መሪዎች” የመቀበል ባሕል እያጎለበትን በመምጣታችን ለቀውሳችን ተጠያቂዎች መሪዎቹ ሳይሆኑ እኛ የመሆናችን ጉዳይ አስገራሚ ያደርገዋል። ይህ “እገሌን ካላ

ጠፋሁ አላርፍምና ፤ ጥላሸት የመቀባት (የመዋሸት) ባሕሪና «ወንጀል ሠርቶ› ሳይጠየቁበት ተንደላቅቆ ያለሰቀቀን በነፃነት እንዲኖሩ አብረን ስንጨፍር፥ውለን አድረን ሠለጠንን ባልንበት ዘመን ወደ አራዊት ባሕሪ ተለውጠን ፤ ይህ አምሐራን አምሐራን በመግደልና በመደብደብ ያየነው የወንጀል ክስተት እነሱ ሲያብዱ ባልታሰበ ድንገተኛ እምርታ እኛም እነሱ ጋር እየዋሸን እና እያበድን ቀስ በቀስ “ዕብድ ሕብረተሰብ” ወደ መሆን እየተሸጋገርን ነው፡ ይህንን እንመን። የፋኖ ታጋዮች፤ የሰው እጅ ቆርጠው አሳይተውናል፤ ኢትዮጰያዊ የአምሐራ ባሕሪያቸውን ጥለው ወደ አረመኔያዊ ባሕሪ ገብተዋል።ፋኖ ውስጥ አባትዋን የገደለች የፋኖ ወጣት ታጋይ በከፍተኛ ሙገሳ ስትሞገስ እንደንበር የቀድሞ የፋኖ አባሎች ይህንን ሲናገሩ ሰምቻለሁይህንን ጭካኔ ማጣጣል ቀጣይ ያደርገዋል።

ፋሺስታዊና አክራሪ የብሔረተኛነት በሸታ «ፋኖ ውስጥ ገብቶ» ይፋ ሆኖ እየኮሩበት ነው። መሁራኖቻቸው ይህንን ሲነግራቸው “ፋኖ ሳይሆኑ ፋኖ እና አማራ መስለው የሚቀርቡ ወያኔዎች እና ኦነጎ ናቸው”” እያሉ ከውነታው ርቀው ሲናገሩ ሰምቻለሁ። የብሔርተኛ ፖለቲካ መጨረሻው ስብእናን ነጥቆ የራሱ ያልሆነውን ነገድ በቻ ሳይሆን አሁን እያየነው እንዳለው የጎጃም ፋኖ “ጀምረናቸዋል እንጨርሳቸዋለን” አምሓራን ለመጨፍጨፍ ዛቻ መጨረሻ የራሱንም ወገን እንደሚበላ ሰሞኑ ራሳችወ ሰው «በማርሸት ፀሐዩ» የደረሰው እያያችሁት ነው።

ማጠቃለያ

ተስፋ አድርገንበት የነበረው የከሸፈው የፋኖ ታጣቂ ቡድንም ይሁን አሁን ሥርዓት የሚመራው ኢትዮጵያ ወስጥ ሕዝብን አሞኝቶ ወደ ሥልጣን በመግባት ለ27 አምት የቆየው አፓርታይዳዊ ሥርዓት እንዲቀጥል ከውጭ ሃይሎች ጋር እየተመሳጠረ በትጋት እየሰራበት ያለው ኦሮሙማው የኦንግ  ሽኔ (አባኦ ABO) መንግሥት

ሁለቱም “በውሸትና ወገንተኛነት” እየተመሩ ነፃነት እንዳትገኝ እሩቅ አድርገዋታል

ሕዝቡ

ሃይማኖቱችም” “የዜና አውታሮችም” በውሸት የሰከሩ ሆነዋል።  ዜጎችም ለ35 አመት ራሳቸው እንዳያውቁ በተለያዩ የማሰርያ ስንሰለቶች ተተብትቦ “ዞምቢ” (Zombie/Zombee) ሆኖ በግዝገዛው አጅንዳ ላይ ተሳታፊ ሆኖ ራሱን እየበላ ሞቱን የሚያቀላጥፍ በሴረኞች ወጥመድ እየደነሰ እንደ “ዞምቢዋ ንብ” («ናላዋ እንደዞረባት ንብ”) ራሱን ስቷል።

የፈረንጁ ቃል “ዞምቢ” ማለት “ናላዋ የዞረባት ንብ ማለት ነው”። ንብዋ አፖሴፋለስ ቦሪያሊስ (Apo Cephalus borealis) በተባለ ባከትሪያ/ህዋስ/ የተበከለች ዝምብ (ፎሪድ ዝንብ) ንብዋን ስትነድፍ ፤ በጥገኛው “ፓራሳይት” ዝምብ”  የተበከለች “የማር ንብ” ሆድ እቃዋ ውስጥ ይራባ እና እንቁላል ይጥላል። እንቁላሎቹ ከተፈለፈሉ በኋላ “እጮቹ” የንብዋን የውስጥ አካላት ይበላሉ። የተበከለቺው ንብ ከመሞቷ ጥቂት ቀደም ብሎ ናላዋ ስለሚዞር ሌሊት ላይ ቀፎውን ትታ ወደ ውጭ ትበራለች። በስሕትተ መብራት ወዳለበት በመብረር “በመብራቱ ዙርያ” ሽክርክሪት እየዞረች የሞትዋን ሰዓት ተጠባበቃለች። ለዚህ ነው የደነዘዘ ማሕበረሰብ ስናይ “ዞምቢ” ብለን የምንጠራው።

ውሸት አየር ነገር አይደለችም ፡ በማሕበረሰቡ ሕሊና ውስጥ የምትኖር ፥ ጠበቃዎችና ተከላካዮች ያሏት የሰዎች ባሕሪ ነች። ማሕበረስቡ በውሸት ዓለም እየዋዠቀ ነው፡ ማሕበረስቡ ወደ ዞምቢነት ተለውጦ ተነስ ብትለው አልነሳ አለ ፥ ማሕበረሰቡ ናላው ዞሮ ወደ ዞምቢነት ከተለወጠ ማን ይታደገው?  ሰላማዊ ሰልፉም ቢሆን ዞምቢው የአዲሰ አበባ ኗሪ የሚያነሳሳና የሚቀሰቅስ  እሰክንደር ነጋን የሚተካ ደፋር እምቢተኛ መሪ እና አዘጋጅ አጣታጣቂውም ገዳይ ሆነ ፥ መንግሥትም አፓርታይዳዊ ጨፍጫፊ ሆነ ፥ ወደ ፈጥሪዋም ለመነች እሱም ዘገየባት፥ታዲያ ከዞምቢነት ለመውጣት ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ ማን ትዘርጋ?

ጌታቸው ረዳ

Ethiopian Semay

 

Friday, May 22, 2026

አበቤች አደኔ አብይና ዝናሽ ሆይ እንደ ዛጉዌው መስራች እንደ ንጉሥ መራ እልፎችን እቤታችሁ ለማኖርና ለመቀለብ ፈቃደኞች ናችሁ? ጌታቸው ረዳ Ethiopian Semay 5/22/26

 

አበቤች አደኔ አብይና ዝናሽ ሆይ እንደ ዛጉዌው መስራች እንደ ንጉሥ መራ እልፎችን እቤታችሁ ለማኖርና ለመቀለብ  ፈቃደኞች ናችሁ?

ጌታቸው ረዳ

Ethiopian Semay

5/22/26

ዛሬ የምንመለክተው ጉዳይ “መጽዋች እና ተመጽዋች” በሕግ አውጥቶ ድሆችን እንደ ቆሻሻ እያየ ከጎዳና እየለቀመ እስር የሚያስገባ (social cleansing) አብይ አሕመድ እና የሱ ታማኝ የሆነቺው በሰው ሰራሽ ውበት የምትዋብ እና የሞዴል  ልዕቶች የማይለብሱዋሸው በውድ ልብሶችና ሽቶዎች የምትሽቀረቀረው የአዲስ አበባ ውቢትዋ አበቤች አደኔ ለድሃ ማሕበረሰብ ያላቸው ጥላቻን እንመለከታለን።

ምንም እንኳ አብይ አሕመድ ለመለመን ይተፈቀደለት ፥ ለማኝ እና ልመናም እንደሚሳካለት የልመና ባለሞያ መሆኑን ሳይሸማቀቅ ቢነግረንም ፤ በሚገርም ነገር ‘ልመና ለአብይ ሲፈቀድ  “አዱንያ አልሆን ብላቻቸው” የዕለት ጉርሻ አጥተው ለሚለምኑ እና ለሚመጸውቱ መጽዋቾች ግን አብረው እንደሚቀጡ አዲስ አዋጅ ተግባር ላይ እየዋለ እንደሆነ በዚህ በተለጠፈው የቪዲዮ እና የድምጽ ማስረጃ ማረጋገጥ ይቻላል ።

 ሳምንቱን አበቤች አደኔ በድሆች ሕይወት ስታሾፍ ሰምተናታል። በዚህ ቪዲዮም ታደምጠዋታላችሁ። በዚህ Ethio forum ዘገባ የሥርዓቱ ጨኻኝነተ እና ንቅዘት ባስገራሚ ማስረጃ ዘግቦ አሳይቶናል (ምስጋና ይግባው!) 

 የሃገራችን ሕዝብ እስላምም ክርስትያንም ይሁን ታዋቂ ሃይማኖቶችን የማይከተል በየዋህ ባሕሪ በመነሳሳት ይሁን የሃይማኖቱን ሕግጋቶች ተከተለው ለታረዙ ድሆች “ልብስ” ለተራቡ “ምግብ” የሚመጸውቱ መጽዋቾች እና ተመጽዋቾች ፣ (የኦነጉ መሪ ሌንጮ ለታ «የኦሮሞዎች መንግሥት) እያለ የሚጠራው «አብይ አሕመድ የሚመራው የኦሮሞዎች መንግሥት» በሕግ ይቀጣል። መጽዋቾች እና ተመጽዋቾችን ለመቅጣት ሰላዮችን መድቦ እየተከታተለ ፤ ከገንዘብ ቅጣት ጀምሮ ንግድ ቤቶችን እሰከማሸግ/ እሰከመዝጋት/ የሚደርስ ሕግ አጽድቆ እየቀጣቸው ይገኛል።

ይህም የነገረችን ለሥርዓቱ ከሚሸቅሉ ሎሌዎች አንድዋ ከላይ ከነ አበቤች አደኔ ፎቶ ጋር የምታይዋት «አለምፀሃይ ጳውሎስ” የተባለች “barbaric” የአዋጁ ምሕረት-የለሽነትና ጭካኔ  ታሪክ ይታዘበኛል ሳትል ፣ሳትሸማቀቅ “ጀርመኖች በ1933 ለድሆች እና ለቤት-አልባዎች ሲያደርጉት የነበረው ዓይነት እስራት፤ቅጣትና ንቀት በኩራት ነግራናለች።

የኦሮሙማው ቡድን  ወደ ሥልጣን ከመጣበት የመጀመሪያዋ ቀን ጀምሮ ውሸት እና መቀደድ የማንነቱ መገለጫ ባሕሪ እንደነበር በሂደት አይተናል። ልምድ አደረጉትና ቅጥ ያጡ ዋሾች እና ከራባት ያጠለቁ ጤናማ የሚመስሉ የአእመሮ በሽተኞችን ከየቦታው ለቃቅሞ እየሾመ ሲዋሹለት ምቾት ሰጣቸዋል። እንዲህ ያሉ ሰዎች የስነ ልቦና ሊቃውንት Mythomania ይሏቸዋል።

ዛሬ የምንመለከተው የአብይ አሕመድ የወንጀል ተጋሪዋ  አበቤች አደኔን ነው።የሕከምና ባለሞያ ዶክተሮች በኑሮ ውድነት በደሞዝ ማነስ የተመጣጠነ ምግብ ቀርቶ በቀን አንድ ቀን ብቻ እየበላን በርሃብ ተሰቃይተናል እያሉ ሲጮሁ አበቤች አደኔ ደግሞ ድሆችን ወደ መመገቢያ ማእክላት ሂዳችሁ “እጃችሁን ታጥባችሁ” የተመጣጠነ ምግብ ተመገቡ እያለች የምትቀልደውን ቀልድዋን አይተን ፣ አብይን ዳብሰን ከዚያም ወደ 12ኛው ክ/ዘመን ንጉሥ እና የድሆች አያያዝን እንመለከታለን።

አበቤች አደኔ ለድሆች ያላት ግሃዳዊ ጥላቻ ከማሳይተዋ በፊት ጥላቻና ውሸት የጀመራት ገና ሥልጣን ላይ ከመውጣትዋ በፊት ቢሆንም ሥልጣን ስትይዝ ግን ድብቅ ጥላቻዋ በግሃድ የወጣው የግምሩክ ሐላፊ ሆና ስትሾም የአማራ ነገድ ሰራተኞች እያባረረች በምትኩ ኦሮሞዎችን ስትቀጥር ከዚያም ጥላቻዋ ወደ ትግሬዎች ዞሮ “ትግርኛ ተናጋሪዎች እንዲጨፈጨፉና እንዲለቀሙ (ቱ ቢ ሃንትድ) ሆን ብላ በማቀድ ‘’ሓጫሉን የገደሉት ትግርኛ ተናጋሪዎች ናቸው” ማለትዋ ሳይበቃ ‘’ ፥ (ፍንፍኔ ውስጥ) ትግሬዎችን ፈቅደንና ወድደን ብናኖራቸው ጠገቡ’’ የምትለን የኦሮሙማው ኢንትርሃሙዌ ቡድን አባል አበበች አደኔ ፡ ሰሞኑን አዲሰ አበባ ውስጥ ሰላሉ ርሃብተኞች እንዲህ ስትል ተናግራለች፡

«አዲስ አበባ ላይ ጎዳና ላይ ወጥቶ ምግብ የሚያስለምን ምንም ምክንያት የለም። አዲሰ አበባ ውስጥ እንደው እውነቱን ለመናገር አዲሰ አበባ ላይ ጎዳና ላይ የሚያስወጣ ምክንያት በአሁኑ ሰዓት  የለም ወደ ምገባ ማእከላት ውስጥ ጎራ ብሎ ትኩስ ፥ ንጹህ እና የተመጣጠነ ምግብ  መመገብ የሚቻልበት ከተማ ሆኗል።ማረፊያ የሌላቸው ደግሞ ቤታቸው ነው፡ ማረፊያቸው ነው። ርቧቸው ምግብ በልተው አረፍ ብለው እርስ-በርሳቸው ተወያይተው የሚሄዱበት ቤታቸው ነው። ስለዚህ በየጎዳና ላይ የዕለት ጉርሻቸው የሚለምኑ ወገኖቻችን ሁሉ መልእክት ለማስተላለፍ እወዳለሁ። “በከተማ ውስጥ የተገነቡ የምገብ ማዕከላትን በመሄድ እጃችሁን ታጥባችሁ በንጽሕና መጥታችሁ መመገብ ትችላላችሁ። የሚያስፈልገው ሰው ከየት እንድየት መጣህ የሚለው ማንም ሰው የለም።” ተላለች ስትቀደድ፡

የሚገርመው፤ ጉልበታቸው ለደከመ አረጋዊያን ፤ ዕርጉዞች፤ ህጻናት እና አካለ ስንኩላን አድራሻ ወዳልተገለጸላቸው የመመገቢያ ጣቢያዎች «ማጓጓዣ አዘጋጅታ የሚያመላልሳቸው አብቶቡስ እና ታከሲ ያዘጋጀችላቸው ይመስል እየሄዳችሁ ተመገቡ ትላለች”።

አንድ መንግስት የድህነትን መዋቅራዊ መንስኤዎችን ከማንሳት ይልቅ የበጎ አድራጎት ገጽታ በመፍጠር ድሆችን ሕጋዊ እና ኢ-ሕጋዊ ድሆች” በሚል ደረጃ በመሰየም በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ በዚህ ዓለም ተሰምቶ የማያውቅ የድሆች ዓይነት ስም እያወጣ በዘር መድለዎ እና በቤት ግንባታ ሽፋን ድሆችን ከተጠለሉበት መኖርያቸው እያፈረሰ ፥ ከሥራቸው እያፈናቀለ፤ መናፈሻ ፓርክ ሰራሁላችሁ እያለ ሲያሟርት ወደ ጎዳና እንዲወጡ ያደረጋቸው ተፈናቃዮችና  ድሆች ፣ የሚያስለምን ምክንያት ምን እንደሆነ አላውቅም ትላለች (እያወቀች)።

አለቃዋም እንዲሁ«ከብት የሚግጠው የጓሮ ቅጠል እጁ ላይ ይዞ እያሳየ)» ሃገራችን  ችግር ውስጥ ሰላለች በርሃብ ከመሞት ይህንን ቀጠል ሸምጥጣችሁ ጨው ጨምራችሁ ፥ ካስፈለገም ትንሽ ዘይት ጨምራችሁበት ለ7 ሰው መመገብ ትችላላችሁ፡ እያለ “በሕዝብ ሕይወት” ቀልድ ይሰራል።

እንደመታውቁት ተምረው የመቅጠርያ ባጀት ስለታጣ  መንግሥት ባጀት የለኝም ሰላላቸው ፤ ሥራ ያጡ 1500 ሃኪሞችና በርካታ ነርሶች ስራ የላቸውም ሲል አዲስ ዘመን እንደዘገበ እናስታሳለን።

ስራ ላይ ያሉ የሕክምና ባለሞያዎችም ደማዛችን  ለኪራይ ፥ ለምግብና ለመጓጓዣ ሰለማይበቃን ቁርስ በልተን ምሳ ሳንበላ ውለን በመከራ እየስራን ነው ፤ በማለት ሥራ ያጡ እና የተራቡ ሃኪሞች በሚል የጻፍኩትን አስታውሱ።በወቅቱ የኢትዮጵያ ጠ/ምኒስተር ነኝ የሚለን የኦነግ ሸኔው ሰው አብይ አሕመድ እሮሮአቸው ሲያቀርቡለት ምን እንዳላቸው ላስታውሳችሁ።

የብዙ ሰው ልብ በሐዘን የነካቺው አንዲት የልብ ቀዶ ጥገና ስፕሻሊስት፡

«እባካችሁ አትግፉን (don't push us) ሀገራችንን ማገልገል እንፈልጋለን»  ስትል፣

አብይ አሕመድ ደጎሞ እኔም የ IT ባለሙያ ነኝ ወደ ውጪ መውጣት አቅቶኝ አይደለም ሀገሬን ላገልግል ብዬ ነው። እኔም ለሃገሬ እያገለገልኩ ነው አሞኝ እንኳ አሞኛል ሳልል እሰራለሁ፡ የሕክምና ሙያ ከምንም አይበልጥም» አላቸው።

ሃቁ ግን አብይ ከድሮ ጀምሮ ወደ ሥልጣን ሳይመጣ ከኋላ የራስ ቅል  (ጭንቅላቱ) ላይ እባጭ (ዒጥ) ስለነበረው ፤ ያችን ሥልጣኑን ተጥቅሞ ወደ ውጭ አገር በመሄድ ቀዶ ጥገና አድርጎ ታክሞ እንደመጣ እሱ ቢክድም ፎቶውን ከማየት ነው። እንዲያውም አዲሰ አበባ ውስጥም “ለአምላክ ምስጋና እና ፍቅር” በሚል ታክሞ መምጣቱን ሕዝቡ ሰላማዊ ሰልፍ እንዲደረግ አድርጎ  ትርጉሙን ሳያውቅ ሕዝቡን ሸውዶታል።

ከተማችንን አዲስ አበባን ለማስዋብ ስንል ባለሃብቶችን ኑ ግቡና አግዙን እያልን ስንት በጀት እያፈሰስን ባለንበት ሰዓት እናንተ ሐኪሞች "ብር" "ብር" አትበሉ ሕክምናን ብር ማግኛ አርጋችው አትስሩ ፡ስትመረቁ በገባችሁት ቃል መሠረት አርፋችሁ ሥሩ! አላቸው።

«ብርን አስባችሁ ከመጣችሁ አታስቡት ፡ ኢትዮጽያ በአሁኑ ወቅት ተመንዝሮ የማያልቅ ተስፋ እንጂ ብር የላትም፡ ምናልባት ለዘይትና ሽንኩርት 500ብር  እንጨምርላቹ ይሆናል።» ሲል ቀለደባቸው።

በሬ እየታረሰበት ሥጋውም እየተበላ ቆዳውም  ለጅማት ክር እየዋለ ይሄ ሁሉ ሲደረግበት ምንም ነገር አይናገርም… ሐኪምም እንደዚ በሬ ነዉ መሆን ያለበት...!"

እያለ በሕኪሞች ላይ ከቀለደ በኋላ አንድ ሓኪም በጻፈው መጣጥፍ ላይ እንዲህ ያለውን ላስነብባችሁ እና ወደ ጉዳያችን እናምራ፤

አብይ ለሐኪሞች እንዲህ አላቸው

ሰሞኑን ሐኪሞች ስላኮረፋችሁ ለኩርፊያችሁ የሚሆን ምሳ ብሉና ቤተ-መንግስቱን ጎብኝታችሁ ወደ ሥራ ሂዱ” አለን። ይላል አንድ ሐኪም። በማስቀጠልም

...ብቻ ብዙ ብዙ ነገር ተብለናል ፣ መሪያችን ባደባባይ ባሪያ መሆናችንን በድጋሚ ሲያበስረን እጅጉኑ አመመኝ።ሲል በቁጭት ለሕዝብ አስረዳ።

ሓኪሞች ሳይቀሩ ለሽንኩርት መግዣ በማጣት በሚሰቃዩባት አገር የባንቱስታዋ ከንቲባ አበቤች አደኔ ደግሞ ወደ ጎዳና ያስወጣቻቸው ድሆች “ኑ የተመጣጠነ ምግብ ተመግቡ” እያለች ታሾፋለች።

በ11 እና 12ኛው ክ/ዘመን የነበሩት መንግስታቶቻችን ስለ ድሆች አያያዝ እና የምግብ ማዕከላት ጉዳይ እንመልከት

የዛጉውዌ ሥርወ መንግሥት የንጉሥ መራ ተከለኃይማኖት የድሆች አያያዝ እና አመጋገብ ከመመልከታችን በፊት የሚክተሉት እንግዳ ቃላቶች ትርጉማቸውን እንመልከት

መጀምርያ የዘመኑ ቃላቶች እና ትርጉማቸውን እነሆ፡

 እልፍ(እልፍ ማለት የግዕዙ “ቁጥር ማለት ሳይሆን- ችግረኛ ሰው፤ ጧሪ እና ደጋፊ የሌላቸው ማለት ነው

 እልፍ አውል- እልፍ አውል ማለት ብዙ ሕዝብ የሚያውል፤ የሚረዳ የሚመግብ ማለት ነው።

እልፍ አስከባሪ--  እልፍ አስከባሪው እናት እና አባታቸው የማይጦሩትን ሰዎች እየተዘዋወረ እየመዘገበ ለቅጣት የሚያቀርብ ክፍል ነው።

ሐሰሴ ፍትሕ - ፍርድ አስፈጻሚ- ፍትሕ ሚኒስተር /ፍርድ አሳሽ /ፈታሽ/ መርማሪ/አጣሪ ማለት ነው

አበጋዝ - በመራ ተ/ሃይማኖት ዘመን  የተቋቋመ “በሐሰሴ ፍትሕ ሠራዊት” ስር የነበረ - ዋና ሥራው የሕዝብ መብት ሲደፈር ፥ገዢዎች ያለ አግባብ  በደል ሲፈጽሙ፤ክፉ ቀን ሲመጣ፤ድርቅ፤አንበጣ በአገሪቱ ላይ ችግር ሲደርስ ፤ ሕዝቡ ሳይጎዳና ርሃብ ሥር ሳይሰድ በአጭር የሚቀጭበትን መንገድ የሚያደርግ።

 ዶሚና የተባለ ደግሞ’ “የሰላም ዘበኛ’’ የመንግሥት ግብር በየወረዳው ሲሰበስብ ሕዝቡን ያለአግባብ እንዳይበደል መቆጣጠር ነው።  “አበጋዝ ከቱርክ የተገኘ ስም ነው” ብለው ቀ/ዳማዊ ኃለስላሴ “ሕይወቴ እና የኢትዮጵያ እርምጃ” በሚለው መጽሐፋቸው  በምዕራፍ 15 ላይ ‘’ቃሉ የተገኘው ቱርክ ሐረር ሲገባ ያመጣው ቃል ነው ቢሉም ፡ ንጉሡ ወይንም አማካሪዎቻቸው ተሳስተዋል። ይህ ቃል በ12ኛ ከ/ዘመን የነበረ በዘመኑ የተጻፉ የግዕዝ መጽሕፎቶች እንደተገኙ (አሁን እኔ ለዚህ መጣጥፍ የተጠቀምኩት መጽሐፍ ደራሲ ይገልጻሉ)። ደራሲውም ከታች አስቀምጣለሁ።

ጉሮጉሮኒንደር- በመራ ተክለሃያምኖት ዘመን ሐሰሴ ፍትሕ (ፍርድ አስፈጻሚ) የፍትሕ  ሚኒስተር የነበረ የከፋ አውራጃ (የአናርያ) ተወላጅ በቆዳ ቀለሙ “ጥቁር ሰው ነበር። በመራ ተክለሃያምኖት ለካም እና ለኩሽ ሰዎች (በቆዳ ቀለም) እየለየ ሥልጣን በመስጠቱ ከጠያይም ኢትዮጰያዊያን የካም እና የኩሽ (የአናረያ እና የመረዌ) ዘሮች ካልሆኑ ሲማዊያን ነን የሚሉ ወደ ጥንት ቦታቸው እንዲመለሱ እና የዓረብ ዘር ሆነው እስልምና የሚከተሉ ዓረቦችም አገራቸው እንዲገቡ፤ ሲማዊያን  ነን የሚሉትም  ከሥልጣን ተገልለው ኢትዮጵያዊያን ሆነው እሰላምና እመነት የሚከተሉ ካሉ ከሃያምኖት ወገኖቻቸው ጋር አብረው እንዲሄዱ ፥ ይህንን አንፈጽምም ካሉ ተጠምቀው ኢትዮጵያ አገራቸው  ሰለሆነች አርሰው የርስት ተካፋይ ሆነው  እንዲኖሩ በመደረጉ፤ በዚህ ላይ ከዮዲት ዘመን ጀመሮ በሃይማኖት ግጭት ሰለተፈጠረ ሰላም ደፍርሶ በመታየቱ።

ጉሮጉሮኒንደር ይህንን በማየት የቀለም እና የሃይማኖት ልዩነት ማድረግ ለሃገሪቱ ሰላም እና ባሕል መረጋጋት ጠንቅ ሰለሆነ ይህንን ማስቀረት አለብን ብሎ እሱ ሲሾም፤ጥቁሮችን ከየቦታው (ከመርዌ -ሱዳን) ሳይቀር በማስመጣት ከቀያዮች እና ጠያይም ኢትዮጵያዊያን ጋር ቀላቅሎ ሠራዊት የመሰረተ በንጉሡ እና በሕዝብ የተወደደ ሰው ነበር። (ስለ ጉሮጉሮኒንደር አስገራሚ የፍትሕ ሰው መሆን ሌላ ቀን እመለስበታለሁ) ዘመኑ ከመላው ኢትዮጵያ የመጡ ሰዎች የገነቡት አስተዋጽኦ መሆኑን ላሰምርበት እሻለሁ። ሥራውና ግንባታው የአገው ብቻ ፥ የአማራ ብቻ የትግሬ ብቻ.... ወዘተ... የሚሉ ደናቁርት ትንሽ መቆጠብ ያስፈልጋል።

አሁን ወደ ድሆች እንግባ፡

ንጉሥ መራ ተክለሃይማኖት ላስታ ውስጥ የተወለደ ነው። መራ በመጀመሪያ የአክሱማዊው የንጉሥ ድል ናኦድ (ጸረ ዮዲት ጉዲት ወገኖች ላይ ከባድ እርምጃ የወሰደ ንጉሥ) የጦር መሪ (በዘመኑ አጠራር “መሪ ፈረሰኛ የሰላም ዘበኛ” ነበር። ከዚያም የድል ናኦድ ልጅ መሶበ ወርቅን አገባ። ቆይቶም አማቹን ገልብጦ የዛግዌ ሥርወ መንግሥት መስርቶ የሰለሞንን ቤት ገለበጠ።

 ይሀ ንጉሥ ጧሪ እና ደጋፊ የሌላቸው “እልፎችን” ድሆችን እንዴት ይረዱ እንደነበር ያዋቀረው ልዩ የሆነ አስገራሚ አያያዝን እንመልከት።

ከላይ እንደተመለከትነው “እልፍ” ማለት ቁጥር ሳይሆን ችግረኛ ሰው/ሰዎች ማለት ነው። እነዚህ እልፎች «እልፍ አስከባር» በሚባል የችግረኞች እንባ ጠባቂ ድርጀት ችግራቸው እየታየ ዕርዳታ እንዲያገኙ ያደረጋል። ዕርዳታ የሚያገኙበት ቦታ ደግሞ “እልፍ አውል” በሚባል የመመገቢያ እና የዕርዳታ ቦታ ነው። እልፍ አስከባሪም ይሁን እልፍ አውል፤ ሁለቱም “በሐሰሴ ፍትሕ” (በፍትሕ ሚኒስቲር) ቁጥጥር ሥር የሚካሄዱ የዕርዳታ ዘርፎች ናቸው።

የእልፍ አውል ዋና ተግባር ወይንም የሥራ ድርሻ፤ ልጅ የሌላቸው መካኖች በበሽታ ወይንም እርጅና ምክንያት መሥራት ያልቻሉ ችግረኞችን መጦር፤ ከሥራ የተገለሉ በሽተኞች ፥ ጧሪ ከሌላቸው መደገፍ፤ ወላጆቻቸው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩና ዘመድ የሌላቸው ሕፃናትን መደገፍ ነው።

ጎረሞሶች ሆነው ሥራ ጠል ከሆኑ ይመረመሩና ወደ ፀጥታ አስከባሪነት ተመልመለው ይገባሉ። ጎረምሶች ሆነው ሥራ በማጣት ሲነከራተቱ የሚበሉት ካጡ ማቆያ ስፍራ ይሰጣቸውና  እና እንደ እየ የስራ ችሎታቸው እየታየ ህንጻ ሥራ ወይንም እርሻ እና ንግድ ከሆነም አጋሰሶች እየተሰጣቸው እንዲሰማሩ ይደረጋል።

ጧሪ እና ደጋፊ የሌላቸው አረጋዊያን እና ልጅ እግሮች ከሆኑ ግን እልፍ አስከባሪው ችግረኞችን እየተዘዋወረ በመሰብሰብ በተሠሪነት  እየገቡ እንዲቀለቡ ያደርጋል። ችግረኞችን የሚቀበለው ሰው ምግባቸውን፤ልብሳቸውንና ንጽህናቸውን የማሟላት ግዴታ አለበት። ተሠሪ የሚቀበለው ድሀው ሕዝብ ብቻ ሳይሆን ከንጉሠ ነገሥቱ ጀምሮ እሰክ ተራው ወታደር ያለውም ነው።

 ንጉሠ ነገሥቱ ሁለት ድርሻ አለው። አንዱ ከሕዝቡ የበለጠ ድርሻ ተሰጥቶት ተነቃናቂ ያልሆኑ እሰከ 300 የሚሆኑ ችግረኞችን ይቀልባል፥ ያለብሳል። በራሥ እና ደጃዝማች ማዕረግ ያሉት ደግሞ በቋሚነት አሥር ሰው በየቤታቸው ይዘው ሲቀልቡ፣ ከዚህ በተጨማሪ በተራ ሲደርሳቸው አንድ እልፍ (አድ ችግረኛ ሰው) ለወር ይቀልብ እና ለተረኛ ያዛውራሉ።

ከፊታውራሪ እሰክ ባላምባራስ ማዕረግ ያላቸው በነዋሪነት ሦስት ሰው ይይዙና በተረኛነት አንድ እልፍ ሰው ለስደስት ቀን ቀልበው ለተረኛ ያስተላለፋሉ።-

እልፍ አስከባሪው ቤተመንግሥት ያሉትን ሳይቀር በመልካም አያያዝ ወይንም በችግር ላይ መሆናቸውን ለማረጋገጥ በየጊዜው ቁጥጥር  ያደርጋል። በቋሚነት የተቀመጡትም ሆነ በወር ተራ የሚዞሩት ደህንነታቸው፥ ንጽሕናቸው፥ ልብሳቸው ፥ ምግባቸው እንደምን እንደሚሰራላቸው በመመርመር ጉድለት ያገኙበት ሰው ካዩ  ጉድለቱ ሰለሚያስጠይቅ በመልካም ሁኔታ የተረከቡትን ሰው ተነከባክበው ይይዙት እንደነበር በግዕዝ የተጻፉ የመዛግብት መረጃዎችን ያመላክታሉ።

እልፍ አስከባሪው እናት እና አባታቸው የማይጦሩትን ሰዎች እየተዘዋወረ በማጣራት ከአጽመ እርስት እንዲነቀሉ ያደርጋል። ከእርስቱ የተነቀለው ለጌታ ብያድርም ተቀባይነት የለውም። እናትና አባቱ ያልጦረ ሰው ፤ አሽከርነት አስገብቶ የተገኘ ማንኛውም ሰው ንብረቱ ተወርሶ ለመንግሥት ገቢ ይደረግበታል።የተወረሰው ንብረትም ድሆች እንዲረዱበት ይደረጋል።

ከዚህ የሥራ ከፍል ሌላ በሐሰሴ ፍትሕ ስር የሚተዳደሩ ብዙ የሕዝብ መብት አስከባሪ ቅርንጫፎች እንደነበሩ በታሪክ ስፍሯል።

አበጋዝ ፦ይህ ሹም በመራ ተክለሃይማኖት ዘመነ መንግሥት የተቋቋመና በሐሰሴ ፍትሕ ሠራዊት ስር የነበረ ነው። የሥራ ድርሻው የሕዝብ መብት ሲደፈር ፥ ገዢዎች  ያለአግባብ በደል ሲፈጽሙ ፥ርሃብን እና ድሕነተን ይሚያመጣ ከፉ ቀን ሲመጣ ፥ድርቅ አንበጣ በአገሪቱ ላይ ችግር ሲደርስ ሕዝቡ ሳይጎዳና ርሃቡ ስር ሳይሰድ በአጭሩ የሚቀጭበትን መንገድ መሻት ነው።

ሌላው በአበጋዝ ሥር የሚታዘዝ የሥራ ክፍል «ዶሚና» የሚባለው የሰላም ዘበኛ ነው። ሃላፊነቱም በወረዳ ውስጥ ያለውን ሕዝብ ግብር በወቅቱ እንዲገብር ማድርግ፥ መልከኛው ሕዝብም “”በግብርም ሆነ በሌላ የተንኮል ዘዴ እንዳይበደለውና ጎዳና ወጥቶ ደህይቶ እንዳይለምን የበላይ ሆኖ መቆጣጠር ነው።

 አበጋዙ ዶሚና የሚሰራውን እና የሰጠውን ጥናት ከዶሚና እየተቀበለ በሕዝብ ላይ የሚደረሰውን ከፈተኛም ይሁን ዝቅተኛ በደል ለአውራጃው አበጋዝ ያቀርባል። አውራጃውም ለበላይ አበጋዝ ያቀርብና እና ለሐሰሴ ፍትሕ ያቀርባል።”

ከዶሚና በታች ደግሞ «ገራዳ» የተባለው አካል አለ። ገራዳ ከዶሚና በታች ሆኖ የሕዝቡን ምሬት ይሁን አቤቱታ እና በደል ለዶሚና ያቀርባል።እነዚህ ክፍሎች በዘመነ መራ ተክለኃይማኖት  የነበሩ አሰራሮች እና ስሞች እንደነበሩ  በልዩ ልዩ የግዕዝ መጻሕፍት ውስጥ ሰፍሮ  ይገኛል።

ሕ ማጣት ለድህነት ምክንያት ከሆኑት አንዱ በመሆኑ በዚህ ንጉሥ ዘመን ከላይ የጠቀስኩት  «ጉሮጉሮኒንደር» የተባለው የናራ (ዛሬ አርሲ) ተወላጅ የነበረ የሰላም ጠባቂ የፍትሕ ሰው የድህነት መክንያት ፍትሕ ማጣት እንደሆነ ሰለገባው ፍትሕ እንዲሰፍን ከመኳንንቱ ጋር በመጋጨት ንጉሡ ሕጎቹን እና አሰራሩን እንዲለውጥ ያሳምነው ነበር።

ምንጭ፤

ጥንታዊ የኢትዮጰያ የሰላም ጥበቃ ታሪክ ከቅራት - እስከ ዘምናዊ ፖሊስ (ከአእምሮ ንጉሤ) ደራሲውም በመላ የኢትዮጰያ ገዳማት በመሄድ ያገኙዋቸውን ሦስት የግዕዝ መጻሕፍትን እንደ ምንጭ ይጠቅሳሉ።

እንግዲህ ከላይ እንዳያችሁት በ12ኛው ዘመን እልፎችን (ድሆችን) ከንጉሡ ጀምሮ ከተራ ሕዝብ ድረስ የተቸገሩትን በወረፋ እና በቋሚነት እንዲመግብ ይደረግ እንደነበር እና ወላጆቻቸውን አንጦርም ብለው ወላጆች ለልመና የዳርጉ ልጆች ንብረታቸው ይወረስ እንደነበር አይተናል።

   «በርሃብ ልናልቅ ነው ደሞዝ ጨምሩልን»ብለው ለጮሁ የኢትዮጵያ ሓኪሞች «ሰሞኑን ሐኪሞች ስላኮረፋችሁ ለኩርፊያችሁ የሚሆን ምሳ ብሉና ቤተ-መንግስቱን ጎብኝታችሁ ወደ ስራ ሂዱ እያለ ለተሳለቀባቸው አብይ አሕመድም ይሁን “የሰጠናችሁ ዳቦ ብቻ እየገመጣችሁ ፖለቲካ ሳታወሩ ተኙ” የምትለን ለሚስቱ “ለፓስተር ዝናሽ ታያቸው እና ለአበቤች አደኔ” የማቀርብላቸው ጥያቄ “እንደ ዛጉዌው መስራች እንደ ንጉሥ መራ እልፎችን እቤታችሁ ለማኖርና ለመቀለብ  ፈቃደኞች ናችሁ?

‘‘የለማኝ ልጅ’’ ከንቲባዋና ሚኒስትሯ|ETHIO FORUM

https://youtu.be/HEMMglhpdmQ?si=TXU1-bO9_7EBzCCJ


ጌታቸው ረዳ Ethiopian Semay