እውን
ትግሬዎች ወያኔን ይቃወማሉ? ያንን ለማመን የሚከተሉት የማሳመኛ መመዘኛዎች ማለፍ አለባቸው
ጌታቸው ረዳ
8/26/26 ዓ.ም
Ethiopian
Semay
ከየዓረብ አገሮች ምስል የተቀዳ መቀሌ ከተማ የቆመው ለእነ መለስ ዜናዊና የፋሺት ድርጅት (ህወሓት) ታጋዮች ለነበሩት መታሰቢያ ሓውልት ለምን ዓላማ ቆመ?
ወያኔዎች ኤርትራን
ለማስገንጠል፤ኢትዮጵያን ባሕር-አልባ ለማድረግና ኢትዮጵያን በቋንቋ ሸንሽኖ <<ራስ ገዝ አፓርታይድ ክልሎችን>>
እና አምሐራንና አማርኛን እንዲሁም ዓድዋ ላይ ጣሊያን ሲሸነፍ የተውለበለበቺው ሰንደቅዓላማችንን ለማጥፋት የተመሠረቱበት አመተ ልደታቸው በየአውራጃዎችና
ወረዳዎች በየአመቱ እስከ ዛሬ ድረድ ጥቂቶች ቢቃውሙትም በርካታው ሕዝብ ግን እያከበረው ይገኛል።
ትናንት “ቴዲ አዋሳ” በሚባል ሚዲያ አንድ ሰው እንዳደምጠው “ዩ-ትዩብ” ልኮልኝ ሳደምጥ አንድ
የትግራይ ወጣት ስለ “አቶ ገዱ አንዳርጋቸው” ጉዳይ እና “ጽምዶ” የሚባለው መሳለቂያ አንስቶ ተናግሮ ሲጨርስ ፣ አወያዩ “ይህ ዛሬ በቅርቡ እየተፈጠረ ያለው አዲሱ የትግራይ ወጣት ልዩ ነው፤ ወያኔን በደምብ አርጎ ይቃወማል...”
በሚመስል አባባል ሲናገር ሰምቸው፤ ይህ እምነት በብዙ ሰዎች ሲነገር የምሰማው እምነት ነው። ይህ እምነት ያልተፈተሸ አይደለም።
እኛ ጥቂቶች በየወቅቱ ወያኔን እንቃወማለን ብለው ብቅ ሲሉ የፈተሽናቸው ክስተቶች ናቸው።
በተለያዩ ወቅቶች ካሁን በፊት
ትግራይ ውስጥ የተነሱ ምናልባትም ክ9 ያላነሱ ተቃዋሚ ድርጅቶች ወያኔን ለመቃወም ሲመሰረቱ አስኳላቸው ገልጠን ስንፈትሸው ሃውልቱንም
ይሁን የፋሺስት ድርጅት ሆኖ ያገለገለው ወያነ የተባለው “ርዕዮት” የሚቀበሉ እና አክባሪዎች መሆናቸውን ሲናገሩ እና ሲከራከሩ አይተናል
አድምጠናል አንብበናል። አንዳንዶቹ እማ ጭራሽኑ ወያኔ ያሰመረላቸው የመገንጠል መብት አክብረው ትግራይን ለመገንጠል የሚንቀሳቀሱ
እንደ አሸን የፈሉ ፋሺስት ድርጅቶች ተፈጥረዋል። ሰለዚህም ይህ በዚህ 1 አመት ብቅ ያለው “የወያኔ ተቃዋሚ ወጣት” የሚባለው ክፍል
የሚከተለው ፈተና ማለፉን አለማለፉን እናረጋግጥ ዘንድ እነሆ እነዚህን መመዘኛዎች እንፈትሽ።
ጥያቄዎችም እነሆ
1ኛ ጥይቄ - “እንደሚታወቀው የሱዳን ፕረዚዳንት የነበረው “ፕረዚዳንት ዑመር አል በሺር (Omar al-Bashir) እና የሱዳን የስለላ ድርጅት National Intelligence and Security Service (NISS) ( ጂሓዝ ኣል ዓምን ዋል ሙኻበራት ኣል ወተኒ) የተባለው የስለላ እና የደህንነት ጽ/ቤት ዋና ሓላፊ የነበረው የወያኔ አባል እና ከፈተኛ ስራ ለወያኔ የዋለላቸው ሱዳናዊው «ጀነራል አልፋታሕ ማርዋን” (General alfataH Marwan) በተገኙበት መቀሌ ከተማ የቆመው ለእነ መለስ ዜናዊና የፋሺት ድርጅት (ህወሓት) ታጋዮች ለነበሩት መታሰቢያ ሓውልት መፍረስ አለበት ብለው ያምናሉ ወይ?
2ኛው ጥያቄ -ወያኔዎች ኤርትራን ለማስገንጠል፤ኢትዮጵያን ባሕር-አልባ ለማድረግና ኢትዮጵያን
በቋንቋ ሸንሽኖ <<ራስ ገዝ አፓርታይድ ክልሎችን>> እና አምሐራንና አማርኛን ለማጥፋት የተዋቀረው አሁን ያለው
የአፓርታይድ አወቃቀር ይቃወማሉ ወይንስ ይቀበላሉ?
3ኛው ጥያቄ- እንዲሁም ዓድዋ ላይ ጣሊያን ሲሸነፍ የተውለበለበቺው ሰንደቅዓላማችንን በነበረቺበት
ክብር እንድትውለበለብ ይታገላሉ?
4ኛው ጥያቄ- “ተጋዳላይ ትግራይ ኣርኪብካ በሎ ነቲ ዓሻ አምሓራይ” እያሉ እየጨፈሩ
በማኒፍስቶ ላይ ያስቀመጡት « አማራ ገዢያችን ነው፤ የአማራ ሕይወት ዕረፍት እሰክታጣ ድረስ እንታገላለን” እያሉ የጻፉትን ዛቻ
እነሆ 35 አመት ሙሉ የአማራ ሕይወት ዕረፍት እያጣ እነሆ እሰካሁንዋ ደቂቃ ድረስ አለ። ይህንን ለማስቆም የመጀመሪያ ማሳያ “የአማራን
ህይወት ዕረፍት ለመስጠት ያመች ዘንድ” ፋሺስቶቹ የተመሠረቱበት «አመተ ልደታቸው» በየአውራጃዎችና ወረዳዎች በየአመቱ እንዳይከበር
ይጥራሉ?
5ኛው ጥያቄ- ‘’አማራ ብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች” የሚባሉ የፖለቲካ ትንግርቶች ጨቋኝ
ነበር ወይስ አልነበረም ብለው ያምናሉ?
6ኛው ጥያቄ- የዘር ፍጅት (ጀንሳይድ) በመፈጸም በጉልበት ወደ ትግራይ የተጠቃለለው የወልቃይትና
አካባቢው ቦታዎች ቅድመ የካቲት 67 የነበረውን የጎንደር መስተዳድር ወደ ቦታው እንዲመለስ ይስማማሉ ወይ?
7ኛው ጥያቄ- በቤተክርስትያናት እና መስጊዶች፤ ትምሕርት ቤቶች፥ ተራራዎች፤ ሕክምና ቤቶች
እና የታሪክ ቦታዎች ሁሉ፤ እንዲሁም በየ በዓላት እና ሓይማኖታዊ በዓላት ወቅት ዘማሪዎች ፤ የቀሳውስት /ካሕናት ልብሶች፤ ጃንጥላዎች፤
እና ሕዝቡ የሚያውለበልበው እና የሚለብሰው የወያነ ድርጅት ባንዴራ መሆኑን ግልጽ ነው። ታዲያ ወጣቱ ይህ ባንዴራ የፖለቲካ ድርጅት
ምልክት ሰለሆነ ሁሉንም የሚወክል የወላጆቻችን ዓድዋ የተውለበለበቺው የነፃነት ምልክት በኢትዮጵያ ባንዴራ መተካት አለባት ብሎ ይቀሰቅሳል?
እነኚህ እና የመሳሰሉ ፈተናዎች ማለፍ ይችላል? የሚሉ ፈተናዎች መፈተሽ አለባቸው።
ርዕሱ ላይ እንዳያችሁት |ብዙዎቹ| ትግሬዎች ይህንን ሲያነቡ እሳት ላይ እንደሚጠበስ ስጋ መንጨርጨራቸው
አይቀርም። ምክንያቱም ፋሺሰቶች ሲነኩ የሚያሳዩት ባሕሪ ስለሆነ አይገርምም። የጥላቻ እና የቂም ሃውልት ቀርጾ ለትውልድ የሚያስተላልፉ ፤ ሕዝብ ለሕዝብ ቀጣይ ጦርነቶችን የሚጭሩ በየገጠሩና ከተሞች የተተከሉ ትግራይ
ወስጥ የቆሙት ሃውልቶቻቸው ካልፈረሱ “ከቂም ወደ ቂም” “ከጦርነት ወደ ጦርነት” ፤ ከውሸት ወደ ዘላቂ የውሸት ትርክት የሚያስቀጥል ምልክት
ሰለሆነ የግድ መፍረስ አለበት።መመዘኛ አድርጌ የማቀርበውም ይህንኑ ነው። ፈተናው ለአኖሌ ሃውልት አምላኪዎች ለኦሮሞ ወጣቶች እና ለኦሮሞ
መሁራን ጭምርም ነው።
እነ መለሰ ዜናዊ እና እነ ሥዩም መስፍን የመሳሰሉት የተሰው ታጋዮቻችን እያሉ የሚጠርዋቸውና ሃውልት ያቆሙላቸው ታጋዮቻቸው “ያልሆኑትን <ነበሩ>” እያሉ በውሸት
እንደሚክቡዋቸው ለዲሞክራሲና ለእኩልት
የተሰው ሳይሆኑ የወያኔና የሻዕቢያ ተዋጊዎች ከትግራይ እና ኤርትራ ተራሮች ጀምረው “በጋራ” ኢትዮጵያዊያንን እየገደሉ አዲስ አበባ ሲገቡ የኢትዮጵያ ሠራዊትን “ወራሪ” “አምሐራይ” እያሉ ከጣሊያን በባሰ መልኩ
ኢትዮጵያዊውን ሠራዊት 1ሚሊዮን የሚገመት “ሠራዊት
እና ቤተሰቦቻቸው” ያለምንም መጠለያና ምግብ ወደ ጎዳና በትኖ ባለማዕርግ መኮንኖች “ኮከባቸው መለዮአቸውን መሬት ላይ አንጥፈው”
ሳንቲም እንዲለምኑ ያደረጉ የፋሺስት አለቆቻቸው ድርጊት ፈጻሚ ታጋዮች የነበሩ ናቸው።
ያለተሰውት የተቀሩት በህይወት ያሉት በየ ዓለማቱም ይሁን በሃገር ውስጥ ያሉ ታጋዮችም ፋሺቱ መሪያቸው መለስ ዜናዊ ሲሞት ደም ዕምባ ያለቀሱ ፡ በፋሺሰት የደህንነት
አለቆቻቸው እየታዘዙ አምሐራ የተባለው ምሁር እና ኢትዮጵያዊነቱ በጽናት የያዘ የትግራይ ተወላጅ “ጸረ ወያኔ ነው እያሉ”
ለቁጥር የሚያዳግት ግድያና ድብደባ በመፈጸም፡ተሳዳጁን እንደ ጅግራ በየገጠሩ እና ጫካ እያደኑ ትግራይ የፍርሐት እና የሽብር መድረክ አድርገው ያንን
ሲፈጽሙ፡
ወደ አዲሰ አበባ እንደገቡም እንደ እነ አሰፋ
ማሩ የመሳሰሉትም ኢትዮጵያዊያን በጠራራ ጸሐይ አደባባይ ላይ ነጻ እርምጃ ሲወስዱ የነበሩ የግድያና የእስር ድርጊት ፈጻሚዎች እንጂ ለሕዝብ መብት ተሰው የሚሉዋቸውም ሆኑ በህይወት ያሉት ተጋዮች ካንድ ኩሬ “ከትግራይ የፋሺሰት ርዕዮት” የተቀዱ የፋሺስቶች
ታዛዥ ተዋጊዎች እንጂ <<ለእኩልነትና ለዲሞክራሲ>> የታገሉ ታጋዮች አልነበሩም።
እነዚህን ታጣቂዎች አሰማርቶ ኢትዮጵያ የተሰራቺበት
ድር እና ማግዋን ጥንታዊ ክሮችዋን እንዲበጣጠስና እርስ በርስ እንዲፋጅ ኢትዮጵያ አሁን ላለቺበት መከራ የዳረጉ ይህንን የፈጸሙ
የወያኔ ትግሬ መሪዎችና ተዋጊዎች ቢያንስ ራሳቸውን ለፍርድ
አቅርበው ይቅርታ ባይጠይቁም ራሳቸው እንደ ኢትዮጵያዊነታቸው
የሚቆጥሩ ከሆነ፡የተጓዙት መንገድና ድርጊት አውግዘው ታጋዮች ብቻ ሳይሆኑ አሁን ያሉት ወያኔን ይቃወማሉ ተብሎ በየሚዲያው
የሚነገርላቸው አዳዲስ የወኔ ተቃዋሚዎች አምነናቸው ለምቀበል «መቀሌ ላይ የቆመው ሃውልትና በየከተማውና ገጠር ጋራ
ሸንተረሩ ያቆሙዋቸው የጥላቻ ቀስቃሽ ሃውልቶች እንዲፈርሱ አቋም መያዝ አለባቸው።
የኤርትራ የሽምቅ
ተዋጊ ቡድኖች ስሜት በመኮረጅ ቀ.ሃ.ስ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ አክራሪ የትግራዋይነት ስሜት በማጎልበት
7ቱ የትግሬ ወጣት ተማሪዎች የመሠረቱት የ1967 ዓ.ም የትሓህት ሽምቅ ተዋጊ ድርጅት መሰረታዊ መነሻው ምንድ ነው?
መነሻቸው ልክ
እንደ ኤርትራኖቹ ለግንጣላ በድምጽ ብልጫ የትግራይ ሕዝብ አስፈቅዶ ከኢትዮጵያ ለመገንጠል- (ሬፈረንደምና ፈቃድ እንደምታውቁት
“ሽፋን” እንጂ ወያኔ አድርግ ያሉት የሚያደርግ ሕዝብ እንደነበርና አሁንም እንደሆነ የምታውቁት ነው። ሆኖም ሥልጣኑንና ሃብቱን
ተቆጣጠሩና ያንን ዕቅድ አዘገዩት) ለዚህም መነሻቸው በዙ ጸረ አማራ መጻሕፍትና ሰነዶችን የጻፉ፤ <<አምሐራንና ኢትዮጵያን ከነ ሰንደቅዓላማዋ እንደ ጠላት ቆጥረው>> ወደ ደደቢት በረሃ
የወጡ ፤ ትምህርታቸው በቅጡ ያላጠናቀቁ ተማሪዎች ነበሩ።
መስራቾቹ እነማን
ነበሩ?
<<ልባቸው
በኤርትራነት ፍቅር የተማረከ ፤ ሙሉ በሙሉ ከኤርትራ ወላጆች የተወለዱ ፤ ወይንም ግማሽ በግማሽ ትግሬና ኤርትራ ፤ እንዲሁም የድርጅቱ
ዋና ምሐንዲስ የነበረው ከጊዜ በኋላ ወደ “ትግሬነት” የተለወጠው <<ከአምሐራው ጎጃሜው የደ/ዝማች አስረስ
ተሰማ ልጅ ከሆኑት አቶ ዜናዊ አስረስ እና ከኤርትራዊትዋ ወ/ሮ አለማሽ ገብረልዑል የተወለደ ሟቹ መለስ ዜናዊ የመሳሰሉ ጸረ
አምሐራ የሆኑ ፋሺስቶች የመሰረቱት ፣ የገነቡትና የመሩት ድርጅት ነው።
ሃውልቱ ለነ
መለስ ዜናዊ ቆየት ብሎም ሞት እየጎተታቸው ለሚገኙት በትግራይ ወጣቶች ነብስ ሲጫወቱ የነበሩት ለወንጀለኞቹ ለነ ስብሐት ነጋ እና
ዛሬም “ሸዋ” የሚል ቃል ከምላሳቸው የማይለየው (የሚዲያ ሰዎች) እና
የወያኔ ታጣቂ “አዋጊዎች” እና የፋሺዝም ትግራዋይነት ፖለቲካውን የሚዘውሩት ለነ ስብሓት ነጋ ፥ ለእነ ደብረጽዮን፤ ጌታቸው ረዳ ፤ ሞንጆሪኖ ፤ ቴድሮስ ሐጎስ፤ ዓለም ገብረዋህድ… የመሳሰሉ
ጸረ አምሐራ እና ጸረ
ኢትዮጵያ የሆኑ ግለሰቦች ሲሞቱ በማስታወሻነት ፎቶግራፋቸው የሚለጠፍበት የፋሺቶች ሐውልት ነው። ለነዚህ ነው የተተከለው።
ሃውልቱ የቆመላቸው
ታጋዮቹም መሪዎችም <<ገመናቸው>> ስንፈትሽና ትግላቸው ስንመረምር <<በወንጀል የተጨማለቁ፤ በጭፍጨፋ
፤ ሃገር በመክዳት ፤ ኤርትራን በማስገንጠል እቦታው ድረስ ሄደው የተገደሉና የገደሉ ፤ ለኢትዮጵያዊነት ሳይሆን የወያኔ
ድርጅት ባንዴራ እያውለበለቡ ኢትዮጵያዊነታቸው ከድተው ለትግራዋይነት የበላይነት ዓላማ “የተሰው” የነ ስብሓት እና የነመለስ ዜናዊ ሎሌዎች ነበሩ።
በአመለካከት
የተቃወማቸው ሁሉ በየገጠሩና በየከተማው እየገቡ እንደ ጅግራ እያደኑ ዜጎችን ሲያሸብሩ የነበሩ <<ማፊዮዚ>>
‘የነብሰገዳይ ድርጅት’ ተዋጊዎችና ተላላኪዎች የነበሩ ናቸው (የራሴው የሥጋ ዘመዶቼም ጭምር)
።
ኢትዮጵያ ወታደሮችን
ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያዊነታቸውን አጥብቀው ያደመቁ ሃገር ወዳድ ኤርትራዊያን ከከሓዲዎቹና አምሐራን በጠላትነትን ከፈረጁ በስሜት ከሚጋልቡ ደናቁርት የኤርትራ ሽምቅ ተዋጊዎች ጋር አብረው መረጃ በመስጠትና
በማሳፈን አሳልፈው ሲሰጡ የነበሩ ፤ እንዲሁም ዓድዋ ከጣሊያኖች ጋር ጦርነት ሲደረግ በድል የተወጣችውን ኢትዮጵያዊያን
አርበኞች ያውለበለቡዋት ሰንደቅዓላማችንን
ጨርቅ ነው ብሎ ኮከባዊ
የሰይጣን አምልኮ ያለበትን ምልክት በማድረግ ሃገሪቱ ውስጥ 44 ባንዴራዎች እንዲወለበሉና “እንድትዋጥ” በማድረግ የሃገራችን ኩራት የሆነቺውን የወላጆቻችን
ዓርማ ከኢትዮጵያዊያን ገላ የገፈፉ ባንዳዎች እንጂ ኢትዮጵያዊ ታጋዮች አልነበሩም። ሰለዚህም ሐውልቱ መፍረስ ቀዳሚ መለኪያ መሆን አለበት።
ጀርመንን እንመልከት፡
አስተዋይ ጀርመኖች
ሃገራቸው ከናዚ አመለካከት እንድትጸዳ ለናዚ ታጋዮችና መሪዎች የተተከሉ ሃውልቶች እንዲገረሰሱ ወይንም ወደ ሚዚዮም እንዲታሸጉና
ናዚያዊነትን ከሕዝቡ ሕሊና ለማፅዳት ሞክረዋል።
ቤተ መፃህፍቶች ሁሉ፣ የያዙዋቸውን
መጽሃፍቶች፣ ትምህርት ቤቶች እና ዩኒቨርሲቲዎች ሁሉንም የናዚ ፕሮፓጋንዳ ቁሳቁሶችን
እንዲያስረክቡ ጠይቀዋል።
ትግራይን እንመልከት፡
በተመሳሳይ
ትግራይ ውስጥ በየትምህርት ቤቶችና መዋዕለ ህጻናት፤ በየሕክምና ተቋማትና ቤተ እምነቶች የወያኔ ናዚ ፓርቲ የሚያወድሱ መጽሐፈቶች፤
ግጥሞች፤ ዘፈኖች፤ መጽሔቶች፤ ጋዜጦች፤ ፖስተሮች፣ ሐውልቶች፣ በማን አለኝነት ጥንታዊ ስሞችን በመሰረዝ በምትካቸው በታጋዮቻቸው ስም የተሰየሙት ሃውልቶች ትምህርት ቤቶች ፥ የመንገድ፤ የወንዝ፤ የተራራ፤ የቅርሳቅርስ አካባቢዎች
ስሞች ምልክቶች
እና አርማዎች በሙሉ ተሰብስበው ወደ ማጎርያ ሙዚየም ወይንም መታጎር ወይንም መፍረስ ወይንም መቃጠል አለባቸው።
በሚያሳዝን
ሁኔታ ጥንታዊ ጥናት ለማካሄድ ወደ ትግራይ የሚሄዱ የውጭና የሃገር የታሪክ ተመራማሪዎችና ጸሐፍቶች በሚያደናግር መልኩ “በአዳዲስ
ስሞች” ብዙ ሸለቆች፤ መንደሮች፤ ገጠሮች ፤ ተራሮች፤ ሜዳዎችና ወንዞች” በታጋዮቻቸው ስም በመሰየማቸው ተመራማሪዎቹ ችግር እንደሚገጥማቸው
እርግጠኛ ሆኜ የምናገረው ለወደፊቱ አዲስ ትውልዶች እና ተመራማሪዎችን ከማደናገሩ በፊት ያንን
ችግር ከማስከተሉ በፊት የተሰየሙት ተጠንተው እንደገና ወደ ጥንታዊ ስሞቻቸው መለወጥ አለባቸው።
ትግራይ የወያኔ ድርጅት ተከታዮች ንብረት ብቻ አይደለችም፡ የወያኔ ተቃዋሚዎች የሆንን የኛም የትውልድ ቦታችንም ነችና ድምጻችን መሰማት አለበት!
ከተሰውት ታጋዮቻቸው
ደምቆ በግዙፍ ፎቶግራፍ በሃውልቱ አዳራሽ የተለጠፈለት የዚህ ድርጅት መሪ የነበረው መለስ ዜናዊ ኢትዮጵያ ያለ ባሕር በር እንድትቀር
ማመልከቻ ጽፎ ለእናት መንደሩ ለኤርትራ ወግኖ የተጫወተው ወንጀለኛው መለስ ዜናዊና መሰሎቹ እንዴት ሲሆን ነው ለነዚህ ከሃዲዎች
ሃውልት ቆሞላቸው “ሰማዕታት” ተብለው
መዘከር የሚኖርባቸው?
የትግራይ ሕዝብ
ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚል ከሆነ <<ሃገር ያስደፈሩ ባንዳ ነብሰገዳዮችና ዘራፊዎችን ማውገዝ አለበት>> ካልሆነ አይደለሁም
ካለም ወያነ ማለት እኛ ነን እኛ ማለት ወያኔ ማለት ነው፤ ስለዚህ የወንጀሉ ተባባሪ ነን የሚለው እውን ሊሆን ነው።የሆነውም ያ
ነው።
ሃውልቱ ቆሞላቸዋል
የተባለላቸው ታጋዮች ምንም የታሪክና የፖለቲካ ምጥቀት ያልነበራቸው ታጋዮቻቸውም በውሸት <<ለዲሞክራሲና
እኩልነት ሲሉ የተሰው ናቸው>> እየተባለ ለነ መለስ ዜናዊና ለታጋይ አሽከሮቹ ሲዋሽላቸው ስሰማ የትግሬዎቹ እውነታን
የማዛባት ባሕሪ መቸ እንደሚቆም ሁሌም ይገረምኛል።
ታጋዮች ሲባልላቸው
የነበሩት እኮ ብዙዎቹ እናውቃቸዋለን። ዲሞክራሲና እኩልነት ምን ማለት እንደሆነ የማያውቁ በህጻንነታቸው ወደ ትግሉ የገቡ
“ሰው ሲገድሉና ሲገርፉ” የነበሩ የፋሺሰቱ የነ ስብሓትና የመለስ ዜናዊ ታዛዥ ተዋጋዎች ሲፈጽሟቸውና ሲዘፍኑዋቸው ከነበሩት
መልዕክቶች አኳያ የዲሞክራሲና የዕኩልነት የሚያስተላልፍ መልዕክት አልነበረም።
ይህ አጽንኦት
የሚሰጠው ለዲሞክራሲና ለዕኩልነት ነበር የተዋጉት የሚባልላቸው ተዋጊዎች ምን ሲያደርጉ እንደነበር እኮ እናውቃለን። ታሪካቸው አንብበናል፤
በአካል አይተናቸዋል፤ አወያይተናቸዋል፤ ስሜታቸው አንብበናል፤ አምሐራ ማለት ምን ማለት አንደሆነ ሲተረጉሙት፤ካንደበታቸው የሚወጣ
አስጸያፊ ቃል አድምጠናል፤ ፍጹም ፤ እየተባለላቸው የነበረው ያልነበሩ ፤ “ግደል ሲባሉ የሚገድሉ፤ ደብድብ ፤ እሰር ፤ አሰቃይ”
ሲባሉ የሚፈጽሙ፤ አባት እህት ወንድም ግደሉ ሲባሉ ቤተሰቦቻው ሲገድሉ የነበሩ Cambodia’s Khmer Rouge; የካምቦዲያ
ኸመሩዥ ኮሚኒሰትና ፋሺስት ተዋጊ ዓይነት ገራፊዎችና በየገጠሩና በየከተማው በሕዝቡ ሕይወት ላይ ሽብር የሚለቁ የፋሺሰት ድርጅት
የሽብርና የጥፋት ታጋዮች የነበሩ ናቸው።
እዚህ ሥልጣን ከያዙ አዲስ አበባ እንኳ ኢትዮጵያዊነታቸው አጥብቀው
ለያዙ ዶ/ር ሃይሉ አርአያ ስለ ትግሬ መርማሪዎችና ፖሊሶች ምን እንዳሉ ታስታውሳላችሁ።
<<…ከቤቴ እየደበደቡና እየተሳደቡ የወሰዱኝ የትግራይ ልጆች ነበሩ። ማዕከላዊ እንደደረስኩ ቀበቶዬን ያስፈታኝ የትግራይ ሰው ነው። ከእርሱ ተቀብሎ አንድ የፍሪጅ ያህል የሚቀዘቅዝ ክፍል አስገብቶ የቆለፈብኝ የትግራይ ሰው ነው። ሲመሽ ሽንት ቤት ወስዶ ያሸናኝ ሰው የትግራይ ሰው ነው።እየተሳደበ ቃሌን የተቀበለኝ የትግራይ ሰው ነው።በእርግጥ እኔ የትግራይ ሰው ሆኜ ከአንድ አካባቢ በወጡ ሰዎች ጥቃት እየደረሰብኝ እንደሆነ ከተሰማኝ ሌላው ሰው ምን ሊሰማው እንደሚችል አስቤ ለትግራይ ህዝብ ከልቤ አዘንኩለት። ይሄ ሁሉ የሚደረገው ለትግራይ ህዝብ ሲባል ነው መባሉ ደግሞ የበለጠ ሰላሜን ነሳው።>>
ይህን ምስክርነት የሰጡት የትግራይ ተወላጁ የቅንጅት ፓርቲ
አመራር የነበሩት ዶክተር ሃይሉ አርአያ ናቸው ። ተሰው ተብለው
ሃውልት የቆመላቸው ታጋዮች በሕይወት ዛሬ ቢኖሩ ኖሮ ከነዚህ አረመኔ ፖሊሶችና መርማሪዎች የሚለዩ አይሆኑም ነበር።
መቀሌ ውስጥ
የቆመው ጸረ ኢትዮጵያ የጥላቻ ሃውልት ለታጋዮቹ መዘክር በሚል ሽፋን የተገነባ ይሁን እንጂ ዋና ተልዕኮው <<በትግሬና
ኢትዮጵያ አስካሁንዋ ደቂቃ ድረስ በታጠቁ ታጋዮች፤ በትግራይ ምሁራን
እና ጋዜጠኞች “ሸዋ”
የሚለው ቃል ዛሬም በየንግግራቸው ሲደነቅሩት የሚታይ የማይበርድ ቀጣይ የአምሐራ ሕዝብ ጥላቻና ጸረ <<ብሔረ ኢትዮጵያ>>
የሆነ “ግጭትና ጦርነት በዘላቂ ለማስቀጠል የቆመ” የወያኔ መሪዎች ያቆሙት የጥላቻ ሃውልት ነው።
ሃውልት አቁማናል፤ በየሰልፉ ለታጋዮች የደቂቃ ጸሎት እናድርግ እያሉ ሕዝብን
ለማታለል የሚጠቀሙበት ማታለያ ዘዴ ካልሆነ በቀር በሕይወት ያሉ በትግሉ ቆስለው እስካሁንዋ ደቂቃ ድረስ ጥይት ከገላቸው ውስጥ ተሰክቶ
የቀረ “ስራ የሌላቸው” የራሴ ወንደሞችና ዘመዶች ፤ በየስብስባው ለፕሮፓጋንዳ ማሳመርያ የሚያደርጉት <ዝኽሪ ንስውኣትና> (ለታጋዮቻችን
የሕሊና ፀሎት) እያሉ በውሸት የሚጸልዩት ማታለያ “ፀሎት” የሚያደርሱትም ሆኑ እነ ስብሓትና እነ ደብረጽዮን”
ሳይሆኑ የሚረድዋቸው እኔ ካለኝ ጥቂት ገንዘብ እየላኩኝ ነው ኑሮአቸው የሚገፉት።
የነዚህ ፀሎት
አድራሾች እውነታ ግን <<ዛሬም ሂድና ሙት ቁሰል ትግራይ ትዕወት>> እያሉ ወጣቱን ማስጨረስ ነው።
በመሪነት የተቀመጡትም የመሪዎቹ ልጆችና ዘመዶች ግን በየፈረንጅ እና ቻይና ሃገር እያላኩ በምቾት አስተምረዋል፤ሃብት ገንብተዋል።
<<ለማያውቅሽ ታጠኚ>> የሚባለውም ለዚህ ነው።
ለዚህ ነው
ድሕረ ናዚ “ጀርመን እንዳደረገቺው” ኢትዮጵያም <<ኢትዮጵያዊ መሪ ስታገኝ>> ሃውልቱ ከስሩ ተደርምሶና ደቅቆ
ወደ ቆሻሻ መጣያ መጣል እንዳለበት ለብዙ አመት የምወተውተው።
አንድ ዘመዶቹ
በግፍ የገደሉበት እስከዛሬ ድረስ ምንም ፍትሕ ያላገኘና ወያኔዎችን መከስስ የማይቻልባት ትግራይ ውስጥ የሚኖር ስሙን ለመግለጽ የማልፈልገው
ሰው ፤ ባንድ አጋጣሚ ለጉብኝት እዚህ አሜሪካ መጥቶ ያነጋገርኩት አንድ የትግራይ ልጅ ስለ ሃውልቱ አንስቶ ሲያጫውተኝ፤ እንዲህ
ይላል፡
<<መቀሌ ጎዳናዎች ስዘዋወር የማያቸው የወያኔ አርማዎችና በተለይ ሃውልቱን ስመለከት በቦምብ የማጋየት ስሜት
ይጫነኛል።የቤተሰበቼ ደም ከንቱ ቀርቶ ገዳዮቹ ሃውልተ ቆሞላቸው ሳይ ብሶቴ ያስቸግረኛል፤ በተለይ ደግሞ እዚህ ውጭ አገር ሆነው የሃወልቱ ምስል
በየ ዩቱባቸው ለጥፈው ስመለከት የቤተሰቦቼ ገዳይ ድርጅት ተባባሪዎች ሆነው ሳያቸው በሰለጠነ ሃገር የመኖር ትርጉሙ “ኮንሴፕቱ” ሊገባ አልችል ብሎኝ ሁሌም አስባለሁ>>
ሲል ምሬቱን አጫውቶኛል።
በሚያስገርም
ሁኔታ ይህ ድርጅት ላለፉት 50 አመት ያመጣልን ምን በጎ ነገር አለ? ብሎ የጠየቀ የትግራይ ሕዝብና ምሁር አላየሁም (ካሉም ጥቂቶች ናቸው)። ሞት፤አካለ ስንኩልነት ፤ ብጥብጥ፤ እርዛት፤ ውርደት፤ የባሕር-በር ማጣት፤ ዘረኛነት፤
ሃገር አልባነትና ስደተኛነት “የወያነ ትግራይ” የትግል ውጤት እንደሆነ ፍጹም ሊታያቸው አልቻለም።
በቅርቡ ከስንት
ውርደትና አካለ ስንኩልነት በኋላ ፤ የትግራይ ሕዝብ ከዚህ ድርጅት ጋር ላለመቀጠል ዛሬ በቅርቡ አንዳንድ ትንሽየ ነጸብራቅ
እንኳ ቢታይም 99.9% ሕዝቡ የድርጅቱ “ባርያ” ሆኖ ለመቀጠል የወሰነ
ነው የምልበትም ምክንያት
ያቀረብኩዋቸው የማለፊያ ፈተናዎች እስካላለፉ ድረስ ነው።
ብዙዎቹ የኢትዮጵያ ሚዲያዎች የትግራይ ሕዝብ ወያኔን ተቃወመ እያሉ ሕዝቡ ለሁለት
ስለተከፈሉት የወያኔ መሪዎች ደጋፊና ተቃዋሚ ሆኖ በመታየቱ ብቻ <<ወያኔን የተቃወመ እየመሰላቸው ብዙ የሚያስጮሁት ሚዲያዎች
ስሰማ የትግራይ ማሕበረሰብ ዛሬም የወያኔ ባንዴራ እየለበሰ በየአደባባዩ ሲወጣ መልዕክቱ ምን እንደሆነ እንኳ ሚዲያዎች ሊረዱት አልቻሉም።
ማሕበረሰቡ
በብዛት ወጣት ነው። ይህ ወጣት ደግሞ የወያኔ ጡት (ፖለቲካ) እየጠባ ማደጉና ወያኔ ማለት የማይረሳ የእናቱ ጡት መሆኑን ምን እንደሚል ላስደምጣችሁና ልደምድም፡
መቀሌ ውስጥ በትምክሕት ሲጨፈር የነበረውን የተለመደው የመቀሌ የእንደርታዎቹ የዘፈን ጭፈራ ንግግር በቪዲዮ የተቀረጸው በደስታ የቀለጠው ትምክሕታዊ የደስታ ጭፈራ እንዲህ ይላል፦
“ናዓና ዝመስል
የለን” (እኛን
የሚመስል ተወዳዳሪ
የለም) ፤ “ትግራዋይ ዝመስል
ባዓል ስረ የለን” (ትግሬን የሚያክል ባለ ሱሪ ወንድ የለም) ፤ “ሃ! ሁ! ምስ ወየነ እየ ዝዓበኹ) ፤ (ሃ! ሁ! ከወያኔ ጉያ ነው ያደጉት!)
“ሃ! ሁ~ ወያነ እንዳበልኩ
እየ ዝዐበኹ”
(፤ ሃ! ሁ!
ወያኔ እያልኩ
ነው ያደግኩት) …መቐለ ፤መቐለ!!! (መቀሌ!
መቀሌ!) “ናይና! ናይና ናይና!!” (የኛ
ነች የኛ!!) “ኣየኹም
ናይና!!” (የኛዎቹ ኣይዝዋችሁ!!)”” ሲል ነበር ጦርነቱ ከመጀመሩ
በፊት።
ይህ ወጣት
ነው ዛሬ በብዙ ኢትዮጵያዊያን ሚዲያዎች በተሳሰተ ድምዳሜ ደርሰው <<የትግራይ ሕዝብ ጦርነት ይብቃን አለ፤ ወያኔ ተቃወመ>>
እያሉ የሚዘግቡት፤ ጦርነት ይብቃን ስላለ ብቻ “የወያኔ ርዕዮት” ተቃወመ ወይንም የወያኔ መለያና አርማ ጣለ አወገዘ ማለት አይደለም። የናዚ ወጣቶች ጦርነት ይብቃ ብለው የስዋስቲካ ምልክትና
የሂትለር ዓርማ ካልጣሉ “ዞር አሉ አልሸሹም ነው”
ናዚ ወይንም
ፋሺዝም የሚኖርበት ፍልስፍና ትዕቢትና እኛ ማን አህሎኝነትና ጦርነት በመቀስቆስ ነው። ስለሆነም ትግሬዎች ፍኖተ ካርታቸው ካላስወገዱት፤
ጦርነት ስለተቃወሙ ብቻ ፤ እስኪደላደሉ እንጂ ያ ጊዜያዊ እንጂ
ዘላቂ አይሆንም (አዲሰ አበባ ከተማ የሚኖረው የአባዲ ዘሞ ልጅ- የመዘክር አባዲ ያስነበብኩዋችሁ ጽሑፍ እና ንግግር አስታውሱ)። ፈረንጆች እንደሚሉት ፖለቲካቸው ካላስተካከሉት <<ጋርቤጅ ኢን ጋርቤጅ አውት garbage in
garbage out>> (ውሃ ቅዳ ውሃ መልስ) ዓይነት ነው።
ስለሆነም ነው
ይህ የወያኔ ጡት እየጠባ ያደገ የወያኔ ሎሌ እራሱን ለማዳን ስንጥርና ስንታገልለት እጅግ ከባድ የሆነብን።
ይህ ትግራይ መቀሌ ውስጥ የተተከለው የነ መለስ ዜናዊ ሐውልት
መታሰቢያነቱ <<ኢትዮጵያዊ ወንድማማችነትን የሚያስታውስ>> ሳይሆን በጣሊያን እና በትግዎች መካከል
የተካሄደ ጦርነተና የቆመ መታሰቢያ ሆኖ የተመሰለ ተምሳሌት ነው። ይህንን የናዚ ፋሺቶችና ወንጅለኞች ሃውልት እንደ ቤተ ጸሎት ሰጊድ ሰላም የሚሰግዱ በርካታ “የድርጅቱ ካልቶች” እያየን ነው። የተለጠፈው ቪዲዮ የሚያሳየን መረጃም ይህ ነው።
ሃውልት ይኑር ከተባለም
<በወያኔዎች ግፍ የተገደሉና ደብዛቸው የጠፋ>> የሚል ሃውልት እና ሚዚየም በየገጠሩ እና
በመቀሌ
ውስጥ ይቁም። ሃውልቱ ማጠቃለል ያለበት ለኢትዮጵያ ሕዝብ መብት የተዋደቁ የባሕር ወደቦችን ለማስከበር ኤርትራ ሳሕል
ተራሮች ላይ መስዋዕት ለከፈሉ በወያኔ ታጋዮች የተገደሉ ጀግኖች እና በመለስ ዜናዊና በትሕነግ አመራር አባሎችና የድርጅቱ “ሓለዋ ወያነ እና ክርቢት በተባለው የገዳይና አሸባሪ ቡድን አባላት” ምክንያት በየገጠሩና በየከተማው በግፍ ለተገደሉ ንብረታቸው የተነጠቁ ፥ ደብዛቸው ለጠፋ ወጣት የትግራይ ታጋዮችም ሆኑ
ድርጅቱን የተቃወሙ አረጋውያን እና ወጣት ምሁራን የትግራይ ተወላጆች፤
እንዲሁም በወያኔዎች ግፍ የተማረረው የኢትዮጵያ ሕዝብ “ሳንፈልጋቸው 27 አመታቸው!” ብሎ የተፋቸው ሥልጣን ላይ በቆየባቸው 27 አመት
ውስጥ በኢትዮጵያውያን ላይ በወያኔ የደህንነት አባላት የተሰወሩ፤ አሰቃቂ ድብደባ ፤ ግድያና ጭፍጨፋ ለተፈጸመባቸው ኢትዮጵያውያን
ጭምር ከወያኔ ሃውልት ጎን ለጎን ሌላ ሃውልት ይቁም።
ስለዚህም ነው ሃውልታቸው “ፀረ መብት፤ ፀረ አምሐራና ፀረ
ኢትዮጵያ ትግላቸው” መልሶ መላልሶ የሚያስታውሰን፤ ለሃገር አንድነት ያልቆሙ ፤ <<ተጋዳላይ ትግራይ አርኪብካ በሎ ነቲ ዓሻ አምሓራይ>>
የሚለው ፤ ጭፈራቸውና መራራ ጥላቻቸው ወደ ትውስታችን አምጥቶ ለኛ ለኢትዮጵያዊያን ዳግም የውስጥ ምሬትና ቁጭት ስለሚቀሰቅስ እርስ
በርስ ዳግም ጸብ ላለመቀስቀስ መፍረስ አለበት። በዚህ አንደ አመት
ውስጥ ወያነ የተቃወሙ ወጣቶች እየመጡ ነው ከተባለ ይህንን ፈተና ማለፍ አለባቸው።
አመሰግናለሁ
ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay)