Monday, December 31, 2018

የቀድሞ የ ኢንሳ ሓላፊ ወያኔው ተ/ብርሃን ወ/አረጋይ አጋአዚያንን በማጠናከር የተቀመጠበት ስብሰባ የፎቶ ማሕደር ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያን ሰማይ)


የቀድሞ  የ ኢንሳ ሓላፊ ወያኔው ተ/ብርሃን ወ/አረጋይ አጋአዚያንን በማጠናከር የተቀመጠበት ስብሰባ የፎቶ ማሕደር
ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያን ሰማይ)

በዚህ የፎቶ ትንተና ዝርዝር ዘገባ እየሰራሁኝ ስለሆነ ለጊዜው ጠብቁኝ እና ፎቶግራፎቹን ብቻ ለዛሬ አቅርብላችሗለሁ። ለaan media ምሳጋና አቀርባለሁ።




ስብሰባው የተካሄደው መቀሌ ውስጥ ሲሆን ከግራ በኩል የታዩት አንዳንዱን በፎቶግራፍ የሚታዩት፤-የፋሺሰት ወያኔ መንግሥት የኢንሳ ሓላፊ የነበረው ተ/ብርሃን ወ/አረጋይ፤በጸረ አማራነት የሚታወቀው የትግሬዎች ፋሺሰት ንቅናቄ አስተማሪው ሽማግሌው መምሕር ገ/ኪዳን ደስታ፤ እመሃል ፊት ለፊት የተቀመጠው ደግሞ የሆርን አፈይርስ ኦን ላይን ማገዚን አዘጋጅ ትግርኛ ቋንቋ የማይናገር አዲስ አበባ ያደገው ወያኔው ዳንኤል ብርሃኔ እና የመሳሰሉ ወያኔዎች ሲሆኑ፤-

ወደ ቀኝ በኩል የሚገኙት ድግሞ በእንግሊዝ አገር የሚኖር የዋናው የአጋአዚያን ክፍል መሪው እዮብ በርሔ (ቅጽል ስሙ ተስፋጽዮን በማለት ራሱን የሚጠራ) ነው። ይህ ሰው በመላ ዓለም የሚገኙ እንዲሁም በዋናነት ደግሞ  እስራል አገር እና በመሳሰሉ አገሮች ውስጥ የሚገኙ በጸረ እስልምና እና በጸረ አማራ የተደራጁ ኤርትራኖች እና ትግሬ ክርስትያነችን ይመራል። ድርጅቱ የእስራሎች ማሕተም በማዳበል የቤተክርሰትያን አናት ላይ የሚተከል የአክሱም ጽዮን መስቀል ቅርንጫፎች ምስል ያለበት ነጭ እና ቀይ አንዲሁም ሰማያዊ ቀለም የተሰመረበት የራሳቸውን የአጋዚ ባንዴረ እና ማሕትም አዘጋጅተው የሚንቀሳቀሱ የኤርትራ እና የትግራይ ክርስትያን ትግርኛ ተናጋሪ ማሕበረሰቦች (ትግራይ ትግርኚ) ንቅናቄ ቅርንጫፎችን ይመራል። እንግሊዝ አገር በሌብነት ተይዞ ነበር የሚባልለት እዮብ ገብረስላሴ በቅጽል ስሙ “ተስፋጽዮን” በሚል በየ ዩቱብ ላይ ማድመጥ ትችላላችሁ። ይህ የአጋዚያኖች ሙላሕ የትግራይ ትግርኚ የታሊባን ሕሊና ርዕዮት በማካሄድ “የራሱ ካልቶችን” በማደራጀት ጸረ እስላም እና ጸረ አማራ አክራሪ ሃይላትን በብዛት በመመልመል የሚገኝ አደገኛ ሰው ነው።

አብረውት በቀኝ በኩል በመደዳ የተቀመጡት ደግሞ ከውጭ አብረውት የመጡት እና ከውስጥ ትግራይ ውስጥ የሚገኙ ጸረ  አማራ እና ጸረ እስላም አክራሪ የአጋዚ አባሎች እና አመራሮች ናቸው። ስብሰባው የተካሄደው ያው ወያኔዎች በመደቡላቸው ባጀት እና መስተንግዶ ትግራይ ውስጥ ነው የተካሄደው። ሰፊውን ዘገባ እየሰራሁበት ስለሆነ ዘገባው ሲጠናቀቅ አቀርብላችሗላሁ። በስብሰባው ውስጥ ሰብ ሕድሪ የተባለ ትግራይ ውስጥ የሚንቀሳቀስ  “ፋሽስት ንቅናቄ” ሕጋዊ እና በዓለም ውስጥም ተገቢ ሥድራውን እየያዘ የሚገኝ ማደግ ያለበት እንቅስቃሴ ነው ብሎ በግልጽ  የሚሰብክ እጅግ አክራሪ ወጣት ክፍል ያቀፈ አማራን ለማጥፋት እና ኢትዮጵያን ለመበተን በግሃድ በአውራምባ ታይምስ ዩቱብ ሚዲያ መልእክቱን የሚያሰራጨው አደገኛ አክራሪ ድርጅትም አለበት።

አስቀድሜ አንደገለጽኩት ደጋግሜ ካሁን በፊት የሰጡሁት ሰነድ ስለሆነ ያንን ያልተመለከታችሁ ካላችሁ ዛሬም በድጋሚ ማስረጃውን ለማየት አጋዚያን ማለት በወያኔ ማኒፌስቶ መሰረት ወደ አክሱም ተሰድደው የመጡ ከዓረብ ዓለም የፈለሱ የዓረብ ዘሮች ማለት ሲሆን ወያኔ የፈለፈላቸው የዛሬዎቹ ወያኔ ጫጩቶች ደገግሞ ፤አጋዚያን’ ማለት “ትግርኛ ቋንቋ የሚናገሩ ኤርትራ እና ትግራይ ውስጥ የሚገኙ ትግርኛ ተናጋሪ እስላሞች ሳይጨምር ትግርኛ የሚናገሩ ክርስትያን ትግሬዎች አጋዚያን ይባላሉ” የሚል ትርጉም ይሰጡታል።

ስለሆነም በወያኔ ማኒሰፌስቶ ሜይ 1983 ኣጋዚአን እነማን መሆናቸው ሲነግረን እንዲህ ይላል

     “The people of Tigray have a rich history of thousands of years. In the past, they were Known by various names such as Axumites, Habeshas, etc. Before 1000 BC, present day Tigray was inhabited by Nilotic and Hametic peoples of African origin, who led a primitive communual life…..the tribes of South Arabian origin known as the Sabean, Agazeans, Habeshats, and Himyarites began to cross the Red Sea and settle in the areas which are todayTigray and Eritrea. These tribes were at a more advanced stage of development than the indigenous people. / People’s Democratic programm of TPLF, May 1983) “

የአዶሊሱ ንጉሥ በሃውልቱ ላይ ጽፎ የተወው ጽሑፍ ደግሞ አጋዚአን  የመሳሰሉትን በውግያ አስገብሮ እንደያዛቸው ይናገራል። እነዚህ አጋዚአያን የሚባሉ በወያኔ ማኒፌስቶ እና በአዱሊሱ የንጉሱ ሃውልት የተጠቀሱት ናቸው።  የዛሬ ትግሬዎች ማንነታቸው ፍለጋ ወደ ላ በመሄድ እራሳቸውን ወደ ጭለማ ዓለም በማስገባት የሕሊና ቀውስ ውስጥ በመሄድ ‘የፋሺት’ ንቅናቄ በማካሄድ ተንሰተው የምናያቸው ምክንያት በማንነታቸው ውስጥ የሚረብሻቸው የበታችነት ስሜት ወይንም የሚረብሻቸው “የበላይነት ፍላጋ” ወደ ላው ወደ ጭለማው ዓለም የሚያስገሰግሳቸው አንዳች ነገር እንዳለ አመላካች ነው። ፋሺስቶች በዚህ በጣም የታወቁ ናቸው። ወደ ላ ቁፋሮ በመሄድ ያልሆኑትን ለመሆን የሚጥሩ የበላይነት ነበራችሁ እንዲባሉ ከውስጥ ስሜት የሚጋፈጣቸው አንዳች ነገር ለማምለጥ ሲሉ የማይፈነቅሉት የታሪክ መረጃ የለም።  ስለ የወያኔ አጋዚያን በሚቀጥለው ሳምንት ስለምንመለስበት እዚህ ላቁም እና ስለ ሌሎቹ የወያኔ ጫጩቶች አንድ ልበል እና ልደምድም።

ብዙ ሰዎች ዓረና ስለተባለ የወያኔ ጫጩት ያልገባቸው ነገር ስላለ አንድ ነገር ልበል።

ከዚህ አያይዤ ልገልጽ የምፈልገው ዓረና እንዲህ አለ ወያኔን ተጋፈጠ ወዘተ…..እያላችሁ እራሳችሁ የምታታልሉ የሚዲያ አውታሮች ዓረናን ከማቆላመጥ ታቀቡ። ዓረና ማለት ብዙ ህይወት ያጠፉ የወያኔ አንጋፋ መሪዎች የነበሩ አሁን ከዚህ ድረጅት ውስጥ ያሉበት፤ በዘመነ ወያኔ ተወልደው አድገው በወያኔ ሕሊና አስተሳሰብ የታጠቡ ወያኔ በዕንቁላልነታቸው ቀፍቅፎ ያሳደጋቸው የወያኔ ጫጩቶች ናቸው። ይህንን ካለመናችሁ ከመሪያቸው አብርሃ ደስታ ጀምሮ የሚሉትን መፈተሽ አለባችሁ።

አብርሃ ደስታ፡
“ከመለስ ዜናዊ ይልቅ ለኔ ጠላቴ ምኒሊክ ነው”።

ስለተፈላጊ የወያኔ ወንጀለኞችም ሲናገር እንዲህ ይላል፦

በትግርኛ
አሕሊፍና አይክንህቦምን፤ ክገዝኡና ግን አይክነፍቅደሎምን! 

አማርኛ ትርጉም

 አሳልፈን አንሰጣቸውም  ሊገዙን ግን አንፈቅድላቸውም (አብርሃ ደስታ በፌስ ቡክ ያስተላለፈው የህወሓት ወገንተኛነቱን ጋሃድ ሲያደርግ)።
      
ኪዳነ አመነ (የዓረና ሥራ አስፈጻሚ አባል) -

 ይህ ወጣት ከተፈለፈሉት ታዳጊ የወያኔ ጫጩቶች አንዱ ነው። በትግራይ ግራ አክራሪ ፋሺስዝም ቅኝትም የተቀኘ ወጣት ለመሆኑ አትጠራጠሩ።

 እንዲህ ይላል፤-

“…በፖቲካ ካልኩለሽን (ቅመራ ማለቱ ነው) ሰለክቲቭሊ (ያነጣጠረ ሴራ ማለቱ ነው) ደክዩመንትሪ ፊልም (የፊልም ዘገባ ማለቱ ነው) በትግራይ ሕዝብ ላይ ተሰርቷል። ይህም ከሁለት ብሔር የተመረጡ ከአማራ ክልል እና ከኦሮሞ ክልል ታሳሪዎች ‘ትግርኛ ተናጋሪው እንደዚህ አደረገኝ እንዲሉ ተደረገ” ነው።”

በመቀጠል እንዲህ ይላል   በፊልም ዘገባ የታዩ ስቃይ ደርሶብናል ባዮቹ አጥፊውን ማለትም የኢሕአዴግ ሥርዓት እንደዘህ አደረገኝ፤ ማለት ሲገባቸው፤ አንደዚያ ማለት ካልቻሉም ህወሓት ነው እንዲህ ያደረገኝ፤ ከህወሓት ውስጥም እገሌ የተባለ ሰው ነው አንዲህ ያደረገኝ ማለት ሲገባቸው፤ “ትግርኛ ተናጋሪ ነው አንዲህ ያደረገኝ   እንዲሉ ተደረገዋል። የዓረና አባላት ከነዚህ በላይ ግፍ የደረሰባቸው አሉ። “

 በማለት እጅግ ነውረኛ የሆነ እንዲሉ ተደርጓል” የሚለው ዓይን ያፈጠጠ የውሸት ውንጀላ እና አሳባቂ ምስክርነቱን አስደምጦናል። ያለ ማፈር ደግሞ ግብረሰዶም የተፈጸመባቸው እና ጎሳቸው እየተነሳ ሽንት በላያቸው ላይ የሚሸናባቸው፤ ወንድ እስረኞችም ሆኑ ሴት እስረኞች፤ ሌላ ቀርቶ “በድብዳባ የተሰቃየ ባለው እስረኛ ፊት ላይ ቀመው ልብሳቸውን አውልቀው እራቁታቸው የሚሻፍዱና የሚያንቋልጡ” ነውረኛ ሴት መርማሪዎች በዓረና ታሳሪዎች ተፈጽሟል የሚል ከሆነ ማስረጃው አላሳየንም። ኪዳነ አመነ የዓረና አባላት ከነዚህ በላይ (አርሱ ትግራይ ሕዝብ ለመወንጀል “ትግርኛ ተናጋሪ ነው አንዲህ ያደረገኝ   እንዲሉ ተደረገዋል።  የሚላቸው የአማራ እና የኦሮሞ ታሳሪዎችን (ትግርኛ ተናጋሪ ነው በሉ ተብለው ተመርተው/ተሰብከው ነው) እያለ እየወነጀላቸው ያለው ግፍ የተፈጸመባቸው ዜጎቻችን) ዓረናዎች ከዚህ በላይ የበለጠ ግፍ ተፈጽሞባቸዋል የሚል ከሆነ ማስረጃውን ለማውጣት ማን ከለከለው። ዩ-ትዩብ- እና ፌስ ቡክ ሚዲያው ክፍት ነው!! አደለም እንዴ?

የሚገርመው ደግሞ “አብይ  አሕመድ ጸረ ትግሬ ነው”፤የአማራ ሚዲያ ጋዜጠኖች ጸረ ትግሬ ናቸው” ሲል ይወነጅላቸዋል። ለዚህ ነው ዓረና ማለት ወያኔ የቀፈቀፋቸው የወያኔ ጫጩቶች ናቸው የምላችሁ።  

አብርሃም አስራት፡
ይህ ደግሞ አንድነት ፓርቲ ምናምን እያለ ሲሸውዳችሁ የነበረ ነው። እልም ያለ ጸረ ምኒሊክ ነው። መ ኢ አ ድ ን የሚኒሊክ ናፋቂዎች ይላቸዋል። በላፈው ኤል ቲ ቪ በተባለ ከኪዳነ አመነ (ዓረና) አረጋዊ በርሔ፤ አበበ ተ/ሃይማኖት እና እርሱ ለውይይት ተጋብዘው በነበሩበት ወቅት እንዲህ ይላል፡-

“የድምበር እና የማንነት ኮሚሽን” ጸረ ሕገ መንግሥት ነው፡ ሕገ መንግሥቱን ይጻረራል። ሕገ መንግሥቱ መከበር አለበት” ይላል።እንግዲህ የታያችሁ - ሕገ መንግሥት እያለ ያለው ፋሺሰቶች የመሰረቱት የአፓርታይድ ሕገ መንገሥትን ነው። ይህ ሕገ መንግሥት ለ27 አመት እልቂት አምጠቶብናል ብሎ ሕዝቡ እንዳልጮኸ ሁሉ አብርሃም አስራት ሕገ መንግሥት ተጥሷል ይላል። ወያኔዎች እና ጸረ አማራው ወንጀለኛው ኦነግ ያረቀቀው ሕገ መንግሥትን ነው “ይከበር” እያለን ያለው። ሕገ መንግሥት ይከበር የሚሉት ደግሞ አስገራሚው “ትግሬዎች እና ኦነጎች ብቻ ናቸው/በብዛት”።  ‘አማራዎችም ሆኑ “ዜጎች” (ብሄር፤ብሔረሰቦች ሕዝቦች የሚለባሉትን አላልኩም) ሕገ መንግሥቱ አያውቃቸውም። አይወክላቸውም፤ሲፀድቅ አልነበሩም፤አልተጠየቁም። ብሔር የለኝም ለሚል ዜጋ መብቱ የት አንደሚሆን አይታወቅም።

አብርሃም አስራት የሚባለው ጉደኛ ነው፦ይህ ብቻ እንዳይመስላችሁ- ባለፉት ወራት ወያኔ ባዘጋጀው የትግራይ ምሁራን ሰሚናር፤ “ትግራይን ለማስገንጠል እንዲመቻቸው” ትግራይን ማእከል ያደረገ ትኩረት አድርገን ምጣኔ ሃብታችንን እንዴት ወደ ትግራይ አምጥተን ማሳደግ ይቻላል የሚል ስብሰባ ሲደረግ አብርሃም አስራት የሰጠው አስተያየት “አዲስ አበባ ብዙ በትግራይ ማሕበረሰቦች የተገነቡ በሚሊዮኖች የመያወጡ ፎቆች እና የንግድ ተቁዋሞች አሉ። እነሱን ከዚያ አስመጥተን እዚህ ትግራይ ውስጥ በመትከል ትግራይ እራስዋን እንድትችል ማድረግ ይቻላል”። ይላል። ኢትዮጵያ ሰላም የለም ትግራይ ሰላም አለ፤ ስለዚህ ባለ ሃብቶቹ ሃብታቸው ይዘው ወደ ትግራይ ይምጡ” ሲል ተናገሯል። ይህ የትግራይ ትግርኚ ምስረታ አንዱ ምክር ነው።

 ከአውሮጳ የመጣው ጉዑሽ በርሄ የተባለ ሪሰርቸር ነኝ ባይ ለትግራይ አማራጭ (አንቀጽ 39 ለመጠቀም እንዲያስችል ለተሰብሳቢው ትምሕርት ሲሰጥ) እንደገለጸው “ትግራይ በምጣኔ ሃብት ትኩረታችን ካደረግን የቅርብ ክልሎች/አማራውን ሸቃይ በማድረግ/ወደ ትግራይ ኢንዳስትሪ ሥራ ፈላጊ/ በማድረግም ይሁን ሌሎች የትግራይ ቅርብ ጎረቤቶች የምጣኔ ምንጭ አከፋፋይ እንድንሆን፤ራሳችን እንድንችል ምሁራን ሃሳባችሁ ለግሱ ባለው መንገድ ነው “አብርሃም አስራትም” በህወሓት የቲ/ቪ ክፍለጊዜ ቃለመጠይቅ ሲደረግለትም ትግራይን የአፍሪቃ “ታይገር” እንዴት አንደሚቻል ሃሳብ የሰነዘረው።

ስለዚህ የትግራይ ኤሊቶች አጅግ በጣም በጣት የሚቆጠሩ ከተገኙ እንጂ ብዙዎቹ ከብሔረተኛነት ጭቃ ያልወጡ፤ከተረገረጉበት አሳፋሪ ታሪክ ለመውጣት የማይሹ ‘ታጥቦ ጭቃዎች” ስለሆኑ ተስፋችሁን ቁረጡ።

 ትግሬዎች ወያኔን መታገል አይፈልጉም ብለን ብዙ ጊዜ ተናግረናል። ወያኔ በትግራይ ልሂቃን የታቀፈ ፋሺሰት ነው፤ ስለሆነም ትግራይ ውስጥ ከባድ ጦርነት አስነስተው የትግራይ ሕዝብ ወደ እሳት ሊማግዱት ተዘጋጅተዋል ብለን ለበርካታ አመታት ተናግረናል። ይኸው እነ ተኽለብርሃን ፥ እነ ሙሉወርቅ ፥ እነ መሓሪ ዮሀንስ (የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ መምህር ነው፦ ይህ ወጣት ሳየው ጣሊያናዊው ወጣት ሙሶሎኒ ተመስሎ ይታየኛል። ባካባቢው ድንገት በታአምር ጤነኛ ፖለቲከኞች   ካሉ  ከወዲሁ እልባት ካልተደረገለት ወጣቱ  ያልተራ ወጣት ከመሆኑ የተነሳ ለሰው ልጆች ሕልውና እጅግ አስፈሪ እና “ለትግራይ እና ለአካባቢው ምናልባትም ለኢትዮጵያ በጣም አደገኛ አክራሪ ሊሆን የሚችል ወጣት ነው ብየ ስጋቴ ከወዲሁ ለማስተላለፍ እፈልጋለሁ)። ከነዚህ ግለሰቦች በተጨማሪ እነ ደብረጽዮን እነ ስብሓት ነጋ እነ ገብረኪዳን ደስታ ትግራይ ትግርኚን ለመመስረት ተነስተዋል። በዚህ ሽፋን ብዙ የወያኔ ወንጀለኞች የወንጀላቸው መደበቂያ ሰበብ እየፈለጉ ነው ማለት ነው።

ለበርካታ አመታት ስነግራችሁ አናምንህም ብላችሁ “የትግራይ ሕዝብ የትግራይ ሕዝብ አይገነጠልም ስትሉ” ሕዝብ የሚባለው ማነው? ብለን ስንጠይቅ ገበሬው ትላላችሁ፡ ገበሬው በታሪክ ወሳኝ ሆኖም አያውቅም “ሊሂቁ” ነው ስንልም አትሰሙም። ሕዝብ ወሳኝ ሆኖ ከነበረ ከዛሬ የበለጠ ወያኔን ለመጣል  አመች ወቅት የት ሊገኝ ነው? መላው አገሪቱ ወያኔን በተቃወመበት ወቅት ዛሬ ድጋፍ እያላቸው ካልተነሱ መቸ ሊነሱ ብላችሁ ልትነግሩኝ ትችላላችሁ?!!!!!!!!!!! ሕዝብ ለምትሉት ክፍል የምሰጋለት ነገር ቢኖር ካሁኑኑ የሚሻውን ጠነኛ መንገድ ካልፈለገ “ከዶፍ ዝናብ በኋላ ከለላ ፍለጋ እንዳይሆን ግን እሰጋለሁ”።
አበቃሁ
ጌታቸው ረዳ (ኢትዮ ሰማይ)



Tuesday, December 25, 2018


ሰሞኑን ከተሰሙ አስገራሚ ንግግሮች እና ዜናዎች
ኢትዮጵያን ሰማይ

ሰሞን የአማራ ራዲዮ ድምፅ ዋና አዘጋጅ እና በላስቬገስ ዩኒቨርሲቲ መምህር የጋዜጠኛነት ሙያ አስተማሪ የነበረው የወንድማችን ጋዜጠኛ ደምስ በለጠ ድንገተኛ ሞት መራራ ሓዘኑን ለቤተሰቡ እና ለሥራ ባልደረቦቹ የኢትዮጵያን ሰማይ ድረገጽ የሓዘን መግለጫ ማውጣቱ  ይታወሳል። ለጋዜጠኛው መሞት ምክንያት እየተጣራ ቢሆንም አንዳንድ በሙያው ስልጠና የወሰዱ ባለሞያዎች አስተያየት አሟሟቱ ብዙ ፍተሻ እንደሚያስፈልገው ለዚህ ድረገጽ አዘጋጅ ጥርጣሬአቸውን ገልጸዋል።

ወደ ሌሎቹ ዜናዎች ስንሻገር የሚከተሉት ለጀሮ የሚስቡ  አጫጭር ዜናዎችን እንመልከት።

የኢሳቱ ጋዜጠኛ ሲሳይ አገና

የኢሳቱ ጋዜጠኛ ሲሳይ አገና “ዕለታዊ” በተባለው የቴ/ቪዢኑ ክፍለ ጊዜ በDec/24/2018  የሚከተለው “እስቱፒዲቲ” (የአማርኛ ቃል ፈልጌ ስላጣሁ ነው) አባባሉ እኔንም ሆነ አብረውት በውይይቱ የተካፈሉ ባልደረቦቹ “ቅንድባቸውን” ያስቆመ አግራሞት የሚጭር አባባል እንዲህ ይላል፡-

“በመንግሥት በኩል መደረግ አለበት ብየ የማምነው እኔ ማንም ድርጅት የተጋደለለትን  ዓላማ ለኢትዮጵያ ነው “ለሰፈሩ” ነው (ኢትዮጵያን ለማፍረስ ለግንጠላ ነው…የሚለውን ጭምር- በዚህ ጸሐፊ ለማብራራት የተጨመረ ማብራሪያ) እንተወው ፤ ግን ለምን ይሁን ለምን “ለመብት፤ለነፃነት” ብለው ሲታገሉ ዕድሜአቸውን ሙሉ “በረሃ ውስጥ ለተንከራተቱ” በተለያዩ ትግል የቆዩ፤ እጅ ላልሰጡ ሰዎች ተገቢውን ክብር የሚሰጥበት ቢኖር ብየ በግሌ አምናለሁ። የኦነግ መሪዎች የታንድ መሪዎች የኢሕአፓ መሪዎች የመኢሶን መሪዎች ..እንዲህ እያልን የቀድሞ ታጋዮች 70ዎቹ 80ዎቹ ዕድሜ ክልል ገብተው ከመከራ ኑሮ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ በምን ሁኔታ ነው የሚኖሩት? …እነዚህ ሰዎች ለአገራቸው አስተዋጽኦ ሲያደርጉ የነበሩ ሰዎች ናቸው እና በመንግሥት በኩል እንዲህ ያለ ክፍተት ቢያይ ለኔ ጥሩ ይመስለኛል።” (ሲሳይ አገና ዕለታዊ ከተባለ የትንተና ክፍለ ጊዜ በDec/24/2018 ከተናገረው ያደመጥኩት የተወሰደ)።

እንዲህ ያለ በኮሚዩኒዝም፤ በናዚፊኬሽን እና በፋሺዝም ርዕዮት አስጠምቀው የኢትዮጵያን ባሕል፥ ቋንቋ፥ ሃይማኖት፥ መተሳሰብን እና ታሪክ “አመድ ዱቀት አድርገው” ኢትዮጵያን አንደ ባዕድ የቅኝ ገዢ ስለው/አስተምረው፤ የኢትዮጵያን ሕዝብ በነዚህ በተጠቀሱት ርዕዮት አስጠምቀው አታልለው ዋሽተው ፥ አሳስተው አስተምረው ሕዝባችን እርስ በርሱ እንዲባላ አድርገው በጠቅላላ ለዚህ ለዚህ ሁሉ መከራ የዳረጉን በአገራዊ ክሕደት እና በወንጀል ተግባር በሕግ ሊጠየቁ የሚገባ ሰዎች ናቸው ብሎ ወደ ሕግ እንዲቀርቡ ከመስበክ ይልቅ ከነዚህ መሪዎች ውስጥ በዘር ማጥፋት የሚጠየቁ ነብሰ ገዳዮች እና በአገር ክሕደት ሊጠየቁ የሚገባቸውን ሰዎች “ክብር እንዲያገኙ” ስለ “ኑሮአቸው ሲጨነቅ” የሰሙት እጅግ አስገራሚ ስብከቱን ያደመጡት ባልደረቦችም ገርሞአቸው “መልሰው እንዴት?! ብለው ይጠይቀውታል።

ገርሞአቸው ሲጠይቁት የባሰውኑ ሓሳቡን አጠናክሮ እንዲህ ሲል መልሶላቸዋል፦

”ዓላማቸው “ለአገር ይሁን ለመንደር” አንድ በጎ ነገራቸው ምንድነው ፤ በሕዝብ ላይ ‘የመብት የነፃነት” የሚደርሰው መከራ አንቀበልም ብለው የግል ምቾትም ቢሆን እነዚህ ሰዎች ከሌላውም (ደርግም) ከቲ ፒ ኤል ኤፍም ሥልጣን ተደራድረው የኖሩ አይደሉም……..” ሲል ከአፈርኩ አይመልስኝ በሚል “ገታራ መልስ” ይመስላል “ለሕዝብ የቆሙ የነፃነት እና የመብት ተሟጋቾች ስለነበሩ እንክብካቤ እንደሚያስፈልጋቸው ተከራክሯል። ባልደረቦቹም በዚህ ሊወጥሩት ይሁን አይሁን ባላውቅም መልስ ሊሰጡ ሲሉ የውይይቱ ክ/ጊዜ ስላለቀ በዚህ ቆመ።

እነ ሲሳይ አገና እንዲህ ያለ ስብከት እየሰበኩ ኦነጎችን እና ወዘተ ….ለኢትዮጵያ ሕዝብ “የነፃነትና የመብት ታጋዮች” ነበሩ ብለው ሲያስተምሩ የፍትሕ ጉዳይ እንዳይነሳ ቦታ ላይሰጠው በአገራችን ሉኣላዊ ነፃነት እና በሕዝብ እና በግለሰብ ህይወት ላይ ሰቆቃ እና የዘር ማጥፋት የፈጸሙ ሲሳይ የጠቀሳቸው ለድርጅት መሪዎች ኑሮ ሲጨነቅ ማድመጥ “ፍትሕ” በኢትዮጵያ ለምን እየተረገጠ እንደመጣ ወይንም ለወደፊቱ ፍትሕ መብት የሚባል ከሕግ አንጻር ቦታ እና ከነጭራሹ የፍትሕ ማስከበር ጠቀሜታ ቦታ እንደማይኖረው የዚህ ጋዜጠኛ ስብከት አመላካች ነው ብየ እከራከራለሁ።

የድርጅት መሪዎች ተጠያቂነት እንዳይኖር ‘ልሂቃን/ኢሊቶች/ እና ጋዜጠኞች ብዙዎቹ በቀጥታም በተዘዋዋሪም አስበውም ይሁን ሳያስቡት ሽፋን በመስጠት ሚና እንደነበራቸው ለ27 አመት ስሟገትብት የነበረ ጉዳይ መሆኑን አንባቢዎቼ የምታስታውሱት ጉዳይ ነው። ይህ ባህሪ ዛሬም ይህንኑ እየተደገመ ነው።

አስገራሚ፡የሚያደርገው ደግሞ ሲሳይ አገና ለዘላቂ ኑሮአቸው ይታሰብበት ሲል ለመንግሥት ቢማጸንም ሲሳይ ከመማጸኑ በፊት አብይ አሕመድ ለነዚህ ድርጅት መሪዎች በግብር ከፋዩ የተሰበሰበውን የድሃ ሕዝብ ገንዘብ “ለሆቴል፥ ለምግብ ለመጓጓዣ ወጪ እና የተመቻቸ ጽ/ቤት” ከፍቶላቸውም ቢሆን ፡እዛው አዲስ አበባ ውስጥ ሆነው “ኢትዮጵያን ለማፍረስም ሆነ በሰው መግደል በዘረፋ እና በዘር ማጥፋት እየተሰማራ ያለው የጥላቻ ቁንጮ እና የብጥብጥ ድርጅት የሆነው “የኦነግን ሠራዊትን” እራሳችሁ ተከላከሉ” ወዘተ…..እያልኩ ትዕዛዝ አስተላልፌላቸዋለሁ” እያለ የጥላቻ መሪው ዳውድ ኢብሳ ትጥቅ ሳይፈታ “በሚገደለው ሕዝብ ገንዘብ” እንዲቀለብ የተደላደለ የጥላቻ ስነ ልብ እንዲያገኝ የሲሳይ አገና አወዳሹ “አብይ አሕመድ” የሚጨነቅላቸው መሆኑን በዚህ አጋጣሚ ለሲሳይ አገና መልዕክት ላስተላልፍለት እፈልጋለሁ።

ጋዜጠኞች እባካችሁ የዚህ ሕዝብ ሰቆቃ ፍትሕ እና ተጠያቂነት ኖሮ ጩኸቱ እንዲደመጥ በነዚህ ሰዎች  ትዕዛዝ እና በነዚህ ሰዎች በራሳቸው እጅ ጥይት የተረሸኑትን የሙታን ጩኸት እንዲደመጥ እና ፍትሕ አንዲሰራ ብትሰብኩ የተሻለ ነውና ፍትሕን እያጣጣላችሁ ስብከት ከመስበክ ጠንቀቅ በሉ። ወንጀለኞች ደጋግመው ሥልጣን ላይ እየወጡ “ፖለቲካውን እያደፈረሱት” አስቸግረውናል፡ ባንድ ቦታ ላይ እልባት ይኑሮው። ዕልባቱም ተይዘው የፍትሕ አለንጋ መቅመስ አለባቸው እንጂ ፍትሕ ከማየታቸው በፊት አስመራ ተቀምጦ “አኒቼ አረቂ’ ሲጋት የነበረ የጥላቻ መሪ ሁላ ከሃገሩ ወጥቶ አስመራ፥ የመን ፥ ሱዳን ግብፅ ሚኔሶታ ሲዊዲንጀርምን… እየኖረ ጥላቻ ግድያ እና አገራዊ ብተና ሲሰብክ የነበረ “አየማራ ነብስ ሲያጠፋ የነበረ ነብሰ ገዳይ ሁላ” “የነፃነት ታጋይ ነበሩ እያሉ ማሽሞነሞኑ” ይቁም። ጋዜጠኞች አፋችሁ ከፈሪሃ እግዚአብሔር ልጓም ጋር ይተዋወቅ!!! የሙታኖች ነብስ ጩኸት ሚዛ አንዲቀንስ የምታደርጉት ሃላፊነት የጎደለው “ፌዝ” ይቁም!!


ሦስተኛው ዜና፡
በትግራይ ፋሺዝም የተጠመቁ የትግራይ ታጋይ ሠራዊት የመራው የትግራይ ፋሺስት ብሔረተኛው ሌ/ጀኔራል ጻድቃን እና በድሮ የኢትዮጵያ ወታደራዊ ከፍተኛ የሠራዊት አዛዥ የነበሩት ሌ/ጄነራል ካሳየ ጨመዳ የተደረገ ውይት
ኤል ቲቪ በተባለ ቴ/ቪዥን ጣቢያ በድሮ የኢትዮጵያ ወታደር ውስጥ የሌ/ጄኔራል ማዕረግ የነበራቸው ሌ/ጄነራል ካሳየ ጨመዳ እና በወያኔው ሌ/ጄነራል በትግራይ ፋሺዝም የተጠመቁ የትግራይ ታጋይ ሠራዊት የመራው የትግራይ ፋሺስት ብሔረተኛው ሌ/ጀኔራል ጻድቃን ገብረተንሳይ እሱ እና የወያኔ ፋሺሰት አመራሮች የበተኑዋቸው በድሮ ወታደሮች ህይወት ላይ ውይይት ተደርጎ ያደመጥኩት ቃለ መጠይቅ/ውይይት/ ቅንድብ የሚያስቆም ሆኖ አግኝቼዋለሁ።

የድሮ ወታደሮች ተበትነው ለጎዳና ተዳዳሪነት ና  ህይወት መዳረጋቸው ስናስታውስ “በጀኔሳይድ/ በዘር ማጥፋት/” ስልት የተፈጸመ ወንጀል መሆኑ ለጥያቄ የሚቀርብ እንዳልሆነ ከኔ ጋር የምትስማሙ እንዳላችሁ አምናለሁ። ሆኖም የቃለ መጠይቁ አዘጋጅ “የፋሺሰት ብሔረተኛ ሠራዊት የመራው ጻድቃን ገ/ተንሳይ ለበተናቸው የድሮ የኢትዮጵያ ወታደሮች “ይቅርታ” መጠየቅ ያስፈልጋል የሚሉ ጠያቂዎች አሉ እርስዎ እንዴት ይመሳሉ ብሎ ጋዜጠኛው ሲጠይቀው “የደርግ ወታደር ለመበተኑ ይቅርታ መጠየቅ ዋናው ጉዳይ አይደለም!“ ይቅርታ አንጠይቅም ከማለቱ አልፎ “ዋና ጉዳይ አይደለም”  እርሱ እና የተቀሩት የፋሺሰት ጓዶቹ “የፈጸሙትን ወንጀል አጣጥሎታል”።


ቅር ያሰኘኝ ግን ጻድቃንን ወጥሮ ልይዝ የሚችል ተከራካሪ ባለመጋበዙ “ሌ/ጄነራል ካሳየ ጨመዳ”  ወንጀል በማጋለጡ በኩል ለስላሳ እና ጥልቀት በሌለው ችሎታቸው የቀረበው መልስ አልተደሰትኩም። ከካሳየ ጨመዳ ይልቅ የቴ/ቪዥን አዘጋጅ ጋዜጠኛው “እጅግ በሳላ እና በመረጃ የታጠቀ ወጣት ጋዜጠኛ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። ከካሳየ ጨመዳ ይልቅ ‘ሌላ ጥልቅ ተመጓች ሰው ቢጋበዝ በመርጥኩ ነበር።   

ሌላው ዜና፡ ስለ ኤርትራ ነው።

ከ7 ቀን በፊት ኤርትራ ውስጥ ስብሓት ኤፍሬም ተባለ የሻዕቢያ ጀኔራል በዲሰምበር 19 /2018 ዕሮብ በ11 ሰዓት ላይ ወደ ቤቱ ሲመለስ እቤቱ በራፍ አጠገብ ሲደርስ ማንነቱ ባልታወቀ በወቅቱ በቁጥጥር የዋለ ተኳሽ ‘በድምጽ ኣልባ ሽጉጥ’ ጭንቅላቱ ላይ ኩፉኛ ስለተመታ ‘ወዲ ምሕፁን’ በተባለ ኤርትራዊ ዶክተር ሸኚነት እና ተንከባካቢነት ለከፍተኛ ሕክምና ወደ ዱባይ ባስቸኳይ እንዲሄድ ተደርጓል።

የቶኩሶ መግደል ሙከራ ሲደረግ ‘ኣሌክስ’ የተባለ የስብሓት ኤፍሬም ልጅ አብሮት እንደነበር ተገልጿል። ስብሓት በጥይት ተመትቶ ሲወድቅ በአካባቢው የቤተሰብ እና የጎረቤቶች የድንጋጤ  የድረሱ ኡኡታ ተሰምቷል።

ለግድያው መነሾ ምክንያት ግንባር ሃገራዊ ድሕነት ኤርትራ “የኤርትራ ሃገራዊ ደህንነት” በመባል የሚታወቅ ተቃዋሚ ፓርቲ የሚከተለው ዜና በትግርኛ አሰራጭቶታል። ስብሓት ኤፈሬም እና ከታች የተዘረዘሩት ባለሥልጣኖች አብሮ በመመሳጠር በኢሳያስ አፈወርቂ ላይ የመፈንቅለ መንግሥት አከናውኖ ከባድሜ ጦርነት ሽንፈት በኋላ “ኢሳያስን ተቃውመው” እስር ላይ የሚገኙ G-15 በመባል የሚታወቁት ኤርትራውያኖችን እና መሰል እስረኞችን ለማስፈታት የታቀደ የመንግሥት ግልበጣ ሴራ በመጨረሻው ሰዓት ጓዶቹን ከድቶ ምስጢሩ ለኢሳያስ በማስተላለፉ አብረውት የዶሎቱት ጓዶቹ በማስያዙ ምስጢር በማውጣቱ የተደረገ የመግደል ሙከራ እንደሆነ ይገለጻል።

ዱሎታውን ያቀነባበሩ የሻዕቢያ ባለሠልጣኖች “ብርሃነ ሃይለ (ወዲ ውነሽ) ከፍተኛ ወታደራዊ  አዛዥ፣ ኮሎኔል ደረስ ገብረ ኣምላኽ የፋይናንስ ሓላፊ፡ ኮሎኔል ባንተ የራዲዮ መገናኛ ጠለፋ ከፍተኛ ባለሥልጣን ፣ እና ሌሎቹ የመሳሰሉት የመግደል ሙከራው ከመደረጉ በፊት ከሦስት ቀን በፊት ማለትም ዕሁድ በዲሴምበር 16ተለቃቅመው መታሰራቸው ተገልጿል። የመግደል ሙከራው የተደረገው በ19 ሲሆን በ16 ደግሞ ተለቃቅመው ታስረዋል።
አመሰግናለሁ!
ኢትዮጵያን ሰማይ getachre@aol.com



Sunday, December 23, 2018

የሓዘን መግለጫ ነብስ ይማር ታጋይ አርበኛ ደምስ በለጠ!! ኢትዮጵያን ሰማይ!


የሓዘን መግለጫ
ነብስ ይማር ታጋይ አርበኛ ደምስ በለጠ!!!
የዐማራ ድምፅ ራዲዮ ዋና አዘጋጅ ፤በላስቬገስ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኛ ሙያ መምህር የነበረው ታጋይ አርበኛ ጋዜጠኛ ፕሮፌሰር ደምስ በለጠ ለጉብኝት ወደ አገሩ ኢትዮጵያ በሄደ በ21ኛው ቀኑ በድንገተኛ ሞት በመቀጠፉ፤ የኢትዮጵያን ሰማይ አዘጋጅ ለቤተሰቦቹ እና አብረው ለሚሰሩት የሥራ ባልደረቦቹ ልባዊ ሓዘኑን ይገልጻል። ሰማዕት ደምስ በለጠ የምትወዳትና የታገልክላትን እናትህ እምየ ኢትዮጵያ በክቡር ማሕጸንዋ አቅፋ በገነት ውስጥ ታኑርህ!
ጌታቸው ረዳ (አሜሪካ) የኢትዮጵያን ሰማይ ድረገጽ አዘጋጅ።

Thursday, December 20, 2018

አብዮታዊዉ ሠራዊት መሣሪያ ይዞ ውሐና ምግብ እየለመነ ወደ እየቀየው ተመመ!!! (ከሻለቃ ላቀው መንግስቴ)


አብዮታዊዉ ሠራዊት መሣሪያ ይዞ ውሐና ምግብ እየለመነ ወደ እየቀየው ተመመ!!!

 (ከሻለቃ ላቀው መንግስቴ)

NotE from the editor;- (ኢትዮ ሰማይ)

ወደ ታሪኩ ከመግበታችን በፊት የዚህ ድረገጽ አዘጋጅ ይህንን መልዕክት ያስተላልፋል።
ታሪኩን ስታነቡ ስሜት ይነካል። ወያኔ በሃገር ክሕደት መከሰስ አለበት ብለን ስንወተውት የነበርነውም በኢትዮጵያ ወታደሮች እና የትግሬ ወታደሮች (የፋሺስት ወታደሮች) የተደረገው ጦርነት፤ በሉዓላዊ ሃገር ተከላካይ ወታደሮች እና በሃገር አፍራሽ ፋሺስት ትግሬ ተዋጊዎች ማሃል የታየው ልዩነት ነው።  የትግሬ ፋሺሰት ወታደራዊ ሃይል ካለ “የደቡብ፤የምስራቅ፤ የምዕራብ እና የመሃል አገር ሕዝብ” ትብብር ነበር “ኢትዮጵያን አሸንፈን መንግሥት ተቆጣጥረናል” ብለው እንደ በፊቱ ዛሬም ኢትዮጵያን አምበርክክን ሥልጣን እንደበፊቱ እንቆጣጠራለን” የሚሉ ከሆነ “ያው ፍጥጫው እየደለበ ስለሆነ” ጥንካሬአቸው በቅርቡ የምናየው ይሆናል።
እዚህ ላይ አንባቢዎች ልትገነዘቡት ምፈልገው “የትግሬ ፋሺስቶች እና የዓረብ ቡቹላው ሻዕቢያ” የኢትዮጵያን ሠራዊት አሸንፈው ሳይሆን ምስጢሩ በጣም በርካታ ቢሆንም አንደኛው ምስጢር ግን “የደርግ ኮሚኒሰት መንግሥት” አፍርሶ የአሜሪካን ቡቹላ “ካፒታሊስት-መንግሥት” (ወያኔ) ሥልጣን ላይ ለማውጣት ስለነበር፤- “ወሳኙ ጦርነት ከመጀመሩ በፊት በአሜሪካኖች የስለላ ሳተላይት ድጋፍ እንደሚያገኙ በተስማሙበት መሥረት ታግዘው ነበር አሸናፊነቱን የተጎናጸፉት (ሌሎቹን ምክንያቶችን ሳንዘረዝር)።
ሱዳን ካርቱም ከተማ ውስጥ በፕረዚዳንት ቡሽ ልኡካን እና ከወያኔም እነ ስየ አብርሃ እና የወያኔ አመራሮች እንዲሁም እነ ጴጥሮስ ሰለሞን..ከሻዕቢያ ስበሰባ አድርገው በተፈጸመው ‘ሴራ’ የተካሄደ ጦርነት እንደነበር ካሁን በፊት ማስረጃውን አቅርቤ በዚህ ድረገጽ እና በሌሎች ድረገፆች ለጥፌዋለሁ)። ዋናው ተልዕኮ  ኤርትራን እና የትግሬ ሪፑብሊክ ለመመሥረት እንደነበር የታቀደው ሴራ ዛሬ የትግሬ ፋሺስቶች ከሥልጣናቸው “ሙሉ ቁጥጥር” ባልጠበቁት ስልት ሲንሸራተቱ በማየታቸው ዛሬ እነሆ የትግል መነሻ ምክንያታቸውን እንደ ዱሮ ሳይሸሽጉ በግልጽ “የምታከብረንን የትግራይ ሪፑብሊክ አገር እንመሰርታለን” እያሉን ነው። ለማንኛውም አሳዛኙ ጦርነት ከዚህ ቀጥሎ ያለውን ያንብቡ እና ይህ ታሪክ ስታነቡ “በፋሺሰት ትግሬዎች” ላይ የምታሳድሩት የቁጣ ስሜት ገምቱት። እነሆ…….

አብዮታዊዉ ሠራዊት መሣሪያ ይዞ ውሐና ምግብ እየለመነ ወደ እየቀየው ተመመ!!!

 (ከሻለቃ ላቀው መንግስቴ)

12/14/2018

ባቄሎ የመጨረሻዋ ጠረዝ

ጓድ መንግሥቱ /ማሪያም ግንቦት 1983 አጋማሽ ላይ ሐገሪቱን የሕዝብ እልቂትነ ለማሥቆምና ለሐገር ደህንነት ሢባል ሐገሪቱን ለቀው እንዲሄዱ ተደርጓል የሚለው የዳሪዎሥ ሞዲ የሬዲዮ መግለጫ ደብረ ብርሀን ጠባሤ ካምፕ ውሥጥ ተሠብሥበን የነበርንውን ተሥፋ አጨለመ፡፡

ጀነራል ከበደ አርምዴ እንዲህ ይሆናሉ ብዬ ባልገመትኩት ሁኔታ፡አገሪቷንም ሕዝባችንንም የትም በትኖ ለአውሬ ጥሎን ሄደ፡፡ተሥፋችን ምንድን ነው፡፡ከጠረፍ እሥከጠረፍ የተዘረጋው ሠራዊት መጨረሻ ምን እንዲሆን አሥቦ በትኖን ሄደ፡፡የእውነት አነቡ፡፡ኮለኔል ግርማ ተካ ኮለኔል ዘርይሁን ፈረደ ሁሉም እምባዎቻቸው ይወርዳሉ፡፡ሁላችንም የቀረችንን የውጊያ ቀጠና ጣርማ በር፡ለሚ መዘዞን እሥከመጨረሻው ተናንቀን ከማ

ለፍ በቀር አማራጭ እንደሌለን ቃል ገብተን መሪ የሌላት አገር ወታደሮች መሆናችን እርግጥ ሆኖ በጀነራል ከበደ አርምዴ/605/ኮር አዛዥ ኮለነል ግርማ ተካ 605 ኮር ድርጅት መኮንን፡ሌኮ ዘርይሁን ፈረደ አሥተዳደር ሆነን ሽፍታ መሠል መሪ የሌለው ተዋጊ ሆነን ወደ ጣርማ በር አመራን፡፡በውጊያ የተመናመነው 6 ሜካናይዝድ ብርጌድን ለመጨረሻ እድል መሞከሪያ ተማምነንበት ልንዋጋ ወሥነናል፡፡ በለሚ ግንባር ሥጋቱ ወደ መሐል እየገፋ ሢመጣ ቤተመንግሥቱን ሢጠብቅ የነበረው ልዩ ጠባቂ ብርጌድ ሁኔታው ሁሉ ጨለማ ሆኖበት የማእከላዊዉ መንግሥት ከአናቱ መፍረሡ ግራ አጋብቶት ሞራሉን ቆፈን ቆፍኖት በፅልመት ተውጧል፡፡የሚበላ ምግብ መጣፈጡ አቁሟል፡፡

በሕዝብ መሐል ማእረግ ለብሦ መሄድ ሞት መሥሎ ታየ፡፡

ቁልፍ ቦታዎችን ለዋሥትና ይዞ ከወያኔ ጋር እንኳን ለመደራደር ወኔ የነበራቸው የመከላከያ ሐላፊዎች ለመኖራቸው አጠራጣሪ ድባብ ወረሠን፡፡ከሁሉም ግን የነበረን ምርጫ ጣርማ በርን ፋይላችን የሚዘጋባት፡የሠማእታት ደብራችን እንድትሆን ፈቅደን ነገር ፍለጋ በሚመሥል መልኩ ደብረ ብርሀንን ለቀን ጣርማ በር መሽግን፡፡የደብረ ሢና ሆቴል ባለቤት አቶ ተገኝ ምግብ እያመጣ ሊንከባከበን ሞከረ፡ መሠሪያም ይዞ አብሮን በቁጭት ተሠለፈ፡፡በነገራችን ላይ ይህን ሠው ወያነ ሥልጣን ከያዘ በሁዋላ ገድለው ጫካ ጥለውታል፡፡ውጊያው ቀጥሏል፡፡ወያነ ድሉን ያረጋገጠ በሚመሥል መልኩ በተኩሥ ጣርማ በር ላይ እያጫወተን በአምቦ መሥመር ጉዞውን እያሣመረ ነበር፡፡

ጣርማ በር መዘዞ የነበረ ጦር

ጦሩ ተሥፋው ተመናምኖ በራሡ ጊዜ የውጊያ ቀጠናውን እየለቀቀ ወደ መሐል አዲሥ አበባ መጓዝ ጀምሮአል፡፡ግንቦት 15 ይመሥለኛል እንደምንም ሥለባንዲራ ብለን እንዲቆም ያደረግንውን ጦር ጀነራል ረጋሣ ጂማ የሦሥተኛው አብዮታዊ ሠራዊት አዛዥ ባንዲራዋን በቀኝ እጃቸው ይዘው ሠራዊቱንልጆቼ በእዚህ እድሜዬ ፈርቼና ሸሽቼ ወደ ልጆቼና ሚሥቴ ልግባ፡፡ልጆቼ ዘመኔን በሙሉ ጦርነት ውሥጥ አሣልፌአለሁ በዚህ እድሜይ እናንተንና ይቺን ባንዲራ ይዤ ልፈር፡፡

አሟሟቴን አሣምሩልኝ ልጆቼ ጊዜ ይቀያየራል እኔም እናንተም ለዚህ ደረጃ በቅተናል ግን ታሪክ ሠርተን እንለፍ ብለው ተንበረከኩና በባንዲራው ፊታቸውን ሸፈኑና ሢነሡ የአባትነት እምባቸውን ከአይናቸው ፈነጠቁ”” የባንዲራችንን ሀይል በእውነት መገመት ያሥቸግራል፡፡ሠራዊቱ መፈክር እያሠማ ከርሥዎና ከባንዲራችን በፊት ብሎ መንፈሡ ወደ ነበረበት ተመልሦ ምሩኝ ልዋጋ አለ፡፡ውጊያው መሥዋእትነትን እየጠየቀ፡መንግሥትም የፖርቲ ሢቢል አባሎችንና የተለያዩ ታጣቂዎችን ከሠንዳፋ በመለሥ በኛ ግምባር አሠልፎአል፡፡ከሁዋላ በአምቦና በጅማ እቅጣጫ በናዝሬት መሥመርም ነገሮች ተበለሻሽተዋል፡፡

ሠራዊቱ የሚችለውን ሞክሮ ወደ መሐል ፍሠቱ ቀጥሏል፡፡የመጨረሻ ባቄሎ ላይ 17/10/1983 የመጨረሻ ውጊያ ገጠመን የጀነራል ከበደ አርምዴ ሬዲዮ ሠራተኛ አይነት 77 ሬዲዮ ይዞ ከሁዋላቸው እየተከተለ ጭንቅላቱ ተመቶ በታማኝነት ወደቀ፡፡ሬዲዮኑን ከላዩ ላይ ተቀብለን ከቅርብ ርቅት በመትረየሥ የሚዘንብብንን ጥይት መከታና ከለላ ያላቸውን የተፈጥሮ መሬቶች እየተጠቀምን በማፈግፈግ ላይ ነን 6 ሜካናይዝድ አዛዥ ሻለቃ አየለና ኤርትራዊዉ የፖለቲካ ሀላፊው ሻለቃ ገብረሥላሤ በኛ ትእዛዝ ሥር ነበሩ ረፋዱ ላይ ጀነራል ከበደ ለብቻቸው ፈንጠር ብለው አረፍ ብለዋል ፡፡አጃቢያቸው ወንዱንም ሤቱንም አንቺ ብሎ የሚጠራው የኦሮሞ ተወላጁ ደበላ ወደ እኔ እየሮጠ መጥቶ ሻለቃ ሠውየው ራሧን ልታጠፋ ነው ድረሽ ይለኛል፡፡ሮጬ ሥሄድ ሁኔታቸው ተቀያይሮ ፊታቸው በሚያሥፈራ መልኩ አብጦ ወረቀቶች አየቀዳደዱ የመጨረሻ ዉሣኔ እደደረሡ ሣያሥቡት ሽጉጣቸውን ከመሬት ለቀም አድርጌ ምን መሆን ፈልገው ነው፡፡ለቤተሠቦችዎ አያሥቡም፡፡

የርሥዎ ሞት ሁኔታዎችን የሚቀይረው ነገር አለ? የተቻለው ሁሉ ተሞክሯል የምንለውጠው ነገርም የለም ይልቅሥ አየለ ብረት ለበሥ እንዲልክልን አደርጋለሁ ብዬ አረጋግቼ ብረት ለበሡ መጣ ጀነራሉን፡ኮ/ግርማንና ዘርይሁንን ከውሥጥ አሥገብቸ እኔ ከላይ አናቱ ላይ ተቀምጬ ሀያ ሜትር እንኳን ሣንሄድ የብረት ለበሡ ጎማዎች ተመቱና መንገድ ሥቶ መንገድ ጠርዝ ቦይ ውሥጥ ገባን ሌላ ፈተና፡፡ጀነራል ከበደ እጅግ ወፍራም በመሆናቸው ከብረት ለበሡ ውሥጥ ለማውጣት ፈተና ነበር፡፡ሦሥቱንም እንደምንም አውጥተን በእግር ጀመርን፡፡ብረት ለበሡ እንደምንም ንፋሥ እየተሠጠው አልፎን ሔደ፡፡እሥከ ሠንዳፋ ደብረ ብርሀን ሥንደርሥ መኪና ቀርቦልን ከሦሥተኛው አብዮታዊ ሠራዊት ጋር ተቀላቀልን፡፡አዛዦቻችን ለሥብሠባ መከላከያ ፈልጓቸው ገቡ፡፡19/10/1983እኔና ኮለኔል ግርማ በአሥር አለቃ መኮንን ተጫኔ አሽከርካሪነት እሣቸውን ወሎ ሠፈር እኔና መኮንን ተጫኔ ደግሞ ወደ አየር ጤና አመራን እኔ እንዲህ በአዋራ ተጎሣቁየ ቀጥታ ወደ ቤት አልሄድም ብዬ አየር ጤና ግሪን ፓርክ ሆቴል ገብቸ አደርኩ፡፡

በሚቀጥለው ቀን ልብሥ አምጥተውልኝ፡እኔ ከግሪን ፓርክ ወያኔ ከጅማ መሥመር እነሡ በድል፡እኔ ደግሞ ለእኔም ሆነ ለቤተሠቤ ቢጠቅምም ባይጠቅምም ነፍሤን ቋጥሬ ወደ እቤት ገባሁ፡፡አባቴን ሣየው የገነፈለ እምባ ከቁጥጥሬ ውጭ ሆኖ አነባሁ፡፡በበራችን ላይ ወያኔ በታንክ በተሽከርካሪ አየተግተለተለ ገባ፡፡አብዮታዊዉ ሠራዊት ጨፍጫፊና ፀረ ሕዝብ ሆኖ ታሪኩን ለባለድሎቹ ወያኔ አሥረከበ፡፡መሣሪያ ይዞ ውሐና ምግብ እየለመነ ወደ እየቀየው ጦራችን ተመመ ፡፡፡፡፡፡ዝርዝር ታሪኮችን ብዙ ቆራርጫለሁ፡፡ለፌሥ ቡክ እንደ አይጥ መርዝ በትንንሹ የቀረበ ነው፡፡ የኢትዮ ኤርትራ ውጊያ 10 ክፍለ ጦር የውጊያ ውሎም አለኝ ይቀጥላል፡፡፡፡፡፡፡፡