Friday, April 24, 2009

አፈር ያልተመለሰባቸዉ ሙታን (ላድርባይ የኪነት ሰዎችና፤ ለገዢዉ ቡድን ብርጭቆ አጣቢ ምሁራን) ጌታቸዉ ረዳ http://www.ethiopiansemay.blogspot.com/ ለዛሬ የማስተናግዳችሁ ከላይ የተመለከተዉ ርዕስ የተገኘዉ ከሶፎንያስ ነዉ። ሶፎኒያስ እና ቀርሜሎስ “አቢሲኒያ”-በመባል የሚታወቀዉ የአማርኛ የግል- መጽሔት ታዋቂ አምደኞች የነበሩ ናቸዉ። እንደ ዱሮዉ ብዙ ባይሆኑም ዛሬም አንዳንድ የፖለቲካ መበለቶች ከየአቅጣጫዉ ብቅ እያሉ “ኣለና!” በማለት የጫካ ፋሽስት-ቡድን አወዳሽ ሆነዉ ስመለከት የሲፎኒያስ ትችቶችን ትዝ አሉኝና፣ “የሚረግጥ ሲመጣ- የሚረገጥ ገላ አለን ብለዉ ለሚመጣዉ ሁሉ ገላቸዉን የሚያስረግጡ ” ለትግራይ ጠባብ ብሄረተኛ የፋሺስት መንጋዎችን በማገልገል ላይ የሚገኙ የኪነት ባለሞያዎች፤የመገናኛ ብዙሃን አለቅላቂዎች፤ የፖለቲካ አጋፋሪዎች እና አልባሌ ሰዎች በጥቅሉ “ከርሳሞችና ሃሳዊ መሲሃን ክፍሎችን” በሰላ ብዕሩ “አፈር ያልተመለሰባቸዉ ሙታን”-በማለት ሶፎንያስ የሰመረበትን ላስነብባችሁ ፈለግሁ። ረዢሙ ሐተታዉ አሳጥሬዋለሁ። እንዲህ ይላል።በ ሦስት አመላካች ጥቅሶቹን ልጀምር ። “በአደባባይ ድፍረትን ሰብከዉ በጓሮ በኩል በፍርሃት የሚሾልኩ ፍርሃትንና ተቻችለን እንገዛ ቃላቸዉን እየረጩ የወያኔ ኢሕ አዴግ ባለስልጣናት አረቄ መሸጫ ቤት ዉስጥ ጠርሙስ መደርደሪያዉ ሥር ተቀምጠዉ ለባለስልጣናት የእንገዛ መጠጥ የሚያንቆረቁሩ ወገኖች እንዳሉ ታስታዉሳላችሁ?” “የገዢዉ ቡድን ጥርሱን ከገለጠላቸዉ ሌላዉ የእንባ ጅረት ሰርቶ በችግሩ ቢዋኙ የቁም ሙታን ናቸዉና ሃዘን አይታይባቸዉም።” “የእንሰሳ ባሕሪ ያላቸዉ ስለሆኑ ሲያባርሩት ተቅለስልሶ እንደሚመለስ ዉሻ ወደ አባረሩአቸዉ ጎብጠዉ እየተመለሱ በሌሎች ወገናቸዉ ላይ ሞት ለማወጅ ቀና የሚሉ ወገኖቻችን ዛሬም ይታያሉ” ለመሆኑ ተቻችለን “እንገዛ”-የሚሉን እነኚህ የወያኔ የፋሽስት ብርጭቆ አጣቢዎች፣ ሳይሞቱ የቁም ሞታቸዉ መሞት የጀመሩት መቸ ነዉ? መልሱ ከሲፎኒያስ ትችት- እነሆ ። “ከአባታችን አዳም ከእናታችን ሔዋን አፈጣጠር ጀምሮ እንሰሳም አራዊትም ተንቀሳቃሽ ነፍሳትም ዉሃ እየተመገበ አፈር እየላሰ አድጎ ፍሬዉን የሚያበላን አትክልትም በሞት መስፈሪያ እየተለኩ ሞትን የቀመሱት ከመቼ ጊዜ ጀምሮ ነዉ?የሚል ጥያቄ ለመጠየቅ አስቤ ነበር። ነገር ግን አንትሮፖለጂስቶች ቀድመዉኝ ፈጣን መልስ ስለሚሰጡኝ ጥያቄዉን ለመጠየቅ ዉስጤ ሳይፈቅድ ቀረ።ለምን ቢሉ የሞት አመጣጥ የተፈጥሮ ሕግ ናዉና ጠየቅኩም አልጠየቅኩም ስለ አጀማመሩ አወክዩም አላወኩም ዉስጤን የሚለዉጠዉ ፋይዳ አይኖርምና ከንቱ ድካም ስለሚሆንብኝ ትቸዋለሁ። እኔን የሚያሳስበኝ አድርባዮች ሆዳቸዉን ከሕሊናቸዉ አርቀዉ በሆዳቸዉ ህሊናቸዉን ለዉጠዉ መቸ መሞት እንደጀመሩ ከማወቁ ላይ ነዉ። ሳይሞቱ የሞቱ ተብለዉ አፈር ያልተመለሰባቸዉ ሙታን መሆናቸዉ የቁም ሞታቸዉን የጀመሩት መቼ ነዉ? የቁም ሞታቸዉን ለማወቅ አለመቻሌ ነዉ። ዉስጤ ዉስጤን ስለጠየቀዉ የኔ ዉስጥ ይህን ጥያቄ መመለስ ስላልቻለ ስነ ስብ አፈጣጠር ተመራማሪዎች ሞት ዘዉዱን ጭኖ በፍጡራን ሕይወት ላይ ሞት በቃ እየተፈረደ መግደል የጀመረበትን ጊዜ እንዲነግሩኝ ሳይሆን አፈር ያልተመለሰባቸዉ ሙታን የሚባሉ እንደሰዉ ተፈጥረዉ እንደ እንሰሳ ማሰብ የጀመሩት መቸ ነዉ? በዚህ ዓይነት አሟሟት ጀምሮ ሞትን ለመሞት በሰልፍ መሰመር ላይ እንደቆሙ የሚያዉቁት ካለ እንዲነግሩኝ አበክሬ እጠይቃለሁ። የሞት መሃከለኛ መንገዱን ሄዶ ከመጨረሻ ግቡ ለመድረስ በእኔ እስኪመጣ ድረስ ሞትን በሌሎች ስለማየዉ የሞት ጨካኝነትና አገዳደሉን መናገር አያስቸግረኝም፡፡ ከሗላየ ተነስተዉ ከፊቴ በመቅደም የሞታቸዉን መጨረሻ ያየሁላቸዉ ሞትን የሞቱ ወገኖቼ በከርሰ መቃብር ዉስጥ አፈር ስለሆኑ ስለ አሟሟታቸዉ አሁን ላነሳ አልፈልግም:። ስለዚህም ክፉዉን የሞት አሟሟት መግለጫ መስጠት ጉንጭ አልፋ ስለሚሆን አፈር ስላልተመለሰባቸዉ ሙታን የምገልጸዉን እንድትሰሙኝ በመግለጫ ወንበሬ አጠገብ እንድትሆኑ ወንበሬ ጠባብ አይደለምና ከጎኔ ተቀምጣችሁ የሞትን ወግ እንድትከታተሉ እጋብዛችሗለሁ። አፈር ያልተመለሰባቸዉ ግን የሞቱ የሚመስሉ ስላሉ ተመራማሪዎቹ መልስ እስኩሰጡኝ ድረስ የራሴን ገለጻ እቀጥላለሁ። በቤታቸዉ ጎጆ ሻማ ለኩሰዉ በሻማዉ ብርሃን የሞት ጉድጓዳቸዉን ጨለማ በምናባቸዉ እያሰቡ ነብሴን በገነት አኑራት በማለት ለፈጣሪ ማመልከቻ የሚያቀርቡ ወገኖች እንዳሉ አዉቃለሁ።ከማመልከቻቸዉም በሗላ ወደ ዉጭ ወጥተዉ ጨረቃን ተመልክተዉ የሚመለሱ በሕይወት መኖራቸዉን የጭንቀት ጡጦ በማጥባት ፍርሃትን ለማሳደግ የሚተጉ እንዳሉ አዉቃለሁ። ቀን ከሰዉ ጋር ተደባልቀዉ በፍርሃት ላይ ይፎክራሉ። ደፋር ለመምሰልም ጠንካራ ገደል እንኳን ቢያገኙ ገደሉን ንደዉ ሜዳ ሊያደርጉት እንደሚችሉ የጉብዝና ዲስኩር ያሰማሉ።ጀግና ቆሞ እንዳይራመድ ባላወቁት ድፍረት ዉስጥ ተሰግስገዉ ፈሪ በመቀፍቀፍ ጀግናን በወሬ እያራዱ ተራማጅ እግሩንና ጣጣር ክንዱን መድሃኒት እንደጠፋለት በሽታ ደካማ ለማድረግ የማስመሰል ምሽግ ሲያመቻቹ የሚዉሉ አሉ። ኢትዮጵያ በብዙ መመዘኛ ጀግና እንደነበራትና ሁሉ ባልተፈለገ ዉዳቂ ሚዛን ፈሪ ቀፍቅፋ እያስመዘነች መቀመጣን እየተመለከትን ነዉ። እነዚህ የፍርሃት መርገምት ሆነዉ በዋሉበት እያደሩ ዉሸትን ሲኮተኩቱ የሚያነጉ የዉሸት አዋቂዎች በሃገራችን በዝተዉ እንደሚገኙ መመስከር እንችላለን። ሌሎቹም እንዲሁ ምናቸዉ ምናቸዉም ሆድና ጉሮሮረ ብቻ የሆኖባቸዉ ወገኖችም አሉ። የሞቱ-“ግን”ያሉ የሚመስሉ አፈር ያሸተቱ እንጂ አፈር ያልቀመሱ የትዉልድ በሽተኞች ሃገራችን እንደፈጠረች ማወቅ ይገባናል። የሚረግጥ ሲመጣ የሚረገጥ ምቹ ገላ አላቸዉ። ክብርን የሚገፍ ሲነሳ ራቁታቸዉን ሆነዉ ድሮም ራቁታችንን ነዉ የተፈጠርነዉ በማለት በራቁትነት መፈጠራቸዉን ዋቢ አደርገዉ አካላችን የክብር ልብስ ለብሶ ስለማያዉቅ ከኛ የሚገፈፍ ክብር የለም ብለዉ ሁሉም ሰዉ ራቁቱን መፈጠሩን መጀመሪያ ይወቅ ብለዉ በገዢዎች ትናግ ዉርደትን ያንቋርራሉ። እነዚህ አስተሳሰባቸዉ ደራሲ ከበደ ሚካኤል የፈጠሩት አዝማሪ ዓይነት ይመስሉኛል”” አዝማሪዉ መንገዱን ሲሄድ ወራጅ ዉሃ ካለበት ወንዝ ይደርሳል። ካሁን አሁን ዉሃዉ ይጎድልልኛል ብሎ ቢጠብቅ ዉሃዉ ሳይጎድል ይቀራል። አስኪ በዜማ ላባብለዉ ይልና ግጥም እየደረደረ ማሲንቆ እየገዘገዘ የወንዙን መጉደል ቢጠብቅ የሰማዉ እየሄደ ያልሰማዉ ይመጣል እንጂ ዉሃዉ አልጎደለለትም። ያዝማሪዉ ሁኔታ ያየ ሰዉ ጠጋ ብሎ እንዲህ አለዉ “ ወዳጄ ስራህ ከንቱ ሆነብኝ፤ግጥምህም ከማያፈራ ጭንጫ ላይ የወደቀ በር መሰለኝ፤ዜማህም ወራጁ ዉሃ አላጎደለዉም፤ማሲንቆህ ይጮሃል እንጂ ዉሃዉን አላሰማም፤ያልሰማዉ መጥቶ ሰምቶ ይሄዳል። ያለ አዋቂ ዜማ ስታዜም ከሚመሽብህ ሌላ መንገድ ይሻላል” አለዉ። በዘመናችን የሚገኙ አንዳንድ ወገኖች በዘመናቸዉ የዕድሜ ጅረት ለሂያጁና ለመጪዉ ሲዘፍኑ ሲቀኙ ዘመን መጥቶ የሄደባቸዉን እስኪያስታዉሱ ለመጣዉ እያጎነበሱ ጥሏቸዉ ሲሄድ በአዲስ መጪ እየተደቆሱ ዘመን የባጀባቸዉንስ እናዉቃለን?በቤትም በጎረቤትም፤በደጅም፤በሩቅ ስፍራም አሉና እነሱንም ማስታወስ ይገባል። ላዲስ መጪዎች አዲስ ቅኝት የምስጋና ክራር የሚያከሩ ዘፋኞች ትላልንት ሞተን ነበር፤ ዛሬ ግን ለሰዉ ልጅ ፍትህና ሰላም ተማጓች በማግኘታችን ከሞት ተነሳን ብለዉ ማሲንቆ የሚገዘግዙ “የነፋስ መጋዞች” አታዉቁም? አንዱ ገጣሚ ከሌላዉ ተቀኝ፤አንዱ አድር ባይ ከሌላዉ አጎንበሽ ለመብለጥ እየተወዳደሩ ከሄደዉ ሳይማሩ ለሚመጣዉ የዉርደታቸዉን ሰርትፊኬት በማሳየት እንደ ወደዳችሁ ግዙን እንደወደዳችሁም አስሰሩን። በወደዳችሁትም የስራ መስክ ቅጠሩን እናገልግላችሁ ብለዉ በወገናቸዉ መሰቃየት ለመኖር ብቻ የዉርደት ዲግሪያቸዉን ለገዢዉ መደብ አቅርበዉ ከዉርደት ድንኳን ስር የሚገኙ ወገኖች አታወቁም?ምኞት አስክሯቸዉ በነሱ የምኞት አረቄ ጤናማዉ ሰዉ ሰክሮ እንዲዋሃዳቸዉ የሚጎተጉቱ የገዢ ቡድን ብርጭቆ አጣቢዎችስ አላያችሁም? በአደባባይ ድፍረትን ሰብከዉ በጓሮ በኩል በፍርሃት የሚሾልኩ ፍርሃትንና ተቻችለን እንገዛ ቃላቸዉን እየረጩ የወያኔ ኢሕአዴግ ባለስልጣናት አረቄ መሸጫ ቤት ዉስጥ ጠርሙስ መደርደሪያዉ ስር ተቀምጠዉ ለባለስልጣናት የእንገዛ መጠጥ የሚያንቆረቁሩ ወገኖች እንዳሉ ታስታዉሳላችሁ? ታሪክን ጊዜ ገልብጦት ታሪክ ጊዜ ሲያነሳዉ ለማየት የታሪክ ምክንያት ሊሆዩ የሚችሉ ወገኖች በጊዜ መጋረጃ ተሸፍነዉ የችግራቸዉን ዉስጥ እንዳናይ በዉጭዉ እይታችን ላይ አስፈሪዉን የትሞታላችሁ ጨረር እየወረወሩብን ሁላችን የዓይናችንን ለማሳወር ድፍረት በሚሉት መድሃኒት ላይ ዋጋ ይሰቅሉብናል። የገዢዉን ቡድን እኩይ ሥራ እንዳንመለከት ሁላችንም ዕዉራን ተብለን እኛም እንደነሱ አፈር ያልተመለሰብን ሙታን እንድንባል በገዢዉ ጠመንጃ ጉልበት ወደ ጨለማዉ ያስጠጉናል። እነሱ ስለጠገቡ በሌላ ዘንድ ረሃብ አለ ብለዉ አያምኑም። የገዢዉ ቡድን ጥርሱን ከገለጠላቸዉ ሌላዉ የእንባ ጅረት ሰርቶ በችግሩ ቢዋኙ የቁም ሙታን ናቸዉና ሃዘን አይታይባቸዉም። ከ አድርባይ ቡድናቸዉ ተሰላፊ እንዱ ቢዋረድ እነሱ መሽቶ እስኪነጋ በጥጋብ ይዘላሉ እንጂ ነግ በእኛም የሚል ሰዋዊ አስተዉሎት አይመጣላቸዉም። እንዲህ መሰል የእንሰሳ ባሕሪ ያላቸዉ ሶዎች ስለሆኑ ሲያባርሩት ተቅለስልሶ እንደሚመለስ ዉሻ ወደ አባረሩአቸዉ ጎብጠዉ እየተመለሱ በሌሎች ወገናቸዉ ላይ ሞት ለማወጅ ቀና የሚሉ ወገኖቻችን ዛሬም ይታያሉ።ከነዚህ በተጓዳኝ የትም ዉለዉ የትም ቢያመሹ ሆዳቸዉን እንኳ ለማሸነፍ የማይቸገሩ ፕሮፌሰሮች፤ዶክተሮች ከእዉቀት አልባ ቡድኖች ጋር ገጥመዉ ቀና ሰዎችን ጥለዉ ለማለፍ የአድርባይነት ተጠባባቂ ተጫዋች በመሆን በተቀያሪነት ለመለወጥ በየቢሮአቸዉ መሽገዉ የአሰልጣኝ ድምጽ የሚጠባበቁ አፈር ያልተመለሰባቸዉ ሙታን አሉ። የወፍጮ እህል አስፈጪዎች፤ቧምቧ አቃኝዎች እንደጠመንጃ ጥይት ወገንን የሚያስፈሩ የጦር አባላቶች፣ እንኳን ዘፍነዉ ቢያለቅሱም እንኳ የምግብ መኖ የማያጡ ዘፋኞች፤ኳስ አባርረዉ ኳስ ለግተዉ በእግራቸዉ ገንዘብ ሊሰሩ የሚችሉ ስፖርተኞች ፣በሰዉ አስቀዉ በእነርሱም ተስቆ ህይወትን በሁለትዮሽ መግለጥ የሚችሉ የኪነ ጥበብ ሰዎች፤በማስመሰል ልቅ አድርባይነት ለገዢ መደብ አጎንብሰዉ የገዢ መደብ ጭቆና በዜጎች ላይ እንደ አረግራጊ ፍራሽ ሲያረገርጉበት የጥጋባቸዉ ክብደት ለማወቅ ሚዛን ፍለጋ ሽቅብ ቁልቁል ይላሉ። እንደ ሰጎን ያጎነበሱ እንደ ሰንበሌጥ የተኙ ወገኖች መቼ ነዉ ቀና ብለዉ አልሞትንም የሚሉት?ብለን በጥያቄ ሌላዉን እናስከትል -“ዓይናችን እያየ አታዩም የሚሉን፤ አናይም ስንላቸዉ ታያላችሁ ብለዉ የሚሞግቱን፤ችግራችንን እየተናገርን ‘የምትሉትን አንሰማም’የሚሉን የዘመኑ ገዢዎች መቸ ነዉ ከእዉነት ማማ ላይ ወጥተዉ የሚታዩት?እኛ እንደሆን የራሳችነን ጥላ እየሸሸን ባለንበት ወቅት የመንቀሳቀስ ነፃነት ሰጥተናችሗል ቢሉን የምናምናቹወ አለመሆናችንን ሊያዉቁልን ይገባል። ይህንን ሳያዉቁ ያልናቸዉን ይቀበላሉ በሚል ደነዝ አስተሳሰብ ሕሊናቸዉን አደንዝዘዉ ፍርሃት ለቀዉብን የደም ብዛት እንደያዘዉ በሽተኛ ግማሽ አካላችን በድን ሆኖ ክንዳችንን ሊያሳጥፉን መመከራቸዉ መቼ ነዉ የሚያቆሙት? ገዢዉን መደብ ጥያቄ ስናቀርብለት ለገዢዉ መደብ ወግ ነዉ የአህያ ተረት እየተረቱ በደመነፍስ የሚንቀሳቀሱ ወገኖቻችን አፈር ያልተመለሰባቸዉ ሙት መሆናቸዉን መቼ ነዉ የሚገነዘቡት? ገዢዎች ጠግበዉ በተራበ ጉልበት ላይ የጎሳ ጥበትን እያሰፉ እንደጋሪ ፈረስ እንድ አቅጣጫ (እሱም ድንቁርና ነዉ) እያሳዩን ለረሃብ ምጣድ ጀርባችንን ሰጥተን የተስፋ እንጀራ በላያችን ሲጋግሩ የምናስተዉል የዚች አገር ዜጎችስ መቼ ነዉ የጀርባችንን እሳት የምናጠፋዉ? እነዚህን አስተያየቶች ስናነሳ አፈር ያልተመለሰባቸዉ ሙታን አልሞትንም ይሉን ከሆነ በየፈርጁ ያስቀመጥናቸዉን መጠይቆች ልብ ብለዉ እንዲያጤኑ እንጋብዛቸዋለን?እኛም ጠያቂዎቹ የሕብረትንና የእምቢ ባይነትን፤ አድርባይነትን በሆድ አድሮ መኖር ክብር እንደሌለዉ አዉቀን የጠየቅናቸዉ ባይመልሱ እኛ ጠያቂዎቹ መልስ መስጠት ይገባናል። አስከዚያዉ መለስ የሚሰጥበት ጥያቄ ልጠይቅ አፈር ያልተመለሰባቸዉ ሙታን ርዕሴን አጠቃልየ እደመድማለሁ። 1- ገበያ ወጥቶ ዋጋ የማይጠይቅ ምንድነዉ? 2- በልቶ የማያመሰግን ማነዉ? 3- ያመረተዉ የማይበላስ ምንድነዉ? መልሱን በሚቀጥለዉ ይዤ አስክመለስ ድረስ- አስከዛዉ በየቤታችን፤በየማሕበራችን፤በየእድራችን ማንነታችንን ማንነትና ሀገራዊ እድገታችንን ወይንም ዉድቀታችንን እየተነጋገርን ካቀረቀርንበት “ድዉይ የመገዛት መንፈስ” መላቀቂያዉን እንፈልግ በማለት ሃሰቤን እገታለሁ”።//-/ http://www.ethiopianseemay.blogspot.com/

Friday, April 17, 2009

በወያኔ ቀዉስ አንቆዝምም “ዕልል!” እንላለን እንጂ!

በወያኔ ቀዉስ አንቆዝምም “ዕልል!” እንላለን እንጂ!
(ከትዝታችን ማህደር) ጌታቸዉ ረዳ
(…በወያኔ ቀዉስ “ቆዝሙ” የሚሉን ክፍሎች “በወያነ ቀዉስ አንቆዝምም ዕልል እንላለን እንጂ!” ወያኔ ከተንኮታኮተ ሀገር ትተረማመሳለች ብለንም እንቅልፍ አናጣም፣ ሀገር እየተተረማመሰች ያለቺዉ በወያኔ ነዉ።ገዢዎች ሥልጣናቸዉን ለማራዘም ሁሌም እኛ ከወደቅን ስምነተኛዉ ሺህ መጣ ማለታቸዉ ተለመደ ነዉ…)
ባለፈዉ ከትዝታችን ማህደር አማዳችን ወያኔ ለሁለት ሲሰነጠቅ በመላ ዓለም የሚኖሩ በተለይም በዚህ በአሜሪካ ሃገር የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች የተሰማቸዉን ሃዘንና ድንጋጤ አቅርቤላችሁ ነበር። ድርጅቱ ለሁለት ከተገመሰ በሗላ አንጃ ለተባለዉ ቡድን ማለትም ለእነ ገብሩ አስራት ደህንነት ምንኛ እንደተጨነቁ/እንደተጠበቡ አይተናል። በዚህ አምድ ደግሞ ሌሎች ኢትዮጵያዉያን ወያኔ በቀዉስ መመታቱ ምንኛ እንደተደሰቱ እና በየጋዜጣዉና ራዲዮኑ ዕልለታቸዉን እንዳስተጋቡ እና መጽሄቶችና ጋዜጦች በጣም እጅግ በበርካታ የደስታ ደብዳቤ መግለጫዎች እንደተጥለቀለቁ እናስታዉሳለን። ለተለያዩ መጽሄቶችና ጋዜጦች የተላኩ የደስታ ምግለጫዎች በጣም ብዙ በመሆናቸዉ ድብዳቤዎችን ከማቅረብ ይልቅ ባጠቃላይ የህዝቡን ወቅታዊ ስሜት ያንጸባረቀዉ የሃዋርያዉ ጋዜጣ “ከዜና ባሻገር”-አምደኛ መስፍን ታምራት ከናይሮቢ የዘገበዉን ሀተታ ለትዝታችን አምድ መርጬ አቅርቤላችሗለሁ። ወደ ሗላ ተመልሰን በወቅቱ ተዘገቡትና የታዩት ሁኔታዎች ስንመለከት አሁን ላለነዉ ሁኔታ አመላካች በመሆናቸዉ፣ በጥሞና እንድናጤናቸዉ ይረዳናል። መብሩክ አለህ ከሪም፣ፈጣሪ ይመስገን፣ ወደ አድባሩ ወደ አተቴዉ ዘምበል ላለላችሁትም በዚያዉ ባመቻችሁ ደስ ኢበላችሁና መብት መጠበቅ አለበትና የዚህ ዓይነት እምነት ለሌላችሁ ደግሞ በምታምኑበት ዓላማ ሆነ ሕዝብ ስም ለሀላችንም እንኳን ደስ አለን ። የመቶ ዓመት የቤት ሥራ ሰጠናቸዉ ብለዉ የትግራይ ትግርኚ ትምክህተኞች በጨፈሩብን በአጭር ጊዜ ዉስጥ እርስ በርስ ጉሮሮ ለጉሮሮ ተናንቀዉ ሲደካክሙ ለማየት በቅተን ተደስተን ሳናበቃ እነሆ የሃገርና የሕዝብ ጠላት የሆነዉ ወያኔ ጭራሽ ሊያንሰራራ በማይችልበት ደረጃ እርስ በረስዩ ተንከረባብቷል።ተስላችሁ የነበራችሁ ሳይዉል ሳያድር ክፈሉ! በዚህ ዓምድ ባለፈዉ ወር ሳይቀር ወያኔ በዉስጣዊ ቅራኔ እየተተራመሰ መሆኑን ጠቁመን ነበር። ሰብሓት ነጋ የእሳት አደጋነት ማለትም የቅራኔ አብራጂነት ሚና እየከሸፈ ራሱም ራሱም የችግሩ አካል ሆኖ እየተነከሰና እየቦጨቀ በመምጣቱ የወያኔ ቅራኔ ሊደበቅ ከማይችልበት ደረጃ ደርሶ በ አደባባይ ፈነዳ። አለቃችሁብን ብለዉ የተላቀሱት የወያኔ ደጋፊ ትግራዉያን እዉነት አላቸዉ። “በወያኔ ተስቆበታል ግን ደምበኛዉ ካካታ ጀመረ እንጂ አላከተመም” ዛሬ የፈነዳዉ የወያኔ ቅራኔ መብሰልሰል ከጀመረ አመታት ቢያልፍም ግጭቱን አከረረዉ ከሻዕቢያ ጋር የተፈጠረዉ ቅራኔ መሆኑን ግልፅ ነዉ። የወያኔ አንጃዎች በምንም ጊዜ ሆነ ቢሆን ስላሉት በደል ፀፀት ተሰምቷቸዉ እንታረም ብለዉ ባነሱት ክርክር ተጋጩ አይደሉም።ከኢትዮጵያ አንፃር ሁለቱም አንጃዎች የሚፈይድ ፕሮግራም ወይንም አመለካካት የላቸዉም ። በጠባብ የትግራይ ትምክህተኞች ዘንድ የተፈጠረዉ ግጭት ማን ይበልጥ ወያኔ እንጂ ማን ንስሃ ገብቶ ክህደትን ትቶ ኢትዮጵያዊ ልሁን በሚል አይደለም። ይህ እንዳለ ሆኖ ግን በጠላት ጎራ የሚከሰት ክፍፍል በደፈናዉ እሰየዉ ተብሎ የሚተዉ ሳይሆን እንዳይረግብ የሚረባረቡበት ነዉና በመለስ አንጃና በእነ ስየ አንጃ መሃከል የተከሰተዉ ቅራኔ እንዳይዳፈን መስራት አስፈላጊ መሆኑን ይታያል። ከዝንጀሮ መረጣ በዳኝነት መቀመጡ አስደሳች ስራ ባይሆንም በአጭር ጊዜም ደረጃ ቢሆን የአንዱ አንዱን ማሸነፍ በተመለከተ የሚጠቅመዉን አይቶ በዚሁ መሰረት ዘምበል ያለ ስራን መስራት አስፈላጊ መሆኑ ይታያል። ወያኔ ገና ከዘመነ “ሕንፍሽፍሽ” ቅራኔዉ ጀምሮ የተፃራሪ የትግራይ ነፃ አዉጭ ድርጅትን (ቲኤልኤፍ)ን-ሲገድልም ሆነ በኢሕአፓ ላይ ጦርንት ሲከፍትና ሗላም ማሌሊት ብሎ እነ አረጋዊና ግደይን ሲያባርር የታየዉ በሞላ ይህ ድርጅት ልዩነትን የዉስጥም ሆነ የዉጭ በጭረሽ ማስተናገድ የማይችልና ከግድያ ሴራ ዉጭ ምንም መፍትሄ የማይታየዉ መሆኑን ነዉ። ይህ ሀቅ ሆኖ እያለ እነ ስየ ላይ የሚበትኑት ወረቀት ላይ ሰፍሮ ሚታየዉ አንድም የእንዚህን ግለሰቦች የማይታረም ወያኔነት ሲያሳይ (ጸረ ዲሞክራሲ ከየት ድንገት ከየት መጣብን ይሉናል!)-በሌላ በኩልም ጅልነታቸዉንም ያረጋግጣል። ለነታምራት ላይኔ ይቅርና ለነተክሉ ሃዋዝና በገዳርፍ ሱዳን በሰንጢ ተቆራርጦ ለተገደለዉ የወያኔ የጀዳ ወኪል (ያሲን)ያላየዉ ዲሞክራሲ ዛሬ በድንግት ከየት እንዲወለድ እንደጠበቁ ያስጠይቃል። ፀረ ዲሞክራሲ የሆነዉ መለስ ብቻዉን ሳይሆን የወያኔ አመራር በሞላ መሆኑን ለህዝባችን ምስጢር አይደለም ። ይሁንላችሁ ብንል እንኳ ባለፉት 10አማታት ብቻ ሳይሆን ገና ከጫካዉ መለስ አላግባብ ሥልጣንን ከዓባይ ፀሃየ በእጁ አስገብቶ መገኘቱ ነዉ። ይህንን ሂደት ደግፈዉ ሲያጫፍሩ የነበሩት እነ ስየ እና ገብሩ ለሦስተኛ ጊዜ የከዳዉ ሐሰን ሺፋን፣ ወላዋዩን ዓባይን ትተን)ራሳቸዉ ናቸዉ። የትኛዉ የወያኔ ዲሞክራሲ ደምቆ ታይቶ ነዉ ጉባኤ ይጠራ፣ ነፃ ዉይይት ይካሄድ የሚሉት?በዘረፉት ገንዘብና ምቾት ኣእምሮአቸዉን ስተዉ ነዉ?ፖሊስና የፀጥታ ሃይሎች በፖለቲካዉ ገቡ፣ አፈና አካሄዱ ሲሉን አስከ ዛሬ የት ነበሩ?አሰፋ ማሩ በማን ጥይት ተገደለ?ተስፋየ ታደሰ በማን ሰንጢ ተቆራረጦ ተገደለ? ፕሮፌሰር አስራት በማን ታሰሩ? እነ ጸጋየ ገብረመድህን በማን ታፈኑ? አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በማን ተደበደቡ.ተሳደዱ፣ታሰሩ?ጋዜጠኛች ለምንና በማን ከረቸሌ ወረዱ?እነ ዶክተር ታየ፣ አበራ የማነአብ፣ ፊታዉራሪ መኮንን ዶሪ፣ ወዘተ በማን ታሰሩ?ያዲስ አበባ መስጊድና የጎንደር አደባባይ እየሱስ ፍጅት የማን ነዉ? ወያኔ ባሁኑ ጊዜ በዘር ማጥፋት ወንጀል ሊከሰስ የሚችል ነዉ?-አርባ ጉጉ ምሰራቅ ወለጋ ወዘተ ለዚህ ተጠያቂዉ መለስ ብቻ ነዉ?በህዝብ ላይ ሲደረስ የቆየዉ ግፍ ዛሬ በአድራሾቹ ላይ እየደረሰ ከሆነ ልናዝንላቸዉ ለምንስ ይጠብቃሉ?ከርቸሌ ያለዉ ታምራት ሳቅ ሰቅ እያለዉ ሰሞኑን ቢቸገር ማን ይፈርድበታል? የአሁኑ ቀዉስ ለትግራይ ተወላጆች በተለይም ለምሁራኑና በባዕድ ሀገር ላሉት የወያኔ ደጋፊዎች በሞላ አዲስ ዕድል ሰጥቷቸዉ ነበር-ከኢትዮጵያ ህዝብ ጎን ሳያወላዉሉ ለመሰለፍ። ሊጠቀሙበት ቀርቶ ከምናዉቀዉና እጅ እጅ ካለን አነጋገርና ትንተና እንኳን ጭራሽ መራቅ አልቻሉም። ቢያንስ እስካሁን። የትግራይ ጠባብ ብሔረተኝነች አባወራ ነን ባዮቹን እነ ስየን በጭፍኑ ደግፈዋል ። ደግፉም እያሉ ኢትዮጵያዊያኑን ይወተዉታሉ።ምን አህል ቢንቁን ነዉ?የኢትዮጵያ ጠላት መለስ የሚባል ግለስብ ሳይሆን ጠባብ ብሄረተኛነት የተባለዉ ቫይረስ ሲሆን-የዚሁ በሽታ ተሸካሚዎች ደግሞ “ኢ አር ፖሲቲቭ” ወይም የሻዕቢያ ቡችላዎች የሚባሉት እነ መለስ ብቻ ሳይሆኑ ወያኔ በጥቅሉ ነዉ። ፀረ ኢትዮጵያ የሆነዉ የትግራይ ጠባብ ብሔረተኝነት ከተነሳ ደግሞ -የዚሁ አስከፊ እምነት ተሸካሚዎችና አስፋፊዎች ከሚባሉት ቀንደኞቹ ዉስጥ በእነ ስየ ገብሩ ጎራ ተሰለፉት ሁሉ ይገኙበታል። ሕገ ወጥ ታምራት ላይኔ በሕገ ወጥ ሲወገድና ለፓርላማቸዉ ቧልት ተጋልጦ መሳቂያ መሳለቂያ ሲደረግና ከዚያም አልፎ ለዚሁ ጠንሳሽና አካሂያጅ መለስ ብቻ ነበር? የእነ ተወልደ፣ዓባይ ሚና ምን እንደነበር ሁላችን ስለምናዉቀዉ ያኔ ያልታየዉን ዲሞክራሲ ዛሬ ጠፋ ቢሉን ከመሳቅ ሌላ የምናደርገዉ አይኖርም። የትግራይ ምሁራንና የወያኔ ደጋፊ የሆኑት የዚሁ አካባቢ ተወላጆች በጊዜዉ ተጠቅመዉ የወያኔን ፀረ ሕዝብነት አዉግዘዉ የመላ ሕዝብን ጥያቄ ደግፈዉ ከሕዝብ ጎን ካልቆሙ በስተቀር መለስን አዉግዘዉ ስየን ሲደግፉ መለስ ካሸነፈ የወያኔና የትግራይ የበላይነት ይበልጥ ይጎዳል ብለዉ ተጨንቁ ከሚል ሌላ መደምደሚያ መድረስ አንችልም። አንድ የኢትኦጵ ጋዜጣ በአንክሮ እንደጠየቀዉ ሁሉ “በተለያዩ የኢትኦጵያ ክፍሎች ተበታትነዉ በንግድና በመሳሰሉ ስረዎች ላይ የተሰማሩትና በአብዛኛዉ ተመችቷቸዉ ሚኖሩት የትግራይ ተወላጆች እንደ ኤርትራዉያን “ወደ አገራችሁ ቀጥሉ” የማይባሉበት ያፈሩትን ሃብት ጥለዉ ወልደዉ ከከበዱበት ወግ ማዕረግ ካዩበት ተዋርደዉ ላለመባረራቸዉስ “ከወያኔ ጉዞ” አንፃር ዋስትናቸዉ ምንድነዉ? ምን ዋስትና? ስየና ገብሩን ደግፉ እያሉ እስከቀጠሉና ለትግራይ በላይነት እስከቆሙ ድረስ ለወያኔ የመጣ በነሱም ላይ እንዳይከሰት መቸስ ዜጎቻችን ናቸዉና እጅግ እንሰጋለን። ። ምክንያቱም ወያኔ አብቅቶለታል።ሟርት ሳይሆን ሀቁን መናገራችን ነዉ።የዛሬ ጠዋቱን ሳይሆን የነገ ቀኑን። የመንግሥት ሥልጣንን በተመለከተ ለመለስ ፈረሱም ሜዳዉም ተለቅቆ ስለከረመ ዛሬ በቀላሉ መንጠቅ አይቻልም።መለስ ሃይሉን ለማደላደል እየተራዋጠ በሌላ በኩል ደግሞ አማራጮች አሉት።ታረቁ ብለዉ ሳይጠሯቸዉ ታረቁ ብለዉ አማላጅ የሆኑትን (ጳጳሱ፣ ሰለሞን ዑንቋይ፣ ደጃዝማች ዘዉዴ ገብረስላሴ ወዘተ)“የባልና ሚስት ጠብ አይደለም”-ብሎ ዘግቷል።ጉባኤ ካልጠራሕ እያሉ የሚንጫጬት ሁሉ እነ ስየን ከከወነ በሗላ ሊጠራላቸዉ ይችላል።ካልሆነም በመቀሌ ሆነ በአዲስአበባ የካድሬዎች ስበሰባ እንዳሳያቸዉ-ሁሉ የራሱን ምርጦች ሰብስቦ እነ ስየ ባሉበት የፈለገዉን ዉሳኔ ሊያስወስንባቸዉ ይችላል። በእነ አረጋዊና ግዴይ አድርጎታልና። ባለፈዉ ሰሞንም ደግሞታል።በወኔ ቢሱ ታምራት ላይኔም ፈፅሞታል። ይህንን ቲያትር የ ኢሕአዴግ አባል ነን ባይ ተለጣፊዎች እንዲደግፉት ማድረግ አይሳነዉም። እነ ስየን ዛሬ ቢያስር የሚከተለዉንም ተቃዉሞ ከተነገወዲያዉ እርምጃዉ ጋር አመዛዝኖ ያዋጣናል ሚለዉን መዉሰዱ አይቀሬ ነዉ። የስየና ገብሩ አንጃ ከሰነዶቹ እንደታየዉ ሁሉ ዛሬም ከወያኔዉ ካቴና ባለመላቀቃቸዉ “ወያኔያዊ ሕዝባዊነትና ዲሞክራሲያችን ጠፋ ይሉናል”።ሰፋ አድርጎ ሕዝብን ሊያስደምጥ ሆነ ባዲስ መልክ ሕዝበን ሊቀሰቅስ ባለመቻሉ ራሱን ነጥሎ ለበለጠ አደጋ አጋልጧል። መድረኩን አጥብበዉታል::በወያኔ ዙርያ ሊወያዩና ችግሩን ፈትተዉ በቀድሞ መንገድ ሊቀጥሉ ነዉ የፈለጉት።በዚህ ዳንስ ደግሞ አንገትም ሆነ ወገብ እየሰበቁ መሽከርከሩን ሞያተኛዉ መለስ ከማንም በበለጠ ያዉቀዋል፣ ይችልበታልም። ቀዉሱ ስላልተጠናቀቀ ካዩትና ካለፈዉ ተምረዉ ሌላ እርምጃ ይወስዳሉ ወይ?ይችላሉስ ወይ?የሚለዉ ገና በመጠኑም ቢሆን ተንጠልጥሎ ያለ ጥያቄ ነዉ። ምንስ ሲቀናጣ በትሩን ወርዉሮ ፍለጋ ይገባል እንደተባለዉ መለስን በራሳቸዉ ላይ ካፈናጠጡና በሥልጣንም ካባለጉት (እሱም በገንዘብና በሥልጣን ካባለጋቸዉ በሗላ)ዛሬ መለስ ያላግባብ በፀጥታና በፖሊስ ሃይል ወይንም በመንግሥት ሥልጣን ተጠቀመ ብለዉ ዋይ! ዋይ! ቢሉ መሰረታዊ ሀቁን የሚለዉጥ አልሆነም። መሰሪዉ መለስ ከደደቢት ጀምሮ ልክ እንደነ ዓባይ ለሳሕሉ ሰዉየ ያደረ ቢሆንም ሻዕብያን በተመለከተ የነበረዉ አቅዋም ሁሉ በአንድ ሰዉ ሊላከክ የሚችል አይደለም። ሻዕቢያን ተቃዉመዉ በነ ገብሩ አስራትና በነ ሐሰን ሹፋ የተሰቃዩ ትግራዉያን ለዚህ ምሳሌ ናቸዉ። መለስ ወደ ሻዕቢያ ካዘነበለና አብዛኛዉ የወያኔ መሪ “እንደሚሉን”አሱን “ይቀወሙት” ከነበረና እነ ስየ “አለ” የሚሉን “ዲሞክራሲያዊ” አሰራር የወያኔ ባህልና ልምድ አሰራር ከነበረ ታዲያ “ለምን መለስ ፍላጎት ብቻ የበላይ ሆነ?” ለሀገራችን መጠቃትና ገና ከጥዋቱ መከፋፈል መሽመድምድ ተጠያቂዉ ወያኔ ነዉ ወይስ አንድ ግለሰብ?-የልዩነት ነጥቦች ተብለዉ የቀረቡት አጥጋቢ ሆነ አሳማኝ ሆነዉ አይገኙም። ወያኔና ሻዕቢያ የተጣሉት በባድሜ አልነበረም። እነ ገብሩ ስየ ወዘተ ከሻዕቢያ ጋር የተጋጩት በሃገራዊ ሉዓላዊነት ሳይሆን ባኮኖሚ በጥቅም ጉዳይ ነዉ::የወያኔ አዲስ ወጥ ከበርቴ ያለምንም ፉክክር ኢትዮጵያን መበዝበዝ በመፈለጉ የኤርትራን ኢኮኖሚያዊ ቋንጃ ሊቆርጥ በመነሳቱ ነዉ ዋነዉ መንስኤዉ። እንኳን ለምናዉቃቸዉ ኤርትራዊያን ቀርቶ ለሱዳን ለኢራን ሳይቀር ያገራችን ሉዓላዊነት አሳልፎ የሰጠዉ ወያኔ በጥቅሉ አልነበረም?ከዚያድ ባሬ ጋር ተፈራርሞ ግማሽ ኢትዮጵያን የምዕራብ ሶማሌ ያለዉስ መለስ ብቻ ነዉ?ለዚህ ሁሉ መለስ መለስ ብቻ ከተባለ ዉሸት ከመሆኑ ሌላ እነ ስየ በወያኔ አለ የሚሉትን ዲሞክራሲ የጋራ አማራር አለመኖሩን አረጋጋጭ ይሆናል። መለስ ዜናዊ የአያቱ የባንዳዉ አስረሱን ቅርስ አንግቦ ሀገራችንን ሊሸጥ ሊያዋርድ ከመጀመሪያዉ የተነሳ ስለሆነ እሱን በተመለከተ ብዥታን አላስተናገድንም። ደቡቡን .ዓፋሩን ባጠቃላይ ሕዝቡን ያስለቀቀሱት እነ ቢተዉ የመለስ አማካሪ የነበሩትን ተወልደና ዓለምሰገድ፣ ገብሩና ስየ የትግራይ ትገንጠል ማኒፌስቶን ፣ዓባይ ፀሃየ ወዘተ ዛሬም “ትግራይ ዓደይ”ከሚሉት ዘፈናቸዉ ሳይርቁና ኢትዮጵያዊነታቸዉን ለማደስ “ፍርጥር አድርገዉ”-“በአጥፍተን ነበር ግለሂስ ሳያጅቡ”እነሱ ይሻላሉ ብሎ መፈረጅ ለጤነኛ ኢትዮጵያዊ ከባድ ነዉ። የእነሱ መጠናከር ማለት ባለፉት አስር አመታት ያየነዉ ዘረኝነት ተጠናክሮ መቀጠል ማለት ነዉና ነዉ። ወያኔ በቀዉስ ሲታመስ የአገሪቱ ነፃነት እየተቃረበ መሆኑን ሲያመለክት፣ በወያኔ ቀዉስ “ቆዝሙ”የሚሉን ክፍሎች “በወያነ ቀዉስ አንቆዝምም ዕልል እንላለን እንጂ!”ወያኔ ከተንኮታኮተ ሀገር ትተረማመሳለች ብለንም እንቅልፍ አናጣም፣ ሀገር እየተተረማመሰች ያለቺዉ በወያኔ ነዉ።ገዢዎች ሥልጣናቸዉን ለማራዘም ሁሌም እኛ ከወደቅን ስምነተኛዉ ሺህ መጣ ማለታቸዉ ተለመደ ነዉ። በዚህ ማስፈራሪያ ወያኔ ይቆይ የሚል ካለ መቸም በወያኔ ስር ቀንበር ያለ ለመሆኑ ያጠራጥራል።ሃገር የምትከፋፈለዉና ለከፋ አደጋ የምትጋለጠዉስ የወያኔ አገዛዝ (በመለስ ሆነ በእነ ስየ”) ባለፈዉ ይዘቱ ከቀጠለ ብቻ ነዉ ። ቀዉሱ ሌላዉ ጫና ሰጥቶ ግልጽ ያደረገልን ነገር ቢኖር ዘረኛዉ ወያኔ በሙስና እንደተጨማለቀና በዘመድ አዝማድ አሰራር እንደሚያምን ነዉ ። የወያኔ ባለስልጣኖች እርስ በርስ የተዛመዱ ከመሆናቸዉ ሌላ (የጻድቃን ገብረተንሳይ ሚስት የስብሐት ነጋ ዘመድ ስትሆን፣ የወያኔ ማ/ኮ አባል ትርፉ ኪዳነማርያም የዓባይ ወልዱ ሚሰት ናት፣ የተወልደ ቦታ የተሰጠዉ ዓባይ ወልዱ የእነ ስየ አንጃ አባል የአዉዓሎም ወልዱ ታናሽ ወንድም ነዉ፣ ሙሉጌታ አለምሰገድና አለምሰገድ ገብራምላክ ዘመዳሞች ናቸዉ።የቅዱሳን ነጋ ማለትም ስብሓት ነጋ እህት ባል የትግራይ ሃላፊ ተብሎ በመለስ የተሾመዉ ጸጋይ በርሐ ነዉ፣ ወዘተ….። የዉልደት ቦታ ክፍል ባይኖርም የምርጦቹ ዓድዋዎቹ በሌሎቹ ዘንድ ተቃዉሞ ማስከተላቸዉ አልቀረም።ይህም። ይህም የቤተሰብና የጠባብ ክልል አልፎም አሰላለፍ ጉዳይ ደግሞ ከቀጣዩ ችግር አንጻር ቦታ ያለዉ ነዉ። እንደተለመደዉ ባዕዳን የሃገሪቷን ቀዉስ ይዘት መረዳት ያቃታቸዉ ከመሆኑ ሌላ የእነ ስየ እንጃ የወያኔ ዝቅተኛና መካካለኛ ደረጃ ካድሬ “ሁላችንም እኩል ነን”ባይ ቅዠታም አስተሳሰብ ለማስተናገድ ሲሉ አጼነትን (ሓፀይነት)ን ማዉገዝና የካዱትን ርዕየተ ዓለምንም ሟጯጯህ በመምረጣቸዉ ባዕዳኑ መለስን ለዘብተኛና የካፒታሊስት ተንከባካቢ ብለዉ ሲፈርጁት እነ ስየን ደግሞ በአክራሪ ግራነት (ማለትም አደገኛነት)ፈርጀዋቸዋል።ያም ሆኑ ይህኛዉ ብርሌ ከነቃ አይሆንም ዕቃን ያስታዉሰናል። ዕልል ሲያንስ ነዉ። ባጭሩ የቀዉሱን ሂደት ስንገመግም “በባእድ ሀገር የሚገኙ በርካታ ትግራዊያን የእነ ስየን አንጃ ደግፈዋል ለዚህም መሰረቱ የትግራዋይነት የበላይነት መቀጠል ፍላጎትና ፀረ-ኤርትራነት እንጂ ለኢትዮጵያ አዲስ ነገር በመመኘት አለመሆኑ ግልጽ ነዉ’’። በዚህ አንጻር መፈክራችን በሀገር ጉዳይ ሕዝብ ይወስን፣ ወዘተ… የሚል መሆን አለበት። የወያኔ ጉባኤ ተካሄደ አልተካሄደ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ጉዳይ ሊሆን አይገባም የዚች ታሪካዊ ክብር ሀገር ዕጣም በወንበዴና ከሃዲ መንጋ ጉባኤ ሊወሰን ሲሞከር ዝም ብለን ማየት የለብንም። ይህ ብቻ አይደለም ቀዉሱ በር ከፍቷል።ዶክተር መስፍን ወልደማርያም “ወያኔ ከፈተዉ”ያሉትን የ “ዲሞክራሲ በር”ማለቴም አይደለም።የተከፈተዉ በር ወያኔን መወጠርያ ትግልን ማፋሚያና ከሆነም ወያነን ጠራርጎ ከታሪክ ትቢያ መቀላቀልያ ነዉ።ከዚህ ባሻገር ደግሞ በወያኔ የንግድ ተቋማት ላይ ዕቀባን ማወጅ የወያኔ ኩባንያ ያመረተዉን ልብስ ላለመልበስ ቢራዉን ላለመጠጣት፣የመሬት ምሪቱን አለመግዛት፣አገር አቀፍ አድማ ተግባራዊ መሆን ይገባዋል።በአንጃ ተከፋፍለዉ ሲፋጁ መገላገል ሳይሆን ስለት ማቀበልና ቀዉሱ በፈጠረልን ቀዳዳ ሁሉ መጠቀም ይኖርብናል መለስ በበኩሉ በሥልጣን ለመቀጠልና ሀገራችንን ለማጥፋት ጥረቱን ቀጥሏል።ብርሃነ ገብረክርስቶስ በአሜሪካ ያሉትን ትግራዊያንን በመለስ ዙርያ ማሰለፉ አቅቶት አብዱል መጅድን አጅቦ አዲስ አበባ ተመልሷል።ሁለቱም ለሹመት ታጭተዋል ይሉናል።ለናይሮቢዎቹ የትግራይ ተወላጆችም ተወልደ ገብሩ (?)ተመድቧል አሉ። ኢትዮጵያዉያንን በሞላ የሚያናግር ግን አስካሁን አልተገኘም።ማን ከቁም ነገር ቆጥሮን! ሀገራችን ተቀምተን መሳለቂያና መጫወቻ ከሆንን አስር ዓመት አልፎ የል?።//-/ ከኢትዮጵያ ሰማይ ኤዲተር-- /- ዛሬም አንቀጽ 39ኙን አንግቦ “ኣለና!!!!” ብሎ ብቅ ያለዉ የእነ ገብሩ አስራት “ዓረና ትግራይ”እና የትግራይ ወንድሞቻችን “ዕልልታ”-ከላይ ያነበብነዉ ማህደር ስታገናዝቡ በወቅቱ ለነገብሩ ደህንነት የሳሱትን ወንድሞቻችን ዛሬም አንቀፅ ሰላሳ ዘጠኝን አንግቦ ብቅ ሲልላቸዉ ድጋፋቸዉ ለምን እንዳልነፈጓቸዉ መረዳት ትችላላችሁ። እነሱ ብቻ ሳይሆኑ መድረክ ተብየዉ “አዲስ ዕቃም” አንቀጽ 39 ይዞ ብቅ ሲልለት አቅፎ መደገፉ “ለኢትዮጵያ አዲስ ነገር መመኘት አለመሆኑ ግልጽ ነዉ።ምስጢሩ ግልጽ ነዉ፣ “ትላንት”-መለስን የአስመራ ቅጥረኛ ስላሉ “ዛሬ”-የወያኔ መንጋ ስለደገፉ ተቃወሚ ብለን-ከምር-መዉሰድ ይከብዳል!መልካም ፋሲካ ይሁንላችሁ! http://www.ethiopiansemay.blogspot.com/

Wednesday, April 15, 2009

The harrowing stories of TPLF mass murders in Tigrai as told by a surviving elder. Posted Ethiopian Senmay by ጌታቸው ረዳ



The harrowing stories of TPLF mass murders in Tigrai as told by a surviving elder

By

ጌታቸው ረዳ

Posted

April 2009

 According to many of your request, here is the English translation of the Tigringa version interview of Fitawrari Gezai Reda. (Editor- www.ethiopiansemay.blogspot.com).

Let me start my view by quoting from an article I read a few years back from Ethiopian Register magazine, under the topic: “Understanding the Machine of Woyane Politics and How It Works." In that commentary, the writer tried to show how the Ethiopian people were trying to identify the government of TPLF and the nature of it. The writer says,

 “As critics and opponents of the Meles regime, we often look like those fabled individuals who try to identify a large animal blindfolded. One character touches the animal’s head, another its back, still another its legs, each one giving an account of the whole beast by the part of the beast it has felt." Similarly, opposition parties and groups describe the Woyane political creature in various limited ways. Some say TPLF rules are similar to an Apartheid-like ethnic tyranny. Others draw parallels with a Marxist-Leninist clique. Still others equate TPLF with a shifta (banditry), two-faced par communist, par capitalist, political entity. We also mark the regime as a worari (occupying) force, clever at operating behind tribal lines, reminiscent of colonialism, yet quick to resort to frontal assault on dissidents, citizens, and communities to bolster its monopoly of power.” End Quote.

Each of these outlines of TPLF rules is right, but only partially. Each depiction highlights a particular feature or element of the Meles dictatorship.” Indeed, as the writer above tried to show the different features of TPLF, each one of these taken separately, or as a mere sum, the depictions do not, however, yield an adequate picture of the gangsters of Woyane Tigray . Even as mercenary as it is, stating Meles and his groups as group of “Banda”, still we can’t describe the nature of the political beast! The nature of the gangs should be interpreted in ways worse than what has been said for years. Can I simply say, “These are beasts dispatched from hell?

Many of us may not have the detail understanding and information how Tigrian farmers and citizens were the subject of these beasts for solid seventeen years. Because of our frustration, many of us blame the Tigrians for harboring the beasts for seventeen years, but in reality the Tigrian farmers and people have suffered more than all of us can imagine. Sadly ethnic affiliation is weird; to that extent still Tigrayan majority supports and likes this fascist beast gangs from hell called TPLF.

Leaving the weakness and the failure of the flamboyant members and sympathizers of the beasts, and leaving aside for a moment, the ugly record of the Tigrian intellectuals and all walks of Tigrians who defended and supported the cruel nature of TPLF leaders and their Bado Shidushte (06) (the notorious security apparatus of TPLF),  for many years, without any doubt, the majority of the Tigrian people, particularly “farmers,” were the direct victims of TPLF savagery more than any society in Ethiopia during the 17 years of the TPLF jungle territory control in Tigray .

In this report you will read a very shocking history from an elderly man from Tigray. Ato Gezai Reda, who was tortured and released after paying Birr 15,000 ($7,500.00 at the time of that era’s dollar exchange rate), after he was captured by TPLF guerrilla fighters in 1969 EC (about 1976/1978), and recently exposed the cruelty and injustice done to the Tigrian farmers and citizens by the so called leaders of Woyane Tigray in his interview with Dejen radio, produced by my friend, Dr. Hailemariam Abebe.

 

 I am working on the full translation of the interview in Amharic, to be published in one of the national papers (already published) . Till then, take the idea home, weigh the gruesome and utterly despicable nature of TPLF, the mass murders and tortures it inflicted on thousands of Tigrians.

Here is the short summary of the Tigrigna interview I translated into English for those who cant read or understand Tigringa:

I have some extensive audio interview that I did with him separately outside the following version of interview. For now, I will present the interview he did with Dejen radio.

Ato Gezai Reda is originally from Enderta (around Mekelle), but worked and spent most of his life in Shire Awraja (Enda-Selassie). He was an employee of the Ministry of Interior before his ordeal. Ato Gezai expresses his thanks to Dejen radio for having him as a guest, and for getting the opportunity to expose the crimes of TPLF to the Ethiopian people, after keeping them with him for many years for lack of a free forum. Ato Gezai Reda, after briefly explaining about his life history, directly goes to his narration. In the mid-'70s, he was a member of “Teranafit” (a group established in shire district before it merged with Prince Mengesha Seyoum's armed rebel group - the Ethiopian Democratic Union - EDU). He said TERANAFIT at first had no intention of fighting against TPLF.

Teranafit was established to fight against then military Junta in power - the "Derg." But TPLF accused members of Teranafit of being “rivals” in recruiting the Tigrian youth. Because of this, he said he and other Teranafit members came under the focus of TPLF hostility. Ato Gezai Reda was captured in March 1969 (1977/78) when he and others were travelling by bus to Axum to celebrate the religious holiday of Hidar Tsion. TPLF fighters threw hand grenades and ambushed the bus in the vicinity of “Af Gah-gah”. Held at gunpoint, the rebels ordered three passengers to get down, and those were: Ato Gezai, Ato Feseha, and Ato GebreTsadik Woldu.

The three "captives" were taken to a locality called Mai Demas, where they were thrown into a closure, and spent a bitter cold night along with livestock. The next day, says Ato Gezai,

"we were taken to Badme. Along the way, every village we passed by, there were many young farmers and elders who were being rounded up by TPLF as Teranafit accomplices." Ato Gezai and other 50 prisoners were taken to a place called Ginbot (near Badme). Ginbot was lush green, and had several springs that watered the site. "Upon our arrival," says Ato Gezai, "all of us were ordered to roll over a field covered with ash which was so thick and over a feet or two high. We did as ordered, but fell to severe coughing, sneezing, and itching. Once our introductory lesson was over, we were thrown into a tiny cell, joining other prisoners who had lost their hairs due to inhuman conditions. Those who were imprisoned before us were seriously emaciated, like they have been starving for a long time. Parts of their bodies were burned with fire, and their skins had turned yellow. With their sunken eyes, they looked like lifeless skeletons.

Their legs were swollen, and their voices coarse." Some of the young men whom Ato Gezai saw in that prison cell were students from Adi-Awala, Adi Dairo in Shirre. The other victims included individuals who suffered from "manic depression," and had already lost their minds, understandably from the complication of constant exposure to cruel torture and loss of hope in life. The next morning Ato Gezai was interrogated as an accomplice of the Teranafit rebel group which TPLF saw as a sworn enemy.

On the second day, they woke Ato Gezai up, took him out, and tied his hands behind his back against a tree, and set a pile of firewood between his legs. He was fixed to a tree trunk as the TPLF guys used tight ropes and wires to wrap him by. They started the fire between his legs, and Gezai Reda's long journey into the world of hell controlled by TPLF starts in earnest. As a thick smoke chokes Ato Gezai, the fire has already created blisters all over his body. Out of desperation, he shouted "Kidus Michael! Kidus Michael..." His torturers heard what he said, and started to make fun of him. The torturers picked up two small rocks and rubbed the stones against each other and, mockingly, asked their victim: “Can you see your St. Michael in these stones?” (At this moment on the Radio, Ato Gezai is overwhelmed with emotions of grief, and slips into silence)

He comes back on air, and continues his narration. "The fire was too much painful," and I cried out: "The fire Is Hell!", and said, "My brothers and sisters! I can't move left or right. I am being eaten up by the fire. You bet Hell is better than enduring this cruelty!" My hands were tied behind me to a tree; there is no way one can escape from the chocking smoke and the flames of the burning wood. My body started to swell like a balloon. My body was covered with blisters, containing water under the swollen skin. And at one time, my skin burst and gushed out water from my entire body. Then my torturers ordered a break, using the military code “erefti!” (Recess/ break!).

After this unbelievable torture of burning and roasting my body with fire, they took me away from the fire, and untied my hands. I was lying on the ground, from where I slipped into unconsciousness. I can’t remember how long I was in a state of shock. I only knew when they woke me up again, and ordered me to stand, walk, and sit back to the burning fire. I couldn’t move my body! I was burned, numb, and roasted; my throat and lungs were coarse like burned; I couldn't talk either. Practically, my body was turned into the size of a monster; my eyes were hanging out of their sockets. My tormentors also knew I that I couldn't move. They looked for other means. They burned a bunch of figs, and threw the fire onto my body. After a few days, I woke up, and tried to make sense of where I was (mind you I was still in severe pain and mentally devastated).

But once more, they took me out in that bad shape, when I was looking just like an invalid. I was asked if I'd learned anything from my being tortured. The interrogator asked me if there was something I could make as a confession. I said: “Other than being a member of Teranafit, I have nothing to confess; I did nothing wrong that harmed TPLF; if there is anything, please show me any evidence of wrongdoing than torturing me for a crime I know nothing about." I begged them to tell me if I'd done anything wrong to them. Ato Gezai went on to say, “The interrogator didn't whet his thirst of cruelty, and said me, 'You still didn’t learn a lesson after all that?!

 He then ordered the torturers to take me back to the torture chamber, where I was hung upside down, and the interrogators started to beat my bare feet with a rubber stick. My body started to burn like I caught fire: I shivered, vomited, moaned with unbearable pain. By the way, I still have difficulty walking, and I often feel pain in my feet.” “Those are not Tigrians, those are not Ethiopians; those are some evil creatures from hell! They have no respect for even to the elders. They were educated by us, by the Tigrian parents; they were schooled by the farmers' and tax-payers' money, they were armed by Tigrians but turned their back on us, and humiliated us in a way difficult to express in words.”

Question- Other victims? 

Ato Gezai:– There were many of them. At least eight people were being executed every day. Every morning, many young ones from among the prisoners would be called out by their names. The prisoners knew they were being taken to be murdered. The young ones would cry, scream, saying, “tell my parents and families that I am executed...goodbye Tigray! Good bye folks!” Mass murder was routine. I can tell you a few more agonizing stories as to what extent TPLF’s cruelty stretches. The crimes of TPLF that I saw with my own eyes are chilling." “There was this elder who was highly respected in Shirre Endaselassie. His name was Gebrelibanos Mezgebo. He was a chief accountant employee of the Ministry of Internal revenue. He and a few other respected individuals like him were selected by the people of Shire and surroundings to go to TPLF bases, and meet with TPLF officials over how to peacefully resolve the war with the Derg.

The idea was proposed by the Derg officials. The Derg explained to the elders of Shirre that war was killing the nation, and such peaceful plan was also being executed in Eritrea. Eritrean elders were also elected by residents to go to the mountains to meet the rebels over a possible dialogue with the Derg. The Derg proposed they can solve their differences with EPLF-ELF for the sake of peace to the war-torn country. Likewise, the elders from around Shirre went to TPLF-held areas so as to meet and discuss the issue with them.

"Mind you!" says Ato Gezai Reda

“...these are respected elders, who know nothing about politics, or who have never been members of any political group. But since the Derg officials ordered them to do something to resolve the conflict, they went out as peace envoys, shouldering responsibilities both by the people and the Derg. The residents also gladly agreed to try the strategy if that would work out for the sake of peace. The elders met TPLF leaders, but they were unlucky: they were thrown into prison immediately.” Dejen radio - And then? Ato Gebrelibanos and the other elders were murdered.

Question:- How come?

Ato Gezai - Well, it is a very sad and shocking scene to witness such tragedy taking place in ones presence. One night EDU rebels came to the vicinity with their full military might. Subsequently, TPLF “firing squads” rushed to where we were being held. And we heard the interrogators saying loudly, "Let us Kill them! Let us finish them!" Immediately, they opened the door and ordered us to line up. They wanted to carry out the execution there and then but they changed their mind, and rushed us to a gorge covered with thick forest. However, they delayed the execution for reasons we did not know. “Let me take you back for a second, to the question of what happened to Ato Gebrelibnos Mezgebos. As I said earlier, we were told EDU rebels were encircling the area. At that moment they tried to kill all prisoners. But later on, they decided to rush us somewhere else. However, Ato Gebrelibanos was badly burned and tortured like myself. He was a sad sight to the eye. He had open wounds on his back and his legs. He was almost crippled from torture. The TPLF decided he should be put to death. THEY FIRED THREE SHOTS INTO HIS BODY AND MURDERED HIM where he was lying!". “With him, there was also a very handsome young man who was their member, a “guerilla fighter," who fell sick with severe malaria. He was shivering with high fever, was unable to walk. He was lying under a shade from the outside of the prison cell that housed us. He was there just to rest and get some medication. He too was shot to death by the firing squad in his sleep. They executed him on the spot because he was unable to walk with the rest of us. This young fighter was from a village called Enticho (Adwa). They pumped three shots into each of the two victims in a cold-blooded murder.

 Question:– Why did they do that?

Ato Gezai - They didn't want to carry them.

Question;-They shot and killed their own fighter too?

Ato Gezai - Yes, they were cold-blooded murderers who had no value for human life. I have no idea how such youngsters came out from the womb of Tigrians and turned into some despicable monsters!

Question: - And then?

 Ato Gezai - We left the two murdered gentlemen behind us as we were rushed to a place called Maay Lam (Mereb). It was very hot, humid, and sand. Many of the prisoners had a difficult time dragging themselves along a very hostile terrain. Many of us never had any exercise, let alone overcome long journeys atop our tortured bodies. We had no power at all. Many of us had headaches, dizziness, and were thirsty and exhausted. Those who were limping and had fallen behind, the rebels pulled them like they were animal carcasses to be disposed of. Rebel harassments were rampant against those who staggered on the way. Among the weak prisoners, I remember there was a respected elder, Balambaras Tilahun. He was from Deki Awuaala. They wanted to riddle his body with bullets. Fortunately, when they were ready to do just that, some higher official of the organization came to the scene, and the firing squad asked the official if they could kill the man whom they saw as a burden. The official asked them if his interrogation was finalized. They said "no." He told them to first get over the investigation. The old man was spared, and was suggested they somewhat carry him. However, they tied him tight to a single long stick (It was supposed to be a stretcher).

They went away rocking the old man left and right his body tied/hooked with that single stick. Finally we reached a place called "La'e-Lai Barka/Uper Barka/ (may be close to Eritrea border), and it was time to spend the night there. On the same night, they told us there would be assignments, and they split us in two: Group A and Group B (the reason was one of the groups would go to the Red Cross for check-ups, while the other would take other assignments. That was what they said).

We formed long columns, but we were worn out. Immediately everyone was asleep. But again in the same night, they woke us up, and called the names of 25 individuals. They took them to a nearby ravine, and in an outburst of gunfire, the 25 were murdered en masse. That day was Ethiopian Easter holiday. The way how the gentlemen were killed was really frightening to human mind. They told the victims to line up like soldiers but they machine-gunned them down all at once. The killers didn’t even bother to bury the victims. Their bodies were later found by Eritrean cattle herders. When the cattle came closer to the sight, they began to retreat as if they had seen predators. This alerted the herders who became curious why their cattle were frightened, and suddenly saw the bodies of 25 Ethiopians murdered at one go.

 "It is really heart-wrenching to recall such tragedies despite the passage of a long time," says Ato Gezai. He mentioned some of the executed individuals by name. Among them: Ato Tewolde Gebresilassie (a town council official from Endaselassie - Shire) Ato Abebe Gebre-Mariam (an old man from Adi Beiray, Deki-Awala) Wodi Goshim, a 16-year-old from Endaselassie. Mohammed, a 12-year-old boy from Adua who came to the Selekleka to visit his aunt. In prison, the boy always cried, saying he wanted to go to his mother and his Aunt and would often ask them "what am I doing here? I want to go to mom”. Altogether with the kid, 25 people were slaughtered.

 By the way, after the herders discovered the mass murder, they immediately notified ELF fighters. The ELF men were shocked, and held an official meeting, and expressed their disappointments by the gruesome murders TPLF committed. ELF told TPLF to move out of their territory. TPLF fighters who were guarding us shared the secret with us. Some of the fighters were very close to us and sympathized with our condition. It was their closeness and sympathy that helped us to get the information that TPLF had differences with ELF with that incident. Unfortunately, many of the prisoners were murdered, (even after the ELF ordered TPLF, move out itself and its prisoners from their area). Those murdered, were murdered in the same fashion: “summary execution!”

 After they relocated us, there were killings as well. There were prisoners like Haleka Tilahun (Adi Hagerai?) , Yigzaw Hailu (I think if I am not mistaken he was the son of Kegnazmach or Dejach Hailu Aduwa). Yigzaw was unique than the rest. He was a strong man. He killed one of the executioners, and stabbed another with the executioner's own knife, and fled on foot. They pursued him with a barrage of machinegun fire. They shot him, but could not find him, dead or alive. After a week, however, his death was confirmed when vultures were spotted, and they were scavenging on the corpse.

Question: - What happened to you finally?

 Ato Gezai - I was told I could bail myself out by paying them Birr 15,000 (then the equivalent of $7,500 U.S. dollars). They ordered me to write a letter to my wife to make the payment. I pleaded for lesser settlement. They told me “TPLF is not a market place for bargaining." Finally, I wrote a letter to my wife and they took the letter to her, and she sold our hotel (the only source of income we had to support my children and my wife at that time while I was under TPLF custody). My wife had no other choice, and she sold our property, met one of the agents, and paid him 15,000 Birr.

 I was released but there was a string to it: If I talked about TPLF brutality, I would be hunted down. No mercy! And they had these so-called fedayeen, (disguised TPLF snipers who infiltrate towns either to kidnap victims, or else, murder them.)…

Question: -

 We have heard many people lost their finger-nails, and fingers and limps were being pulled off the bodies of victims during torture. And we heard TPLF was forcing its victims to dig their own graves before they were shot dead.

Question:-It that true?

Ato Gezai - Many despicable things have befallen too many innocent people. One day, they decided to kill me. My hands were tied, and I was watching when they were digging my grave. They dug it themselves because I was too weak to do anything. I was tied very tightly, and asked them: “My hands are tied and it is hurting me badly. Can you please loosen the rope?" One of my guards got upset and said: “This is your grave; in our law, you were supposed to dig your own grave. But because you have no muscle to do that, we are doing you a favor. Therefore, you better shut up and get ready to enter your warm grave!”

I was put down in the grave. Then, the firing squad gathered and started to lower down their heads to the ground with their formal whispers (prayers par communist zealots), called “zikri sema'atat” (a prayer in memory of our martyrs). When they prayed their version, I was also praying loudly: “ABUNE ZEBESEMAYAT... (Oh, our Heavenly Father...) at that moment, one of them by the name “Mesele” asked me, “what are you chanting for?" When he was asking me this very question, another messenger called Alemseged came running and screaming so loud towards us. They said, "who is that guy?" He screamed so loud from a distance, and told them, "wait, wait! Don’t do anything! Don’t kill him!" Alemseged told them higher officials were saying that the prisoner had more interrogations and should be spared of the execution.

The amazing thing was a member of the firing squad was my neighbor’s son by the name “Nuguse Lilai”. This young man was a promising soccer player in Shire Enda-Selassie, back in the good old days. At that time, I used to encourage him and his friends to pursue their sports. Occasionally, I used to support them financially. I also used to take their pictures, extending some form of fatherly help. He was the first one who jumped into the grave, and pulled me out, by cutting the rope that had tied my hands. I saw him and his friends beaming with joy in the presence of the executioners who were suddenly ordered to delay my death. However, I felt like they were playing with me like a toy. I begged them to finish me off. I asked them why they were playing with my soul, and asked them to fire a single shot, and get over with me, instead of taking me back and forth to the same hellish life. They replied, “We have orders that you have more interrogations."

So to answer your question, "Yes, they used to make us dig our graves before they killed us. Indeed, they were evil, anti-Tigray, anti humanity, anti their own family, anti Ethiopia, generally they were demons from devil knows where."

Question: – you have seen and witnessed all these nightmares, and the unbelievable evilness of TPLF. I think to my understanding hearing this shocking story, do you think you considered them as Tigrians? This is barbaric. Their action is even worse than Fascist Mussolini’s atrocities. How were you judging them at that time?

Ato Gezai — Oh! We took them as the disciples of Satan. Given their lack of humanity, I could only say I was saved by the power of God! They were cruel. They fed us very salty food so that we would feel thirsty, and they would punish us by denying us water. They added gasoline to the injera and soup so that we would suffer with hunger. It is hard to explain their cruelty.

They kept prisoners in dungeons; there were dungeons in Kalema (Jihanem) near Gondar, another one in one of the Tekeze River hills, and another in Tembien. Those underground prisons were dug beneath the hills. I heard it was very hard for strangers to tell if there were underground prison chambers or not.

Question - Have you had children at the time? Did they ever know where you were?

Ato Gezai - I had young children, all of them under seven. They didn’t know where I was till my release.

Question - After your wife sold the hotel and paid TPLF the money they had asked, how did you end up going back to EDU? What forced you to leave town?

Ato Gezai - Let me tell you, whether I like it or not, they could have taken the money anyway.

Question:- How is that?

Ato Gezai - What they did to many innocent families, they could have done to my wife too. There are more and more sad stories. For instance, they execute their victim. By the way, they cover the heads of their victims with some sort of garment. Then they execute them. After that, the TPLF prepares a letter as if it were written and signed by the victim. TPLF would write as though the victim was alive, and was a dedicated fighter. In the letter, they would write as if their victim would tell his family that he would never abandon TPLF, and for his cause, he was dedicating the family property to his organization “TPLF”.

So when the family gets the letter, given the reign of TPLF terror in the area, would be forced to hand over the property. Don't forget TPLF has already killed the individual. Many families were robbed of their children and property by such sordid TPLF crimes. They never cared that their victimized family had kids, and would perish to hunger.

 Let me tell you about the fate of one promising businessman in Adi Hagerai, Adiabo. His name was GebreTsadik Tsige, the son of Haneta Tsige. They were of Eritrean origin that lived as good Ethiopians. The young businessman had heavy-duty trucks and over a thousand heads of cattle. They killed him. On top of that, they ordered his wife to pay Birr 12,000. She said she had 6,000 Birr to pay right away, and not the entire sum of money. She asked them to give her more time. They demanded she had better paid the full amount right away. When she could not find the money, they took the trucks, 500 heads of cattle from the family ranch.

Now, let me go back to your question and answer what happened to me after I was released.

I gave my hand to Colonel Kale-Kristos Abai, then regional governor of Tigrai province. I visited the colonel's office, where I was interviewed by the governor himself and other attending senior officials. Upon hearing my harrowing stories of tortures and mass killings, they were heart-broken, shocked and truly disoriented. On my part, I begged them to keep the stories to themselves. "If the stories leaked and reached TPLF," I told them, "they will kill me. No doubt about that." But the officials were overwhelmed with the gruesome murders TPLF was carrying out against innocent people. They immediately called for public meeting with the residents of the town. They began to tell the people the crimes being committed by TPLF.

At that moment, they wanted an eye-witness, and called my name to testify. I heard them calling my name, but I kept quiet. I did not want to risk my life for I knew TPLF would murder me. In the first place, I didn't want to disclose TPLF crimes to the Derg. But the Derg was also another problem, and I had no choice but to tell them what I went through. Immediately on the third day, TPLF sent me a “death warrant.” They sent one old man relative of my family. The letter told me to get prepared for my death any time.

I prepared myself in a few days, kissed my kids and my wife good-bye, and after a long trek through the jungle, I joined EDU combatants.

Question:- Dear Ato Gezai: You have seen TPLF in detail. TPLF is anti Tigray, anti Ethiopian culture. They changed everything, even the names of villages and hamlets. They devalued the honor of our mothers; they chopped away our territories, and ports preserved by our forefathers. Would you share your views with us on these points?

Ato Gezai:- “TPLF is insane; they are evil, anti Christian, anti religion and anti our culture. They went against Tigrian culture. They desecrated churches. They smoked cigarettes inside churches. They turned churches into dancing halls. They tore down holy church garments and used them as sacks for stolen goodies. They used Medhani-Alem churches in Sheraro as their dancing floor for their "artistic troupe." They forced elderly priests to lead their dances. They forced priests to throw their crosses, and made them carry guns and forced them to shoot. This was the most disturbing time in the history of our country. After having been an EDU combatant, I was forced into the world of exile, and I will never be able to visit my country until I make sure TPLF is removed and gone forever.” Concluded Ato Gezai Reda.

NOTE FROM GETACHEW REDA: Who is Ato Gebrelibanos Mezgebo? I am his son in law. Ato Gebrelibnos Mezgebo is from Yeha, near Adua. His wife, Woizero Yeshi is from Aduwa, Yeha. Woizero Yeshi, an elderly mother is still alive with her 7 children and many grand children. Justice will reveal, murderers who killed elders and young children as old as 12 years would one day face the wrath of justice.

The cold-blooded murderers can fool only to the fools pretending like they are peaceful individuals and peaceful leaders not for those few of us knew who they were and still who they are. Regardless of their camouflage, their blood-soaked life would one day end up in front of the court of justice.

I thank Ato Gezai Reda from my heart, and Dejen radio in behalf of the family. The family may not question TPLF currently for fear of persecution. We the family are many and we are everywhere to challenge the thugs and murderers. Justice will prevail! There will no more be a mystery. The curtain that had covered the criminal and murderous nature of TPLF is uncovered for all to see, and for all to add their voices they had up to day kept for themselves for fear of being added to the long list of the thousands of men and women TPLF firing squads murdered in the quiet fields of northern Ethiopia.

In Recent interview, Fitawrari Gezaie Reda exposed his torturers and prison chiefs who sent many young kids and elders to their death chamber as Abebe Teklehaymanot (filed name Usman) he was the ETPLF/EPRDF Air force chief. Awalom Weldu (real name Tiku Weldu- the brother of Abay Weldu currently Abay Weldu is TPLF’s CC) – Awalom was the first TPLF/EPRDF Ethiopian Ambassador to Eritrea. (Currently, Ass/chair and CC of Gebru Asrat’s “Arena” party).

Mesele was also the x-Derg Lieutenant Officer, who later fled to TPLF and became one of the executioners. The story will be published in book version for history to document it (update- already published). getachre@aol.com (Ethiopian Semay) ጌታቸው ረዳ _//-

 
.com

Sunday, April 12, 2009

የትግራይ ተወላጆች ትዝታቸዉና ትዝታችን




የትግራይ ተወላጆች ትዝታቸዉና ትዝታችን
“እዚህ ዉጭ ሀገራት የሚኖሩት የትግራይ ተወላጆችም በህወሐት ዉስጥ ስለ ታየዉ መከፋፈልም ሆነ ስለ የትግራይ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገብሩ አስራት ከስራ መወገድ አስመለክቶ ግራ እየተጋቡ ነዉ። እዚህ ዩናይትድ ስቴትስ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆችም በጉዳዩ የተቆጡ የጥቆቶቹ ተወካዮች አንዳንዶቹን ተወካዮችን አነጋግረናል”። የቪኦኤዋ ጋዜጠኛ አዳናች ፍስሃየ ነበረች ይሄነን ዘገባ ያስደመጠችን (“የዛሬ 7 ዓመት”)፡ ወቅቱ ትዝ ይላችሓል?ወቅቱ የኢትዮጵያ አምላክ ጠላቶቿ አንድ ባንድ ይበታትናቸዋል ሰንል “ይሳቅብን” የነበረበት ወቅት ነዉ። ያዉም እንደዛሬ ዙርያችን ሁሉ የሸራቶን ጠረፔዛ አሟቂ የነበረዉ ሁሉ ባልታጠረበት ወቅት፣ በጣም .እጅግ በጣም አናሳዎች በነበርንበት፡ ሽዋዉአን ተጋሩ!አማሓሩ፣ ተስፋ የቆረጡ፣ ደርጎችና ነፍጠኞች በምንባልበት ወቅት፣ የወያኔ ጎረምሶች ደረታቸዉ በጠብስና በክትፎ ቅቤ ተደፍኖ፣ የሚሆኑት አጥተዉ “ኤርትራዊት አዶ እዚ ኩሉስ አይሳላኺንዶ” ዘፈን አንግበዉ፣ የሻዕቢያ ባንዴራ ሙትት አድርገዉ እየሳሙ፣ እያዉለበለቡና እየዘለሉ “ምን አባህ!” ሲሉን በነበረበት ወቅት! አይ! አይ! አይ ጊዜ መስተዋቱ! ሁ….ሉ…..ም!!!!!!!! አሳየኸን! አየ ተላላዋ “ገመል” እንሰሳዋ! ልቤን ሰቅዞ የሚይዝ ቃል ቢኖር ይኼኛዉ ቃል ነዉ፡ “ትዝታ!” የፍቅር ትዝታ። መጥፎም ደግም ትዝታዎች አሉዋቸዉ። ሁሉም ባንጀት ዉስጥ ይሰፍራሉ። ያዉም በጣም ከዉስጠኛዉ ክፍል ከጎድጓዳዉ ስፍራ ሁሉም ከሚደብቅ፣ ሳይታዘዝ ሳይታስብ “ብቅ” ይልና በትዝታ ልብን የሚሰቅል የሚያከንፍ በቃጠሎ ልብን የሚያነድድ፡ አይ ትዝታ! የረሳችሁት አንጀት የቋጠረዉ የድሮ ፍቅር ቢኖርባችሁ ቀሰቀስክብን እንዳትሉኝ ትዝታዉን ትቼ ወደ ፖለቲካዉ ትዉስታዉ ልዉሰዳችሁ:፡ እኔ እንደታዘብኩት ፖለቲካም ክፉ ፍቅር ያስይዛል፡ “ካልት”ይሉታል ፈረንጆቹ ። ያነሆልላል፣ ያሳብዳል “መሰዋእቲ””ይሉታል መሰለኝ ‘ተጋደልቲ’!“ሌላን ፍጡር አስከመግደል ራስንም አስከ ሞት መስጠት”-የሚያደርስ ኩፉ የድርጀት ፍቅር። ያዉም የጎሳ እማ ክፉኛ ለክፎ ያስሳብዳል።የጎሳ ፖለቲካ ሲወሳ ትዝታችን የሚያስታዉሰን እዉጭ የሚገኘዉ ምናልባትም 95ከመቶ የትግራይ ተወላጆች “ለወያኔ ትግራይ” አልያም ለጎሳቸዉ ያሳዩት ትኩረት ከፍተኛ ነበር። “የባድመ ጦርነት ምስጋና ገብቶት አይግባዉና” ወያኔዎች ለሁለት ሲሰነጠቁ “እሩቅ እጅግ በጣም አሩቅ”ጥሎዉት የነበረዉን የኢትዮጵያዊት ባስቸኳይ በነብስ አድን ፍለጋ ዉስጥ ገብተዉ “ኢትዮጵያ! አገራችን!” ሲዘምሩ ብዙ ሰዎች ተስፋ አድርገዉ “እንሰሳዋ ገመል”የናዚ ንቅሳትዋን በላጲስ ለማጥፋት ሕሊና ለበሳለች ብለዉ ነበር። እንደተጠበቀዉ ሳይሆን ቀረና-የግመሏ ተከታዮች ትንሽ ሳይቆዩ “ሶሊዳሪቲ ትግራይ” የሚባል ድርጅት መሰረቱ፡ እርስ በርስ ተናከሱና ተበታተኑ። ችግራቸዉን ላለማወቅ ለብተናዉ ምክንያት በመለስና በስብሓት ነጋ ካድሬዎች አሳብበዉ ተበታተኑ፡ የጎሳ በሽታ ል ዕድሜ ደርሶ ሲጓዝ ሀገራዊ ራዕይ ስለሚያጥረዉ ይበተናል። ሲበተን ሁሉም አባሎቹ ኩፉኛ ይደናገጣሉ::ዙርያዉ ሁሉ ጠላት ስለሚመስላቸዉ የፈረሰዉ ለመጠገን እንደገና ይጥራሉ::በዉጭ አገር የትግራይ ተወላጆችም ሆነ በዉስጥ አገር የትግራይ ተወላጆች ዘንድ እየሆነ ያለዉ ትዕይንት ይኼዉ እንደገና አሁንም መልሶ መላልሶ በጎሳ የመሰባሰብ በሽታቸዉ እያገረሸባቸዉ ነዉ። ዛሬም ተምልሰዉ በወያኔ ትግራይ በእነ ገብሩ አስራት ትዝታ ተጠልፈዉ “በዓረና ትግራይ” ለዳግም ግንጠላ ይሁን ኩርፍያ ለብቻቸዉ እንዲጓዙ መንገዱን መልሰዉ እየገነቡት ነዉ:: ይኼ ሞኝነት ይሉታል አንዳንዶቹ፡ እኔ የምለዉ በሽታ ነዉ፡ ጎሰኝነት በጣም ሃይለኛ በሽታ ነዉ ። ከዛ ገትፍፍግ ብሎ መወያየጡ “ኣጆኻ! ኣጆኻ!” ወገንተኝነቱ የተከናነቡበት ብርድልብስ ወርዉሮ መነሳቱ ለአደጋ የሚያጋለጡ ስለሚመስላቸዉ በጎሳ ጠረን ያደፈዉ ብርድልብስ ከገላቸዉ ገፍፍዉ መጣል “ሞት”መስሎ ይታያቸዋል። ከነ ገብሩ እና ከነ አረጋሽ ከነ አዉዓሎም ወልዱ ከነ ስየ አብርሃ ሌላ መለስ ዜናዊን የሚጥል ከቶ ሌላ ሃይል የለም ባዮች ናቸዉ። ታጥቦ ጭቃ ! ባለፈዉ ዓመት በተከታታይ በገንዘባቸዉ አዋጥተዉ እነ ገብሩን አሜሪካ ድረስ እያስመጡ መለስ ዜናዊን ይጥሉታል እያሉ የሚሞኙ ሰዎች አዳዲስ የትግራይ ተወላጆች ሳይሆኑ ያዉ የቆዩት የወያኔ ደጋፊዎች ወይንም በሶሊዳሪቱ (ሁሉም ማለት ሳይሆን)ተደራጅተዉ የቆዩና ወያኔ ሲሰነጠቅ የነገብሩ የነመለስ ደህንነት በእጅጉ ያሳሰባቸዉ፣ ወደ ስልጣናቸዉ እንዲመለሱ ሲሟገቱ የነበሩት ሁላችንም በሚዲያም በአካልም በግልም ያየናቸዉና የምናዉቃቸዉ ናቸዉ:: በጥቅሉ “መሪዎቻችን” ብለዉ ሕዝባዊ ግምባር! ወያኔ ትግራይ! ሲሉ የነበሩ የእነሱ ባንዴራ አዉለብላቢዎችና እስክስታ አዉራጆች/የሚዲያ አገልጋዮቻቸዉ ዛሬም 95 ከመቶዉ ከተወልደና ከመለስ የወያኔ ድርጅት ወጥተዉ ወደ ገብሩና አረጋሽ አዉዓሎም ወደ “ዓረና ወያነ”ገብተዋል። እነማን ናቸዉ ብሎ ለሚጠይቅ የሺዎቹን ተከታዮች ስም ዝርዝር መጥቀሱ ስለሚከብድ ሲሰነጠቁ ሲጮሁላቸዉ የነበሩት ታሪክ ራሱን ይደግማልና ዛሬም ራሳቸዉን በጨዋታቸዉ ለማጫወት ዝግጅታቸዉ በግልጽ እያየነዉ ነዉና ወደ “ትዝታችንና ትዝታቸዉ”ማሕደር ልዉሰዳችሁና አቁዋማቸዉና ለወያኔ መሪዎች የነበራቸዉን ፍቅርና ያ ትዝታ ዛሬም በከፋ መልኩ እንዴት ሕያዉ እያደረጉት እንዳሉ ከማሕደራቸዉ ላስደምየጣችሁ። ወያኔዎች ለሁለት ሲሰነጠቁ የተሰማቸወዉ ድንጋጤ የስሰሙት እሮሮ እና ስሞታ ለዚህ ሳምንት በትግራይ ተወላጆች ስንጀምር ፡ በሚቀጥለዉ ሳምንት ደግሞ ሰፊዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ያስሰማዉ የደስታ መልክትና ጽሑፍ ፈንጠዚያና ጸሎት በሚቀጥለዉ እትም ይቀርባል። ልዩታቸዉንም አንመለከታለን፤፡ ዛሬም ለነገብሩና ለነ ስየ በፍቅር የመንገብገቡ ቁርሾዉ መቸ አንደጀመረ ማሕደራችን የመዘገበዉን ታሪክ እንመልከት ከሰባት ዓመት በፊት የቪኦኤዋ አዳነች ፍስሃየ የሚቀጠለዉ ዘገባ አቅርባ ነበር_ “ከዚህ ከዋሽንግተን ከቨርጂኒያ ከሜሪላንድ ከኒዉዮርክ ከቦስቶን ከፍላደልፊያና ከአትላንታ የተወከሉ ባለፈዉ ሳምንት መጨረሻ ላይ ስለሁኔታዉ ከተወያዩ በሗላ አንድ “ኮሚቴ” መመስረታቸዉን፣የኮሚቴዉ አባል የሆኑት አቶ ሙሉጌታ አረጋዊ ገልጿል ። ኮሚቴዉ የተመሰረተዉም የሕዝቡን ድንጋጤና ስሜት ለኢትዮያ መንግሥትና ለሕዝባዊ እንዲሁም መንግሥታዊ ያልሆዩ ድርጅቶች ለትግራዩና ላጠቃላዩ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ለማስተላለፍ ነዉ ሲሉ አቶ ሙሉጌታ አረጋዊ አስተላልፈዋል። አስራ አንዶቹ አንጋፋ የህወሓት አባላት የተወገዱት በሕገወጥ መንገድ ነዉ ይላሉ። ይህንን መሰረት በማድረግም የሚከተሉትን ዉሳኔዎች በማብራራት አቶ ሙሉጌታ እንዲህ ይላሉ፦ “በመጀመርያ እነዚህ አስራሁለት የማአከላዊ ኮሚቴ አባላት በተለይም በቅርቡ ማለትም ከሻዕብያ ጋር የተደረገዉ ጦርነት…ጀግንነታቸዉ ያስመሰከሩ፣ አገር ወዳድነታቸዉ…በግልጽ ያሳዩ ከመሆናቸዉም በላይ፣ አሁን ታግደዉ ,ከስራ ተባርረዋል። ስለዚህ ሕይወታቸዉ አደጋ ላይ የወደቀ ይመስላል። ችግር ብያጋጥማቸዉ አንድ ነገር ይፈጠራል ብለንም እናምናለን። ችግር ቢገጥማቸዉ ያባረራቸዉ መንግሥት ተጠያቂ እንደሚሆን፡ ከዚያ ቀጥሎ ያስተላለፍነዉ ዉሳኔ ምንድነዉ፦ እነዚህ የተባረሩ አስራሁለቱ ሰዎች ያለ ቅድመ ሁኔታዎች ወደ ነበሩበት እንዲመለሱ፦
ሦስተኛ በድርጅቱ ሕግና በሌሎችም ተጓዳኝ ሕጎች መሰረት የህወሓት ቁጥጥር ኮሚቴ ባሳለፈዉ መሰረት አስቸኳይ ጉባኤ ተጠርቶ ጉዳያቸዉ በጉባኤ እንዲታይ፡-
አራተኛ፦ ጉባኤ አስኪጠራ ድረስ ነጻ ሚድያ እንዲፈቀድላቸዉ፡
አምስተኛ፦አሁን በስልጣን ላይ ያለዉ ክፍል በነዚህ ሰዎች ላይ የሚያካሂደዉ ፕሮፖጋንዳ ስም በማጥፋት፣ በራሳቸወና በቤተሰቦቻቸዉ ላይ ቀጣይ የማባረር እርምጃ ..ባስቸኳይ እንዲያቆም፡
ስድስተኛዉ ዉሳኔ ደግሞ፦ ከኤርትራ ጋር የሚደረገዉ ድርድር በታገዱት በሰላማዊ የቲ-ፒ-ኤል-ኤፍ አባላች ተሳታፊነት መካሄድ ሲገባ አሁን ግን አስራ-ስምነት ብቻ ስለቀሩ ባስራ ስምንቱ ብቻ 2/3ኛ ድምፅ ሳይኖራቸዉ ማለት ነዉ፡ በነሱ ብቻ የሚደረግ ድርድር ተቀባይነት ሊኖረዉ ስለማይችል ድርድሩ ባስቸኳይ እንዲያቆም ነዉ።”” (አቶ ሙሉጌታ አረጋዊ) ካሉ በሗላ ትላለች አዳነች ፈስሃየ “የትግራይ ክፍል ሀገር ተወላጆችን ወክለዉ የተናገሩተር አቶ ሙሉጌታ በመቀጠል “የህወሓት ካድሬዎችና በተለይም የመከላከያ ሠራዊቱ አገሪቱን ከዚህ ቀዉስ በሰላም እንድትወጣ የማድረግ ግዴታ እንዳለባቸዉ ሳያሳስቡ አላለፉም። ሌሎቹም የኢሕአዴግ አባሎች ያስታራቂነት ሚና እንዲጫወቱ የትግራይ ተወላጆች መጠየቃቸዉ ገልፀዋል።”” አሜሪካ የኢንዲያና ክፍለሃገር አቶ ሃይለማርያም አበበ ደግሞ ከ70 አባላት የሆኑ ኢትዮጵያዊያን አባላት ወክለዉ ተናግረዋል። አቶ ሃይለማርያም አበበ Ethiopian Commentator”የተባለ መጽሄት አዘጋጅ ሲሆኑ በሙያ “Micro Biologist” ናቸዉ። “በዚህ መጽሄት ዙርያ የተሰባሰቡት ሰዎች ባለሞያዎች ሲሆኑ ቡዱኑ የፖለቲካ ስብስብ አይደለም: ያለዉን ሁኔታ ኢንፎርመሺን ለሕዝቡ ለማሳወቅ ሲባል ብቻ የተደራጀ ነዉ” ሲሉ አቶ ሃይለማርያም አበበ አስምረዉበታል። በዚህ ዙርያ በህወሓት የተፈጠረዉ ችግር የቡዱኑ ስሜት አንጸባርቀዋል።
“ባሁኑ ጌዜ በኢትዮጵያ የተፈጠረዉ ችግር የኛ ሜምበሮች ተሰባስበን አቋም ወስደናል። ይህም ምንድነዉ የነዚህ አስራሁለቱ በተመለከተ በእዉነቱ የእነ አቶ መለስ ዜናዊ ቡድን የህወሓትን ሕግ ጥሰዉ እንዳገድዋቸዉ ሙሉ በሙሉ እናምናለን። እንዲሁም እዚህ ያሉት የትግራይ ተወላጆች በሙሉ (በእነ አቶ መለስ የተወሰደዉ እርምጃ) መቶ በመቶ ከሕግ ዉጭ መሆኑን ያምናል። እርምጃዉ ከሕግ ዉጭ መሆኑን ያምናል። እኛም እናምናለን፡በዘህ ትልቅ፣ትልቅ ቁጣና ንዴት ተሰምቷቸዋል።ስለዚህ የተባረሩት ሰዎች ወደ ስራቸዉ ባስቸኳይ እንዲመለሱ በብዙ ከተሞች የሚኖሩ ትግራይ ተወላጆች ለአቶ መለስ ዜናዊ የቅሬታ ደብዳቤ አስተላልፈዋል፡ ለዚህ አስካሁን ድረስ የተሰጠ ምላሽ የለም ። በጣም በጣም የሚያሳዝን ሁኔታ ነዉ።”” አዳነች ፍስሃየ ትቀጥልና “አቶ ሃይለማርያም አበበ አያይዘዉም “በህወሓት ሕግ መሰረት የትግራይ ምክር ቤት መሰብሰብ የሚችለዉ ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ ገብሩ አስራት ናቸዉ:: አሁን ግን የትግራይ ምክርቤት ባቶ መለስ ተጽዕኖ ራሱ ስበሰባ ጠርቶ ፕረዚዳንቱን ማዉረዱ ራሱ ተገቢ አይደለም። ካሉ በሗላ “ዲሞክረሲን በመርገጥ ዲሞክራሲን ማምጣት አይቻልም” ብለዋል።..በመጨረሻም አቶ ሃይለማርያም “ዉጭ ያለን ኢትዮጵያዊያን አገራችን አደጋ ላይ ወድቃለች የሚል እምነት ስላለን ሕዝቡ ያልተበረዘና ተገቢ የሆነ ኢንፎርመሺን ለማግኘት የራዲዮ ስርጭት ለመክፈት እየተዘጋጀን ነዉ ብለዋል:” : ስትል የቪኦኤዋ አዳነች ፍስሃየ የህወሓትን መሰንጠቅ አስመልክቶ ከመቀሌ እና ከዉጭ የሚኖሩ የትግራይ ክፍልሃገር ተወላጆች የተጠናቀረዉን ዘገባ እላይ የተዘገበዉ ዓይነት ለነገብሩ የድጋፍና የደህንነት መቆርቆር ስሜት ለዛሬዉ የዓረና የፍቅር እርሾ መነሻዉ ያኔ ያስተላለፏቸዉ ዉሳኔዎች እንደነበሩ ልብ ልንለዉ ይገባል። በነገራችን ላይ ሃይለማርያም አበበ አዳነች አንደገለጸችዉ በሙያ Micro Biologist ሲሆን ደጀን ራዲዮ ተብሎ የሚታወቀዉ ራዲዮ አዘጋጅ የነበረ ነዉ። አቶ ሙሉጌታ አረጋዊ ደግሞ ድሮ መቀሌ በድረጉ ጊዜ የምርት-ካድሬ የነበረ እና ባሁኑ ሰዓት የሕግ ጠበቃ ባለሙያ ነዉ:: እንግዲህ እንዲህ ካልን ዘንዳ ያ ሁሉ ልቅሶና “አገር አደጋ ላይ ወድቃለች” እሮሮአቸዉ ለእነ ገብሩ ታዝኖላቸዉ እንደሆነ የምናዉቀዉ እንጂ አገር አደጋ ላይ የወደቀችዉ ሲሰነጠቁ ሳይሆን አገሪቱ በተቆጣጠሩዋት ወቅት እንደነበር ደጋግመን በጮህንበት ወቅት የነበረ ቢሆንም “ጨኸን ጮኸን እንዳልጮኽን ሆንን” ያለዉ ቅዱሱ መጽሐፍ ሆኖ ባስገራሚ ሁኔታ አገሪቱን ለአደጋ የጋረጥዋት ጋሬጣዎች “ሲቧጨቁ” ከዉጭ ሆነዉ “አገር ምድሩ አዳጋ ላይ ወደቀ” ብሎ መጮች ታሪክ የማይረሳዉ ማሕደር ቢሆንም:- ፍጹም ሰዉ የለምና ከስሕተት ተምሮ ስሕተትን አርሞ እንደገና ለቀና መንፈስ ተነሳስቶ ጋሬጣዎቹ በሓላፊነት ከመጠየቅ ይልቅ ዛሬም እነ ገብሩን ስልጣን ላይ ለማስቀመጥ ከ7 ዓመት በፊት በጉባኤ ያስተላለፉት ላለመፋታት ዉሳኔ እዉን ለማድረግ ቃል ኪዳን ገብተዉ ነበርና ያነኑ እዉን ለማድረግ ተከታታይ ቴሌ ኮንፈረንሶች በደብቅም በግልጽም ይጧጧፋል። በግሌ እንኚህ ሰዎች ያልተባበረ ሕብረታቸዉ አስተባብሬ ሁላችንም በኢትዮጵያዊነት መስመር እንጂ በብሔረሰብ ሰልፍ ተሰልፎ አላስፈላጊ መበታተንና የዘር መጎነታተል እንደቆየዉ 33 ዓመት እንዳይቀጥል የተቻለኝን ያህል ለማድረግ በየስቴቱ በስልከም በኢሜይልም በማነጋጋር ሞክሬ አልሆን ብሎኝ በትዝብት ትቼአቸዉ ዛሬም ያንኑ አንቀጽ 39 አስከ “መገንጠል” የነገብሩ የወያነ ትግራይ የፍቅር ትዝታ አልለቅ ብሏቸዉ “እምቢ ካላችሁ እንገነጠላለን” ከሚሉን ከነ ገብሩ ከነ ሰዉ በላዉ አዉዓሎም (ዲያብሎስ ይሉታል በቅጽል ስሙ የህወሓት አስረኞች} ከነ አረጋሽ አዳነ ( ዲያቆን ገብረሕይወትን በአረመኔዉ “ወዲ-ሻምበል” መቀሌ ጽ/ቤቷ ስር አንደር ግራዉንድ አስገብታ ያስመረመረቺዉ) እያወዳደሱ ለነሱ መከላከሉ ቀጥለዉበታል። ታሪክ ነዉና እኛም የመጨረሻ ትግሉ ከነማን እንደሚሆን በታሪክ ዓይን በጎሪጥ እየተከታተለነዉ እንገኛለን። ኢትዮጵያዊነት ለ33 ዓመት ጎልብቶ ከታሰረበት ኬላ እየሰበረ በመዉጣት አሸናፊነቱን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየደመቀ መጥቷል፡ ብሄረተኞች ከጎሳቸዉ እና ለጎሳቸዉ አስከመገንጠል ሲያቅዱ እኛም የጊዜ ጉዳይ እንጂ “ኢትዮጵያዊነት” የመጨረሻዋ ተራራ በመዝለቅ ያሸናፊነቱን የችቦ መብራት ይዞ በታሪክ ፊት በከራት ይቆማል! ጌታቸዉ ረዳ www.ethiopiansemay.blogspot.com

Tuesday, April 7, 2009

ለደረሰብኝ የሞራል ዉድቀትና የንብረት ዉድመት

ለደረሰብኝ የሞራል ዉድቀትና የንብረት ዉድመት ተጠያቂዉ ማን ነዉ? ጌታቸዉ ረዳ

(መጋቢት 2002) ዛሬ ቀን የህዋ ሰሌዳዎችን ስጎበኝ ኢትዮጵያ-ዉስጥ-ይታተማልተብሎ በተቃዋሚነት ስም የሚታወቅ ጋዜጣ ባወጣዉ ዜና አቶ በረከት ስሞኦን “መንግሥት በሰብአዊ መብት ላይ አሳፋሪ ሪኮርድ-የለዉም”-ሲሉ ለጋዜጠኖች መግለጫ ሰጡ፡ ሲል የዘገበዉ ዜና ሳነብብ፤ አጋጣሚ ሆኖ ሰብአዊ ጉዳዮችን በመዘገብ ዜጎች ብሶታቸዉን የሚያሰሙበት ጦቢያ ጋዜጣ ላይ “እንነጋገር”የሚል መድረክ ሳነብብ ነበር። ታዲያ በዛ አምድ የተዘገበ ያንድ ዜጋ እሮሮ አንብቤ ስጨርስ ሕሊናየ ተቃጥሎ እንዳለ ፡የበረከት ስሞኦን የ “ህወሓት መንግሥት” አኩሪ ሰብአዊ መብት ሪኮርድ እንዳለዉ የሰጠዉ ጋዜጣዊ መግለጫ ሳነብብ ይበልጥኑ የተቃጠለዉን ሕሊናየ ተቃጠለ። እወቁ ያገራችን ዘፋኝ ጥላሁን ገሰሰ የዘፈነዉ “ፍጡር ካላዘነ ለፍጡር ስቃይ ከቶ ጤና የለም በዚች ምድር ላይ…”እያለ አንጎራጎረዉን ትምርታዊ ዜማ አስታወሳኝ። በረከትም መለስም ስብሐትም እነ ገብሩም እነ አዉዓሎም ወልዱ እነ አበበ ተክለሃይማኖት እነ አረጋሽ አዳነና… እና እነ እነዎቹ…የዜጎች እሮሮ የረገጡበትን ማሕደር ወረቀቱ ነክሶ ይዞታልና ለመዋሸት ቢዳዳቸዉም፤ ማሕደሩ አይለቃቸዉም። ያነበብኩት በወረቀት ላይ ተዘግቦ የቆየ የዜጎችን እሮሮ አብራችሁ እንድታነብቡ የወያኔ መንግሥት “ለደረሰብኝ የሞራል ዉድቀትና የንብረት ዉድመት ከማን እካሳለሁ? በማለት እሮሮአቸዉን በማሰማት “ኤርትራዊዉ የህወሓት መንግሥት” በሰመ ሞክሼነት አስሮ ያንገላታቸዉ ኢትዮጵያዊ ዜጋ በረከት ስሞኦን እየዋሸ ያለዉ ቡክን ሕሊናዉ መጪዉ ፍትሕ ምን እንደሚጠይቀዉ ላስገነዝበዉ እወዳለወሁ። “የወያኔ ገበና ማሕደር” ዓምዳችን የመዘገበዉ አሳዛኙ የዜጎች እሮሮ እነሆ።- “ለደረሰብኝ የሞራል ዉድቀትና ንብረት ዉድመት ከማን እካሳለሁ?” (ከበደ ገርቢ) - ጦቢያ (ጋዜጣ) ሰባተኛ ቁጥር19 ነሓሴ 11 1999 ዓ.ም. ሥራየ ንግድ ነዉ። በናዝሬት ከተማ ትዳር መስርቼ ፤ንብረት አፍርቼ ከመኖር በስተቀር በፖለቲካ ሥራ ዉስጥ ምንም ተሳትፎ አልነበረኝም፡ አሁንም የለኝም። በዘር ማጥፋት ወንጀል ሕዳር 15 ቀን 1990 ዓ.ም ተይዤ፤ በአቃቂ መታጎርያ ካምፕ ለ2 ዓመት ለ7 ወር ታስሬ የአካልና የሞራል ጉዳት፤ የንብረት መዉደም ጉዳት ደርሶብኛል። የእሥራቱ መንስኤ “የሻሸመኔ” ወረዳ አስተዳደር በነበርክ ጊዜ ሰዎችን በሥልጣን አስረህ በደርግ አባሎች እንዲገደሉ አድርገሃል” የሚል ነዉ። እኔ በሻሸመኔ ከተማ ኖሬም አላዉቅም። ከንግድ ሥራ ዉጭ የመንግሥት ሹም ሆኜም አላዉቅም በማለት ደጋግሜ አቤት ብልም የልዩ ዓቃቤ ሕግ ባልፈጸምኩት ወንጀል አገር ሰላም ነዉ ብየ ከተቀመጥኩበት ቤቴ አዉጥቶ ይህን መሰሉን አሳዛኝ ድርጊት ፈጽሞብኛል። እኔ አስከማዉቀዉ ድረስ የታሰርኩበት የሻሸመኔ ወረዳ አስተዳዳሪ የነበረዉ አቶ ከበደ ገብሬ ነዉ በማለት ነዉ። በስመ መኩሼና በይመስላል። በእሱ ቦታ እኔን ለጭዳ ያቀረቡኝ ሰዎች ይህንን ወረዳ አስተዳዳሪ ወደ አልሰራበት አካባቢ ወስደዉ ሕዝቡም እና እንኳን ወንጀሉን ቀርቶ ሰዉየዉንም ራሱን አናዉቀዉም አሰኝተዉ በነፃ እንድሰናበት ማስደረጋቸዉን በአሉኝ መረጃዎች አማካይነት በማጣራት ላይ እገናለሁ። እስቲ አንባቢ ይፍረደዉ! “ከበደ ገርቢ” እና “ከበደ ገብሬ” በእዉነት የስም ሞክሼነት አላቸዉ?የአባት ስም እንዲህ ተለያየቶ እያለ በእዉነት የስም ሞክሼነት አላቸዉ? የአባት ስም እንዲህ ተለያይቶ እያለ የአያቶቻችን ስም ሳይፈተሽ ልዩ ዓቃቤ ሕግ የትኛዉን መረጃ ሰብስቦና የትኛዉን ጭብጥ ይዞ እኔን በወንጀለኛነት እንደፈረጀ ለማወቅ በእጅጉ ግራ ያጋባል። የልዩ አቃቤ ሕግ አሠራር እንደዚህ በዘፈቀደ ከሆነ በይሆናል የተከሰሱትን ሰዎች ብዛት ቤት ይቁጠረዉ ብሎ ዝም ማለቱ ይሻላል። ያም ሆነ ይህ እኔም በዘር ማጥፋት ወንጀል በመዝገብ ቁጥር 925/89 በልዩ ዓቃቤ ክስ ቀርቦብኝ ያላንዳች ጥፋት ሁለት ዓመት ከሰባት ወር በእሥር ፍዳዮን ቆጥሬ መፈጠሬን ጨርሶ በጠላሁበት ወቅት ጉዳዬ የቀረበለት የፌደራሉ የከፍተኛ ፍረድ ቤት የወንጀል ችሎት የቀረበብኝን የዉንጀላ ክስ ዉድቅ በማድረግ ሰኔ 29/92 ዓ.ም. በነፃ አሰናብቶኛል። እንግዲህ ምንም ወንጀል ሳልሰራ ወይንም ወንጀል ለመስራቴ በፖሊስ ምርመራ ተጣርቶ መረጃ ተሰብስቦ ሳይቀርብለት ከሜዳ ላይ እንደከብት ነድቶ በእሰር ያማቀቀኝ የልዩ ዓቃቤ ጸ/ቤት ነዉ ወይንስ መንግሥት የአካልና የሞራል ካሳየን የሚከፍሉኝ?ይህ ተጠያቂነት በማን ላይ እንደሚያርፍ ተለይቶ አስካልታወቀ ድረስ በደል የደረሰበትና እየደረሰበት ያለዉ ኢትዮያዊ ሁሉ እየተበራከተ ሊሄድ ነዉ። በዚህ እሥር ሳቢያ በንብረቴ ላይ የደረሰዉ ዉድመት ደግሞ በእጅጉ የሚሰቀጥጥና የሚያስደነግጥም ነዉ። እኔ 52 ዓመት አስኪሆነኝ ድረስ በየቦታዉ ተንከራትቼ ንብረት አፍርቼ ነበር። ልዩ ዓቃቤ ሕግ እኔን ከመኖርያየ ጨምድዶ ወህኒ ቤት የወረወረኝ በድነገት ስለነበረ ንብረቴ በየቦታዉ ተዝረክርኮ የሚጠፋ ሆነብኝ። ይህንን ለመከላከል ባለቤቴን ወ/ሮ መቅደስ ወልዴን ለንብረቴ አስተዳደር ወኪልና ሙሉ ነገረ ፈጅ አደርጌ መሾም ግድ ሆነብኝ። ባለቤቴም በዘር ማጥፋት ወንጀል ተይዘዉ ፍርድ ቤት እንኳን ሳይቀርቡ 9 ዓመት በእስር የሚማቅቁ ሰዎች መኖራቸዉን ስለምታዉቅና የእኔም ጉዳይ እንደዚያዉ ይሆናል በማለት ገንዘቤን መዝረፉን ተያያዘችዉ። አዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ አስቀምጨዉ ከነበረዉ ገንዘቤ ዉስጥ በቼክ ቁጥር ኢ.ቢ.ዋይ101622 በአንድ ቀን ብቻ 56፣000 ብር አዉጥታ ወስዳለች። ዳግመኛም በአቶ ክፍሌ ተፈራ ዳኝነት ከሚሰበሰብ ዕቁብ 31,000 ብር ተቀብላለች። ከአቶ ሰይድ ራሕመቶ እጅ 30,000ወስዳለች። በተጨማሪም ወ/ሮ ብዙነሽ ገብረ ሚካኤል10,000በደረሰኝ ተረክባለች። እንግዲህ የምወዳት ባለቤቴ ይህንን 127000 ብር በጥሬ ገንዘብ በእጇ አድርጋ ልዩ ዓቃቤ ሕግ አይለቀዉም በሚል እምነት እርግፍ አደርጋ ተወቺኝ። ከዚያም ያለ ጥያቄ እስር ቤት ወድቄ ቀረሁ። ይህ ብቻ አይደለም። የ3መኪናዎች ገቢ የ31 ወር (የ2 ዓመት ከ7 ወር ገቢ) እንደተዘረፍኩኝ ነኝ። እንደገናም ሙሉ የቤት ዕቃ፤የምግብ ጠረጴዛ ፎቴ፤ማቀዝቀዣ፤ቴሌቪዥን፤ቴፕሪኮርደር በርካታ የሱፍ ልብሶች በአጠቃላይ ከ35000 ብር የሚበልጥ ንብረት ተዘርፌአለሁ። ሌላዉ ቀርቶ ባለቤቴ መኖርያ ቤቴን ሳይቀር በኮንትራት አከራይታ አንዱን የጋራ መኪናችንን ከዉጭ በወለደቺዉ ልጅ ስም አዙራ ለዕለት መዉደቂያ እንኳን አሳጥታኝ በአሁኑ ጊዜ የ የማድረዉ ከዘመድ ቤት ተጠግቼ ነዉ።የዘረፈቺኝ ባለቤቴ መፈታቴን ስትሰማ የት እንደደረሰች አላዉቅም። ፈልጌ አፈላልጌ ላገኛት አልቻልኩም። ስለዚህም በምስራቅ ሸዋ ዞን ፓሊስ መምሪያ ክስ መስርቼ ወ/ሮ መቅደስ እየተፈለገች ነዉ። እንግዲህ ከሕፃንነት ጀምሮ በመታሰሬ ተዘርፌ የቁም ሙት ሆኛለሁ። በዚህ መልክ በልዩ ኣቃቤ ያልተጣራ ክስ የስንቱ ቤት እንደፈረሰ፤የስንቱ ቤት እንደተዘረፈ መገመት ትችላላችሁ። ይህንን ጉድ እያዩ ሰዉ አገር አለኝ፤ሰብአዊ መብቴ ይከበራል፤የሕግ ጥበቃ ይደረጋል ብሎ መናገር ይቻላል?በሕግ ከለላ ቤቴ ፤ንብረቴ፤ሕይወቴ ከአደጋ ተጠብቆ እኖራለሁ ብሎ ይተማመናል? በአጠቃላይ ከእሩብ ሚሊዮን ብር በላይ ለወደመዉ ንብረቴ፤በእስራት ለተሰቃየዉ ሰዉነቴ፤በሚያሳዝን ሁኔታ በደል ለደረሰበት ሞራሌ ካሣ የሚከፍለኝ ማነዉ?” በማለት ዜጎች በራሳቸዉ ቃል “ይህንን ጉድ እያዩ ሰዉ አገር አለኝ፤ሰብአዊ መብቴ ይከበራል፤የሕግ ጥበቃ ይደረጋል ብሎ መናገር ይቻላል?በሕግ ከለላ ቤቴ ፤ንብረቴ፤ሕይወቴ ከአደጋ ተጠብቆ እኖራለሁ ብሎ ይተማመናል?” በማለት የጠየቁትን የስንቱን ቤት እንደፈረሰ የስንቱን ዜጋ መብት እንደተረገጠ “በረከት ስሞኦን” ተጎትቶ ለፍረድ ሲቀርብ የሚመልሰዉ አንዱ ጥየቄ ይኼኛዉ ይሆናል። በረከት ስማኦን “አኩሪ የሰብአዊ መብት ሪኮርድ አለን” በማለት ፋሽስታዊ ግፍንና ብልሹ አስተዳደርን አኩሪ ሪኮርዱ ይሄንን የዜጎችን ግፍ ነዉ! የዜጎች እሮሮ በጊዜ እርዝመት ምክንያት ተድበስብሶ እንዳይቀር ሁሉም ዘብ ይቁም ፤ማሕደሮቻቸዉን እንቆፍር፤ህያዉ ይሁን፤ይመዝገብ፤ይወራ፤ይሰራጭ!አዳዲስ ግፎችን ለጊዜያዊ የፖለቲካ ማስጠበቂያ እያወራን ከባድ ፤ከባድ ወንጀሎቻቸዉ እንዳይረሱ እንጠንቀቅ ። ጌታቸዉ ረዳ www.Ethiopiansemay.blogspot.com

Saturday, April 4, 2009

ተሸብበዉ የሚጎተቱ ቡችሎች

ተሸብበዉ የሚጎተቱ ቡችሎች ጌታቸዉ ረዳ

መቸስ የትግራይ ነጻ አዉጭ የተባለዉ በኢትዮያ ምድር ላይ የወረደ እርግማን አስካለ ድረስ ማረፍ-አልቻልንምና፣መለስ ዜናዊ-የአክሱም-ሃዉልት ለሀዲያዉ ምኑ ነዉ!? እንዳላለ ሁሉ፣ሰሞኑን-ደግሞ ይግረማችሁ ብሎን ያንዱ አፍሪካዊ ችግርና ዕድገት-የሁላችን-ችግርና ዕድገት ነዉ በማለት አህጉሪቱን እወክላለሁ ብሎ እንግሊዝ አገር ሄዶ ፊቱን ለጌቶቹ ሲያስመታ መሰንበቱ የምታዉቁት ዜና ነዉ። የዚህ ኩታራ ሰዉ አጨብጫቢ የሆኑት የህዋ ሰሌዳ (ኢንተረኔት)እና ቴሌቪዥኖቹ አገልጋዮቹ ሲያቀርቡት የነበሩትን መለስ ዜናዉ የተባለዉ ጸረ ኢትዮጵያ ቅጥረኛ ዓለም ከረገመዉና ካወገዘዉ “የቀድመዉ ያሜሪካ ፕረዚዳንት “ቡሽ” ከተባለዉ አረመኔ ሰዉ ጋር ጎን ለጎን ተመችቶት መመሪያ ሲቀበል የተነሳዉ የቆየ ፎቶግራፍ ሳይቀር መለስ ዜናዊ ምንኛ “ከፍተኛ መሪ”እንደሆነ የዋሆቹን ለመማረክ በፎቶግራፍ አስደግፈዉ አሳፋሪ ፎቶግራፎቹን ለሕዝብ ሲለጥፉለት አለማፈራቸዉ ሲገርመኝ ይባስ ብሎ መለስ ዜናዊ “ያፍሪካ እርግማኖች” በተባሉት በአፈሪካ ጨቋኝ መሪዎች ፎቶ ተከብቦ በጉንጉን አበባ ያሸበረቀ ፎቶግራፍ እንደትንግርት ሆኖባቸዉ በኩራት ለጥፈዉት ስታዩ እኔ እንደገረመኝ እናነተንም እንደገረማችሁ አልጠራጠርም። ጌቶቹም አፍሪካን ለመጨቆኛ የሚጥሉለት ፍራንክ ምን ምን ማድረግ እንዳለበት ትዛዝና መመሪያ ሲሰጡት ከተለያዩ አዉሮጳዊና አሜሪካ ጌቶቹ ጋር ቆሞ ሲነጋገር ጣቶቻቸዉ በረዢሙ ወደ ሆዱ ሲቀስሩበት የተነሳዉ ፎቶ ሁሉ እንደ ኩራት ቆጥረዉት ሲለጥፉትና ሲኩራሩበት ስመለከት፣ ለካ ይሄ በየሚዲያዉ ሃላፊ እና ወኪል እያለ የሚሾማቸዉ ሙያም የላቸዉ! አልኩኝ። ለካ የምሩ ነበር “የኛን ዓለማ አስካራመደ ድረስ ዘበኛም ማንበብ መጻፍ የማይችልም ሚኒስትር መሆን ይችላል” ያለን ለማለት በቃሁኝ። “ቤን ዌብ ሳይት” የተባለዉ “የወያኔ ትግራይ አጋፋሪ” ‘ማ በዌብሳይቱ ላይ ኦባማ የተባለዉ ያሜሪካዉ መሪ በመለስ ዜናዊ ሆድ ላይ ረዥም አመልካች ጣቱ ቀስሮ መመርያ ሲሰጠዉ የሚያሳየዉ ፎቶ እንዳይታይ ለጌታዉ ክብር ሲል “ከወገቡ በላይ ቆርጦ አቅርቦታል” በሱ ቤት የሱ ጌታ በታችነት ስሜት እንዳይታይ ሲባል ነዉ። ወይ ጊዜ! አምርሮ የገረመኝ ግን የነዚህ አልነበረም። ከሕግ ዉጭ ሆኖ ሕብረተስብን ባሕልን አገርንና ሕግን በመናቅ አማራ ያልሆነ የአማራ ወኪል ነኝ ብሎ ብዙ ግፍ የፈጸመ በአማራ ሕብረተሰብ ላይ የቀለደዉ ኤርትራዊዉ በረከት ስሞን በለንደን ከተማ ስበስባ ጠርቶ ባንዲት ጠባብ ክፍል “እንደተሸበቡ ዉሾች” በመቁጠር ናላቸዉን ሲያሻቸዉ፣ ያሳዩት የነበረዉን ስሜት ለታዘበ ሰዉ.፣ የሰዉ ልጆች ደካማነት ምን ያህል እንደሚጓዝ ምሳሌ የሆነን መሰለኝ። ሰዉ እንዴት ድፍን 18 ዓመት አይማርም? እንዴት ሰዎች ከሕግና ከእዉነት የተጣሉ፣ በሕገ አራዊት በጫካ ባሕሪ እና ትእቢት-የሚጓዙ እነ በረከት ስመኦን የመሰሉ ራሳቸዉን በጊዜያዊ ጥቅም አሳዉረዉ፣በመጪዉ ሕይወታቸዉ ላይ መዉጫ ቀዳዳ የተደፈነባቸዉ ፣ተስፋ የቆረጡ በራሳቸዉ የፈረዱ “ፈሪዎችን”ባሕሪ መገንዘብ ያቅተዋል? ኤርትራዊዉ ስሞን አማራ ሳይሆን አማራ ነዉ ብለዉ እነ መለሰ በአማራ ሕዝብ ላይ ጭነዉ የመለስ አጀንዳ አስፈጻሚ ሆኖ ብሔራዊ ወንጀልና ሰብአዊ መብት ረገጣ የፈጸመ ለከት የሌለዉ የዉሸት ቱጃር ምን ይረባናል ብለዉ በዛች ክፍል ዉስጥ ተሸብበዉ እየተቁለጨለጩ ጊዜአቸዉ አንዳጠፉ ለኔ ይገርመኛል። ይህ ግለሰብ መጀመርያ በኢሕአፓ የሻዕብያ ሰላይ የነበረ ነዉ ይባላል። ኖረ አልኖረ ያ አደለም ጉዳዩ። አሳሰቢዉ ግን፣ ግለሰቡ እዉነትን ምን ያህል ረግጧል ነዉ። ስለ ኢትዮጵያ እታገላለሁ ብሎ ወጥቶ የሗላ ሗላ ወያኔ ወደ ጎሳ ድርጅት ሲያዞሮዉ “እሺ”ብሎ በአማራ ሕዝብ ጫንቃ ላይ ወጥቶ በስሙ ተተከለ። ብእዴን በረከት ስማኦንን (ኤርተራዊ-) ኦሆዴድ ሰለሞን ጢሞ (ህወሓት-ትግሬ) ደሕአዴግ ቢተዉ በላይ (ህወሓት-ትግሬ) ሕላዌ ዮሴፍ (ብእዴን- ኤርትራዊ/ትግሬ)እነዚህ በደም በቋንቋ ወያኔ የሆኑ ሰዎች በተጠቀሱት ብሔረሰቦች እንዲወክሉ ማድረግ ተወካዮቹ (እነ በረከት)እና ወካዮቹ(እነ ስብሐትና መለስ) ከዉሸት ጋር ምንኛ እንደተጎዳኙ ሰዉ እንዴት ይህነን ለመረዳት የማያዳግት ሴራ መረዳት ያቅተዋል? ይሄ መሆኑ እያወቁ በረከት ሲሰበስባቸዉ ቅንድቡ እንደታሸ ቡችላ እየተርገበገቡለት በካሜራ ተቀርጸዉ ለታሪክ ማሕደራቸዉ ሲዘገብ ትንሽ አፍረት አይሰማቸዉም ወይ? ጂ-20 ብለዉ ራሳቸዉን የሚጠሩ ቱጃሮች ሲሰበሰቡ በለንደን ላይ ተገኝተዉ ከየዓለማቱ የተሰበሰቡ በ IMF ላይ ቅሬታቸዉን ያስሰሙት ሰላማዊ ሰልፈኞች “ዓይጋ-ፎረም” የተባለዉ የመለስ ዜናዊ ዌብሳይት አዘጋጅ የሰልፈኞቹን ፎቶ በመለጠፍ “Anarchists and Anti Capitalist” በማለት ሰልፈኞቹን ሲዘልፍ ያነበባችሁ አንደኔዉ ተደንቃችሁ ይሆን?ይህ የህጻናት ድረ-ገጽ ስለ የካፒታሊዝም ትርጉም የገባዉም አልመሰለኝም። ጌታዉ መለስ ዜናዊ የካፒታሊዝም ስርዓት ሳይሆን “አብዮታዊ ዲሞክራሲ” እንደሚከተል ያወቀዉም አልመሰለኝም። ወያኔ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ አራማጅ መሆኑ እያወቅን ለማሞኘት ሲቃጣዉ “የወንዙን የዓድዋዉ ልጅ”መለስን ብቻ ለመከለከል ሲል ሊታመን የማይችል ጭፍን መከላከል እያደረገ ስመለከተዉ ልጁ ምን እሚሉት ሕሊና እንደተሸከመ ሁሌም ይገርመኛል። ልጁ የኢሐአፓ ታጋይ እንደመኖሩ መጠን የካፒታሊዝምና የሶሻሊዝም ልዩነቶች አበጥሮ ማወቅ ነበረበት የሚል ግምት አለኝ፡ነገር ግን የራሱን መሪ ለመከላከል ሲል ብቻ ኮሚኒሰት/ፋሺስቱ የመለስ ዜናዊን ስርዓት “ካፒታሊሰት“ አስመስሎ ሊነግረን ይሞክራል። “የአብዮታዊ ዲመክራሲ መሰረታዊ መርሕ ደግሞ የተወሰነ መደብ ነጻነት በማርክሲሰት ሌኒኒስት ፍልስፍና በእዝ ኢኮኖሚ ላይ የተመሰረተ ነዉ። ይህም የሊቤራል ዲሞክራሲ የመሠረት ድንጋይ የሆኑትን የግለሰብ ነፃነትን፣ የግል ሀብት ባለቤትነትና ነፃ ኢኮኖሚ የሚፃረር ነዉ። በመሆኑም ወያኔ የሕዝብን ፖለቲካዊ ኢኮኖሚያዊና ማሕበራዊ ነፃነት የገፈፈ ዘረኛ መንግሥት ነዉ። ፖሊሲዎቹ ከቀድሞዎቹ ሶሻሊስት መሪ ኢንቨር ሆጃ አመለካከት የተቀዱ ናቸዉ። (ተክሌ የሻዉ-ገጽ406)፤ በዛ ፍልስፍናም ነዉ መሬትን በመንግሥት ቁጥር ስር እንዲሆን ያደረገዉ።“መንግሥት”ማለት ደግሞ ልዩ ክስተት ማለት ሳይሆን “ወያኔ” ማለት ነዉ። ነጻ ገበያ የሚያራምድ አገር ደግሞ ከቶዉንም መሬት በመንግሥት ቁጥጥር ለማድረግ የማያስበዉ ነዉ። ታዲያ ጸረ-ካፒታሊዝም መባል የሚገባዉ-ሰልፈኞቹ-ወይስ የመለስ ዜናዊ “አብዮታዊ ዲሞክራሲ”የወያኔ መንገሥት? በዚህ አቋሙ “ጸረ ግለሰብ”-ስለሆነ-ግለሰቦች-ባላቸዉ ፖለቲካዊ አቋም “በቀጣሪዉ” “መንግሥት/ወያኔ” በሚያዝዛቸዉ-ወይንም"ባለንብረት-በሆነበት የእርሻ መሬቶች/መስርያቤቶች/ተቁዋሞች እንዳይሰሩ ተደርጓል/ታግደዋል። “የገጠርም ሆነ የከተማ መሬትና የተፈጥሮ ሀብት ባለቤትና መብት የመንግሥትና የሕዝብ ብቻ ነዉ።"(የኢፌድሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ40(3)በሚለዉ ሶሻሊሰስታዊ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ መርሕ መሠረት የተቃኘዉ ሕገ መንግሥት የሀብት ምንጭና መሠረት የሆነዉን መሬት መንግሥት (ወያኔ) በቁጥጥር ሥር አዉሎ ገበሬዉን ጭሰኛ አድርጓል። ይህም ነፃ ገበያ ዋልታ የሆነዉን የግል ሀብት በባለቤትነት የሚፃረር በመሆኑ ወያኔ ለነፃ ገበያ መርሕ ያልቆመ ተቃራኒ መሆኑን ያሳያል። ወያኔ የገጠርና የከተማ መሬትን የመንግሥት እንዲሆን ያደረገበት ሁለት መሠረታዊ ምክንያቶች አሉት፣አንደኛዉ የሚያራምደዉ ርዕዮት የማርክሲስት የመርክሲሰስት ሌኒንስት ርዕዮተ ዓለም አካል የሆነዉ አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ መሆኑ ሲሆን፣ ሁለተኛዉ በመሣሪያ ተግል ያገኘዉን የፖለቲካ ሥልጣን ይዞ ለማቆየት ኢኮኖሚዉን በባለቤትነትመቆጣጠር የግድ ይለዋል። በኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ ደግሞ የኢኮኖሚዉ ምሰሶ-ግብርና ነዉ።85-በመቶዉ የሚተዳደረዉ በግብርና ነዉ። የህም ያገሪቱ ያኮኖሚ የጀርባ አጥንት ብቻ ሳይሆን አብዘዛኛዉ ህዝብ ኑሮ መሠረት መሆኑን አሳያል። ስለዚህ ወያኔ ይህን ሠፊ ሃይል በቁጥጥሩ ሥር አዉሎ የሥልጣን ማስጠበቂያዉ መሣርያ ማድረግ ካልቻለ ሲቋምጥለት የኖረዉ ሥልጣንና በእርሱም መሣሪያነት ኢትዮጵያ የመናድ ዓላማዉ ግብን አይመታም።…በሥልጣን ላይ ለመቆየት የሚችለዉ መሬት በዜግነት መብት ሳይሆን በፖለቲካ አቋሙ መስፈርት ለደጋፊዎቹ ሲሰጥና ተቃዋሚዎቹ ወይንም ይቃወሙኛል የሚላቸዉን ሲከለክል ነዉ።”(የሥልጣን ተሻሚ ትግሬዎችና የ ኢትዮጵያ አንድንት ተክሌ የሻዉገጽ 407..) አንጀቴ! የመለስ የነፃ ገበያ! እንዲህም ብሎ ካፒታሊዝም የለ! በባዶ ሜዳ የሚጮሁለት የመለስ ነፃ ገበያ-“ጉድ”አብዮታዊ-ዲሞክራሲ ቅራቅንቦ ዉስጥ ቀሚሱ ከላይ ካዋቂዎቹ ያነብነዉ በቅርብ ባገሬዉ የነበሩ የተሰቃዩ ያይን ምስክሮች ሰነድ ነዉ። እነኚህ የፈረንጅ አጎብዳጆች ግን እንደ “ሕዳር-ጽዮን እንደ አስተርዮ እንደ ቁልቢ በዓል” ወደ ለንደን እየሮጡ ተኳኩለዉ ሲመጡባቸዉ “እዉነትም የነፃ ገበያ ወኪሎች ይመስል “ኩሪቱ ኢትዮጵያ” ዛሬ፣ ዛሬ በነዚህ “የፈረንጅ ቡችሎች” ምክንያት ዜጎቿ “ፈረንጅ አምላኪ” እየሆኑ “ህሊናቸዉን” ሊያስገዙ ኮሚኒዝም እያራመዱ የካፒታሊዝም ሰባኪዎች ሆነዉ አዲሱን ትዉልድ በላቲን ቋንቋ እንዲጽፍ እያደረጉ ታዳጊ ወጣቶች ሕሊናቸዉ የሚያየዉ በነቀዘ “የልማት ስበከት” ሃብት እያካበቱ ዋነኛ ግባቸዉ ያገር ደህንነትና ኩራት መጣል ነዉ። ለዚህም ነዉ “የዛሬዉ ኢትዮጵያ ትዉልድ ለአዉሮፓ፣ አሜሪካ፣ ካናዳ፣ አዉስትራሊያ ያለዉ ናፍቆትና ጉጉት እበረታ የሄደዉ። በቅኝ ገዢዎች ቀንበር ሥር ያለፉት አፍሪካዉያን ታዛቢዎች “አዉሮፓዉያን ቅን ገዢዎች “እኛን” የገዙት “አካላችንን” ሲሆን “ኢትዮጵያዊያንን” ግን “ሕሊናቸዉን” ነዉ” ከሚል ድምዳሜ እንዲደርሱ ያስገደዳቸዉ መለስ ዜናዊ ከነገሰ ወዲህ ነዉ።” (ሥልጣን ተሻሚ ትግሬዎችና የኢትዮጵያ አንድነት” ተክሌ የሻዉ ገጽ 390)። የጎሳ ፖለቲካ ቀያሽ የሆነዉ ወያኔ ኢትዮጵያን ለማጥፋት ከፈረንጅ ጋር መሮጥ የጀመረዉ ገና የዛሬ-33-ዓመት ሆኖታል።ከታሪካዊ ጠላቶቿ የተሰጠዉ የቤት ሥራ-ደግሞ በሚገባ እየተወጣዉ ነዉ።አንድነታችን ለማፍረስ የተላኩት “ኢሳያስ፣ መለስ፣ ስብሓትና ስዩም” እንደሆኑም አትዘንጉ። “እጅ የሚያስቆረጥም ዶሮ-ወጥ ካሻችሁ ኢሳያስ አፈወርቅ ከባረከላችሁ ለመበለቱማ መለስ አለላችሁ” (ምንጭ እንደላይኛዉ ገጽ 392) ያለዉን ያገሬ ገጣሚ ስንኝም ልብ በሉ። www.ethioppiansemay.blogspot.com