Saturday, September 29, 2018

የኦሮሞዎች እና የትግሬ ናዚዎች ያስፋፉት የወንጀለኛ ስነልቦና ባሕል ለማስወገድ ሦስት ትውልድ ሊጠይቅ ነው ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay)


የኦሮሞዎች እና የትግሬ ናዚዎች ያስፋፉት የወንጀለኛ ስነልቦና ባሕል ለማስወገድ ሦስት ትውልድ ሊጠይቅ ነው
ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay)
OLF’s awful propaganda tool in action.The OPDO and Oromo Liberation Front's production of hate presented as trophy to its cults. It is intended to install barabarism, hate and vengeance in the mind of the Oromo youth. (read the detail analysis posted at Ethiopian Semay)

ከአዘጋጁ ማሳሰቢያ፦
በዚህ ‘ኢትዮጵያን ሰማይ’ ድረገጽ ላይ በየወቅቱ የሚቀርቡ ጽሁፎች፤ በረዢሙ የተጻፈ ረዢም ምርምር እና ትችት ያካተተ ጽሁፍ ለማንበብ ፍላጎት እና ልምድ ላላቸው አንባቢዎች የሚዘጋጅ እንጂ አንድ ሁለት ገጽ ትችት በማንበብ የሚሰለቻቸው አንባቢዎች የሚዘጋጅ ድረገጽ ስላልሆነ ከወዲሁ ጊዜአችሁን መድባችሁ በጥሞና አንብቡት።

ከላይ የምትመለከቱት ፎቶግራፍ በደም ቀለም የተቀባ ለማየት የሚዘገንን ኦነጎች እና የኦሮሞ ሊህቃን ከጥላቻ ልቦና በመነሳት በልብወለድ የፈጠሩት “አኖሌ” የተባለው የጥላቻ ምርታቸው ለምስኪን ጀሌዎቻቸው በሽልማት መልክ የሚያበረክቱት የተቆረጠ የጡት ምስል የያዘ በደም የተነከረ የሰው እጅ ነው

እንዲህ ያለ ለማየት የሚሰቀጥጥ ለሕሊና እጅግ የሚከብድ የኦሮሞ ናዚ መሪዎች ፕሮፓጋንዳ የሚሰራጭበት ምክንያት በተከታዮቻቸው ሕሊና ውስጥ የጥላቻ እና የጭካኔ ባሕሪ እንዲቀረጽ በማድረግ ተከታዮቻቸው ተመሳሳይ ድርጊት እንዲፈጽሙ የሚያበረታታ የማስተማርያ ስልታቸው ነው። ተደመሩ/ተቀላቀሉ/ ከተባለ ጀምሮ አብይን ከመገድል ሙከራ አንስቶ በቅርቡም ቄሮ እየተባሉ በኦሮምኛ ቋንቋ የሚጠሩ ወጣት ኦሮሞዎች ቡራዩ፤ አሸዋ ሜዳ እና የመሳሰሉ በአዲስ አበባ ዙርያ የሚገኙ ኗሪ ዜጎቻችን ላይ የፈጸሙዋቸው ለዓይ እና ለጆሮ የሚዘገንኑ ዘርን (ጎሳን) ያተኮረ ጭፍጨፋ ለምን እንደተፈጸመ እና ለምንስ እንዲህ ያለ “አንገት ቆራጭ እና ጡት ቆራጭ ኦሮሞ  ትውልድ ሊከሰት ቻለ” ብለን ብንጠይቅ የሚጠቁመን አመላካች መረጃ ‘በርካታ የኦሮሞ ወጣቶች የጥላቻ ምሬታቸው የናረ፤ጨካኝ እና ነብሰ ገዳዮች ሆነው እንዲያድጉ የሆነበት ምክንያት ይህ ከላይ የተመለከተው አኖሌ የተባለ የጥላቻ ሃውልት በስጦታ እየተበረከተላቸው ስላደጉ ነው።

እንዲህ ያለ ለማየትም ሆነ በእጅ ለመያዝ የሚዘገንን በደም የተጨማለቀ የአኖሌ ሽልማት መሸለም የተጀመረው አገር ውስጥ በኦፒዲኦ (የዛሬው ‘ኦዲፓ’) እና በዲያስፖራው ዓለምም በነ ጃዋር መሐመድ (ኦ ኤም ኤን) በኩል ሽልማቱ ሲካሄድ እንደነበር የዓይን ምስክሮች ይናገራሉ።

ስለሆነም እነ አብይ እና እነ ለማ በሚሊዮን ብር የተከሉት የጥላቻ ማስተማሪያ  የሆነው “አኖሌ” የተባለው ሃውልት በኦሮሞ ወጣቶች ሕሊና እንዲቀረጽ በመደረጋቸው ምክንያት  ከዚህ በታች የምታዩት ቡራዩ ላይ ዘር በማጥፋት የተሰማሩ ነብሰገዳይ የኦሮሞ መንጋዎች በጭካኔ የቀጠቀጡት ኢትዮጵያዊ ዜጋ የአኖሌ ሃውልት የስራ ውጤት እንደሆነ አንባቢዎች እንዲገነዘቡት አሳስባለሁ። ሕግ ቢኖር እነ አብይ እና እነ ለማ እና በጠቅላላ አብዛኛው የኦሮሞ ሊሂቅ እና ብዙዎቹ አዝማሪዎቻቸው ተጠያቂዎች ናቸው የምንለውም ለዚህ ነው።
Ethiopian citizen, a victim of the so called “Oromo Qero” a violent Oromo youth group photo taken in its  genocidal campaign. ቄሮ የተባለ መንጋ በአዲስ አበባ ዙርያ የሚገኙት ከከተማው ወጣ ያሉ እንደ ቡራዩ እና የመሳሰሉ አካባቢዎች  ኦሮሞኛ የማይናገርን ሰው ሁሉ በገጀራ አንገቱን እየቀላ ገድሏል ።ሴቶች ደፍሯል ።ንብረት አውድሟል፣ዘርፏል።


ስለ የትግሬዎች ፋሺስት ግልገሎች ጭካኔም ትንሽ ልበል።

አሞራው በታበለ በወዳጄ ግደይ ባሕሪ ሹም የተጻፈ መጽሐፍ በረዥሙ የዘገበው ባጭሩ አሳጥሬ ላስነብባችሁ። እንዲህ ይላል፦

ደደቢት ከወያኔ መሠረታዊ ሜዳ ላይ ባዶ ሽድሽተ (ዜሮ 6) ተብሎ በሚጠራ እስር ቤት ለትግራይ ሕዝብ  የናዚ ሰርዓት የሚፈጸምበት ነበር። ለሞት ተፈርዶ ወደ እዚህ ክፍል የተላከ እስረኛ ሥጋው በፍጹም አሞራ አልበላውም።የእስርቤቱ ጭካኔ ‘አጽረጋ’ ከተባለው ሌላኛው የማሰቃያ እስርቤት እንደጀመሩት ዓይነት ማሰቃያ ስፍራ ነው።

የኢድህ ደጋፊ ነህ፤ልጅህ ወይንም ወንድምህ የኢድህ/አዲዩ/ ደጋፊ ነው ተብሎ ይያዝና ወደ እዚሁ ቦታ ይወሰዳል። እንደ ደረስም ስለንብረቱ ብዛት እና መጠን የት ቦታ እንዳለ ይጠየቃል።ለጥቂት ቀናት ደህና ምግብ እየተሰጠው በሁለት ሦሰት ቀን ውስጥ ከሌላ እስረኛ ጋር እየተረዳዳ ቢያንስ ሁለት ሜትር ጥልቀት ያለው ጉድጓድ እንዲቆፈር ይታዘዛል።የጉድጓዱ ስፋት ዓይነት የሰው መቃብር አይመስልም። እንደ ውሃ ጉድጓድ ጠበብ ብሎ እየተቆፈረ አፈር ዙርያውን ይከመራል፡ እስረኛው የቁም መቃብሩን ቆፍሮ እንዳበቃ በገመድ  እጅ እና እግሩ ታስሮ፤ዓለም በቃኝ ወደ ቆፈረው ጉድጓድ ይመልሱታል።

ወያኔዎች እስረኛው ከመሞቱ በፊት ሲሰቃይ ማየት በጣም ያረካቸዋል። ቶሎ እንዳይሞት ትንሽ ቂጣና ጥቂት ውሃ በሜንጦ መሳይ በገመድ እያሰሩ ወደ ታች በመጣል ያቀብሉታል። ሽንትም ሆነ ዓይነ ምድር መጸዳጃው ከዚያችው ጉድጓድ ውስጥ ነው።


አንዴ ወደ ቆፈራት ጉድጓድ ከገባ ከተጣለ በኋላ በምንም ተአምር መልሶ መውጣት የለም። እስረኛው በዛች ጠባብ ጉድጓድ ውስጥ እግሩን መዘርጋትና በጎን መተኛት አይችልም። ተጨብጦ መቀመጡም ከደከመው፤እቅሙ ከቻለ ማድረግ የሚችለው መቆም ብቻ ነው። ኩርኩም ብሎ በቀን የፀሐይ ሃሩር፤ሌሊት በብርድ እና በጤዛ እተሰቃየ የተፈጠረባትን ቀን እና አገር ዘር እየረገመ፡ ከመሞቱ በፊት ከመሬቱ እና ከሰውነቱ በሚፈጠሩት ትሎች (ዱዱቃ)፤ ገላው እየተበላ፤በሰው ላቦት እና በመሬት ሙቀት የሚፈጠሩ ትሎችም መርዘኞች ስለሆኑ፡ ተሎ አይገድሉትም።ቆዳው ሰርስረው ሥጋውን በልተው፤አጥንቱን መፈርከስ ሲጀምሩት ፤ እስረኛው በመጨረሻ በአፉ እና በአፍንጫው በዓይኖቹም ትሎች እና ዱቅዱቃዎች ይፍለቀለቁና አሰቃቂ በሆነ መርገም ህይወቱ ካለፈች በኋላ፤በዚህ የመርገመ ትዕይንት የማይሰቀቁ ወያኔዎች በጉድጓዱ ዙርያ ያለውን አፈር መለስ አድርገው እጅ እግሩን ታስሮ እንደ ተኮረኮመ እዚያው ቅብር ያደርጉታል።…”

 በማለት ዘግናኙ የወያኔ ትግሬዎች ጭካኔ በሰፊው ገልጸታል። (ወዳጄ ግደይ ባሕሪሹም ባንባቢዎቼ ስም እጅግ አመሰግንሃለሁ። ሰሞኑንም እደውልልሃለሁ)።

እንግዲህ ወያኔዎች እንደዚህ ባለ የጭካኔ እርምጃ እየወሰዱ አዲሱን የትግራይ ሕሊና የት ወዴት እየመሩት እንደሆነ በግልጽ ስንመለከተው የኦሮሞ እና የሶማሌ ወጣቶቹም አንገት መቁረጥ ጡት እና የወንድ ዘር ብልት መቁረጥ፤ቤተክርስትያን እና ቀሳውስት ካህናት መግደል  ማቃጠል፤አዛውንት እናቶች እና ህጻናት ሴቶችን መድፈር..የመሳሰሉ በእንዲህ ያለ የጭካኔ ወንጀሎች ሊሰማሩ የቻሉበት ዋነው ምክንያት የወንጀል አስተማሪዎች እየቀረጹ በሚያስተምሩዋቸው የጥላቻ ታሪኮች እና ምልክቶች የፈጠሩት ውጤት ነው::

የተወለድንባት ኢትዮጵያ ባሁኑ ወቅት በምን ዓይነት እርካብ ነች ያለቺው? የሚል ጥያቄ ብናነሳ ሁላችንም የምንስማማባቸው “አስቸጋሪ፤ አስፈሪ” በሚባሉ የሕይወት ዳገት ውስጥ እንዳለች እናምናለን። ጥንትም ዛሬም አሁንም ለጥፋትዋ ያሴሩባት የፖለቲካ ተዋናያን ለበርካታ አመታት የበሉዋቸው ተከታዮቻቸው ዛሬም ስለሚያመልኩዋቸው ፤ ለዘመናት ሲቀሰቅስዋቸው የነበሩት የጥላቻ ቅስቀሳዎች  ዛሬም ‘ህያውነታቸው’ እየጠነከረ ሄደዋል። በሚገርም እንቆቅልሽ እነኚህ የኦሮሞ፤የሶማሌ እና በጉምዝ ክልል ያሉት ‘ወጣት ሞገደኞችን” መቆጣጠር ያቃተው የአብይ አሕመድ አመራር በተከተለው የመደመር አናርኪያዊ ፍልስፍና ምክንያት የጭካኔ ወንጀሎች ተበራክተዋል።

ለዘግናኝ ወንጀሎች መከሰት አባባሽ ምክንያት የሆነው ደግሞ አንዳንድ ‘ፋናቲክ’ ፖለቲከኞች የፖሊሲ እና የመንፈስ ህድሳት ሳያደርጉ ያለ ምንም ገደብ ወደ አገር እንዲገቡ በመፍቀዱ ነው። በፖለቲካቸው የሰከሩ በጥላቻ ስሜት የሰከሩ “ጀብደኛ” ጀሌዎቻቸው በጥላቻና በግንጠላ ስብከት ያሰከርዋቸው መሪዎቻቸው በአሸናፈነት እንደገቡ ተመስሎ ስለተነገራቸው ባንዴራዎቻቸውን እያውለበለቡ ይሆናል ተብሎ ባልተገመተ ሁኔታ እና ወቅት ቅጽበታዊ ጭፍጨፋዎች በዜጎች ላይ ፈጽመዋል። በተጓዳኝም ይህ ክስተት ሥልጣኑ ባልጠበቀው መንገድ እየተሸረሸረበት ለሚገኘው ‘በመገንጠል እና ባለመገንጠል’ ውሳኔ ላይ መድረስ የተቸገረው “በውጥረት ገምድ” መሬት ለመሬት እየተጎተተ ያለው የህወሓት ስርዓት በሥልጣን ለመቆየት ጥሩ ክፍተት ፈጥሮለታል::

አስገራሚ የሚያደርገው ደግሞ እነዚህ በኦነግ እምነት የተጠመቁና የሰከሩ ጀሌዎች በአብይ አሕመድ የነብስ ግድያ ላይ እና በበርካታ ዜጎች ህይወት ላይ ግድያ እና የአካል ማጉደል አደጋ ያደረሱ መሆናቸው ከታወቀ በላም ቢሆን

OLF criminal cults wanted to assassin Prime Minister Colonel Dr Abey Ahmed.

በድጋሚ ‘ጅግጅጋ’ (ኦጋዴን ‘ክልል’) ላይ በኦጋዴን ሶማሌ እስላማዊ አክራሪዎች የተሰነዘረው የዘር እና የሃይማኖት ጭፍጨፋ በሚያስደነግጥ ሁኔታ ከተከሰተ በላም ቢሆን ስርዓቱን የሚመሩት የህወሓትም ሆኑ የአፒዲኦ/ኦዲፓ/ ጥምር መሪዎች የሚመሩት ስርዓት “አናርኪ” በመሆኑ የኦነግ እና የግንቦት 7 መሪዎች ወደ አዲስ አበባ ከገቡ በላም እንደገና በጣም አስደንጋጭ እና ተመሳሳይ የዘር ማጥፋት እና የሴቶች መደፈር የንብረት ዘረፋ እና ግድያ በተለያዩ ክልሎች እና በአዲስ አበባ አካባቢ እና በከተማ ውስጥም ተከስቷል። ይህ ክስተት ከምንም የተከሰተ ሳይሆን አሁን ያለው የአብይ አህመድ አመራር በሚከተለው ጥራት ያልተከተለ የመደመር ፍልስፍና የከፈተው በር ተጠቅመው ነው።

አዲስ አበባ የገቡት አብዛኛዎቹ የኦሮሞ ፖቲከኞች በጥላቻ የሰከሩ የዘር ጭፍጨፋ እንዲካሄድ ፕሮፐጋንዳ ያሰራጩ፡ አንዳንዶቹም በዘር ማጥማፈት ላይ ቀጥተኛ ተጠያቂዎች የሆኑ ጸረ ኢትዮጵያ ሃይላት ስለሆኑ የለመዱበት የማጋጨት አመል (ባሕሪይ) አዲስ አበባ ገብተውም ሊለቃቸው አልቻለም። ግንቦት 7 የተባለውም እንዲሁ አገር ቢገባ እውጭ አገር ሲያደርገው የነበረው የመከፋፈል ሴራ እና የብልጣብልጥነት ባህሪው ስለሚያጠቃው ልክ እንደ ወያኔ እና የኦነግ ጀሌዎች “የመጎደኛነት ጸባይ” የሚያሳዩ ተከታዮቹ ችግር ስለሚፈጥሩ ባይገቡ ይመረጣል ብየ ከብዙ አማታት በፊት በጽሑፌ የዘገብኩት ስጋት መሰረት እንደሰጋሁትም ዛሬ በኢሳያስ አፈወርቅ ትዕዛዝ ከኤርትራ በመባረራቸው ምክንያት መሄጃ ስላጡ ምሕረት ተሰጥቶአቸው አገር ውስጥ እንዲገቡ ቢፈቀድላቸውም “ፍየል ከመድረስዋ ቅጠል መበጠስዋ” ሆኖ ኦነግ እና ግንቦት 7 በሚገርም ንትርክ ሚዲያ ላይ ቀርበው ሲዘላለፉ እና ሲወነጃጀሉ መስማት ለኔ አስገራሚ አልነበረም።

በዚያ ንትርካቸው በርካታ ንትርኮች ብንሰማም እጅግ የገረመኝ ግንቦት 7 “የኦነግ ባንዴራ እንደሚያከብሩ እና ለዚያ መብት እነሱም በኦነግ ስም ሆነው በዲያስፖራው ዓለም ሆነው ሲሰብኩላቸው እንደነበረ’ ያለ ማፈር የግንቦት 7ቱ ኤፍሬም ሲናገር ሰምቼው ‘ሰውየው “የግንጣላ ምልክታቸው የሆነው የኦነግ ባንዴራን ማክበር ኢትዮጵያዊ አርበኛነት መስሎት ሲመጻደቅ ሰምቼው ዛሬም ያለመማራቸው ሲገርመኝ በዚህ መስመሩ ግንቦት 7 ድሮ እንደተነበይነው ‘ለዚያ ራስን በራስ ማስተዳዳር ግብ ተብየው የኦሮሞዎቹ የማታለያ ሽፋን’ ፕሮፓጋንዳቸው እንደሚታገልላቸው በድጋሚ ግልጽ አድርጎልናል።

በዚህ ሂደት አገራችን አስፈሪ ማነቆ በአንገትዋ ስር አጥልቀውላታል ብሎ በግልጽ መናገር ይቻላል። ጽንፈኞቹ ከአስመራ ከተማ ከተባረሩ ወዲህ የሕዝባችን ጥንታዊ አንድነት ለማፍረስ አናርኪዎቹ የከፈቱላቸው በር ተጠቅመው ከመቸውም በበለጠ ትንፋሽዋን ለማሳጠር ተዘጋጅተዋል። በዚህ አስቸጋሪ ምዕራፍ ውስጥ በገሃድ የምናያቸው ሦስት የጥፋት ሃይላት እንዳሉ ግልጽ እንዲሆንላችሁ እፈልጋለሁ።ኦብነግ ኦነግ እና ህወሃት። ሦስተኛው አክራሪ እስልምና የሚከተለው በሲያድ ባሬ ፖለቲካ የሚዘወር ኢትዮጵያ አይደለሁም የሚለው “አብነግ” ወደ ጎን አቆይተን፡ ሁለት ግልጽ የሆኑ የጥፋት ተዋናያናዮቹ የኦሮሞ እና የትግሬ የፖለቲካ ሊሂቃን በስርዓቱ መዘውር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ አሉበት።

እነዚህ ያዋቀሩት የመንግሥት አስተዳደር አጅግ ወደ ኋላ ዘመን ሄዶ የጉልተኞችን አስተዳዳር ጎትቶ በአስከፊ መልኩ በማሳደስ፤ “ተጠያቂነት የሌለበት” “አጉራ ዘለል” አስተዳዳር ቀርጸው በሕዝብ ላይ አስከፊ ጭፍጨፋ እና አስተዳደራዊ ግፍ አስፍነዋል።

 አስገራሚ እና ልዩ የሚያደርገው ደግሞ ይህንን ግፈኛ አስተዳዳር ያመጡብን ብዙዎቹ በዘር ማጥፋት የተካፈሉ ሊሂቃን ዛሬ ለውጥ መጣ በተባለበት ወቅትም ከሥርዓቱ አልተወገዱም። አልተወገዱም ብቻ ሳይሆን  ‘ተለውጠዋል’ የሚባለው ስርዓት ውስጥ ሆነው ዛሬም ያለ ምንም ስጋት ተደላድለው እየነሩና እያስተዳደሩ ናቸው። ሳይነኩ በምቾት የመኖራቸውን ብቻ ሳይሆን ‘ለውጥ’ አለ የሚባለውን ለውጥ በተቀመጡበት የሓላፊነት መንበር ላይ ተቀምጠው እኛ የሰጠናችሁን ስርዓት እየተጣሰ ስለሆነ በግዳችሁ ትታዘዙታላችሁ እያሉ የጥገና ለውጡ መሪዎችን ወደ “አብዮታዊ ዲሞክራሲ” አሰራር እንዲመለሱ ሲያብለጠሉጥዋቸው መስማት አስገራሚ ነው።

አስገራሚ ካደረገው ልዩ አስገራሚነቱ ደግሞ የወያኔ አመራሮች “ሪቮሊሽናሪ ዲሞክራሲ” ፋሺስታዊ ማኣከላዊነትን የሚከተል የኮሚኒሰት ስርዓት አሰራር መሆኑን እያወቁ ‘ፋሺዝም’ መቀጠል እንዳለበት ሲሰብኩ ሰዎቹ ደረቅነታቸው (በሊጅረንት- ነታቸው) ስንመለከት ፈረንጆቹ “weird/ዊርድ” የሚሉት ቅንድብ የሚያስቆም ባሕሪ በመከተላቸው እጅግ እንግዳ እና ልዩ ሰዎች ያደርጋቸዋል። በምድራችን ያልታዩ ልዩ ሰዎች ስለመሆናቸው የሚገልጸው ባሕሪያቸው “የባሕሪ ምድሪ” (ባሕረ ምድር/ኤርትራ) ጉዳይ ስትመለከቱ ‘ኢትዮጵያ ያለ የባሕር በር መውጫ እንድትቀር ማድረጋቸው ብቻ ሳይሆን’ የገዛ መሬታቸው እና ሕዝባቸው ከተቀሩት ቤተሰቦቻቸው ጋር ተለይተው ለሁለት ተቆርጠው በሁለት አገር እንዲተዳደሩ ወደ ተባበሩት መንግሥታት እራሳቸው ሄደው የግንጠላ ማመልከቻ ማስገባታቸው ስንመለከት bizarre/ “እንግዳ ሰዎች” የሚለው ቃል ሊገልጻቸው የሚያንስ ገለጻ ነው። ይህንን አዲስ ክስተት “በባንዳነት” ቢተረጎምም ለተማሩ የታሪክ እና የሕግ ተመራማሪ ሊቃውንቶችም ሊገልጽዋቸው እንሞክር ቢሉም ለመግለጽ ቃላት “የሚያጡ” ናቸው ብየ እገምታለሁ። 

ለውጡ ያልተለመደ ክስተት ስላለው ‘ለውጥ አራማጁ’ እና ‘ለውጡ አሁንም እጃችን ሥር ውስጥ ነው’ የሚሉ የዚህ ስርዓት ሁለት ገፆች ስንመለከት ኢትዮጵያ በነዚህ ሃይላት የአንድነት እና የውጥረት ክስተት መታመስዋ እጅግ ለተንታኞች አስቸጋሪ ፖለቲካ አድርጎታል። ለውጥ አራማጁ/ጠጋኙ ቡድን/ ከምን እንደመነጫ ባይገባኝም በህወሓት ላይ ‘ድፍረት’ እያጣ መሞዳሞዱን እንደ ስልት በመጠቀሙ ፤ ህወሓቶች ሥልጣኑ አሁንም በእጃችን ስር ነው የሚለው የህወሓቱ ክፍል ዛሬም ጀብደኝነቱ እቦታው ላይ እንዳለ ለማሳየት አላስፈላጊ ግሳት ‘ሲያገሳ’ እየሰማነው ነው።

ህወሓት በመንበሩ ላይ ነኝ እያለ የውስጥ ሴራ ሲጎነጉን፤ ሁለተኛው ጽንፈኛ ኦነግ ደግሞ ለበርካታ አመታት የበከላቸው “የጥላቻ ታጣቂዎቹ” በአባልነታቸው አገር ውስጥ ያሉት ኦሮሞ ወጣቶች በድብቅ ስልጠና ሰጥቻቸዋለሁ የሚላቸው “የቄሮ ብሉሲማ” አባሎቹ በግድያ አልተካፈሉም ብሎ ቢክድም በቄሮ ስም የሚንቀሳቀሱ የስም ነጠቃ የተላበሱ ቄሮዎች ካልሆኑ የኔ ቄሮዎች በግድያ አልተካፈሉም ቢልም፡- ለ27 አመት በኦነግ እና በኦፒዲኦ የጥላቻ ቅስቀሳ የተበከሉ “ቄሮዎች” ‘በቡድንም ሆነ በተናጠል ከፍተኛ አሰቃቂ የግድያ ወንጀል እየፈጸሙ እያየን ነው። የጥላቻ ቅስቀሳ ለ27 አመት ለመላ ኦሮሞ ቄሮዎች ስለተሰበከ ቄሮዎች አባሎቻቸውም ይሁኑ አልሆኑ እነሱ ባስተማሩዋቸው የጥላቻ ቅስቀሳ በመበከላቸው የኦሮሞ ‘ቄሮ’ ለፈጸማቸው ወንጀሎች ሁሉ የወያኔ ፤ የኦፒዲኦም ሆነ የኦነግ መሪዎቹ በሃላፊነት መጠየቅ አለባቸው።

 ተገንጣዮቹ እነ በቀለ ገርባ እና ዲማ ነገዎ የተባለው በሕግ መቅረብ ያለበት አደገኛ ሰው በጋራ ሆነው በአዲስ አበባ መግለጫ ሲሰጡ Oromo extremist organization decalred to destroy the existence of Ethiopia and its people colaborating withe foreign enemies.
Egyptian Islamist extremists wearing OLF Flag in Cairo city where Egyptians organized  Oromo public gathering and vowed to destroy Ethiopia.ከላይ የሚታዩት የኦነግ ባንዴራ ለብሰው የሚጣዩ የብፅ እስላማዊ ሃይሎች ናቸው። ግብፆች እና ኦሮሞዎቹ በጠሩት  በዚህ የኦሮሞዎች ስብሰባ አዳራሽ ውስጥ ኢትዮጵያን አፍርሶ ኦሮሚያ የተባለ አገር በመመስረት በኣያቶቻችን የተሸነት ግብፆች ዛሬ የልጅ ልጆቻቸው በር አግኝተው አገር ለማጥፋት የተሰለፉ የሰው ልጅ አንገት እና ጡት በመቁረጥ ሰላማውን ዜጋ በማሸበር የሚገኙት የተገንጣይ ኦሮሞ አባሎች የኢትዮጵያን ህልውና ከምድረገጽ ለማጥፋት ግብፆች እና ኦሮሞዎ ቃል ኪዳን ሲገቡ የሚያሳይ ፎቶግራፈ ነው።

ታሪኩን ስንለመከት፡ እነዚህ የኢትዮጵያ ናዚዎች ከየት ተነስተው አሁን ወደ ደረሱበት በጣም አስፈሪ እድገታቸው ለመድረስ እንደቻሉ ለመፈተሽ ስሞክር፤ መነሻቸው እና መድረሻቸው ለማወቅ “የኢትዮጵያ ኦሮሞ  እና የትግሬ ናዚዎች ጉዞ ከየት ወድየት” የሚል መጽሐፍ የሚጽፍ ተመራማሪ ጸሐፊ ካልተገኘ በስተቀር በቀላሉ በጥቂት ገጾች መግለጹ የነዚህ የሰው አራዊቶች ወንጀል እና ባሕሪ ለመግለጽ እጅግ አስቸጋሪ ነው።የኦሮሞዎች እና የትግሬ ናዚዎች ያስፋፉት የወንጀለኛነት እና የጥላቻ ስነልቦና ባሕል ‘ለመቀነስ’ ቢያንስ ሦሰት ትውልድ (60-70 አመት) ሊጠይቅ ነው።

እኔ እና በጣም ጥቂት እውቅ ምሁራን የሆኑ የታሪክስነልቦና እና የስነ ኣእምሮ ተመራማሪ ወገኖቼ፤ ከሁለቱ ጎሳዎች የተገኙ ሁለቱ የፋሺስቶች ፖለቲካ አቀንቃኝ ቡድኖች የመነሻ ጥያቄአቸው ሰብአዊነትን እና ኢትዮጵያዊነትን ከምድረገጽ ለማጥፋት የተነሱ እንደነበረ ከጥዋቱ ስለነቃንባቸው፤ የቻልነውን ያህል ግለሰባዊ ትግል አድርገን ማሕበረሰባችንን ለማስረዳት እንደጣርን ብዙዎቻችሁ የምታስታውሱት የቅርብ ትግላችን አሻራዎች ይመሰክራሉ። በዚህም የተነሳ ብዙ ዘለፋዎች እና ወከባዎች ደርሶብናል።

ታስታውሱ እንደሆነ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት የታሪክ ምሁራን ባጣንበት ብዙዎቹ የታሪክ አዋቂዎች ‘አፋቸው ዘግተው በተቀመጡበት ወቅት’ ወደ መድረኩ ብቅ ብለው ስለ አገራችን ታሪክ እያስተማሩ የታሪክ በራዦችን በማጋለጥ እና በማሳፈር ብቃታዊ ትምህርታቸውን ያሳዩን እወቁ እና ብቸኛው ገናናው የታሪክ ምሁር የሆኑት ኢትዮጵያዊው ክቡር ዶ/ር ኅይሌ ላሬቦ ላይ የደረሰባቸው የተግንጣይ ኦሮሞዎች ዛቻ እና በሥራቸው ላይም ተጽእኖ ለማድረስ የተደረገው እጅግ አስገራሚ እና አሳፋሪ ዘመቻ ምን ያህል ፈታና እንደታለፈ ሁላችሁም ታስታውሱታላችሁ። እኝህ “የ2011 (2018) የአመቱ ምርጥ” የታሪክ መምህር እና በጸረ ኢትዮጵያ ሃይላት መካከል የታየው የታሪክ ሙግት ከቶ አይረሳም።

ምሁሩ ባላቸው የታሪክ ከፍተኛ ብቃት ባሳዩት አኩሪ ውይይት የተነሳ የታሪክ ከላሾችን ተገቢውን የታሪክ አስተምህሮ ስለሰጥዋቸው የኦሮሞ በራዥ ፖለቲከኞች አካዳሚያዊ ሓፍረት ተከናንበዋል። ስለሆነም ለሓፍረታቸው አማራጭ አድርገው የወሰዱት የተለመደው ባሕሪ የኚህን ስመጥር ምሁር ስም “ጥላሸት መቀባት” ነበር። በእኚህ ምሁር ላይ የተደረገው የስም ማጥፋት ርብርብ የተቆጩ ኢትዮጵያውያን ዘመቻውን በአሸናፊነት አክሽፈውታል። ለዚህም ኢትዮጵያውያን ያሳዩት ታላቅ ስራ ታሪክ በኩራት ዘግቦታል። አጋጣሚው ያሳየን ክስተት የተገንጣዮች ጨቅላነትና አለመብሰል ያየንበት አጋጣሚ ነበር ። ዛሬ እነዚህ ክፍሎች በመደመር ሰበብ አገር ውስጥ ገብተው ገበርዲን/ሱፍ/ ለብሰው ‘ክራባት’ አስረው ‘ሰው መስለው’ በሚዲያ ለሕዝብ ቀርበው ስለ ዲሞክራሲ እና የመጻፍ የመናገር መብት ሲመጻደቁ ስናይ የዚህ አለም አታላዮች ባሕሪ እና  የሓፈረት ትርጉም የማያወቀው ትዕይንታቸው ለመተንተን ብንሞከር ከመገረም አልፈህ ሌላ ምን እንደምትላቸው ይጨንቃል።

ብዙዎቹ በወንጀል ድርጊት የተካፈሉ ስለሆኑ ጤነኛ ፖለቲካ ሊከተሉ ያስቸግራቸዋል። አገር ሰላም ከሆነ በሕግ እንደሚጠየቁ ስለሚያውቁ ብጥብጥ እና ሽብር እንዲቀጥል ፍላጎታቸው ነው። ለዚህም ነው የመገንጠል አባዜአቸው ሊለቃቸው የማይፈልጉት። አሁን እየተፈጸመ ያለው የግድያ፤የዘረፋ፤ ሴቶችን አስገድዶ መድፈር እየታየ ያለው ክስተት እነዚህ ክፍሎች ያስተማሩት የበሰበሰው የጭንቅላት ውጤት ነው። ይህን ክስተት እንዳይከሰት ገና ከጅምሩ ታግለናቸዋል። እኛ በጣም ጥቂት ስለሆንን የፋሺስቶቹ ዕድገት አሁን ወደ አለበት ደረጃ ከመድረሱ በፊት ልናቆመው ብንሞክርም በፍጥነት ማስቆም አልቻልንም። ይህ ሊሆን የቻለው ደግሞ ብዙ ምክንያቶች ቢኖሩትም ዋናው እና እንቅፋት የሆነብን በምሁር ደረጃ ያለው አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ዜጋ እና በጋዜጠኛነት ተሰልፈው በቴ/ቪ እና ድረገጾች በውጭም በውስጥም ሲረጭ የነበረው ጸረ አገራዊ ሴራ እየተቀበሉ ሲያስጋቡላቸው ስለነበረ ነው።

የሚገርመው ደግሞ እነዚህ ክፍሎች በአገራዊ ደህንነታችን ላይ ጉዳት እንደማያመጡ በእነሱ ስም ሆነው “እየተለሳለሱ”፤ የነዚህ ናዚዎች የትግል እንቅስቃሴ “የፍትሕ” ጥያቄ እንጂ  ኢትዮጵያን ለማተራመስ እንዳልሆነ እያወናበዱ ለሕዝብ በመቀስቀስ ከጎናቸው በመቆም ከፍተኛ የመተባበር ስራ በመስራታቸው እነሆ ዛሬ እነዚህ ክፍሎች ከጊንጥነት ወደ ዘንዶነት እንድያድጉ ረድተዋቸዋል።

እንደሚታወቀው ጥቂቶች እንደ ዕብዶች እየታየንም ቢሆን እንዲያም ሆኖ አድካሚ ትግል አድርገን በርካታ ተቃዋሚ ወደ ጎራችን አስሰልፈናል። አሁን እየታየ ያለው በርካታ ተቃዋሚ ወደ እኛው ጎራ የተቀላቀለበት ምክንያት በእኛ የትግል ጥረት እንደሆነ ታሪክ የሚክደው አይሆንም። እንደምታወቁት ወያኔ ከገባ በላ ለበርካታ አመታት ተቃዋሚ የሚባል እጅግ ጥቂት ነበር። ታዋቂው የሕግ መምህር እና ጠበቃ “አል ማርያም”ም እራሱ እንደነገረን ከቅንጅት ወዲህ (1997) ነበር ወደ ትግሉ ብቅ ያለው። ባጭሩ ስንት ተቃዋሚ እንደነበረ ሕሊናችሁ የሚያውቀው ነው። በእዛው አስቸጋሪ ዘመን በብቸኛነት እየተሰደብን እየተገለልን ‘ችቦው’ እያቀጣጠልን እዚህ ድረስ አድርሰነዋል። የሚገርመው ሌላው ጎኑ ግን ተቃዋሚ በተበራከተበትም ወቅት  የትግሉን አቅጣጫ በከሉት። ለትግሉ ይጠቅማሉ ተብለው ተስፋ የተጣለባቸው የሕግ አዋቂዎች በሰብአዊ ወንጀል የተካፈሉ በርካታ ወንጀለኞች እዚህ አውጭ አገር እየተመላለሱ እየተንሸራሸሩም ሆነ በኗሪነት እየኖሩ እየታወቀ አንድም ወንጀለኛ ለማስተማሪያ የሚሆን በሕግ ከስሰው በሕግ ሊያስቀጡ አልቻሉም።

እነ አል ማርያም ወንጀለኞችን እያደኑ ወደ ሕግ ከማቅረብ ይልቅ የባንክ ሠራተኛ ይመስል ገንዘብ በማሰባሰብ ስራ ተጠምደው ወንጀለኞች የሚከታተል የሕግ ባለሞያ ስለሌለ ወንጀለኞቹ ተዝናንተው እያሾፉብን ይኖራሉ።ያውም በገሃድ እነሱንም ጭምር እየቀለዱባቸው ለበርካታ አመታት ዘልቀዋል። ሌላ ቀርቶ እነ አልማርያምም ሆኑ እነ ግንቦት 7 ከቅንጅት ምስረታ እና መፍረስ በላ  የተከሰቱ ታጋዮች ቢሆኑም ወደ ዲያስፖራው የትግል አለም ሲመጡ አይተነው እና ሰምተነው የማናውቀውን ክፍፍል እና ቡድናዊ ንትርክ ውስጥ ጎትተው አስገቡን። ከአገር ይዘዋቸው የመጡ ካድሬ ጋዜጠኞቻቸው እና እዚህ የነበሩ ተከታዮቻቸውም ይብልጡኑ በሹል ምላሳቸው ትላልቁን ዛፍ “ሌባ” በማለት መወንጀል ጀመሩ። ሃይሉ ሻውልን እና የኢትዮጵያ መምህራን ሊቀመንበር የነበረው ታየ ወልደሰማያትን በዚያ ጸያፍ ውንጀላ ይዘረጥጡዋቸው ጀመር። በዚህ መልክ በርካታ ጀሌ ምሁራንን በማሰማራት አንድነታችንን ከፋፈሉት። ኦነግ ከጊንጥነት ወደ ዘንዶነት እንዲያድግ አስተዋጽኦ አደረጉ።

 -
ዛሬም አብይ መጣ ተብሎ አይተናቸው ሰምተናቸው የማናወቅ ሰዎች ትግሉን መቀላቀላቸው የሚበረታታ ቢሆንም ከጥቅሙ ለጉዳቱ አመዛኝ ብትር እያቀበሉ ሆነው እያየናቸው ነው። መደመር የሚለው “የአፍዝዝ ወ አደንዝዝ” የስነ ሕሊና ጠለፋ ውስጥ የገባው በሚሊዮን የሚቆጠር ምሁር እራሱን ለዳግም መሳቂያ እንዳይሆን ካልተጠነቀቀ አሁንም ወዴት እየሄድን እንደሆነ መንገዱን በጥንቃቄ ካልተራመዱት አስቸጋሪ ማጥ ውስጥ እንዳይከተን ስጋት አለኝ።

ለውጡን በበጎ ማየት ጥሩ ነው። ነገር ግን እንደ ዕብድ ነጣለችንን ጥለን ሰማየ ሰማያት የምንከንፍበት ባሕሪ ግን ቆም ተብሎ መፈተሽ አስፈላጊ ነው እላለሁ።ካሁን በፊት ያየነው ልምድ ያንን ያሳየን ነው። እነ በቀለ ገርባ እነ ጃዋር ፤ እነ ተስፋየ ገብረአብ አፍራሽ ሃይሎች ናቸው ብለን ስንላቸው አንሰማም ብለውን የፖለቲካ ሃሁ ያልገባቸው ‘አዝማሪዎችን’ በማሰማራት በቀለ ገርባን ብርሃኑ ነጋን አንዳርጋቸውን እና ኤፍሬም ማዴቦን፤ሌንጮን የመሳሰሉ ጊንጥ ፖለቲከኞች በዘፈን እና በግጥም እያወደሱ የዜጎች ሕሊና መበከል ጀመሩ።

አስገራሚ የሚያደርገው ክስተት ‘አፄ ምንልክ፤ አፄ ቴዎድሮስ እና ደጃዝማች በላይ ዘለቀ እንዲሁም የዛሬዎቹ አርበኞቻቸው መረራ ጉዲና እና በቀለ ገርባ እንዲሁም ብርሃኑ እና አንዳርጋቸው ጽጌ ከነዚህ ነገሥታት ጋር ባንድነት አገናኝተው’ የዘፈን ቪዲዮ ቀርጸው ሲያሞግሱዋቸው፡ “ዮሃንስ” ትግሬ በመሆናቸው ብቻ “የአማራ ጠላት ነው” በሚል ወይንም ከወያኔዎች ጋር በማገናኘት ይመስለኛል፤ በታተመው ቪዲዮ ውስጥ ነጥለው እሳቸውን ብቻ አስቀርተዋቸዋል።

ይህ ዘረኛ እና አሳፋሪ የቪዲዮ ቀረጻ የተከናወነው “አሞኛል በለው!” በተባለው ሙዚቃ ውስጥ ነው። የቪዲዮ እና አውድዮ ዳሬክተሩ የሹክሹክታ እንዲሁም የዘሓበሻ እና የሳተናው ድረግጽ ዋና አዘጋጅ የሆነው ወጣት ሄኖክ አለማዮህ የተባለው የመኔሶታ ነዋሪ ነው። ያ ቪዲዮ ስመለከት የዘመናችን ወጣቶቹ ሕሊና ከዘሙ ፖለቲካ ጋር እያገናኙ “ደማቸው አፍስሰው “ሰፊ አገር” ላስረከቡን ታላላቅ ነገሥታቶቻችን እና ወላጆቻችን ያላቸው አነስተኛ አክብሮት ስታዘብ “አገራችን እና ታሪኳ” ወዴት አቅጣጫ እየተገፋች እንደሆነች ሳስበው አንጀቴ ይቃጠላል።

እንዲህ ያሉ በጥላቻ ሕሊና የሚቀረጹ ለትውልድ የሚተላለፉ ቪዲዮዎች/ፊልሞች/ በጥንቃቄ ካልተቀረጹ ጥላቻው የሚቀጥለው ትውልድ ይረከበዋል። የሚዲያ ሰዎችም እንዲህ ባለ አስገራሚ ቡድንተኛነት ገብተው ፖለቲካው ይበልጡኑ እንዲደፈርስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማድረገቻው ያሳዝናል። እነዚህ ሁሉ የማን ውጤቶች ናቸው ብንል ቀስ እያለ ረዢም ጉዞ የተጓዘው የህወሓት፤ ኦፒዲኦ፤ ግንቦት 7 ፤ ኦነግ፤ ጃዋር እና ፣….ወዘተ…ወዘተ.. ውጤቶች ናቸው። እነኚህ ወገኖች በምሕረት ወደ አገር ከገቡ በኋላም ቢሆን እየተደመጠ ያለው ‘ዱላ ቀረሽ’ ንትርካቸው አዲስ አበባ እና አካባቢዋ አስቸጋሪ ከተማ አድርገዋታል። በተበከለው አየር ሌላ ተጨማሪ ብከላ!

ኦነግ እና ተመሳሳይ የኦሮሞ ድርጅቶች በዘር ማጥፋት የተካፈሉ የወንጀለኞች ሕጋዊ መድረክ ተከፍቶ ወንጃለቸው እስኪጠየቅ ድረስ መንግሥት ተብየው ስርዓተ አልባው ሥርዓት የባሰውኑ ጥፋት ሳያስከትሉ “ይቆጣጠራቸው” ወይንም ወደ ተጠረዙበት አገር ወደ ኤርትራ እንዲመለሱ ይጠርዛቸው። ሆኖም አቤቱታችን “ውሻ ነከሰኝ ብሎ ለጅብ አይጮኹም” ስለሚሆንብን አምላክ ኢትዮጵያን ከውሾችም ከጅቦችም እራሱ ይጠብቃት ከማለት የምንለው ነገር የለም። አምላክ ደግሞ ከሰዎች ፍርድ በበለጠ በቅጽበት ፍርዱን የሚወስን ስለመሆኑ በመለስ ዜናዊ እና በአባ ጳውሎስ የወሰነው ውሳኔ ምስክር ነው።

የትግሬ እና የኦሮሞ ናዚዎች በወንጀለኛነት ስነልቦና የበከሉት ወጣት ሕሊናው ጤናማ ለማድረግ ብዙ አመት ለምን እንደሚፈጅ በክፍል ሁለት እንመለከታለን ። እነ ለማ መገርሳ እና እነ አብይ አሕመድ የተከሉት አኖሌ ሃውልት ወጣቱን ከዚያ የቂም አመንዣኪነት እና የውሸት ሕሊና ብክለት ለማጽዳት ሦስት ትውልድ ብቻ ሳይሆን 100 የሚፈጅ ይመስለኛል። ለምን የሚለው በክፍል ሁለት እንመለከታለን። ክፍል 2 ይቀጥላል….
      ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay) getachre@aol.com



Sunday, September 23, 2018

አዲስ አበባ የመጀመሪያ ስሟ (ሐብታሙ ተገኘ) Note from the Editor (Ethiopian Semay)


አዲስ አበባ የመጀመሪያ ስሟ (ሐብታሙ ተገኘ)
Note from the Editor (Ethiopian Semay)-
What is the Original name of አዲስ አበባ? Can the Oromo leaders answer this question? I doubt they can challenge this document. Lying is the guideline of the secessionist Oromo leaders since creation of this organization. Lema Megersa, I have heard you all the time calling ‘Addis Abeba’ as ‘Finfine’. Who taught you to call Addis as Finfine? Is not it, the OLF? If not the OLF, then who taught you to say it as Finfine? And you believed their lies and kept lying with it as we speak. But can you answer this challenge, if you really have one to answer? This question is not only to you, but, to all misguided, miss taught OLF criminal and liar leaders. Please read this document and come with an answerer if you have one at all.  We doubt none of you liars have an answer to the following document! Shame on you liars! Your flag is lie, your way of presenting history is lie. Lying after lying...after lying....endless lie.
አዲስ አበባ የመጀመሪያ ስሟ (ሐብታሙ ተገኘ)
September 22, 2018
ሐብታሙ ተገኘ
የአዲስ አበባ የጥንት ስም “በረራ” ነው፡፡ በረራም ፣ የነገስታቱ ቀዳማዊ ዋና መቀመጫ ከተማ በመሆን ፣ ከአፄ ዳዊት ቀዳማዊ ዘመን ፣ (ከ1380-1413 ) ድረስ ፣ እንዲሁም በአፄ ልብን ድንግል ስርወ መንግስት ዘመን ፣ማለትም (ከ1408-1480) ፣ በረራ ከመቶ አመት በላይ አገልግላለች፡፡ በረራ ወረብ በሚባል አውራጃ ስር ትተዳደር እንደነበር ፣ የታሪክ መዛግብቶች ያስረዳሉ፡፡ ወረብ ታላላቅ አብያተክርስቲያኖች እና ቤተመንግስቶች የነበሩበት ፣ በጣም ሀብታም አውራጃ ነበር፡፡ በዚሁ ዘመን ፣ የግራኝ አህመድን ጦርነትን ከግራኝ ወታደሮች ጋር እየተዘዋወረ ሲዘግብ ፣ ወረብንና በረራን ያየው ፣ ሻሀብ አደዲን እብዱልቃዲር ፤ “ፉቱህ አል ሃበሽ” በተሰኘው መፀሐፉ ፣ “በረራን የሐበሾች ምድራዊ ገነት” ይላታል::
የበረራን ታሪክ የፃፍነው አንዱን ነባር ሌላውን መጤ እና እንግዳ ለማድረግ አይደለም፡፡ ፅሑፉን ለማዘጋጀት የተፈለገው ስለ አዲስ አበባ የኋላ ታሪክ ያለውን የታሪክ ክፍተት በተወሰነ መልኩ ለመድፈን ያግዛል እንዱሁም ስለቦታው ታሪክ ኢትዮጵያዊያን ትክክለኛ መረጃና እውነት እንዲኖራቸው በማሰብ ነው፡፡ የዚህ ፅሑፍ ይዘት ያልነበረን ወይም ያልተነገረን አዲስ ታሪክ ለማስተዋወቅ አይደለም፡፡ ለዚህ ፅሑፍ የተጠቀምናቸው ማስረጃዎችም ከዚህ በፊት ስለ በረራ ታሪክ መፃፋቸው የታወቁ ምንጮች ናቸው፡፡ ይህ ፅሑፍ ሁለት አላማዎች አሉት፡፡ አንደኛው የበረራን ወይም የአዲስ አበባን የኋላ ታሪክ ባጭሩም ቢሆን ለመዳሰስ ነው፡፡ ሁለተኛው ስለ በረራ በኢትዮጵያዊያንም ሆኑ በውጪ አገር ፀሐፊዎች የተፃፉ ታሪኮችን ለአንባቢ ለማስተዋወቅ ነው፡፡ በተለይም የቦታው ተወላጆች ስለበረራ በሰጡት ምስክርነት ላይ የተፃፉትን ለማካተት ይሞክራል፡፡ የበረራን ታሪክ ያጠኑ ተመራማሪዎች ኦጂኤስ ክራውፎርድ ሪቻርድ ፓንክረስት እና ሀርትዌትግ ብሪትሪት ሳሙኤል ዎከር እና ማርኮ ቪጋኖ ይገኙበታል፡፡ በተጨማሪም ታዋቂው ጣሊያናዊ የካርታ ባለሞያ ፍራ ማውሮ በረራንና ባካባቢው ያሉ ከተሞች ወንዞች ተራሮች እና ገዳማት 1450 አመተ ምህረት ባዘጋጀው የአለም ካርታ የቦታውን ተወላጆች በመጠየቅ አስፍሯቸዋል፡፡
ፍራ ማውሮ የአለም ካርታ ፣ በትክክለኛነቱ በአለም የተደነቀ ነው፡፡ ካርታው ፣ አውሮፓውያን ኢትዮጵያን ጨምሮ አለምን ለማሰስ በዘመኑ ባደረጓቸው ጥረቶች ውስጥ ፣ ከፍተኛ ሚና ተጫውቶላቸዋል፡፡ ፍራማውሮ ለሳይንስ እውቀት እድገት ላደረገው አስተዋፅኦ እውቅና ለመስጠት ፣ የጨረቃ የተወሰኑ አካላት በስሙ ተሰይመውለታል፡፡ የበረራ ታሪክ ፣ ከአፄ ዳዊት ፣ ማለትም ከ1380-1413 – ቀጥሎም እስከ አፄ ልብነ ድንግል ዘመነ መንግስት ፣ ከ1508-1540 ፤ ስለ በረራ የመጀመሪያው የታሪክ ማስረጃ ፣ በ1450 የተሳለ የአለም ካርታ ነው፡፡ በዚህ ዘመን የኢትዮጵያ ንጉስ የነበሩት አፄ ዘረ-ያእቆብ ፣ ከ1434-1468 ድረስ የገዙት ናቸው፡፡ ነገር ግን የበረራ ታሪክ ከዚህ ይጀምራል ማለት አይደለም፡፡ ከተማው ተመስርቶ ፣ አድጎ ፣ ለነገስታቱ መቀመጫነት እስኪበቃ ድረስ ፣ ብዙ አመታት መፍጀቱ አይቀርም፡፡ የአፍቃል መረጃ እንደሚያስረዳው ፣ “እንጦጦ ፣ ወይም በረራ” ፣ በዋናነት የአፄ ዳዊት ከተማ እንደነበር ነው፡፡ አፄ ዳዊት የዘረ ያእቆብ አባት ሲሆኑ ፣ የነገሱት ከ1380 አመት ጀምሮ ነበር፡፡ ስለዚህ ከፍራማውሮ የአለም ካርታ መዘጋጀት በፊት ፣ በረራ የአምሳ አመት እድሜ አስቆጥራ ነበር ማለት ነው፡፡ ካርታው በያዘው መረጃ ብዛትና ጥልቀት ፣ በዘመኑ ተወዳዳሪ አልነበረውም፡፡ የፍራማውሮ ካርታ የመጀመሪያው የሚታወቅ ሳይንሳዊ ካርታ ነው፡፡ ሳይንሳዊ የሚያደርገው ፣ በመሬት ላይ ባሉ ተጨባጭ እውነታዎች ላይ እንጂ ካርታው ከሃይማኖታዊ ግብአቶች ይልቅ ፣ በመሬት ላይ ያሉ ነበር እውነታዎች ላይ ተመስርቶ የተዘጋጀ በመሆኑ ነው፡፡ በካርታ ስራውም ብዙ ባለሞያዎች ተሳትፈዋል፡፡ የኢትዮጵያን ካርታ የሚያሳየውን የዚህን ካርታ ክፍል እንደ ማስረጃ ተጠቅመነዋል፡፡
መረጃውን የሰጡ ሰዎች በተለይም የአዋሽን ወንዝ በረራን እና የዝቋላን ገዳም የሚያውቁ መሆን ነበረባቸው፡፡ ካርታው በሚያስደንቅ ሁኔታ መሬት ላይ ያለውን ሁኔታ ያንፀባርቃል፤ በረራንም በደንብ ያሳያል፡፡ በተጨማሪም የንጉሱ ዋና መቀመጫ መሆኑንም በደንብ ይገልፃል፡፡ በበረራ አካባቢ ያሉ ከተሞችን ወንዞችንና አድባራትን ያሳያል፡፡ ከነዚህም ውስጥ የአዋሽ ወንዝ የዱከም ወንዝ የዝቋላ ገዳምና የአምባ ነገስት ተራራ ይገኙበታል፡፡ ሁሉም እስከዛሬ ድረስ በትክክለኛ ካርታው ላይ በተገለፁበት አቀማመጥ እንዳሉ ይገኛሉ፡፡ ዱከም ከየረር ተራራ የሚመነጭ አነስተኛ ወንዝ ነው፡፡ በዚህ አካባቢ ያሉ ስሞችን ኦሮሞዎች ከዘመናት በኋላ ስያሜዎቹን ቢቀያይሩትም ዝቋላበጥንታዊ ስሙ እስካሁንም አለ፡፡
በዚህ ፅሑፍ ውስጥ ያሉት ፎቶዎች እና አንድ ቪድዮ፣ የአዲስ አበባን ጥንታዊ የፈረሱ የነገስታት መኖሪያ ቤተመንግስት የሚያሳይ እና በአውሮፓዊያን የአጥኚ ቡድን እቦታው በመሆን ባደረጉት የቁፋሮ ጥናት የተረጋገጠ ነው፡፡ በተጨማሪም የሳተላይት ካርታው የምኒሊክ ቤተመንግስት ከተመሰረተበት እንጦጦ አካባቢ ይህ የቀድሞዋ ጥንታዊ ከተማ በረራ በትክክል የት ከስድስት መቶ አመት በፊት ተመስርታ ታገለግል እንደነበረች የሚያሳይ ማስረጃ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ ብቻ ሳይሆን የፍራ-ማውሮ ካርታ እና የፍቱል ሃበሻ የአይን እማኝ ምስክርነቶች እና አያሌ መዛግብት፤ የአሁኗ አዲስ አበባ የቀድሞዋ የበረራ ከተማ ለመሆኗ በከፍተኛ ማስረጃ የተደገፈ ታሪካዊ የቀዳማዊ አፄ ዳዊት መናገሻ እንደነበረች ማሳያ ነው፡፡ በንባቡ ይማሩበት ሌሎቹንም ማስረጃዎች መርምሮ ለማስረዳት በዚህ ፅሑፍ ውስጥ የተጠቀሱትን ተመራማሪዎች ስራዎች በማየት ማረጋገጥ ይችላሉ።
Posted at Ethiopiansemay.com