Saturday, December 28, 2013

ግንቦት 7 እያካሄደ ያለው ማፊያዊ የግድያ እና የአፈና ዘመቻ ተጋለጠ! ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያን ሰማይ)

ግንቦት 7 እያካሄደ ያለው ማፊያዊ የግድያ እና የአፈና ዘመቻ ተጋለጠ!
ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያን ሰማይ) December 29, 2013
እነዚህ ፎቶግራፍ ላይ የሚታዩ ኢትዮጵያዊያን ዛሬ ከኤርትራ ምድር ሸሽተው በበጎ አድራጊ ወገኖቻቸው እርዳታና ተባባሪነት በድብቅ ላይ ይገኛሉ። በግንቦት 7 ያዙልኝ ባይነት በሻዕቢያ አፋኝ ሰዎች እየታደኑ ስለሆኑ ተደብቀው ይገኛሉ። ታሪካቸው ወደ ታች እንመለከታለን።
ካረንት አፌርስ (ECADF) (ኢትዮጵያን ካረንት አፌርስ) ድረገጽ እና ፓልቶክ በተባለ የመወያያ መድረክ ላይ ተለጥፎ በነበረው አስፈሪ የማፊያ መሳይ ማስተወቂያ ነው ጽሑፌን የምጀምረው። ቴድሮስ ይባላላል። የግንቦት 7 ሕዝባዊ ሃይል ታጋይ የነበረ ነው። ስለ ቴድሮስ መታፈን እና ግድያ ከላይ በጠቀስኩት የግንቦት 7 ደጋፊ ድረገጽ የተለጠፈው አስፈሪ ማስታወቂያ እንዲህ ይነበባል፡

ይ ህ ሰው   አደ ገኛ    ይፈለጋል!! የሚል ስታወቂያ  ከረንት አፌርስ የመ ያያ ረክ እና ድረገጽ ላይ  ተለጥፎ የነበረ ነው። እንዲህ ያለ አስፈሪ እና የሰው ልጅ በነፃነት ምርጫን የመምረጥ ተጻራሪ የአፈና ባሕሪ ሚዲያዎች ተባባሪዎች ሆነው የግድያ እና የአፈና ስራ እንዲቀጥል ሲጥሩ ማየት አስፈሪ ክስተት ከመሆን አልፎ፤ እንዲህ ያለ የግድያ እና የሰው ልጅ ማስፈራራት ባሕሪ ማስታወቂያ መለጠፍ የሚያሳየን ምልክት ቢኖር በሚቀጥለው መጪው ስርዓትም ቢሆን የግንቦት 7  መሪዎች እና ተከታዮቹ ስልጣን ላይ ቢወጡ ከወያኔ እኩል ወይንም በባሰ መልኩ አፋና እና ነብሰገዶዮችን በሕዝቡ ላይ የሚያሰማሩ መሆናቸው ጠቋሚ ምልክት ነው።ኢካዴፍ እና ኢሳት የመሳሰሉት ሁሉ የግንቦት 7 ፕሮፓጋንዳ አሰራጪዎች ስለሆኑ የምትለግሱት የገንዘብ ዕርዳታ ካለ ካሁኑኑ አቋማችሁን መመርመር ይኖርባችሗል።
 
ባለፈው ዓመት በውሽት ደልለው ከወሰዷቸው መካክል ዕድል አጋጥሞት ያመለጠው ቴዎድሮስ የሰጠውን ምስክርነት እዚህ በመጫን ያዳምጡ።http://ginbot7d.org/audio/LetterInsiderPartf1.m3u http://ginbot7d.org/audio/LetterInsiderFromPartf2.m3u ይህንን ሰው ነው ኢካዴፍ/ECADF የተባለው ድረገጽ “አደገኛ ተፈላጊ” እያለ ታድኖ እንዲታፈንና እንዲገደል በሕይወቱ ላይ ማስተወቂያ ለጥፈውበታል። አሁን በየቤታቸው ሆነው በኢንተርኔት ባቋቋሙት “መንግስታቸው” ሰው አንዲታፈን ሲያዙ መንግሥት ሲሆኑ ምን ያደርጉን ይሆን? ድረገጹ የሚያከሂደው ግለሰብ ደግሞ ከናዳ ውስጥ የሞቀ ኑሮ እየኖረ ነው ሰው ለምን ከአንዳርጋቸው ጽጌ አፈና እና ብልሹ ችሎታ ሸሸ በማለት የሸሸ ሁሉ መገደል አለበት እያለ በድረገጹ እና በፓልቶክ ክፈሉ የለጠፈው (ድረገጽና ፓልቶኩ  የሚያካሂዱት ሰውየው እንደልቡ ሲሆን ሴትዮዋ ደግሞ ሙያየ ምስክር እያለች ራስዋን የምትጠራ የድሮ ራዲዮን ሰራተኛ ነበረች የምትባል የትግሬ ሕዝብ ጠሊታነቷ በግልጽ በመናገር ዘረኛነቴን እኮራበታለሁ አንጂ  አላፍርበትም “ከእንግዲህ ወዲህ ዘረኛ ነኝ” እያለች የምትናገር በዘረኛነቷ የምትኮራ ሴት ነች )። ይህ ፓልቶክ እና ድረገጽ ነው ታማኝ በየነ የተባለው የኢሳት አፈቀላጤ “ሓብላቒ” በትግርኛው ቋንቋ ሓብለቒ (ማርኛው ምናልበት ዘብራቂ (?) “እናት ክፍሌ” እያለ በማሞኳሸት የሚኩራራበት እና  የሚጠራው። አንዳንድ ተቺዎች ይህንን የፓልቶክ ክፍል በዘረኛ እና በሰካራሞች ሁሌም ስለሚጣበብ  “በቅባ ቀዱስ ታጥቦ የማይጠራ ክፍል” ይሉታል፤፡

ብርሃኑ ነጋ እና አንዳርጋቸው ጽጌ ‘የተባሉ ሁለት የወያኔ  አገልጋይ የነበሩ ወዳጆቹም (በተለይም አንዳርጋቸው ጽጌ ወያኔን በመወከል ፋሺስታዊው የወያኔ የጐሳ ርዕዮተ አለሙ ክፍል ከመለስ ዜናዊ ቀጥሎ ተወካይ እና ግምባር ቀደም ተሟጋች ካድሬ እንደነበረ እራሱ ነግሮናል።)

እነኚህ ሁለቱ ‘ቅንጅት’ ሲባል የነበረው ሀገራዊ የፖለቲካ ተቃወሚ ድርጅትን እንዴት ሾልከው ገብተው አንዳመከኑት ብዙዎቻችሁ ታስታውሷቸዋላችሁ።

ከዚያም ቀጥለው በርቱካን መዲቅሳ የተባለቺው ወጣት ዳኛን አንደ አበባ መሃላቸው ላይ በማስገባት እሷን እየገፉ እነሱ ከሗላ ሆነው የተጫወቱት ማፊያዊ “ኮንሰፒራሲ” ተንኮላቸው አንዴት እንዳከናወኑት እና እሷንም ከሃይሉ ሻውል ቡድን ነጥለው ከጨዋታ ውጭ አንዴት  እንዳደረጓት ታስታወሳለችሁ። በሗላ ብርሃኑ ነጋ ኡደት ሲፈጽምበት በነበረበት አገር እዚሁ አሜሪካ ውስጥ በመቅረት “ምስጢራዊ እገዛ” እና እንክብካቤ ተደርጎለት ግንቦት 7 የተባለ  ተቃዋሚ ድርጅት በመመስረት በርከት ያሉ ‘አቃጣሪ ሊሂቃንን’ በማሰባሰብ ማሕበረሰቡን በማጃጃል መጠኑ የማይታወቅ የገንዘብ ገቢ እና ሙገሳ አግኝቷል።
የድርጅቱ መሪዎች ሥራ ተቀጥረው ኑሯቸው እየገፉ ለ6 ኣመት የህል ያለ ምንም ወታደራዊ እንቅስቃሴ ከኣገር አገር እየዞሩ ጅላጅሉን ሕብረተሰብ የሕልም እንጀራ እያስቦኩ አዳራሽ ውስጥ ሲያንጨበጭቡት ቆይተው በሗላ ከኤርትራው የሻዕቢያ መሪ ከኢሳያስ አፈወርቂ ጋር በመገናኘት ወታደራዊ እርዳታ እንዲደረግላቸው ወደ አስመራ በመጓዝ የጠየቁት ተደረገላቸው። ሃረና በተባለው የማስለጠኛ ጣቢያ ቦታ ቢሰጣቸውም፤በሁለት አመት ውስጥ በድምሩ ከ37 ሰልጣኖች በላይ ማግኘት አልቻሉም። አሁን ከ7 እስከ 10 የሚሆኑ ታጋዮች እንደቀሩ ነው ከእዛው አምልጠው ነብሳቸውን ያዳኑ ታጋዮች እየገለጹልን ያሉ።
ከእስራት፤ ከድብደባ/ቶርች፤ከአምባ ገነናዊ ምስቅልቅ፤ከእርስ በርስ ንትርክ እና ድብድብ እና አናርኪ አስተዳዳር እየሸሹ ጎረቤት አገሮች ውስጥ ተደብቀው የሚገኙ የግንቦት 7 ታጋዮች ሰሞኑን እያስተላለፉት ያለውን አስፈሪ አሳዛኝ ታሪክ እና የድረሱልን ተማጽኖ ግንቦት 7 ዲ በተባለው ድረገጽ ጥሪያቸውን ይፋ ሆኗል።
ሆኖም የህ የድረሱልን ጥሪ እና ግንቦት7 የተባለ በብርሃኑ ነጋ ፤ በኤፍሬም ማዴቦ እና አስመራ በሚኖረው አንዳርጋቸው ጽጌ የሚመራ ወንጀለኛ የማፊያ ድርጅት በነዚህ ግለሰቦች ሕይወት ላይ አደጋ ለመጣል ተሸሽገው ባሉባቸው አገሮች/በረሃዎች (በዊች ሃንት ዳሰሳ) በመከታታል አስጨንቀው “ሃራስ” በማድረግ አፍነው እንደገና ወደ ኤርትራ ለመውሰድ ዘመቻ በማካሄድ ላይ ናቸው።
ይህ ዜና ግን የሕዝብ ዓይን እና ጀሮ ነኝ እያለ በውሸት የሚኮፈስ “ኢትዮጵያዊ ሚዲያ” ነኝ የሚለው ሌላኛው በግንቦት 7 በኩል በሻዕቢያ የሚደጐም ‘ኢሳት’ ሆን ብሎ ዜናው እንዳይሰራጭ አፍኖታል። ይህ በኢሳያስ እና በአረቦች ገንዘብ የሚተዳዳር ሳተላይት ቲቪ እና ራዲዮን የነዚህን ኢትዮጵያዊያን ፎቶግራፍ በግዳጅ ላይ እንዳሉ በማስመስል ሻዕቢያ በትከሻቸው ላይ የማያውቁትን ላውንቸር እና መትረየስ በግድ ጭኖባቸው ተሸክመውት የተነሱትን ፎቶግራፍ በየጊዜው በማሳየት ሕዝቡን በማሳሳት ዘመቻ በውሸት ተጠምዶ አንዴ ‘የድምሒት’ አንዴ የግንቦት 7 ‘ሕዝባዊ ሃይል’ ወታደራዊ ዜና እያለ ውሸት ሲያቦካ የነበረውን ዜና ጋብ በማድረግ ሕዝባዊ ሃይል ሲለን የነበረውን ወታደራዊ የግንቦት 7 ሃይል “ዛሬ” ምን በላው ለሚሉ ጠያቂዎች ምንም ምላሽ ሳይሰጥ ጣቢያው በባለቤትነት ከሚያስተዳድረው ከግንቦት 7 ጋር አፉን ዘግቶ ይገኛል።
ይባስ ብሎ፤ ማስልጠኛ ጣቢያው ውስጥ አንዲት ጎጆ ከሁለት ፈርኬታ፤ጥቂት ሹካዎች ፤ሳህን አንዲት ትሎች የፈሉባት የደፈረሰ ውሃ የያዘች በርሜል፤ እና አንድ ‘ኮምፑተር ላፕ ታፕ’ እና 7 ታጋዮች ያሉት ‘ሕዝባዊ ሃይል” የሚባል ህይወት እንዳለው በማስመሰል የሚዋሸን “ኢሳት” የተባለው ጉደኛ  የዜና ጣቢያ፤ ባለፈው ወር “የግንቦት 7 ሕዝባዊ ሃይል መሪ አንዳርጋቸው ጽጌን ለመግደል የተላከ ነብሰገዳይ በሕባዊ ሃይል የስለላው ክፍል እና ችሎታ ተጋለጠ” በማለት አስቂኝ የሆነ የወያኔ  “አኬልዳማ’ የሚሉት የሚመስል ‘ድራማ’ በማዘጋጀት በተዳጋጋሚ በቲ ቪ ው ጋዜጠኞች ሲተች፤ሲኳል፤ሲሞገስ ሲለጠጥ እና ሲሰራጭ ሰምተናል።
ይህ ዜና ግን ውሸት የተጨመረበት መሆኑ በቅርቡ ታጋዮች አጋልጠውታል። ዜናው እውነትንት ቢኖረውም ግንቦት 7 እና የዚሁ ድርጅት ቲቪ የሆነው ኢሳት የተባለው ጣቢያ ያቀረቡት አቀራረብ ግን እጅግ የተጋነነ እና ውሸት የተጨመረበት እንደሆነ እና ‘የስለላና መረጃ ድርጅት” የሚባለው የግንቦት 7 ድርጅት “እንደሌለ እና ቢኖርም “ግድያ ከሸፈ” ከሚባለው ታሪክና ወቅት ጋር ምንም ግንኙነት እንደሌለው ተጋልጣል። እራሱ በራሱ ፍላጐት አነሳሽነት ያጋለጠ “ሰላይ/ነብሰ ገዳይ ተያዘ” ተብሎ በግንቦት 7 እና በኢሳት የተሰራጨው የግለሰቡ ዜና  አጋጣሚውን ተጠቅመው ለድርጅቱ መጠቀሚያ ትኩስ ዜና ተደርጎ ማጋነኛ ፍጆታ /ለፕሮፓጋንዳ ስራ/ አንዴት እንደተጠቀሙበት ለሕይወታቸው ሰግተው አሁን ተሸሽገው ከሚገኙበት ቦታ በስልክ እውነተኛውን ምስጢር ነግረውናል።
ኢሳት ያስተላለፈው ዜና የሚጻረር አዲስ ክስተት ብቅ ሲል ግን ዜናው እንዳይታወቅ እና የነዚህ ግለሰዎች ሕይወት አደጋ ላይ እያለ እያወቀ ጀሮ ዳባ ማለቱ ለግንቦት ሰባት የቆመው “ኢሳት” በተጋዮች ሕይውት አስኮናኝ የሚዲያ ጨዋታ እየፈጸመ ነው። በግንቦት 7 እና ኢሳት አፈ ጮሌዎች የተጠለፈው ጅላጅል ሕዝብ ግድ ባይኖሮውም እኛ የቁርጥ ቀን ጥቂት ልጆች የነዚህ ወገኖቻችን ሕይወት አየተካታተልነው መሆኑን ኢሳት የተባለው የዜና ማሰራጫ እንዲያወቅው ይሁን።
ኢሳት ከዚህ በታች የሚከተለው ታሪክ “በሚገባ ያውቀዋል። ለምሳሌ ግንቦት7 በኢትዮጵያውያን ላይ የሚያደርሰው ግፍ እና ውሸት ከሚችለው በላይ ሆኖበት ድርጅቱን በመልቀቅ የድርጅቱን ውሸትና የሚያደርሰውን አፈና እና ስቃይ በማስመልከት ዳንኤል የተባለው በቅርቡ ከድርጅቱ ሸሽቶ በኤርትራ አፋኝ ሃይሎች በእንዳርጋቸው ትዕዛዝ እየታደነ ያለው ዳኒኤል የተባለው የግንቦት 7 ታጋይ የተናገረውን እዚህ ያዳምጡ።
አሳት የተስፋዬ ገብረአብ ሻዕቢያነት ከሁለት አመት በፊት ሰነዱ እንደተገኘ አውቆት እያለ ከሕዝብ እንደደበቀው ሁሉ ኢሳትም ይህንን የዳኒኤል ቃለ መጠይቅ እና የድረሱልን ጥሪ ዜና ያውቃል። ሆኖም ሆን ብሎ ሌት ተቀን  የአንዳርጋቸው ጽጌ ግድያ ሙከራ ካንድ ገጽታ ብቻ አንዲታይ ያልጣረው የዜና ስርጭት እና መደበኛ ጊዜ ሰጥቶ ያላደረገው ፕሮፓጋንዳ ሙከራ አልነበረም።
ተቃዋሚ ነኝ የሚሉት አንዳንድ የዲያስፖራ ሚዲያዎች እያደሩ ማፊያዊ ሚዲያ ዓነት ለግለሰቦች አገልግሎት እና ዝና ውለዋል። በቅርቡ ይህ ኢሳት የተባለው የዜና ተቋም የግንቦት 7 መሪዎች እና የኢሳያስ አፈወርቂ ሰብአዊነት የሚሰብክ ልሳን በአንዳርጋቸው ጽጌ በኩል ለኢትዮጵያ ሕዝብ አንዲተላለፍ ሲያደርግ፤ ኢካዴፍ ECADF (አትዮጵያን ካረንት አፈይርስ ድረገጽ) የተባለ ፓልቶክ እና ድረገጽ  ደግሞ የበኩሉን ማፊያዊ የግንቦት 7 ስራውን ለመወጣት ሲል ከግንቦት 7 “ቶርቸር’ አምልጠው የሚመሸሹ ዜጎችን “ተፈላጊ ወንጀለኞች” እያለ እንዲታፈኑ እና በያሉበት አንዲገደሉ ማሰታወቂያ በመለጠፍ ፋሺስታዊ/ማፊያ የባሕሪ በሽታ እየተናወጠው ነው።
 


ይህ ፎቶ ከግንቦት 7 እና ሻዕቢያ  አፈናና ግድያ በመከራ አምልጠው ከወጡት የህዝባዊ ኃይል ተብየው  አመራሮች አባስ/ ማስረሻ (የስልጠና ከፍል ኃላፊ) አና ኮስሞስ (የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ) ነው

ይህ ፎቶ የኢሳት ቲቪ እና ECADF;  የግንቦት 7 ድረገጾች እና ኢካዴፍ ሕዝብን ለማሞኘት ለጥፈውት የነበረ የውሸት ፎቶግራፍ ነው። ውሸትነቱ ደግሞ በዚህ ፎቶገራፍ ብረት ይዘው የሚታዩ በነሱነታቸው በሚዲያ የተነገደባቸው ሰዎች ለምሳሌ ለውንቸር ይዞ የተነሳው የግንቦት 7 የስልጠና ክፍል ሃላፊ ተብሎ ተመድቦ የነበረው “አባስ (ማስረሻ)” የሚባለው ታጋይ ሻዕቢያ ላውንቸር አምጥቶ ለፎቶ ግራፍ ፍጆታ በትከሻው ይዞ እንዲነሳ የተደረገ መሆኑን እና የያዘው ላውነቸር ምንነቱ አይቶት አንደማያውቅ በቃለ መጠይቁ ተናግሯል።አብሮት ያለው መትረየስ የያዘው ደግሞ ዘመኔ ካሴ ይባላል። እሱም አንደዚሁ በትከሻው ተጭኖበት ለፎቶ ፍጆታ ግንቦት 7 የተጠቀመበት የውሸት እይታ ነው። በዚህ ጽሑፍ ላይ የተለጠፈው አውድዮ ቃለ መጠይቅ ለማስረጃ ይሆንዎት ዘንድ  ከራሳቸው ከአንደበታቸው ያድምጡ።
ይህ ጉደኛ ዘመን በእንዲህ ያሉ ተቃዋሚዎች እና የዜና ማሰራጫዎች እየታጀበ ጉደኛነቱ እያሳየን ያለው በጣም አስገራሚው የግንቦት 7 እና የኢሳት ቅንብር ውሸት ለየት ያደረገው የወሩ ጉደኛ ዜና ደግሞ  አንዳርጋቸው ጽጌ ለመግደል የተያዘው “ኦ ሚለዮኔም” በሚል ስያሜ የተቀነባባረው የግድያ ተልዕኮ ከወያኔ የተላከው ነብሰገዳይ በግንቦት7 የስለላ ድርጅት ተደርሶበት ተይዞ ስልክ ሲነጋጋር ለበርካታ ወራት በትእግስት እንዴት የስልኩን ልውውጥ እንዴት ይጠልፉት እንደነበረ ሳያፍሩ ለሕዝብ አስተላልፈውታል።
ታሪኩ ግን የግንቦት 7 እና የኢሳት ጋዜጠኞች አንዳናፈሱት ሳይሆን ልጁ በገዛ እራሱ ለነብሱ ሲል ኑዛዜ/ንስሃ ገብቶ ከላይ በፎቶግራፍ ለሚታየው ለዘመነ ካሴ (ለጋደኛው) ምስጢሩን ነግሮት ድርጅቱም ማወቅ አለበት ብሎ በንጽህና ራሱ በራሱ ያጋለጠና የሰጠ ሰው ንፀሁና መወደስ የነበረበት ሰው፤ የግንቦት 7 መረጃ ክፍል ደርሶበት ተጋለጠ ብሎ በውሸት ያልሆነ የሃሰት ወሬ አስሰምተውናል።
ሲያስደውለው የነበረው ደግሞ ዳኒኤል ነው።http://ginbot7d.org/audio/YegedeyaMukera.mp3 ዳንኤል ደግሞ በዚህ አውድዮ የምትሰሙት ከኤርትራ አምልጦ አሁን ከግንቦት 7 የሻዕቢያ አፈና የግድያ ቡድን ጥቃት ለማምለጥ ተደብቆ ሕይወቱ አደጋ እያንዣበበት ላይ ያለ ኢትዮጵያዊ ነው። አስገራሚው ድራማ ደግሞ፤ ተፈላጊው ተገዳይ አንዳርጋቸው ጽጌ ሳይሆን “ሻምበል ዳዊት” የተባለ በወያኔ የሚፈለግ ኤርትራ ውስጥ የኒገኝ የአማራ ድርጅት አባል ተፈላጊ ነው። ነግር ግን ድራማው ወደ አንዳርጋቸው ጽጌ እንደተደረገ ተደርጎ ተቀነባበረ። በሗላ ልጁ ግድያው ላንዳርጋቸው ጽጌ አንደተጠና ተደርጎ ‘ድራማ’ አንዲሰራ ከተገደደ በሗላ፤ በምስጢር ባንዳርጋቸው ፈቃድና ተባባሪነት ለሻዕቢያ ተላልፎ ለድብደባ እና ልዩ ምርመራ ለስቃይ ተዳርጎ እስካሁን ድረስ ሁኔታው የት አንዳለ የሚያውቅ ሰው የለም።
ይህ አሳዛኝ ወንጀል በግንቦት 7 ተቀነባብሮ በኢሳት ጋዜጠኞች በኩል ሰፊ ሽፋን እና ሰዓት ተሰጥቶት ሕዝብን በማደናገር ወንጀል ኢሳት ተባባሪ ሆኗል። ኢሳት የግንቦት7 እና በሻዕቢያ ገንዘብ የሚደጐም የዜና ተቋም ቢሆንም፤ ወደፊቱ ከዚህ መሳይ አደናጋሪ እና የሃሰተኛ ድርጅት ፕሮፓጋንዳ አሰራጭነት የወንጀል ተባባሪነቱ እንዲታቀብ እንማጸነዋለን።
ይህ የግንቦት ውሸት ዜና ኢሳት ሳይውቅ ነው ያሰራጨው አንኳ ቢባልም፤ ሰላዩን/ነብሰገዳይ ተብሎ የተወነጀለው ሰው እየተከታተለ ስልክ ሲያስደውለው ከነበረው በድራማው  ክንዋኔው የነበረው ታጋይ ዳኔኤል የሰጠው ቃለ መጠይቅ ይፋ ከሆነ በሗላ እንኳ ኢሳት (ገለልተኛ ሚዲያ ነኝ እንደሚለን እውነትነት ካለው) የዳኒኤልም ሆነ የቴድሮስ እና የመሳሰሉ በርከታ የግንቦት 7 (የሕዝባዊ ሃይል ተብዬ) ታጋዮች የነበሩ ኢትዮጵያዊያን ዜና እና ያስተላለፉት ተማጽኖ አንደ ተቀረው ዜናዎቹ  ከየትም ድረገጽም ሆነ ከውጭና ከውስጥ አገር የዜና ማሰራጫዎች “ኮፒ ኤንድ ፔስት” አድርጎ ለሕዝብ እንደሚያሰደምጠው ሁሉ ፤የነዚህ ታገዮች የድረሱልን ጥሪም ሆነ በአንዳርጋቸው ጽጌ ትዕዛዝ በእስር ተዳርገው የቶርች ሰለባ የሆኑበትን የብሶት እሮሮ ለማስደመጥ ፈቃደኛነቱን አላሳየም። በዚህ ጥያቄ ኢሳት እምራለሁ ብሎ የተቀመጠ አንድ ደንቆሮ ኩናኩንት ብጤ በኢመይል ጠይቀው በዚህ ተፋጥጠን አንድ ሁለት ተባብለናል።
የኢሰት ጋዜጠኞች የነ ኮስሞስ (ከሳውዝ አፍሪካ ወደ ኤርትራ ወደ ግንቦት 7 ሰልጣና የሄደው) በቶርች በእስራት የተሰቃየ ልጅ፤ የነ ቴድሮስ፤ የነ ዳኒኤል ወዘተ… ሕይውት እና በፋሺሰት ባሕሪ የሚንቀሳቀሰው በዘረኛው በአንዳርጋቸው ጽጌ ብልሹ አምባገነን አሰራር ተበሳጭተው ትግሉን ጥለው ለመሰናበት ጠይቀው ማመልከቻ አስገብተው ለእስራት፤ድብደባ እና ሞት፤ አንዲሁም ለሻዕቢያ የዘንጋዳ ቆራጭ የዳረጓቸው አንዳርጋቸው ጽጌ እና ብርሃኑ ነጋ እንዲሁም ኤፍሬም ማዴቦ ለእነዚህ ሕይወት ተጠያቂዎች ናቸው። ይህ ተደብቆ የቆየው የግንቦት 7 ወንጀልና ምስጢር ያጋለጠው ዳኒኤልም ሆነ ሌሎቹ እየተከታተላችሁ ለማደን እና ለማፈን የምታደርጉት የፋሺሰት ተግባር አንድታቆሙ ይህ ብዕርተኛ በጥብቅ ያስገነዝባል።
ግንቦት 7 ብሎ ራሱን የሚጠራ አጭበርባሪ የሻዕቢያ ተላላኪ በዜጎቻችን እና በታጋዮቹ ላይ እያደረሰው ያለው ግድያ እና ከድርጅቱ እየሸሹ የተደበቁ ሰዎችን እያባረረ ለማፈን እያደረገው ከአለው የወረበላ ባሕሪው ይታቀብ። አብዛኛዎቹ የግንቦት 7 መሪዎች ዋሺንግተን እና መኔሶታ ስቴት እየኖሩ በሰው ሕይወት ላይ ግድያ፤እስራት፤ቶርች አደና እና አፈና እንዲፈጸም ማድረግ እና ተባባሪ መሆን በሕግ አንደሚያስጠይቃቸው እና ለሚኖሩበት አገር እና የስደተኞች መስርያቤት እና አስሬ ወደ እሚሮጡበት ወደ ኮንግሬስ ጽ/ቤት እና ወደ ፕረዚዳንቱ ጽ/ቤት አቤቱታ ማቅረብ እንደምንችል እንዲያውቀት።  ይህ ብዕርተኛ በእነዚህ እየታደኑ ሽሽት ላይ ባሉት ሰዎች ህይወት የሚደርሰው አደጋ የግንቦት 7 መሪዎች እና ሚዲያዎቻቸው አንደሚሆኑ በብርቱ ማስጠንቀቂያ ያስገነዝባል!!!!!!! I am not joking here!
አሜሪካ ኮንግሬስ ድረስ እየሮጡ ስለ ሰብአዊነት መቆርቆርና ስለ ዲሞክራሲ ማጣት መለፍለፍ ፤ አውሮጳ አገረሮች እየሁዱ ገንዘብ ድጐማ መስበስብ ባንፃሩ ሰዎች እያሳፈኑ እና እየገደሉ እያሳደዱ ሰው መስሎ መለፍለፍ ማብቃት አለበት። የግንቦት 7 የሻዕቢያ አፋኝ ቡድን አፈና ለማምለጥ ተሸሽገው ካሉት ወገኖቻችን የተሰጠ የድረሱልን ጥሪ ለማንበብ ከዚህ በታች ቀርቧል። የሰብአዊ ድርጅት ተሟጋች ነኝ የሚል የኢሳት ሰውየም በመደበኛ የሰብአዊ ጉዳይ ክፈለጊዜው ሃቅ ካለው ይህንን አቤቱታ ለሕዝብ ይፋ አንዲያደርገው ይህ ጸሓፊ በብርቱ ያሳስባል።http://www.ginbot7d.org/documents/ኤርትራየሚፈፀምወንጀል.pdf  የሙለው እና ከዚህ ጋር በማያያዝ “ከግንቦት 7 የቀን ጅቦች እና ከሻዕቢያ መንጋጋ ያመለጡ ታጋዮች” የሚለውን http://www.ginbot7d.org/ ሙሉውን ያንብቡ።
ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያን ሰማይ ድረገጽ አዘጋጅ) getachre@aol.com Google-it!!!!!-(Ethiopian-Semay) www.ethiopiansemay.blogspot.com
 
 





Wednesday, December 11, 2013

የጌታቸው ረዳ መልዕክት በስዊድን ለሞረሽ ወገኔ ዐማራ ድርጅት ህዝባዊ ስብሰባ

የጌታቸው ረዳ መልዕክት በስዊድን ለሞረሽ ወገኔ ዐማራ ድርጅት ህዝባዊ ስብሰባ
 
የተከበራችሁ ክቡራን እህቶች እና ወንድሞች፤

እንዲሁም የጉባኤው አዘጋጆች።

በአካል በስብስባው ባለመገኘቴ ይቅርታ እየጠየቅኩኝ ፤ በዚህ ደብዳቤ ላስተላልፈው የፈለግኩት መልእክት ጉባኤው ስለተጠራበት ጉዳይ ትንተና ለመስጠት ሳይሆን ማስገንዘብያ ብቻ ነው። በአካል ስለማልገኝ ትንታናውን ለሌሎች ወንድሞቼ እንዲወጡት ትቸዋለሁ።አድማጩ አንዲያውቀው አስፈላጊ ነው ስለምለው ጉዳይ አነጋጋሪ ስለሆነ አጭር መልእክቴ እነሆ።

እኔ በተወለድኩበት ትግራይ ክፍለሃገር ውስጥ ወያኔ የትግራይ ሪፑብሊክ ለመመስረት መነሻ አድርጐ ያሰራጫቸው መግለጫዎቹ መሰረት በማድረግ “ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ” ብሎ እራሱን ሰይሞ ወደ ጫካ በመግባት ከደርግ ወታደራዊ መንግሥት ጋር ባካሄደው የትጥቅ ትግል በተለያዩ ምክንያቶች “በለስ ቀንቶት” ደርግን አሸንፎ የመንግሥት መንበር ከተቆጣጠረ ወዲህ ኢትዮጵያን እንደ ደቡብ አፍሪካ ዘረኛው የነጮች መንግሥት በጐሳ/በቋንቋ አስተዳደር አዋቅሮ “ጸረ አማራ” ሕብረተሰብ እና “ጸረ አገር” ዕቅድ ነድፎ ሕዝቧን እና አንድነቷን ለማበጣበጥ የተመሰረተ የፖለቲካ ድርጅት እንደሆነ በተለያዩ ጊዜያት በጽሑፍም በቃለ መጠይቅም በመጽሐፍቶቼም ገልጫለሁ።

 

አሁን በሥልጣን ላይ እየባለገ ያለው “ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ” በታሪካችን ውስጥ ለጆሮ እና  ለዓይን የሚከብዱ፤ በሕዝባችን እና በአገራችን ሉአላዊ ክብር ላይ ብዙ አስነዋሪ ወንጀሎች የፈጸመ ቢሆንም፤ ለዓይን እና ለጀሮ ጐልቶ የሚታየው ጥቃት በአማራ ሕብረተሰብ ሕይወት ላይ ፈጽሟል። ይህ የአማራ ጥቃት ከመላ የተለያዩ የአገሪቱ ጐሳዎች ሁሉ በይበልጥ የጥቃት ማሕደሩ የተከመረው በአማራው ላይ ነው።

በዚህ ጎሳ (ዘር/ሀረግ) ላይ ያነጣጠረው የወያኔ ጥቃት በምንም መለኪያው በማንኛውም ጎሳ ላይ የደረሰው ጉዳት ሲነጻጸር የት የሌለ ነው። አማራው ለዘመናት ሲኖርባቸው አካባቢዎች ውጣ እየተባለ ከነቤተሰቦቹ ሲባረር፤ኦሮሞው፤ትግሬው፤አደሬው፤ሶማሌው፤አፋሩ፤ጋምቤለው፤ወላይታው፤ወዘተ…ወዘተ… አልተባረረም። ከነ ነብሱ ወደገደል ተገፍትሮ አልተጨፈጨፈም።በዚህ-ከተማመንን፤አማራው ለምን ለብቻው ጥቃቱ አንዲነገርለት ተፈለገ ብለው ለሚጠይቁን ዜጎች ለምን አንድንጮኽለት እንደተፈለገ ግልጽ ይሆንላቸዋል።

ከላይ አንደገለጽኩት የዚህ ሕብረተሰብ ጥቃት እና መፍትሔው ምን መሆን እንዳለበት ለመግለጽ በአካል ስላልተገኘሁ በጽሑፍ መዘርዘሩ ቦታ ስለማይበቃ፤ይህንኑ ገለጻ ለወንድሞቼ በመተው አድማጩን ለማስገንዘብ የምፈልገው ነገር  አለኝ የምለው ነገር የሚከተለው አጭር ማስገንዘብያ ነው።

ይኸውም፤ ይህ ጉባኤ ለምን በአማራ ጥቃት ላይ ማተኮር አንዳለበት ቅሬታቸውን በማሰማት በግል ‘በቴክስት’፤ ‘በኢመይል’ መልእክት እና ‘በስልክ’ በጉባኤው  እንዳልሳተፍ ከተሳተፍኩ ደግሞ በሚዲያ ስሜን እንደሚያጠፉት በማስጠንቀቅያ መልክ ያስጠነቀቁኝ ወገኖች እና የአማራው ልዩ ጥቃት ሁኔታው መረዳት የተሳናቸው ግብዝ ወገኖች አንዳሉ ለማስገንዘብ እፈልጋለሁ።

እነኚህ ግለሰቦች ያልተረዳቸው ሁኔታ ‘አማራው’ ከማንኛውም ኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ተለይቶ “በሻዕቢያ”፤ “በወያኔ” ፤ “በኦነግ”፤ ዓረባዊ ነኝ በሚለው “ኦብነግ” እና በተቃዋሚው ክፍል የሚንቀሳቀሱ አንዳንድ የዜና ማሰራጫዎች፤በተለይ በውጭ አገር የተቃዋሚውን መልሕቅ የተቆጣጠረው ከኤርትራ ሻዕቢያው ቡድን ጋር የተቆራኘው ግንቦት 7 ብሎ እራሱን የሚጠራው “ጸረ አማራ” ኤሊቱ ክፍል በአማራ ሕብረተሰብ ላይ የአካል እና የስነ ልቦና ስብራት አድረሰውበታል።

ተምረናል ብለው ራሳቸውን የሚያመጻድቁ ግብዝ ኤሊቶች አማራውን ሕብረተሰብ በመጽሐፋቸው “ቀጥቅጠውታል” (የዘረኛውን የአንዳርጋቸው ጽጌ ‘የአማራ ሕዝብ ከየት ወዴት” መጽሐፍ- በጥሞና ማንበብ አለባችሁ)። በጥይት ረሽነውታል። እርጉዝ እናቶች እና እህቶች ከነህይወታቸው ወደ ገደል ተወርውረዋል። ከሚኖሩበት አካባቢ በጉልበት ተገፍተው ንብረታቸው ሳይዙ እና ከቤተሰቦቻቸው እየተነጠሉ ፡ አንዳንዶቹ ከመቅጽበት አንዳንዶቹ ደግሞ በ24 ወይንም በ48 ሰዓት የጊዜ ገደቦች ተሰጥቷቸው አንዲባረሩ ተደርጓል።  

በጥቂት አመታት ልዩነት የሌሎቹ ጎሳዎች የሕዝብ ቁጥር ሲጨምር አማራው ግን  2 ሚሊዮን አማራ ሕብረተስብ ከምድረገጽ መጥፋቱ በእኛ ጥናት ብቻ ሳይሆን በወያኔ ስታትስቲክ ጭምር ወያኔ በፓርላማው አምኖ ገልፆታል። በወጣት እናቶች እና በአዛውንቶች ክብር ላይ ጥቃት ተፈጽሟል። ‘ዓይነ ስውራን’ ወንዶች አዛውንቶች ‘ብልታቸው’፤እናቶች ደግሞ ‘ጡታቸው’ በቢላዋ ተሰልበዋል።  ህፃናት በትምህርት ገበታ ላይ አንዳሉ አንዳይወጡ የየክፍሎቻቸውን መዝግያዎች ተቆልፎባቸው ከነ ነብሳቸው ተቃጥለው እንዲሞቱ እሳት ተለኩሶባቸው አልቀዋል። እናቶች አንዳይወልዱ ማሕጸናቸው አንዲደርቅ መርዝ አንዲወጉ ተደርጓል።  አሁንም ጥቃቱ አላባራም።  

ግብዦቹ ‘ይህንን ጥቃት’ ነው “አታጋልጡ” የሚሉን።በዚህ ጉባኤ ስለ አማራ ጥቃት እና ውረደት ስቃይና መከራ ለሕብረተሰብ መንገር “ጸረ ኢትዮጵያዊነት” ነው እያሉ የአማራው ሕብረተሰብ ጥቃት ተሸፍኖ እንዲቀጥል በማወቅም ባለማወቅም አስተዋጽኦ የሚያደርጉ ወገኖች አንዳሉ ለመግለጽ እወዳለሁ።

በተለይ ለምን አንደዚህ አንደሚሉ ጥቂት ልበል። ስለ አማራ ሕብረተሰብ ጥቃት ማጋለጥ፤መፈትሄ ማፈላለግ ማለት የወያኔ የጐሳ አወቃቀር ፖለቲካ መከተል ነው በማለት “ጐሰኝነት” ነው ይሉታል። ይህ “ጥርቅም” ያለ “ድንቁርና” ለወያኔዎች እና ለመሳሰሉ ለጸረ አማራ ቡድኖች የሚያመቻች ተጨማሪ ጥቃት ነው።

 

እኛ አማራው “ይገንጠል” የራሱ ክልል ይከልል፤በአካባቢው የሚኖሩ ትግሬዎች፤ኦሮሞዎች፤የደቡብ ሕዝብ ጎሳዎች ከአማራ አከባቢ መሬቶች ይባረሩ፤ይገደሉ፤ የሚል ቅስቀሳ እና አጀንዳ የለንም። እኛ እና ወያኔ በጎሰኛነት በመወንጀል የሚያያይዙን “ደንቆሮዎች” የዘር ማጥፋት ወንጀሉና ሰበቡ  አላጠኑም ወይንም ሆን ብለው የአማራው ጥቃት አንዲቀጥል የመሰሪ ቡድኖች ተላላኪዎች ናቸው ማለት ነው።ለመሆኑ ከኛ በላይ የጐሳ ፖለቲካ አምርሮ የተቃወመ እና በየሚዲያው የተከራከረ እና መጽሐፍትም የጻፈ ማን ነው? ማን በማን ላይ ነው ስለ ኢትዮያዊነት ለመመጻደቅ የሚሞክረው? ስለ አማራ ጥቃት መናገር እኛ ጐሰኞች፤እነሱ ልዩ “ኢትዮጵያዊያን” የሚሆኑበት በየትኛው መመዘኛቸው ነው?

በጣም የሚገርማችሁ ደግሞ፤ በቴክስት እና በስልክ ያስጠነቀቀኝ ግለሰብ “ዶክተር አስፋ፤ ዳኛ ከተማ ደኔ እና አንተ አቶ ጌታቸው ረዳ፤ ስለ አማራ ሕብረተሰብ ጥቃት ስትናገሩ ‘አማራ’ ወክሎናል የምትሉት የምስክር ወረቀት አሳዩን ማለቱ “በጣም አስገራሚ ድንቁርና ከመሆን አልፎ፤ ነገሩ በጣም አስቆኛል። ስለ ትግሬ ወይንም ስለ ኦሮሞ ጥቃት ስንናገር ወይንም “ታሪክ፤ባሕል፤ጦርነት፤ፖለቲካ” አንስተን ስንተነትን ይህ አነጋጋር ‘ወያኔዎች’ አንዲሁም ‘ኦነጐች’ ስለ ጎሳችን ‘እኛ’ እንጂ አንናተ አያገባችሁም፤ስለ እኛ ወክለህ ተናገርልን ብሎ የሰጣችሁ ፈቃድ አሳዩን፤ እያሉ በጠባብ ሕሊና የሚንቀዠቀዡት የጠባብ ቡድኖች ቅጂ ቅስቀሳ ሰለባዎች አንደሆኑ ነው የተረዳሁት።

ለነገሩ ወያኔም እኮ “ዲያስፖራ ተቃዋሚ ስለ አገር ውስጥ ላለው ሕዝብ መናገር አይችልም። መበት የለውም፤ ውክልና ወረቀት አምጡ፤ እያለ ድንቁርናውን እያስተጋባብን ነው። ታዲያ የኛ የምንላቸው ተቃዋሚዎች ተመሳሳይ ጥያቄ ሲጠይቁን ከወያኔ ድንቁርና በምን ይሻላሉ?

ማን ወከላችሁ? ብሎ ለጠየቀኝ ሰው መልሱ ጥቃት የደረሰበት “አማራ ሕብረተሰብ” ስለ ጥቃቱ እንድንናገርለት በአንደበቱ ጥሪ አድርጎልናል! ይህንን የቴፕ ድምፅ ለማስረጃ አንዲደመጥ ልኬአለሁ። 45 ደቂቃ የፈጀ ዝርዘር  በኢትዮጵያን ሰማይ አውድዮ ቪድዮ ክፍል ተለጥፎ ይገኛል። ድረሱልን ያሉንን ጥሪ ግን ባጭሩ ይኼው። እነሆ ከ4 አመት በፊት ጥሪው በጀርመን ራዲዩ ። Active ethnic cleasning in Ethiopia በሚል ርዕስ በዩቱብ እና በኢትዮፕያን ሰማይ ድረገጽ የተለጠፈው ድምፅ እነሆ ያድምጡ።

http://youtu.be/aJDyueu2Kek

የተጠቂዎቹን የድረሱልን ድምፅ መልእክቱ እንዳዳመጣችሁት፤ መልእክቱ የሚለው “ለሚመለከተው ክፍል እባካችሁ ስለ እኛ ስም ሆናችሁ አነጋግሩልን አደራ! አደራ! አደራ!”  የሚለውን የአደራ መልእክት ተንተርሰን ነው እኛም የተጠቂዎቹ አደራ ላለመብላት እዚሁ እየተነጋገርን ያለንበት እና ያስገደደን ምክንያት። ስለዚህ  ስለ አማራው ሕብረተሰብ እንደትናገሩ ማን ወከላችሁ? የውክልና የፈቃድ ወረቀት አሳዩን፤ በማለት የሚዘላብዱ እና ስለ አማራ ሕብረተሰብ እናቶች እና አባቶች ጥቃት ‘ትንፍሽ’ አትበሉ የሚሉን ወገኖች የአጥቂዎቹ ተባባሪዎች ከመሆናቸው በፊት ልቦና አንዲገዙ አጋጣሚውን ተጠቅሜ ልመክራቸው እፈልጋለሁ ።

በዚህ አጋጣሚ በተጓዝኩበት አካባቢ አመች ሆኖ ካገኘሁት ከናንተው ጋር ለመቀላቀል እሞክራለሁ፡ ካልሆነልኝ ግን  ባለመገኘቴ እያዘንኩ፤ የዚህ ሕብረተሰብ ጥቃት ተጠንቶ  አጥቂዎቹ ወደ ሕግ የሚቀርቡበት ሁኔታ ማመቻቸት አስፈላጊ መሆኑን ተገንዝበን፤ የተጠቂዎቹ ልሳን ዕርዱን በማለት ያስተላለፉትን  “አደራ!” ተግባራዊ ለማድረግ እንበርታ፤ በርቱ።

አማራው በዘር ማጽዳት ዘመቻ ሲጠቃ፤ በደፈናው “ስለ ኢትዮጵያ” ጥቃት እንጂ ስለ አማራ ጥቃት አትወያዩ የሚል ስሜት ያሰከራቸው አገራዊ ትርጉም በቅጡ ያልተማሩ ጋላቢዎች፤ የአማራው ሕብረተሰብ ጥቃት ሰሚ ጀሮ አንዳያገኝ የሚጥሩ ወገኖች እየጋለቡበት ካለው ልጓም የበጠሰ ስሜት መቆጠብ ይኖርባቸዋል።

በዚህ መሰሪ የወያኔ የጥቃት ዘመቻ የአማራ እናቶች ማህፀን ቢመክንም ከአጥቂዎቹ እጅ ያማለጣችሁ የአማራ ተወላጆች ሁሉ የእናቶቻችሁ እና የእህቶቻችሁ ትኩስ እምባ እንዲቆም ለማገዝ ሐላፊነቱ በናንተው በአማራዎች ብቻ ሳይሆን በሌሎች ኢትዮጵያዊያንም ዘንድ የዜግነት ግዴታቸው አንዲወጡ ጥሬየን አቀርባለሁ።

በዚህ አጋጣሚ ከአማራ ሕብረተሰብ የተወለዱ ውጭ አገር እና ውስጥ አገር የሚኖሩ የሕግ ጠበቆች በየድረገጹ የሚያቀርቧቸው ሳምንታዊ/ወርሃዊ “የፖለቲካ ጅላጅል ትንተናቸውን” አቁመው የወላጆቻቸው እና የእህቶቻቸውን የድረሱልን ጥሪ፤ በቅርቡ በዓለም አቀፍ ፍርድ አጣሪ ተቋም በማመልከት “ኢትዮጵያዊያን ኦጋዴን ሶማሌ ተቃዋሚዎች” በወያኔ ላይ እንዳስመዘገቡት ክስ፤ እናንተም የወላጆቻችሁ እና የእህቶቻችሁን እምባ ማድረቅ እና ወንጀለኞቹን ወደ ሕግ የማቅረብ ሐላፊነት ከናንተው ይጠበቃል።

ይህ የክህደት ዘመን በመንደላቀቅ እና በምቾት ኑሮ በውጭም በውስጥም አገር ጆሮውን ደፍኖ ሰምቶ አንዳልሰማ ያጠረመመው ‘አማራው ልሂቅም ’ ሆነ በግንቦት 7 ስም ከኤርትራው ቡድን ጋር ትከሻ ለትከሻ እየተሻሸ ያለው አማራው ሊሂቅ እና ተከታየቹ ብቻ ሳይሆኑ ይህንን ጐሳ ያጠቁትና በመጽሀፍቶቻቸው እና በሕዝባዊ ንግግራቸው የዘለፉትና የከዱት፦ የንጉሥ ተፈሪ የልጅ ልጆች ነን የሚሉን ውጭ አገር እና በውስጥ  አገር የሚኖሩ መሳፍንቶች ‘አማራን እያጠቃ ካለው የወያኔ ቡድን እና መሪዎች ጋር በመተባባር’ አሳፋሪ የሆኑ የክህድት ተግባሮች ፈጽመዋል።

ለመግለጽ የፈለግኩት ጥንቃቄ የጎደለበት በውጭ አገር የስለላ መረቦች እየታገዘ የፖለቲካ ቁማር እየተጫወተ ያለው የምሁሩ ክፍል ብቻ ሳይሆን፤ የንጉሱ የልጅ ልጆች ጭምር ስለ አማራ ጥቃት ከመጤፍ ያለመቁጠራቸው አንዱ አሳዛኝ እና መራራ ያደረገው ገጽታው ስታዘብ ሃዘኔ እጅግ የበረታ ያደረገዋል።

ይህ የክህደት ዘመን ስትመለከቱ “ለአማራው” ማን ያልቅስ? ስለ አማራው ጥቃት አንድትነጋገሩ “በስሜ አንድትናገሩልኝ ወክያችሗለሁ ብሎ የሰጣችሁ የምስክር ወረቀት ውክልና አሳዩን” የሚሉ ተቃዋሚ ነን የሚሉን የአማራ ተወላጆችም ሆኑ እንዲሁም  “አማራ ብቻ ስለ አማራ ቢናገር ያምርበታል፡ትግሬ የሆናችሁ ተቃዋሚዎች በዚህ ላይ አያምርባችሁም”፡ የሚሉን የወያኔ ሰዎች እና ተቃዋሚዎች የሚሰነዝሩትን አስገራሚ ተቃውሞ ጉባኤው እንዲነጋገርበት አሳስባለሁ።

የገረመኝ ነገር፡ ስለ አማራው ጥቃት መነጋጋር ማለት ስለ ኢትዮጵያ ጥቃት መነጋጋር አይደለም ወይ? ስለ አማራው ጥቃት እና እንዴት ይቁም የሚለው መነጋጋር እንዴት “ጐሰኝነት” ነው ያስብላል?

ስለ አማራ ጥቃት መቆርቆር በአገር በታኝነት ወይንም በጎሰኛነት አውቀውም ሆነ ባለማስተዋል የሚከሱን ወገኖች፤ ለጸረ አማራ ቡድኖች አመቺ መንገድ አመቻቺዎች እንዳይሆኑ የዕውቀት አድማሳቸው እንዲያሰፉ ከወዲሁ ለማሳሰብ እወዳለሁ።

ከዚህ በተጨማሪ፤ በቅርቡ በሳውዲ አረብ በዘረኞቹ አረቦች የተቀነባበረው በኢትዮጵያዊያን ላይ የደረሰው የዘር ጥቃት ባንድነት አንደጮኽን ሁሉ፤ ከዚያ በከፋ መልኩ በወያኔ  እና በወያኔ ተላላኪዎች አማካኝነት በአማራው ሕብረተሰብ ላይ የተፈጸመውና አሁንም በመፈጸም ላይ ያለው ጥቃት ተባብረን በመጮኽ ለዓለም ሕብረተሰብ ያላሰወቅንበት እና የሕግ ባለሞያዎች ነን ብለው በሳውዲ ዓረብ የደረሰው ጥቃት ለማጣራት ፈቃደኝነት ያሳዩን ወገኖች፤ ለምን በአማራው  ጥቃት ላይ ታከቱ? ወይስ ጥቃቱ በውጭ ሰው ስለተከናወነ ልዩ ጥቃት ሆኖ፤ በውስጥ ጠላት በአማራው የተፈጸመ ጥቃት ግን እንደ ጥቃት ውርደቱ አልተሰማንም? ለምን? አገር ውስጥ  ያለው ተቃዋሚም “ሰላማዊ ሰልፍ ሲታገድ” ፊቱን አዙሮ ወደ እየቤቱ ከመመለስ እና በጋዜጦች እሮሮ ከማሰማት ሌላ ምን አድርጓል? እስክንድር እና ጓደኞቹን አንኳ ለማስፈታት “የረሃብ አድማ ሲያደርጉ እና የተጥለቀለቀ እምቢታ፤ የስራ ማቆም አድማ፤ ልገማ ወዘተ.. ለማድረግ የማይችል “ድውይ” ተቃዋሚ ነው። አማራው በዚህ ዳይለማ/ ትንግርት ስቃዩ የሚጮኽለት አጥቷል። የታወቀው የህግ ባለሞያ ደ/ር ያዕቆብም “የተለመደው አፉን ከፍቶ የሕግ አንቀጽ ከመጥቀስ ሌላ” እሱ በደምብ አድርጐ ከሚያውቀው እና ከሰራበት የዓለም አቀፍ መድረክ ፍርድ ቤት እና የመሳሰሉት ተቋማት ወደ ውጭ አገር  ተጉዞ መሰል የሕግ ባለሞያዎችን አስተባብሮ ስለ አማራው እልቂት “የመሰረተው” አቤት ያለበት የሕፈግ ክስ የለም። ለምን?  

አሁንም አንድ ነገር ልጨምር። በሚገርም ሁኔታ ከማንኛውም ተቃዋሚ ጸሐፊዎች ቀድሜ በሳውዲ የደረሰው ጥቃት ስሰማ የጻፍኩት እኔ ነበርኩ። በዛው መልእክቴ ላይ “ኢትዮጵያዊያን የሕግ ባለሞያዎች ከውጭ አገር ባለሙያዎች ጋር በመነጋጋር ” ሳውዲ ድረስ ሄደው ጥቃቱ አንዲያጣሩ የጠየቅኩኝም የመጀመሪያው ሰው እኔ ነበርኩ (የለጠፍኩትን ፋይል እና ቀን ተመለክቱ)።  

በዛው አንጻር በአማራው ሕብረተሰብ ላይ የደረሰው ጥቃት ከብዙ አመታት በፊት በተደጋጋሚ “የሕግ ባለሞያዎች” ጉዳዩን አጣርተው ወደ አለም ተቋማት አቤት አንዲሉም ተደጋጋሚ ተማጽኖየን አቅርቤላቸው ነበርኩ። በቅርቡ አምናም አንዲሁ ከብዙ አመታት በፊት አማራን በማጥቃት በጥቃቱ የተሳተፉ ግለሰቦች “ፎቶግራፋቸው” እና “አድራሻቸው” “የፈረስ ስሞቻቸው ጭምር” የት አንደሚገኙ ተልኮላቸው፤ “የክስ እና የማጣራቱ ሁኔታ ለመጀመር ዝግጁ አይደለንም ” ብለው መልስ የሰጡኝ አሁን በሳውዲ ሁኔታ ግምባር ቀደም ተዋናይ ሆነው የቀረቡ የሕግ ባለሞያዎች ስታዘብ፤ ይህ አማራ የተባለው ወገን “ተከላካይ ጠበቃ” ለምን አንዳጣ ሳስበው በጣም ይገርመኛል።    

የሕግ ባለሞያዎች ናቸው የሚባሉት ኢትዮጵያዊያን ምሁራን በአማራው ሕብረተሰብ ፍትሕ ለማስገኘት እንዳይረባረቡ ያገዳቸው “ድልድይ” ምን ይሆን? የጀመሩት አቤቱታ ካለስ ለምን ይፋ አላደረጉትም?

ይህ ብቻ አይደለም።ስለ ሳውዲ ጥቃት ማንሳቴ ላልቀረ ለሳወዲ ተጠቂዎች ትብብር አንፈልጋለን በሎ የተመሰረተው ቡድን አንድ ነገር ልበል። ቡዱኑ ትብብራችሁ አንፈልጋለን ብሎ ለመላ ወገኖች ጥሪውን ካስተላለፈ በሗላ፤ “በኮሚቴው ውስጥ ካሉት አንዳንድ ወገኖች የፖለቲካ ልዩነት ቢኖረንም፤ ችግሩ የጋራ በመሆኑ ለተጠቂዎቹ ሲባል ፖለቲካ ልዩነታችንን ለጊዜው ወደ ጐን ገፍቼ  እናንተ በምታዋቅሩት እርዳታ የገንዘብም ሆነ የሕሊና ድጋፍ ለማድረግ አቅሜን ለማድረግ ዝግጁ ነኝ፡ በርቱ። መልሳችሁ እጠባበቃለሁ” ብዬ የላኩላቸውን “ኢመይል” ደብዳቤ እስካሁን ድረስ አንድ መስመር የምታክል ‘መልእክትህ ደርሶናል’ እንኳ መልስ አልሰጡኝም። ለምን? በጣም ግልጽ ነው። ይህ በፖሊተካ የነቀዘ ‘የኤሊት ስብስብ’ (ወንዱም ሴቱም) ነገሮችን የሚያዋቅረው ‘በቡድናዊ ትውውቅና የፖለቲካ ጥልፍያ’ የተተበተበ ኤሊት ክፍል ነው (ሚዲያውም ጭምር ያካተተ ‘አዲሱ አዲስ አበባዊ ኤሊት’)።  ይህ ስሞታ የኔ ብቻ አይደለም፤ ብዙ ሰዎች ቅሬታ አላቸው። ይህን በተመለከተ ለወደፊቱ የምትመለከቱት ስዕል ይሆናል።

የነዚህ ኤሊቶች ‘ደወል’ የሆነው “ኢሳት  ቲቪ  ስለ አማራው ጥቃት የጮኸ የመጀመሪያ የዜና ማሰራጫ ነው እያለ በውሸት ከንቱ የምጐሳ ንጥቂያ ሲያደረግ በጋዜጠኖቻቸው እና በተወካዮቻቸው አንደበት ሰምቻለሁ። ኢሳት የኦነግ፤ የሻዕቢያ፤ የኦብነግ ባንዴራ አሸብራቂ፤ የወያኔ ኢትዮጵያ የቆዳ ስፋት ካርታ ‘ለጣፊ’ ቀስቃሽ ሚዲያ መሆኑ “የመጀመሪያው ቲቪ” ነኝ ቢል ያምርበታል። ኢሳት አሁን ነው የተመሰረተው። የጀርመን ራዲዩ፤ የቪኦኤ፤ የኢሕአፓው “ፍኖተ ራዲዮ”፤ የካናዳው የሃዋርያ ጋዜጣ፤ ኢትዮጵያን ረጅሰተር፤ መኢዐድ፤ ጦቢያ ጋዜጣ፤ በግል ደግሞ እነ ዶክተር አሰፋ ነጋሽ እና እኔው እራሴ እና የመሳሰሉ ዜጎች እና ሚዲያዎች ኢሳት የሚባለው የግንቦት 7 አቀንቃኝ ሚዲያ ከመመስረቱ በፊት ስለ አማራው ሕብረተሰብ ጥቃት በሚገባ ለመላው ዓለም እያጋለጡ ከ1991 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን የዘለቁት ተቋማት እንዳልነበሩ በማድረግ “ኢሳት” የመጀመሪያው የአማራውን ጥቃት ያጋለጠ ሚዲያ ነው ሲል ታማኝ በየነ በለመደው ዘባራቂነት ባሕሪው ሲዋሽ ሰምቻለሁ። ይህ ውሸቱ “ያረመው” ሰውም ሆነ ሚዲያ የለም። የነቀዘው ሕብረሰተሰብም ከነጠቃው ባሕሪ ጋር አብሮ ኖግዷል። ይህ ነጠቃ ባንዳንድ የነቀዙ ኤሊት ጸሓፊዎች እየተደገመ ነው።    

ይህ ማሳሰቢያ ባጭሩ ጉባኤው እንዲነጋገርበት ይህ መልእክት እያሳለፍኩ ፡ ጉባኤው አንዲሳካ ምኞቴ ነው።ትግሉ ረዢም እና መራራ ቢሆንም፤ በመጨረሻ ግን  የተጠቃው ሕዝብ ባሸናፊነት በድል ተራራ ላይ ቆሞ የተነጠቀው ክብሩን እና ሰንደቃላማው እንደገና ያውለበልባል።

አመሰግናለሁ።

ጌታቸው ረዳ (ኢትዮፕያን ሰማይ ድረገጽ አዘጋጅ)-ካሊፎርኒያ  -ሳንሆዘ  (2006) getachre@aol.com


 

   

Thursday, November 14, 2013

A Call for all Tigrayans!


A Call for all Tigrayans!


Getachew Reda (Editor Ethiopian Semay)           


The current Saudi Arabia AlQaida/Wuhabi orchestrated government conspiracy to carry Ethnic cleansing against Ethiopians (the perpetrators used questioner “Are you Ethiopia or Habesh?”) in Saudi Arabia cities should alarm Tigrayans who are Supporters of TPLF government how far their thuggish group in Ethiopia calling itself “Ethiopian Government” is keeping its mouth low for fear to the Saudi Petro Dollar Wuabi kingdom for not to temper its relation, so to keep the Arab Petro Dollar pumped to their personal banks who are stashing it all over the Worlds Banks in return to the vast agricultural lands given to the Wuhabi Saudi Tycoons in Ethiopia.

The recent brutal ethnic cleansing operation by the AlQaida/Wuhabi Saudi Police and citizens against Ethiopian youth, pregnant women and children is well orchestrated by the Wuhabia connected to the issue of the Islamic Movement in Ethiopia. You and the other lunatic  foreign media analysis can describe it as economy issue/immigrant illegal activities/ illegal immigration issue/Saudi citizens economic frustration issue… whatever your explanation would be; nothing could be further from the truth that this operation is Ethnic cleansing carried by the Wuhabi/AlQaeda religious fervors under the name of cleaning illegal immigrants. Arabs  hate Ethiopians regardless we have some brainwashed Ethiopian Muslims who speak, act, walk, behave and dressed like Arabs- they too are dehumanized with the rest. That is a walk up call for those Arab pretenders as well.

 You can see this photo how the Wuahbi/AlQaida are holding poor Ethiopian immigrants as if they captured Lions and Tigers. Do not they look like the Afghanistan or Pakistan or Somali or of the Nigeria Boko Haram  AlQaeda groups ready to slaughter the neck of a human being?  Any other explanation for such brutal attack is nothing but AlQaeda mission.  If this is not Wuhabi orchestrated work- what will be?  

 You can see with your own eyes and ears how far the thuggish TPLF group in power is hand and glove with the Wuahabist kingdom of Saudi Arabia and went far, to the extent, Mr. Ahmed Salaham a fellow who is a spokes person of the TPLF Embassy in Saudi serving as a counselor of the department on labor division “denying the claim of the victims, saying ‘there was adequate visitation, water, electric city, toilet /latrine facility, enough food and no one dies” (VOA Amharic Tuesday  November-12/2013  http://www.voanews.com/mp3/voa/africa/amha/amha1800aTUE.mp3).

This TPLF little puppy dog waging his tail to defend his masters even questioned the victims’ claim confronting the VOA reporter Adanech Fissihaye “how could someone sustain life without eating for 4 days?” He  openly accused the victims as “liars”.  I doubt if this man is not Wuahbi insider himself, I do not know what else he could be.

These nerd and his his likes are little puppy dogs who are sent to do the crime seen to lie on behalf of the big TPLF Dogs and for  the Saudi Alqaeda police. The big Dogs like Adhanom and Tsegay Berhe and the like who are the Wstern and Arab servants and apologies are behind the screen pushing these puppy dogs to do the job of lying for them. The Eritrean Adhanom is busy talking rescuing the Kenya Ethnic cleansing criminals from going to ICU, while he is sitting his ass in Sheraton Hotel drinking Coffee telephoning the Saudi Wuhabists to act as he is defending Ethiopians.

Tigrayans, it is time for you to rise up as the Eritreans are rising up against their lord Isayas Afewerki.  Tigrayans is been comfortably sleeping for a long time without exposing the crime of TPLF as Eritreans are writing it in books and public speeches.   You the Tigrayan TPLF supporters have a long way to catch up Eritreans where they are now. The blame is now coming to you direct or indirect accused by many Ethiopians.   Tigrayans as I always keep arguing are primary responsible for TPLF mess. Eritreans woke very, very late, but still better than you the TPLF supporters who are worshiping murderers and helping them to sustain for this long. I know why! You are been primary beneficiary from the looting (to use TPLF’s correct slogan “Ethiopia as a booty won in battle) (to check what took place during the looting from 1991-1994/5- to benefit Tigrayans and future Tigray. I urge all those who disagree with me to read “The Pillage of Ethiopia by Eritreans and Tigrayan surrogate” Authored by Dr. Assefa Negash. We can’t have this SHIFINFIN game anymore. We have to openly talk as it is! Enough is enough! Rise up or else you are accountable for the mess!

 Some asks why not majority of the Ethiopian people can’t able to topple TPLF, why Tigrayans? The answer is simple to such argument.

Others were dehumanized worst than some few Tigrayan victims of TPLF. TPLF is a government which Ethiopians of non Tigrayan origin rightly consider as an occupation force. Tigrayans do not conceder TPLF as occupational force (with the exception of few).  Why majority can’t toppled TPLF why only Tigrayans? Many reasons. Some of it is the following-:

 Ethiopian people except Tigraysns are disarmed. Tigrayans are armed to their teeth at this moment. If they want, they can arrest the few Eritrean Ethiopian Tigrayans and their puppets and give us peace. (Which I believe Army coup d’état will be the only way in Ethiopia to topple the Tigrayan armed gangs. Mark my word- do not forget my prediction! ) Its  defense national army over 3 t0 500,000 thousand armed personals (with their family 2  Million people) are made to perish systematically or openly and replaced by Tigrayan guerrilla army. 38,000 Ethiopians were thrown out from Eritrea with a permission and cooperation of Meles Zenawi/TPLF and made dumped on the street of Addis like a waste. We know from the evidence, Tigrayans were highly beneficiary Through “Structural Adjustment Program” and made strong economically, spiritually and morally. You are capable to stop this thuggish group in power by gun or by economic power. Nothing can do the job currently better than you the armed Tigrayan group inside the Army or inside the bureaucracy who are armed legally . Gun is mighty!

 Let me finish my reasons:- the so called “SAP” project targeted Amhara ethnic and others as well who refused to cooperate with TPLF mission of hegemony. This project mainly fired or layoff Amhara ethnic intellectuals from their work and replaced them by Tigrayans (including few Gurage or Ormo ethnic were and others were victims as well ) who were running universities, colleges, Army training Centers, Civil and justice Departments, institutions, health, cooperation, bank and Airline, Hotels, transportations, IRS offices (import and Export), ELPA, Coffee and Sugar Corporation, Industries and Agriculture, Water supply and Sewage Authority, Trade, commerce, distribution and the entire defense …etc..Etc… were given to Tigrayan intellectuals and including to the thousands and thousands of its guerrilla fighters as well.

Majority Ethiopians are made emasculated intentionally through the Structural Adjustment Program to benefit Tigray and Tigrayans. Religion and ethnic conflict  (TPLF fostered radical Saudi Wuhabi followers in Ethiopia intentionally – Abu Haider and his likes was fostered and still fostered and actively engaged his subversive mission through Pal Talk communicated from inside Ethiopia  with the Diaspora Wuhabi Ethiopian Muslim community, allowed  by TPLF government in Addis Abeba) in order to kill the nation’s unity to easily subjugate the people of Ethiopia under their mercy similar to  the barbaric Arabs are capturing poor Ethiopians under their brutal arm seen on the above photo. 

This is why Ethiopians of none Tigray origin still as we speak see TPLF group as ‘occupiers’. The SAP was designed by CIA and implemented by TPLF after counseling its masters in the World Bank controlled and supervised by Americans and Mossads (who bought the Felasha and shipped them to Israel in broad day light. While the Mossad also openly shot civilian Ethiopian Airline while flying on the air from Lebanon warning TPLF to shut its mouth. And it did as told. Ethiopia’s humiliation is many).

Therefore, majority Tigrayan elites went with such subversive act of TPLF, Mossad & CIA in Ethiopia and still continue now openly  by the Arabs.

As we all know, TPLF claimed to represent Tigray and its name indicates is to Liberate Tigrayans from Ethiopia (even after 22 years still there). Tigrayans might have face repression here and there after 22 years which is inevitable and expected from thuggish group. But not deportation as the Amhara are facing. Some young Tigrayans such as a fellow by the name Abraha Desta living in Tigray teaching at Mekele University urged recently not to oppose or blame the Islamo Fascist Jawar of OLF or the anti Amhara EPLF agent Tesfaye GebreAb. The dilemma or the question is-,  what could  have Abraha Desta’s reaction could have been if Tesfaye Gebreab’s book “YeBurQa Zimita” was urging the ethnic cleansing of Tigrayans by the Oromo as he was urging Oromo to be armed fully and clean the Amhara population from the Oromo lands?

The present abuse by the Wuhabi Saudi government did not pop up from nowhere. The Arabs knew there is no Haileselassie or Mengistu type nationalist government who can order the Americans to be out rash from Asmara /Kangew in 48 hours or the lion the African icon; Haileselassie who was feared in the world Arena equally with the Super powers. The Arabs knew the present thuggish group were their beggars who knew them well, when they were begging them money, office and Passports and provided them women for their sexual hungers when they were Guerrilla fighters roaming all over the Arab countries. They know them all by their names!

These thugs have no national pride as an Ethiopians. They are thieves supported by Ethno nationalists. That is why Arabs are now abusing our people openly knowing no nationalist government who can embarked on them like a lion to the farting womanizer Wuhabist Arabs any time they start to disrespect Ethiopian citizens!

Ethno nationalists can claim ‘Ethiopia, Ethiopia’ orally, or write internationalism or slogan of anything resemble of that. But, as long as they see the Amharic problem or the Oromo or Gambela or other repressed citizens apart from their ethnic – they are still part and parcel with the Ethno Fascist groups in principle.

Why am I calling Tigrayan TPLF followers to stop giving support to the TPLF thuggish group? Let me finalize it why. With all these national crimes committed by TPLF against Ethiopians (particularly against the Amhara Ethiopians) for the last 21 years, a good size number of Tigrayans  went along with the crime of TPLF. Last night, I visited by accident one Pal Talk room. The speaker is a lady and it was in pure Amharic (presumed Tigrayn origin as some of her accent hints), she was completely in defense of her TPLF government and ridiculed the immigrants claim regardless she was made to hear the audio record aired via VOA Amharic.

She seemed to be on denial that TPLF can’t lie when it comes to anything. Sadly, she was accusing the victim as Amharu puppets. This reminded me the Geza Tegaru Pal Talk Admin by the name “Hidiyat” (went to school in Addis Abeba – now living in New York City- some times travel to Africa for NGO related works) when she was accusing the Guraferda Amhara Deportee as “POPOP Corn! and “violators ” with her conclusion of support to the Deportation as “Big deal! So what, if they deported them!!!!!?”  (You can hear this on my weblog- Ethiopian Semay- on the audio video section posted there for the record). TPLF supporters do see human abuse by their leaders as “legitimate” as long as it is not their ethnic.

In other words, justice in definition when Tigrayan defining it - has different definition. Here is how.  The Ethiopian giant scholar Dr Assefa Negash’s research explains it briefly as the following.

“For Tigreans, any issue in which a question of justice is involved, abstract considerations of what is just or unjust play a lesser role than that of the ethnic identities of the conflicting parties or persons engaged in the particular conflict. In short the Tigrean culture, the issue of justice is not as important as the issue of the ethnic identities of the offender and the victim. In other words, the Tigrean sense of justice is a function of biological or ethno-linguistic relationship to the would-be offender and victim in a conflict.

For The Tigringa speaker, something is experienced as injustice when that injustice is perpetrated on a Tigrean by an outsider, depending on the relationship of this outsider to the would-be victim. For a Tigrean, any criminal offense that a Tigrean may commit against a non-Tigren does not constitute an injustice as long as the one committing the offense is a Tigringa speaker.  

Understanding such specific traits would help us understand why almost all Tigringa speakers, particularly the most enlightened ones in the Tigrai-Tigringa ranks, have jumped on the EPRDF band-wagon and have thrown their support behind this ethnocentric regime. That is why Tigringa speakers, with very insignificant exception, have failed to condemn the injustice EPRDF is operating on non-Tigreans.” Assefa Negash, MD –The Pillage of Ethiopia by the Eritrean and their Tigrean Surrogates (1996) the Tigrean Sense of Justice Revisited- P, 86-87).

Here we are now seeing placed Ethiopians in Wuhabi/Nazi concentration camps in Saudi openly in this century to murder them as the Jew by the Nazi in Germany! Ethiopians are humiliated many times by the Arab slave masters for the last 22 years under TPLF era (even when they were guerrilla they were selling Tigran women to the Sudanese and Arabs for sexual acts in order to kill or arrest or to kidnap their opponent living in those countries by the hand of those country’s security and spy officers. General Faruk in Sudan- during the Numeri ear and similar other corrupt security chiefs were given Eritrean or Tigrayn wives/concubines.

 This time is not individual abuse. It is ethnic cleansing approved by the Wuhabi Saudi King and his entourages lost their humanity drunken by petro dollar wealth pushing Ethiopians to the “King Abdela Concentration Camp” hack Ethiopians by bayonet knives, murdering pregnant women, gang raping young girls, starved them and refuse them, shutting down any available water and electric city, no bathrooms or toilets/latrine to be used by the concentration camp. This is beyond immigration issue. This is Alqaeda mission orchestrated by the Wuhabi regime in Saudi Arabia linked to the Ethiopian Muslim issue. Ethiopian are humiliated and placed on concentration camp intentionally to kill our people allowed by the Saudi government.

I here call, to all Tigrayan TPLF government supporters not to be a hypocrite by calling for protest in front of all the Saudi Embassies (though it is good intention and good start if at all you going to do it!) only, but you need to call your members to condemned your TPLF government and over throw it once for all! That is what all Eritreans are doing against Isayas Afewerki this days; and it crucial also and expecting  the same from you all Tigrayan TPLF supporters if you want such abuse to stop once for all from the land of Ethiopia, so dignified Ethiopian pride will again revive back from the hellish ground TPLF buried it deep. Thanks.  Getachew Reda (Editor Ethiopian Semay) getachre@aol.com   Google it (Ethiopian Semay)

                                                                                                        

Tuesday, October 29, 2013

ድምፃችን ዛሬም ነገም የጎሹ ወልዴ ነው!

 
The Ethiopian Gallants in Eritrea before they fall by conspirators and mercenaries!
 Goshu The Lion Shaming the Ethiopian Enemies
Getachew Reda still stand against all odds!
 ድምፃችን ዛሬም ነገም የጎሹ ወልዴ ነው!
(ጌታቸው ረዳ ኢትዮጵያን ሰማይ አዘጋጅ) October 29/2013


 
የርዕሰ ጉዳዬ መነሻ የምመራበት ‘የፖቲካ መርሃ ግብር’ የለኝም፤ ለመንበረ ሥልጣን አደለሁም የምታገለው እያለ ውስጠ ስራው እንዳይታወቅበት የሚሸሸገው ግንቦት 7 ብሎ ራሱን የሚጠራ ‘ፌክ ቡድን’ (የክቡር ዶክተር ማንከልክሎት ሃይለስላሴ ቃል ልዋስ እና)  ከኤርትራው ሻዕቢያ ቡድን ጋር ያለው የቅጥረኛ ግንኙነትን የሚያትት ነው።
 ለነገሩ ኤርትራ ሄደም አልሄደም ‘ዲሞክራሲ’ የሚባል የማስገንጠያ ሽፋን ተጠቅሞ ‘ኦኖጎች እና መሳይ ተገንጣዮችን” በ40 የጐሰኞች ባንዴራ የተሰነጣጠቀቺው  አገራችንን ግብአተ መሬቷን ለማጠናቀቅ ቃል ገብቶ እየሰራበት ስለሆነ  አስመራ ሄደ አልሄደ ለኛ ትርጉም ባይሰጠንም፤ ባንዳዎችና አርበኞች ልዩነታቸውን ‘በአወድዮ በቪዲዮ’ ታሪክ ቀርጾ የተወልንን ምስክርነቱን እንድታደምጡ ግን አግባዛችሗለሁ። በዚህ እንነጋገራለን።
ከዚያ በፊት ግን በአማራዎች እና በክርስትያኑ ማሕበረሰብ ላይ የዘር ማጥፋት ዘመቻ የፈጸሙ እና ለወደፊቱም እንዲካሄድ የሚያበረታቱ እና የሚቀሰቅሱ ‘የፖለቲካ ወንጀለኞችን’ የጥላቻ ዘመቻ እያካሄዳችሁባቸው ነው እያለ “የሚወነጅለን” ከወደ ትግሬ ከመቀሌ እየጮኸብን ስላለው ወጣት አንድ ብየ ወደ ርዕሴ ልሻገር ነው።
ዛሬ፤ዛሬ “ባንዳነት” ነውር እንደሌለው እየተቆጠረ በወጣቱ ሕሊና ሰፊ ቦታ እያገኘ ነው። ብዙ የተበሻቀጠ የባንዳ ትምህርት አስተማሪ እና ተቀባይ ተማሪ እንደ ጉንዳን ተራብቷል። ከትግራይ እስከ ምስራቅ ከደቡብ እስከ ምዕራብ በግንጣላ ስራ እና በዘር ማጥፋት ተግባር የተሳተፉ የድርጀት መሪዎች እና ግለሰቦች በሕብረተሰቡ ዘንድ ምንም ዓይነት ቅዋሜ እንዳይደርሳቸው በ1983 ያየነው ዓይነት ጥብቅና ዛሬም ለሁለተኛ ጊዜ ከእኛው ጉያ ተከላካዮቻቸው ሆነው የሚያገለግሉ እያገኙ ነው።
በወያኔ ዘመን የተወለዱ ወይንም ህጻናት የነበሩ  ወጣቶች ዛሬ አድገው ባደጉበት የተመረዘ የፖለቲካ ትምህርት በመዋኘት ግንጠላም ሆነ የዘር ማጥፋት ቅስቀሳ የሚያስተምሩ እንደ እነ ጃዋር መሐመድ የመሳሰሉት አደገኛ ‘የሰው አንስሳት’፤ ከትግራይ ከመቀሌ ‘አብርሃ ደስታ’ እያለ ራሱን የሚጠራ ወጣት እና የዓረና ድርጅት አባል ‘በፌስ ቡክ’ እና ዘሐበሻ በተባለው ድረገጽ የሚያሰራጨው የነቀዘ ቅስቀሳው ‘ለጃዋር መሐመድ’ (ኢትዮጵያ አውት ኦፍ ሶማሊያ! ኢትዮጵያ አውት ኦፍ ኦሮሚያ! ፈካሪ) በተደጋጋሚ ለሦስተኛ ጊዜ  ድጋፍ በመቆም “በጃዋር ላይ የጥላቻ ዘመቻ አራማጆች” በማለት ወንጅሎናል።

አንደ አሜባ እየተራቡ የባንዳ ደጋፊዎች እየሆኑ የመጡ  አገራዊነት በቅጡ ያልተረዳቸው በወያኔ ዘመን የተወለዱ ወይንም ህፃናት ሆነው ያደጉ እንደ አብርሃ ደስታ የመሳሰሉ “በግማሽ የተለወሱ ሊጦች” ታሪኩን በሚገባ ሳያጠኑ እራሳቸውን ተጃጅለው ሌላውን  በማጃጃል ‘በአገር የግዝገዛ’ ዘመቻው ላይ ተዋናይ እየሆኑ የመጡበት ወቅት ስለሆነ የአንድነት ሃይሉ፤ በተለይ ምሁራን እንዚህን ‘ጐደሎ ወጣቶች’ የግዝገዛው ሱታፌአቸውን  ከማስፋፋታቸው በፊት፡ እነኚህን የተጃጃሉ ወጣቶች መቋቋም የሚችል ኢትዮ ጵያዊ አዲስ ትውልድ አዘጋጅቶ  ማስተማር ለነገ የማይባል አጣዳፊ የቤት ስራችን ነው።


ወጠቱ አብርሃ ደስታ በጃዋር መሐመድ የሚመራው “ኢትዮጵያ አውት ኦፍ ኦሮሚያ፤ እና “የክርስትያን አንገት የቆረጣ አብዮት” ቀስቀሳ እና የኦነግ ፕርንሲፕል ዘመቻ  ደጋፊ በመሆን በጃዋር ላይ የጥላቻ ዘመቻ እያካሄዳችሁበት ነው ብሎ የቀሰረብንን የውንጀላ ብዕሩ እና “ተበዳይ በድየሃለሁ ብሎ ለበዳይ ይቅርታ” ይጠይቅ ያለበትን ፍረደገምድል ጽሑፉን  ላመንበብ እዚህ ጫን ይበሉ።

ወደ ርዕሳችን እንግባ። ውይይታችን ስለ ኤርትራ ነው። በሰሜን አይጦች የተቦሮቦሮ የተደፈረው የአንበሶች  ቤት አንዲህ ‘በእርሱት እርሱት’ በግንቦት 7 ደላላዎች ተጃጅለን የምናልፈው አይሆንም።  ያልተቋጨው የኤርትራና ኢትዮጵያ ጉዳይ ሲነሳ ፤ ሻዕቢያ ወያኔን ወልዶ፤ወያኔ ደግሞ ግንቦት 7ን በአምሳያው ወልዶ ወያኔና ሻዕቢያ  ያላጠናቀቋቸው የመጨረሻ የቤት ስራዎቻቸው በግንቦት 7 በኩል አንዲፈጸም ጥረት እየተደረገ ነው። የማስፈፀሚያው ድብቅ መሳሪያው ደግሞ ‘ዲሞክራሲ’ነው። እነ ሂትለር እነ ሴዛር የማሰሰሉት አምባገነኖቸን ወደ ስልጣን ያመጣ “ዲሞክራሲ” ግንቦቴዎችም በዛው መሰለላል ለመረማመድ ዲሞክራሲን ተጠቅመው “በማጆሪቲ ካርድ” መፈክር አገር ለማፍረስ ተዘጋጅቷል። በዚህ ላይ በሰፊው እመለስበታለሁ (ሌላ ቀን)።
እስከእዚያው ድረስ በነሓሴ ወር 2005/2013 ‘ንሂሊስቶቹ’ “ዲሞክራሲ” አገር በማፍረስ የሚጫወተው ሚና እና የግንቦት 7 እና የኦኖግ ተዋናዮቹ በአገር ዕጣ የሚሸርቡበት የዲሞክራሲ ካርዳቸው ተጠቅመው እንዴት አንደሚያጠናቅቁት የሰጠሁት ቃለመጠይቅ  “You Tube”  ላይ ሰፍሯል፡ ያንን ያድምጡ።
ወዳጄ ደራሲ፤ገጣሚ እና አርበኛው ኢያሱ አለማዮህ (ሃማ ቱማ) “በቀዳዳ ጨረቃ” መጽሐፉ ላይ በገጽ 29 እንዲህ ይላል፡
“…ከጥቂት ደቂቃዎች በሗላ ስነሳ ውሻይቷም ቢራቢሮቹም ጠፍተው አገኘሁ። ላም የሚያክል ጥንቸል ፈገግ ብሎ-አራት ጥርሱን እያሳየኝ- ሲመለከተኝ አገኘሁት።
          “አንተ ማነህ? በብስጭት ድምፅ።”
          “መሪህ ነኝ አለኝ።
          “የማን መሪ?”
          “የቀጣይ ጉዞህ።”
          “ወዴት?”
          “ሳትደርስ፤ሳታየው ስሙ ምን ያደርግልሃል? “ተሳፈር” አለኝ። ላም የሚያክል ጥንቸል መሳፈር የለመድኩ ይመስል ፍንጥር ብየ በጀርባው ወጣሁ።ላም-ጥንቸሉ በመጋለብ ፍጥነት ጨመረና በረረ። ጥቅጥቅ ያለ ጨለማ ሆኖ የማየው አጣሁ። ወደላይ ባንጋጥጥ ቀዳዳ ጨረቃ ይበልጥ ተበጣጥቃ አየሁ። ብዙም ሳንበር ላም-ጥንቸል ከወገቡ አሽቀንጥሮ ወደ ጨለማው ቁልቁል ወረወረኝ።” (ቀዳዳ ጨረቃ ደራሲ ሃማ ቱማ)
የመጪው ጊዜ መሪዎቻችን (ዕድሜ ከሰጠን) እነማን ናችሁ? ሲባሉ፤ የምትመሰርቱት የአገር አንድነትስ የስርዓቱ ስልት ምን ይመስላል፤ሲባሉ- እዛው ሳትደርሱ ምን ያደርጉላችሗል። ይሉናል። የሰሜን ሽፍቶች እጆቿን  በካቴና አስረው አፏን በጨርቅ አፍነው አዘናግተው የጠለፏት ‘ጨረቃዋ ኢትዮጵያ’ እየታመጸች ከምትገኝበት ዝግ ቤት ነፃ ለማውጣት ‘በሕግም ሆነ በጉልበት” በሩን መበርገድ የሚያስችል ባሕሪ የላቸውም። ብዙ የሚጠየቁ ጥያቄዎች አሉን።
ቢሸፋፍኑትም ለጥያቄዎቻችን ሳያስቡት ድንገት ቀጥተኛ መልስ አግኝተናል። የግንቦት 7 መሪዎች በብርሃኑ እና በዋና ጻሐፊያቸው ‘በአንዳርጋቸው ጽጌ’ እንዲሁም በሕዝብ ግንኙነት ክፍል ተጠሪያቸው ‘ኤፍሬም ማዴቦ’ አማካይነት ግልጽ የሆነ መልስ አግኝተናል። ሲያወላውሉ “እዛ ሳትደርሱ? ምን ያደርግላችሗል!” ሲሉን፤  ደፈር ሲሉ ደግሞ “አይቻልም!” ብለውናል። ሲነሽጣቸውም በማደንቀው ወዳጄ ጋዜጠኛ እና ደራሲ በመስፍን ማሞ  ተሰማ  መጽሐፍ የጆርጅ ኦርዌል “አኒማል ፋርም” ትርጉም “የእንስሳት አብዮት” ላይ የተተረከው ‘የሸንኮር አገዳ ተራራ’ ታሪክ ለሚጥማቸው ለአማኞቻቸው ጀሮ ያስደምጣሉ።
በመግቢያ ላይ እንደጠቀስኩት ለማንኛውም የችግራችን መሰረት ከአክሱም ዘመነ መንግሥት ጀምሮ እስካሁን ድረስ በአክሱማዊያን እና በእነ ዘርዓ ያዕቆብ በእነ ዓምደ ጽዮን እና በተፈሪ የተጠበቀው የምድራችን ምድሪ ባሕሪ እና ተያያዥ ሁኔታ እኛኑን በእኩል በሚጠቅም መልኩ ካልተጠናቀቀ ኤርትራኖች የሶማሌ ዕጣ ፈንታ ይደርስባቸዋል። (እመኑኝ)። ጠላቶቻችን ሰብረው የሚገቡበት ቀዳዳ በር በኤርትራ ነው። ለዘመናት የተፈታተኑን ጠላቶቻችን ተሳክቶላቸው ‘በሩን’ ተቆጣጥረውታል። ኢትዮጵያም ያለ ባሕር በር ቀርታ በጠላቶች ተከብባ ትገኛለች።ዝም በሉ የሚሉን እና ጦርነት ናፋቂዎች እያሉ የሚያጃጅሉን ባንዳዎችን አንታግሳቸውም።
ይህ ያለ ህግ በሸር እና በአመጽ የተጠናቀቀ የኤርትራ ግንጣላ እና የኢትዮጵያ የባሕር እገዳ፤ አርበኞቿ ዛሬም ኢፍትሓዊው አመጽ ለመቀልበስ የተቻለንን  የፖለቲካ ክርክር በማድረግ ላይ አንገኛለን። በአንጻሩ ለጠላት የሚያጎበድዱ ደካማ ፍጡሮችም የጠላት ፕሮፓጋንዳ ሕጋዊ አድርገው በመቁጠር ከኤርትራኖቹ ወግነው ‘ኢትዮጵያን’ አመጸኛ በማድረግ ‘ጠላፊዎቿን’ ከወንጀላቸው ነፃ ለማድረግ ከኤርትራኖች በላይ ኤርትራኖች እየሆኑ ያሉትን በግንቦት 7 ተደራጅተው እየተንቀሳቀሱ የሚገኙ ባንዳ መሪዎቻቸው እና ተከታዮቻቸውን በጥብቅ እንኰንናለን።
ግንቦት 7 ምንም ተዋጊ ሠራዊት ሳይኖረው በባዶ ጉሮሮው ቢጐረናም፤ የተማመነው ተዋጊ ሃይል “ድምሒት” የተባለው ኢሳያስ አፈወርቂ ያሰለጠነው ቅጥረኛ የትግሬ ሚሊሻ ተዋጊውን ለመጥለፍ በማቀድ ነው። እዚህ ላይ የኤርትራን ውስጣዊ ጉዳይ በቋንቋ እጥረት ምክንያት አብዛኛዎቻችሁ ለማትከታተሉ ሁሉ፤ ልነግራችሁ የምፈልገው ነገር አለ። ድምሒት የተባለው ሰራዊት ‘አርማው’ የአገራችን ሰንደቃላማ ሆኖ ከመሃሉ ‘የአክሱም ሃውልት’ ጨምሮበታል (ይህ ሕገ ወጥ ቡድን  ስልጣን ቢወጣ ወያኔ እንዳደረገው ሁሉ ያለ እዚሁ አርማ ሌላ አንዳይውለበለብ ሕግ ያወጣል ማለት ነው)። ድምሕት የተባለው ቡድን ግን ተዋጊዎቹ በበረሃ እና በውጊያ የተጎሳቆሉ ሳይሆኑ ቁንድላ ተሰርተው ጎፈሬ አበጥረው ወዛቸው ለምልሞ በሙዚቃ ባንድ ታጅበው የምታዩዋቸው የትግሬ እና ኤርትራ ድብልቅ ወጣቶች ዋነኛ ስራቸው ድምበር
የኤርትራን ድምበር መጠበቅ እና አስመራ ውስጥ ከዘመቻ የሚሸሹትን ወጣቶች እና በሻዕቢያ የሚፈለጉ ሰዎችን በየቤቱ እና ጎዳናው አድፍጠው በመሰማራት “ድብዳባ” እና “አፈና” የሚፈጽሙ /መርሲናሪ/ ታጣቂዎች አንደሆኑ ከሁለት ዓመት በፊት ከአንድ ውስጥ አዋቂ ሰው ያገኘሁትን መረጃ አስነብቤአችሁ እንደ ነበር ይታወሳል።
 
ዛሬም በድጋሚ ያንኑ ዘገባ ተንተርሶ ከወደ አስመራ ሽው የሚለው ወሬ እየተናፈሰ ነው። የኢሳያስ ቡድን ችግር ውስጥ ሲገባ ድምበርም ሆነ ከተማውን በመቆጣጠር ‘የሹት ትኪል’ (ነጻ እርምጃ) ሃላፊነት የሚሰጣቸው እነሱ እንደሆኑ እና፣ ድምበር ላይ ሰውን በማሻገር ገንዘብ የሚቀበሉም እነኚሁ መሆናቸው በሰፊው ይወራል።
ሰሞኑ አስመራ እና በመሳሰሉት ከተሞች “አሰሳ” እየተደረገ ነው።በዚህ ስራ የተሰማራውም ይህ ቅጥረኛ ቡድን ነው እያሉ ኤርትራኖቹ ይህንን ቡድን ይወነጅላሉ። በነዋሪዎቹ አጠራር  “ከምድላዬ” የሚል ቅጥያ ተሰጥቷቸዋል። “እንዳሻኝ” ይሏቸዋል። ‘አጋሜ’ እያልን አንዳላሳነስናቸው ሁሉ የግረም ብሎ የድምበሮቻችን እና ከተሞቻችን ጸጥታ አስከባሪዎች ሆነው የቤቶቻችን በሮች እያንኳኩ አፋችን ከድነን በፍርሃት ተውጠናል። እስከማለት ኤርትራኖች ምሬታቸው እየገለጹ እንደሆነ ለዚህ ጸሐፊ የተሰጠው መረጃ ያስረዳል።
ከወዲሁ የግንቦት7 ጸሓፊው የኢሳያስ ተክለሰውነት እያሞካሸ ለሕዝብ መስበክ የጀመረበት ዋናው ምስጢርም ፤ ድምሕት የተባለው ኤርትራ እና ትግሬ የደበላለቀ ተዋጊ ሃይል በኢሳያስ ትእዛዝ ለፕሮፓጋንዳ መጠቀሚያ እንዲሆነው በግንቦት 7 ቁጥጥር ስር አንዲውል በድምሕት ላይ እየተሸረበ ነው የሚሉ የውስጥ አዋቂዎች ይናገራሉ። ኤርትራ በረሃ ውስጥ አለ የሚባለው “አርበኞች ግምባር” የግንቦት 7 ሴራ አስቀድሞ ስለገባው ከበትናቸው ጽጌ (አንዳርጋቸው ጽጌ) በግምቦት 7 እንዳይጠለፍ አስቀድሞ ስለተጠነቀቀ ነበር ‘ብርሃኑ ነጋ’ በግልጽ ኢሳትን ‘እንግዲህ ወዲህ ስለ አርበኞች ግምባር ህልውና በኤርትራ ውስጥ አለ ብሎ ኢሳት አያወራም” ብሎ ትዕዛዙን ለኢሳት ያስተላለፈለት።    

ኤርትራ እነዚህን ሁሉ እየሰባሰበ የሚረዳበት ምክንያት ኤርትራኖች የሚያሰጋቸው መጪው ሕጋዊ የጦርነት ዳመና “በኢትዮጵያ የአንድነት ሃይል ተዋጊዎች እና መሪዎች” እንዳይከፈትባቸው ስለሚሰጉ ነው። ዋናው ጉዳይ ግን ‘ድንገት አገራችን ሁከት ውስጥ ብትገባ’ የኢሳያስ የግል ወዳጅ የሆነው ጀኔራል ስብሓት ኤፍሬም የተባለው መልከ ጥፉ ዘረኛ “ፈንቅል” በተባለው የሻዕቢያ ወታደራዊ መጽሔት በሰጠው ቃለ መጠይቅ አንደገለጸው “በጐመራው ላይ እየነደዱ ያሉት እንጨቶች ስንት አንደሆነ በቁጥር እናውቃቸዋለን፡ እሳቱ ተቃጥሎ አመድ ለመሆን ጭልምል እያሉ ያሉት ጭራሮዎች፣ኢ ስንት እንደሆኑ እናውቃለን። ነድደው ለማለቅ የቀራቸው እነኚህ ጭራሮዎች የቀራቸው ጊዜ ጥቂት ነው፡ በእሳቱ ዙርያ ቆሞ እሳቱ ነድዶ እስኪያልቅ ድሰር እየቆሰቆሰ በቅረብ እየተቆጠራጠረው ያለው ሃይል ደግሞ እኛ ስለሆንን የተነጠቅነውን መሬትም መልሶ ለመንጠቅም ሆነ (ባድመ) በፖለቲካ ማዕበል እየተንገላታች ያለቺው ምሲኪኗ ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እኛ ትዘረጋለች” ብሏል።
 
ትዕቢቱና ሴራው ስናገናዝብ አሁን ለሚረዳቸው ግነቦት 7 እና ኦነጐች ሶማሌዎች ኦጋዴኖች ሲዳማዎች፤ቤንሻንጉሎች….ለምን እንደሚራዳ የምትስቱት አይመስለኝም። ነድደው ያለቁ ትላልቆቹ ግንዶች ወደ ጭራሮነት ተለውጠው አመድ ሲሆኑ በነሱ ምትክ ለመተካት አንደሆነ አትስቱትም።

እራሱ እድሜ አይኖረውም እንጂ እቅዱ እነዚህን ቡድኖች አስከትሎ ከሗላ በመሆን የመቶ አመቱ የቤት ስራው የመጨረሻ ፍጻሜ ለማጣናቀቅ ነው። ሆኖም መጀመሪያ ማን አመድ አንደሚሆን የሚታይ  የማይቀር ትርኢት ቢሆንም ለጊዜው የኤርትራ ጉዳይ የተዳፈነ እሳት ቢሆንም የታመጽነው አመጽ ፍትሕ እሰኪያገኝ ድረስ ዘመናትም ይፍጅ “ጦርነቱ ይቀጥላል!!!!”። ይህ የኔ እምነት እና መመሪያየ ነው። “ጦርነት አትቀስቅሱ” ፤ “አንዴ የሆነ ሆኗል” ፤ “ስታተስ-ኮ”-ውን ተቀብልን  ሰላም አንፍጠር”  እያለ ያለው ክፍል፤ እራሱን ያጃጀለ ምሁሩ ክፍል ስለሆነ ከነ’ዚህ “ቆሻሻዎች” ጋር ላለመነካካት ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋ።
   
ጠላቶቻችን እኛን አላሸነፉንም፤ እኛን ያሸነፉን የኛ የምንላቸው የቆሸሹ ወገኖቻችን ናቸው። የወቅቱ ቀዳሚ የውጊያችን ደግሞ በ1983 የተከሰተው “የክፍሌ ወዳጆ ሲንድሮም” (የጋሸ ቀለሙ ርዕስ ልዋስ እና) በሽታ አንደገና በድጋሚ አንዳይከሰት ሕዝባችንን ማስተማር ነው። ወጣቱ እኛን ማድመጥ አለበት። አሻፈረኝ ካለ፤ የሚኖሩባት ኢትዮጵያ ወጣቱ እንጂ እኛ አልፈንባታል። ለራሳችሁ ስትሉ ኢትዮጵያን ጠብቁ። ካልሆነ በየጐጣችሁ ታፍጋችሁ ማንነታችሁ ይፋቃል። ሲገነጣጠል ተገንጣዩም፤አስገንጣዩም ችግር ውስጥ አብሮ ይዳክራል። ማንኛችሁም ነጻ አትሆኑም።ለኔ ሳይሆን ለራሳችሁ ስትሉ ታገሉ! እኔ የምኖረው እዚህ ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ኢፈሲያነስ 6 ላይ ‘የምንታገለው ሰይጣንን እንኳ ቢሆንም ትግላችን እሱ ካሰማራቸው ጃንደረባዎቹ ጋር ነው።’ ይላል።  
እያናገረን ያለው ጥቃት ነው። እኛ ተጠቅተናል! እስካሁን ድረስ ለጉዳታችን ተጠያቂ ሆኖ በፍትሕ ፊት ቀርቦ የተጠየቀ የለም።ስለዚህም ጥቃት ፈጻሚዎቹ ዛሬም የወቅቱ ፖሊተካ መድረክ በአስመሳይ ምላሳቸው በመቆጣጠር ዳግም ወደ ቀረቺዋ ኢትዮጵያ ጠላቶቻችንን ለማስገባት የረቀቀ ሴራ እየሸረቡብን ነው።  
በኤርትራ ምድር ለዘመናት የከፈልንበት የደም ግብር አለ። አያቶቻችን እና ወላጆቻችን እህቶቻችን እና ወንድሞቻችን አጥንታቸው በኤርትራ ባሕር እና በኤርትራ በረሃዎች ተረጭቷል/ተዘርቷል። በዚህ የማንንት ጥያቄ አርበኞቻችን የዘሩት አጥንት መልቀም ይኖርብናል። ያለ ምንም ሰቀቀን ኤርትራ በረሃ ውስጥ ሄደው በእነዛ አርበኞች አንጥንት ላይ እየተረማመዱባቸው ያሉት የግንቦት 7 መሪዎች የአርበኞቻችን አጥንት በማርከሳቸው በወንጀል ይጠየቃሉ።
ያልተሰማችሁ ብዙዎች ናችሁ። በሰሜን አካባቢ የተወለድን እና የነበርን የዓይን እና የጀሮ ምስክሮች እኮ ያለፈው ትንንቅ አሁንም ከሕሊናችን አልለቅ ስላለን ነው። አንዲያ ያለ ብርታት እና ትንንቅ ተደርጎ ከሗለችን ‘በሴራ’ ስንመታ አንዴት ነው በእኛ ላይ የምትፈርዱብን?
እስኪ ላንዳፍታ ወደ 1983 ግንቦት ወር ሕሊናችሁ መልሱት እና ለ22 ዓመት ተጉዛችሁ አሁን ወዳለንበት ፌርማታ/ማቆሚያ/ አተኩሩ። የደረሰብን ጥቃት ሊስቱ/ዝርዝሩ ስንት ገጽ ነው? ይህ ሁሉ ጥቃት ሲጫንብን የቆዳችን ውፍረቱ እና ቻይነቱ ለታዛቢ የሚገረም አይመስላችሁም። ጥቃታችን አንድንረሳ ተጃጅለን አንድንኖር እና ኢትዮጵያ በጠላቶች የተሸረበባት የባሕር ወደብ እገዳ ሕጋዊነት አንዳለው በማስመሰል ለኤርትራ ወንበዴዎች ዛሬም ጥብቅና የቆሙ ተቃዋሚዎች ስንመለከት አዲስ ውርደት ላይ ገብተናል። ለምን ዝም በሉ እንባላለን?!
ወታደሮች ፤ አርበኛ ሚሊሺያዎች እንዲሁም ሲቪል እና የመንግሥት ሰራተኞች በዛው ምድርና እና በሕር የገበሩት የሕይወት ግብር ያፈሰሱት ደም አንዴት ነው አታንሱት የምትሉን? የስድባቸው ክምር እኮ ድፍረቱ አንዴት አንዳገኙት ለኔ ይገርመኛል።እንዲያ ተበድለን አጥቂዎችችንን ነጻ እንዲያወጡን እኮ ነው እየሰበኩን ያሉት? ኢሳያስ ነጻ እንዲያወጣን የሚያምኑና የሚማጸኑ የግንቦት ሰዎች ‘በስቶክ ሆልም ሲንድሮም’ ልክፍት የተጠቁ ይመስሉኛል ። በሽታ ካልሆነ እንዲያ ላለ እጅግ ክፉ ጠላት እና አጥቂ አንዴት ጥብቅና ቀሞ መልካም ዝና ይሰጡታል?
ያለማፈር እና በተቃዋሚው ጐራ እየተለመደ እየመጣ ያለው የባንዳነት ባሕሪ አስገራሚ ክስተት ‘ጋሻ ቀለሙ’ የተባሉ አርበኛ ኢትዮጵያዊ ጸሐፊ ከጥቂት አመታት በፊት ( ከ5 አመት በፊት) ያቀረቡት ቆየት ያለ ትችታቸውን ቀንጨብ አድርጌ ላቅርብላችሁ እና ባንዳነት ምን ያህል ተቀባይነት እያገኘ አንደሄደ እነሆ እንዲህ ይላሉ:-
 
“Politics should have been a game with rules and boundaries enforced by integrity, morality and truth. It is only the rational political argument that hits the target and accomplishes its goal not the irrational argument that can be pushed to get a result of false positive which crumbles down when it encountered the real truth.
We can’t reason with people who position themselves purposely to deceive us……..The method used to attract followers and attack opponents is beyond my imagination; you don’t hear or read in history books this kind of characters a few decades ago. The old way of showing and keeping your dignity by respecting your opponent is a thing of the past. So does not selling yourself to the highest bidder. Unlike our contemporary politicians in the old days treason was unthinkable, even if one or two in history has done it, they were outcastes and ashamed alienated themselves from the glaring eyes of society. But these days our politicians are advertising their treasonous acts through internet radios and their foot soldiers, no shame is involved anymore.
 They are not only treasonous and backstabbers themselves, they are teaching the next generation to do the same thing like they do, act like they act. Being sellout is not a shame it has to be glamorized adapted and followed.”  Gashe Kelemu ( Kifle Wodajo Syndrome)
ጸሐፊው ባንዳነት አዲስ ትግል ፈር ሆኖ ቀርቧል፤ ነው የሚሉን። ከአምስት አመት በፊት የነገሩን እኚህ ኢትዮጵያዊ ሃቅ  መሆኑን ዛሬ በግንቦት 7 እና አጫፋሪዎቻቸው ገሃድ ሆኖ ስለ ሻዕቢያው መሪ ሰብአዊነትና ስለ ኢትዮጵያ ተቆርቋሪነቱ ሳያፍሩ በሻዕቢያ ገንዘብ እርዳታ የሚደጐመው በኢሳት ቲቪ በኩል ቀርበው ሰፊ የባንዳነት ስራ ለሕዝባችን የሕሊና አጠባ አጋዥ እንዲሆን ቅስቀሳው ወደ ኢትዮጵያ ተላልፏል። ባንዳነት  ተቀባይነት እያገኘ፤ አገርን የመገዝገዙ “የክፍሌ ወዳጆ ሲንደሮም” ዘመቻ ሁለተኛው ዙር በግንቦት 7 መሪዎች ተጀምሯል።

ለዘመናት እስካሁንም ድረስ ጠላቶቻቸን የመረጡት  ይነተኛ የመጫወቻ ሜዳ “የኤርትራ ጉዳይነው”።ኤርትራ የማን ናት? የግንጣለው ሕጋዊነትስ ምን ያህል ሕጋዊነት አለው? ሁለት ወገኖች ያላቸው አቋም በስእለ ድምጽ አስደግፌ ላቅርብላችሁ እና ልደምድም።
 
Our heroes Professor Mesfin W/Mariam and Colo Dr. Goshu Wolde
Banda of the Year 2013 Efrem Madebo of Ginbot 7 propagating in defense of Eritrea and dehumanizing our Ethiopian heroes on behalf of Eritrean bandits calling them extremists

ኢትዮጵያዊነት ምን ማለት እንደሆነ እና ጠላት የሸረበብንን የመጥለፊያ መረብ አንቀበልም የሚለው አንድ አርበኛ ኢትዮጵያዊ እና በሌላ በኩል ደግሞ የጠላት ሴራ ሕጋዊነት ተቀብሎ በጠላት ቅስቀሳ የተሰማራው የመጥለፊያው መረብ ተቀበሉ የሚለን  አንድ ‘ኢትዮጵያዊ ባንዳ’ የሚታይ የሕሊና መራራቅ አድምጣችሁ መንፈሳቸውን መዝኑት እና እናት ኢትዮጵያ በዥጉርጉር አንጀቷ አንዴት ሁለት ዓይነት ልጆች ወልዳ አንዱ አጥቂዋ ሌላው ተከላካይዋ አንደሆነ ከዚህ በታች ያለው ‘ስእለ ድምፅ’  ከፍታችሁ አድምጡ። የተከበረው ኩሩ የኦሮሞው ተወላጅ ኢትዮጵያዊው “ዶክተር ኮሎኔል ጎሹ ወልዴ” ጠላት ባዘጋጀው መድረክ በመገኘት የወያኔ እና የሻዕቢያ ባንዳ ወኪሎችን እሳት በለበሰው አንደበተ ርቱእ ተጠቅሞ አንገታቸውን ያስደፋ፤ ፈረንጅን የገዛ ቋንቋው ተጠቅሞ አፉን አስከፍቶ አንዲያደንቀው ያደረገው ዓለም ያስደነቀ ተከራካሪ በዚህም ይሁን ባለፈው ትውልድ እንደ ጎሹ አይነት እናት ወልዳ አታውቅም። የጎሹ ቃል ዛሬም ሆነ ነገ ቃላችን ነው። አርበኛው ቀብራራው ኦሮሞ ኢትዮጵያዊው ጎሹ ወልዴ ማድነቅ አለባችሁ። የፈለገው ስህተት ቢኖረውም ጎሹን የሚያክል የባንዳን አንገት ያስደፋ ኢትዮጵያዊ በክብር ማህደር መመዝገብ አለበት።

ቀጥሎ የማቀርብላችሁ  የስዕለ ድምፅ ማሕደር በሁለት የተከፈለ ነው። አንደኛው ማሕደር የግንቦት 7 አመራር አባል የሆነ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ለኤርትራ/ሻዕቢያ የቆመ ባንዳ ሲሆን፡ ሌላው ያው፤ ቀብራራው ኢትዮጵያዊው ኮሎኔል ጎሹ ወልዴ ነው።  ከሁለቱም ተከራካሪዎች ካንደበታቸው የሚወጣው የኢትዮጵያዊነት ትርጉም እና ስለ ኢትዮጵያ ዘብ መቆም ምንነት፤ ስለ ኤርትራ ጉዳይ እና የደረሰብን ሴራ እና ኢፍትሓዊነት የቀረበው ተቃራኒ ክርክር መዝናችሁ አርበኛችሁን ምረጡ። ስእለ ድምጽ 1 ስእለ ድምፅ 2 ከዚህ በታች ቀርባል።

Colonel Goshu Wolde - Historical Speech http://youtu.be/orod3OU3jfM

Ephrem Madebo of Ginbot 7 Ethiopian opposition movement at Eritrean  http://youtu.be/pW1mopFgf2k

አመሰግናለሁ ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያን ሰማይ አዘጋጅ) getcahre@aol.com ድረገጽ እና ፌስ-ቡክ ለመጐብኘት ለምትፈልጉ (Ethiopian Semay)ጉጉል ብታደርጉ በቀላሉ ታገኙታላችሁ። በዚህ አጋጣሚ አዳዲስ መጽሐፍቶቼ ዳግም በጥቂት ቅጅ ታትሞ ለገበያ ቀርቧል። ጠይቁ። አመሰግናለሁ። ጌታቸው ረዳ። (Ethiopian Semay)