Wednesday, December 30, 2015

3ኛው ዙር የኦሮሞዎች ፋሺዝም አብዮት! ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያን ሰማይ ብሎግ አዘጋጅ)



3ኛው ዙር የኦሮሞዎች ፋሺዝም አብዮት!
ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያን ሰማይ ብሎግ አዘጋጅ)
ስትፈልጉ “From Fascism to Fascism (Aleme Eshete) ወይንም በኔው አገላለጽ The Recycling of the Ormo Fascism! The third cycle of the oromo Fascism” (Getachew Reda) ብላችሁ ርዕሱን መተርጎም፤ መረዳት ትችላላችሁ። ወደ ትንታኔዬ ከመግባቴ በፊት መጀመሪያ አርበኛው፤አገር ወዳዱ እውነተኛው የኦሮሞ ተወላጁ እጅግ የማከብረው ኢትዮጵያዊው ወዳጄ ዶ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ የኢትዮጵያ መሬት በፋሺስቱ የወያኔ ቡድን ለሱዳኖች በገጸ በረከት በድብቅ ለመሸለም በምስጢር እየተሯሯጠ ባለበት ጊዜ እየተደረገ ያለ የአገር ክሕደት በተያያዘ ጉዳይ ሰሞኑን ተቃውሞውን በሰላ እውቀቱ በዝርዝር በማስረዳት፤ ለሕዝባችን ማስተማሩ እጅግ አክብሮቴን እየገለጽኩ፤ እንደ ደ/ር ፍቅሬና እዚህ አብሮን አካባቢያችን የሚኖሮው ወዳጄ ደ/ር ደምሴ ኦሉማ እና ስማቸው ለመጥራት እጅግ የበዙብኝ ሀቀኛ የኦሮሞ ነገዶች፤ ስለ ኢትዮጵያ አገራቸው ክብርና ሰላም በመቆማቸው፤ አንባቢዎቼ እንድያመሰግኗቸው ጥሬዬን አቀርባለሁ። በተለይ ሁለቱም ወዳጆቼ ከተገንጣይ ቡድኖች ጋር ከፍተኛ የሆነ አታካራ በመግጠም፤ በሕዝብ ፊት ሃቀኛ ኢትዮጲያዊነታቸውን በማመስከራቸው፤ በተገንጣዮቹ በመጥፎ ዓይን የሚታዩ ታጋዮቻችን ናቸው። ለዚህም ክብር ምስጋና ይገባቸዋል።

በዚህ ጽሑፌ ስለ ተመለከተው ርዕስ ስተነትን ፤ እነዚህና በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኦሮሞ ወታደሮች፤ምሁራን፤ገበሬዎች፤አትሌቶች፤የኪነት ሰዎች፤ሐኪሞች፤ የሃይማኖት መሪዎችና ምዕመናኖች፤ በአንድነት ሃይሉ የተሰገሰጉ ሃቀኛ ኦሮሞ ኢትዮጵያወዊያን ታጋዮች፤ጋዜጠኞች፤ ሰራተኞች፤የዛሬና የድሮ የኦሮሞ አርበኞችን እና የመሳሰሉ በኢትዮጵያዊነታቸው የሚያምኑ የኦሮሞ የሕብረተሰባችን ክፍሎች ፍጹም አይመለከትም። ይህ ርዕስ እና ትንታኔ የሚያተኩረው በኢትዮጵያ ሕዝብ ላብና መስዋእትነት ነፃነታቸውና ዜግነታቸው ጠብቆ “ለከፍተኛ ትምህርት” አድርሶ አስተምሮ፤ ለማዕረግ ያበቃቸውን የኢትዮጵያን ሕዝብ ለማበጣበጥ በውጭ ጠላቶች እየታገዙ ኦሮሞን ከወገኖቹ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ነጥለው አገር ለመመስረት ለብዙ ዓመታት ሳያቆሙ እስከ ዛሬ ድረስ ብጥብጥ በመፍጠር ላይ የሚገኙ የኦሮሞ ተገንጣይ ምሁራንን ነው የሚመለከተው።

በዚህ ሰሞን የተከሰተው የኦሮሞ ተማሪዎች በፋሺስቱ ወያኔ ላይ እያካሄዱት ያለውን የአንገዛም አምቢተኛነት በወያኔ ስርዓት ላይ ያነጣጠረ ይሁን እንጂ ከስሩ/ከንጣፉ በታች (ኣንደር ዘ ራግ) “የሚጨሰው/የሚቦነው የእምቢተኛነት አቧራ” ያነጣጠረው ‘ኦሮሞ ያልሆኑ ኢትዮጵያዊያን ዜጎች’ ኦሮሞ የሚባል ክልል የባለቤትነት መብት እንደሌላቸው” የተንጸባረቀበት እንቅስቃሴ ነው። መፈክሮቻቸው “ኦሮሚያ የግላችን የኦሮሞዎች ነው!” ይላል። ይህ መፈክር፤- “የግንጠላ ዜግነት” ፍለጋ ጎልቶ የወጣበት፤ ተገንጣይ ኦሮሞ መሪዎችና ድብቅ ኦሮሞ የግንጠላ አቀንቃኞች በየሚዲያው ወጥተው “የአንቀጽ 39 መብት” እና “የራስን በራስ ማስተዳዳር “የነገድ ክልል”/ *የግሩፕ* መብት” እንዲከበር የቀሰቀሱበት ትዕይንት ነው።
ይህ “ባንቱስታናዊ ክልል” ስንመለከት፤ “ወያኔም ሆነ ተቃዋሚዎቹ” “ተቀናቃኞች ሆነዋል”። ይህ ማለት  ለፖለቲካ የበላይነት የሚያደርጉት ግብግብ ውጤት ነው   

በዝግታ እየተራመደ ያለው የሁለቱም “ተቀናቃኝ” ክፍሎች ባሕሪ ፤ በነገድ ላይ ያነጣጠረ “አዛዡ እኔ ነኝ፤ የኔ ነው፤ የኔ ነው፤ የድምበር ባለቤትነት” ክርክር በመሆኑ፤ “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዜጋ በኦሮሞ ምድር የበባለቤትነት መብት የማያከብር -፤ ዜጎችን ባይተዋር ያደረገ” ስለሆነ፤_ ሁለቱም ተቀናቃኞች “ፋሺስታዊ ባሕሪያቸው” (ተማሪዎቹ የባንቱስታኒክ ክልል አክባሪዎች ሲሆኑ፤ ወያኔ ደግሞ ፋሺስት ነው) ወደ “ፈጣን ፋሺስታዊ የመገዳደል እምርታ” እንዲሸጋገር ፍላጎት አላቸው። ተዋናዮቹ ደግሞ፤ በውጭና በውስጥ ሆነው የመገንጠልንና ለባንቱስታናዊ የክልል መብት የቆሙት ሃይሎች፤ የሁለቱም ፍጥጫ በሰውም ብንብርትም የፈለገው ጉዳት ይምጣ ኣንዲገፉበት ይፈልጋሉ።

በአዲስ አበባ ከተማ ኦሮሞ ወሰን አካባቢዎች ያሉት መሬቶች፤ በማስተር ፕላን ምከንያት  በብዙ መቶ ኪሎሜትሮች ርቀው የሚገኙ “በብዙ የኦሮሞ ከተማዎችና ክልሎች” የሚገኝ ኦሮሞዎች ተቃውሞው ለሳምንታት ሲዘልቅ “ከነጸብራቁ ብልጭታ” የሚነግረን ስዕል “ባንቱስታናዊም ሆነ ከዚያ ቢያልፍም የግንጣላ ፖለቲካ እውን እንዲሆን” ለፖለቲካ ሱፕረማሲ የሚደርጉት ግብግብ ነው። ኢትዮጵያዊነት የለውም የምልበትም ምክንያት ይህ ነው። ምክንያቱም “የአንድ ኦሮሞ ድምበር” ሲነካ ‘መላው ኦሮሞ አንደተነካ’ ተቃውሞአቸው በስፋት አስተጋቡ እንጂ 24 አመት  ሙሉ “የአንድ አማራ ድምበርና ህይወት በኦሮሞ ወረበሎች ሲደፈር፤ “መላው ኦሮሞ አንደተነካ አላሳዩንም”። ጥያቄአቸው፤ ባንቱስታናዊ እንጂ አገራዊ አይደለም የምልበትም ለዚህ ነው።   

 ይህም ቢሆን። በረብሻው ውስጥ የተጎዱ፤ህይወታቸው ያጡ በርካታ ኦሮሞ ወጣቶች “ነብስ ይማር” እያልኩኝ “ነብሰ ገዳዮቹም” ለፍርድ ቀርበው (ፍትሕ የለም እንጂ) ቅጣታቸው እንዲያገኙ የሚገባ መሆኑን እያመንኩ፦ ባጠቃላይ ቢያንስ “ለአንድ አመት ሙሉ” (ከአምና ጀምሮ) የታየው አመፅና የተደመጡት መፈክሮች የሚያሳየው  “የማስተር ፕላኑ” ጭቅጭቅ “ምክንያታዊ ደማሚት” ይሁን እንጂ “ሁለት ፋሺስታዊ ንቅናቄዎች” (ጊዜ ወስዳችሁ ተገንጠሉ የሚለው ብረት የታጠቀው ወያኔ እና በአንቀጽ 39 የግንጣላ ርዕዮት የታጠቀው ተገንጣይ የኦሮሞ ክፍል) አገርን በማፍረስ ላይ ያነጣጠረ “የግሩፕ ሱፕረማሲ ትግል” ስለሆነ፤በሁለቱ ክፍሎች እያየነው ያለው ግብግብ  ለአገራችን ህልውና አደጋ ላይ የሚጥሉ “ፈንጆች” ስለሆኑ ሁለቱም ክፍሎች ፋሺስታዊ ርዕዮት የሚከተሉ ናቸውና ቅዋሜዬን አቀርባለሁ።

 ተቃዋሚዎቹ፤የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተማሪዎች እንደመሆናቸው መጠን “ሁላችንም ከነዚህ ወጣቶች የምንጠብቀው” የባንቱስታን አከላለል ‘በደም፤በቋንቋ፤በአጥንት፤በነገድ” መተዳደር “ናዚያዊ” ዘረኛነትን መከተል ስለሆነ እንቃወመዋለን እንዲሉ ነበር እንጂ “ባንቱስታናዊ ክልል” ሕጋዊ አድርገው እንዲተገበር የሚጠይቁ ወጣቶች ይከሰታሉ የሚል አምነት አልነበረንም። ስለሆነም ነው አደጋነቱን እንድታዩት የምፈልገው፡

ሁለቱም ግብግብ የገጠሙ ክፍሎች ፋሺስት ርዕዮት ያነገቡ ናቸው ብያለሁ። ፋሺስም ምን እንደሆነ ወደ ታች እንመለከታለን። ወያኔ ፋሺስት መሆኑን ሁላችንም የምናወቀው ሃቅ ነው። ኦሮሞዎች፤ የወያኔ ፋሺዝም “የኦሮሞ መሬትና ተፈጥሮአዊ ሃብት፤ ለኦሮሞ ቋንቋ ተናጋሪ “ብቻ” እንዲሆን ፋሺስታዊ ሕገመንግሥቱን አጽድቀወ፤ፈርመው አመስግነው ተቀብለውታል። ይህ ፋሺስታዊ ሕገ መንግሥት የቀየሱትም “እነ ሌንጮ ለታ/ኦነጎች” እንደሆኑ ሰሞኑን በግልጽ ነግረውናል (ጥንት የምናውቀው ምስጢር ቢሆንም)።

ተማሪዎቹም እንደ ወያኔ ጀሌዎች “የፋሺስቶች ርዕዮት ተከታዮች” ናቸው። ወያኔዎችና ኦሮሞ ሊሂቃን ሕዝቡ እራሱ ወዴት እየመሩት አንደሆነ በሚገባ በግልጽ ያውቃል የሚል እምነት አለኝ። እየተጓዙበት ያለው አቅጣቻ፤ አምኖውበት ለ24 አመት ተቀብለውት እየተጓዘበት ያለው “የጎሰኛነት” (ፋሺስታዊ) ርዕዮት ቆም ብሎ የማሰብ ሁኔታ እያየን አይደለም። ስለሆነም ታማሪዎቹ፤ “ባልታወጀ በኦሮሚያ የዜግንት ምኞት” ሰክረዋል። ሕዝቡም፤ ኦሮሚያ የሚል ባንዴራ ተቀብሏል፤ላቲን ፊደል የኔ ነው ብሎ ተቀብሏል፤ኦሮሚያ የሚል ባንቱስታናዊ/የክልል ድምበር የኔ ነው ብሎ ተቀብሏል። ሰለሆነም የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ በቀር “ከፍተኛ” ብጥብጥ እፊቱ ላይ ተደቅኗል።

እኔ እንደ ትግሬነቴ ፤ለብዙ አመታት የትግሬ ሊሂቃን እና ሕዝብ የወያኔን ፕሮፓጋንዳ ተቀብለው ‘ጸረ አማራ” ሕሊና የመሸከማቸው ጉዳይ ባደባባይ ስኰንን እንደነበር ታወቃላችሁ። ኦሮሞዎቹም ከትግሬ ወገኖቼ የምትለዩበት ነገር የለም። ምናልባትም በባሰ መልኩ ኦሮሞዎች አፍራሽ ሃይሎችን ከውስጥም በውጭም ያሉት ጸረ አንድነት የሆኑ የኦሮሞ ምሁራንና ካድሬዎች እንደ መሪዎቹ በመቀበል፤ ኦሮሞዎች እየተጓዛቸሁበት ያለው “አደገኛ ድልድይ” መፈተሽ ይኖርባችሗል የምለውም ለዚህ ነው። ምስኪኑ ኦሮሞ ገበሬ ወደ እማያውቀውና ወደ አልተረዳው ገደል እየተገፋ ነው።

ይህ የተነጠፈላችሁ አደገኛ ድልድይ በቅጡ ካልፈተሻችሁት፤ ለናንተም ሆነ ለመላይቱ አገራችን ከፍተኛ አደጋ አለው። ይህ ደግሞ ሁላችንም እሳት ውስጥ የሚጠብስ አደጋ ነው። በገንጣይ ሃይላት ተገፋፍታችሁ ከመላ ሕዝብ ጋር ያስተሳሰራችሁን ክር ይልቅ “የባንቱስታናዊ የጎሳ ኑሮ” ይበልጠናል ብላችሁ ከበጠሳችሁት “እናንተንም ሆነ” “በኮሎኒያሊሰትነት የተፈረጅነው የተቀረነው ኢትዮጵያዊያን/ኢትዮጵያ” ክሩን መልሰን እንቀጥለው ቢባል ፍጹም የማይቻል ይሆናል። ወደ ሃዘን ጭለማ አብረን አንጓዛለን። አንዴ ወደ ጭለማ ከተገባ ገንጣዮቹ አብረዋችሁ አይገኙም። አፋቸው ከመለፍለፍና በንዚን ከማርከፍከፍ አልፈው በውጭ አገር የተደላደለ ኑሮአቸው ጥለው እናንተ ወደ “ወደቃችሁበት ጭለማ” መጥተው ይረዱናል ብላችሁ አታስቡ።

ካሁኑ ሽሽት ይዘው እየኖሩበት ያለውን “የተንደላቀቀ” የውጭ አገር ህይወታቸው ማስተማሪያ እንዲሆናችሁ ልብ በሉ።እዚህ ያሉት ኦሮሞ ምሁራንና ወጣቶች እንኳ በምሳሌ ብትወስዱዋቸው “ከፓልቶክ ፉከራና ራዲዮን ከፍተው በንዚን ከማርከፍከፍ” አልፈው፤ እያርከፈከፉበት ወደ አለው እናንተ ወደ እምትኖሩበት ጫካና ኑሮ “መጥተው” ለመዋጋትና መስዋዕት ለመሆን ዝግጁነት እንደሌላቸው የምታወቁት እውነታ ነው። ኤርትራዊያን እንኳ፤ ነፃ ለመውጣት አመታት ተዋግተው፤ነፃ ከተባሉ በኋላ አዋጊዎቻቸው፤ ተዋጊዎቹና ምሁራኖቻቸው ‘ከኤርትራ እየሸሹ”፤ የተደላደለ የውጭ ኑሮ መርጠዋል። ከዚህ ትምህርት ውሰዱ። ሞኛችሁን ፈልጉ! በሏቸው እላለሁ። ይህ አጭር ምክር ላብቃ እና ወደ ጉዳያችን እንግባ። 

ግንጣላን ለሚያቀነቅኑ መልስ እነሆ።
 እዚህ ላይ መዘንጋት የሌለው ጉዳይ፤ ታሪክ በምጠቅስበት ጊዜ፤ ታሪክ እንደታሪክነቱ መቅረብ ስላለበት፤ ቅር የሚላቸው ወገኖች ካሉ፤ እኔን ሳይሆን መቀየም ያለባቸው ለዚህ ትንታኔ እና ክርክር እንድንበቃ እየገፋፉን ላሉት የኦሮሞ ተግንጣዮችን እንደሆነ ለመግለጽ እፈልጋለሁ። እነሱ ሲያብዱ አንተስ ማበድ አለበህ ወይ? የሚሉ ሊኖሩ ይችላሉ፡ ነገር ግን መታወቅ ያለበት ቢያንስ ሌላውን ዘመን ትተን ፤ ለ24 አመት እንኳ የተዘረጋው ውሸትና በነዚህ መሰሪ “ፋሺስት ተገንጣይ ኦሮሞዎች” አበራታችነትና መሪነት፤ “አማራን ከኦሮሞ ለማበጣበጥ” የተገነቡ “የጥላቻ ሃውልቶችና  በየሚዚየሙ የተሰበሰቡ “የውሸት ቅሬቶች” እንዲሁም “የክልል-ድምበሮች” በተመለከተ ያለ ብዙ ተቃውሞ “ነገሩን ለማረጋጋት” እየተባለ በብዙ ወገኖች በትዕግስት እንደታለፈ ታውቃላችሁ። ይህ ውሸት ተደጋግሞ ያለ ተቃውሞ በመለቀቁ፤ ዛሬ ወጣት ኦሮሞዎች ውሸቱን እውነት አድርገው በመውሰድ

(አስገራሚ ቢሆንም፤ ወያኔን እና ተገንጣይ ሀይላትን እንቃወማለን የሚሉ አክቲቪስቶች ነን የሚሉ አንዳንድ ወገኖችም ሳይቀሩ፤ይህ ውሸት እውነት ነው ብለው የተቀበሉና፤ ኤርትራ ሄዳችሁ ስለ አማራ ይቅርታ ጠይቁ አንደተባሉ አንዳንድ “ሕሊናቸው የተነጠቁ” ግለሰቦች ባላነሰ መልኩ በመካከለችን የሚገኙ ተቃዋሚዎችም፤ “አማራ”  የተባለ ገዢ ሥርዓት “ኦሮሞውን”  አንደበደለ በማስመሰል ነገር እያምታቱ በየአዳራሹ በተቃዋሚ ጎራ ሆነው የሚዘላብዱና የሚጽፉ ይቅርታ ጠያቂዎችም ጭምር እብዳሉም አንስትም። የኦሮሞ ነገድ የሆነው ባንዳው ንአመን ዘለቀ (የሻዕቢያ ቱልቱላ) “ተገንጣያቹ ወደ ማሃል እየመጡ ነው” እያለ ስለ አንድነት የቆሙትን ሀይሎችን “ባለጌዎች” በሚል ዘለፋ በመዝለፍ ፤ በቅርብ ቀናት ሰሞን ጀሌዎቻቸው በሚሰበሰቡበት “ኢካዴፍ” በተባለ “ፓልቶክ ክፍል” የሰነዘረውን የተግማማ ባንዳዊ  ማጃጃያ ፕሮፓጋንዳውን ልብ በሉ። )

ውሸታቸውንም ለማጠናከር እንዲመቻቸው፤ አማራውን “በጡት ቆራጭነትና በገዢነት እየፈረጁ”፤ ኢትዮጵያ የምትባል አገር “የመቶ ምናምን ዕድሜ ያላት” ምኒሊክ የመሰረትዋት አገር እንደሆነችና “የኬኒያ፤የሶማሊ፤የታንዛኒያ…ኦሮሞዎች “ጋላ” የሚል ስም የሰጧቸው ምኒሊክ እና ሃይለስላሴ እንደሆኑ እና አሁንም የኬኒያ ጋላ ነገዶች ያንን ተቀብለው በዛው እየተጠሩ እንዳሉ በመዋሸት “ኦሮሚያ” የሚባል አገር፤ መንግሥትና ሰንደቃላማ የነበረው እንደነበረና፤ በሗላ ግን “አማራዎች” መጥተው እንደገዙት፤ አሁን ግን ከትግሬ እና ከአማራ “ኮሎኒያሊስቶች/ከኢምፓየር አቢሲኒያ” ነፃ መውጣት እንዳለበት ሰብከዋል።
ያንን ውሸት መሰረት አድርገው፤“ወያኔና ኦነግ” በቅጥፈትና በውሸት፤ አገሪቷን ለመዝረፍ እንዲያመቻቻው፤  
 ተማክረው በከለሉት ኦሮሞ በሚባል “የባንቱስታኒክ ክልል” ያለ መላው ኢትዮጵያ ሕዝብና የታሪክ ግኝት፤የቤተሰብ ትስስር፤ የሰብአዊ ነክ ፤የምጣኔ ዘርፍና የፀጥታ ጉዳይ አዋቂዎች እና ስለ አገሪቱ ጠቅላላ ህልውና ምክክርና ተሳትፎ ሳያደርጉ፤ “ብቻቸውን” በረሃ ላይ “ሴራውን” በመቀየስ “ኦሮሚያ” የተባለ “አዲስ የፈጠራ ክልል/አገር” መስርተው ከወያኔ ቁጥጥር “ነፃ” ለመውጣት የተቻላቸውን ያህል በማድረግ ላይ ናቸው። ወደ ግንጣላ የሚመራቸው የመጀመሪያው ጉዞ ጨርሰውታል። ይህም “ክልል” ይባላል። አሁን እየታየ ያለው “የቡራዩ ኬኛ፤ ሱሉልታ ኬኛ፤ ኦሮሚያ ኬኛ!” መፈክር ፤ ግንጠላውን ለማፋጠን የሚደረግ አዳጋቹ  “ሁለተኛውና የመጨረሻው ጉዞ” ፤የመጀመሪያው እርከን፤ የፍትጊያው እንቅስቃሴ ሂደት ጀምረውታል”።

ከዚህ እንቅስቃሴ በፊት እዛው ክልል ውስጥ ለዘመናት የኖረ ማሕበረሰብም በታጠቁ የኦሮሞ የክልል ወታደሮችና በኦነግ ወታደሮች ጥይትና ሳንጃ፤ የግድያ፤የዘረፋና የመባረር ከፍተኛ ወንጀል እንደተፈጸመበትና፤ በቅርቡም “በደቡብ  ምዕራብ  ሸዋ፣ አመያ ወረዳ በተባለ ወረዳ” በጅምላ ከተቃጠ ሉት የዐማሮች መኖሪያ መንደሮች  አንዱ  ከዚህ በታች የተመለከተው የፎቶ ማስረጃ ይመለከቱ። ዘርዝር ዘገባው ለማወቅ “ሞረሽ ወገኔ የአማራ ድርጅት”ረቡዕ ታኅሣሥ ፲፫ ቀን ፪ሺህ፰ ዓ.ም. ያወጣውን
 አንድነት ከማን ጋር? ሚለውን ሃተታውን ይመልከቱ። (ምንጭ፦ የቀለም ቀንድ ጋዜጣ ቁጥር 22 ቅጽ 3 ታሕሣሥ 12 ቀን 2008 ዓ.ም.)   
Amhara land burned by Oromo secessionist thugs
ይህ የምታዩት የፈቶ ማስረጃ የተቃጠለ መንደር የአማራ ገበሬዎች መንደር ነው። በአመያ ወረዳ በሚገኙ ሦስት ቀበሌዎች፦ ማለትም «አብቤ መድኃኒዓለም»፣ «ኩኖ ቁሊት (ቀርሳ ቁሊት)» እና «መሪ መገሪ (ባሬዳ)» በተሰኙት ነዋሪ የነበሩ የዐማራ ነገድ ተወላጆች ንብረት ውስጥ 1,000(አንድ ሺህ) ቤቶች ማጀት በጎረሰ፣ ደጃፍ በመለሰ ያለ የሌለ ንብረታቸው ከነቤቶቹ ተቃጥለው ወደ አመድነት ተቀይረዋል። በእያንዳንዱ የቀበሌዋ ነዋሪ ዐማራ ከ70,000 (ሰባ ሺ) እስከ 1,000,000 (አንድ ሚሊዮን) ብር የሚገመት በርበሬ ተቃጥሏል” (አባሪ ፎቶግራፍ ይመልከቱ)።

ይህ አማራ እየተገፋ ባለበት ትኩስ የግፍ ዜና ፤ያውም “በባንቱስታኒክ ኦሮሞዎች” ሲፈጸም፤ የወያኔ ተቃዋሚ ሃይሎች ነን የሚሉ በሺዎቹ የሚቆጠሩ ውጭ አገርና ውስጥ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ተቃዋሚ ሃይሎች፤ ቡራኬአቸውና ድጋፋቸው የለገሱት እንዲሁም ጮክ ብለው እየጮሁላቸው ያሉት ለቡራዩ ኬኛ! ፤ለሱሉለታ ኬኛ!፤ለኦሮሚያ ኬኛ! “ባንቱስታኒክ” ፈካሪዎች መሆኑን ልባችንን አድምቶታል።

ይህ ሳንነጋገርበት ለ24 አመት በቸልተኝነት ዝም እየተባለ፤ ዛሬ “ወጣት ኦሮሞዎች” ከገንጣይና አስገንጣይ ክፍሎች የቀሰሙትን የ24 አመት ቅስቀሳ፤ ”ቡራየ፤ኬኛ፤ ሰበታ ኬኛ…….ኦሮሚያ ኬኛ….” ወደ እሚለው የግንጠላ መፈክር ደርሰዋል። አሁን ዝምታችን መስበር የግድ ነው!!!

ይህ ደግሞ በወያኔ ዘመን የተወለደ “ወጣት ኦሮሞ” ይህን “የፈጠራ ታሪክና የኤትኒክ ፌደራሊዝም አደገኛ አወቃቀር”  ከህጻንነቱ ጀምሮ እየተኮተኮተ “እውነትነት ያለውና ጤነኛ አስተዳዳር መስሎት” ያለ ምንም “ሕሊናዊ ምርመራ” አምኖ በመቀበሉ፤ በየታላላቅ የትምህርት ተቋማት ሳይቀር ፡ “ ኢሚፓየር ኢትዮጵያ” “ሳብጁጌሽን” የሚሉ ቃላቶችን በመጠቀም በግልጽ ሳይሸሽጉ፤ ሳያፍሩና ሳይሸማቀቁ “በዩቱብ አውድዮ እና ቲቪ ሚዲያዎች” የለጠፉት የተለያዩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኦሮሞዎች ተቃውሞ ተመልከቱ። አምና በተለቀቀው አውዲዮ ላይ ወደ መጨረሻ ገደማ የሚያሰሙትን መፈክር አድምጡ፡- የተቀረጸውን ስታደምጡ፤ ወጣቱ እውነትም ነጋሪ በማጥት ሕብረተሰቡም ሆነ እራሱን ይዞ ገደል እየገባ መሆኑን ማየት ትችላላችሁ።

እነኚህ አፍላ የኦሮሞ ወጣቶች ለብዙ ዘመናት “አፍሪካኖችና ጃማይካኖች” እንደ “ብሌን ዓይናቸው” የሚመለከትዋትን ሰንደቃላማችን “አያውቋትም”።  “ኦነጎች የቀየሱላቸው “የዋርካ ዛፍ ምስል” ያለበት እና ሌላው ደግሞ “በእስለማዊ እና በዓረብ አገሮች፡የሚውለበለቡ ቀለማት ያሉበት ባንዴራ” ነው አሁን ወጣቶቹ የሚያውለበልቡት (አገርም ውስጥም/ ውጭም)።

ችግሩ እርግጥ አገር ከመሰረቱ በሗላ ቀርቶ፤ ገና ኦሮሞዎቹ አገር ሳይመሰርቱ ዛሬ “እርስ በርስ” በመናከስ ኤርትራ እና እዚህ ሜኔሶታ/አሜሪካ ውስጥ ፍርድ ቤት ድረስ እየተካሰሱ “እኔ ነኝ ሕጋዊው ኦነግ”፤ “መሪያችን እገሌ እንጂ እገሌ አይደለም” “ስትፈልጉ እናንተ ስማችሁ ቀይሩ እንጂ ኦነግ እኛ ነን” ወዘተ…ወዘተ…በሚል አታካራ ገብተው “እየተራኮቱ” ናቸው። አገር ቢመሰርቱ ካሁን በፊት እንደገለጽኩት “ኦሮሞ እስላም/ከኦሮሞ አርቶዶክስ/ “አሮሞ ፕሮቶስታን/ ከኦሮሞ ኦርቶዶክስ” ኦሮሞ እስላም ከሁሉም እምነት፤ ሁሉም አምነቶች ከዋቆ፤ ዋቆ ከወዘተ…ካፒታሊዝም/ሊበራሊዝም/ገዳኢዝም/ሶሺያሊዝም/ካሊፋ-ኢዝም/ሸሪዓ-ኢዝም… ወዘተ.. ወዘተ…ወዘተ… እየተናከሱ “ምድሪቷ የአልሸባብ ሶማሌ ዓይነት ኦሮሚያ” እንደሚያደርጓት ሳይታለም የተፈታ ነው።

ስርዓቱም፤ ስፓኒሾች እንደሚሉት “ley de la calle” እንግሊዞቹ “mob rule” አማራዎቹ “ወሮ በላ ስርዓት” የሚሉት። በሳይንሳዊ የፖለቲካ ስሙ “ኮሎክቲቪዝም/ፋሺዝም/ማብ-ሩል/ማፍዮኢዝም/ኦሊጋርኪ” የሚባለው። በእነ ጃዋር “የትንቢተ ስርዓታቸው” ፖሊሲ “የሜንጫ ስርዓት” የሚሉት ማለት ነው።

የኦሮሞ ፋሺዝም አዙሪት ምን ማለት ነው? ፋሺዝምስ ምን ማለት ነው?

በውስጡ ባሉትና በዙርያው ባሉ ማሕበረሰብ ክፍሎች የራሱን ጎሳ የበላይነት (ኤትኒክ ሱፕረማሲ ‘ሴት/ንብረት/መሬት/ሥልጣን/ሃይማኖት…’) ለመንጠቅና ለማስፈን፤ ያንን የበላይነት እውን ለማድረግ ከመዋጋት አልፎ፤ ለማመን እና ለማየት እጅግ በሚዘገንን ጨካኝ ጭፍጨፋ’ዝርፊያና አመጽ” በሌሎቹና እሱን በሚቃወሙት የራሱ ጎሳዎች ሳይቀር “ሰይፍ በመምዘዝ” “ፀጥ” በማሰኘት ሕብረተሰቡን ሽብር ውስጥ አስገብቶ በፍርሃት የሚገዛ፤የሚያርበደብድ፤ሰላም የሚነሳ፤ ሁውከተኛ የብጥብጥ ስርዓት ነው።
የዘመኑ ፋሺዝም ብዙ ትንታኔዎችን ቢሩትም በቃላሉ “የሰው ልጅ ፤ከግለሰብ ነፃነት እየወጣ፤ በሕብረት መተዳዳር ከጀመረ ጀምሮ “ጀነሪክ ፋሺዝም” የሚሉት፤ አገርን በማውደምና መንደሮችን ማቃጠል፤ጭካኔን  ምርኩዝ እያደረገ፤ እረፍት የሚነሳ፤ በደም ጥራት የሚጓዝና የሚያስተዳድር፤ ጥቂት ወረበሎች የሚፈጥሩትና የሚመሩት የሽብር ስርዓት ነው፤ ፋሺዝም ማለት!”     

ኦሮሞዎች እንዲህ ዓይነት ጭካኔና ስርዓት ፈጽመዋል? የሚል ጥያቄ ሊቀርብ ይችላል። መልሱ፦ “አዎን፤ በሚገባ!!”። የጥንት ኦሮሞዎች ድሮ “ጋላ ሲባሉ የነበሩ ነገዶች፤ መንደር፤ሕዝብ፤አገር አውድመዋል። ይህንን ሲፈጽሙ እጅግ ዘግናኝ እርምጃ እየወሰዱ ነበር የፈጸሙት። “ዲሞክራሲ” ነበር እያሉ በውሸት የዛሬ የተማሩ ኦሮሞዎች የሚያሞግሱት “የገዳ ስርዓት” እንኳ ሳይቀር ስትመለከቱ “እጅግ ማመን የሚያዳግት” ባሕሪዎች ታይተውበታል። ይህ ደግሞ በጽሁፍ መረጃ “ኦሮሞዎች ወደ መሃል አገር፤ወደ “ከፋ” (እርግጥ ከፋ ውስጥ ጥቂት ነገዶች ከጋላዎቹ ጭፍጨፋ ድነዋል፤ለዚህ ምክንያት “የደኑ ብዛት” የኦሮሞዎቹ ከብቶች ማስገባት ወደ ውስጥ ሰርስረው መዝለው ስላቃታቸው፤ ወደ ውስጥ ደን ገብተው ነዋሪውን መጨፍጨፍ አልቻሉምና ከመአቱ የዳኑ ጎሳዎች እንደነበሩ እንደዳኑ፤ታሪኩን ያጠኑ ተመራማሪዎች ይገልጻሉ።) እንዲሁም “ጅማ”፤ ሸዋ፤ትግሬ፤ወሎ፤ጎጃም ጎንደር……ሲስፋፉ በወቅቱ የተፈጸመ ድርጊት፤ ፋሺስታዊ ዘግናኝ ጭፍጨፋና ዘረፋ ተካሂዷል።

ይህ አሁን “ኦሮሚያ ኬኛ” እያሉ ወጣቶች የሚዘምሩት መፈክር፤ በዘረፋና ባሰቃቂ ጭፍጨፋ የድሮ ጋላዎች ከነባር ኗሪዎች የነጠቁት መሬት እንደነበር በግልጽ ማወቅ ይኖርባቸዋል። በወቅቱ እንዲህ ያለ ፈጣን እና ባጭር ወቅት ወደ ኢትዮጵያ የተስፋፉበት ምክንያት ፤በወቅቱ” ኢትዮጵያ “በግራኝ አህመድ” ጂሃዳዊ ወረራ ምክንያት ሃይሏ ተዳክሞ ሕዝቧ አልቆና በጦርነቱ ደክሞ፤ ታርዞና መዋጋት ሰልችቶት ስለነበር፤ ኦሮሞዎቹ ከታች ከኢትዮጵያ ድምብር ገሰግሰው በመምጣት አጋጣሚውን ተጠቅመው ሰፊውን መሬት ከኗሪው እየነጠቁ ዛሬ ለራሳቸው አድርገውታል። ሃቁ ይህ ነው።

ከወረራው በፊትና በወረራው ወቅት የነበሩ ግዛቶችና “የቦታ ስሞች” በውጭ አገር ጎብኚዎች በወቅቱ የተነሱ የካርታ ምስክሮች ዛሬም በሊቃውንት ቤቶችና መጽሐፍት ቤቶች ይገኛሉ። እነሱ ማን ምን ይባል እንደነበር ቁልጭ አድርገው ይነግሩናል። የተረሳው ፋሺስታዊ አዙሪት ነብስ ዘርቶ እንደገና ሌላ ዘላቂ ‘የሁውከት” አዙሪት ከመደገሙ “ግልፅ ግልፁን” በመነጋጋር እንዲህ ማዝገም ስለሌለበት ዝምታችን መስበር የግድ ነው!!! አማራው ሕዝብ “በባንቱስታኒክ ኦሮሞዎች” ቤቱና ህይወቱ እየወደመ “ወደ መሃል እየመጡ ነው” “ግንጠላን ትተዋል” የሚሉንን ደላሎችና ከጂዎችን ማመን አቁሙ! (በዚህ በሰሜን ክፍላችን ደግሞ የወልቃይት አማራ ወገኖቻችንን “በትግሬ ፋሺዝም ተስፋፊ አይዲኦሎጂ” ምክንያት እየደረሰባቸውና የገጠማቸው ፋሺስታዊ የዘር ማጥፋት በትልቁ ሳይረሳ ማለቴ ነው!!!!)

በ15ኛው ክ/ዘመን አካባቢ የታየ አገርና መንደርን ማውደም፤ ዛሬ በቃ ማለት ጊዜው ነው! ጥንት በኦሮሞ ከብት አርቢ ወራሪዎች “በአማራ፤ በጉራጌ፤በሐረሬ፤በሲዳማ፤በጋሞ…በወላይታ…ወዘተ…ኗሪዎች ግፍ ፈጽመዋል።  በወቅቱ የነበሩ ጅማ “ሙርጡላ ማርያም” (?ከተሳሳትኩ አርሙኝ) ገዳም  ውስጥ የነበሩ ሊቃውንት (ለምሳሌ አባ ባሕርይ) የመሳሰሉ በዓይናቸው ያዩት “ፋሺስታዊ ዘግናኝ ድርጊት” በጽሑፍ መዝግበው ትተውልናል። በነገራችን ላይ መነኩሴው አባ ባሕርይ የኦሮሞን ባሕል፤ታሪክ፤ነገድ አመጣጥ/ትውለደ ሐረግ… ከማንኛውም ኦሮሞ ነኝ ባይ እንደሳቸው አውጣጥቶ በንፁር የዘገበ የለም። ለኦሮሞውና ለተቀረነው ትውልዶች መዝግብው የተውለትና ያስተማሩት ባለውለታ ናቸው። በኦሮሞዎቹ የታሪክ ምሁራን በእነ ዶ/ር መሐመድ አህመድ ፧ ሳይቀሩ የአባ ባሕሪ የኦሮሞዎች ትውልደ ሐረግ ዝርዝር/ጥናት አምነው በአክብሮት የተቀበሉት ሃቅ ዩሆነ ሰነድ ነው።

ባለውለታ ናቸው የምልበትም ምክንያቱም “ጋላዎቹም” ሆኑ የዛሬዎቹ “ኦሮሞዎች” የንግግር እንጂ “የጽሑፍ ሥልጣኔ ቋንቋ” ስለሌላቸው ለመጀመሪያ ጊዜ በግዕዝ ጽሑፍ ጽፈው “የጋላ ትውለድና ክፍሎች፤ እና አስተዳዳር” በሚገርም አተናተን ዘርዝረው ስለተውላቸው ብዙ ኦሮሞዎችና የውጭ ምሁራን/ተመራማሪዎች ያንን የመጀመሪያና ብቸኛ ትምህርትና፤የዓይን ምስክርነት ሰነድ ምንጭ ሰለሆነ ኦሮሞዎች ዛሬ ሐረጋቸው እየቆጠሩ ያሉት እሳቸው ሰንደው በተውላቸው ሰነድ ነው።

 ሆኖም እሱም (ዶ/ር መሃመድ አሕመድ) ሆነ የመሳሰሉ ተገንጣኢ ኦሮሞ ምሁራን “ያቺን የሃይማኖት ችግራቸውና ተገንጣይነት” ሉጓም ሆና ስለምትይዛቸው፤ ሙሉ በሙሉ አባ ባሕሪን አያመሰግኗቸውም። ስለሆነም ተገንጣዮቹ የአባ ባሕርይ የዓይን ምስክርነት መፋቅ ስለማይቻላቸው ለግንጣላ ታሪክ አልመች ስለምትል የሳቸውን እና ሌሎችን “የሃገር ውስጥ ምንጮችን አይቀበሉም”። ካለመቀበል አልፈውም “ያጥላላሉ”።የደብተራ ጥናትም ሲሉ ያጥላሉታል። ግብዝነት አደጋ ነው፤ ይባል የለ!

ክቡር ፕሮፌሰር ጌታቸው ሃይሌ እንዲህ  ይላሉ፤

   “የሀገር ውስጥ ምንጮችን የሚያጥላሉ ዘመናዊ ታሪክ ጸሐፊዎች ካሉ ባይመዘገብ የሚወዱት ስለተመዘገበ ነው….።”(ጌታቸው ሃይሌ፤  ገጽ 31 የአባ ባሕርይ ድርሰቶች፤ ኦሮሞዎችን ከሚመለከቱ ሌሎች ሰነዶች ጋር)። እውነት ነው። ይህ ወርቃማ አገላለጽ፤ ከሺህ ገጽ መጽሐፍ በበለጠ ከፍተኛ ትርጉም እና ቀላል አገላልጽ የያዘች ዓረፍተነገር ስለሆነች፤ ምን ማለት እንደሆነ ሁላችሁም በትኩረት መገንዘብ አለባችሁ።  ባይመዘገብ የሚወዱት ክፍሎች እነማን ናቸው? በውሸት የሚጓዙ የጋላ ታሪክ ባይመዘግብ የሚመርጡ እንደ እነ ኦነጎች የመሳሰሉ ፋሺስት ክፍሎች ናቸው።  በወቅቱ “ጋላ” ተብለው ሲጠሩ የነበሩት “የኛ ዘሮች ናቸው” የሚሏቸው የዛሬዎቹ ኦሮሞ ምሁራን (ጋላዎቹ እርግጥ ከወረራ በሗላ ከተቀረነው ኢትዮጵያዊያን በደም በስጋ ስለተዋሃዱ፤ እነ አባ ባሕርይ በነበሩበት ጊዜ የነበሩ ንፁሕ “ጋሎች” አይደሉም የዛሬ ኦሮሞ ነን እያሉ እየነገሩን ያሉት “ኦሮሞዎች”።

ምክንያቱም አሁን ያሉት “ኦሮሞ ነን” የሚሉት “ከተቀረነው ጋር” ከተደበላለቁ በሗላ የመጣ ድብልቅ/ክልስ የጋላዎቹ ትውልደ ሐረግ መሆኑን አንባቢዎቼ ልብ አንድትሉ እፈልጋለሁ። ምናልባትም ብዙዎቹ ኦሮሚኛ ስለሚናገሩ ከዘመናት የመደባለቅ ሂደት በላ ኦሮምኛ ተናጋሪ ይሁኑ እንጂ “ኦሮሞዎች” ያልሆኑ በሚሊዮኖች እንደሚቆጠሩ እርግጠኛ ነኝ። ትግሬዎች በመባል እየተጠራን ያለን የዛሬዎቹ ትግሬዎች “የድሮ አክሱማዊያን” “ያልተደባለቀን ንጹሕ “አክሱማዊያን”/”አጋአዚያን”…ማለት የዛሬዎቹ ትግሬዎች ነን ብለን በልበ ሙሉነት መናገር አንደማንችል ሁሉ (የሚያገናኛቸው ነገርና ሐረግ ቢኖርም የዛሬ ትግሬዎች የድሮ አክሱሞች ነን ብለን 100/100 እርግጠኛ ልንሆን አንችልም) ፤ ኦሮሞም የድሮዎቹ ንፁሃን ጋላዎች፤ የዛሬዎቹ “ክልስ ኦሮሞዎች” “ንፁህ /ያልተደባለቅን ጋላዎች/ኦሮሞዎች፤ ነን” ቢሉም “ከስሜትና ከቅዠት” የተነሳ “ድንቁርና እና ፋሺስታዊ ስሜት ያሰከረው  ንፁህ ደም” ፍለጋ ባሻገር ከመሆን ዘልሎ ሊሄድ አይችልም። ታሪክ ነው እየተነጋገርን ያለነውና ታሪከ እንደ ታሪኩ እንድትረዱልኝ እፈልጋለሁ። ግልፅ ግልፁን! አለ ወዳጄ ጋዜጠኛው ድምጸ መረዋው “ኢሳያስ ልሳኑ”!

የጀመርኩት ጭብጥ ከመቀጠሌ በፊት ግን ይህ “ጋላ” የሚባል ነገድ ዛሬ በኬኒያ በሶማሌ እና በመሳሰሉ እንዳሉ ይታወቃል። የኛዎቹ “ኦሮሚያ ነን” የሚሉ አስገራሚና አስቂኝ ኦሮሞ ተገንጣዮች “ጋላ” የሚለው ስያሜ “ስድብ” ነው ብሎ፡የነገራቸው ማን እንደሆነ እና ስድብ ነው የሚል የትኛው መጽሐፍ  እንዳገኙት ባናወቅም፤ “ጋላ” የሚለው ትከክለኛ የተከበረ የድሮ የጋላ ነገድ ስም (የተከበሩ ክቡራን ወላጆቻቸው “የጋሊቷ ልጅ” እያሉ ወላጆቻቸው በቀና እውነተኛ ኢትዮጵያዊ መንፈስ ሲፎክሩበት አንዳልነበረ ሁሉ) ነውር ነው/ደሮጋቶሪ ነው//አስጸያፊ ስም ነው” ፤ እያሉ ብዙ ኦሮሞዎች በፈጠራ ፕሮፓጋንዳ  ተታልለው በብዛት ተቀብለውታል።የለወጡትም በደረግ ጊዜ ነው። ደርግ ሲመጣ፤ የደርግ ስርዓት የመሩት ኦሮሞዎች ስለነበሩ” ያንን ስም ወደ ሁለተኛው ስም በቀላሉ ወደ ሁለተኛ ስማቸው ወደ “ኦሮሞነት” እንዲለወጥ በማድረግ፤ “ጋላ የሚለው ሌላኛው “ከጥንት ጀምሮ እስከ ኬኒያ፤ ሶማሌ… ድረስ ሲጠራበት የነበረ ሕጋዊ የነገዱ አጠራር” “ስድብ” ነው፤ ብለው “ብረይን ኮንትሮል ፍሪኮቹ” አስቁመውታል። ይህ ሲሆን፤ በውሸት ወጣቱንና ሕዝቡን አሳመኑት።

 ይህንን በሚመለከት ከኢትዮጵያ ድምበር አልፈው ሌላ አገር ድረስ፤ ማለትም ኬኒያ ድረስ ተሻግረው ጋላ የሚለው ስያሜአቸው ወደ ኦሮሞ እንዲለዉጡ “ሌላ አገር” የሚኖረውን ሰላማዊው “የጋላ” ነገድ “ኦሮሞ ተብሎ አንዲጠራ ኢትዮጵያን አገራችንን “በጥብጠው”፤ በሰው አገር ድረስ ተሻግረው ለማበጣበጥና “ሕጋዊ የነገዳቸውን ስማቸውን” ለማስቀየር የጻፉትን ማመልከቻ ከዚህ በታች ያለውን ለማስረጃ ባጭሩ ተመልከቱልኝና ወደ እዛው እንቀጥላለን።
ባጭሩ አንዲህ ይላል፦
FROM: OROMO REFUGEE TEACHERS, THE OROMO
REFUGEE COMMUNITY LEADERS, KENYA.
December 20, 2013
TO: KENYAN EDUCATION MINISTRY
NAIROBI, KENYA.
P.O.BOX 30040-00100,

REQUEST TO REMOVE AND BAN THE USAGE OF TERM GALLA IN KENYA.
We, the Oromo teachers from Oromo refugee community in Kenya, are writing to you to bring into your attention the negative impact of the usage of a derogative and abusive word Galla to identify the Oromo in the text books of social studies used in primary and secondary education in Kenya. It is wrong terminology usage against Oromo identity which is unjustifiable historically to educate the nation.

In fact the people identify themselves as Oromo and their language as Afan Oromo, which is the correct terminology usage.
Although the Oromo nation is the second largest in Africa, it is forgotten by or still unknown to the majority of the world today, even the name Oromo. This is partly because of the colonial Ethiopian Emperors Menelik and Haile Sellesie and their successors which continued until today to treat Oromo with utmost cruelty due to their resistance to colony. The Oromo people endured a stagnant existence where ignorance and famine have been coupled with ruthless oppression, subjugation, and exploitation in all spheres of  life and above all extermination. Everything possible was done to destroy Oromo identity, language, culture, custom, tradition, name and origin.

In short, the colonizers maintained the general policy of genocide against the Oromo and use the term Galla to dehumanize and victimize Oromo and to destroy their identity and language. Such insulting name to the nation were abolished and eradicated by oppressed nation of 1974 revolution in Ethiopia and the usage of the term Galla is officially banned.

And sadly, to deny the Oromo the right to identity and as if this is not enough and to add insults to injuries, the term Galla is in use interchangeably for Oromo in text books of social studies used for education system in Kenya. To cite few books; the Evolution World, a History and Government course Form 1, by Oxford new edition 2010, under the topic Cushitic…………………the  Cushites group comprised of……….Galla(Oromo)………>> on page 78 and under the topic  Borana…………..the Boran are branch the Oromo or Galla people……….they speak Cushitic language called Galligna……on page 81 and also in other course book-Milestone in History and Government Form 1 by Longhorn publishers…..reprinted in 2010 under the topic Eastern Cushitic comprise of the Elmolo, Gabra, Oromo(Galla)…..on page 40. And also in some many other course books published by Kenya Literature Bureau.
Hence, as we clearly tried to indicate above, such wrong terminology usage for Oromo identity  is illegal and it allows subjugation and victimization of Oromo children and people at large,infact it is clear violation of basic human Right Declaration of children’s basic right to good education and right to identify of Oromo nation.And this should not be allowed to continue by free and Democratic nation of Kenya and Africa.

Therefore,kindly we the Oromo refugees in Kenya would like to request the honourable education office and concerned authorities of institutions to totally remove the use of the term  Galla from educational books and further ban the usage of such abusive term against people in any written or oral form in Kenya.
THANKS FOR YOUR UNDERSTANDING AND LEGAL ACTION!
YOURS TRULY,
THE OROMO REFUGEE TEACHERS
THE OROMO REFUGEE COMMUNITY LEADERS
KENYA

ክቡራን አንባቢዎቼ ሆይ!
ይህ ጉደኛ ደብዳቤ ተጻፈው ከሁለት አመት በፊት ነው ወደ 2013 አካባቢ ‘በፈረንጅ’። አስገራሚ የሚያደርገው ደግሞ፤ “ጋላ” የሚለው ስያሜ የሰጡት አፄ ምኒሊክና አፄ ሃይለስላሴ በማስመሰል፤ ኬኒያ ፤ሶማሊ፤ኢትዮጵያ፤ ሌሎች አገሮችም ካሉ፤ እራሳቸው ይዘርዝሩት፤…… ሁለቱ ንጉሦች ጋላ ብለው የሰየሙዋቸው ይመስል፤ በውሸት እየከሰሱ፤ ይህ ኦሮሞ የተባለ የነገድ ስም “ጋላ” እንደተባለ እና “ሰፊው” የኦሮሞ ሕዝብ (ሰፊ፤ትንሽ፤ ትልቅ፤ማይኖሪቲ/ማጆሪቴ የሚለው የትምክህት/ኢጎ/ ትንታኔ ምን ማለት እንደሆነ ባይገባኝም) “በዓለም ሕዝብ” እንደ “አገር” አንዳይታወቅ ያደረጉት እነኚህ ሁለት ንጉሦች መሆናቸውን ባስቂኝ ደብዳቤአቸው ገልጸዋል።

እነኚህ ተገንጣያችና ፋሺስቶች እያመለከቱ ያሉት “ለኬኒያ” ነው። ኬኒያ ደግሞ ኢትዮጵያ አይደለም። ምኒሊክም ሆኑ ተፈሪ አልገዙትም፤ ስለሆነም ጋላ ብለው ነገዱን አልሰየሙትም። ጋላ ማለት ነውር ነው ብለው የነገድ ስም ለማስቀየርና ብጥብጥ ለማስነሳት እየጣሩ ያሉት፤ ባዕድ አገር ሆነው ነው። እየነሩት ያሉትም በጥገኛነት ነው። የኬኒያ መንግሥት እነዚህ ሰዎች አያውቃቸውም; ዜጎቹ ሳይሆኑ ስደተኞች ናቸው፤፡  እዛው ኬኒያ ያሉ የጋላ ነገዶችም እነኚህ ነገሥታት እንደገዟቸው አስመስለው ነው ስማቸው በዓለም እንዳይጠራ አድርገው እነዚህ ነገሥታትን እየከሰሱዋቸው ያሉት። ጋላ የሚለው ስም አማራዎች ሰጡን ሲሉን የነበረው፤ አሁን ደግሞ ኬኒያ ያሉት አውነተኛ ጋሎችን “አማራ” የሚባል ገዢ  (ምናልባትም በፋሺስቶቹና ተገንጣዬቹ ውንጀላ ‘በምኒሊክ/በሃይለስላሴ’) እንደተሰጠ አስመስለው ነው “ስለ የኬኒያ ጋላ ነገዶች” ተቆርቁረው “ኦሮሞ እንዲባሉ” ነው ለኬኒያ የትምህርት ሚኒስትር ደብዳቤ የጻፉት።

ይህንን ዕብደት ስትመለከቱ በምን ቃላት ልትገልጹት ትችላላችሁ፤ “እናንተየ!!”? በስደት እየኖሩ በሰው ጋር ሄደው የሌላ አገርን ነገድ ስም ይቀየር ብለው ሲሟገቱና የዛው አካባቢ “ነገደ ጋላ” ባላሰበውና ባላስተነተነው ዓላማ “ለማቃዠትና ለማነሳሳት” ሞመከራቸው፡ እነኚህ ተገንጣዮች፤ ለመሆኑ ድምበር፤ ዜጋ፤መንግሥትና ስርዓት እንዲሁም “ስደተኛ” ማለት ምን ማለት አንደሆነ ያወቃሉ? ወይስ የኬኒያ ጋላዎችቹንም ኢትዮጵያዊያኑን ኦሮሞዎች እንዳሳሳትዋቸው ጭምር የኬኒያዎችንም እንዲሁ እያሳሳቱ “ከኬኒያ ገንጥለው” ኦሮሚያ ለምትባል አዲስ የቅዠትና የፋሺስቶች  ቅርምት ሊጨምሯቸው ዕቅድ ስላላቸው?

እነዚህ ክፍሎች “የዜጋነትና የድምበር ትርጉም ስለማይገባቸው” ድምበር እየተሻገሩ፤ አንዲህ ያለ ብጥብጥ እየፈጠሩ ስለታዘቡ መሰለኝ ባለፈው ወር፤ በኢትዮጵያና በኬኒያ የፀታ የጋራ ስምምነት ሲያደርጉ “ኦ ኤል ኤፍ” የተባለ “thug” “ወረበላ” ሲሉ የኬኒያ ጋዜጦች፤ቃል በቃሉ፤“thug” “ወረበላ” ሲሉ ጽፈውባቸዋል። ኬኒያኖቹ እራሳቸው በደምብ አድርገው የዚህ ወረበላ /mob ምንነት ስለሚያውቁ፤ የኬኒያ ጋሎችን ሰብከው ኬኒያንም ለማበጣበጥ፤ እስከ ታንዛኒያ ድረስ እየሰበኩ እንደነበረ አንድ ሰነድ ሳነብ አጅግ ገርሞኛል። ይህ ዕብደት ከማለት አልፋችሁ ከዚህ የከፋ ሌላ ቃላት ካላችሁ እባካችሁ ፈልጋችሁ በክፍተቱ ሙሉት።

እንግዲህ ይህን ላሳያችሁ የፈለግኩት ውሸታሞቹ ወደ ኬኒያ ድረስ ማመልክቻ እየጻፉ ኬኒያዎችንም “ጋላ” አይደላችሁም” ኦሮሞ ነው የምትባሉት እያሉ የስደተኛ ህይታቸው የኬኒያን ሕግና ስርዓተ ትምሕርት አክብረው ህይወታቸው እንዳይገፉ፤ አገራቸው ያልሆነውን ኬኒያን ሌላ ብጥብጥ ለመፍጠር የኬኒያ ዜጎች ምንም ሳይሰማቸው፤ ስለ እነሱ አፈቀላጤ ሆነው “ጋላ” የሚለው የጥንቱ እውነተኛ የነገድ ስም “ኦሮሞ” እንዲባል እዛም በስደት እየኖሩ በህፃናት ሕሊና ላይ ጥርጣሬ እንዲያድርባቸው “ሁውከትና የራስ የበታችነት ስሜት” ለመፍጠር፤ ድምበር ተሻግረው እንኳ ሳይቀር የሚሰሩት ባሕርይ ለመግለጽ ነው መረጃው የጠቀስኩት። የኬኒያ የጋላ ነገዶች ከተቀረው የኬኒያ ሕዝብ ጋር በስም ለውጥና አጠራር ሕዝብን ከሕዝብ የማጋጨት ባሕሪያቸው ድምበር ሸገርም አልተዋቸውም።

እሺ ኢትዮጵያ ያሉትንስ “አማራዎች/ምኒሊክ/ሃይለስላሴ…..” ጋላ ብለው ስሙን ሰጡን ይበሉ፤ እሺ፤ ኬኒያና ሶማሌ ያሉትንስ ስማቸው ካልሆነ ጋላ ብሎ ማን ሰየማቸው? ምኒሊክ/ሃይለስላሴ/አማራ? በየት በየት ተሻግረው? አረ እባካችሁ እነኚህ ሀፍረተቢሶች በምን ቃላት አንደምገልጻቸው አሁንስ እየጨነቀኝ ነው!?
እንግዲህ ጋላ የሚባል ስም ለምን እንዳስጠላቸው፤ እራሳቸው ከሚፈለስፉት ቅዠት በቀር ሌላ መረጃ የላቸውም። EEDN በኖርኩበት የውይይት መድረክ ውስጥ ይህንን ለብዙ አማታት እንዲያብራሩልኝ ፤ምንጫቸውም እንዲያቀርቡ ጠይቄአቸው፤ ከመሪዎቹም ቢሆን አንድም መልስ ለመስጠት አልቻለም። ዛሬም “ድፈን፤ድፈን ነው መልሳቸው”። አሳዛኙ ግን፤ የዚህ ነገድ ክፍሎች በራሳቸው ላይ “የበታችነት ስሜት የሚፈጥሩ የአሮሞ ምሁራን ግን፤ ከዚህ ሊማሩ አልቻሉም። ኦሮሞ የሚለው አንዳንዱ “ሖሮሞ” “ዎሮሞ” “ሃራሙያ” እያለ ገበሬው ስለሚጠራው እሱንም አስጠልቶናል እና ‘ኦሮሞ’ የሚለው ትትን “ሌላ ስም ለውጠናል” ይሉን ይሆናል። ማን ያውቃል! ከጋሊቷ ልጅ ኢትዮጵያዊ ፉከራ ፤ ወደ ኦሮሚቷ ልጅ ከዚያ ደግሞ “ነገ ሌላ ስም ሊፈጥሩ ይሆናል (ልክ እንደ ተለያዩ ባንዳራዎቻቸው፤ መጠሪያቸውም እንደዚሁ)።ማን ያውቃል። ጠርጥር! ያለ ማን ነው፤አንድ ፀሐፊ አንቢቤአለሁ፤ ጥሩ አባባል; ጠርጥር!

ወደ ርዕሳችን እንመለስ።ኢትዮጵያ ሳይሆን አቢሲኒያ ነው የሚሉን። እኛ ኦሮሞዎች በዲሞክራሲ እንተዳደር ነበር፤ ግን አቢሲኒያዎች/ምንሊክ “የቅኝ ተገዢአቸው አደረጉን” ገዙን ይሉናል። አንድ ባንድ እንመለከታለን።፡የጋላ ነገድ ዲሞክራሲ ነበር እያሉ ይዋሻሉ። ስሙም “የጋዳ ሥርዓት” ይባላል ይላሉ። እኔ ግን “ፕሪሚቲቭ/ፐሪማቱር ፋሺዝም” እለዋለሁ። በዝርዝር ባጭሩ እንመለከተዋለን። የዛሬዎቹ “የግንጠላ ጠበቃዎችና፤ የኦሮሞ ባንቱስታን የክልል አስተዳዳር አቀንቃኞች” የሆኑ የኦሮሞ ፋሺስቶች ባሕሪ መነሻ የሚያደርጉት፤ “ከዚያ ከፕሪማቱር የገዳ ፋሺዝም ዘመን የመነጨ” ባሕሪ ነው። ያንን ያከብሩታል። ለኦሮሞ ህልውናም ዛሬ እያሳዩን ያለውን “የቦታ ሄጂመኒ/ነጠቃ/ወረራ/” መሰረታዊ መመሪያቸው ሲሆን፤ ከዚያ ዘመን ጀምሮ ወደ ሰፊዋ ኢትዮጵያ፤ ከዚያም ኦሮሞዎች “ደርግ የሚል ወታደራዊ ስርዓት መስርተውና ተሰግስገው ኢትዮጵያን ሲያስተዳድሩ” ያሳዩት ፋሺስታዊ ስነምግባር እና ከዚያም ሲወድቁ፤ ያደራጁትን “ኦነግ” የተባለው ገንጣይና እጅግ “ፋሺስታዊ” የሆነ ወንጀለኛ ድርጅት ከወያኔ ጋር ሰምሮ፤ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አማራዎችና ኦሮሞ ወታደሮች በትኖ፤ ለልመና ዳርጎ፤ የቀሩትንም ጨፍጭፎ፤ከክልሉ አስወጥቶ የሰራውን ግፍ፤ ታሪክ ዘግቦታል።

(ደርግ ኦሮሞዎች ነበሩ ያስተዳዳሩት ሲባል፤ ግራ የሚገባቸው ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ። ይህ ምስጢር ነው የተገለጸልን። አስገራሚው ደግሞ “ደርግ” አማራ እያሉ ኦነጎች አውቀው ሲወነጅሉት፤ ደርግን የመሩ አማራዎች ሳይሆኑ አብዛኛዎቹ “እራሳቸው ኦሮሞዎች ነበሩ”። ወንጀለኛው ኦነግም፤መኢሶንም የደርግ ዋና የቀይ ሽብርና የወንጀል ታካፋዮች ነበሩ።ከቁንጮው ከሊቀመንብር መንግሥቱ ጀምሮ፤ተካ ቱሉ፤ተስፋዬ ገብረኪዳን፤ ደበላ ዲንሳ፤ደምሴ ቡልቶ፤ መርዕድ ንጉሴ፤ ረጋሳ ጂማ፤ ወብሸት ደሴ… ስንቱን ኦሮሞ ባለስልጣኖችንና ወታደራዊ አዛዦችና ደብዳቢ ካድሬ ኦሮሞዎች የነበሩትን ስንት ብለን እንቁጠር….! የፖለቲካ ክፍሉን የመሩት እነ ነገደ ጎበዜና፤ሃይሉ ፊዳ የማሳሉትን  የፖለቲካ ቀያሾቹ  ስንት ብለን እንቁጠራቸው! አሁን፤ አሁን፤  ደርግን በአማራነት እየከሰሱ “አማራውን” ሲያብለጠልጡት መስማት አጅግ ይገርማል። አስገራሚው ደግሞ “ባለፉት ግፈኛ ስርዐቶች” ኦሮሞ ሕዘብ ተበድሏል ይላሉ፤! ደብዳቢው፤ግፈኛውማ ገዢው፤ማን እንደነበር እየተዋወቅን! ) ‘ ውሸቱ እንደካሁን በፊቱ ውሸት እየተቀበልን በቸልተኛነት መቀጠል የለበንም፤! ግልፅ ግልፁን! እንነጋገር።

ቀስ በቀስ በለመዱት ብልጣብልጥ ስልታቸው፤ ቀስ ብለው በወያኔ ትከሻ ተንጠልጥለው፤ የገቡት፤ ኦነግ ብቻ ሳይሆኑ፤ የኦሮሞ “አክራሪ” እስላማዊ ፋሺስታዊ ኦሮሞ ድርጅቶች” እንዲሁም፤ ለ24 አመት የቀጠለ “የቀኝ አክራሪ ፋሺስታዊ ኦሮሞ ምሁር” እና አሁን እንደ አዲስ የተፈጠረው “በወጣት ኦሮሞ ምሁራን” የቀጠለው አዲሱ “የሜንጫ ኦሮሚያ አብዮት” የሚባለው ምሁራን የሚመሩት ፋሺስታዊ ቅስቀሳውን ባጭሩ ዳስሰን እንሰናበት።

ባጭር አገላለጽ፤ አሁን ላለው “ኦሮሚያ ኬኛ” የተማሪዎች መፈክር ምንጩ የሚከተለው ይሆናል።

 1)  ጋላዎች ከቦታ ቦታ፤ ካገር አገር፤ከግጦሽ ወደ ግጦሽ፤ በመዘዋወር ጥንት ከብት በማርባት ሲኖሩበት ከነበሩበት “ገላን” ከተባለ ከታች የኢትዮጵያ ጠረፍ በመነሳት እነኚህ “ጋላ” በመባል የታወቁ የተለያዩ የጋላ ነገዶች ወደ መሃልና ወደ ከፍተኛው ቦታ፤ አንዲሁም ምስራቅና ምዕራብ፤ እንዲሁም ሰሜን ኢትዮጵያ ውስጥ  በየማአዝናቱ ተከፋፍለው ንብረት/አገር/መሬት/ሴት/ከብት ለመዝረፍ የተከተሉት ፋሺስታዊ የወረራ ጭፍጨፋና ቤቶችን ገዳማትን በማቃጠል፤ የተፈጸመ ፋሺዝም  እንመለከታለን፡

 2) በደርግ ወቅት የተካሄደው ኦሮሞዎች የመሩት ፋሺስታዊ ስርዓት

3) በወጣት ምሁራን ኦሮሞዎች የተካሄደው ኦነግ፤ እና “ኢስላማዊ ኦነግ” እንዲሁም “የሜኒጫ አብዮት” ተብሎ የሚታወቀው “የኦሮሞ ፋሺዝም” ያካሄደው በአማራ ነገድ የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ።
እነዚህ የኦሮሞ ፋሺስታዊ ስርዓቶች ማለትም “From Fascism to Fascism (Aleme Eshete) ወይንም በኔው አገላለጽ “The Recycling of the Ormo Fascism!” The third cycle of the oromo Fascism” (Getachew Reda) ወይንም “ሦስተኛው ዙር የኦሮሞዎች ፋሺስታዊ አብዮት” ምንነት በየተራ እንመለከታቸዋለን።           

የገዳ ሰርዓት የጀመረው እጅግ ላ ቀር የሆነ የጭካኔ አስተዳደሩን እንመለከታለን፤ ከዚያ ያነሳሁዋቸው በየደረጃቸው ያሳዩት ፋሺስታዊ ድርጊቶችን ባጭር ባጭሩ እንመለከታለን። ከዚያ ማን ነው የተበደለው? ማን ነበር ስርዓት ላይ የነበረ፤ አሁን ኦሮሞዎች “የኛ ነው” እያሉ ማንም ሰው መግባት ማረስ፤መውጣት፤ማስተማር ፤ማስተዳዳር፤መኖር፤ ካለ ኦሮሞዎች በጎ ፈቃድነት “አይፈቀድለትም” በማለት የራሳቸው አጥር አጥረው ለግንጠላ እየተበረታቱ ያሉ ወጣቶችን “ራስ በራስ” ማስተዳዳር ማለት “ሞብ ሩል” የወረበሎች/ኦሊጋርኪ ስርዓት እንጂ “የግለሰብ ነፃነት” የሚባል ነገር “በነገድ ፌደራሊዝም ከቶ መጠበቅ ቅዠትና ስህተት መሆኑን እንመለከታለን።

እነዚህ አሁን ሰፊ መሬት አለን፤ ሰፊ ነን፤የኛ ነው፤ ማጆሪቱ ሩል….ወያኔ ራሳችን አንድናስተዳዳድር “በነገድ ፌደራሊዘም ሕገመንግሥት ተፈቅዶልናል” ወዘተ እያሉ የሚፎክሩበት “ክልል” የማን መሬት ነው? የኢትዮጵያ ሕዝብ መሬት ነው! አይደለም እንዴ? ዜጎች አይደለንም የሚሉ ከሆነ ተማሪዎቹ በግልጽ ይንገሩን።
ሆኖም እነሱ ወደ እሚሉንም ብንሄድም፤ ‘መብታችን በሕገመንግሥቱ መሰረት” ራስችን እንድናስተዳድር ይፈቀድልን፤ የሚለው ቅዠት፤ የክልል ፌደራሊዝም ስርዓት “ሞብ ሩል/የወረበሎች/ ያካባቢ የመሳፍንቶች ሰርዓት አስተዳደር ነው” ነው። ማንኛውንም ኗሪ ራሱን ሊያስተዳድር ኣይፈቅድለትም። ምክንያቱም “ፈቃጅ ካለ፤ በማንኛውም ጊዜ ፈቃጁ የሰጠህን ፈቃድ ሊነጥቅህ ይችላል”። ምክንያቱም ኤትኒክ ፌደራሊዝም “ሞብ ሩል” ስለሆነ” “ዐለም ዓቀፍ መስፈርት የተከተለ “ሰውን እንደ ሰውነቱ” በሕግ አያውቀውም።  ፀባዩ አይፈቅድለትም። “ኮለክቲቭ ራይት” ብቻ ነው የሚያውቀው።

ሁሌም የጅብ መንጋዎች ከታችም ከውጭም፤ከላይም ስለሚያፈራ “ኦሊጋሪኪ/ሩል” እንጂ ግለሰቦች ነፃነት የላቸውም። መሬት የመንግስት ነው፤ የክልል ነው። የግለሰብ አይደለም። ስለሆነም፤ ንብረት ስለሌለህ “ነጻ’ ልትሆን አትችልም፡ “የፌደራልና የክልሉ ዴፐንዳንት/ጥገኛ ነህ”። ልትሸጥ፤ልትለውጥ አትችልም። ተከራይ ጭሰኛ ነህ። ቴናንት ነህ። ዜጋ አይደለህም። የክልሉ ወይንም የማአከላዊ ፌደራል መንግሥቱ ጭሰኛ ነህ ከሆንክም፤ “ነፃ” ዜጋ አይደለህም። የክልሉ መንግሥት ጭሰኛና ተከራይ እስከሆንክ ድረስ ስለ የመሬትና ንብርት መከራከር መብት “የቅዠት መብት” ብቻ ነው ሊኖርህ የሚችለው። ክልል ፌደራሊዝም ያንተው የግለሰብ ሁለተኛው ላንድ ሎርድ/ጌታህ ሲሆን/ የእርሱም ዋናው ጌታ “ማዕከላዊ መንግስት/ፌደራል” የሚባል “በሞብ ሩል ሕግ” የሚመራ አካል አለ። በነዚህ ውስጥ “አንተ” የሁለቱም “ጭሰኛ ነህ”። አራት ነጥብ!!!!!!!!

አሁን ኦሮሞዎች የያዙት መሬት እንዴትና ከማን ነጠቁት?  

ስለ ጋዳ  ስርዓት  ትንሽ ልበልና ልደምድም። እውነት ነው ጋላዎች የተለያዩ ጎሳዎች ነበሩ። በዘመኑ ወደ መሃል ኢትዮጵያ የተስፋፉ “ጋላዎች” አንድነት አልነበራቸውም። እርስ በርስ ሲጋደሉና ሲዘራረፉ አንደነበር ሊቁ ጌታቸው ሃይሌ ገልጸውልናል። ቀደም ብየ የገለጽኩት መጽሐፋቸውን (የአባ ባሕርይ ድርሰት ተመረኩዘው ከግዕዝ ወደ አማርኛ የተረጎሙልንን ተመልከት)፤ ለዘመናት ጀምሮ የተረጋጋን የኢትዮጵያ መንግሥት “ጋላዎቹ” ከገቡ በላ፤ አገሪቷን ብትንትኗ  እንዳወጧት አባ ባሕርይ ንብረታቸውና መጽሐፍታቸው እንዲሁም ገዳማቸው ጅማ ውስጥ ሲያቃጥሉላቸው ያዩትን ነግረውናል።

ጋዳ ወይንም “ሉባ” (ኦሮሞዎች አስተዳደር ዲሞክራሲ ነው) ተብሏል። ምን ማለት ነው? እኔ “ፋሽሰታዊ የወንዶች ራስን በራስ የማስተዳዳር ስርዓት” እለዋለሁ። 5ቱ ጋላ ነገዶች  8ት፤ 8ት አመት ይሾማሉ፤ የተሾመው መሪ “ሉባ” ይሉታል። ስርዓቱ ወንዶችን በየበላይነት ያስቀመጠ፤ ወንድም ቢሆን ለሥልጣን እርከን ለመድረስ ፤ግድያ፤ብልት ሰለባ ፤ጸጉር በቅማልና በቁጫጭ መበላትን፤ ልጆችን መጣልን ወዘተ…ወዘተ.. ያጠቃልላል። ዲሞክራሲ የሚሉት ይህንን ፋሺስታዊ ባሕሪ ያካተተ ነው ዲሞክራሲ ነው እያሉ ወጣቱን በዛሬው ባሕሪ እንዲጓዝ የሚመሩት።

ይህ ሁሉ የዛሬዎች ኦሮሞ ምሁራን ውሸት ከጥንት ጀምሮ “ከጋላ” ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ ሕዝባዊ ዲሚክራሲ ነበረን፤ አቢሲኒያዎች/አማራዎች/ምኒሊክ…ወዘተ..  ነጠቀን፤ የሚሉትን ቅዠታቸውን እስኪ ታሪኩን ባጭሩ እንመልከትና እንደምድም።

የጋሎችን ታሪክ የተወሉንን የመጀመሪያው የዓይን ምስክርና የጋላ ታሪክ ዘጋቢ አባ ባሕሪይ የጻፉትን በሊቁ ጌታቸው ሃይሌ የተተረጎመ (የአባ ባሕሪይ ድረሰቶች በገጽ 152 የተዘገበውን እንመልከት።
“…ከማህላቸው አባ ሙዳ የሚሉትን አንዱን ወንድ አይሁድ ሙሴን፤እስላሞች መሐመድን እንደሚተማመኑበት ይተማመኑበታል። ከሩቅ አገር ድረስ ወደእሱ እየሄዱ እጅ እየነሱ የማሸነፊያ ቡራኬና የመዝረፊያ ቡራኬ ይባረካሉ። ምራቁን በድኝ ላይ ይተፋላቸዋል፤ እነሱም ከሚወጉት ዘንድ ሁሉ የውጊያ ዕለት ተስፋ እንዲሆናቸው (ምራቁን) በድኝ ቋጥረው ይይዙታል።

ደግሞ ጋሎች ሁሉ በየነገዳቸው ሁነው አምስት መደቦች ናቸው። (አምስቱ መደቦች) በየተራቸው በየስምንት ዓመት ይሾማሉ። የተሾሙት ባለተራዎች ሉባ ይባላሉ። ይኸ ሹመት ማለት ሉብነት እስኪደርሳቸው ድረስ እስኪታቸውን አይገዘሩም፤ወንድም ሆነ ሴት (ልጅ) ሲወልዱ (ልጆቹን) እደጅ ይጥሏቸዋል እንጂ  እንደወላጆች ሥርዓት አያሳድጓቸውም።

ደግሞ በሹመታቸው ዘመን ሰው ካልገደሉ የራሳቸው ጠጉር አይላጩም። የሞት ፍርድ እንደተፈረደበት ዘወትር እያለቀሱ በሐዘን ላይ ይኖራሉ እንጂ ሰው ለመግደላቸውም ምልክት (የሚሆነውን) ቁንጮ አያወጡም።

  እነዚህን የጋላ ልምዶች ሁሉ ንጉሥ ሥልጣን ሰገድ አስተዋቸው። በአብ፡ በወልድ፡ በመንፈስ ቅዱስ ስም እንዲያጠምቋቸው አዘዘ። ወረነሻዎች ሁሉም ተጠመቁ። የጌታችን የመድሃኒታችን የእየሱስ ክርስቶስን የሥጋውንና የደሙን ምስጢር ተቀበሉ። (ቆረቡ)። ከክርስትያኖቹ ሁሉ ጋራ ያንድ እረኛ አንድ መንጋ ሆኑ። ወረንሻዎች ከሰባቱ በረንቱማ ነገዶች አንዱ ነገድ ናቸው።” (ጌታቸው ሃይሌ - እንደላይኛው ገጽና ምንጭ)።
ክቡራን አንባቢዎቼ፤ ይህ እውነታ ነው የኦሮሞ ምሁራን “ዲሞክራሲ ነበረን” እያሉ ሳይሸማቀቁ በየጋዜጣ፤መጽሐፍት ጭምር እየጻፉ አግላይና፤ በነገድ ሐረግ ብቻ የሚተዳደር ስርዓት፤ ወንድ የሚነግሥበት፤ ሴት የምትናቅበት፤ለዚህ ስርዓት መሪ ለመሆንም “ዘግናኝ የሆነ፤ ሰውን በመግደልና በመስለብ ጭካኔን እንደ አዋቂና አስተዳዳሪ ማሳያ ተደርጎ፤ የሚወሰድ “የጫካ ሕግ” ነው፤ ዲሞክራሲ ነበር እያሉ ማሕበረሰቡንና የዋህ ፈረንጆችን እየዋሹ የሚያሳስትዋቸው።

ይህ ስርዓት ነው፤ራስን በራስ በዲሞክራሲ ስንተዳዳር የነበረውን ሥርዓታችን አቢሲኒያዎች አፍርሰው ኮሎኒ አደረጉን እያሉ የሚመጻደቁብንና ወጣት ኦሮሞውን የሚያጃጅሉት (ልክ አንደ ኤርትራ አሳፋሪ ውዥምብራም ፤ውሸታም ሊሂቃኖች)። እነኚህ ነገዶች “ሉባ” በሚባለው ዝርፍያውና ወረራው እንዲቀናቸው እየመረቀ ወደ ወረራ ሲያሰናብታቸው፤ አሁን ድረስ ተንሰራፍተውበት የሚታዩትን እስከ ትግሬ ድረስ መጥተው የሰፈሩበት ምክንያት በሰላም ሳይሆን “ወረራና የጭፍጨፋ” ድርጊት እየፈጸሙ ነበር የያዙት፦

ከላይ የጠቀስኩት ምንጭ እንዲህ ይላል፤-

(መስከረም የ 1633 ዓ.ም መጀመሪያ፤ዕለት ቅዳሜ፤(ዘመኑ) ማቴዎስ፤
(ንጉሡ) ጎጃም ሄደ። በዚህ ዓመት ስሙ ለበቻ፤ መጠኑ አርባ ሺሕ የሆነ ጋላ ወደ ትግሬ መጣ፤ ሰራዌንም አወደማት። ሲመለስ የፅራዕና የተምቤን ሹማምንት በምድረ አላ ላይ ከበው ምንም ሳያስተርፉ ፈጁት። ንጉሡ በዶቢት ተቀመጠ። የበኽር ልጁ አቤቶ ቄስጠንጢኖስ ሞተ። (ምንጭ የአባ ባሕሪይ ድርሰቶች፤ ደራሲ ጌታቸው ሃይሌ፤ ገጽ 136)

 እንግዲህ በአለም የተደነቀ ራስን በራስ የማስተዳዳር ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ኦሮሞች ነበራቸው፤እያሉ የሚዋሹንን የጋላዎች ዲሞክራሲ እስከ ትግሬ ድረስ በዝርፊያ፤በግድያና በወረራ የመስፋፋት ባሕሪይ በየክፍላተ ምድሩ “ጥንታዊ ፋሺዝም” ኦሮሞዎችም እንዴት ያራምዱት እንደነበረ ባጭሩ ለማየት በቅተናል። ይህ ሁሉ ርቀት ተጉዘው ባጭር ጊዜ የኢትዮጵያን ሰፊ መሬት ሊቆጣጠሩ የቻሉበት ምክንያት አስቀድሜ እንደገለጽኩት፤ የተመለከትናቸው የጋላ ከብት አርቢዎች፤ ያገሪቱ /ኢንዲጅነስ “ነባር ሕዝብ” እያባረሩ፤ ሰው የሌለበት ጭር ያለ “ቤት የሚጠብቅ” ጠባቂ “ከልብ” (ውሻ) ሳይቀር፤ በጦር እየወጉ፤ መሬቱ፤ሚስቱ፤ንብረቱ፤እርሻውና ቤቱ፤የተነጠቀበት ምክንያት “ግራኝ አህመድ” አገሪቷን አቃጥሎ ስላዳከማት፤ ክፍት ቦታ አግኝተው ፤ ሰተት ብለው መላውን ሰፊ ቦታ ተቆጣጥረው፤ ዛሬ “ኦረሚያ ኬኛ” (ኦረሚያ የኛ) ወደ ማለት የደረሱበት ዋና ምንጩ “አገር ያወደመ” የጋሎቹ ወረራ ውጤት ተጠቅመው ነው ዛሬ “በክልላችን ማንም ሰው ዝር እንዳይል” በማለት ክልል የተባለ ባንቱስታናዊ “ዘረኛ አስተዳዳርን” በአክብሮት ተቀብለው ወደ ግንጠላ ጉዞ እያዘነበሉ “አንቀጽ 39ኝን” ማስፈራሪያ ካርድ እያሳዩ ሊያስፈራሩን እየሞከሩ የሚገኙት።

ለማጠቃለል፤በ24 አመት ውስጥ ለእልፍ አእላፍ አማራ ሕብረተሰብና ገበሬ ከኦሮሞ አካባቢ አገርህ አይደለም “ውጣ” እየተባለ የተባረረ፤እርጉዞች ማህጸናቸውና ሆዳቸው በቢላዋ የተዘረገፉበት፤ህጻናት በፋሺስታዊ ቢላዋ “አንገታቸው የታረዱበት” ንግዳቸውና አንብረታቸው  እየተዘረፉ፤በግፍ የተጨፈጨፉ አማራዎች “ዜግነታቸው” የተነጠቁበት ምክንያት “የኦሮሞ ባንቱሳናዊ “የክልል” አስተዳዳር ቀያሾችና ጀሌዎቻቸው ምክንያት የቀየሱት “ሦስተኛው ዙር *የኦሮሞዎች የፋሺዝም* አብዮት ውጤት መሆኑን ልነገራችሁ እፈልጋለሁ።

“ሦስተኛው ዙር *የኦሮሞዎች የፋሺዝም* አብዮት ተጠያቂዎች እነማን ናቸው? ወያኔዎችና የወያኔ ጀሌ ኦሮሞዎች፤እንዲሁም፤ በዕድሜ የገፉ “የኦነግ መሪዎች”፤ እንዲሁም “የሜኒጫ አብዮት” ተብሎ በእስላም የኦሮሞ ምሁራን ወጣቶች ልብ ያደረው እነ “ጃራ” የመሰረቱት “እስልምናን ከፖለቲካ አቀናጅቶ፤ የኦሮሞ እስላም ማሕበረሰብ፤ ኦሮሚያን ነፃ አድርጎ፤ እስላማዊት ለማድረግ፤ የተመሰረተው “ኦሮሞአዊ ፖለቲካል ኢስላም” አራማጆችና ተከታዮቻቸው ናቸው።

የኦሮሞ ፋሺዝም” ያካሄደው በአማራ ነገድ ላይ የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ አልፎ፤ ‘አሮሚያ” ነፃ ካወጡ ፤ኦሮሞ ማሕበረስብ እንደሚቀዳጅ የተሰበከውን “ማርና ወተት፤ራስን በራስ ማስተዳዳር ዲሞክራሲ ያገኙ ይሆን? ወይስ ኢስላሚክ ኦሮሚያ፤ በሸሪዓ እንድትተዳዳር በሚሉ ክፍሎችና፤ “ሞብ ሩል” በሚከተሉ “ኦነጎችና መሰል ተመጻዳቂ ምሁራን ኦሮሞዎች” ፍጥጫና እንደ ሶመሌ “የዕርስ በርስ” ፍጅት ተከትሎ “የኦሮሞ ሜንጫ ካሊፋት አብየተኞች” የበላይነት ይዳኙ ይሆን? ይህ ከሆነ ወጣት ኦሮሞ ሴቶች ምን ይገጥማቸው ይሆን?  “ማስተማሪያ አትንሳኝ” ይባላል እና ትምህርት ቢሆናቸው የአፍጋኒስታናዊያን ወጣት ሴት ልጃገረዶች የተናገሩትን ትምህርት “በጥቅስ የተናገሩትን” አንብቡና እንሰናበታለን።

"Every girl," recalled Saira Noorani, a female surgeon, "could go to high school and university.We could go where we wanted and wear what we liked. We used to go to cafes and the cinema to see the latest Indian film on a Friday and listen to the latest music. It all started to go wrong when the mujaheddin started winning. They used to kill teachers and burn schools. We were terrified. It was funny and sad to think these were the people the West supported."

ኦሮሚያ ተመስርታ ያ ሁሉ ቀውስ ቢመጣ፤ ካፌና ሲነማ መሄድ የለም፤ እምየ ኢትዮጵያ ሞታለች፤  መሰደጃ፤መላወሻ መረማመጃ፤መሸሺያና መጠለያ መንገድ አይኖርም። ሁሉም እንዴት እዚህ አረንቋ ልንገባ ቻልን? የሚል ሶማሌዎች መልስ ያጡበት ጥያቄ “በየአጥሩ ታጥሮ” “እየተጫፋጨፈ” መልስ ሊያገኝ ቢለፋ፤ መልስ ሰጪ አይኖርምና ከዚያ ከመአቱ ይሰውረን!  አመሰግናለሁ። ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያን ሰማይ ብሎግ አዘጋጅ Ethiopian Semay)  getachre@aol.com



  

Wednesday, December 23, 2015

“የነገድ ፌደራሊዝም” የግማሽ ንክ ግለሰቦች የፖለቲካ ቅዠት ነው ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay ብሎግ አዘጋጅ)


“የነገድ ፌደራሊዝም” የግማሽ ንክ ግለሰቦች የፖለቲካ ቅዠት ነው
ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay ብሎግ አዘጋጅ)

ወደ ርዕሴ ከመግባቴ በፊት መጀመሪያ አበራታች የሆነ የምስጋና ኢመይል ለጻፋችሁልኝ ለወንድሞቼ አቶ ተድላ አስፋውና አቶ ሰመረ አለሙ እንዲሁም በርካታ እህቶችና ወንድሞች ጊዜ በማጣቴ በጊዜ መልስ ያልሰጠሁዋችሁ ወገኖቼ እንዳትቀየሙኝ እዚህ ላመሰግን እወዳለሁ።

ቀጥሎም፤ አበበ ቦጋለ የተባለው በግንቦት 7 የተጠለለው የኦነግ ፕሮግራም አራማጅና የግንቦት 7 አማራር አባል፤ ሰሞኑን እሱን በሚከተሉ ጀሌዎቹ ፓልቶክ ተጠርቶ ስለ የሰሞኑ የአሮሞ ተማሪዎች ንቅናቄ እንዲያብራራላቸው በተጠየቀበት ወቅት፤ ካሁን በፊት ደጋግሜ አንደገለጽኩላችሁ ልክ አንደ ብርሃኑ ነጋ፤ አበበ ቦጋለም ፤የመገንጠል ጥያቄ በሕግ/በፖሊሲያችን አንገድብም! መገንጠል እፈልጋለሁ የሚል የፖለቲካ ነገድ /ደርጅት ካለ፤ (ይታያችሁ ለኢትዮጵያ ሕዝብ አይደለም ለሬፈረንደም የሚያቀርበው) አዲስ የሚዋቀር መንግሥት ‘አላረካኝም’ ካለ “ለነገዱ ሕዝብ” አቅርቦ “በደምፅ ብልጫ/ሬፈረንደም” ሊገነጠል ይችላል ብሏል።

እኔ ካሁን በፊት ግንቦት 7 የማልደግፍበት ምክንያት ወደ ኤርትራ ሄደ/አልሄደ ሳይሆን ዋነኛው ክርክሬ፤ መክንያቶቼ ብዙ ቢሆኑም (1ኛ) ጸረ አማራ በመሆኑ (አመስረጃ አቅርቤአለሁ) (2ኛ)-ልክ አንደ ወያኔ አንቀጽ 39ኝን ተግባራዊ ለማድረግ የፈለገ አገርና ቤተስብ አፍራሽ ሁሉ በድምፅ ብልጫ እንደ ኤርትራ የመገንጠል መብቱ የተጠበቀ መሆኑን ደጋግመው ስለመግለጻቸው፦ (3ኛ) ግንቦት 7ን አምነው ወደ ኤርትራ የሄዱ ዜጎቻችን “ሄልኮፕተር” ተብሎ በሚታወቀው ኤርትራኖች ሰው የሚያሰቃዩበት እኛ “ወፌ ላላ” የምንለው የድብደባ ስቃይ እንዲሰቃዩ፤እስር ቤት እንዲማቅቁ በማድረግና ለሻዕቢያ ገራፊዎች አስተላልፎ ደብዛቸው እንዲጣፋ በማድረግ የተሰወሩ ሰዎችን በግድያ የሚጠየቅ ሰብአዊ መብት ተጠያቂ የሆነ ወንጀለኛ ድርጅት መሆኑን የመሳሰሉ ነጥቦችን፤ ግንቦት 7ን የማልደግፈው መክንያት የተከራከርኩበትን ነጥቤን ግልጽ አድረጌአለሁ። ከዘረዘርኳቸው ሦስቱ ውስጥ “በሁለተኛ ነጥብ” የተጠቀሰው “የግንጣላ ጉዳይ” ዘሬ አበበ ቦጋለ ሳይደባብቅ ግንቦት 7ትም ልክ እንደ ወያኔ እንደሚያምን ግልጽ አድሮጎላችኋል። አሁን ግንቦት 7 እና ወያኔ መምረጥ ምን እሳት አንደሚጭርባችሁ መገንዘብ ካልቻላችሁ፤ የራሳችሁ ጉዳይ!

በተያያዘም፤ ምስኪኗ ጋዜጠኛዋ ርዕዮት፤ ግንቦት 7ን  መቀላቀሏን ነግራናለች። ግን….ግን…. በተቀላቀለችበት ድርጅት ውስጥ ደብዛቸው የጠፉና የተደበደቡ፤ ኢሳት በፍርሃት ምክንያት ለአለቆቹ ወግኖ እንዳያቀርባቸው አምቢ ብሎ፤ “ከድብደባው” እንደ ዕድል ያመለጡ ታጋዮች “ግንቦት7 ዲ” በማለት ድረገጽ ከከፈቱ በኋላ የግንቦት 7 መሪዎች “ጉድ” ያስነበቡን ግለሰቦች ፤……. ፤ ኢሳትን በደብዳቤ “ሕዝብ እንዲፈርደን ከግንቦት 7 መሪዎች ጋር በራዲዮናችሁ፤ ቴሌቪዢናችሁ አገናኝታችሁ አነጋግሩን፤ ብለዋቸው “መድረክ” ስለ ተነፈጉ ሰዎች አንደ ጋዜጠኛነቷ እና ተጋይነቷ ኤርትራ ድረስም ሄዳም ሆነ  አውሮጳ ያሉትንም “ሃቁን” አጣርታ ታቀርብልን ይሆን? የሚል ጥያቄ አቀርብላታለሁ። ከዚህ ጸረ አማራ ድርጅት ሆኜ ለመታገል “ተቀላቀያለሁ” ብላለችና  ኤርትራ ከሄደችም ፤ እሷንም ከዚያ ማኣት ማርያም ትጠብቃት ከማለት ሌለ ምን ይባላል። አስገራሚ ጊዜ። ከድጡ ወደ ማጡ!

ወደ ርዕሴ ከመግባቴ በፊት በሌላ ቀን፤ በዚህ ጉዳይ እስክመለስበት ጊዜ አስገራሚው የሆነ ብዙዎቻችሁ ስትሞኙና ስታሞኙ የነበራችሁ ጀሌ“ግርምቢጦች” አበበ ቦጋለ ግልፅ ያደረገላችሁን ልንገራችሁ። ግንቦት 7 ፖሊሲ/ፕሮግራም የለውም፤ ምንግሥትነት/ለሥልጣን አይደለም እየታገለ ያለው ሲሉ ደጋግመው ሲዋሹዋችሁ፤ እናንተ ጀሌዎቹም ተቀብላችሁ ስታስተጋቡ ነበር። አበበ የነገርን ግን፤ ግንቦት 7 “ፖሊሲን አስምልክቶ የፖቲካ ድርድር ማድረግ እንደሚችል” ፤ “የመገንጠልን ያክል አንገብጋቢ ፖሊሲ” ሳይቀር “በሬፈረንደም” መግንጠል አንደሚቻል ድርጅቱ የሚፈቅድ መሆኑ፤ ወዘተ ወዘተ ነግሯችኋል። ግንቦት 7 ወያኔ ለመጣል እንጂ “የፖለቲካ ፍላጎትም ሆነ፤ፖሊሲ/መመሪያ ፕሮግራም የለኝም” እያለ ሲዋሽ ቆይቶ፤ ሬፈረንደም ሁሉ እስከመፍቀድና፤ ከማንኛውም ተደራዳሪ “የሚጠይቀው ሁሉ ‘ግንቦት 7 ኮምፕሮማይዝ” የሚያደርግ “ተደራዳሪ ድርጅት” እንደሆነ ዛሬ ግልፅ አድርጓል።  ካሁን በፊት ለተጃጃላችሁ ምስኪኖች፤ ደርጅታችሁ “ድርጅቱ የሚመራበት ፕሮግራምና ፖሊሲ” የለም ሲል፤ ሲያጃጅላችሁ ከርሞ፤ ዛሬ ሳያስበው ድንገት አበበ ቦጋለ “በድንገት ባርቆበት” ፖሊሲያቸውን ግልጽ አድርጎላችኋል። በዚህ አጋጣሚ ኦነጎችና መሰል ተገንጣይ ፋሺስቶች ወያኔ ተክቶ ሲመጣ ግንቦት 7 የወያኔን ኮፒ/አንቀጽ 39ኝን ተግባራዊ እንደሚያደርግላችሁ ቃል ስለገባላችሁ “አንኳን ደስ አላችሁ!” እላለሁ። ለዚህም ነው ኦነጎችና ኤርትራኖች ግንቦት 7ን ከሌሎች ድርጅት የሚደግፉት ዋናው ነጥባቸው።

ይኼ ፖለቲካ ራስ ምታት ነው ጃል! አይደል? ወደ ርዕሳችን እንግባ።

ፖለቲካው ስንገባ ፖለቲካ ማለት በቀለለ ትርጉሙ “የአስተዳዳር ዘይቤ፤የቅስቀሳ ዘዴ” ብዬ ተርጉሜዋለሁ። በራሳችሁ ትርጉምም ሂዱበት፡ ግድየለኝም። ዛሬ ለማሳየት የፈለግኩት ግማሽ ዕብድ ፖለቲከኞች የሚወዱት ፖለቲካ ነው። ፌደራሊዝም የሚባል ፖለቲካ!

ለበርካታ አመታት “ፌደራሊዝም” የውጭ ቋንቋ ሆኖ፤ ትርጉሙም በትክክል ባይታወቅም፤ ያገራችን ታዋቂው “ቀልድ ነጋሪው” ታማኝ በየነ ካልተሳሳትኩ “ፌዝ-ራሊዝም” የሚል ትርጉም የሰጠው መሰልኝ (በደምብ ትዝ አላለለኝም ተሳስቻለሁ መሰለኝ አርሙኝ) አውነትም ቀልድ ነው። ከዚህ ቃላት ጀምሮ ማለትም  “ፌደራሊዝም”፤ “ዲሞክራሲ”፤ “ብዙሃን/ማጆሮቲ”፤ “ጥቂት/ ንኡሳን/ማይኖሪቲ”፤ “ሕዝበ ውሳኔ”፤ “ብሔር/ብሄረሰቦች/ሕዝቦች”…. የመሳሰሉ፤በቃላት እንጂ “በተግባር ሲተረጐሙ” ትርጉመ ቢስ ወይንም ስራ ላይ ሲውሉ “ዲክታቶሪያላዊ” ውጤት ሆነው እየታዩ ነው።

“ማርና ወተት” የሚያምበሸብሹ “እስከሚመስሉ” ድረስ “ተደጋግመው” ሲነገሩ ሰምታችኋል። እነኚህ የተጠቀሱት “አስተዳደሮችና ትርጉሞች” “ለሰው ልጅ” መብት ሰላምና ብልፅግና “በር ከፋች” መንገዶች ናቸው ብለው ባብዛኘው የሚነግሩን ክፍሎች ደግሞ እነማን ናቸው ብላችሁ ብትጠይቁኝ፤ ለግለሰብ ሰብአዊ መብት የቆሙ ክፍሎች ሳይሆኑ “ለብዙሃን መብት” ቆመናል የሚሉ “ኮለክቲቪስት” የሚባሉ ክፍሎች ናቸው። ኮለክቲቪስቶች ደግሞ “ፋሺዝምን”  “ሶሺያሊዝምን/ኮሚኒዝምን/የብዙሃን ዲክታቶር-ሺፕ/ የሚያራምዱ ሰዎች/ድርጅቶች/ ናቸው።” ማጆሪቲ ጋቨርንስ ዘ ማይኖሪቲ/” ብዙሃን ይመውኡ”፤ ንኡሳን ማለትም ግለሰብንም ያጠቃልላል፡ መብቱ ተረግጦ ለብዙዎቹ ተገዥ ይሆናል ማለት ነው። አንድ አማራ ወይንም ጥቂት አማራዎች፤ ብዙሃን ኦሮሞ ወይንም ብዙሃን ነገዶች ክልል…. በሚኖሩበት ክልል ውስጥ ከኖረ፤ ግለሰባዊ/ዜጋዊ መብቱ በብዙሃኑ ፍላጎትና ውሳኔ ይነጠቃል ማለት ነው። ይህ ደግሞ “ዲክታተሪያል” ይባላል።

የኮለክቲቪስት ፖለቲካ ርዕዮት የጀመረው ‘ከሶቭየት ሶሺያሊስት/ከቻይና/” እስከ ሂትለራዊት ጀርመን እና ሞሶሎኒትዋ ጣሊያን እና የነዚህ ክፍሎች ርዕዮት ተቀብለው ያራመዱ በየአገሩ እሰከ አሁኗ የወያኔ ኢትዮጵያ እና እስከ ኦነግ/አብነግ ወዘተ የመሳሰሉ በብዙሃን እና በነገድ (ለፖለቲካ) የተሳባሰቡ ክፍሎች ብዙ ሕዝብን ያበጣበጠ ርዕዮት ያጠቃለለ ነው። እነዚህ ክፍሎች የቆሙት” ለግለሰብ ነፃነት ሳይሆን “ለብሔራቸው፤ለሃይማኖት ድርጅታቸው፤ለቤተሰባቸው፤ለክልላቸው፤ለፖለቲካ ድርጅታቸው፤… መብት” የቆሙ እንጂ “ለሰውልጅ/ለግለሰብ” መብት ቀዳሚ ትኩረታቸው አይደለም። ይህ ሲሆን፤ ከስብስቦቹ/ከኮለክቲቪስቶቹ/ “ማሕበር ውጭ” የሆነ “ግለሰብ” (የሰው ልጅ) እነሱን ካልመሰለ፤ ለማሕበራቸው የተከራከሩለትን “መብት/ነፃነት” ተጋሪ አያደርጉትም።

 ስለሆነም፤ ኮለክቲቪስቶቹ (በነገድ (ጎሳ) ተከልለው የራሳቸው አስተዳደራዊ መዋቅር፤ ባንዴራቸውና ቋንቋቸው ዘርግተው….) የተዋቀሩ ክፍሎች የግለሰብ መብት ተፃራሪዎች በመሆን፤ እነሱን የማይመስል ግለሰብ “ከማሕበሩ ባይተዋር እንዲሆን በማድረግ፤የቆየ የበሰበሰ የተረሳ፤መሰረተ ቢስ የሆነ ታሪክ እየመዘዙ ዘላቂ ፀብ ለመጫር አንዲመቻቸው “ኦነሌ የመሳሰሉ ሃውልቶችን በመትከል” ወይንም እስከ ግዲያ እስከ ማባረር፤ንብረቱን እስከ መዝረፍ፤ማንገላታትና ማሰር በሚደርስ” ወንጀል ተዋናይ ይሆናሉ (በሌላ አነጋገር ከዱር እንሰሳት ሕሊና ያልወጡ ተበቃዮች ይሆናሉ ማለት ነው)። ተዋናዮቹ ‘ማሕበረሰባችን/ነገዳችን/ክልላችን’ ብለው ከከለሉት አጥር ውጭ ተሻግሮ/ዘልሎ የሚመጣ “እነሱን የማይመስል” ሁሉ እንደ ‘ጠላት/ወራሪ/ በማየት ‘የንብረት፤የመሬት ተቀናቃኛቸው’ አድርገው እንዲመለከቱት ያደርጋሉ።

ሕዝባቸውን በቁጥጥር ለማድረግ አደራጂዎቹ የሚጠቀሙበት ዘዴ “እንወክለዋለን የሚሉትን ማሕበር” በወንጀል ባሕሪያቸው ተካፋይ እንዲሆን፤ እነሱን በማይመስሉ ነገዶች ምክንያት “ማንነቱ/ባህሉ፤ቋንቋው፤ንብረቱ/መሬቱ/ሚስቱ/ተራራው/ወንዙ/ሃይማኖቱ/ባህሉ…” እንደተነካ ወይንም ሊነጥቀው አንደመጣ “ወራሪ” አስመስለው በመቀስቀስ ‘በመጤዎች’ ላይ አመፅ እንዲያስነሳ በመገፋፋት፤ ለረዢም ጊዜ ጠብ አንዲኖረው በማድረግ “ነገዳቸው በአንድነት/በጋብቻ’ “ከመጤዎቹ” ጋር እንዳይቆራኝ አድርገው “ነገዳቸው በማንነት ክር” ተብትበው “በቁጥጥራቸው” ሥር ያደርጉታል።

የነገዶቹ ግለሰብ አባላት ከሌሎች ጋር የነበራቸው ማሕበራዊ ግንኙነቶች በሙሉ “ለዓይን በማይታይ ሕሊና ውስጥ የሚፈነዳ ቦምብ በማቀጣጠል” አፈንድተው እንደማይሆን አድርገው ይበታትኑታል። ሕብረተሰቡ ውሎ አድሮ “ከቅዠቱ ሲባንን”፤ ደራሲውና የ ኢሕአፓ መስራች መሪ “ሃማ ቱማ” (ኢያሱ ዓለማየሁ) “GIVE ME A DOG”S LIFE ANY DAY” African Absurdities II” በሚባለው ድንቅ መጽሐፉ እንደገለጸው ‘ነፃነት’ ብለው የደገፉት *ነፃነት* ተስፋ በሚያስቆርጥ ውጤቱ *ባርነት፤ችጋር፤ኢፍትሓዊ በደልና ውርደት ነግሶ* እነኛ በማስገንጠልም ሆነ በኤትንክ ፌደራሊዝም ማርና ወተት ታገኛለህ ብለው ያሞኙት “የክልል መሪዎችና ገንጣዮች “ዙፋን” ላይ ተቀምጠው የባሰውኑ “ጨቋኞችና ብጥብጥ አስነሺዎች” ሆነው ያገኛቸዋል። ኗሪዎቹ ሕይወት አዳጋች ሆና ያገኟታል። ኤርትራ የተጓዘችበትና የታየው ክስተት፤ እንዲሁም “ሶማሊያ” የተጓዘቺበት መንገድ ስትመለከቱ የሊሂቃን/የጎሳ/ክላን አባቶች/መሪዎች (ዋር ሎርድስ) የቀረጹት “የኮለክቲቪስት ርዕዮት” ውጤት ነው።

ፌዴራሊዝም በስያሜውና በስነ ትርጉም “የመብት አጎናጻፊነትን ልብስ የሚያለብስ ይመስላል። ሆኖም ከማንኛውም ‘አሃዳዊ/ፓርላሜንታዊ ስርዓት’ ይልቅ በነገድ/ በኮለክቲቭ/ በቋንቋ የተዋቀረ ፌደራሊዝም “ሥርዓተ አልባነትን” በሰፊው ያሰፍናል። ሶማሌ ውስጥ ስትመለከቱ “ሰቴት-ለስ/መንግሥት አልባ” የሆነችበት መንገድ ሲመረመር፤ አንዳንድ ኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች፤ የሶማሊ ኤሊቶች እና የውጭ ተንታኞች “የውጭ ጣልቃ/ፕሮክሲ” “ኢትዮጵያ በወረራ ስለገባችት ነው” የሚል ምከንያታዊ ሽፋን ቢሰጡም፤ አሃዳዊው “የስያድ በሬ” መንግሥት ከፈረሰ በላ፤ ማሕበረሰቡ “ገደብ የለሽ የራስ ገዝ አስተዳደደር መብት” እናመጣልሃለን ብለው ፖለቲካውን ብጥስጥሱ አውጥተው አገሪቱን ያናጓት የሥልጣን ጥመኛ ሊሂቀን ክፍሎች፤ ጫና በመበርታቱነው።
ይህ ደግሞ “በናሺናለዝም ሽፋን” (የባዕድ ወራሪ መጣብን ሽፋን) “ግማሽ ዕብደት” የተጠናወታቸው በሶማሊ ውስጥ  የሚገኙ የተለያዩ “የወታደራዊ፤ የጎሳ፤ የዓብደል ውሃብ ሃይማኖት አቀንቃኝ “ውሃባይት’ መሪዎች፤ በየመአዝናቱ ተበትነው “በሰለጠነ ሕግ ያልተዋቀረ/ቁጥጥሩ የላላ፤ ስርዓተ አልባ የሆነ ፤ “የራስ ገዝ/ፌደራሊዝም” ግማሽ ንክ በሆኑ ክፍሎች መሪነት ትርጉም ላይ ሲውል ያስገኘው አሳዛኝ ውጤት ነው።

የሶማሌ ውድቀት ላገራችን ማስጠንቀቂያ ሊሆን ይገባል። ክላኖች/ነገዶች በቋንቋቸው፤በሃይማኖታቸው የራሳቸው አስተዳዳርና ተከታዮች ኖሯቸው “ሙሉ ነፃነት” አውጀው፤ እርስ በርስ በጠላትነት እየተያዩ፤ እስከ አልሸባብ ድረስ “የተጓዙበት መንገድ” ምክንያት የሆነው “የጎሳ መሪዎች/ፖለቲከኞች” ማአከላዊ መንግሥት በቅርበት የማይቆጣጠረው “ገደብ የለሽ” (ወያኔዎችና ኦነጎች “ያልተሸራረፈ” መብት የሚሉት ዓይነት) ራስን በራስ ማስተዳደር ማለት “የክልል-አምባገነኖችን” እያራባ መፈልፈል እንጂ ማስወገድን የማይችል በመሆኑ ነው።

አምባ ገነኖችን ማራባት ብቻ ሳይሆን፤ እንደ ሶማሌ “በይፋ ያልታወጀ” ይሁን እንደ ኢትዮጵያ በይፋ በመንግሥት የተዋቀረ አዋጅ የተዘረጋ “ቋንቋን/ጎሳን መሰረት ያደረገ “ፌደራሊዝም” ሥራ ላይ ሲውል፤  እንደ “ጎበጠ ምስማር” ለማስተካካል እጅግ የሚያስቸግር “ጠማማ” ስርዓት ነው። ለማስተካካል ሲሞከርም ‘እሳት ጭሮ’ በማሕበረሰቡ ውስጥም ሆነ ባካባቢው የሚኖሩ ነገዶች የማያባራ ብጥብጥን ያስከትላል። ፌደራሊዝም ዕብዶች የሚከተሉት የኮለክቲቪስት ርዕዮት ነው የምልበት ምክንያትም ይህ ነው። ሰሞኑን በጉልህ የወጣው የወልቃይት አማራዎች የጥጥቅ ንቅናቄ ስትመለከቱ “Hegemony/ሄጀሞኒ/ወይንም አኔክሰሺን/ በትግርኛ “ጉብጣን” የምንለው፤ አማርኛ ምን አንደሚባል አላውቀውም (ምናልባት ‘መዋጥ/መውረር’ (?)) ያስከተለው ‘ኮሊክቲቪሰት ፋሺሰትቶች” የዘረጉት “ኤትኒክ ፌደራሊዝም” ብሎ የሰየመው አስተዳዳራዊ “የሄጀመኒ” ውጤት ነው። የነገድ ፖለቲካ ማለቂያ የሌለው “ውረር ተዋረር” አቤቱታና ግጭትን የሚያስከትል “ጤነኛ” የነበረ ማሕበረሰብ ወደ “ዕብድነት” ለውጦ “ንክ” የሆነ ማሕበረሰብን የመፍጠር በር ይከፍታል። 

ኤትኒክ ፌደራሊዝም ፋሺስታዊ ነው ብለን መደምደም ብቻ ሳይሆን “አስጎምጂ” መስሎ፤ “ስትይዘው” ግን “ከእጅ አምልጦ” የሚሰበር “ዕንቁላል” ነው። “አስኳሉ” ከፈሰሰ በላ፤ ዕንቁላሉ “መልሼ ልጠግን” ብትል ውጤቱ ፍፁም የማይቻል “የፈሰሰ ውሃን የማፈስ” ከንቱ ሙከራ ይሆናል። አገር ለማፍረሰም ፌደራሊዝም ጥሩ የማፍረሻ ዘዴ ሆኖ የተገኘ “ግማሽ ንኮች/ዕብዶች” የሚከተሉት የአስተዳደር ዘዴ ነው። የውጭ ሃይላትም ወዳጅና አማካሪ መስለው፤ ይህ ሥርዓት እንዲስፋፋ በጉጉት የሚፈልጉትና እጅግ የሚደግፉበት ምክንያታቸው አገርን ያለ ውጊያ በቀላሉ ለማምበርከክ ሲፈልጉ የሚጠቀሙበት ቀላል ዘዴ ስለሆነ ነው። እንድንጠነቀቅ ሁሌም ደጋግሜ የምገልጸው ቃል “ሳብቨርዢን” የምለውም ይህንን አዳጋ የሚያስከትል በመሆኑ ነው።
ይህ አደጋ በተለይ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚከተለው የጎሳ ፌደራላዊ አስተዳዳር “መገንጠልን” ሕጋዊ ያደረገች ብቸኛ  አገር እንደመሆኗ መጠን “የጣሊያን ፋሺስት ወራሪዎች ኢትዮጵያን ለቀው ከሄዱ በላ፤ ለመተግበር አቅደውት ዕቅዳቸው ተቀጭቶ ባጭር የቀረው የመጨረሻ ግባቸው፤ ዛሬ በትግሬዎች መሪነት ግቡን በመምታቱ አንጀታችን እየተቃጠለም ቢሆን ፤ግባችሁ እንደማንኛውም ስርዓት ቀኑ ደርሶ፤ አርጅቶ ራሱ እስኪፈራርስ ድረስ “ፋሺስቶችና የፋሺስት ጀሌዎች እንኳን ደስ አላችሁ” እንላችለን ።

እጅግ የሚገርመው ክስተት ደግሞ፤ ፌደራሊዝም የሚያራምዱ ሊሂቃን፤ ለተመልካች በአካል ጤነኞች ይምሰሉ እንጂ “አገርን የማፍረስ፤ነገድን ከነገድ ማናከስን” የሚያረካቸው እንደ “ልዩ ጀብድ” አድርገው ይመለከቱታል። ስለሆነም በስነእምሮአዊ ጤንነታቸው “ግማሽ ንክ” ናቸው። በተለይ “ኤትኒክ ፌደራሊዝም” (ብሔር/ነገድ ብለው የሚጠሩት የራስ ገዝ ፌደራሊዝም) የሚከተሉ ሰዎች (ኦነግ እና የወያኔ ጀሌዎች ንግግራቸውና ጽሑፋቸውን ስመለከት) “ፋሺዝምን” በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በቀላሉ የሚተረጎምበት አስተዳዳራዊ ስልት መሆኑንም የተረዱ አይመስሉም። እንደምገምተው “ጎሰኛነት አስካሪ ስሜት ስላለው” ፤የሚራመዱት የተወላገደ እርምጃ የት አንደሚረገጥ አይታያቸውም።

 ጎሰኞች ሊፈላሰፉ ፤የኔን አባባል ሊያሳንሱ ይሞክሩ ይሆናል። ሃቁ ግን ፌደራሊዝም ምንም በሉት ምንም፤ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ “ከሌሎች ጋር ተዋህዶ ላለመኖር” ፋሺስቶች የሚመርጡት ‘የመከላከያ ምሽግ’ ነው። አሜሪካም ሆኑ ሌሎች በፌዴራል የሚተዳደሩ አገሮች መነሻቸው “ጥበትን የሚያተኩር/አካባቢያዊ” ስርዓትነው። ለምሳሌ አሜሪካ ስትምለከቱ “ደቡብ/ሳውዝ/” ያሉት የፌዴራል መንግሥታት/ስቴቶች’ የጋራ እይታ፤የጋራ ብልጽግና/አስተዳዳር/… የሚሉ ቃላቶች በሕልማቸውም የለም። ኮለክቲቪስቶች/አካባቢያን/ቡድንተኞች ሆነው ነው የምታይዋቸው። ሆኖም እንደ  ወያኔዎችና ኦነጎችና ኦብነጎች “ጸረ ኢትዮጵያ” አፍራሾች ሳይሆኑ፤ ለአገራቸው ለአሜሪካ የቆሙ፤ በአሜሪካ ላይ ‘ያነጣጠረ’ የፕሮፓጋንዳም ሆነ የአካል ጥቃት ሲመለከቱ አጅግ ላገራቸው ለአሜሪካ የሚብከነከኑ “ናሺናሊሰቶች/ብሔረተኞች” ናቸው።

ሆኖም፤ ፌደራሊዝም አካባቢያዊነትን ስለሚያጎለብት፤ ለተወሰኑ አካባቢ የሚኖሩ “ነጮችን” መብት የቆመ፤የሚከራከር አግላይ የፌዴራል መብት የሚደግፉ ናቸው። ፌዴራሊዝም ያንን አግላይ/ዘረኛ ባሕሪያቸው አንዲጠብቁበት ሙሉ መብት ሰጥቷቸዋል። “Fire Eaters” የተባሉ በፈረንጆች ዘመን አቆጣጠር በ1861 አካባቢ የተነሱ ተገንጣዮች (ካልተሳሳትኩ 13 መንግሥታት ነበሩ ግንጣለን ያቀነቀኑ) መነሻቸው ዛሬ እነ ኦነግ እነ ወያኔ እነ ኦብነግ ወዘተ…..የሚቃዡት “ራስ በራስ ማስተዳዳር” የሚባለው የጎሳ/ዘር አስተዳዳር ተሞርኩዘው “የራስ ገዝ /ፌደራል አስተሰዳዳርን ተቀብለው” ቀስ ብለው፤ ወደ “ግንጣላ ጥያቄ” ያቀነቀኑ የደቡቦች ተገንጣይ ንቅናቄ ክፍሎችን ስናስታውስ፤ የዚህ ቡድን ንቅናቄ አነሳስ ስትምለከቱ ፌደራሊዝምን እንቀበል ከዚያ ግን ጉዱን መርምረን ካልተመቸን ከሰሜኖቹ ‘እስቴቶች’ እንገነጠላላን የሚል ታክቲክ ያዙ።

 አንዳንዶቹ ደግሞ፤ “መነሻቸው” የሆነው “ባርያን/አፍሪካኖቹን” አንደ ንብረት የመቁጠር መብታችን ልንነጠቅ ነው፤ ስለዚህ የእንግሊዝ ኮሎኒ ነበርን፤ ብለው “አንደንትን በማንኳሰስ” እንገንጠል ብለው ወደ ግንጠላ ሄደዋል/ተዋግተዋልም።

ወደ አገራችን ተገንጣዮች ስንመለስ ደግሞ፤ “የጥቁር ሕዝቦችን ክብር” ከትቢያ አንስተው “በወርቅ መንበር እንዲቀመጥ” ዓለምን ያስገደዱ የጥቀር ሕዝቦች ባለውለታ የሆኑት፤ ንጉሳችን አፄ ሚኒሊክን ዛሬ  ተገንጣይ ኦነጎች “Holy War! “the Bloodthirsty Tyrant in Human History. Menlik II of Ethiopia!  (አፍሪካዊ ሂትለር) በማለት የኦሮሞ ነፃ አውጪ ግምባሮችና መሰል ኦሮሞ ድርጅቶች፤ በዩቱብ ቪዲዮ የዘረጉት፤ ፕሮተስታን አስፋፊ ጀርመኖችና፤ ‘ፋሺስት ጣሊያኖች’ የፈጠሩላቸው ፈጠራ ተመርኩዘው፤ አሁን የደረሱበትን ንግግርና መፈክር ስትመለከቱት፤ አዲስ አበባ ውስጥ እየኖሩ “ፌደራል መንግሥቱ እና እኛ የተለያየን አካሎች ነን” አንተዋወቅም/ጎረቤታሞች ስለሆንን ‘መሬታችን’ እሱ አያዘውም በማለት “ነገዳዊ የሆነ ፌደራሊያዊ የራስ ገዝ ቢቀበሉም“ እራሰቸው የቻሉ የተገነጠሉ አገሮች” ሆነው ስለሚቆጥሩ ኦሮሞዎቹ “ፌደራል መንግሥት” ተብየውን “ድምበራችንን አልፈሃል” በማለት “አናውቅህም ብለውታል”። በጣም አስገራሚ ዘመን!

ወደ “ፋየር ኢተሮቹ” ታሪክ ከመመለሳችን በፊት ‘ሰሞኑን’ ባየነው የኦሮሞዎቹ “ድምበራችንን አትዝለል” ተቃውሞ አንድ ምሳሌ ልስጣችሁ።

በቀለ ገርባ ይባላል። ኦሮሞ ፌደራል ፓርቲ ብሎ ራሱን ከወያኔ እውቅና ያገኘ ‘የነገድ ድርጅት’ አማራር ቢሆንም፤ ሲፍቁት ግን ድብቅ  የሆነ “ኦነግ” የሚል ቆዳው ላይ ማንበብ ይቻላል። አስገራሚው ደግሞ፤ ተቃወሚዎችና ሚዲያዎቻቸው ይህ ገንጣይና አፍራሽ ግለሰብ በወያኔ ታስሮ በነበረበት ወቅት “ሃቀኛ ኢትዮጵያዊ” “ለአንድነት የቆመ ነው” እያሉ “ኡ ኡ ሲሉለት ነበር”። ኡኡ እንዲሉለት ሲያሞኟቸው የነበሩ ክፍሎች ደግሞ “ተግንጣይ ቡድኖች ናቸው”። ልክ ታስሮ አንደተፈታ፤ እዚህ አሜሪካ አገር መጥቶ እሳት ላይ ተጋብዞ “አማራዎች አሮሞዎችን ይቅርታ መጠየቅ አለባቸው” ሲል አላመፈር “ፀያፍ ትፋቱን” ተፍቶብን የሄደ “ውለታ ቢስ” ግለሰብ ነው።
 ሰሞኑን የኦሮሞ ተማሪዎች “Burayub KeNga (ቡራዩ የኛ) Sebeta SKenGa!  (ሰበታ የኛ!)” ሆሆታው አስመልክቶ እንዲያብራራ ቃለ መየጥቅ ተደርጎለት እንዲህ ሲል ተናግሯል፦

መጀመሪያ ማኀበረሰብ..ሕዝብ..ብሔርና ብሔረሰብ ሀገርና ክልል የሚለውን ማወቅ አለባችሁ!!
የኦሮሞ ጥያቄ የብሄር ነው…ባሕል ቋንቋችን ክልላችን ከሌላው መደባለቅ የለበትም። አሜሪካ የምትከተለው ፌደራሊዝምና የከተማ መስፋፋት ከእኛ ጋር አንድ አይደለም። እነሱ “አንድ ሕዝብ ናቸው አንድ ቋንቋ ይናገራሉ…” እኛ ግን “ልዩ ህዝቦች ሆነን ኦረሚያና ፌደራሉ መንግስት ጎረቤታሞች ናቸው።”
   ይላል፤ በቀለ ገርባ።

እንግዲህ እንደ ምታውቁት አሜሪካ ከኢትዮጵያ በሰፋ መልኩ “የተለያዩ ነገድ/ቀለም/ባሕል/ባሕሪ/ዘር/እምነት፤ቋንቋ/ፆታ፤ድረጅቶችን” ያቀፈ አገር ነው። ተገንጣዩ በቀለ ገርባ ተከታዮቹን ለማመቻቸት ሲል ግን አሜሪካ “አንድ ሕዝብ” ናቸው፤ “አንድ ቋንቋ” የሚናገሩ ናቸው፤ እኛ ግን “ልዩ ሕዝቦች ነን” “ጎረቤታሞች ነን” ሲል ልዩ አገርና ሕዘብ መሆኑን ግልጽ አድርጎ ነግሮናል።
 “ኦሮሚያ” የተባለ “ክልል” እንደ የአገር አካል/ግዛት ሳይሆን “ልዩ ሕዝብና ጎረቤት” አድርጎ እራሱንና ኦሮሚያን ከኬኒያና ከሱዳን ጋር በማመሳሰል “ያልታወጀ የራሱን ኦሮሚያ የተባለ አገር ቀርፆ መከራከሩን የሚያሳየው “ልክ “ፋየር ኢተሮቹ/ እሳት በሊታ” የተባለው በ1861 አሜሪካ ደቡባዊው ግዛት ክፍል ውስጥ የነበረው ተገንጣይ “ዘረኞች ክፍሎች” ያነሱት የነበረው ጥያቄ ይመሳሰላል። በቀለ ገርባ እና የመሳሰሉ ተገንጣይ ኦሮሞ ኤሊቶች “በወያኔ ማዕቀብ” ውስጥ በመሆናቸው “ጥያቄአችን ግንጣላ ሳይሆን የክልል/ስቴት ራይትስ/ State’s rights ነው” ቢሉም፤ ቀጥተኛ ትኩረታቸው እና ንግግራቸው የሚያመላክተን ‘ቋንቋን፤ባሕልን፤መሬትን” አስታክኮ “ግንጠላን ማራመድ” ነው።

“ፋየር ኢተሮቹ/Fire Eaters” ሲሉት የነበረው፡ ልክ እንደ ወያኔና ኦነግ እንዲሁም መሰል ተገንጣዮች ፌደራሊዝም ለረዢም ጊዜ ተቀብልን “ነፍጠኛን ካባረረን በኋላ፡ “የተወረረብንን መሬትም ካለ እያስመለስን፤ድምበራችን እያስፋፋን እየከለልን ከቆየን በኋላ” አንቀጽ 39ኝን ተጠቅመን ቀስ በቀስ ወደ ግንጣላ እናመራለን እንደሚሉት ሁሉ፡-

“እሳት የላሱ” በመባል የሚጠሩ የደቡብ ነጭ ዘረኞችም በተመሳሳይ ያራመዱት ሂደት አሰሜነኞች ልንዋጥ/ልንተዳዳር ነው፤ “ንብረቶቻችን የሆኑ “አፍሪካኖች” ለኛ እንዳይገዙ፤ በኛ ላይ እንዲነሱ ለማድረግ በሴራቸው ውስጥ አንዲተባባሩ በማድረግ ‘ነፃ’ እንዲወጡ ሊያደርግብን ነው፤ ሰፋፊ ለም እርሻ መሬቶቻችንንና ዓሳ መፈልፈያ ሃይቆቻችን፤ወንዞችና የባሕር ውሃዎቻችን ሊሻሙን ነው። ስለዚህ ፌደራል መንግሥት የተባለው የሰሜኑ ክፍል፤ ወደ ደቡባዊ ድምበር ተሻግሮ “ልማትን ማስፋፋት፤ አስተዳዳራዊ መዋቅርን ጣልቃ መግባት፤ድምበራችንን መነካካት” የለበትም ባይ ናቸው። እኛ ከሰሜኑ የሚለየን ልዩ ባሕል አለን።አንድ ያደረግን ነገር ቢኖር በእንግሊዝ ቅንመበር “አገራችን” ተይዞ በኮሎኒ ተይዘን የነበርን ነን” አሁን ግን ከሌሎች አካባቢዎች እየፈለሱ እየተዳቀሉ መሬቶቻችን ሊሻሙን ነው ባዮች ነበሩ።

Professor Charles B Dew’s የተባሉ ‘Apostles of Disunion” በሚል መጽሐፋቸው በትክክል የሚሉት “race and slavery, not States’ rights, were what motivated Southerners to secede.ይላሉ። በቀለ ግርባም ሆኑ ኦሮሞ የጎሳ ኤሊቶችም ያሳሰባቸው ነገር “የክልል መብት ሳይሆን፤ ባሕላችን፤ቋንቋችን በሌሎች መጤዎች ሊዋጥ ነው፤ሊበላሽ ነው” ሲሉ በግልጽ እየተናገሩ ነው/ሳይሸሽጉ!!!!።  ይህንን አበክራችሁ አስተውሉ። ፋሺስዝም ‘የጎሳ ጥራትን” ያቀነቅናል የምለውም ለዚህ ነው።

ደቡቦቹ ያሳሰባቸው በፌደራሉ ስርዓት ተደማጭነትና ቦታ ያላቸው መሆኑን ቢያውቁም ደቡቦቹ  ወደ መገንጠሉ ያቀነቀኑበት ምክንያት ይላሉ ፕሮፌሰር ቻርለስ፤-

With the above brief historical sketch one can understand why Southerners in the mid-nineteenth century were on the defensive. Their economy was extremely strong and their power in the US Federal Government was impressive yet their position was being gradually undermined by the North’s fast-growing (due to immigration) population and western expansion. Southerners saw a time approaching when they would be unable to stop anti-Southern legislation in the US Congress. The prospect of this was frightening given the increasingly radical political noises that came out of the Northeast and Upper Midwest. The Era of Good Feelings was over; the North and South were locked in a struggle for political supremacy, control of the Union and, ultimately, cultural and economic survival.”

የሚገርመው ነገር በፌደራላዊ ሥርዓት ሆነውም “ነጮቹ ባርነትን እንደ ሕጋዊ ንብረት የመያዛቸው መብታቸው የጠበቀላቸው የፌደራል ስርዓት ነበር” ይህ በላ አነሳዋለሁ። እንዲያም ሆነው፤ በፌደራል ሥርዓት መኖር አልረኩም። ምከንያቱም፤ ከላይ ያያችሁት አንዱ ምክንያት፤ የሰሜኑ ክፍል በልማትና በሕዝብ ወደ ደቡቡና ማዕከላዊ ምዕራባዊ አሜሪካ ግዛት ፍልሰት መቀጠልን ሲገነዘቡ፤ እንዲሁም “ሥር ነቀል” ፖለቲካዊ ንቃት የማደጉ ጉዳይ ወደ እነሱ እንዳይዘመት በመስጋት “ከዚህ ወዲህ አትለፍ” “ይህ “የኛ ድምበር ነው” ፤ “እኛና ፌደራሉ ጎረቤታሞች ነን”፤ አንተ እዚህ መገንባት አትችልም፡” በማለት ነው ግንጣላቸው መነሻ የሚያደርገው። ይህንን ስትመለከት፤ የነ በቀለ ገርባና ኦሮሞዎቹ ንቅናቄ/ተቃውሞ ልክ አንደ “እሳት የላሱ” ዘረኛ ነጭ ተዋጊዎች የኛዎቹ “ኦሮሞ ለኦሮሞ!” ኢትዮጵያ አውት ኦፍ ኦሮሚያ” ፈካሪዎች “በግልጽ አንዳስቀመጡት፤ Burayub KeNga (ቡራዩ የኛ)  Sebeta SKenGa!  (ሰበታ የኛ) የሚለው መፈክር በግልጽ ከተቀሩት የግንጣላ አቀንቃኞችና ፋሺዝምን በሕገ መንግሥት ሕጋዊነት እንዲኖረው ያጸደቀውና የጻፈው መንግሥት ቡድን ጋር “በድምበር መሳሳብና በልማት ሰበብ” ግብግብ መግጠማቸው የሚያሳየን “They are locked in a struggle for political supremacy”.

 ሁለቱም (ወያኔና የተቀሩት አሁን በሥሩ ያሉት የክልል ነገሥታቶች)  አገር በሚያፈርስ የፋሺስት ዲዛይን/ክልል ተሞርኩዘው በግብግብ ትግል በሚገኙበት በዛሬው ወቅት፤ “the Responsibility of intellecctuals” የኢትዮጵያ ምሁራን ሃላፊነት፤ በተለይም “አንድነትን” የሚከተሉ “ኢትዮጵያዊነታቸው የሚያምኑ” ምሁራንና ሚዲያዎቻቸው፤ “ከዚህ ድምበር ወዲያ እኛና ፌደራሉ ጎረቤታሞች ነን፤ ማንም ኢትዮጵያዊ  በሱሉልታ፤በቡራዩ፤ በመላ ኦሮሚያ ክልል ‘ማረስ፤ መገንባት፤መራመድ፤መስፋፋት፤ ሰርቶ ገንብቶ መኖር፤የተከለከለ ነው’” በማለት እንደ ዶናል ትራምፕ” ድምበራቸው ዙርያ ላይ “ግንብ ለሚያጥሩት” የዘመናችን “Fire Eaters” ፋሺስታዊ ንቅናቄ አራማጆች፤ መልስ ብለው በየድረገጹ የሚጽፉላቸው ጽሑፍና “እሰጥ አገባ” መልስ ፈራ ተባ በማለት ‘አድርባይነታቸው” ዛሬም እንዳልለቀቃቸው በግልጽ ማየት ችያለሁ።

የኦሮሞ ምሁራን ተብየዎች የሚያቀጣጥሉት ትግል የኦሮሞ ገበሬዎች መብት ለመከላከል በሚል ሽፋን እያስተጋቡት ያሉት ነጥብ፤ ቢመረመር (እነ ጃዋር መሐመድ እስከ ጅማ ድረስ ትናንት ድረስ ወጣቶችን ሳነጋግር ነበር የዋልኩት፤ እያለ የልጅነት ጀብደኝነቱን ለማሳየት ወጣቶች በወያኔ ሰንሰለት ሥር እንዲገቡ ምክንያት እየሆነ፤ በግልጽ በሚዲያ የሚናገረው ምራቁ ያልዋጠ ጀብደኝነት ባሕሪው ወደ ጎን ትተን) የኦሮሞ ገንጣዮች በጉልህ የምናየው ፍላጎታቸው የታዘብነው ነገር አለ።  እሱም፦

 “ኦሮሞዎች፤በሕዝብ ብዛት ተመሳሳይ ከሆነው ከአማራው ነገድ እጅግ የተሻለ /መጠነኛም ቢሆን ‘የራስ ገዝ’ አስተዳደር መጎናጸፋቸው አሌ የማይባል ነው (ወያኔ በበላይ ሆኖ ቢያዘቸውም፤ አማራን/”ነፍጠኛን”/ ማባረርን በሕግም በንግግርም ከወያኔዎችና ከኦነጎች የተላለፈላቸው መብት ተሰጥቶአቸዋል።) ስለሆነም ነው ጥያቄአቸው፤

 “ኦሮሞ ከሌላ ማሕበረሰብ ጋር አንዳይቀላቀል ፍራቻ አለን፤ባሕላችን እንዳይበረዝብን ፍራቻ አለን፤በላቲን የምንጽፈው ቋንቋችን በኢትዮጵያዊያ ፊደል እንዳይበከልብን ስለሰጋን አዲስ አበባ ወደ እኛው እየተስፈፋች ከመጣች ማቆሚያ ስለማይኖራት “መጤዎች ደማችን፤ፖለቲካችን፤ፍትሓዊ ስርዓታችን፤ ባሕላችንን ያቆሽሹብናል” ሲሉ በአደባባይ የሚሟገቱት ምክንያት ግልጽ ነው።

*፡ዘራችን፡* የተለየ ስለሆነ “ኦሮሞ ያልሆነ” “ማንም” እየመጣ፤ እየገፋ ድምበር በጣሰ ቁጥር፤ ማንነታችን ከሌሎች ጋር እየተቀላቀለ “የቆሸሰ ማንነት/ባህልና ደም” ለመቀበል እንዳንገደድ “ከቡራዩ፤ከሱስሉልታ” ወዲያ ማለፍ በጥብቅ የተከለከለ ነው” ማለታቸው  ፋሺስቶች/የኢጣሊያን ሙሶሊኒዎች/የአሜሪካ ደቡባዊ ግዛት ‘ነጮች’ ከጥቁር ዜጎችና ፈልሰው ከየዓለማቱ ወደ ደቡብ ክፍል በሚፈልሱ ስደተኞች ጋር ደማችን ባህላችን ቋንቋችን እንዳይበከልብን “ድምበራችን መከለል/መዝጋት” አለበት ሲሉ racial amalgamation / መቀላቀሉን መቀበል ማለት ለኦሮሞዎቹ (which would mean the end of… ) የኦሮሞ ህልውናን የመጻረር ነው ሲሉ ደምድመዋል።

ፋሺስቶች ራሳቸውን የሚመለከቱት “as a distinct ethnic group” ስለሆነ፤ ከሰዎችነት የተለየ ከመጤዎች ጋር መቀላቀል የማይገባው ‘ልዩ’ የሆነ ማሕበርሰብ ነው” ብለው ስለሚያምኑ፡ ኦሮሞዎቹ “በግማሽ ንክ” ምሁራኖቻቸው በሚመሩት በሚመራ ጠባብ “የጎሳ ፍቅር” እየተመረዙ በእንዲህ ያለ scenario ትዕይንት ገብተው ግብግብ ገጥመው በምንም መልኩ አንቀበልም የሚሉበት ምክንያታቸውም “ደማቸውን ላለማቆሸሽ” ነው።ራት ነጥብ!

 ከተቀላቀሉ “ባህላችን፤ቋንቋችን፤ማንንታችን ይበከላል” የሚሉት ሲተረጎም “ንፁህ ኦሮሞኣዊ ደም ከቆሸሸው የሌሎች ነገድ ደም ጋር በማቀላቀል አናቆሽሽም” የሚለው ግልባጭ ትርጉም ይሰጠናል። ኮለክቲቪስት ማሕበረሰብ፤ ከግለሰቦች/ የሚለያቸው ኢንዲቪጂዋልስቲክ አራማጆች ጋር ከተዋሃዱ “ማንነታችን እናጣለን” የሚል ክርክራቸው፤ ሲጤን የሰው ልጆችን መዋሃድ የሚቃወሙ መሆናቸው አያከራክርም።

 racial amalgamation ወይንም ሌላ ነገድ ላለመዋሃድ የሚደመጠው የነ በቀለ ገርባ ክርክር ሲጤን፤ወይንም ኦሮሞ ተማሪዎቹ Burayub KeNga (ቡራዩ የኛ)  Sebeta SKenGa!  (ሰበታ የኛ) በሚለው መፈክርራቸው የተደገፈው “የድምበር ይያቄ ግጭት”   በገቤሬዎች የመሬት መብት “ሽፋን” ቢንጸባረቅም ኢትዮጵያዊያን አይደለንም ነው የሚሉት። ሲጀመር እስኪያልቅ በወያኔ ስርዓት የኔ ነው ብሎ ገበሬው የራሱ የሚሸጠውና የሚለውጠው መሬት የለውምና!!! ስለዚህ ክርክሩ አጉል ሆኖ “ለግንጣላ ዓላማ ቅስቀሳ እንዲመች” ግን እንደ በንዚን ሆኖ አገልግሎአቸዋል።

በሚቀጥለው ስለ የጎሳ ፖለቲካ ወያኔና ኦነግ ለምን እንደሚጋጩ በጥልቀት አቀርባለሁ። ከዚያም ጊዜ ከተገኘ “ጸጋዬ አራርሶ” የተባለ የፌደራል አቀንቃኝ ቅስቀሳው እንመለከታለን። ይህ ግለሰብ የሕግ ምሁር ነው። አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕግና የሕገመንግሥት መምህር ነበርኩ የሚል ነው። ይህ “ኦነግ” ያልሆነ “አዲስ ኦነግ” ደግሞ ብቅ ብሎላችልና ለፍልፎ እስኪተነፍስ ድረስ አዲስ የሕግ ተንታኝ ብለው “ቪ ኦ ኦ ዎች” ሰሞኑን “እየወለወሉልን” ነው።

ሰውየው ካሁን በፊት ከተዋጣለት ጋዜጠኛው ወንድም ካሳሁን (የአውስትራልያ S B S ራዲዮ አዘጋጅ) ጋር ባንድ ወቅት አንቀጽ 39ኝ ዙሪያ አስመልክቶ ጋዜጠኛ ካሳሁን “ፀጋየ አራርሶን” ሲጠይቀው “አንቀጽ 39 ወደፊትም ዛሬም መኖር ያለበት የኢትዮጵያ አንድነት የዋስትና አርማ ነው” ሲል ፋሺሰታዊ አንቀጽ ሲከላከል አድምጣናል። አዲስ በመሆኑ፤ ማሕደሩና ማንነቱ ባናውቀውም፤ይህ “ኒሂሊስቶች ርዕዮት” የሚከተል ወጣት፤ ወያኔ በሚቆጣጠረው ትምህረት ተቋም በሕግ ትምሕርት ሲያሰተምር የነበረ ዛሬ ለዶክተሬት ትምሕርት እዚህ ተልኮ “እሳት የላሰ ኤክስፐርት” ለመሆን እየተሯሯጠ ነው። በዚህ እምለስበታለሁ።

ጸጋዬ አራርሶ አንቀጽ 39 በመጪው ስርዓት የሚደነገግ ሕገመንግሥት እንዳይፈርስ ሲከራከር፤ “የጎሳ ፌደራሊዝም” አቀንቃኞች፤ “Burayub KeNga (ቡራዩ የኛ)  Sebeta KenGa!  (ሰበታ የኛ)” የሚለው የነ ጃዋር መሓመዳዊያን መፈክር የሚደግፍ መሆኑን ሰሞኑን በቪኦኤ ተደምጧል።  “ኢትዮጵያዊ ዜግንትን ለመንጠቅ “በመከለል”፤ አገር ለማፍረስ ደግሞ “ሬፈረንደም” ተጠቅሞ ማስገንጠልን” ለሰው ልጆች እድገትና ጤነኛ ፖለቲካ ነው ብለው የሚሰብኩ ምሁራን “ግማሽ ዕብደት” የተጠናወታቸው ፖለቲከኞች ናቸው፤ የምለውም ለዚህ ነው። ወያኔ መሬታችሁ ነው ብሎ ኦሮሞዎችን ከሰጣቸው “ማንም ሰው ከዚህ ድምብር ማለፍና ማልማት ክልክል ነው” ብለው ቢሉ ጥፋቱ የነሱ ሳይሆን “ፌደራል” የሚባለው “ወያኔም” ሙሉ በሙሉ የራሱ ጥፋት መሆኑን እንመለከታለን። ዝርዝሩ በክፍል 2 እንመለከታለን፡….. ይቀጥላል፡
አመሰግናለሁ፤
ጌታቸው ረዳ Ethiopian semay ብሎግ አዘጋጅ ( getachre@aol.com )