Friday, January 29, 2016

የተቃዋሚ ሚዲያዎችና ድርጅቶች ኢትዮጵያን ለማበጣበጥ የተነሱትን የኦሮሞ ፋሺስቶችን እያገዙ ናቸው! ጌታቸው ረዳ (Editor Ethiopian Semay)



የተቃዋሚ ሚዲያዎችና ድርጅቶች ኢትዮጵያን ለማበጣበጥ የተነሱትን የኦሮሞ ፋሺስቶችን እያገዙ ናቸው!
ጌታቸው ረዳ (Editor Ethiopian Semay)
Getachew Reda -Editor Ethiopian semay
እንደ ወትሮው ወድ ወንድሞችና እህቶች የደብዳቤ መልእክትና ስልክ በመጻፍና በመደወል፤ በርታ ብላችሁ ላበረታታችሁኝ  ወገኖች ጊዜአችሁን ሰውታችሁ ለምታበረክቱልኝ አበራታች ልሳን ሁሉ ዛሬም እጅግ አመሰግናለሁ።

ይህ ጽሑፍ ካለፈው ክፍል 1 ‘ቅር ሳይላቸው የሚናደፉ ፖለቲከኞች’ ከሚለው ተያያዥነት ያለው ቀጣይ (ክፍል 2) ትችት ነው። በርካታ ፋሺስት ግለሰቦችና ድርጅቶች ከ1983 ዓ.ም ጀምሮ በአገራችን ተከስተዋል። በነዚህ ፋሺሰት ግለሰቦችና ድርጅቶች ምክንያት በሚሊዮኖች እና ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ለስደትና ለሞት ተዳርገዋል። ከነዚህ ፋሺሰቶች ውስጥ ግምባር ቀደምትነቱን የያዙት የወያኔ ትግሬ እና ብዙዎቹ የኦሮሞ ድርጅቶች አሉበት።

ሁለቱም ድርጅቶች እጅግ አሰቃቂ የሆነ በዓለም የፍርድ ተቋማት የሚያስጠይቃቸው በአማራ ማሕበረሰብ ላይ “የዘር ማጥፋት” (ጀነሳይድ) ወንጀል ፈጽመዋል። ይህ ወንጀል በአማራ ማሕበረሰብ ለመፈጸምም ሆነ ኢትዮጵያ እንደ አገር አንደማትቀጥል ለማበጣበጥ በፖሊሲያቸው የቀረጹት መርሃ ግብር ተከትለው ነበር የፈጸሙት። ለዚህም ሳይፈሩና ሳይሸማቀቁ እስካሁን ድርስ ድርጊቱ ለመፈጸም ወደ ሗላ እንደማይሉ አሁን እየፈጸሙት እንደሚገኙ የነዚህ ድርጅቶች ሰለባ የሆኑ በሕይወት የተረፉ ጉዳተኞች ከሚናገሩት የአውድዮ፤ የፎሮግራፍና የጽሑፍ ማስረጃዎች ማረጋገጥ ተችሏል።

በተለይ ሽግግሩ መንግስት ምስረታ በመሪነት የተካፈሉ የአሮሞ ማሕበረሰብ ግለሰቦች፤ በኦፒዲኦ፤ በኦነግና በእስላማዊ ኦሮሞ ድርጅቶች ውስጥ የነበሩ በወንጀሉ ስራ የተካፈሉ የበላይና በታች ወታደራዊ/የሽምቅ ተዋጊ እና ነጋዴ ግለሰቦች የነበሩ፤ ዛሬ አሜሪካና አውሮጳ በስደት ተሰግስገው እንደሚገኙ፤ ጉዳዩ የሚከታተሉ አገር ወዳዶች ባጠኑት መሰረት አድራሻና የሚሰሩበት ቦታ ከነፎቶግራፋቸው እነ ማን አንደሆኑ አይቻለሁ። ግድያውና ጭፍጨፋው ሲፈጸም በመሪነት የነበሩና በወያኔ ፋሺስታዊ ስርዓት በሚኒሰትርነትና እና አስተዳዳሪነት ደራጃ ተሹሞው፤ የኦሮሞን ማሕበረሰብ ወክለናል ብለው ድርጊቱ ሲፈጸም ግፋ በለው ሲሉ የነበሩ ከፍተኛ የኦነግ ፖለቲካ መሪዎች፤ ዛሬም ‘ሳይጸጽታቸው’ነባርና አዳዳስ የተለያዩ የኦሮሞ ድርጅቶችን በመምራት “አጼ ምኒሊክን” በመወረፍ “አማራን በመወረፍ” “አገራችን ኢትዮጵያን በመዝለፍ” በየፓልቶክና ድረገፆች በመጻፍና በሚሰጡት ቃለ መጠይቅ እያደመጥናቸው ነው። 

ይግረም ብለው ድግሞ፤ ተቃወሚ ነን የሚሉ ጥቂት ግለሰቦች፤  እኛም አማራዎች ነንየሚል መግለጫ ሳያወጡ፤ ዛሬእኔም አሮሞ ነኝ/እኛም ኦሮሞዎች ነንየሚል አድላዊ መግለጫ እያስደመጡን ነው። በትግሬዎችና በኦሮሞ ፏሺስት ግለሰቦችና ድርጅቶች በሚሊዮን የተፈጀው አማራ፤ ሚስቱን በወሮበላ ኦሮሞዎችና በትግሬ ወሮበላዎች የተደፈረችበት አማራ፤ ንብረቱን የተነጠቀ አማራ፤ ለም መሬቱ የተነጠቀው አማራ፤ ሲያለቅስ እያዩ ፤እየሰሙእኔም አማራ ነኝ፤እኛም አማራ ነንብለው ፈርመው መግለጫ ያለማውጣታቸው ይገርማል።

ይህ ኦሮሞ የተባለ ማሕበረሰብ እንዴት ዕደለኛ ነው? 16ኘው ክፍለ ዘመን ጅምሮ በወረራ የተያዘውን መሬት እያደር ባለቤት ሆኖ፤ ከዚህ እንዳታልፉ እያለን ነው። በ1983 / ደግሞ በጠመንጃ ሃይል በወያኔ ፈቃጅነትና ሻጥር/ኮንስፒራሲ ሰፊ መሬት በካርታ ተከልሎለት ባለቤት ሆኖማንም ከዚህ እንዳያልፍ እያለ/ ’ኦሮሚያ ኬኛ’ መፈክር’ ከተማሪዎቹ ጋር አብሮ ሲጮህ አይተናል። 

አማራ ጡታችንን ቆረጠንብሎ ኦኖሌ የተባለ የፈጠራ ሃውልት ተመስርቶለት፤ በጭፈራ ተደስቶ አማራን የሚዘልፍ፤ የሃሰት ሃውልት አሜን ብሎ ተቀብሎ የመኖሩ ጉዳይ ሳስበው፤ዛሬምእኔም ኦሮሞ ነኝ’ የሚሉ ትግሬዎች ማግኘቱ ዕድለኛ ነው ያሰኛል። ወይ ምስኪኑ አማራ ሞት ብቻ ሳይሆን ስጋህንም አጥንትህንም በሰው ልጆች እንደ ጅብ ተበላህ! አማራ ሆይ ማን ይጩህልህ?ማን ይጨነቅልህ? ምንስ ይበጅህ ይሆን!
 
በጣም የሚገርመው ደግሞ “ዊኪ ፔዲያ” በሚባለው ድረግጽ ስትገቡ “ክራይም ኢን ኢትዮጵያ/ የወንጀል ዓይነቶች በኢትዮጵያ” በሚለው ርዕስ  ውስጥ 10 የወንጅል ዓይነት/ካታጎሪ ድርጊቶች በኢትዮጵያ ምድር ውስጥ መፈጸማቸው ሲገልጽ “በሚሊዮኖች ነብሳት የቀጠፈው በኦሮሞ ድርጅቶችና በወያኔዎች የተፈጸመው፤ በአማራ ማሕበረሰብ የተፈጸመው የዘር ጭፍጨፋ /ጀነሳይድ/” አንድም የጠቀሰው ነገር የለም። እስከዚህ ድረስ ምሁራኖችና ተቃዋሚ ድርጅቶች ስራቸውን እንዳልሰሩ ማየት ትችላላችሁ። ወንጀል ተብለው የተዘረዘሩት ‘ስርቆት፤ጠመንጃ መተኮስ፤ በሴቶች ላይ አመጽ፤ ወዘተ……ወዘተ…ናቸው። እንግዲህ በአማራ ገበሬ ቀረጥ/ታክስ ተመግበውና ተምረው የሕግ ባለሙያ የሆኑ ምሁራኖቻችን ምንኛ “የትልቁ ዳቦ ሊጦች” መሆናቸወን መገመት አያቅታችሁም።

ይህ እንዲህ ሲሆን፤ አገር ውስጥ ያሉ በወያኔ ስር ተሰግስገው ባንድ በኩል የወያኔ ተላለኪነት ሥራቸውን ሲያከናውኑ፤ ባንድ በኩል ደግሞ ‘ኦ ፒ ዲ ኦ’ በሚል ስም የሚጠሩ ‘ድብቅ’ ኦነጎች ሆነው፤ በአማራ ሕብረተሰብ የተፈጸመ የዘር ፍጅት ወንጀላቸውን ለመደበቅ ሲሉ፤ ተበዳይ መስለው ኦሮሞ “በምኒልክና በአማራ ነፍጠኞች” የኦሮሞ ሴቶች “ጡት” ተቆርጧል እያሉ በታሪክና በራሳቸው ሊቃውንት ሳይቀር የተጻፈና የተረጋገጠ የራሳቸውን “የመስለብ ባሕል” ወደ አማራው በማላከክ “ኦኖሌ” የሚል ጥላቻን የሚያድስ፤ የውሸት ሃውልት አቁመው “የዛሬ ወጣት ኦሮሞዎች” ኢትዮጵያዊነታቸውን አስክደው፤ “ኦሮሞ ነኝ” እንዲል እና “ኦሮሚያ የሚባል አገር እንጂ፤ ኢትዮጵያ/አቢሲኒያ/አበሻ ከሚባል አገር አይደለሁም” እንዲል በመስበክ አስክደውታል።

የራሱን ባንዴራ አስሰፍቶ ሲያውለብልብና በላቲን ፊደል የሚጻፍ ኦሮሚኛ በትምህርት ገበታ እያስተማሩ፤ ከተቀረው የኢትዮጵያ ማሕበረሰብ የሚግባባበት ቋንቋ አጥቶ፤ ‘በማይታይ ግምብ እራሱን አጥሮ’ “ደንቁሮ እንዲቀር” በማድረግ ከፍተኛ የሆነ ትውልድን የማደንቆር የወንጀል ድርጊት እየሰሩ ይገኛሉ። አገር ደርሰው የመጡ ሰዎች ሲነግሩን እጅግ ያሳዝናል። 

እነዚህ ፋሺስቶች ሁሉም እንደ የወንጀል ሱታፌአቸው እስከዛሬ ድረስ ፍርዳቸው ሳያገኙ እየቆጨንና እንዴት ወደ አለም ፍርድ ቤት መቅረብ እንዳለባቸው ጥቂት አገር ወዳዶች ተጨንቀው ተጠብበው ሌት ተቀን ሲጥሩ፤ ተቃዋሚ ነን የሚሉ ግን ‘23’ አመት የወያኔን ዕድሜ እያራዘሙ፤ ሕብረተሰባችን ሲያጃጅሉ ነበሩ። ዛሬም ከማጃጃል ተግባራቸው ሳይቆጠቡ “እኔም/እኛም ኦሮሞ ነን/ነኝ” እያሉ ኦሮሞ አሁን ያለበትን ማሕበራዊ ስነልቦና ሳያጤኑ “ከኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት” የተነጣጠለበትን ክር ተበጥሶ እያዩ ዛሬም ስለ ኦሮሞነት እየሰበኩ፤ የተገንጣዮችና የፋሺስት መርሃ ግብር በመደገፍ ላይ ናቸው።

ተቃዋሚዎቹ ምንም እርባና እንደሌላቸው ለብዙ አመታት ስከራከር ማመን እምቢ ብለውኝ፤ እኔን ሲዘልፉ የነበሩ ሁሉ “ተቃዋሚዎቻቸውን” ወያኔን ከስልጣን ሊያስወግዱልን ነው እያሉ ወደ ውጭ አገር እያስመጡ ሲያሞካሽዋቸው፤በየሬስቶራንቱ እያዞሩ ሲመግቧቸው የነበሩትን ሁሉ ዛሬ ውጤታቸው ምን እንደሆነ አይታችሁታል። ዛሬም ቃሌ ያው ነው። ተቃዋሚ የሚባል ማጭበርበሪያ ምናልባትም አንዳንዶቹ ወያኔ ያስሰለፋቸው ሆነው ብዙዎቹ ግን በፍርሃት የተሸበቡ፤ “ሰላመዊ ሰልፍ” ሳይሆን “ሰላማዊ ዕንቅልፍ” ሲለጥጡ የነበሩ ዛሬም እንቅልፍ ላይ የሚገኙ ናቸውና ፤በዚህ እርማችሁን አውጡ!

ዛሬ ለበርካታ አመታት ስነግራችሁ የነበረውን ሃቅ እውነታነቱ ኮለል ብሎ እየታዬ ነው። ከጥቂቶች በቀር አብዛኛዎቹ “በተለይ ዋና፤ዋና የሚባሉ ሚዲያዎች” ዛሬ እየዘገቡትና እየደሰኮሩት ያሉት በሚገርምና ባስደንጋጭ ሁኔታ የምታዩት ያንኑ ሳስጠነቅቃችሁ የነበረውን የጠላት ፕሮፓጋንዳ መሳሪያ ሆነው ሚዲያቸው በተገንጣዮች ፕሮፓጋንዳና ቃለ መጠይቅ ተጣቧል። የኦሮሞ ተገንጣይ ፋሺስት ድርጅቶች የኢትዮጵያን ተቃዋሚና ሕብረተሰብ ‘ሳብቨርት’ የማድረግ የመጀመሪያ አጀንዳቸው ባልጠበቁት እምርታ ተቃዋሚ ሚዲያዎች እያሳኩላቸው ነው። ተሸናፊዎቹ እራሰቸው ተምበረካኪ ሆነው ሕዝባችን ለተገንጣይ ፕሮፓጋንዳ እንዲንበረከክ እየጣሩ ነው።

ሕዝባችን የዘመናችን የባንዳዎች መልክ ተለዋዋጭ በመሆኑ ተሎ ለይቶ ለማወቅ እንደቸገረው ብዙ ምልክቶች እናያለን።አንድ ወዳጄ አንደጠረጠረው፤ አንዳንዶቹ የሚዲያ በለቤቶች፤ ትውልድ ሐረጋቸውና ብዙውን እድሜአቸው ያደጉት ኦሮሞ አካባቢ ስለሆነ  ኦሮሞ ጋር የተገናኘ ሆኖ ‘አሁን አሁን’ ሳስበው “የኦነግ” ሰላዮች ሳይሆኑ አንዳልቀሩ እጠረጥራለሁ ብሎኛል።

ለበርካታ አመታት አማራው በወያኔ/ኦነግ/ሻዕቢያ እና አሽከሮቻቸው አማካይነት በፖሊሲ ተቀይሶለት በላዩ ላይ “ጀነሳይድ” የዘር እልቂት እንዲፈጸምበት ሲወሰን፤ በትምህርት ዓለም ከነበሩበት ጊዜ ጀምሮ፤ ጫካ ከወጡበት አንስተው በተስማሙት መሰረት፤ አማራው ጭፍጨፋ ሲፈጸምበት፤ተቃዋሚውና በተቃዋሚነት ቆመናል የሚሉ ‘የሃሰት ተቃዋሚ’ የዜና ማሰራጫ መደብሮች/ድረገፆች/ራዲዮኖች፤ አማራው ሕብረተሰብ በተጠቀሱት “ነብሰገዳዮች” እንደበግ አንገቱ በቢላዋ ሲታረድ “ሆን ብለው” የኢትዮጵያ ሕዝብ እና የአማራ ወጣት ዜናው እንዳይሰማውና በነብሰ ገዳዮቹ ላይ “የአመጽና የሕግ ጥያቄ” እንዳያነሳ ስለ “ዲሞክራሲና መድበለ ፓርቲ ግንባታ” *ብቻ* እንዲያተኩር እየሰበኩ የአማራው ‘ደምና ሬሳ’ የትም ፈስሶ እና ተጥሎ እንዲቀር ከፍተኛ ድርሻ አድርገዋል።ለዚህም ተጠያቂዎች አድርጌአቸዋለሁ።

ተቃዋሚዎቹ፤ጋዜጠኞቹ እስርቤት የገቡም ያልገቡም፤አብዛኛዎቹ ሲነታረኩበት የነበረው ንትርክ “ዲሞክራሲ…፤ ዲሞክራሲ፤….ዲሞክራሲ..ሕብረት፤አንድነት፤ጥምረት፤” በሚል እራሳቸው ተጃጅለው አዲሱን ትውልድ አጃጅለውታል። ስለ አገር፤ስለ ሕዝብ ምን እና ምን ግምባር ቀደም አጀንዳ ተቀርጾላቸው ለትግል መቅረብ እንዳለባቸው ለሕዝቡ የቀረጹለት የማታገያ ስልትና የመዳረሻ ምዕራፍ የላቸውም። ተቃዋሚዎች ወጣቱን የቀረጹት “ዲሞክራሲ” የሚባል “የሥልጣን ጥመኞች፤ ሃሰተኛ ልሂቃን፤ ፋሺስቶችና ናዚዎች፤ ብዙሃን በጥቂቶችና በግለሰቦች መብት የሚጫኑበት፤ እራሱ ፈጥሮ እራሱን የሚገድል ሥርዓት” ማስፈን አለብህ እያሉ ሲያጃጅሉት፤ 

ወያኔ ደግሞ “ከሕብረተሰቡ እቅም በላይ የሆኑ ያጌጡ ልብሶችና መኪኖች አገር ውስጥ እንዲሸጡ በማድረግ፤ያንኑ ለማጌጥ ሲል፤ ግድያና ንቅዘት እንዲገባ በዘዴ ሕሊናውን በመጥለፍ፤ ጫት፤ሽርሙጥና፤መጠጥ፤ የወንዳገረድ ዝሙት፤ስርቆት፤ሀሰት፤ማጃጃያ የሆኑ ልብን የሚነጥቁ የመዝናኛ፤ የቀልድና የዳንስ መድረኮች፤ የቁንጅና ውድድር፤የዝሙት ፊልሞችና ዕፆች፤ እንዲሁም አክራሪ ሃይመኖቶችን…..” የመሳሰሉ ማታለያ ስልቶችን ‘በአዲሱ ዓለም ሕግ’ መሪዎች፤ አገር ለማፍረስ በተሰማሩ በውስጥና በውጭ አገር ሰላዮች እየተመራ ፤ እነዚህን አታላይ ስልቶችን በየከተማው የሚዘረጉለት “የሰው አሳማዎች” በመቅጠር እንዲስፋፉ በማድረግ ፤ሕብረተሰቡ ሥልጣኑን እንዳይቀናቀኑት አደንዝዞአቸው ይገኛል።

ካለይ የተጠቀሱ ‘አገር ገዳይ’ ስልቶችን ከኢምፔሪያሊስቶቹ እና አሽከሮቹ የምንጠብቀው ተልእኮ ነው። ያልተጠበቀው ግን ‘ተቃዋሚ ነን” እያሉ “አገር ለመግደል” ተራችሁ ጠብቁ ተብለው “በመጠባበቅ ለይ ያሉ”  በሁለተኛ ዙር የተመደቡ ጸረ ኢትዮጵያ ሃይሎችን “ድረገጾቻቸውና ራዲዮኖቻቸው” ነፃ በመልቀቅ “የድምጽ ማጉያዎቻቸው” ሆነው በማገልገል መሆናቸው ደጋግመን ስንታዘብ እንቆቁሉሽ ሆኖብናል።

ተቃዋሚዎችና ሚዲያዎቻቸው ለኦሮሞ ፋሺስቶች መቆማቸው አዲስ አልነበረም። ለምሳሌ በግልጽ ክልልን መሰረት ያደረገ የነገድ/ኤትኒክ ፌዴራሊዝም የተባለ “የፋሺስቶች አስተዳዳር” እንደግፋለን ብሎ በግልጽ መግለጫ ያወጣ ECADF የተባለው ዛሬ በግንቦት 7 ዕዝ ስር የሚንቀሳቀስ ድረገጽ Ethiopia After Meles: International Crisis Group report
Posted by: ecadforum  August 22, 2012  በሚል ርዕስ ያሰፈረውን እንመለክት፤

“In recent years, Meles had relied ever more on repression to quell growing dissent. His successor will lead a weaker regime that struggles to manage increasing unrest unless it truly implements ethnic federalism and institutes fundamental governance reform.” ሲል የፋሺስቶችን የነገድ ፌደራሊዝም ሕጋዊ ሆኖ ቀጣይ እንዲሆን በመግለጫ አቋሙን ነግሮናል። ኢትዮጵያ ሰላም ለማምጣት “ፋሺስታዊና አፓርተይዳዊ የሆነ ቋንቋን መሰረት ያደረገ ፌደራሊዝም ኢትዮጵያ ውስጥ ስራ ላይ ሲመሰረት ነው ብሏል።
 ቀጠል ያደረግና ፦ “TPLF has become increasingly repressive, while failing to implement the policy of ethnic federalism it devised over twenty years ago to accommodate the land’s varied ethnic identities.” ሲል በ1925 በጣሊያኖች፤ ዛሬ ደግሞ በ1983 በወያኔ እና ኦነግ ፋሺስቶች የተጻፈው ሕገመንግሥት የደነገገው ኢትዮጵያን ለመበተን የታቀደው “የነገድ ፌደራሊዝም” ሕጋዊ ባለመሆኑ፤ ይብልጥ ሕጋዊነት እንዲሆን ፋሺሰትነትን ተግባር ላይ በይብልጥ እንዲተገበር ደግፏል። 

ይህ ድረገጽ እነ ማን እንደሚያስተዳድሩትና ጹሑፉ በማን እንደተዘጋጀ፤ የማን አቋም መሆኑ ልታውቁት የሚያዳግታችሁ አይሆንም። አስገራሚው ደግሞ ተቃዋሚዎች የተበታተኑ ስለሆኑ እባካችሁ የውጭ አገር ሃይሎች ገብታችሁ አስታርቁን ሲል እንዲህ ይላል፡
 
“The political opposition, largely forced into exile by Meles, will remain too fragmented and feeble to play a considerable role, unless brought on board in an internationally-brokered process.ይላል፤

 ለዚህም ይሆናል በሻዕቢያ የሚመራው ግንቦት 7 የተባለው “ኢሳት” በሚባለው ሚዲያው በኩል የኢትዮጵያ ጠላቶች የሆኑት እነ ሄርመን ኮኸንን ወደ መድረክ በመጋበዝ ምን ትመክረናለህ እያሉ ለዳግም ጥፋት በመጋበዝ ስናደምጣቸው የከረምነው። ለነገሩ ኸርመን ማን ነው? ብላችሁ ብትጠይቁ ኸርምን ኮኸን የሚከተለው የራሱ መግለጫ ከሰጠ በሗላ በቢሲ ተጠይቆ
የመለሰው መልስ ሁላችሁም ታስታውሳላችሁ፡
በፎቶግራፉ ላይ የሚታየው ሰነድ ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩ ወዳጄና መምህሬ የነበሩት ክብሩ ፕሮፌሰር አለሜ እሸቴ ከጣሊያን አገር የላኩልኝ ሰነድ ነበር።ስለሆነም ለባለቤቱ ምስግና እቸራለሁ።በሰማይ ነብሳቸውን በሰላም ያኑርልን።

እንዴት በሕግ ማንነቷን አስመስክራ ጸንታ የቆየች ሉአላዊት አገር ፤ እንዲህ ያለ የሞራልና የሕግ ጥሰት ትፈጽማለህ? ተብሎ በቢሲ ሲጠየቅ የHerman Cohen መልስ :-
 “It does not bother me: No American Lives are involved.. No American lives are involved” ነበር ያለው። 

እሱም ኢሳት በተባለው ሚዲያ ባዘጋጀው መድረክ ተጠይቆ “ጄምስ ቤከር” (የቡሽ አስተዳዳር የውጭ ጉዳይ ሚኒሰቴር የነበረ ነው) ኢትዮጵያን ለምን ትበታትናታለህ ፤ከሕግ ውጭ ነው እየተደረገው ያለው ብሎ ሲቃወመኝ፤ ዛሬ ስሕተት እንዳደረግኩ ገብቶኛል። እርሱ በኮዞቮ እኔ ደግሞ በኢትዮጵያ በደል ፈጽመናል። ሁለታችን ስሕተት አድርገናል፤ ሲል ኤርትራን ማስገንጠሉም በይፋ ጥፋት መሆኑን አምኗል።

የውጭ ሃይላት ኢትዮጵያ ላይ ያደረጉት አመጽ ትክክል እንዳልነበረ በይፋ ሲያምኑ፤ ተቃዋሚ ነን የሚሉን ደግሞ ያንኑ ዓመጽ እንዲደገም የፋሺስቶች ማሳሪያና ልሳን ሆነው መድረካቸው በፏስቶች እና ተገንጣዮች ፕሮፓጋንዳ ሲያሰራጩ መድረካቸው ተጨናንቋል (አንዳንድ ሰሞንማ በሚያስግርም ሁኔታ ዋና፤ዋና የሚባሉት የተቃዋሚ ሚዲያዎቹ የኦነግ ድረገጽ እስኪመስል ድረስ ነው ባንዴራቸው፤መሪዎቻቸው፤ፕሮፓጋንዳቸው፤መግለጫዎቻቸው እየተለጠፈ ሲጣበብ የምታዩት)። 

ወረርሺኙ በዚህ ሳያቆም ወይንም ሴራው በዚህ ሳያቆም፤ አገር ውስጥ ያሉት ደግሞ ከኦሮሞ ፋሺስቶች ጋር ግምባር በመፍጠር ኤትኒክ ፌደራሊዝምን እና የግንጠላ ግባቸው ካደረጉት እና ኦነሌ ሃውልት ሲገነባ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እና እጅ ከነበራቸው የጋር ግምባር መፍጠራቸው ነግረውናል። ዜና እቅራቢዎች እንዲህ ይላሉ፦

“የግንቦት ሰባት ኣርበኞች ግንባር መሪ ፕሮፈሰር ብርሃኑ ነጋም ሁሉም ከያለበት ጥያቄውን እያነሳ ትግሉን መቀላቀል እንዳለበትና ከኦሮሞ ተማሪዎች ጎን እንዲቆሙና ለነጻነታቸው እንዲታገሉ ትብብር ኣስፈላጊ መሆኑን ኣጽኖት ሰጥተው ጥሪ ኣቅርበዋል፣ በሃገር ውስጥም የሰማያዊ ፓርቲ ከኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግሬስ (ኦፌኮ) ጋር በጋራ ለመስራት መስማማታቸው ታውቋል።

እንግዲህ የኦሮሞ ተማሪዎች ጥያቄ ምንድ ነው? ካሁን በፊት በዝርዝር ገልጫለሁ። ኦሮሚያ ኬኛ፤ ሱሉልታ ኬኛ፤ አዳማ፤ቡራዩ፤አምቦ……ኬኛ ወዘተ ኬኛ፤ ….ወዘተ ኬኛ ወዘተ……ወዘተ…” ነው። በፋሺስቶቹ ካርታ እና የክልል መስረታ ደምብ የታጠረው የመሬት/ንብረት/ማአድን/ደን/ግጦሽ ሁሉ የኢትዮጵያዊያን ሳይሆን፤ ባለቤቱ “ኦሮሞ የተባለ ኦሮሚያ አገር/ብሔር የሚኖር ዜጋ መሬትና ንብረት ነው” ብለውናል። ስለሆነም፤ ይላሉ የኦሮሞ ወጣቶች በመፈክራቸው ያደመጥነው፤ “ኖ ሞር ኢምፔሪያል ኢትዮጵያ! ኖ ሞር ሳብጁጌሽን! ኦሮሞስ ቱ ዘ ኦሮሞስ! ፍንፍኔ ኬኛ! አዳማ ኬኛ!.... ሲሉ ተደምጠዋል።

ከዚህም በማከታታል፤“በኢትዮጵያ ስም የሚሸቅጥ የፖለቲካ አጭበርባሪና ተምበርካኪ” የሆነው ሰማያዊ የተባለው ተቃዋሚ ግምባር ፈጠርኩ ብሎ፤ የጠባብ ብሔረተኛ ኦሮሞዎች የሚመሩት “ኦፌኮ” የተባለው መሪዎቹና መስራቾች ደግሞ (እነ በቀለ ገርባ..ጌታቸው ጂጊ (ይህ ጌታቸው ጂጊ የተባለ ማሃይም የሆነ ግለሰብ፤ ባልተገራና ባልበሰለ ማይም ጭንቅላቱ የሚያወጣው ‘የሚሊሺያ’ ቃላት ብታደምጡ እጅግ ያስተውካችሗል።ይህን በዶክተርነት ለማስተማር ገንዘብ ከፍላ ያስተማረቺው አገር በከንቱ ገንዘቧን መቃጡሉ እጅግ ያስገርማል)፤ቡልቻ ደመቅሳ…ወዘተ) የተባሉት ደግሞ ተማሪዎችን በመከተል፤ ኢንቬስተሮቹ እየገፉ በመጡ ቁጥር’ ኦሮሞ ባሕልና ቋንቋ ይበረዛል፤ ኦሮሞ የሚባል ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ከተደበላለቀ ባሕሉ ሊጠፋ ነው (እነ በያን አሶባ……ኦሮሞ ሚዲያ ኒውስ በተባለው ቲ/ቪ ቀርበው የሚናገሩት ብታደምጡ ትገረማላችሁ) ሲሉ በግልጽ ነግረውናል።

አሁን ያለው አዲስ አበባ ተብሎ በአማራዎች የሚጠራው “ፍንፍኔ” ገና ሲመሰረት የኦሮሞ ዋና ከተማ የነበረ ነው፤ይላሉ። (አትሳቁ እባካችሁ፤ከስድስት ኪሎ ዩኒቨርሲቲ በስተጀርባ ተቆፍሮ የተገኘው የ15ኛው ክፍለዘመን የዳዊት ቤተመንግሥት ባለፈው ጊዜ እንድታዩት የዘረጋሁትን የቅርስ ምስክር ቪዲዮ አስታውሱ። የነ አብርሃ አጽብሃ ጥንታዊ ቤተክረስትያናትን ሳንጠቅስ ማለት ነው። በ16ኛው ክ/ዘመን እነ ፋሲል፤ እነ ሃመልማል፤ አማራዎች፤ትግሬዎች አገዎች ወዘተ መሪዎችና ጦርሰራዊቶች… ከወራሪ የጋላ ዘላ ጦሮኞች ጋር  ‘ዛሬ ጋላዎች በወረራ ከያዟቸው ወዲህ ስማቸው ቀይረው “ሓረር፤ባሌ፤ጅማ፤አርሲ…’  እየተባሉ በሚጠሩ አካባቢዎች ምን ዓይነት ጦርነት እንዳሳለፉ በታሪክ የተመዘገበ፤ነገስታቱ ትተውልን የሄዱ ግጥሞችና የታሪክ ሃቅና ቅርሶች ማየት ችለናል። )

፤አማራዎቹ እነ ምኒሊክ፤ ኦሮሞ ኗሪውን በግፍ ጨፍጭፈው አባርረው አገራችን ይዘው፤ ወደ ዳር ገፍተው፤ አሁን ‘ፍንፍኔ/አዲስ አበባ ለማለት ነው’ በመሃል አገር ሰዎች ተጠቅጥቆ “አማርኛ” ብቻ  ነው በበላይነት የሚነገረው፡ ስለሆነም እንዲህ ከተማዋ እየገፋች ከሄደች፤ አርሲ ፤ባሌ፤ ወለጋ፤ሐረር፤ጅማ ድረስ እየሰፋች መጥታ “ኦሮሚያ’ የሚባል አገርና ባሕል፤ቋንቋ፤አገር፤ሕዝብአይኖርም፡ ስለዚህም “ማሰተር ፕላኑ” ማንነታችን ስለሚያጠፋ ተቃወመነዋል።ብለዋል።” አስገራሚ !!!!!!!

ይህ ደግሞ በየሚዲያው፤ በቪ ኦ ኤና ፋሺሰት ፕሮፓጋንዳ በሚያነፍሱ የተቃዋሚ ሚዲያዎች በብዛት ኦሮሞ የሚባል ከኢትዮጵያ ውጭ የሆነ አገር አስመስለው እያቆነጃጁ ኢምፓየርዋ ኢትዮጵያ፤ ኦሮሚያ የተባለቺዋን አዲስ አገር/ብሔር የወረረቻት አድርገው እያጋነኑ ከተገንጣዮቹ ፕሮፓጋንዳ በበለጠ እያስጮኹ እየዘረጉት ነው። ከዚያ በፊት በሌላ አካባቢ እንዳልተፈጸመ፤ ኦሮሞ ጋር ሲደርስ ግን ጭሱ ሰማይ አድርሰውታል

ይቀጥልና ሲያትል በሚባለው ከተማ የሚኖሩ የኦነግን ፕሮፓጋንዳ በማራገብ የታወቁ ግለሰቦች ያሉበት፤ በተቃዋሚ የሚታወቁ ስብስቦች፤ ካሁን በፊት ባዘጋጁት ስብሰባ ላይ “አማራ ማሕበረሰብ ሲጨፈጨፍ የተውለበለበች የነብሰገዳዮች “የፋሺስቶቹ ባንዴራ” የሆነቺውን የኦነግ ባንዴራ አዳራሽ ውስጥ አብራ ከኢትዮጵያ ሰንደቃላማ ጋር ካልተውለበለበች፤ ስብሰባው አይካሄድም የሚል አቁዋም ይዘው ከፋሺስቶች ጋር አብረው የኢትዮጵያ ሰንደቃላማ እንዳይውለበለብ ማድረጋቸው ብዙ ጊዜ የተቸሁበትን አስታውሱ። ይህ ሁሉ ጸረ ኢትዮጵያዊነት ርብርብ ተደምሮ የምትወስዱት ግንዛቤ፤የኦሮሞ ፋሺስታዊ ብሔረተኞች ጉልበት እያገኙ የሄዱት በራሳቸው ጥንካሬ ሳይሆን በወያኔ እና በተቃዋሚዎች እርዳታና ሱታፌ “ኮምፐሮማይዝ/ሰጥቶ መቀበል” በሚባል ስልት” እንደሆነ የሚካድ አይደለም።

ከመለመሉትና ካጃጃሉት ማሕበረሰባቸው ውጭ ወጥተው ሌላውን ሕዝብ ማሳመን ያልቻሉ፤ በጦር ሜዳ “ተሸንፈው” እግሬ አውጪኝ ብለው ወደ ውጭ አገር ሸሽተው በስደት የምጽዋት ኑሮ እየኖሩ፤ “የአውሮጳ ብርድ አልቻልነውም ፤ እባካችሁ አገር አንኳ እንግባ ፍቀዱልን” ብለው ወያኔን ለምነው አትገቡም ተብለው የተፈነፈኑ/የሚያነሳቸው ያጡ/ የተነፈጉ የፖለቲካ ጡረተኞች” መሆናቸውን እያወቁ፤ ዛሬም አገርን በማስገንጠል ሴራ ተሰማርተው፤ ዛሬም አለን፤ አለን ብለው ከሞቱበት ህይወት ወጥተው ነብስ እየዘሩላቸው ያሉት ተቃዋሚዎች ተጠያቂዎች መሆናቸው እንዲሰመርበት እፈልጋለሁ።

ተቃዋሚዎቹ ሚዲያዎች የጠላትን ፕሮፓጋንዳ ከማናፈስና ሕብረተሰቡ ከመበረዝ አልፈው፤ ተቃዋሚ ፖሊተካ ድርጅቶች ደግሞ ከፋሺስቶቹ ጋር የጋራ ሕብረት እንፈጥራለን እያሉ፤ የመርህ አልባ ትግል በማድረግ፤ ለፋሺስቶቹ ተጨማሪ ሕይወት እየዘሩላቸው ይገኛሉ።

የተቃዋሚዎቹ ሕብረት የሚያምኑት (ከ-እሰከ- አንዳንዱን ሳንጨምር) ኢትዮጵያ የብሔሮች/ብሔረሰቦች (ምን ማለት እንደሆነ ባይገባኝም) እስርቤት ነበረች፤ ስለሆነም ዛሬም የኢትዮጵያ ሕዝብ አንገብጋቢ ጥያቄ ይህ ጥያቄ ነው፤ እያሉ ግራ በገባቸው ግራ ዘመም ተማሪዎች የተወላገደውን ‘ምርምር’ ዛሬም በመድገም “የነገድ” ችግር ቀዳሚ ነው እያሉ ነው። ተቃዋሚዎች በተለመደው፤በበሰበሰው በእዛው የጎሳዎች ከበሮ ምት እየዘለሉ፤ የፖለቲካ እስክስታቸውን እያቀለጡት እያየናቸው ነው (መአድ የተባለውም ባለፈው የመጨረሻው ምርጫ ኦሮሞም ሆነ ሌሎች በተመሳሳይ ‘ኤትኒክ ፌደራሊዝም’ እንዲመራ እናደርጋለን፡ አንቀጽ 39ንም እንፈልጋለን፤ አንፍልግም ካለም ሕዝቡን በድምጽ እንዲወስን እናደርጋለን ብለዋል።አስገራሚ ተቃዋሚ ነው ያለው።

ዲሞክራሲ በድምጽ ብልጫ ተጠቅመው “ፋሺዝምና ናዚኢዝም” ማንገስ እንደሚቻልና አገርንም ማፍረስ አንደሚቻል ነው ከብዙ አገሮች የታዘብነው። ከዚህ ዓይነት አሰራር ተቃዋዎች በማታውቁት ስልት ገብታችሁ አገርና ሕዝብን ከማተራመስ እንድትታቀቡ ተቃዋሚዎችን የማስጠነቅቀው። አገር በድምጽ አይፈርስም!!!!! በደምጽ አይገነባም!!!!! አራት ነጥብ!!!! ከሁለት አመት በፊት፤ አሜሪካ ውስጥ በቀን አክራሪ ነጮች እና ከበርቴዎች የሚመሩ 19 አሜሪካ ስቴቶች/ክ/ሐገሮች የመገንጠል ጥያቄ አቅርበው “ዞር በሉ!” ነው የተባሉት።

ኢትዮጵያን ለማፍረስ የሚሮጥ ካለ “የአውሮጳ ብርድና ቆፈን መቋቋም ከቻለ” ጦርነቱ መቀጠል ይችላል! መለስ ዜናዊ ስንቶቻችሁ ነው “ኤርትራ በጉልበት ከያዝናት፤ጦርነቱ አያባራም” ሲላችሁ አምናችሁ የሱን ከበሮ የመታችሁ? ዛሬ ትግራይ ኔት እና አይጋ ዌብሳይት ባለቤቶች “ዓሰብ” በዓረቦች ተያዘ ሲባል እኛን በደርግነት ሲሰድቡን የነበረው “ዓሰብ ለመያዝ ጦርነት መከፈት አለበት” የሚል ከበሮ ማስደመጥ ጀምረዋል፤ አሜን!

ምን እሱ ብቻ፤ ኤርትራ ነፃ እንድትወጣ ያደረግንበት ምክንያት ጦርነት ይቆማል፤ ሰላም ይገኛል በሚል ነው ሲል፤ መለስ ዜናዊ ሲዋሽ እናንተም፤ እኛኑን “ጦርነት ናፋቂዎች” እያላችሁ ስንቶቻችሁ ናችሁ የዘለፋችሁን (ለነገሩ እማ ኤፍሬም ማዴቦ/ግንቦት 7ትን ወክሎ እኛን ጦረኞች፤ነፍጠኞች ብሎናል አይደል; መለስን ተክተውታል ማለት ነው፡ ) አስገራሚው ግን፤ ኤርትራ ነፃ ወጣች በተባለችበት 7ኛ አመቷ ‘ታይቶ ተስምቶ’ የማይታወቅ 100,000 ነብስ በጦርነት ተማግዶ; ተጠያቂ የሌለው ወንጀል ተፈጽሞ ተገባደደ፤ አሁንም አልበረደም። ይህ ምንን ያሳያችሗል? አገር በድምፅ ብልጫ አይፈርስም፤አይገነባም። መገንጠልም፤ መከለልም፤ራስን በራስ የማስተዳደር ቅዠትም ተፈቀደ አልተፈቀደ ብሄረተኞችና ገንጣዮች ፍትሕ ሊያመጡ አይችሉም።ለፍትሕ ጋር የተጣሉ ናቸው። አይተዋወቁም።

ማወቅ ያለብን፤  ጦርነት ተፈርቶ ለጠላት አይምበረከኩለትም! ለየትኛዋ አጭር ዕድሜና ነብስ ተብሎ ነው አገርን እስከ መሸጥና ማፍረስ የምንደርሰው? ስንት ዘመን፤ሰንት ህይወት፤በስንት ጀግኖች አጥንትና ስጋ ተገንብታ ነው የቆችው? ይህንን ከባድ ጉዞ ይገባችሗል? ለመሆኑ አገር ከፈራረሰ የክብደቱ ሸክም ገብቶናል? በነፃ በዲሞክራሲ ፈቃድ መሰላችሁ አገራችን ለዘመናት የቆየቺው? ሁሉም ሕግ አለው። አግዜርም ዲሞክራሲ የለውም፤ አገርና ፈጣሪ ያስቀመጧቸው ሕግጋቶች አሉ።ማክብር ግድ ይላል። ዲሞክራሲ የአገር ዘበኛ አይደለም። አፍራሽ ነው። ዲሞክራሲ ፋሺስቶችም/ናዚዎችም የሚወጡበት መሰላል ነው። ዝግ በሉ! ምኞትና ቅዠታችሁ ልክ ይኑሮው።

ሄደም መጣም፤ተገንጣዩ፤ማርክሳዊው እና ብሔረተኛው-ከበርቴ ባሕሪው ‘ጥላቻ፤ መጥበብና አገር ማፍረስ’ ስለሆነ፤ ቢገነጠልም ያው “ጦርነት” ከመጫር አይቆጠብም። ከኤርትራ ወዲያ ምን መልካም ማስረጃ ትፈልጋላችሁ? ከሱዳን፤ከጂቡቲ፤ከኢትዮጵያ፤ከየመን ጦርነት ገጠመ፤ ምን ትሉተታላችሁ? ኦነግም፤ኦብነግም ቢፈርሱም ቢገነጠሉም ሰላም የሚሰጡ ፍጡራን አይደሉም። ሌሎችም ፎከሩ አልፎከሩ፤ አገር አይፈርስም! አራት ነጥብ! ይፈልጋል፤ካዋጣው ወደ ጫካ ይሄድ! በኦሮሞና በኦጋዴን መሬት ማንም ኢትዮጵያዊ አገሩ ነው፤ ኦሮሞዎችና በኦጋዴኖች ሊታገድ አይገባም።ታሪክ ዛሬ ልንለውጠው አንችልም።

 ዜጎች በእነዚህ ሁለት አካባቢዎች አገራቸው ነውና ሰርቶ የመኖርና የማስተዳዳር መብታቸው ማንም ሊነጥቃው ከቶ አይቻለውም። ራስ ገዝ፤ራስን በራስ የሚል ቅዠት መስርቶ “ኦሮሞ ለኦሮሞ፤ ኦጋዴን ለኦጋዴን…. መፈክር” ተፈቅዶ ዜጎች ዜግነታቸው እንዲጣስ ለድርድር አይቀርብም! አፓርታይድ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ቦታ ሊኖረው አንፈቅድም! ሰንደቃላማችን አንዲት ነች፤ የ44 ዓይነት ነፃ አውጪ ድርጅቶችና ነብስ ሲገድል እድሜው ሙሉ ያሳለፉ ገዳይ ወንጀለኞችና የፋሺስቶች ባንዴራ እውቅና አንሰጥም። አዲስ አገር አንፈጥርም። አገራችን የነበረችና የምትኖር በታሪክ የተጓዘችና የምትጓዝ አፍሪካዊት ምህዋር አላት፤ተፈጥሮአዊ ምህዋሯን ተከትላ ትጓዛለች። ምህዋርዋን ለማናጋት የሚሞክሩ ካሉ ልጆቿ ጥቂቶች ብንሆንም፤ እንከላከልላታለን፤ የኛ ፈልግ የሚከተሉ እኛን የሚያነቡ አሉ። የኛ ጥቂትነት ሳይሆን መፍራት ያለባችሁ መለስ ዜናዊን በምህዋርዋ ጎማ ጠልፋ እንዳስወገደቺው፤ የተቀሩትንም ጠላቶቿ በተአምራታዊ ምስጢርነቷ ታስወግዳቸዋለች!

ነገድ የሚባል እየተጋነነ ሲነገር ዘመን አልፎታል። የነገዶች ችግር በሽታ፤ድህነትና ባንዳን  ማስወገድ እንጂ “ብሔር ብሔረሰብ እስከ መገንጠል” ቀዳሚ ችግር አይደለም። የነገድ ችግር ለአገራችን ቀዳሚ ችግር አይደለም።ከፋፍሎ ለመግዛት ጣሊያኖች፤ወያኔዎች፤ኦነጎች….
የፈለሰፉት የፖለቲካ ቅጥፈት ነውና አንቀበለውም። እውነቱን ለመናገር ከሆነ፤ አንድ ወዳጄ ሁሌም እንደሚለኝ የኢትዮጵያ ሕዝብ ችግር “የብሔሮች…ቅራቅምቦ ችግር ሳይሆን” “የድሕነት፤የጤና ችግር” ነው ሲል ይከራከራል። ክርክሩ ትከክለኛ እና ፍጹም ያልተጣመመ እውነታ ነው። ‘ብሔር ብሔረሰብ ሕዝቦች’ ብለው ኦነግ፤ወያኔ እና ሻዕቢያ በሚያስተዳደሯቸው አካባቢዎች፤ አንዲት ‘ቃርያ’ አንዲት ‘ፍሬ-ቲማቲም’ በደርግና በሃይለስላሴ ዘመን የነበረው የበግ ዋጋ ሆኗል። 
ማርና ቅቤ አምጡ አሉነ፤
     ማርና ቅቤ አሁን የት ተጌንቶ?!
    በሃይለስላሴ ተቀልጦ ተበልቶ፤

ያለቺው ጎንደሬ አስለቃሽዋን አስታውሱ።

ስለ ብሔረሰብር/ነገድ….ጉዳይ ቀዳሚ ትኩር የሚያደርጉ እነ ማን ናቸው? ብላችሁ ብትጠይቁኝ ፤ ፋሺስቶች፤ብሔረተኛ ኤሊቶች/ምሁራን (በድሮ አባባልም ፊውዳሎችም ጭምር) ሁሌም ስለ ነገድ እያነሱ ለራሳቸው ዝና እና ክብር ለማግኘት ነገዳቸውን ተበድለሃል እያሉ ወደ ብጥብጥ እንዲገባ እየገፋፉ የሚንቀሳቀሱ ክፍሎች ካልሆኑ በቀር ‘እራሱ ሕዝቡ’ እንዲህ ያለ የመገንጠልም ሆነ የመሳሰሉት ፋሺስቶቹ ሚጠይቁትን (ለምሳሌ….በላቲን የመጻፍን ፍላጎት፤የመገንጠል ጥያቄ…፤ አማራ ጠላት ነው የማለትን..) ወዘተ የሕዝብ ጥያቄ እንዳልነበረ በሚገባ መከራከር ችለናል። ዛሬ ጠልፈው አሳስተውታል።የማያውቀው ባንዴራ እንዲያውለበልብ አድርገውታል። አማራ እንዲጠላ አስተምረውታል።

ፋሺሰት ብሔረተኞቹ፤ ከብረቴዎችና ድሃዎችን በአንድ መስመር እንዲሰለፉ በመስበክ፤ የድሕነትና የጤና ችግር እንዳይቀረፍ፤ አትኩሮቱ “ወደ ነገድ” እንዲያዘነብል፤ ሆን ብለው አቅጣጫውን አሳስተውታል። የሶሺያሊሰት ፈላስፋዎች እንደሚሉት “የጠባብ ብሔረተኞች” በዛሬው አነጋጋር ፋሺስታዊ ብሔረተኞች ጥያቂዎቻቸው ሁሌ የሚያተኩረው በነገድ ላይ ያተኮረ ሲሆን፤ የሚያነሱትም ንኡሳን ከበርቴዎችና ከብሔሩ የወጡ ሊሂቃን ናቸው ” ይላሉ።እነዚህ ክፍሎች “መፍትሄ ከሚያመጡ ይልቅ ‘አዳዲስ ችግሮችን’ በመፍጠር የታወቁ ናቸው” ይላሉ።

እነዚህ ክፍሎች ደግሞ ትግራይ ውስጥ በሁለተኛ ወያኔ፤ በቀዳማይ ወያኔ የመሳሰሉትን በግልጽ አይተነዋል።ዛሬም ኦሮሞዎች እና በተማሪዎች እንቅስቃሴ ‘መሪ ተዋናዮች’ ሆኖ እየታዬ ያለው ይህ ክፍል ነው።እነ ዋቆ ጉቱ የመሳሰሉ በስረ-ትውልዱ የሶማሊ ኦሮሞ ሆኖ ባሌ ተወልዶ ያደገ ኢትዮጵያዊ ኦሮሞ የነበረ፤ ወደ ተራ ሽፈታነት አምርቶ ልክ እንደ እነ ብላታ ሃይለማርያም ረዳ (ትግራይ) ከጫካ ወጥተው እንዴት የገበሬውን ጥያቄ እንደሰለቡት የሚታወቅ ነው። እነ ጃራ የመሳሰሉ አክራሪ እስላሞች ስንት መነኮሳትን ቀሳውስት እንዳረደ ታስታውሳላችሁ። እነዚህ እና የመሳሰሉ ናቸው “ብሔር” እስከ መገንጠል ምናምን እያሉ የኢትዮጵያ ችግር “የነገድ ችግር ነው” እያሉ በዜጎቻችን ህይወት የሚጫወቱት።

ተቃዋሚው ደግሞ ያለማፈሩ እነ ጃዋርን እነ ጃራን እነ ዋቆ (የሶማሌው የስያድ ባሬ ቅጥረኛው) የመሳሰሉ በየድረገጾቻቸውና ኢሳት ቲቪ/ሕብር-ራዲዮ (ቬጋስ ከተማ የሚገኘው ማይሞች የሚያዘጋጁት ራዲዮ ጣቢያ) እና /ዘሀበሻ… በመሳሰሉ ሚዲያዎች እየተሞካሹ አርበኝነታቸውን (ወንጀለኛነታቸውን) ለሕዝብቻን በማሳሳት በአማራውና መነኮሳት ነብሳት ሲሳለቁ እያየናቸው እንገኛለን።

 ተቃዋሚው፤ የኢትዮጵያን ምሰኪን ሕዝብ ችግር “ዲያግኖስ/ሲመረምር” የት እንደሆነ ሲፈትሽ “የብሔር/ብሔረሰብ/ሕዝቦች/ራስን በራስ ማስተዳዳር ችግር” እንጂ “የኑሮ እና የጤና መቃወስ” ችግር አይደለም፤ እያለ በመርህ እየተንቀሳቀሰበት ያለው ጠማማ ፖለቲካ አገሪቱ ላለችበት ላሁኑ ቀውስ ዳርጓታል።

ስለሆነም የዛሬ ተቃዋሚዎች (ውስጥም በአገርም) “ሶሊዳሪቲ” የሚባለው ማጃጃያ በመከተል እሳትና ጭድ አብረው እንዲጣመሩ አድርገዋል። በሕዝቡ እይታ ተሸሽገውም ‘ወያኔ ቢወድቅ” እኛን ምን እንደሚያደርጉን ስለ እኛ የሚዶሉት እንደሆነም ቅር ሳይላቸው እየነገሩን ነው። ዞሮው ዞረው “ችግሩና መፍትሄው ብለው እየነገሩን ያለው” ያው የወያኔና የኦነጎች ፋሺስታዊ የአስተዳዳር ስልት ነው። “ብሔር/ብሔረሰብ/ሕዝቦች” ‘ኮሚኒሰት ሊህቃን የፈለሰፉት ሰው ሰራሽ የማሕበረሰብ አሰላለፍ ፊክሽን’ (ኢሊት ማኒፋክቸርድ ፊክቲሽየስ) ነው። “ራስን በራስ ማስተዳዳር” “ቋንቋን መሰረት ያደረ ያስተዳዳር አወቃቀር” ፍጹም አግላይ ሆኖ በሃይሞነትም፤ በሞራልም ሆነ በማሕበራዊ አስተዳዳር ፍጹም ዘረኛ የሆነ አስተዳዳር ነው።

ይህ ደግሞ ተማርን በሚባሉ የተደገፈ አስተዳደራዊ ስልት ነው። ሙሁራኖቻቻን በዚህ ጅልነት የዘተዘፈቁት አሁን አይደለም። ቆይቷል። ለምሳሌ “ተቃዋሚውን “ወጣቱ ትውልድ” ይምራው ብሎ “የወያኔ ኮቴ” ኮሽ ባለቁጥር የሚበረከከው ‘ሰማያዊ’ ለተባለው “አማራ የሚባል የለም” የሚል ‘ፓርቲ’ ቡራኬውን የሰጠው ‘ዥዋዥዌው’ ዶ/ር ያዕቆብ ሃይለማርያምም IMBYLT A1991/Volume 1 Number3/4/በታበለ ወያኔን በማጀብ ሲንደፋደፉ የነበሩ  “ምሁራን” የሚጽፉበት የነበረው በእምቢልታ መጽሔት ላይ ባጭሩ በእንግሊዝኛው “ሎካል አውቶኖሚ” “ሰልፍ ጋቨርንመንት” እያለ የነገድ ፌዴራሊዝምን መፍትሄ አድርጎ እንደሰበከው ዓይነት ከመሆን አያልፉም።

ሁሉም ተቃዋሚዎች፤ በ1960 እስከ 74 …1983..እስካሁን 2016…ድረስ የሚያምኑት ኢትዮጵያ ችግር “ተማሪዎቹ” በማርክሲዝም እየታጀቡ ሲለፍፉት የነበረውን “ችግር” ብለው በቅድሚያ ያስቀመጡትን የተሳሳተ የፖለቲካ እይታና መፍትሔ ብለው የሚነግሩን ዛሬም ከወየኔ ውድቀት ቀጥሎ የሚመጡት ተቃዋሚዎች እንደሚከተሉት በግልጽ እየነገሩን ያለው ፖሊሲ ያው ዋለልኝ/ወያኔ/ኦነግ….ወዘተ ወዘተ…የሚከተሉትን ፖለቲካ ነው።

 እንደ ችግር እና መፍትሔ ብለው ያስቀመጡት መፍትሔ በማንም ክልል ውስጥ  “የነገዱ ተወላጅ” ካልሆነ በስተቀር ማንም ሌላ ዜጋ በሚከለሉ “የቋንቋ/የነገድ ፌደራሊዝም አስተዳደር” ክልሎች ሄዶ፤ተወዳድሮ መስራትና ማስሰራት፤ንብረት ማፍራት፤መሬት መያዝ፤መሸጥ መለወጥ አይፈቀድለትም። ምክንያቱም አስተዳዳሩ የሚዋቀረው ልክ እንደ ዛሬው “ለነገዱ ተወላጅ ብቻ ነው። የሚገኘው ጠቀሜታ ቅድሚያ የሚሰጠው” ለነገዱ ነው። በነጭ ናካባቢ ለነጮች ብቻ፤ በጥቁር አካባቢዎች ለጥቁሮች ብቻ፤ እንደማለት። ሳውዲ ላይ ቅድሚያ ‘ለሳወዲዎች’ ካልሆነ ሳውዲዎች በእውቀት ማነስ ቦታው ሊይዙት ካልቻሉ፤ በቅጥር ሌሎች ዜጎች እንደሚይዙት አሰራር ማለት ነው። ራስን በራስ አስተዳዳር እያሉዋችሁ ያሉት ይኼ ነው።

ይኼ ነው፤ ሌት ተቀን እየለፉ “የራስን በራስ፤የራስ ገዝ” እያሉ ጣሊያናዊና ማርክሳዊ እንዲሁም ፋሺስታዊ የሰው ልጅ አሳፋሪ አስተዳዳር እየሰሩልን ያሉት። ሰው እንደሰውና እንደ ዜጋ ሳይሆን “የክልሉ ተወላጅ ስለሆነ ብቻ ቅድሚያ የሚሰጥ “አድሎአዊ” የኣፓርተይድ አሰራር ከወያኔ ውድቀትም  ለማስፈን በመሯሯጥ ላይ ናቸው። አለማፈራቸው በጣም በግልጽ ነው እኮ ደግሞ የሚናገሩት! ራስን በራስ የሚሉት!

ያ አልበቃ ብሏቸው፤ የአገራችን ሰንደቃላማ ህልውናዋ እንድታጣ በየሚዲያዎቻቸው የጠላት ባንዴራዎች እያውለበለቡ ሕጋዊ አድርገው እውቅና እየሰጡ ናቸው። በዚህ ተቃዋሚውና ተገንጣዮቹ የጋራ ግምባር በመፍጠር በአገራችን ላይ ደባ በመስራት ላይ ስለሆኑ በታሪክ ዓይን እንፋረዳቸዋለን፤ ወንጀለኞች ናቸው!!!! ተቃዋሚ የሚባል ድርጅት በአጭበርባሪዎችና በተምበርካኪዎች ስለተሞላ ጭራሽኑ እንዳታምኗቸው።ለ24 አመት አገራችን ውድቀቷን እንጂ ትንሳኤዋን አላመጡልንም። ጭራሽኑ የተገንጣይ ባንዴራ እና ፕሮፓጋንዳ ድምጽ አሰራጪዎች ሆነው ስላየናቸው ‘እንግዲህ ወዲህ’ ተስፋችሁ በነዚህ አጭበርባሪዎች እንዳታደርጉ።

ጥቂት አገር ወዳድ ተቃዋሚ ግለሰቦች ካልሆኑ በቀር ወያኔም ተገንጣዩም ተቃዋሚውም ከነሚዲያው፤ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽ ናቸው። አህያ ላህያ ቢራገጥ ጥርስ አይሰበርም! የኢትዮጵያ ሚዲያዎችና ተቃዋሚዎች ኢትዮጵያን ለማበጣበጥ የተነሱትን የኦሮሞ ፋሺስቶችን ሌት ተቀን በሚዲያዎቻቸው እያገዙዋቸው ናቸው። የተለያዩ ኦሮሞ ድርጅቶች ብሔረተኞቹ በሚጠሩት የራሳቸው ስብሰባ ላይ የኢትዮጵያን ሰንደቃላማ ማውለብለብ እስካልጀመሩ እና እስካላየናቸው  ድረስ፤ መደራደር ፤መወያየት የለምብንም!!!! ኢትዮጵያዊ አይደለሁም ካለ የውጭ አገር ሰው  በአገርህ ላይ የሚያይበት ምን ጉዳይ ቢኖሮው ነው? የውጭ ሰው ነኝ ብሏል፤ አልወያይም ማለት ለምን ይከበድሃል? ኢትዮጵያዊ ነኝ ይበል፤ ተወያይ። ካልሆነ የራሱ ባንዴራ ይዞ፤ የራሱ ካርታ ይዞ ‘ልወያይ’ ሲልህ አገርን የሚያክል “የንግድ ውይት” አይደለምና “ቅድመ ሁኔታውን አስቀምጥለት!!!!!! ንግድም የራሱ ሕግጋትና ቅድመ ሁኔታዎች ተከትሎ ነው ውይይት የሚደረገው። በቃ ማለት ተማር! መብርከክ፤መጃጃል፤ለፋሺስቶች፤ ለነብሰገዳይ ወንጀለኞች መልፈስፈስህን አቁም!

ፋሺስቶቹ ከ40 አመት በላይ ተሸንፈዋል፤ ዛሬ ግን እንድንሸነፍ በዘዴ ገብተው ተቃዋሚዎችን ይዘው በፊት ለፊት በር እየመጡብን ነው። ተገንጣይን “ዞር በል” የሚል ተቃዋሚ በእልልታ እንቀበለዋለን! ተገንጣይ ይዞልን የሚመጣና የሚንከባከብ ደግሞ ዞር በል እንለዋለን። ፋሺስቶችና ተገንጣዮች “በተፈጥሮአቸው” ዋሾች ስለሆኑ “ድረድር፤ሰላማዊ አስተዳደር፤አንድነት….” የሚባሉ ፖለቲካዎች ደማቸው ውስጥ የለምና አይረቡም ፤ውግያ ከፈለጉም ይቀጥሉ! ብዙ አርበኞች፤ተዋጊዎች፤ገጣሚዎች፤ሰባኪዎችና አራስ ነብር ሴት እህቶች ኖረዋል፤ ዛሬም ለወደፊትም አሉን፤ ለወደፊትም ይኖራሉ።

ዲፕሎማሲና ፕሪንሲፕል ለይታችሁ ማወቅ አለባችሁ! በፕሪንሲፕል መደራደር የለም! አይ ምፅዋ! የሚለው መጽሐፍ አንብቡ። አርበኞች በባንዳ ጄኔራሎች (ጥላሁን)፤ለነ ጄኔራል ተሾመ ተሰማ እጃቸው ለሻዕቢያ እንዲሰጡ በራዲዮ ስልክ ጥሪ ሲደረግላቸው፤ “አሳፋሪ ጀኔራል፤ ትከሻህ ላይ የተሸከምከው የአምበሳ ኮከብ በቀበሮ ምሰል ተካኸው”? ብለው ነበር ከራዲዮ መገናኛ መስመሬ ውጣልኝ! ብለው እምቢ በማለት፤ “ለፕሪንሰፕል” ራሳቸውን ያጠፉ ብዙ ጀግኖች ነበሩን (ታየ ወልደሰማያትን እና አስራትን አትርሱ)፤ዛሬም አሉን።

አንዳንዶቹ ጋዜጠኞችና ፖለቲከኞች እምቢ ብለው ለፕሪንሲፕል ሞት እየተቀበሉ በወያኔ እስር ቤት ውስጥ እየማቀቁ የሚገኙ አሉ። በግልጽ ጠላት ፊትና በጠላት ዳኞች ቆመው “ኢትዮጵያዊነት የሚከላከሉ ደፋር ወጣት ገጣሚዎችና ዘፋኞችና ሙዚቀኞች አሉን። እዚህ ያሉ ተቃዋሚ ነን የሚሉ የባንዳ ግብር በሎች ግን፤ “እስር ቤት ሳይገቡ” “ፕሪነስፕል” እየለቀቁ፤ እየተደራደሩ ፤ ጅቡምዘንዶውምእባቡምከብቱምበጉምፍየሉምውሻውምድመቱምቀበሮውምእርግቢቱምወፉምአህያውምአንበሳውምአዞውም… ሁሉ እያሰባሰበ፤ የኖህ መርክብ ይመስል “አንድነት” እናመጣለን እያሉ ከተፈጥሮም ከሳይንስም ሕግ ውጭ የሆነ ክስተት ለመፍጠር ሲጥሩ እያየናቸው ነው።

ሲወጡ ልክ እንደዛሬዎቹ  “እኔም ነጋሶ ነኝ፤ እኔም ቡልቻ ደመቅሳ ነኝ፤ እኔም በቀለ ገርባ ነኝ፤እኔም ኦሮሞ ነኝ….” እያሉ የዛሬዎች “የኦነግ ዶማና አካፋዎች” እንደሚፎክሩብን ሁሉ፤ ያኔም በ1983 በርከት ያሉ ‘አሳማዎችና በጎች’ እኔም ‘ትግሬ ነኝ፤እኔም ወያኔ ነኝ፤እኔም ኢሳያስ ነኝ፤እኔም ሓይሎም ነኝ፤እኔም ክንፈ ነኝ… (ክንፈ ሲሞት’ማ “ኢትዮጵያ አንድ ደግ ልጇ አጣች” ብለው የተናገሩ አሉ፡ ያውም እውቅ ተቃዋሚ፤ ያውም ሊቅና ፕሮፌሰር)፤ ሲሉ፤ ብዙ ሰው ተገርሞና ግራ ተጋብቶ ነበር።
አስመራ ድረስ ሄደው ስለ አማራን በሃሰት ወንጀል በመክሰስ ተገንጣይ አባንዳዎችን ይቅርታ በመጠየቅ እምባቸው ያፈሰሱ አሳፋሪ መንጋዎች አይተናል። ትግሬ፤ትግሬ ባለ ቁምጣ ሱሬ ፤ወያኔ፤ ወያኔ፤ እያሉ እየዘለሉ እያሽቃበጡ ሲጮሁ፤እስክስታ ሲረግጡ የነበሩ መንጋ አህዮችም አይተናል።
ሆኖም እያደረ ትግሬም ከበሮውን፤ሳክስፎኑም ክራሩም፤ጊታሩን አንስቶ የሻዕቢያ ‘ባንዴራ’ እያውለበለበ “ኤርትራዊት ኣዶ እዚ ኹሉስ ኣይ ሳላኽ’ንዶ” (አንቺ ጀግና ወላጅ ኤርትራዊቷ እናት…….) እያሉ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ሲጨፍሩ ካዩ በሗላ “እኔም ትግሬ ነኝ ፤ ደርግ የጣለልን ጀግና፤ እኔም ሓየሎም ነኝ! እኔም ስየ አብርሃ ነኝ! እያለ የወያኔ በርባሶ ማጥለቅ አምሮት የነበረ አዳማቂና አለቅላቂ ሁላ…..፡” እኛን መሳደቡንና መዝለፉን ትቶ ‘እራሱን እያከከ’፤ ያየውን ማመን አቅቶት ግማሹ ከኛ ጋር ሆኖ ዛሬ ከኛው ጋር ተቀላቅሎ “አንኳን ደህና መጣህ” ባልነውና በተንከባከብነው ‘ብድራችን’ እኛንኑን መዝለፍ ስራዬ ብሎ የተያያዘ ክፍል ብዙ ነው። አንዳንዱም፤ “ያለ እኔ ተቃዋሚ የለም” እያለ ወያኔን ሲያወግዝ፤ እኔም ኦሮሞ ነኝ፤ በቀለ ገርባ ነኝ፣……’ ማለት ጀምሯል።  ወይ ማርያም አኽሱም!

ብዙዎቹ አለማፈራቸው ደግሞ ከአገር እየሸሹ እዚህ መጥተው “ውጭ አገር” ሚዲያ መስርተው የተገንጣዮች ደምፅ ማጉያ ሆነው ዛሬም ስለ ተገንጦች አጀንዳ እያስተጋቡ ሕዝቡን በመበረዝ ላይ ናቸው። የአገራችን ሰንደቃላማ እንድትናቅ፤ተጥላ እንድትቀር፤ ላገራቸው የደከሙ ታላላቅ ነገሥታት እንዲሰደቡ በማድረግ፤ አማራ እንዲዋረድ በማድረግ፤ ታሪካችን እየተዘለፈ፤ ኢትዮጵያ ሉአላዊነቷ ጠብቃ እንዳትቀጥል የፕሮክሲ/proxy እጅ አዙር የተግንጣዮች ስራ ፤ባንዴራ፤ ፕሮፓጋንዳቸው በማባዛት እንዲዘረጋ እየተባበሩ ናቸው። ሳብቨርት እየተደረግን ነው። እያደነዘዙን፤እያጠቡን ነው።
አርበኞች የኢትዮጵያ ልጆች ጽሑፌን አገር ውስጥ ላለው ሕዝብ እንዲዳረስ እያደረጋችሁ ላላችሁት አርበኞች ሁሉ ዛሬም እያመሰገንኩኝ፤ ይህ ጽሑፍ በፌስ ቡክ በኩል ባላችሁ ስልትና መንገድ ወደ ኢትዮጵያ ወጠቶች እንደወትሮው እንድትዘረጉት ይሁን። ተቃዋሚዎችና ሚዲያዎቻቸው የጸረ አንድነት ሃይላት “ፐሮክሲ/መሳሪያ እጀታ/ ሆነው አገራችን ሕልውናዋን ለሁለተኛ ጊዜ ስልጣን ለመያዝ በኢምፔሪያሊስቶች መዝገብ የተያዘላቸው ተገንጣይ ቡድኖች በሙሉ እያገለገሉ ናቸው እና ሕዝባችን፤ “በተለይ አማራው ሕብረተሰብ” ተቃዋሚና ሚዲያዎቹ ከድተውሃል እና “መከታ” አለኝ ብለህ ከውጭም ከውስጥም አትጠብቅ (ውጭ ጥቂት ልጆችህ አሉህ እነሱም እየታገሉዋቸው ነው)፤ እራስህ ከአምላክህ ጋር ቆመህ እራስክን ለመከላከል ሞክር፤ እግዚአብሔር መወጣጫው ይስጥህ!

አሳዛኙ ኢትዮጵያ ትግል በነዚህ ተምበርካኪዎችና ባንዳዎች መኮላሸቱ በግልጽ እንድታውቁት ይሁን። 24 አመት የተጓዙት ጉዞ ትምህርት ካልሆናችሁ፤ እናንተም የአገራችሁ ቀብር አብራችሁ ቅበሩ፤ እኔና ጥቂት አርበኛ ጓዶቼ የነ ብርጋዴር ጄኔራል ተሾመ ተሰማ እና እልፍ ኣእላፍ አርበኞች በምፅዋ ወደብ እና በኤርትራ ተራራ ስር የወደቁ የአርበኞቻችን ኢትዮጵያዊያን አደራ ይዘን እስከ ህልፈተ ሞታችን ጠላቶቻቸውን በማጋለጥ ለታሪክ እየነገርን እናልፋለን። ሕሊናችን በቆመው ተራራ ላይ ቆመን ሰንደቃላማችንን እያውለበለብን በጽናት ቆመናል።አዲሱ ትውልድም ያንኑን አርማ ያነሳል።

የሚሊዮኖች የሰው ሕይወት ግብር የተከፈለበት  ክቡር መሬት ህያው ይሆናል። ፋሺስታዊ ብሔረተኞች፤ ኢትዮጵያ ከመግደላችሁ በፊት እንደ መለስ ዜናዊ ‘በሳጥን ወስጥ ታሽጋችሁ ትሰናበታላችሁ”። የኢትዮጵያን ክፋትዋን ለማየት የወጠነ፤ ዕድሜው አጭር ነው። ይህ ደግሞ በመለስ ዜናዊ የታየ ታምራዊ የእናት ኢትዮጵያ ስራ ነው። በዚህ ታአምር የማታምኑ በማርክስና በሙሶሎኒ የማሾፍ መብታችሁ ተከብሯልና ማሾፍ ትችላላችሁ።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር! ጌታቸው ረዳ ከሰሜን አሜሪካ (Editor Ethiopian Semay) getachre@aol.com