Sunday, September 28, 2008

Our Taye , the leader, the teacher, the living her Of our time

በጀግኖቻችን አንገት ላይ የሚገባ ገመድ ሲፈትሉ ዝምታን የመረጥን ህዘቦች መሰደድና ሞት ሲያንሰን ነዉ! ጌታቸዉ ረዳ የቁም ሞት ሞታችንን የማየት እና የማሳየት እሽቀድምድሙ እየበዛ በሄደ ቁጥር ገዳዮቻችንን አፍ’ጠን የምንከላከልባቸዉ ዓይኖቻችን በሰሜኖቹ ባንዳዎች ላይ የማትኮሩን ስራ ቀርቶ፤ አብረዉን እየተጓዙ የቁም ሞታቸዉን እየሞቱ እኛን መስለዉ እኛኑንና ጀግኖቻችንን የሚገድሉብን እነየቶቹ መሆናቸዉን ስናቅ አንጀት ያቀጥላል። አክ እንትፍ ብለዉ አያጠፉት ነገር፡ እጅግ የጨነቀ ነገር!
ታላቅ ሕዝብ እና ታላቅ አገር ተብሎ ስነቴና ስነቴ ተነገረ። ያዉም ለሺዎቹ ዘመናት። ታላቅነቱ ያስመሰከረ፤ ማንነቱን ያልስረከበ ያ ታላቅ ህዝብ አስከ ትናንት ነበር። ታለቅነቱን ለዉሾች አስረክበን ታላቅ አገር፤ ታላቅ ሕዝብ ሊያስ’ሰኙን ያስቻሉ ነባር አሴቶቻችን እንደ ዛፍ ቆርጠን፤ቆርጠን ግንድ ቅጠሎቻቸዉና ስሮቻቸዉ ሳይቀሩ በጥስን፤ነቅለን ከጣልናቸዉ ይኸዉ የሰዉ ዕደሜ አስቆጠርን።
የኢትዮጵያ ህጻናት በአዲስ መጤ የሃይማኖት ሰባኪዎች የአዲስ ዙር የቅኝ አገዛዝ የፈረንጅ ሰለባዎች ሆነዉ ህጻናቶቻችን ለእርዳታ ሲጮሁ ያዉና ዉርደታችን በቀኝ በኩል በዚህ የህዋ ሰሌዳ ተለጥፎ የምታዩት ቪድዮ ሕያዉ ምስክር ነዉ። ማነህ አንተ ድምበር ጥሰህ መጣህ!? ብሎ የሚል የግዙፋኑ ድምጽ ከየት ይምጣ? ልቅሶዉን ሁሉ ለህጻናቶቹ አስረክበን ይሄዉ አረፍነዉ።ሁኔታችን ሁሉ ልቅሶ ብቻ። አልቅሶ ላይመልሱት ነገር። ሰማይን የሚያክል ከባዱ ሸክም ሲሸከሙልን የነበሩት አሴቶቻችን ለመሆኑ አንዴትና በእነማንሰ ተባበሪነት አንደተወገዱ እናዉቃለን? በነባር አሴቶቻችን እግር አዳዲስ እሴቶች ብቅ ባሉ ቁጥር በመርዘኛዉ ቅናታችን እየኮረኮምን እንደተቃጠለ ኮከብ ቦግ እያሉ እንዲሰወሩብን አደረግን። የትላልቁን ድምጽ ባፈንን ቁጥር ታላቅነታችን ወርዶ በማንም አላፊ እና አግዳሚ የሚደፈር አንገቱ የደፋ ጊላ/ባርያ ሆነናል። በማንም የሚደፈር ዜጋ ደግሞ ያገር ትረጉም ስለሚያጣ ፤ አገሩን ለደፋሮች አስረክቦ፤ እንጀራ ፍለጋ ሩቅ ተጉዞ የሰዉ ጥራጊ የመሆኑን ኑሩ በመሻት እሱም በፋንታዉ ብቅ ያሉትን የመኮርኮሙን ባህል ይዞ እየቀጠለ ይታያል። ከላይ ጎልተዉ የሚታዩት ፎቶግራፎች ኢትዮጵያ በስንት ምጥ አምጣ ከወለደቻቸዉ ጥቂት ከታላላቆቹ የኢትዮጵያ ድምጸች አንዱ ብሁራዊ ጀግናችን የ120.000 የምመህራን መሪዉ ፤ ሊቁና የፍትሕ ተማጓቹ ደ/ር ታየ ወልደሰማእት ነዉ። ታየ ብሔራዊ መዘክራችን ነዉ።ታየ የኢትዮጵያ ገድል ታሪክ ነዉ። ታየነቱን የኢትዮጵያዊነት ታሪክ ለመሆን በጨለማዉ ጉዞ በድፍረት ለማንም ሳያጎነብስ በክብርና በኩራት እንደ ጧፍ በርቶ አብረቶልን የተጓዘ ጀግና ነዉ። ታዩ፡ወያኔን ያለ ጠመንጃ በተማጓች ድምጹ ብቻ ያስጎነበሰ፤ያስደነበረና ያስጨነቀ ከትላልቆቹ ዛፎቻችን በህይወት የሚወዛወዝ ረዥሙ ዛፈችን ነዉ። ዛፍ! ያዉም ስጋ የለበሰ ትልቁ ዛፍ! ይሄን ዘፍ ለመቁረጥ፤ ብዙ ተመኮረ። ያዉም ከመሃላችን እዚሁ በዉጭ በስደቱ ዓለም። እኛኑን መስለዉ፤ እኛነታችን የመገዙን! ዛሬ ታየ በሕይወት እንደሌለ ለማስመሰል ሚዲያዎቻቸዉ በመጋዦች ተርመስምሷል። ታየ በግምባር ቀደም ሰልፉን መርቶ በሺዎቹ እንዳላታገለ፤ የከፈለዉ መስዋዕት የእያንዳንዳችን የጉራ ቁምጣ ሱሪዎቻችን እንዳላስነቀ ሁሉ፤ መስዋዕትነቱን ሁሉ ዉሃ በጠማዉ ምድረበዳ መሬት ላይ በከንቱ ተረጭቶ እንዲደርቅ በዚህ ሁለት እና አንድ ዓመት ዉስጥ እንደተሞከረ የምታዉቁት ጉዳይ ነዉ። ያልታደለዉ ህዝብ ታየን ያክል ትልቁን ሰዉ ለማሳጣት ስንሯሯጥ የሞራል ድጥ ሰርተን ስንንከባለል ጀግናዉን ስናሳዝን ፤ስናስቆጣ ታይተናል። የትግራይ ባንዳዎች ባዘጋጁለት የጨለማ እሰር ብቻዉን ዘግተዉበት መከራዉን አይቶ ፤ ዓለም እሪ ብሎ ባእዳን ሁሉ ያደነቁትና የጮሁለት ጀግና፤ከእስር ሲለቀቀቅ ዓለም በተጠንቀቅ ቆሞ፤ መላ ያበሻ ህዝብ ምድሪቱ ሰንደቃለማዋን እያዉለበለበች የተቀበለችዉን በሕይወት ያለ ጀግናዋን፡ ትንሽ ሰዉ ለማድረግ የሞከሩትን ትከሻ ለትክሻ ገጥመዉ ከባንዳዎች ጋር እየተሻሹና እየተሳሳቁ ዉስኪ ሲራጩና ሲጨልጡ አስራ ምናምኑ ዓመታት ወያኔን በንግድ በዲፕሎማቲክ ኮሩና በሕጉ ዘርፍ፤ የጎሳ የደም፤ የቋንቋ በናዚ ፍልስፍና ህዝበን የሚሰብኩ ትምርቶቻቸዉን ሲጽፉና ሲያሰራጩ፤ በከንቲባነት እና ባማካሪነት ለባንዳዎቹ ለነ መለስ እና ለነ ገብሩ አስራት መንግሥት ደፋ ቃና ሲሉለት የዘመኑትና የከረሙት እነ ብርሃኑ ነጋ፤እነ አንዳርጋቸዉ ጽጌ፤ብርሃኑ መዋ፤ወርቅየ ብርየ፤ጋዜጠኞቻቸዉ እነ ዳዊት ከበደ እና ክንፉ አሰፋ የመሳሰሉት በመምህራኑ መሪ በታየ ላይ ብዙ ዘለፋዎችና አስጸያፊ ዉረፋዎች በመከመር ጀግናዉን ለማሳነስ እና ከመድረክ ለማሰወገድ ያልጣሩት ያልቆፈሩት ድንጋይ አልነበረም። ከናንተዉ ጋር ነን ብለዉ እንደ ጆፊ አኮብክበዉ አለ ሃፍረትና ርህራሄ ሲቦጭቁትና ሲከቡት አብዛኛዎቻችን ተመልካቾች ነበርን። አሳዛኙ ገበናችን ጀግናን ስናስቆጣ እና ስናሳዝን አስከመቸ አንዲህ ሊቀጥል እንደሚችል ሁላችን መፈተሽ የሚገባን ጉዳይ ይመስለኛል? አሜሪካኖች…..ይላሉ የጦቢያዉ ጸሃፊ ጸጋየ ገብረ መድህን አርአያ “አሮጌ እሴቶች እና አዳዲስ ሃሳቦችን” ሲያወሱ ከብሄራዊ አክብሮት ጋር ነዉ። “አባቶቻችን” ይላሉ፡ “ጀግኖች ወላጆቻችን ይላሉ”። ከትንሿ ዘመን- ለአጭርዋ የህልዉና ታሪካቸዉ ዘመን ከፍተኛ አስተያየት አላቸዉ። በዚሁ በአጭርዋ ዘመን ታሪካቸዉ እንዲህ ሲኮሩና ሲያጌጡባት፤አንደ እሳት ሲሞቁባት፤እንደ ሻማ ሲቀልጡባት ባሕላዊ እሴቶችን ሲፈጥሩ በአዳዲስ እና ገንቢ እሳቤ ሲያበለጽጉት ሰባት ሺህና ከዚያም በላይ ዕድሜ ያለዉ ታሪክና አገር ያለን ወገኖች ስናፍርበት ስንረግጠዉና በዉሻ ፊት ስንወረዉረዉ እንገኛለን። በፋሺስቶች ዘመን የነበረዉን የኢትየጵያዊንን ተጋድሎ ከመስማት እና አልፎ አልፎም ከማንበብ በቀር ሁኔታዉን በዓይኔ ለማየት አልታደልሁም። ነፍስ ማወቅ እንደጀመርሁ ግን ( ---------ነዉ- የተወለድሁት) አጎቶቼና ያክስቶቼ ልጆች፤ ጎረቤቶቻችንና አንዳንድ የመንደራችን ሰዎች ጠመንጃቸዉን ከጎናቸዉ፤ ጥይት የሞላበት ዝናራቸዉን ከወገባቸዉ ሳይለዩ በየቀኑ በኩራት በመሃላችን ሲንጎራደዱ ከእነሱ የበለጠ ሰዉ አለ ብየ ገምቼ አላዉቅም። አንድ ቀን እንደነሱ ጠመንጃ ተሸክሜ፤ዝናር ሙሉ ጥይት ኖሮኝ ለወዳጅ ኩራት፤ለጠላት ሥጋት ሆኜ መኖር እመኝ ነበር።” ይላሉ ጸሃፊዉ። ጸሃፊዉ እንዳሉት እወነትም በዚች አገር ጎልያዶች ነበሩ። በዳዊት ጠጠር የሚሸነፉ ዓይነት ጎልያዶች ሳይሆኑ በእርግጥ ሰማዩን ሁሉ የሚሸከሙልን የሚመስሉ የታለቅነት መለያዎች ነበሩን። “ብዙዎቹ አይቻቸዋለሁ” ይላሉ አቶ ጸጋየ ገብረመድህን ይህንኑን ሲያረጋግጡ፡ “ብዙዎቹ አይቻቸዋለሁ። እምብዛም ሳልቆይ እና ይልቁንም ወደዚህ አዲስ አበባ ወደ ሚሉት ባቢሎን ስመጣ ድንክየዎች (pigmies) አያለሁ ብየ አላስብኩም፤አልሜም አላዉቅም ነበር። ይሄ አስቆዝሞኛል። ርዕሱን ረሳሁት እንጂ በማስተወቂያ ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ክፍል ባለዉ መጻሕፈት ቤት የሚገኝ መጽሐፍ ስለ ቴዎድሮስ ያወሳል። የመጻሕፍት ቤቱ ሠራተኛ ወደዚያ ብቅ ስል መጽሓፉን ከፍቶ ይጠብቀኛል። “አጤ ቴዎድሮስ አገሬ ገነት ናት። የሚኖሩባት አህዮች ሆኑ እንጂ አሉኝ” ይላል ደራሲዉ። ለንዴት የጣፏቸዉ መይሳዉ ካሳን አይወቅሱም። በሕዝብ ድፍረት አይከሰሱም። ባይሆን እህያ ወይም ሰዉ መሆናችንን ማጣራት ያለብን እያንዳንዳችን ነን። እንደትናቱ ዛሬም ታዲያ በየዘመኑ ከመሃከላችን ለሚነሱ አድባር አዉራዎች ደንቃራ አይደለንም ያሰኛል?። እንዴት ብሄራዊ ህልም እንጣ?” ሲሉ ጭነቀታቸዉን በጥያቄ የወረወሩልነን ዓመታቱ ልብ በሉት። በጣም ረዥም ጊዞ ሆኗል።ዛሬም ያዉ ነን። አልተለወጥንም። እንዲህ ያለ ረቂቅ ድምጽ መስጠት ስለማንችል፤ ጀግኖቻችን በሌቦች በዋሾችና በዉሾች ሲነከሱ አልተከላከልንላቸዉም። ጋዜጦች፤ራዲዮኖችና ቴሌቪዥኖች ታየ አንዳያስተምርበት እና እንዳይቀሰቅስበት መድረኮቻቸዉን ለታየ አግደዉ፤ ለግብር ይዉጣ ብለዉ የ120 ሺህ ምመህራን መሪዉን በጨለማ ላሰረዉ ለስርአቱ መስራች ገብሩ አስራትን አስከ ትግራይ ድረስ በስልክ እያፈላለጉና አስካለንበት ዓለም ድረስ እያስመጡ እየረገጠን ንቆን እንዲሄድ አዲስ ጀግና ሊፈጥሩብን የሚሞክሩትን ዲስኩረኞቹ ያዲስ ድምጽ ራዲዮ አዘጋጆቹ እነ አበበ በለዉንና ምንትስ ምንትሴዎቹ ሁሉ ጠዉልገዉ የነበሩትን ኮትኩተዉ ዉሃ እያጠጡ እያበቀሉብን ያሉት እሾህ ችግኞቻቸዉን እንዳይወጋን ካሁኑ በንቃት ተከታተሉት። ከትናነት በስትያ ጸጋየ ደብተራዉና ጓደቹ አንቀዉ ሲወስዱብን፤ ዝም አልን።ቀጥሎ አሰፋንና በህታዊዉ ፈቀደ ስላሴን በጠራራ ብርሃን በጥይት ሲነጥቁብን ዝም አልን። ትናንት የደቡቡ ጀግና ህዝብ የመረጠዉ ፊታዉራሪ መኮንን ዶሪንና የባህረ ነጋሹ ኢትዮጵያዊዉ ጀግና አበራ የማነ አብን ሲነጠቁብን ዝም አልን። ኢንጂኔሩ አረጋዊዉ የእልፋ እላፍ ሕዝበ መሪዉ ሃይሉ ሻዉል ተምሞብን ሲታከም “አልታመም- አምሮበት ነዉ” ሲሉን፤ ዝም አልን። ዛሬም በተቀሩት ጀግኖቻችን አንገት ላይ የሚገባ ገመድ ሲፈትሉባቸዉ እያየን ስንቶቹን ጀግኖቻችን በዝምታ አናስነጥቅ? ጌታቸዉ ረዳ መስከረም 2001

Monday, September 22, 2008

Red Terror by Eritrean liberation fronts in the forests of Eritrea



 ከላይ የሚታዩት ፎቶግራፎች፤ አንዱ ኢሳያስ አፈወርቅ ሲሆን ከመማሃል ኢሳያስ አፈወርቅ በ1984 በፈረንጅ አቆጣጠር የድርጅቱ ከፍተኛ አመራር አባላትን ስብሰባ ሲመራ ነዉ።ሌላኛዉ አሲያስ ገድሎታል እየተባለ የሚነገርለት የኢሳያስ አለቃ ነበር የሚሉት አብራሃም ተወልደ ነዉ። “Most Eritrean elite were victims of their fellow guerrilla leaders, and not the Ethiopian regimes”
Getachew Reda ከዚህ በታች የቀረቡ ሁለት የተለያዩ ጽሁፎች በሁለት ኤርትራዊያን ጻሃፍት የተጻፉ ናቸዉ። በጽሁፎቹ ዉስጥ የቀረቡት ሰነዶች በወቅቱ በኣካል ከነበሩ የዓይን ምስክሮች የተገኙ ሲሆኑ፤ ሰነዶቹ የሚዘረዝሩት የኤርትራ የነጻነት ግመባሮች በታጋዮቻቸዉ ላይ ያካሄዷቸዉ የጭካኔ እርምጃዎች፤ግድያዎች፤ እስራቶች፤ ድብደባዎች ባጠቃላይ በኤርትራ በረሃዎች ዉስጥ አስከዛሬ ድረስ በምስጢር ተይዘዉ የቆዩ ብዙም ይፋ ያልነበሩ ከደርጉ የከተማ ቀይ ሽብር ያልተናነሱ የበረሃ የቀይ ሽብር እርመጃዎች እንዴት ይካሄድ እንደነበር ይዘረዝራል። ለዚህ ሰነድ መነሻ የሆነኝ፤ ባለፈዉ ሰሞን አንድ ኤርትራዊ አንባቢ በዚህ የህዋ ሰሌዳ ላይ ንጉሱ ለሥልጣን ሲሉ ኤርትራን ያለፍትሕ ወደ ኢትዮጵያ ማዋሃዳቸዉን እና እንደዚሁም በደርግ ጊዜ በጀኔራል አማን እንዶም ላይ የተካሄደዉ ግድያ ኤርትራን አሳብቦ ሰሥልጣን መወጣጫ እንደነበር ክፉኛ ሲኮንን፤ የተፈጸሙ ጥፋቶች፤ወንጀሎች፤ስሕተቶች ፤ኢሰብአዊ ምግባሮች እና ግድያዎች ሁሌም ሲፈጸሙ የነበሩት በኢትዮጵያ (በተለይም በጠላትነትና በሃላፊነት የተፈረጀዉ የአማራዉ ሕዝብ) በኩል ብቻ እንደሆነ አጉልተዉ በመጻፍ እና በማስተማር ህዝቡ በተለይም ደግሞ በወያኔ እና በኤርትራ ነጻ አዉጪ የጥቅጥቅ ፕሮፖጋንዳ ሰለባዎች ተወናብደዉ ኢትዮጵያን (አማራዉን በጠላትነት ፈርጀዉ) የጋኔሎች ምድር የኤርትራ የነጻነት መሪዎች ግን በሙሴዎች እና በቅዱሳት መላእክት መሪዎች የተሞላ አድርገዉ ሲኮንኑ ዛሬም እያነበብናቸዉ ስለሆነ፡ ኤርትራዊያን ወንድሞች እና እህቶች እንደዚሁም አንዳንድ ግራ የገባቸዉ ኢትዮጵያዊያን ወንድሞቻችንን ይረዳ ዘንድ ነጻ አዉጭ የተባሉት አማራን ሲከስሱ የነበሩት ክፍሎች ለሥልጣን ሲሉ አብረዋቸዉ በተሰለፉት ጓዶቻቸዉ ፤ወንድሞቻቸዉ እና እህቶቻቸዉ ላይ የፈጸሙት ጭካኔ በጥሞና አንብቡት። ጽሁፉ ረዘም ቢልም፤ ጠቃሚ ሰነድ በመሆኑ፤ በትዕግስት እንደምታነብቡት አደራ ስል፡ -በዚህ አጋጣሚ ወያኔዎች ትግራይ ዉስጥ ያካሄዱት የጫካዉ ቀይ ሽብራቸዉ አስከ ዛሬ ድረስ ከሁለት ወይም ከሦስት ጸሃፈት ብቻ (ያዉም የም ቢሆን “ነካ ነካ ብቻ እንጂ ዝርዝሩን አይገልጽም) እንጂ የቀረበ ሰነድ አስካሁን ድረስ ስለሌለ፤ የትግራይ ምሁራኖች/ታጋዮች ከኤርትራዊያን ጸሃፍት ትምህርት ቀስመዉ እውነቱን ገሃድ አድርገዉ ትግራይ ዉስጥ በንጹሃን ላይ የተፈጸሙት ግፎች እንሚያስተምሩን አደራ እያልኩ፤ አሁን ወደ የኤርትራዉ የበረሃዉ ቀይ ሽብር ታሪክ አናምራ። አነሆ፦
The Dirty War In The Dejen By Zekere Lebonna - Feb 02, 2004 To state that most Eritrean elite were victims of their fellow guerrilla leaders, and not the Ethiopian regimes', is not an overstatement. The dirty war in the Dejen is largely responsible for it. The modest effort to give names and faces to the unknown multitude that has lately begun is an eye opener, and should be commended. The series of anecdotal evidences submitted so far by this writer will continue. The 70s in Ethiopia was a terror decade for all sorts of opposition groups. The military junta's Ethiopia Tikdem Yale menem Dem remained a hollow slogan. The urban dwellers, and particularly the intellectuals, were the disproportionate victims. According to some historians, Ethiopia lost a generation of intellectuals during this mayhem. It is often compared with the Italian Fascist onslaught after the failed assassination attempt on Graziani in the 1930s. Luckily, Eritrea's armed struggle had by then already established semi-liberated areas in the countryside. When the terror was unleashed in Ethiopia, hundreds of them were able to escape either singly or in groups. Unlike their counterparts, the Ethiopian elites, they were spared the ignominy of facing the military courts, and the firing squads. They were, according to the Tigrigna phrase, Wtsa�e Me�at. Or were they? A weird reception awaited them in the Dejen areas of the Selfi Nasnet. After trekking for several days, emaciated, they arrived at the training camps in the Sahel. They then had to put up with the rigorous military training and the grueling criticism and self-criticisms sessions (denunciation) for weeks. To instill fear in them, propaganda about the "Menkae" was not excluded.
Soon enough, they would be visited by the Halewa Sewra [Revolutionary Guard] heavies. They were often interrogated by Solomon Woldemarian, Haile Jebha, and Tekle Aden. They would be questioned about people they know in the �Meda� (field), books and pamphlets (Tehisa is often mentioned) they read. This was a trap to isolate the educated types. Most would soon be demoralized and submissive; the rest were dealt with.
Prior to the Halewa Sewra, Selfi Nasnet "security" concerns were largely handled haphazardly. A list of peoples name under suspicion in folded notes will reach the ganta leaders and commissars from Isaias. Envelopes were scarce. The suspects are then singled out from their platoons, and led to the valleys before dusk. The platoons leave for Teshkil or Defa�e at the mountains. Then the executions begin. To stifle the unfortunate victim's cry, empty cooking oil drums are beat incessantly in lieu of a Kebero. A particular incident is worth mentioning here. Asmerom Ghebreegziabher, a member of the five-man leadership then, arrived with a large sized cassette player. Meanwhile, I saw a column of unarmed fighters being stealthily led to the riverbed in the proximity, at Tegih. An "impromptu" guayela [dance] followed accompanied by the loud blare for a couple of hours. It reminds me now of the violins that were being played in the Nazi death camps. The Selfi Nasnet, a totalitarian organization since its inception, had some sort of cubbyhole for everybody. In the beginning, suspects and victims were mostly from the semi-proletariat class, according to the Marxist lexicon. Intellectuals appeared immune from the witch-hunting. This temporary reprieve did not last long. The first victim from such group was Meles Ghebermariam, before the bell tolled for many. I believe he was a former university student, and joined the Selfi Nasnet from overseas. After serving as a ganta commissar, he was suddenly apprehended in 1973, and executed. Nobody raised a finger for him. Fear and conformism reigned then. Everything was hushed up, except for dubious rumors. He was allegedly a foreign agent, and particularly the CIA. The fact that his father was a high-ranking officer in the then Emperors' army (possibly from Digsa village) was a factor thrown around. The victims of Halewa Sewra and its predecessors were not solely intellectuals. The series of purges carried by Isaias: the "Menkae" movement, the "Desawi" group led by besay Goitom, and the "Yemanawi gugele� under Solomon Woldemariam are lately getting publicity. To dwell on the fate of these victims only is, to me, elitist and biased. Halewa Sewra's victims were from all walks of life, and include hundreds who did not subscribe to any opposition politics in the meda. They have remained faceless, and nameless, among the thousands of our disappeared.
We have, therefore, to "confess" a thousand times without any moral compunction, notwithstanding the advice from some corners to refrain from doing so. For some of the current victims were victimizers too. Eritrea's recent history has lately been a gruesome scene of successive victimizers turned victims. Except for the supreme victimizer, Isaias, who has still remained unscathed.
The Menkae Memory”
(By Meharena Hadgu)
The word Menka stirs interest in people. It has become a household word, and yet, most have no clear understanding of it. For many years the EPLF leadership of being a regionalist movement labelled it. It was a forgotten issue of a sensitive part of the Eritrean guerrilla movement. The recent repetition of this has made us want to know more of these Menka martyrs. The Menkae were not even honoured as martyrs but hushed away and their files closed, according to a video interview with the president in 1996.Many went to meda after they graduated or little time left to graduate. In the 60s and 70s it was a great honour for a family when their child graduated from the university. It was a big celebration with relatives and friends invited. The future was bright for the graduated and became respected members in their areas. When these students went to meda they knew how much they were sacrificing in their personal lives. They preferred to live in constant fighting, no beds or good food and their lives at stake anytime to be lost. Their sole aim was the liberation of their country Eritrea, which had suffered much and most were acutely aware of the situation. Many students living abroad chose to join the struggle from Europe, USA, Arab countries and the eastern block. In fact, the students of the eastern countries made agreements that the one finishing his/her studies was to join meda directly. This is regarding both fronts ELF and EPLF. The starting of the "Menkae" movement was not a consolidated or united movement. This was a mosaic of different grievances that was named Menkae. Meharena Hadgou is a war veteran in EPLF joining in 1974 until liberation time. The narration below is his recollections in his early years while joining the front. I thank him for his memories and his kindly patience to answering my numerous questions. Stories like Meharena make us understand the daily lives of fighters which so far have been told very little of. It shapes the picture of the reality of those days. He has given out a video narration concerning the Menkae martyrs. Though this story was of the bad times, there were many good and worthwhile days in meda. The book, "Destructive Movement" was written by Essaias in 1976 and it was distributed to all fighters, 3 years after the movement. We all read it. A political commissioner, or a Cadre of a haili kept it. I was a Cadre and member of the Party. Anyone opposing was taken away, as many were taken away secretly.
The movement started sept 73 went on slowly until the end of 1976. Then another incident, the "Yemeen" were accused making the previous movement as past history. It was said that these Yemeen were acting against the Menkae and that all should be careful from them. What Essaias said about the Yemeen was that they were the ones who purged and liquidated the Menkae, like Selomon Welde Mariam. He and his group were accused of pretending to be against the Menkae were fertilizing their own agenda, regionalism. Food was scarce in the struggle time. The cheapest commodity salt was not available to us daily. Sugar was forgotten that we did not drink for many years. We ate no breakfast and usually had one meal a day. Fighters sacrificed a lot for their independence and what we are seeing today was not their payment. After liberation fighters wanted to be governed with written laws, wanted peace with neighboring countries, wanted their rights to be fulfilled. But Essaias soon became like a king and demanded only he knows what is best for the country. He discredited any person with knowledge and held all power. Only he wanted to dictate on land, constitution, multi-party systems etc. Those governing under him also became against us. At last even they understood this was taking the country into ruins and told him to make changes and reform. He instead charged them of treason and losing the fight, though they were experienced leaders. To tell you briefly again what I had said on the video, the movement started publicly in Sept 73. Essaias and Romadan though said that it had started earlier secretly. When these people started the movement, the gedli did not have a program or bylaws. It had no structure. It was controlled by guerrilla rules. There were 22 or 32 military rules in the PLF, or Hizbawi Hailetat -:H. H. Examples are, if one breaks a needle, or seen suspiciously, 7 days punishment. If one damages a weapon, or aims his gun on your comrade, if one leaks secret to enemy, etc have their punishment. This could not bring us close to the civilians. When those like Musie, John etc joined the front, they were university students, and they had read many books, different laws, knew of the structure of foreign guerrilla fronts. They started giving advice how the front should be. They would constantly write in daytime returning to their difaE by night. They and Essaias and others formed the programme how H:H: was ruled by. This was done when Isayas with agreement made them committee to draft the structure of the front. That time the H:H: were three groups, the first one led by Romadan, the second one by Isayas and the third, the Obel. Totally they were less than 500, maybe 300. It was the progressives (dubbed Menka) who said since we live along civilians, should form civil relations, civil and fighters to be ruled differently, Jemahir, and the medical section. When wounded, people should not be treated abroad and medical staff should be made for civilians and military separately. To start a news department which should publicize the struggle. Better storage of weapons as water, floods and rain damaged weapons. There should be a group who oversees everything. That the enemy should not make counter offensive we need intelligence unit, who follow the enemy's positions to hit it on its weakest point and study its strong positions, and how to confront it. The army should have a leading military staff. If the Eritrean society is to change, all the civil areas we control should be given basic education, as well as all fighters. Fighters should be made politically conscious. Foreign relations should be structured.
Those abroad should have close contact with the front and be able to supply what the front need. All the structures were drafted in Gereger, Sudan. (I had not joined the front yet). Then, the 1st and 2nd groups (PLF1 and PLF2) shimageles met and decided that their present position was favourable for the enemy that they should unite, Isayas and Romadan. And the unity came into being. But the Obel group said they wanted to stay out until what they did not understand became clear for them. The first two groups made the mixing up. They were about 6-7 Haylitat, including the Kifletat. One Hayli comprised of 50-60 fighters. What the progressives now said was, since two of the fronts have united, the situation is progressing and we are getting larger, we should make the drafts we made into action. Anyone can make rules suitable for their situation; one does not have to be well educated to do that. If one fighter deserts, though he joined the front knowing he would probably be killed in battles, is condemned to death and his family has to compensate the weapon. The progressives argument against this was, "my parents did not send me to the front, they expect me to be living either in Addis or Sudan, or even dead. Why should they be made to pay? I should be killed deserting; even death is mild, because I am betraying my oath. Why should my family pay for my deeds? We have worked very much to draft the rules as agreed and let us make it into use". Isayas then said, after having exploited their minds, about their timing. He even accused them to be against the 2 groups uniting, that they wanted to split our unity, saying we are progressing well and these want the destruction, they should be charged, they are opportunists etc, when victory is near hand. (Just like what is happening now). The new Cadres like Wuchu (uneducated) were told by Isayas that these educated ones are suppressing the uneducated wanting the power for themselves; they want to destroy us, these with Gelegif pants (word used by the rurals for city boys wearing belly bottom pants). The situation that time was not as open as now.Many of us were new, naive and students. We suggested that confrontation should be solved democratically, if they are destructive should be charged, this is not right way for the front to condemn them without their say. Also, there were horrible battles between the Jebha (ELF) and us. The Menka suggested we are brothers killing each other prolonging the struggle and losing fighters unnecessarily. It must be stopped and with selected shimageles, come into agreements. Isayas and co answer was, "aha, the Ama (Jebha was then known as Ama) tried to wipe us out and we survived. Now shall we ask forgiveness for their guilt?" This was made a great deal of. Isayas accused them further that they told the Obel to stay away and join when the Menkae took power.
At that time, the Ethiopian EPRP fighters like Berhane Meskel were in Sahel to train, and the Menka were accused telling the EPRP to wait until the Menka came into power. And inside the front the Menka were charged of being regionalists dividing the front. This was not true, but charged by Isayas. (the same for the present situation). Those of us who suggested this be solved peacefully were imprisonment. This was making us to sit under trees. At night we were surrounded taken away separately far away and beaten badly to confess. We had to comply to stop the beatings. They then told the others that we had recanted because we did not know the whole thing. Most of us students were beaten. Some of us are lucky to have survived this long, maybe so that we will tell. Otherwise, survival was difficult, with the constant hunger, thirst etc.
As prisoners, we could not move an inch. Even if a snake came to bite us we ask the guard first and we were infested with lice. One having diarrheic has to ask permission to relieve himself and told to wait that he passed it inside his pants. Then he is accused of deliberately passing into his pants to make a bad smell and thus beaten. A dehydrated person unable to control himself is beaten badly, as I have seen it. Those not having seen this cannot believe they are so cruel to their own fighters. Prisoners are put around a tree their backs to the tree and about 3 guards to each group. The others, of Musie group were separated from us. We cannot talk to each other. If a person wants to urinate, he asks the guard for permission who answers wait. Times we are tied in hands are when a fighter is in discomfort and asks another prisoner to lend him his blanket, without permission from the guard. Then he is taken out and asked what this code meant and is beaten to confess. The prisoner tells the truth and the guard says he should have asked first. The guards had all power on us and were cruel. He is tied hands and legs and after beating put in the sun all day. There is a plant called Ubel growing in riverbanks and taking its time to dry, it twists like a whip. One beaten with it is horribly hurt their backs becoming open wounds. Some have died of this beating. Too bad those who could have told have done. If a person wails in the beating, cloth is stuffed into is mouth and only the eyes communicate. The beaten person faints and goes into shock, shaking. It happened to me and I saw it on others. Yet we continue serving the front and did not think of fleeing lest those behind me get all the punishment. When visiting the "toilet" prisoners are taken out in 2-3 lines.
The first line take off their pants and kneel down, facing their guards. The next in line face to the opposite. It was a humiliating situation. I used to see the 4 female fighters when I was new. The living way was such that by the riverside we lived, the girls used to come and visit us. Then a 5th girl joined them, Abeba Haile who lives in Europe now, wife of Stifanos Bruno. (Dehab Tsafatsion and Aberash Melke were executed) .Werku Zerai and Maasho are still living in Asmera. She was imprisoned for a long time, and I do not know what she said to have been freed. Abeba was an airline hostess.
Though she was in training when the situation arose, she too was imprisoned. Since Maasho was from the peasant, they said she knew nothing of it and let her free. She was not educated like the others. Abeba too was not imprisoned after having been in the training and was carefully handled. In 76 she had tried to write a book about women, a handwritten diary that was negatively looked upon.The torturers were later exterminated accused of being "Yemin" in turn. We were told they beat us and we should do the same to them, but we refused. That was the leaders of mela (strategy), to make us revenge, leaders giving them to us. This was a game, was very difficult time. We are sorry for the happenings and we cannot forget them. When I told this in the video recording, some people called me. One, called Kidane living in Canada said I told of his story.
He could not remember me. I remembered him and told him he was from Akhria area of Asmera, and thru the phone conversion slowly started remembering me. He was one of the beaten ones. I told him don't you remember we met in Amader, Tsellima when you joined the ELF and I was disappointed asking you what our oath was. He remembered that conversation but not me. Some fighters were told they were misled by so and so, from their circles, come to your senses etc. Much was tried to make them betray their comrades. They answered that they were "acting innocently, wanted democratic solutions, nobody wants to hurt another fighter, we are not regionalists, what fabrications you make recently we have no hands in them."
Most of who beat us are already martyred. I remember one called Tekie martyred in the battle of Genfelom near Keren He was a Haili leader in Deboloch difa then. He was from the peasantry. Isayas had convinced them the educated ones were trying to take their power of the masses. But we were fighters for our country. We the army were later told of the death decision on the Menka, but not how. After we were released, others there told us that the prisoners were taken away one by one, when we asked them how they were killed. I have a friend residing in Atlanta now, who was prisoner after my release. He said they were taken tied with handcuffs (Ganshur, chain). Handcuffs could be brought from Sudan or Ethiopia. The prisoners were taken tied and the handcuffs alone were returned. This means the prisoners were killed. Earlier, we thought they were taken to a "court" because we assumed we had one.Or that they were sent to Hailitat or discharged. Then when the handcuffs alone was being returned, word spread out secretly that it means it was killing practice. Seeing the cuffs, one said, when is my turn? Knowing it meant certain death. What could this person do? Even if prisoners were together for a year, not talking or even seeing each other was allowed.
The executions of the progressives were widespread. Their killings became known because they were fighters before us, were more educated, were political commissioners etc. There are many more who were killed and not talked about because we were constantly moving and in between battles that when they are taken away with some excuses, we assumed they were just transferred from us. Some were accused to being spies and those who knew of their innocence are not living to tell. Although there could have been spies inside us, they should have been charged democratically, not beaten to death in interrogations. I know Memhir Tesfu Zewde and what is said is true because he was a prisoner. (He stated in audio interview that the Menka were slaughtered by knives). He was taken away to be killed, saying he was being freed, but to be killed, and the Sudanese rescued him, he had lost a leg earlier. He was imprisoned, let out to fight and again imprisoned. In the DM 73, Isayas wrote the progressive ones were spoiled and had class problems. They were not at all spoiled in the meda, they suffered much on the contrary. The female fighters had shed away their city upbringing habits. Even sanity pads were not available for them. They were beaten like the men, killing was not denied them. All prisoners were beaten almost on monthly basis; to make them tell whatever secrets they were supposed to have. How many brave fighters were crying in pain. Those like Sebhat and Petros were with the movement, but passed all info to the leadership and were put into the leadership circle. Sebhat has even forgotten his 30 years comrades, let alone of that time. Those who were beating were under Selomon Weldemariam who himself did the beatings and ordered beatings. Naizgi Kiflu was a beater. The leadership, Isayas etc, did not like Selomon the scoundrel. There was disagreement inside the leadership and the Menka debacle was used to solve it. They accused him of being a regionalist and isolated him. Musie and the others defended him why this was done.
He was told the Menkae were using him to take power that he became their adversary. He was made chief of Halewa Sewra and did the ordering and killing of the Menka. At last he himself was eliminated, and died badly. Isayas gave him free reign to kill anyone, even though they disliked each other. Isayas wanted Selomon to do crime and later told that Selomon was the head beater and killer, who spilled much innocent blood.
Because of that people are beginning to dislike the revolution and that he was placing selected people in positions. Selomon does not show easily his personality, seeming like a te-waz-aye, but was rough. We used to dislike him he killed many people. He was a bad regionalist. What Isayas starts Selomon followed. It became as if they did not dislike each other. Teklai Aden was brought later. He was then brought to the Central Committee, and scared others. He started beating Selomon. This all was like a drama. Anyone following the truth ended up dead. He joined with us and knew of the Menka, but was afraid to join. He came from Aden, several years there, and spoke Arabic unlike us who came from Asmera. He was a university student and read books. From Haili leader he came to the CC after the guba-e, but with little vote. He had not matured well. There were others brought to the CC quickly. He then was made head of Halewa Sewra and used his power. He was a drinker and womanizer living in Dekemhare and was recalled to Sahel to lead the Halewa Sewra. He was in contradiction with some leadership members like Ali Said Abdella and Duru, with confrontations and arguments. We do not know what his disagreement with Isayas was. His personality became obvious and was accused of corruption. It was then mizlak time.
It was said that Isayas (megnahti), rebuked him, only they know the case. We knew their arguments. Suddenly we heard he had deserted and spilled many secrets. I do not have his writings or radio interview. We in the meda did not see it, and if the leadership got it we saw nothing, not spread to the lower cadres. It must have reached abroad. We were discouraged from listening to his words. Duru was not in the Menka situation. The Ethiopians imprisoned him. Haile Menkerious was not in the leadership then. I forgot who the charging committee were, but it was said that Adhanom boycotted the committee. And in vengeance for that, Shabia was against him always. Selomon was against Tewelde Eyob and Asmerom. Isayas criticized Selomon that he had said negative words against these two. Mussie and others were there in the meeting and said old critics are not valid now. Musie said Selomon was a democratic person why are you isolating him and because of that the meeting became dispersed. Said the front should advance democratically not bring old feuds here, showing his opposition against Isayas and you others should observe this situation. Another day others were added to quell the conflict. Musie criticized Tsegai Keshi why one leaves a meeting, it is not a handkerchief, mendil to sit and leave as one wishes. Then Tsegai hits Musie and the meeting is dispersed. Musie was sent to clinic and Tsegai in temporary prison, military rule. I was new then in training centre and the clinic was there that after 3 days Musie was with us.We were all in one riverbank. The fighters used to come and talk with us there. Musie had come to our centre to talk those he knew, and his head was bandaged. We did not know each other, it was the first time I saw him. Fighters are made to dig told it was for planting trees or latrine. When enough dug, they themselves are killed and buried there. Some fighters were killed by gun in riverbanks. When being killed, we are told an investigation was made but we have no proof. Since we all did not know each other, one may say so and so was taken away from us. We did not know all who were taken away from us. The situation of the Menka became talked of because they were known fighters, in position and cadres, were visible by the military for their movement. One marks seeing them being taken and others say so and so was taken from our group, taken to Halewa Sewra. And with no news from them it becomes known they were killed. They did not need to make music to silence the killing. Because we lived in an isolated area, one can shoot to kill apes, snakes, birds, or try a new weapon, that a shot heard was not concerning.
We had a fierce battle with Ethiopia then, for 2 weeks, end of December to mid January. It was just then the military revolted against Haile Selassie. The Ethiopians started the fighting coming to Sahel. 5 fighters were martyred then, one called Amr and one Alem Negassie who joined 3 months earlier and trained, Haile, Osman Drei, others I remember. We were told of the outcome that 5 were martyred, the numbers of wounded and that it was a difficult fight amidst our lack of food, that Ethiopia has lost morale. A little note was brought and read to us. The Menka were killed in Bliquat. We had moved from Gereger to Bliqat, unpopulated area near Alghen, which was military base of Ethiopian army later taken by us led by Adhanom Gebre Mariam. After over a year we heard rumours that the Menka were killed. Some had escaped from the prison. ELF said that those known as Menka were killed naming them that those who escaped from Shabia told of this. ELF gathered people and told this and we heard from the people. The ELF in their seminars told secrets of us. On the 23 January 1977 conference, their execution was told then. We were not told before that. Since we were fighting the enemy, many things were kept secret from us. In different times we heard so and so was taken prisoner because he was Menka, and those allegedly caught deserting that we did not notice the happenings.
It was after the Menka happening that Halewa Sewra was put to use. I read the writing of Isayas "Destructive Movement" in 1976, I do not know when it first came out, we knew publicly of it then as we cadres were taught of it, after the 5th round, zuria. We were in rounds, 150 to 200 fighters getting cadre education, gathered from all hailetat and kifletat of the front. Mesfin Hagos was one of the top leadership and nothing is done without their signing. Isayas was the chairman, others being Mesfin, Selomon, Tewelde Eyob who was later killed being part of Menka, and Asmerom Gerezghier. From the PLF 1 leadership were Ali Said Abdella, Romadan Hamed Nur and others unknown who were added. So in the killings of the Menkae, Alamin and others were selected as committee. If this comes out publicly there will be tewatet, sahabo guteto. 6-7 committee members were elected, and those like Mesfin were top leaders.
A brave member of the leadership, Tewelde Eyob was killed, he did not even sign for the killing. He said let us democratically solve the situation. When it was said this movement was destructive, Tewelde said no, this is a conflict only not a destructive one and we can lead them to the right way, it is not a criminal charge, but was said he too was against Shabia and eliminated.
The Menka movement started in September and Isayas talked of it in January. A paper is lost written by Tewelde Eyob "at Adobha meeting we claimed our youth were killed and we condemned the ELF. This will be our everlasting condemnation, the case must me democratically changed." He was charged to becoming Menka and secretly taken down from top leadership post. He was imprisoned in June or July of 1974 and killed like the Menka. We all knew he was killed. Nothing is kept secret forever. Some secrets are known from leaders. Goitom Bisay was made shimagelle in first committee to study the conflict and said the proceeding was wrong that Menka were correct. He was called Menka and put down from responsibility and followed upon. Was said he was writing a book for the front, translating, and made to disappear. Wedi Fenkil was a known warrior. Dr Bemnet was charged to being Menka. He was from Addis, was in cadre school. He asked about the Menka, though I never saw him. It was said hat he bombed himself. He was of same school as Yohannes and Musie. He wanted clarification, which was regarded suspiciously. A person is followed upon and disappears. It was common saying one killed himself even if he was a liked person that they killed him while trying to desert, what was not said. Deserting was crime to be killed. The life was difficult and one may want out. Someone plans escape and was caught. After the 1973 experience, we were demoralized not to inquire about our comrades or ourselves. When a comrade is taken away we did nothing.New comers were told about the Menkae as a lesson. Anyone seen reading Marx, Lenin or Mao etc was seen suspiciously believing he will be a Menkae, that many stopped reading in fear. It was the ELF who held a weapon in one hand and a book in the other, unlike us. Many pretended to be uneducated because they were demoralized to what happened to those who read. It was not time to write against Shabia in struggle times, and many secrets untold. ELF as the adversary wrote much against Shabia. As ELF was condemned by Shabia as a lords group, and unable to liberate Eritrea we belittled them. Some deliberate lies were found out that everything else was unbelievable. Haile Selassie Gebremedhin was one of the top Menka. He was educated. He was in Ala in 70 and taken prisoner by Ethiopia. He was not imprisoned long; his family worked hard to have him freed bribing the authorities saying he had planned to give himself up. He had asked why the movement was seen negatively, but be studied, telling this to Isayas. Many who were with the movement changed sides when fighters were imprisoned. He, John, Afwerki, Tareke, Rusom Amma, Dehab Aberash, Werku, Debesai G Mikel (friend of Musie, taken later than the others he was taken from the front line). Some succeeded escaping from prison. I know one called Wedi Blatta (mayila Tsenadegle) of Menka movement. He joined ELF and was martyred fighting. It is said he told of many secrets. Maybe the security members of ELF have the documents. Abraham Tewelde died 3 years before Derg came. I heard about him, as a brave man. Haile Jebha was one of the Menkae beaters and than himself killed for being a torturer. Tekle Aden came after the Menkae time. As prisoners we did not sit together like in a house. Prisoners were ordered by their guards to build a fence, like animals fence, and imprisoned them. I cannot remember all the names. Many names are forgotten except the leadership or familiar ones. Fighters were taken away from front lines and disappeared. Some fighters came from Addis and abroad hearing of the Menkae killings and asked about it. They were met suspiciously and made to disappear. Petros Yohannes had stared inquiring already from the US. Why the fighters were imprisoned because the educated ones asked for democracy, and what more have the ELF done? So what was the reason Shabia split from ELF then?
Though I did not meet him, he was said to be a brilliant person. We heard that a man called Petros Yohannes had entered meda from the US and was killed. We heard that Petros was made to stay behind since they were called to meda for work. One wanted in meda was told to represent and go to meda and held there. Meriam Hagos is an example. She was invited to meda to see progress and forced to stay and she was in meda until the end. Nobody knows about them. Though we did not see them we heard rumors. The secret comes out somehow some saying so and so was taken away from us and killed, like the US ones too. So and so was killed yesterday, etc. But nobody dared asked openly, all the lost ones were made to disappear. Even now it is the same situation. In 1986 there was a big fighter’s movement. Those living standards were bad and differences between fighters and leadership. I have heard that some of those who started this movement were taken away and killed, or made to disappear. And some who just when it started knew they would be killed and fled to Sudan. There are prisoner fighters who are still in prison now. Bitweded after liberation was made administrator of Assab at first. Then he was imprisoned. Nobody has officially inquired about him though all knew about him. Some say he stole, some say he refused Isayas to send goods to Ethiopia that it belonged to Eritrea, telling Isayas to order him in writing. That he dared Isayas, and some say he was trying to sell the goods contraband to Ethiopia and the fighters doing that were caught. When imprisoned and asked, they said it was Bitweded´s order and they got free and he taken in. Nobody knows the exact reason why Bitweded has been imprisoned for 13 long years. We can understand those inside Eritrea are afraid to ask. What about those abroad? They were systematically made to ask nothing. "You cannot enter home (Eritrea), Shabia´s stick is long it will reach you". When I first came here and started telling against the Shabia, people began to evade me, even those I knew for many years. I was told I was already a convicted man by the government and they were afraid to be implicated with me.
They are afraid from being imprisoned in Eritrea saying they were together with Meharena. It is obvious when going in gatherings like a funeral, they stare at me and when I stare back, they bow their heads, even the higdef ones. Because they send false reports and rumours against us, especially in a democratic country of USA. What is the meaning of democracy if one cannot ask? What is the meaning of having served meda for many years, martyred, even become handicapped? The reason I fought for my country was to see a free and democratic government, free to live in. That is why I decided to come open. Who should be the free man, all the people should have equal rights. Those who fought for their country should not be regarded as enemies.


Tuesday, September 16, 2008

The Third wave and the unsolved Eritrean and ethiopian issue






ይድረስ ጥያቄየ ለአቶ ክፈሉ ታደሰ
እና
ለተቀራችሁት የኢሕአፓ አመራሮች ከጌታቸዉ ረዳ የኢሕአፓ ከፍተኛ መሪ የነበሩት አቶ ክፍሉ ታደሰ በኢሕአፓ ዲሞክራሲ የህዋ ሰሌዳ ተለጥፎ ያዳመጥኩት “የፓል-ቶክ” ቃለ መጠይቅ እጅግ ጠቃሚ የሆነ ብዙ ትምርቶችና ካሁን በፊት ተደብቀዉ የቆዩ አንዳንድ ምስጢሮች ሳይቀሩ ለሕዝብ ይፋ ያደረጉበት መድረክ ነበር።እንዳዳምጠዉ ለጠቆመኝ ወንድም አመሰግናለሁ።

ከዚህ በታች የማቀርበዉ እላይ በጠቀስኩት መድረክ ተገኝቶ ኢሕአፓ ስለ ኤርትራ ጉዳይ የነበረዉ አቋም እንዲያብራራ ሲጠየቅ የሰጠዉ ምላሽ የተሸፋፈነ ከመሆኑ አልፎ ኢሕአፓ በፕሮግራሙ አስፍሮአቸዉ የነበሩትን ኤርትራን በሚመለከቱ ጉዳዮች ለምን በቀላሉ ሊያልፈዉ እንደፈለገ አልገባኝም።
የሶማሌዉን ክብደት በመስጠት ጠለቅ ያለ ማብራርያ አሰጣለሁ ብሎ በይደር ለሌላ ቀን ቀጠሮ ሲያስመዘግብ፤ ሕሊናችንን ሁሌም የቀለበዉና ለወደፊቱም ከህሊናችን ላንዳፈታም ቢሆን በቀላሉ የማይታየዉን የኤርትራ እና-የኢትዮጵያ ጉዳይ ኢሕአፓ የነበረዉ ግንኙነትና እንዲሁም ለወደፊቱ ኢትዮ ጵያ ምን ዓይነት ስልት ብንከተል በልጆቿ ባንዳዎች እና በዓለም ዙርያ ባሉት ጠላቶቿ ሴራ እየተደረገባት ካለዉ ግፍ በእንዴት ፍትህ ልትቀዳጅ እንደምትችል ካለዉ ሃበታም ልመድ እና ዕዉቀት መግለጽ ነበረበት እላለሁ። ያ አላደረገም። ወንድሜ አቶ ክፍሉ “ሦስተኛ መስመር” የሚለዉ የኢሕአፓ መፍትሔ ምን እንደሆነ ስላላብራራዉ በእኔ በኩል በፍጹም ምን ማለት እንደሆነ አልጨበጥኩትም።
እንደ አባባሉ “ሦስኛ መስመር” ከሞላ ጎደል ቅንጅት የተከተለዉን ዓይነት መስመር እንደሆነ ነካክቶታል።የኤርትራ ጉዳይ በሕዝብ ድምጽ (በሁለቱም ህዝቦች መካከል?) መፈታት አለበት ሚባል ከሆነም እዚያ ሊያደርሱ ሚያስችሉንን የትግል ስልቶች “3ኛ-መስመር” የሚባለዉ ነገር ካሁን በፊትም ሆነ አሁን የዘረዘረዉ ነገር ስለሌ ያንኑን ማብራራት ነበረበት። አስካሁን ድረስ መፍትሄ ያላገኘ ለወደፊቱም ከፍተኛ የግጭት መንስኤ የሚሆነዉን የኤርትራ እና የእኛዉን ጉዳይ ህዘቡ በተለያየ ስልት ተሰልፎ መፍትሔ አጥቶ “አልቦ ስልት” ሲዋዥቕ 3ኛ መስመር እንዴት “ብቸኛ” መፍትሔ መሆን እንደሚኖርበት ግልጽ አንዲሆን ጋባዦቹ ተመልሰዉ ጥያቄዉን ብየነሱት መጠቆም እሻለሁ።

ያስ ባልከፋ፡ወንድሜ አቶ ክፍሉ ለኤርትራ ጉዳይ ተጠያቂዎቹ ንጉሱ እና ደርግ ሲያደርግ 3ኛዉን መስመር ሙያ ላይ ቢዉል ዓይነተኛ እና ብቸኛ የግጭቱ መፍትሔ ፍትሕ አመንጭ ይሆን አንደነበር በሙሉ ድፍረት አስቀምጦታል። ኤርትራን በሚመለከት የንጉሱ ሹማመንት የተከተሉት/የፈጸሙት/ ስለቶች እና ያስተዳደር እርምጃዎች ባንዳንድ ሁኔታዎች የሰላም እና የፍትሕ መብት ተጻብኦ እንደነበር ባይካድም፡ ኢሕአፓ በትግሉ እና በስልቱ እንዲሁም በፕሮገራሙ ላይ የፈጸማቸዉ አንዳንድ ስሕተቶች እንደነበሩት ሁሉ ንጉሱም በዛ መልክ ባስተዳደራቸዉ የታየዉ የትግል ስልት እና ድክመት “የጥላቻ እና መለያያ መንገድ ያስተናገደ ወይም በር የከፈተ” ተብሎ መወንጀል ተገቢ አይመስለኝም።

የጥላቻ ፖለቲካ መነሻ እና ፈጣሪዎቹ/አስተናጋጆቹ ዓረቦቹ እና ዓረቦች ነን ብለዉ ጸረ ክርስትያን ሃይማኖት እና ጸረ ኤርትራዊያን-ክርስትያን የቆሙት ጸረ-ኢትዮጵያ “ቪቫ-ኢታሊያ- (ፕሮ-ኢታልያ-የጣልአን ደጋፊ)” እና በምዕራባዊ ቆላ ተወለጆች የራቢጣ አል ኢስላሚያ/ጀብሃ..ሓራካ… እስላሞች እና በሗላም በትዕቢት የተወጠሩ ሲ.አይ. ኤ ያደራጃቸዉ የክርስቲያን ጎሰኞች እነ ኢሳያስ አፈወርቂ የመለያየት እና የጥላቻ በር ከፋቾች ምክንያት የሆኑት እንጂ ንጉሡ እንዴት ሊሆኑ ይችላሉ?
ዛሬ ኤርትራ የምትባል የድሮዋ “ምድሪ ባሕሪ”- “ባሕሪ ነጋሲ”-“ባሕረ-ነጋሽ” “መረብ ምላሽ”…..” ዛሬ ለኤርትራ መገንጠል እንደዋነኛ ተከሳሽ ሆነዉ በየመድረኩ እየተከሰሱ ያሉት ንጉሱ በትግላቸዉ ባስመለሷት ኤርትራ ተመልሰን መዉቀሳችን ሊገባኝ አይችልም።ኤርትራ ከኢትዮጵያ በፌደረሽን ትቀላቀል ብለዉ 46 አገሮች ድምጽ ሰጡ። ኮሚሽኑም ኤርትራ ሄዶ ሕዘቡን ስሜት ይዞ የወሰነዉን ታዉቁታላችሁ።በፌደረሽን ለጊዜዉም ቢሆን (10ዓመት) ትተዳደር አሉ እንጂ ለወደፊቱ ከኢትዮጵያ ጋር እንዳትዋሃድ የሚል እኮ የለበትም። ከሕዝባችን ጋር እንዋሃዳለን ብለዉ ዉሳኔ ያሳለፉትም እኮ “ትዋሃድ ብለዉ የደነገጉት” ንጉሡ ሳይሆኑ የኤርትራ ምክር ቤት ማንም ተጽዕኖ ሳያደርግበት ፍጹም በሆነ ዲሞክራሲ ተመርቶ መዋሃዱን እንፈቅዳለን ሲል ህዳር 5 ቀን 1955 ዓ.ም ውሳኔ አሳለፈ። ውሳኔዉ ለኢትዮጵያ ፓርላማ ቀርቦ በዚህም ፓርላማ ዉስጥ ከ250 የሕዝብ እንደራሴዎች 25ቱ የኤርትራ ሕዝብ እንደራሴዎች 25ቱ የኤርትራ እንደራሴዎች ናቸዉ። ከ125 የሕግ መወሰኛ አማካሪዎች 5ቱ ኤርትራዊያን ነበሩ።ከነሱ መሃል አንድም እንኳ የተቃዉሞ ድምጽ አላሰማሙ።ብለዉ ከፓርላማዉ እና በዉሳኔዉ ውስጥ ተካፈሉት ምስክሮች አሉ።(የአፄ ሃይለስላሴ ታሪክ -ደራሲ ብሪሁን ከበደን ይመልከቱ)-;-
ታዲያ ይህ ሕጋዉ መድረክ ጥሰወዉ በጉልበት ፍትሕን ለመዳጥ የተነሱ ለዓረብ ያጎበደዱ ህሊናቸዉ የሳቱ “ወገኖቻችን” እነ አድሪስ ዓዋተ በፈጠሩት ጥላቻ እና ጦርነት በምኑ ስሌት ንጉሡ ተጠያቂ ሊሆኑ ይችላሉ። ጦርነት የጀመሩት ንጉሡ ሳይሆኑ በዉስጣቸዉ እንኳ መስማማት አቅቷቸዉ የሃይማኖት ፤የነገድና የቡድን ግጭት ፈጥረዉ ቢያነስ 17 ዓመት እርስ በርሳቸዉ “እስላሕ”፤- “ኮሚቴ-ተጋደልቲ”- “ሱሉሳዊ- ሓድነት( ሱሉሳዊ -ሓድነት-ኢሳያስ የነበረበት አንጃ ነዉ) እያሉ ገና ጃብሃዎች ትግሉን “ሃ” ሳይሉ ራሳቸዉ የፈጠሩት የመገዳደል እና የጥላቻ ፖለቲካ እንዴት ተኩኖ ንጉሱ ለጥላቻዉም ሆነ ለመለያየቱ ተጠያቂ ሊሆኑ ይችላሉ?
የደርግ ሠራዊት አመራር በማጣቱ አንጂ ጥያቄው እኮ የአገር እኮ ነዉ።ወደብ እኮ ነዉ። “የመኖር” ወይንም “አለ-መኖር” የባሕር በር ጉዳይ ባለቤትነት ጉዳይ ጥያቄ እኮ ነዉ። የተካሄደዉ ትግል እኮ አበሻነታቸዉ በጣሉ አዉደሐዋሪያቸዉ እና አዉደ ዓመታቸዉ በፈረንጂኛዉ የሚቆጥሩና ከሚያከብሩ አበሾቹ ወገኖቻችን ብቻ አልነበረም።ትግሉና እና ጦርነቱ እኮ የተካሄደዉ ከራቢጣዎቹ ብቻ ሳይሆን ከትልልቆቹ፤ከጥንት ጠላቶቻችን ከ ዓረቦች ጋር እና ከፈረንጆች ጋር ጭምር ነበር!
ኤርትራን እንደገና ከራሷ ደም እና አጥንት ጋር ያዋሃዷት የንጉሱ ጥረት ታክሎበት እኮ ነዉ። ታዲያ አሳቸዉ ባሰመለሱት አንዴት ተመልሰን አስነጠቁን ብለን በግምባር ቀደም ተወቃሽ እንወቅሳቸዋለን? ምድሩ የተወሰደዉ በ1881 ዓ.ም ሲሆን በተወሰደች በ66 ዓመት በ1945 ዓ.ም ነዉ። የ አክሱም ሃዉልት ያን ያህል ዓመት በጣሊያን ይዞታ/አገር ቆይቶ ወደ ቦታዉ ዛሬ ሲመለስ 60 ዓመት በጣሊያን እጀታ ነበር እና ሃዉልቱ የኢትዮጵያ ንብረት ቅርስ መሬት ድንግያ አፈር ዕዉቀት እና ታሪክ ቢሆንም በሬፈረንደም በሕዝብ ድምጽ ለጣሊያኖች ወይም ለእኛዉ ለባለንበረቶቹ ይወሰን እንዴት ማለት ይቻለናል? የተበታተነዉን ሕዝብ የሰበሰቡ፤ያገናኙ ናቸዉ። ጥፋት አድረገዉ ነበር? አዎ! በሰዉ ሕይወት ወንጀል እና የመብት ረገጣ ፈጽመዉ ነበር? አዎ! ማን አለ በዚያ የስህተት ጎዳና ያልተሸጋገረ የፖለቲላ መሪ?

ኦጋዴንም በተወሰደ በ1923 በ21 ዓመቱ በ1947 ዓ.ም አስመለሱት።

ጋምቤላም የተወሰደዉ በ1894 ዓ.ም ሲሆን በተወሰደ በ56 ዓመት በ1950 ዓ.ም ወደ ህዝቡ ተቀላቀለ።
በጠላት ተወስደዉ የነበሩት የተበታተኑ ህዝቦቿ ያስመለሱት ንጉሱ የጦርነቱ ቀስቃሽ እና የመለያየት ቆስቋሽ ተደርገዉ መታየት በእዉነቱ አዲሱ ትዉልድ የተሳሳተ ታሪክ ከማስተማር አልፈን “ኤርትራዊያኖቹ ከተጠያቂነት” ነጻ አድርጎ እንደ “ተበዳይ” አድርጎ የሚያቀርብ ሰዕል ይመስለኛል።ያ መቀጠል የለበትም።

እንዴ እኛም እኮ አግዚሃርን እኮ መፍራት ተገቢ መሰለኝ። እኛም እኮ ያስረከቡንን መጠበቅ ወይም ማስመለስ ቢያቅተንም ጦርነቱ በከፋ (160 ሺሕ ሕዝብ ለሞት ተዳርጓል) ከንጉሱ በሗላም ከነፃነታቸዉ በሗላም ዛሮም እኮ ቀጥሏል። ንጉሱ አንዴት ተኩኖ የድክመት ማምለጫ ሁሎም እንጠቀምባቸዉ? ሃጥያት እኮ መፍራት ተገቢ ነዉ።

ንጉሱ ያደረጉት የኮሎኒ/የቅኝ አገዛዝ/አያያዝ ሳይሆን ከኛዉ አስበልጠዉ እነሱን ተንከባክበዋል። ታሪኩ በትክክል ይጻፍ። ጣሊያን ከ4ኛ ክፍለ በታች እንዳይዘልቁ ሲያደርግ ንጉሱ ኤርትራዊያኖችን በገፍ ዉጭ አገር ሄደዉ በነጻ እንዲማሩ አድርገዉ አስካሁን ድረስ የሚኖሩበትን ተንደላቃቂ ኑሮ እና እዉቀት ለግሰዋቸዋል።የጥላቻ እና ፖለቲካ በር ከፋቾቹ አነሱ እንጂ ንጉሱ ሊሆኑ አይችሉም።ስለዚህ ተጠያቂነቱ ለሁሉም ቢዳረስ ድርሻ ድርሻዉን ቢያነሳ ጥሩ ነዉ፡የሚል አመለካከት አለኝ።
ለነገሩ 3ኛዉ መስመር የሚባለዉ የቱ ነዉ?ኢሕአፓ የተከተለዉ 3ኛ መስመር የተባለዉ በ1976 ዓ.ም ለኤርትራ መፍትሄ ብሎ ያወጣዉ የሚከተለዉስ ይጨምራል? እሱ ከሆነ እንዴት ከንጉሱ ይልቅ በ1976 ስለ ኤርትራ ጉዳይ መፍትሔ የተባለዉ የኢሕአፓ ፕሮግራም መፍትሄ እና ተመራጭ ሆኖ አቶ ክፍሉ አስካሁንም ቢሆን 3ኛዉ መስመር በተግባር አልዋለም ቢዉል ኖሮ ሰላም እና መፍትሄ ያመጣ ነበር ማለቱ ሊገባኝ አልቻለም።
ኢሕአፓ አወጣዉ ከተባለዉ ሰነድ ልጥቀስ።

መጋቢት 1976 የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ የፖለቲካ ፕሮግራም;(በጥራዙ ሽፋን ላይ የሚታየዉ እርእስ- )
በዉስጥ ገጾቹ ደግሞ እንዲህ ይላል ልጥቀስ፦

"የጭቁን ብሄሮች የራሳቸዉን ዕድል በራሳቸዉ የመወሰን መብት/አስከመገንጠልና የራሳቸዉ የሆነ ነፃ መንግስት አስከማቋቋም ድረስ/ መከበር እንዳለበት ማስተማርና መታገል እንዳለብን ሁሉ ጭቁን ብሔሮች በፈቃደኛነትና በእኩልነት ከጨቋኙ ብሔር ሠፊዉ ሕዝብ ጋር መዋሃድ እንዳለባቸዉም ማስተማርና መታገል አለብን…"
 
"….በዛሬይቱ ኢትዮጵያ ዉስጥ ለ23 ዓመት ሲካሄድ የቆየዉንና አሁንም እየቀጠለ ያለዉን የኤርትራ ህዝብ የነፃነት ትግል መደገፍ ትክክልና ተገቢ ነዉ።አሁንም ኢሕአፓ የኤርትራ ሕዝብ ሚያካሂደዉ የነፃነት ትግል ይደግፋል።..."

በዘሁ ፕሮግራሙ ኢሕአፓ ስለ ብሔሮች ምን ይላል? ገጽ 23-24 አንቀጽ አራት ቁጥር 1-4 እንዲህ ይላል;--
1- "ጭቁን ብሔሮች ሁሉ ያላቸዉን የራሳቸዉን ዕድል በራሳቸዉ የመወሰን/አስከ መገንጠል ድረስ/ ሙሉ መብት አዉቆ ወዲያዉም ፈቅዶ መዋሃድ በሚለዉ መርህ መሠረት የሚፈልጉትን ዓይነት የሕብረት/መንግሥት በእኩልነትና በወንድማማችነት እንዲያቋቁሙ የፖለቲካ ትግል ያካሂዳል…"
 
ብሎ እንደነበር የሚታወስ ነዉ። ከተሳሳትኩ ልታረም። እላይ የተጠቀሰዉ 3ኛ መስመር ከሚባለዉ አንዱ እንደማይሆን ደግሞ ተስፋ አለኝ።3ኛ መስመር የጀመረዉ ያኔ ከሆነ የሚያነጋግር ይመስለኛል። በሗላም በ1976 የቀረበዉ እላይ የተጠቀሰዉ አስከ መገንጠል ጉዳይ በዲሞክረሲያ በ1982 “አንዳንድ ማብራሪያ” ብሎ ባወጣዉ የማሻሻያ ሃሳብ አቅርቦ

 "… የኤርትራን ጥያቄ በመገንጠል ደረጃ ሳይሆን ከቀረዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል ጋር በተሳሰረና ከቀረዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕድል ጋር በዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ዉስጥ በተቆራኘ መንገድ መፍትሔ እንዲያገኝ ማድረግ፤ለዘለቄታ ሰላም፤ለዘለቄታ የሕዝብ ጥቅም ለጋራ ብልፅግና አስፈላጊና ገሃድ የሆነ ምርጫ ይሆናል…" በማለት በዲሞ/ቅፅ 15፡ ልዩ ዕትም ገፅ 14 አርሞታል።
የንጉሡን በኤርትራ የተከተለዉ ፖሊሲ የሚጻረር የኢሕአፓዉ 3ኛዉ መስመር እንደ መፍትሄ ሆኖ የቀረበዉ በ1976ዓ.ም ነዉ ወይስ በ1982ዓ.ም? ይሄ የማሻሻያ ፕሮግራምም እኮ ቢሆን ኤርትራኖቹ አይቀበሉትም።ለአንዴም ለሁልም ባሕራችሁን ነጥቀናል፤ ተዘግታችሁ ኑሩ። እያሉን ነዉ። ታዲያ 3ኛዉ መስመር እየተባለዉ ያለዉ በኤርትራዊያኖች በኩል ሰሚ ካጣ “መፍትሄዉ” ከጉልበት ሌላ ምን ሊሆን ይችልላል ብላችሁ ትገምታላችሁ? ይህ “ዲሞክራሲ” የሚባል ወይንም “የሕዝብ ድምፅ” የሚሉት በወረቀት የተኳኳለ በግብር የማይዉል ፤በዚህ ነባረዊ ዓለም የማይሰራ ምን ቢደረግ ይሻላልል ትላላችሁ? ገራገር ያገሬ የኢትዮጵያ ልጆች አስከ መቸ ድረስ ገራገሮች ሁናችሁ እየተበደላችሁ አገርን ያክል ወደብን ያክል ተዘግቶባችሁ ዲሞክራሲ የሚባል ጠንቋይ ፍትህ ይዞልን በወርቅ ሳህን ይመጣል እያላችሁ ልትኖሩ ነዉ? ወይ አገሬ ዳር ድምበርን እና ወደብን ሚስት እና አገር ዲሞክራሲ ይወሸማቸዉ ብለዉ ፍትሕ በዛ ብቻ ይገኛል ብለዉ የሚዋዥቁ አዲስ ትዉልዶች ካሉ ለመጠቆም ከንጉሡ አንደበት እንዲማሩ አንድ ነገር ልበላችሁ።

(”…ወይ ጉድ? የዚህ ዓለም ሁኔታ የሚያስገርም ነዉ። በግፍ ከተወሰደብን ከራሳችን መሬት ተቆርሶ ወደ በሕር መተላለፊያ በር አንዲሰጠን ስናመለክት መልሱ ወደፊት ይታሰብበታል ሆነ።በዚህ አኳሗን የተወሰደብን መላዉ ግዛታችን ይመለስልን ብለን ጠይቀን ቢሆን ምን ልንባል ኖሯል?...”)

ውስጣቸዉ የነደዱት ንጉሥ ተፈሪ መኮንን። (የኤርትራ ጉዳይ -ዘዉዴ ረታ)
ይህ ሁኔታ በጥልቀት ሲጠና ዛሬ የኤርትራ ነፃነት ያረጋገጠዉ “ዲሞክራሲ” የሚባል ጠንቋይ አንደነበር አስመስለዉ ዛሬም የሄንኑ Dimocracy የሚባል ጠንቋይ አገር እና ወደብ ያስመልሳል የሚሉን

“የዲሞክረሲ” ምሁራን፦ ንጉሱ ከገጠማቸዉ የተለየ ዓለም እየኖርን እንደልሆንን ፖለቲካዉ ለእምቦቆቁላዉ በስሜት ለሚጋልበዉ ላልበሰለዉ ወጣት እናስረክበዉ የሚሏችሁን አዛዉንቶች ለምን መምራት አልቻላችሁም ብላችሁ ብትጠየቋቸዉ ምንኛ ደግ ነበር? ዲሞክራሲ የሚባል ጠንቋይ ወይም 3ኛዉ መስመር የሚባለዉ መመሪያ ሽማግሌዎቹ ካወቁበት በስሜት በቅሎ የሚጋልበዉ የዘመኑ ወጣት መሪ ሆነዉ እየገሩ ካላሳዩት በምን ልምዱ ይጋልበዉ? እያየነዉ! ለመሆኑ አንደዛሬዉ ዓይነቱ “ሊጥ” “ቡሆ” የሆነ ወጣት ታይቶስ ተሰምቶስ ይታወቃል?

በጣም የሚገርመኝ ነገር፦ በንጉሱ ምክንየት ኤርትራኖች እኛ ያላገኘነዉን ክብር እና ዲሞክራሲ አገኙ አንጂ እንደተበደሉ ተመስሎ ፤”ተገፉ፡ አስራቅናቸዉ፤እንዲርቁን በር ከፈትንላቸዉ….” እየተባለ የሚነገረዉ ስህተተኛ ፕሮፖጋንዳ/ቅስቀሳ በቀና ኢትዮጵያዊያን መደገም መቆም አለበት እያልኩ “የኤርትራ ጉዳይ” ታሪክ ፀሃፊዉ ክቡር አቶ ዘዉዴ ረታ ከተናገሩት ልጥቃስ እና በታለቁ ዲፕሎማት በአክሊሉ ሀብተወልድ ምሬት ትምርታዊ ንግግሮች ልሰናበታችሁ።
"ኤርትራዊያን ወንድሞቻቸችን ለሃምሳ ዓመታት የጣሊያን ቅኝ ሆነዉ ከተሰቃዩ በሗላ፤ ለዓሥር ዓመታት በእንግሊዝ ወታደራዊ አስተዳደር በተያዙበት ዘመን ኢትዮጵያዊነታቸዉን ለማረጋገጥ “ኢትዮጵያ ወይም ሞት” ብለዉ ያን ሁሉ መከራና ፈተና ለምን ሲሉ እንደተቀበሉ፤ በመጨረሻም እናታችን ነሽ ብለዉ ከኢትዮጵያ ጋር ከተዋሃዱ በሗላ፤ምን ቢጎድልባቸዉ መገንጠልን እንደመረጡ ፤ምን ቢበደሉ እናት ኢትዮጵያን እንደጠሉ ታሪክ የሚያቀርብላቸዉን ጥያቄ በወጉ መመለስ ያለባቸዉ እነሱ ናቸዉ። {ዘዉዴ ረታ-የኤርትራ ጉዳይ ገፅ 10}

"…ሀገሬ ኢትዮጵያ በዓለም ሸንጎ ላይ ፍርድ ተነፍጓት ስታዝን የመጀመሪያ ጊዜ አይደለም።…..ኢትዮጵያ ያለፉት ታሪኮቿ በትክክል እንዳስረዱት፤ለነፃነቷና ለመንቷ፤በኮሎኒያሊስቶች ጣሊን ጋር በየጊዜዉ ስተዋጋ፤ያሸነፈችዉ ብቻዋን ነዉ። የተጠቃቺዉም ብቻዋን ስለሆነ፤አገሬ መቸዉንም ለሚደርስባት አደጋ ከማንም እርዳታ አገኛለሁ ብላ አትጠብቅም።ዛሬም ሆነ ነፃነቷን ለመጠበቅ፤ታሪኳን ለማስከበር አስፈላጊዉን ዝግጅት ማድረግ ያለባት፤እሷ ራሷ ብቻ ነች።…" {አክሊሉ ሀበተወልድሕዳር 21 ቀን 1949 ዓ.ም}

Friday, September 12, 2008

The record that speaks of Priests and Deacons abused in Tigray by the TPLF leaders






The Record That Speaks of Priests and Deacons Abused In Tigray by the TPLF Leaders
የትግራይ ድያቆናትንና የቀሳዉስት ዕምባ (ለማስታወሻዎ) የህወሐት ታጋዮች በሰባት ጥይት ድብድበዉ ጫካ ወስደዉ ጣሉኝ”
(ምንጭ፦ ኢትኦጵ መጽሄት- ቅጽ 2 ቁጥር 016 መስከረም 1993 ዓ.ም) ( ጌታቸዉ ረዳ) ( ሳን ሆዘ ካሊፎርኒያ )
ይህ ታሪክ ኣማርኛ ለማያነቡ የትግርኛ ተናጋሪዎች ተርጉሜ መሳ ለመሳ ሰሞኑን በዚህ የህዋ ሰሌዳ ቀርቧል። ሃቅን አድበስብሶ ለጊዜዉ በመሸፋፈን ዜጎችን ያስለቀሱ ወንጀለኞችን ባንዳንድ አድረባዮችና ጅላጅል ተቃዋሚዎች ሽፋን ሰጪነት፤የህወሐት አመራር ወንጀለኞች የህዝብ ኣሳቢዎች እንደነበሩና ዛሬም ነጻ ያወጡናል ብለዉ በየራድዮናቸዉና በህዋ-ሰሌዳቸዉ አጉል ቅስቀሳ ሲያደርጉላቸዉ ብንታዘብም ፡ እዉነት ተሸፋፍኖ አይቀርምና፤ ሰሚ አጥተዉ ፤ የሚጮህላቸዉ ዜጋ ፍለጋ ለዓመታት የደም ዕምባ ላፈሰሱት የወያኔ አመራር ሰለባዎች ደግሞ በኛ በኩል በዚህ ዓምድ ዕምባቸዉና እሮሮአቸዉ ለሕዝብ እናስተጋባለን። ፈራጁ ታሪክ እና በዓይን የሚታይ ጥቃት እንጂ “ዘመን የለገሳቸዉ ግራ ተጋብተዉ የዋሁን ማህበረ ሰብ ግራ የሚያጋቡ አፈጮሌ ባለ ራዲዮኖችና የህዋ -ሰሌዳ ባለቤቶች ” አይደሉም።
ስለዚህም የሕዝባችን ጥቃት ከማስተጋባት ወደ ሗላ ያላልንበትን ቃል ኪዳናችንን መሬት ተንተርሰን የመጨረሻዋ እስትንፋሻችንን እየተነፈስንም ቢሆን ትግላችን ይቀጥላል። አገር እና ሕዝብ ያስለቀሱ የባሕር በራችንን ያስሳጡንን <በረሃ እያለን ለፈጸምነዉ ወንጀል አንጠየቅበትም> ብሎ በስልጣን ማን ያህለኝነት የፏለለዉ ገብሩ አስራትን እንደ እስራኤሉ ሙሴ ነጻ አዉጪያቸዉ አድርገዉ በመቁጠር እሱን ለማስተዋወቅ የሚጥሩት የዋሽንግተን የሚድያ ኮበሌዎችና መሰሎቻቸዉ ፤በስመ ዲሞክራሲ ወንጀለኞችን የሚኳኩሉበትን ዕብደታቸዉና <”ይቻላል” እያሉ በራቸዉን ክፍት አድርገዉ ከሄያጁም ከመጪዉም በመተሸሸት የፖለቲካ ዉርዴ የሚሸምቱ “የፖለተካ -መበለቶችን” እግዚሃር እንዲምራቸዉ እየተማለልን “ታሪክ እኛኑን ወይንም እነሱን ከሁለት አንዳችን ይጥለናል>።የድሮ የወያኔዉ ትግራይ መንግሥት አስተዳዳሪ እና አዲሱ የወያኔዉ ድርጅት የዓረናዉ መሪ “ገብሩ አስራት እና የሱ አመራር አባል አረጋሽ አዳነ” ስልጣን ላይ እያሉ “ተበደልን ፍትሕ እንፈለጋለን” ብለዉ ለጠየቁ የትግራይ ህብረተስብ አባላት መልሳቸዉ ምን እንደነበር ከሚቀጥለዉ የወያኔዎች የገመና ማህደር እንመልከት። የኢትዮጵያ ሰማይ ለአዲሱ ዓመት እንኳን አደረሳችሁ የሚለዉ በዳመናዉ ዉስጥ እየተንሳፈፈ የፍትሕ ያለህ በማለት እየጮኸ ያለዉ ‘ወያኔ” የደም ዕምባ ያስለቀሳቸዉን የዜጎችን እሮሮረን በማሰማት ነዉ። ጌታቸዉ ረዳ።
አሁን ወደ ታሪኩ ልዉሰዳችሁ፡ << እንግዳችን ብርሃኔ ገ/ሕይወት ይባላል። ወደ ሕዝባዊ ወያነ ሐርነት ትግራይ (ህወሓት) ትግል ዉስጥ እንዲቀላቀል የቀረበለትን ጥሪ ባለመቀበሉና በመቃወሙ፤ በተደጋጋሚ መታሰሩንና በመጨረሻም በአሰቃቂ ሁኔታ በሰባት ጥይት መደብደቡን ይነግረናል። ይህ ወጣት ቤተክርስትያን በማገልገሉም ሳቢያ፤ከፍተኛ ተፅእኖ ተደርጎበት የድቁና መታወቂያዉንም የሕወሐት ታጋዮች ቀድደዉታል። የደረሰበት ጉዳት ከፍተኛ በመሆኑ በሐገር ዉስጥ ህክምና የማይድን መሆኑንም የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሰኔ 20 ቀን 1986 አረጋግጧል። ይህንንም ማረጋገጫ የሰጡት ከፍተኛ ህክምና አንደሚያስፈልገዉ ያረጋገጡት ደ/ር ተመስገን ፍጡር (ቀዳጅ ሐኪም)፤ ዶ/ር ዘሩ ገ/ማርያም (ሜዲካል ዳይሬክተር) ፕሮፌሰር W.Mcquillan (የቀዶ ሕክምና አማካሪ) ናቸዉ።
ይህ የ35 ዓመት ወጣት ከዚህ በሗላ ከደረሰበት ጉዳት ለመዳን ዕርዳታ ያደርጉለት ዘንድ የግብረ-ሰናይ ድርጅቶችን አነጋግሯል። “ዳዉተር ኦፍ ቻሪቲ” ከተሰኘ ግበረ-ሰናይ ድርጅት ጥሩ ምላሽ በማግኘት ከዉጭ ሃገር ገንዘብ ቢሰበሰብለትም ገንዘቡ በድርጅት ሓላፊዎች መበላቱንና በሗላም እሱ ሜዳ ላይ መጣሉን ይናገራል። ወጣቱ በዚህ ጉዳይ ኬንያ ድረስ ሄዷል፤ ወደ ትግራይ ብቅ ብሎም የትግራይ ክልል ዋና ፀሐፊ ወ/ሮ አረጋሽ አዳነን አነጋግሯል። እዚያም አንደር-ግራዉንድ (ከመሬት በታች) ዉስጥ እንዲገባ በማድረግ ለረዢም ሰዓት በጥያቄ እንዳፋጠጡት ይናገራል ።ይህ ወጣት ሰዉነቱ ላይ ያለዉ ቁስል እያመረቀዘ እንዳስቸገረዉ ለማየት ችለናል።…ይህን ቁስሉን ለማዳንና ከበሽታዉ ለመፈወስ 6 ሚሊዮን 200 ሺህ የኬኒያ ሽልንግ (103 ሺህ ዶላር) እንደሚያስፈልግም ደ/ር ጆን.ኢ.ኤ የተባሉ በኬኒያ የሚገኙ ሃኪም ያረጋገጡበትንና እ/ኤ/አ ዲሴምበር 21/98 የተፃፈ ወረቀትም ይዟል። ሁሉንም ከእርሱ እንከታተል።>> ኢትኦጵ -ቅፅ 2 ቁጥር 016 መስከረም 1993 ዓ.ም }/- ስምህ ማን ይባላል? ብርሃነ፦ ብርሃነ ገ/ሕይወት። ትዉልድና ዕድገትህ ብርሃነ፦ ትዉልዴ አድዋ አዉራጃ ሲሆን፤ቀበሌዉ ጣቢያ ኮረም መንደሩ እንዳ መትከል ስብሃቱ ይባላል። አድዋ አዉራጃ እያለህ የደረሰብህ በደል ምነድ ነዉ?-
ብርሃነ፦ ቤተክህነት ተማሪ እያለሁ በ1975 ዓ.ም ከአክሱም ጽዮን ድቁና ተቀብ ስሄድ በወድቅት ሌሊት የማላዉቃቸዉ ሰዎች ኢሳ ወደ ሚባል ወረዳ አስረዉ ወሰዱኝ። በአሁኑ ወቅት ያለዉ ጳጳስ ከደርግ ጋር ሰዉ እንዲገደል ያወጀ ስለሆነ ቅስናንም ሆነ ድቁናን ሊባርክ አይችልም።” የሚል ምክንያትም ስጡኝ። ጳጳሱ ማን ነበሩ? ብረሃነ፦ ስማቸዉን ዘንግቼዋለሁ በዚያ ሰዓት ስማቸዉ መታወቂያየ ላይ ነበረ። የትግራይ ተወላጅ ናቹዉ? ብርሀነ፡- እኔ እንጃ…አማርኛ ነበር የሚናገሩት።
በተያዝክበት ወቅት ማለትም በ1975 ዓ.ም አካባቢዉን የሚያስተዳድረዉ ደርግ አልነበረም እንዴ? ብረሃነ፦ ከተማዉ ደርግ ነዉ፡በገጠር ወረዳዎችን የሚያስተዳድሩት ወያኔዎች ነበሩ። ከገጠር ነበር ያያዙህ? ብርሃነ፦ አዎ! ከገጠር ነዉ የያዙኝ። እኔ ስለ እናንተ ዓላማ አላዉቅም፡ ከዚህ በፊትም አላዉቃችሁም። እኚህ ጳጳስ ደግሞ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ መሪ መሆናቸዉን ብቻ ነዉ የማዉቀዉ እንጂ፤ ጦርነት ያዉጁ አያዉጁ እኔ የማዉቀዉ ነገር የለኝም ፡ስላቸዉ በቅጣት 10 ቀን አስረዉ መታወቂያየን ቀዳደዱት። በሗላም ደርግ ካለበት አካባቢ እንዳልደርስ አስጠንቅቀዉ በዋስ ለቀቁኝ። ሌሎችም ቅስና እና ድቁና የተቀበሉ ከ50 በላይ የሆኑ ሰዎች ታስረዉ ነበር። እነሱም ከእስራትና ከቅጣት በሗላ መታወቂያቸዉ ተቀምተዋል።
የተቀሙት የድቁና መታወቂያቸዉን ነዉ? ብርሃነ፦ የድቁና እና የቅስና መታወቂያቸዉ ነበር የተቀሙት።ከዚያ እዚያዉ ቆይተን በ1981 ዓ/ም በግድ ወደ ግንባር ዝመቱ አሉን። በ1975 ዓ.ም እንደተያዛችሁ እንድትዘምቱ አልጠየቅዋችሁም? ብርሃነ፦ ይጠይቁን ነበር፤ ነገር ግን ግዴታ አልነበረብንም። በዘፈን ይቀስቅሱን ነበር። በስብሰባ ያስቸግሩናል። ይቆጡናል እንጂ የጠነከረ ግዴታ አልነበረም። በ1981 ዓ.ም ግን ዉጥረቱ ሲበረታባቸዉ ነዉ መሰል ግዴታ ታገሉ አሉን። እኛ “አንታገልም፤እናንተ ታገሉ፡ እኛ ድሆች ነን፡ ገና ዳቦ አንኳን አልጠገብንም” ስንላቸዉ፡”ማን አጥንቱን ከስክሶ ሊያኖርህ ፈለግክ?” በማለት በተለይም “ቢሄን” የተባለ ታጋይ አፈር በእጁ ከመሬት ቆንጥሮ በማፈስ ወዳፍንጫችን አስጠግቶ እንድናሸት አስፈራራን። በአገራችን መኖር ካልቻልን ተሰድደን እንሄዳለን፡ ይለፍ ብቻ ስጡን ስንል ስትፈልጉ በሰማይ ሂዱ እንጂ አይሰጣችሁም፡ እያሉ ያፌዙብን ነበር።
“ታዲያ የት እንድረስ?” ስንላቸዉ “የራሳችሁ ጉዳይ!ከፈለጋችሁ አገራችሁን ነፃ አዉጡ። ነፃ አናወጣም የምትሉ ከሆነ ግን የዚህችን ምድር በረት አትረግጡም። አሉን። “ከማን ነዉ ነፃ የምናወጣት?” ደርግም ኢትዮጵያዊ ነዉ እናንተም ኢትዮጵያዊያን ናችሁ።” ስንል <ከበስተጀርባችሁ የሆነ ነገር አላችሁ!> በማለት ማሰር እና መቅጣት ጀመሩን።
ስንት ትሆናላችሁ? ብርሃነ;- 1500 እንሆናለን። ከዚያ ምን ተከተለ? ብርሃነ;- ፦ወላጆቻችን ታሰሩ። የእርሻ ማስታዎሻችንም ተወረሰ። ቀንደኛ ዓድመኞች ናችሁ በተባልን በተወሰንን ሰዎች ላይ ከባድ ቅጣት ተፈጸመብን። ከ6 ወር አስከ ዓመት በእስራትና በግርፋት ተቀጥተናል። ክንዶቹ ለረዥም ጊዜ በቀጭን ጅማት ነገር በመታሰራቸዉ ምክንያት ጣቶቹ ደም አስከ ማንጠባጠብ የደረሰ ጓደኛችንም ነበረ። በጅማት ታስሮ እጁ ደም ያንጠባጠበዉን ጓደኛህን ስም ታስታዉሰዋለህ? ብረሃነ፦ የአንዱ ስም አላስታዉሰዉም። ሰለዳም የሚባል ቀበሌ ነዋሪ ነዉ። ሌላዉ በግርፋት አንድ እጁ እና አንድ እግሩ ሽባ የሆነ ጓደኛየ ሃለቃ ሓዲሽ የባላል። ቢዚያን ወቅት <ሙሹሮችና ካህናት> ሳይቀሩ <በህማማት ጊዜ ከቤተክርስትያን> ተወስደዉ ከሽማግሌዎች በቀር ሁሉም ታፈሶ ተወሰደ። ለመሸሽ የሞከረዉን እንደጅግራ እያሯሯጡ በጥይት ያሳድዱት ነበር።
ይህ ሁሉ የተፈጸመዉ መቸ ነዉ? ብርሃነ፦ የካቲት ወር 1981 ዓ.ም ጀምሮ ማለት ነዉ። ትግራይ ነጻ ከወጣች በሗላ ማለት ነዉ? ብረሃነ፦ አዎ:: ከዚያ… ሰዉ እንደ አዉሬ በአካባቢዉ እየተበተነ በአካባቢዉ በቀን ሰዉ የሚባል አይታይም ነበር። እነሱም እንደ ጅግራ እያደኑ ይዉላሉ፤መሬታችንም ለታጋይ ቤተስብ ታድሎ የምንቀምሰዉ የምንልሰዉ አልነበረም።ከቀበሌ ወደ ቀበሌ የሚያስተላልፉ የነሱ ካድሬዎች ካዩን ጥይት ይተኩሱብናል፤ የተኮሱብን ጥይት አልመታንም እንጂ ቁጥር የለዉም።ከዚያ በሗላ እየተንከራተትንና እየተራብን ቆይተን ህዳር 21/1983 ዓ.ም ገረዳ ተብሎ በሚጠራ ቀበሌ ገበሬ ማሕበር ለአቶ በርሄ እህል ስንሸከምላቸዉ ዉለን፤ቤት ገብተን ገበታዉ ቀርቦ እህል ልንበላ ስንል ቤቱ ተከበበ። የማይታወቁ ታጣቂዎች ናቸዉ። ከተሰበሰበዉ ሰዉ እኔን ጠሩኝና ዉጣ አሉኝ። መጀመሪያ እህል ይብላ እና ዉሰዱት ብለዉ የቤቱ ባለቤት ቢጠይቁም <<አስቸኳይ መልዕክት ስላለን ነዉ፤አሁን ይመለሳል>> ብለዉ ወሰዱኝ።ሌሎችም ከያቅጣቻዉ ተሰበሰቡ።ወደ 5 እንሆናለን። ሁላችንም በስብሰባ ላይ የምንከራከራቸዉ ነበርን። <<እነዚህ ካልጠፉ ወጣቱ አይታገልም፤በታኞች ናቸዉ፤ከደርግ ለይተን አናያቸዉም>> በማለት ከዚያ በፊት እንዳጠፏቸዉ ወጣቶች እኛንም ለማጥፋት ተዘጋችተዉ እየወሰዱን ሳለ፤ እርስ በርሳችን እንነጋገር ነበር። ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ይሆናል።
የት ነበር የሚወስዷችሁ? ብርሃነ፦ ጫካ ነዉ፤ እኛ አናዉቀዉም። ኢሳ የሚባል በረሃ ነዉ። ምን ይሻላል? ለመሞት ለመሞት እዚሁ እንሙት እየተባባልን እንደገና ጉዞ ጀመርን። አልፎ አልፎ ነዉ እንጂ እኛን ባንድ ላይ አይወስዱንም ነበር። አንድ እዚህ፤ አንድ ደግሞ ራቅ አድርገዉ ሊወስዱን ከፊት ያለዉን ገፍቼ ሸሸሁ። ቁጥር የሌለዉ ጥይት እላየ ላይ ዘነበ። ፀጉሬ ላይ ትንሽ ነካኝ እንጂ አልመታኝም። አምልጬ ሕግ ያለ መስሎኝ ወደ ዋናዉ አለቃ ሄጀ <የማይታወቁ ታጣቂዎች ሌሊት መጥተዉ በደል አደረሱብኝ፤ በነዚህ ሰዎች ላይ ክትትል ይደረግልኝ፤ከየት እንደመጡ ማን እንደላካቸዉ ይጣራልኝ> ብየ አቤቱታ ሳቀርብ፡ <<እኛ እናጣራዋለን፤ እንከታተላቸዋለን>> ሚል መልስ ሰጡኝ። በዚህ ሁኔታ ላይ ሳለሁ ጥር 23 ቀን 1981 ዓ.ም ሥራ አድሬ ከንጋቱ 12 ሰዓት አካባቢ ወደቤቴ ስሄድ……..
ምንድነዉ ስራህ? ብርሃነ፦ የቤት ስራ፤ቤት በደቦ ስንሰራ ደክሞኝ እዚያ አድሬ ነበር። አባቴ ሞቷል..እናቴ አለች፤ የእናቴ ትንሽ መሬት ነበረችን፡ ቤቴ እንደደረስኩ በረቱን ከፍቼ ለበሬዎቹ ድርቆሽ ልሰጣቸዉ ስል….የ.ማላዉቃቸዉ ሰወች ብትንትን ብለዉ ተኝተዉ አገኘሗቸዉ። ቤቱ ተከቦ ነዉ ያደረዉ። እናንተ እነማን ናችሁ? ስላቸዉ አንዱ እያናገረኝ ሌላኛዉ በሰባት ጥይት መታኝ። በሆዴ እና በአንጀቴ ላይ ደሙ እየተንዠቀዠቀ ሲፈስ እናቴ እንዳታይና እንዳትጮህ ውስጥ ግቢ አሏት። ከዚያ በሗላ <እግሬና እጄን አንጠልጥለዉ ጎትተዉ ጫካ ዉስጥ ጣሉኝ>። አንጀቴ ተበጥሷል። እንጀቴ ይታያል፡ቅጠላቅጠል አልብሰዉኝ ተሰወሩ።ይህ ሁሉ ሲሆን ከሩቅ ይከታተሉ የነበሩ የአካባቢዉ ሰዎች እነማን እነደሆኑ አይተዋል።
ስንት ነበሩ? ብርሃነ፦ ወደ 10 ይሆናሉ። ሕዝቡ ተከትሏቸዉ፤ << እነማን ናችሁ? ቁሙ! ነፍስ አጥፍታችሁ አትሄዱም>> ሲላቸዉ “እየሳቁ” ሄዱ ። በመጨረሻ ከወደቅኩበት አንስተዉ በሰልፍ ተሸክመዉኝ ዓድዋ አዉራጃ አሰተዳደር ወሰዱኝ።<<የዛሬ ብርሃነ ዕድል ነገ ለኛ ነዉ። ይሄ ልጅ ምን አጠፍቶ ነዉ በወጣትነቱ የተቀጠፈዉ?>> ብሎ ህዝቡ አቤቱታ አቀረበ። በዚህ ወቅት ሕዝቡ መቷል ብሎ ስላመነ ጉድጓዴ ሳይቀር ተቆፍሮ ነበር። ጫካ ወስደዉ እንደጣሉኝ የተነገረኝም በሗላ ነዉ። ሕዝቡ አሰከረኔን ተሸክሞ <<ደርግን ግፈኛ ትላላችሁ እንጂ ይሄዉና የናንተም ግፍ!>> ሲሏቸዉ 15 ወጣቶች በሲሚንቶ የተሰራ የጣሊያን ጉድጓድ ዉስጥ አስገብተዉ አሰሯቸዉ። በአጠቃላይ ሕዝቡ 500 (አምስት መቶ) ይሆን ነበር። ወጣቶቹን ካሰሩ በሗላ ህዝቡን በዱላ በታተኑት። እኔንም የሚያዉቁኝ ሰዎች ወደ አክሱም አመጡኝ በአጋጣሚ ነጮች ነበሩ ኦፕራሲዮን አደረጉልኝ።
የት ነዉ ኦፕራሲዮን ያደረጉልህ? ብርሃነ፦ አክሱም ሆስፒታል። ሁለት ሰዎች ደም ሰጡኝ። ደም ጨርሼ ነበር። ይሄን ሲነግሩኝ እንጂ እኔ አላዉቅም። ለ3 ወር ያህል ሕይወቴን አላዉቅም ነበር። የተኛሁበት የጀርባየ ጠባሳ አሁንም አለ። ሕይወቴ መቆጣጠር ስላልቻልኩ መቀሌ ታከምኩ። እዚያም ስላልቻሉ አዲስ አበባ ጥቁር አምበሳ መጣሁ። ጥቁር አምበሳ የመጣኸዉ መቸ ነዉ? ብርሃ፦ በ1984 ዓ.ም ሚያዚያ 4 ቀን አዲስ አበባ መጣሁኝ። ጥቁር አምበሳ ሆስፒታልም አስከ መጨረሻ ጥረት አደረጉልኝ። ሕይወቴን ለማዳን በህክምና ብቻ ሳይሆን በተለያየ መልኩ ሲረዱኝ ቆይቶ መጨረሻ ሲያቅተዉ በ1986 ሰኔ 16 ዉጪ ድረስ ሄጄ እንድታከም ወስኖ አሰናበተኝ። ከዚያ በሗላ አማራጭ አጣሁኝ። ቀኑ ጨለመብኝ።
ከጥቁር አምበሳ ስትወጣ ወዴት ሄድክ? አዲስ አበባ ቤተሰብ አለህ? ብረሃነ፦ የለኝም። ታዲያ የት አረፍክ? ብርሃነ፦ እዚሁ ሆስፒታል ኮሪደር ላይ ነበር የምተኛዉ ። ከተሰናበትክ በሗላ? ብርሃነ፦ አዎ። ከዚያ ወደ ትግራይ ሄድኩ ። የማላዉቃቸዉ ሰዎች አዋጥተዉ ቲኬት ቆረጡልኝ ። ትግራይ ከሄድኩ በሗላ ከብዙ ደጅ ጥናት በሗላ የክልሉ መንግሥት ጸሃፊት ወ/ሮ አረጋሽ አዳነን አነጋገርኳት። <ምን ሆንክ> አለችኝ። <በጥይት ተመትቼ> <ማን መታህ?> <የህወሃት አባላት><እንዴ! ምን ብለዉ ይመትሗል? ክሰሳቸዉ።>
<ምን ብየ እከሳቸዋለሁ? ታዉቁት የለም እንዴ ራሳችሁ። እንደ ብርሃነ አንዳትሆኑ እያላችሁ መድረክ ላይ ስበሰባ ላይ ትናገሩ አልነበረም አንዴ? ከ500 ህዝብ በላይ አቤቱታ ለማቅረብ ሲቀርብ በዱላ አላባበረራችሁትም? ወንጀለኛ ከሆንኩኝ ግደሉኝ፤ካልሆንኩ ግን አሳክሙኝ። አናዉቅም የምትሉኝ ከሆነ ደግሞ ስንብት ወረቀት ስጡኝና የትም ሃገር አቤት ልበል>> ስላት፡<የለም ምንግሥት አይመታህም> አለችኝ።<መንግሥቱ ሃይለማርያም አሰቃይቶ የገደለዉ ሰዉ የለም። የእርሱ ወታደሮች ግን ሰዉ ገድለዋል።የህወሐት ወታደሮችም እንደቅጠል ነዉ የቀጠፉን፤የገረፉን።ዕድሜ ልካችንን ሲያሰቃዩን ነዉ የከረሙት። ስለዚህ ለዉጥ የለዉም።ፍረድ ቤት በደርግ ጊዜ ነበረ አሁንም አለ። ያለዉ ፍርድ ቤት ነዉ እንጂ ማሕበራ ፍርድ ቤት አይደለም።የመሰላችሁ ፍትህ ስጡኝ> ስላት፡ <ግብረሰናይ ድርጅቶች ጠይቅ አለችኝ።> <ከ300 በላይ ግብረሰናይ ድርጅቶችን አነጋግሬ “መንግሥት ማንንም ሰዉ በግለሰብ ደረጃ እንዳትረዱ የሚል ማስጠንቀቅያ ሰጥቶናል” ብሉኛል፡ አኔ ከ60 ሚልዮን ሕዝብ በላይ ስለማልበልጥ ብጠይቃቸዉም መልስ አጥቻለሁ።> ስላት <ይህንን ነገር እንዴት ልታወቅ ቻልክ?> <ይሄማ ግልጽ የሆነ እኮ ነዉ>ስላት <ይሄማ የፓለቲካ አዝማሚያ ነዉ> ብላ ወዲ ሻምበል የሚባለዉን የፖሊስ አዛዥ ጠራች ።አሱም መጣ።ሌሎችም ተከተሉ።ድምፅ እንኳ ወደማይሰማበት “አንደር-ግራዉንድ” አስገቡኝ።
አንደርግራዉንዱ አዚያዉ ምክር ቤት ዉስጥ አካባቢ ነዉ ያለዉ? ብርሃነ፦ አዎ። ከ8፡00-1130 ድረስ ጎሮሮየ ደርቆ መናገር አስኪያቅተኝ ድረሰ በጥያቄ አፋጠጡቡኝ። የሚጠይቁህ ምን ነበረ? ብርሃነ፦
የደረሰብህ ነገር ተንትነህ በሙሉ ንገረን፤ያየሀዉ ነገር ሁሉ ተናገር፤ሙሉ መብት ሰጥተንሃል አሉኝ። እኔ በመጀመሪያ የቤተክህነት ተማሪ ነበርኩ።ወላጆቼ ቤተክርስትያንን እንድታገለግል ለቤተክርስትያን ሰጥተንሃል አሉኝ። እኔ በመጀመሪያ ደረጃ የቤተ ክህነት ተማሪ ነበርኩ።ድቁናየ ስቀበል ደግሞ ታጋይ ሐጎስ የሚባል የወረዳ አስተዳዳር “የድቁና የምስክር ወረቀቴን ቀደደዉ”።ቀጥለዉ ታገል ተባልኩ። እኔ አልታገልም ሰርቼ ነዉ የምበላዉ ስላቸዉ፡ “የለም መታገል አለብህ ” አሉኝ። መጨረሻ ወጣቱን በታኝ ነህ! አሳዳሚ ነህ!> አሉኝ።የበተንኩት ሰዉ የለም።ብርሃነ እንዳትታገል ብሎኛል የሚል ሰዉ ካለ አምጡት አልኳቸዉ።
መጨረሻም ወጣቱን ማፈን ጀመሩ። መፈን መባረር ሲጀምሩ እኛም የምንገባበት ቦታ አጣን።ተረበሽን፤ የት እንሂድ? ገሚሶቹ ወጣቶች ወላጆቼ በእኔ ሰበብ ከሚሰቃዩ አኔ ልሙት እያለ ወደ ትግል ግምበር ሄዶ ሞቷል።እላዩ ላይ ሳር በቅሎበታል።የተቀረንም ሰዉነታችን በጥይት ተበሳስቷል።እሳት ጨብጦ፤ፈንጅ ረግጦ ለስልጣን ያደረሳችሁ ወጣት በየፌርማታዉ ወድቋል፡ግማሶቻችንም ጠፍተናል።
ለምሳሌ ያህል ይግዛዉ ጣሰዉ - ከማይጓጓ ፍቱሕ ገ/ሕይወት - ከማይዳዕሮ አለቃ ሐጎስ- ከማይደዕሮ ገ/እግዚአብሔር= ከደዕሮ ሸዊቶ ዓለምሰገድ ይግዛዉ -ከዳዕሮሸዊቶ አረፋይኔ ከገረዓ፤ አበበ ገብረአብ - ከገረዓ ሲጠቀሱ ከነዚሁ አንዱ አኔ ነኝ
እነዚህ የተገደሉ ናቸዉ? ብርሃነ፦ ታፈነዉ ተወስደዉ የጠፉ፤አድራሻቸዉ የጠፋ ናቸዉ። አሁንም የት አንዳሉ አይታወቅም? ብርሃነ፦
የሉም! በቃ!....ለአብነት ያህል ከነዚህ ሰዎች አንዱ እኔ ነኝ። ጊዜ ከሰጣችሁኝ በመቶ ሚቆጠሩ ሰዎች አዉቃለሁ አልኳቸዉ። በመጨረሻ <መሬት ተወስዶብኛል ብለሃል ማን ነዉ የወሰደዉ?> አሉኝ። አኔ እዚህ ሆኜ መሬቴ ተወስዷል፡መሬት የለኝም።የሚል መለስ ሰጠሗቸዉ። <በምን ትደዳራለህ> አሉኝ፤ <ለምኜ ዕድሜ ለሕዝቤ> የሚል መልስ ሰጠሗቸዉ። <በል አሁን የምትፈልገዉ ምንድነዉ? ደረሰብኝ የምትለዉ በደልስ ምንድነዉ?> አሉኝ <<እኛ የትግራይ ተወላጆች በሦስት ፓርቲ ብዙ ችግር ደርሶብናል።ከኢትዮጵያ ሕዝብ በተለየ ሁኔታ የትግራይ ህዝብ በደረግ በሻዕቢያ በህወሐት ተበድሏል። እንደዚህ ሆኖ እያለ የደርግ ባለስልጣኖች ለፈጸሙት ግፍ በፍረድ ቤት ሲጠየቁ እኛስ ለምን መፍትሔ ለምን አይሰጡንም?ለምሳሌ ለደርግ ባለስልጣናት በጀት መድባችሁ ጠበቃ አቁማችሁ ፍ/ቤት እንዲቀርቡ አድርጋችሗል።በህወሐት እና ፡በሻዕቢያ በኩል በደል የደረሰብን ሰዎችስ ምን እንሁን?እኛም እኮ ሰዎች ነን።ቅጠል አይደለንም።መፍትሔ ለምን አይሰጠንም?>>
ብየ መልስ ሰጠሗቸዉ።አንዲያዉም የትግራይ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገብሩ አስራት <<በትግላችን ወቅት ያጋጠሙን አንዳንድ ችግሮች በአሁኑ ሰዓት ሊያስጠይቁን አይችሉም።>> የሚል መለስ በመድረክ ላይ ተናገረ።
በስብሰባ ላይ ነዉ? ብርሃነ፦ በስብሰባ ላይ የተናገረዉና በቴሌቪዥን የቀረበ ነዉ ፤መልስ የሰጠዉ። እኔ የተናገርኩት እና ሌሎችም ቤተሰቦቻችን አምጡልን፡ሞተዉም አንደሆነ ንገሩን ብለዉ አቤቱታ በማቅረባቸዉ ነዉ። ከእነ ወዲ ሻምበል ጋር በእንዴት ተለያያችሁ?
ብረሃነ፦ መጨረሻ ላይ አሁን የት ነዉ ምትኖረዉ አሉኝ? እኔም አቅጣጫ ቀይሬ አዚህ ቦታ ነዉ የምኖረዉ አልኳቸዉ። ተከትለዉ ሊይዙኝ ነዉ የፈለጉት። እዚያዉ ትግራይ ዉስጥ ነዉ ያልከዉ? ብረሃነ፦ አዎ።መቀሌ ዉስጥ የሀሰት አድራሻ ነግርያቸዉ፤ ከከተማ ወጥቼ ቲኬት አስቆርጨ አ/አበባ መጣሁ። አ/አበባ እንደመጣሁ ድርጅቶች ዉጭ ልከዉ አንዲያሳክሙኝ ጠየቅኩ።
የዉጭ ድርጅቶችን ነዉ? ብረሃነ፤_ አዎ “ዳዉተር ኦፍ ቻሪቲ” ወደ ሚባለዉ ድርጅት ሄጀ “ሲሰተር ካትሲል ካሲን” የምትባል አነጋግሬያት አልቀበልም ብላኝ ነበር።ዶክሜነቴን ካየች በሗላ ግን ተቀብላ ፈቃደኛ ከሆንክ ዉጭ ገንዘብ አሰባስቤ ለንደን ወስጄ ላሳክምህ አለችኝ። እኔም ፈቃደኛ ሆኜ ያለኝን ዶክሜንት እና ፎቶግራፌን ጭምር ሰጠሗት። እርግጠኛ አይደለሁም ገነዘቡ ሲገኝ እነግርሃለሁ አለችኝ።እሺ ብየ ስጠብቅ በ1988 ዓ.ም ነሐሴ አካባቢ “ሲስተር እዉነቱ” የምትባል የሷ “ጸሃፊ” እና አሷ ሆነዉ <ገንዘቡ ተገኝቶልሃል ዉጭ ትሄዳለህ፤አሁን አሁን ፎርሙን ትሞላለህ > አሉኝ። እሺ ብየ ፎረሙን ሞላሁ።የምታዘጋጀዉ ነገር ካለ አዘገጅ አለችኝ። ተዘጋጀሁ። በዝግጅት ላይ እያለሁ ነሐሴ መጨረሻ ታመመምኩ። ምኒሊክ ሆስፒታል ተኛሁ።
ከምኒሊክ ሆስፒታል ተኝተህ ከወጣህ በሗላ ከሲሰር ካትሲል አልተገናኘህም? ብርሃነ፦ ለምሳሌ ያህል ሲሰተር ጤናየ በአካል ጉዳዩን ታዉቀዋለች። ዶ/ር ሙሉጌታ እና ዶ/ር ሥዩም የሚባሉ ባሉበት “ሲሰተር ካትሲል” <እኔ ከሁለት ሳምንት በሗላ ወደ ዉጭ አልከዋለሁ።ጊዜያዊ ዕርዳታ አድረጉለት ገንዘብ አሰባስቤለታለሁ> ትላቸዋለች። እነሱም የዉጭ ዜጋ ሆነሽ እንደዚህ ካደረግሽ እኛ የኛ ወገናችን ሆኖ ዕርዳታ የማናደርግለት ምንም ምክንያት የለም። አሏት። ከዛ አስወጥታ ቤቷ ድረስ ወሰደችኝ። ቤቷ ከወሰደችኝ በሗላ…
እራሷ ቤት? ብርሃነ፦ አዎ። መኖሪያ ቤቷ ከወሰደችኝ በሗላ፤”ሲሰትር ጆኣን” የምትባል ሃኪም ነበረች። እገሬም መንቀሳቀስ አይችልም ነበር፡ በጣም ደክሜአለሁ። ከሆስፒታል የታዘዘልኝ መርፌ ነበርና <ልዉጋህ መሬት ዉረድ ከአልጋ > አለችኝ።አሁን “ሴንት ሜሪ” ነዉ የምትሰራዉ። አስክትነግሪኝ ድረስ አልቆይም ወርጄ እወጋ ነበር፤ነገር ግን አቅም የለኝም ሁሌም አልጋ ላይ ነዉ ተኝቼ የምወጋዉ> ስላት፤እግሬን ጎትታ መሬት ላይ ወረወረችኝ።ደም ፈሰሰኝ።አለቀስኩ። በሗላ የትግራይ ኢሮብ አካባቢ ተወላጅ የሆነች “ሲሰተር ሳባ” የምትባል የሰጠችኝ መልስ << ብርሃነ! ይህ እኮ የካቶሊክ ድርጅት ነዉ፡ ለምን ቅድስት ማርያም ሄደህ አትለምንም?>> አለችኝ። ከዚያም ለሲስተር ካትሲል <<የካቶሊክ እማኞች እያሉ ይሄ እንዴት ይሄዳል? የተሰበሰበለት ገንዘብ በካቶሊክ ድርጅት እንጂ በኦርቶዶክስ ድርጅት አይደለም፤ሊሄድ አይችልም>> ብላ ተቃዉሞ አቀረበች። በወቅቱ ለእኔ ይነገረኝ የነበረዉ ግን ገንዘቡ እንደመጣ ከሁለት ሳምንት በሗላ አንደምሄድ ነበር የተነገረኝ።>>
ሲስተር ሳባ የተቃወመችህ ኦርቶዶክስ ስለሆንክ ነዉ ወይስ ከህወሐት ጋር ግንኙነት ኖሯት ኖሯል ይሆን? ብርሃነ፦ ያን ጊዜ በህወሐት እንደተመታሁ አያዉቁም ነበር። እንዲያዉም ግልፅ አድርጌ አልናገርም ነበር። ከዚያስ ምን ተከተለ? ብረሃነ፦ በሰኔ ወር 1990 ዓ.ም ፈረንጇ አዲስ ወረቀት አምጣልኝ እና እሞክራለሁ ስላለችኝ ሆስፒታል ከጤና ጥበቃም ጭምር አስፅፌ ሰጠሗት። ማስረጃዉን ስሰጣት ክረምቱን ዉጭ ነዉ የምቆየው ገንዘብ አሰባስቤ እመጣለሁ አዚሁ እየሰራህ ቆየኝ>> አለችኝ። ተመልሳ ስትመጣ <<ትንሽ ገንዘብ አግኝቼአለሁ እና እንዳልከዉ ኬኒያ ብትሄድ ምን ያህል ያድኑኛል ብለህ ታምናለህ? >> አለችኝ። እኔም <<እርግጠኛ አይደለሁም፤ ነገር ግን ወደዚያዉ የሚመላለሱ ነጋዴ ዎች ስላሉ ከነሱ ጋር ልመካከር።>> አልኳት። እንግዲያዉስ ተነጋገርና በአጭሩ ቀን መልሱን ስጠኝ>> አለችኝ። ነጋዴዎቹ የሕክምና ማስረጃየን ኬንያ ከወሰዱ በሗላ <ኬኒያ ደርሰን ለዶክተሮች አሳየነዉ፡ የሕክምናዉን ወጪ ግምቱን እንጂ ከወዲህ ይህን ያህል ይፈጃል ማለት አንችልም፡የራጁ ዉጤት ስለሌለም ለመገመት ያዳግተናል፤አንደሚታየዉ ጉዳቱ ከባድ በመሆኑ ከ15ሺህ ዶላር በታች አይበቃዉም>> መባላቸዉን ገለጹልኝ። ይህንኑ አምጥቼ፤ በአማርኛ ተጽፎ የነበረ፤ በእንግሊዝኛ አስተርጉሜ ሰጠሗት።ስላት፡<<በል ተዘጋጅ፤ አሁን ትሄዳለህ፡ፓስፖርት አዉጣ>> አለችኝ።ፓስፖርት ካወጣሁ በሗላ ወደ ናይሮቢ ከመሄዴ በፊት ገንዘቡ ይሰጠኝ ችግር ሊያጋጥመኝ ይችላል እና ትለልቅ ሰዎች ስላሉ ገንዘቡን ለነሱ ስጪሊኝ>> ስላት <<የለም እዚህ አልሰጥም ከኢንግላንድ ቀጥታ ከአባ ሚካኤል 15 ሺህ ዶላር ተቀብለህ ታክመህ ትመጣለህ።ካነሰህ ከዚያ ደዉለህ ንገረኝ>> ብላ አድረሻ ሰጠችኝ።
ኣባ ሚካኤል ደግሞ መናቸዉ? ብረሃነ፦ የአባታቸዉን ስም አላቅም፡ ፈረንጅ ናቸዉ።ካቶሊክ።አድራሻቸዉ ጽፋ ሰጠችኝ።ያለ ተቀባይ ቀጥ ብየ ሄድኩ። ከዚያ ስደርስ ችግር መጉላላት ደርሶብኛል።እግዚአብሔር ጥሎ አልጣለኝም ከዚያ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ከፍተኛ ትብብርና ዕርዳታ አድርገዉልናል። በገንዘብም በሌላም።ከእኝህ ሰዉ ጋር ያገናኙኝም አነሱ ናቸዉ።በሗላ ግን የተጠቀሰዉገንዘብ አላገኘሁም።
ሰዉየዉን ስታገኛቸዉ የለም አልሁ? ብርሃነ፦ ትንሽ ገንዘብ ነዉ ያለዉ አሉኝ።<ምን ያህል አለ?> ስላቸዉ <2ሺህ> አሉኝ። 2ሺህ ዶላር በናይሮቢ ደረጃ ለቀለብ እንኳን አይበቃም ብየ ለሲስተር ክርስቲና አዲስ አበባ ደወልኩላት። በኬንያ የታወቀ ሆስፒታል ስንት ዶላር እንደሚያስከፍሉ ተመርምረህ ወይም ግምቱን ላክልኝ ወይም ይዘህ ና አለችኝ፤፡ አኔም ኬንያ ዉስጥ አጋርካን በሚባል ሆስፒታል ደ/ር ጆን የሚባል ሃኪም ለ1 ሳመንት መርምሮኝ ዋጋዉን አሳወቅኳት።ሁሉን ነገር ካየ በሗላ 4 ወር ትተኛለህ፤ሦስት ዓይነት ኦፐራሲዮን ታደርጋለህ እግርህም ይድናል። እንደነበረዉ ይሆናል። ለአጠቃላዩ ወጪ 6ሚሊዮን 200 ሺህ የኬንያ ሽልንግ ወይም 103 ሺህ ዶላር ትከፍላለህ አለኝ።ይህንኑ መልስ ለሲሰተር ካሰቲል ሰጠሗት። ሲስተር የሄን ጊዜ ፈነጠዘች። <3ጊዜ>። <አንዳለ ፈረንጅ በሙሉ የግምቱን ወረቀት ሲያይ አጨበጨበ>።
ለምን? ብርሃነ፦ በዚህ ሰነድ ከብዙ ሃገሮች ገንዘብ ስለሚሰበስቡ።..በካናዳ፤ በአሜሪካ፤ በእንግሊዝና በሌሎችም አገሮች ለሚገኙ በጎ አድራጊዎች ወረቀቱን እበትነለሁ። በዚህ ሰነድ ገንዘብ ሲመጣ ተመልሰህ ትሄዳለህ ትለኛለች። እሺ ብየ በመጠባበቅ ላይ እያለሁም ለ”ጋሽም” የጉዞ ወኪል ልካ ገንዘብ ጨምረን ስለምንልከዉ ተመልሶ ለሕክምና ስለሚሄድ ከቲኬቱ ከሚመለሰዉ ገንዘብ እንኳ መልሱት ብላ እዚያዉ አስቀሩት። ከታህሳስ አስከ ሚያዚያ ሲያመላልሱ አቆይተዉኝ አለርት ሆስፒታል እንሂድ አሉኝ።
<< አለርት ሆስፒታል ስጋ ደዌ ህክምና ነዉ ያለዉ፤የኔን በሽታ አይመለከትም፡ ባለሞያወቹ ጥቁር አምበሳ ሆ/ል ነዉ ያሉት ስለዚህ አልሄድም> ብል፡ <እገሌ ከሚባልደ/ር ጋር ተስማምተናል።> አሉኝ።ምነድነዉ ምትስማሙት 5 ዓመት ሙሉ መለመኛ ሆኜ ተቀምጫለሁ። ከዚህ በሗላ መለመኛ ሆኜ መቀጠል አልፈልግም። ያገኘሁት ፋይዳ የለም። ስለዚህ ባላችሁት መሰረት ላኩኝ፡ አንልክም የምትሉ ከሆነ ግን በስሜ የተዋጣዉን ገንዘብ ስጡኝ፡ የትም አገር ሄጄ ታክሜ እድናለሁ> ስላቸዉ ሲስተሯ ተደበቀች።
በሗላ ባሕር ዳር ሄዳ መሸሸግዋን አወቅኩ። ባሕር ዳር ሄጀ ለፓሊስ ኮሚሽኑ እንዲህ ያለች ሴትዮ አለች ተባበሩኝ አልኳቸዉ። ያለችበትን ንገረን እንተባበርሃለን አሉኝ። እኔን ስታይ ትደበቃለች ብየ በሌላ ሰዉ ሳስጠይቅ እንዲህ የምትባል እዚህ የለችም አሉኝ። ከባህር-ዛፍ ዉስጥ ተደብቄ ቆየሁና መኪና ይዛ ስትወጣ ያዝኳት። ሕግ ቦታ አንሂድ ገንዘቤን ስጪኝ። ስላት፡
<<ተዉ አታጋልጠኝ፡ እኔ ሲሰትር ሜሪ ለምትባል አዉስትራሊያዊትና ለሲስተር ትብለጽ አስረክቤ ነዉ የመጣሁት፡ 1 (አንድ) ቀን ብቻ ስጠኝና አስጨርስልሃለሁ።>> አለች ።ችግር የለም፡ አልኳት።በሗላ ግን ተመልሳ ወደ አዲስ አበባ ጠፍታ ሄደች። አግኝቻት ነበር፡ ጠፋች አልኩ።ለፖሊሶች።ፖሊሶች ለአየር መንገድ ስልክ ደወሉ። በየጠዋቱ በረራ እንደመጣች አረጋገጡ። ከባሕር ዳር መጥቼ “ሴንት ሜሪ ” አዲስ አበባ ከተማ አገኘሗት። ሳገኛት <<በይ አሁን ኡ! ኡ! እላለሁ! መፍተሄ ስጪኝ፡>> ስላት፡
<<አዲስ አበባ የመጣሁት እኮ ስላንተ ጉዳይ ለመነጋገር ነዉ። የባንክ ደብተር ከፍተህ እኔ ጋር ና>> አለችኝ። እዉነት መስሎኝ ይህንን ሰኔ 20ቀን 1991 ዓ.ም ከተነጋገርን በሓላ ሰኔ 22 ደብተር ከፍቼ ወደ ሴንትሜሪ ስሄድ ጽሁፍ አዘጋጅታ ድርጅቱን ሰራተኞችና ሌሎችም የማይታወቁ ሰዎች ይዛ “አንደር-ግራዉንድ” ዉስጥ አስገብታ፤መስኮትና በር ተቆልፎ በቀኝና በግራ እጄን ይዘዉ በማላምንበት ወረቀት አልፈርምም አሉኝ። በማላዉቀዉ ጉዳይ አልፈርምም አልኩ።
ምንድነዉ የምትፈርመዉ? ብርሃነ፦ ሕክምና አልፈልግም፤… ምናምን የሚል ይዘት ነበረዉ። አላነበብከዉም? ብርሃነ፦ ትንሽ ነዉ ያየሁት አላነበብኩትም።3ገጽ ነዉ የተጻፈዉ።በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ። አምቢ ስላቸዉ ጊዜ ሰራተኞቹ ለመኑኝ። <<የሰዉ እንጀራ አትዝጋ፡ ለምን አትፈርምም? የሰጠችህ ገንዘብ አለ።አሉኝ። ልወጣ ስል ከለከሉኝ።በየት ልዉጣ?! በሩ ተቆልፏል። ከዉስጥ ሌላ ክፍል አለ፦ ፊታቸዉ እንዳይታይ ኦፐሬሽን እንደሚያከናዉን ዶ/ር ዓይናቸዉ ብቻ የሚታይ ሰዎች ጩቤ እና መሳሪያ ይዘዉ ደረቴ ላይ ደገኑብኝ። ካሁን በሗላ ወይ ለጋዜጠኛ አልያም ለፖሊስ ከተናገርክ ወዮልህ! ትፈርማለህ …አትፈርምም? የማን ገንዘብ ልትበላ ነዉ?ካንገራገርክ እዚሁ እንደፋሃለን!>> አሉኝ። የነሱን ዘዴ ስላወቅኩ ገድለዉ በቆሻሻ መኪና ሊጥሉኝ እንደፈለጉ ግምት ስላደረብኝ ችግራችሁ ይሄ ከሆነማ አምጡ፡ እፈርምላችሗለሁ።>> ብየ ፈርሜ 5 ሳንቲም ሳልይዝ ወጣሁ። ሁሉንም ለፖሊስ ጣቢያ፤ለጠቅላይ ሚ/ሩ ቢሮ ለፍትሕ ሚ/ርና ለዉጭ ጉዳይ መ/ር በአስቸኳይ አሳወቅኩ።
ማመልከቻ ነዉ? ብረሃነ፦ ማመልከቻ ባስቸኳይ በፖስታና በተለያዩ መንገዶች ከ70 ብር በላይ አዉጥቼ ላክሁ። የተሰጠኝ መልስ ግን የለም። የዉጭ ጉዳይ ሚ/ር ከስንት ጊዜ በሗላ እንዲጣራ ብሎ ለፌደራል ፓሊስ አስታወቀ። መጨረሻ የማይረባ ገንዘብ ሰጥተዉ አሰናበቱኝ። ማን? ብርሃነ፦ እነሱ። እነሱ እነ ማን? ብርሃነ፦ እነ ሲሰተር ክርሰቲኒ፡ ምን ያህል ላኩልህ? ብርሃነ፦ ወደ አስር ሺህ ገደማ ላኩልኝ።በዛችዉ ስታከም ቆየሁ። መንግሥትም ዞር ብሎ አላየኝም። አስካሁን ድረስ በዛች ገንዘብ ነበር ቆየሁት። አሁን ግን የምቀምሰዉ እንኳ ቸግሮኛል። ጠ/ሚ/ሩ ቢሮ አመልክተህስ ምንም ምላሽ አልመጣም? ብርሃነ፦ ከሦስት ወር በሗላ ከፍትሕ ሚ/ር እና ከአደጋ መከላከል ጠይቅ የሚል መልስ ነዉ የተሰጠኝ።
በፖሊስ በኩልስ? ብርሃነ፦ ፖሊስ እና ፍትሕ ብንጠይቃቸዉ አቃቤ ሕግ የዉጭ ዜጋ ለመያዝ ማን ፈቀደላችሁ? ብሎ የከ’ሰናል! ስለዚህ ዓቃቤ ህግ የጻፈልን እናጠራለን ብለዉኝ ነበር። ፌደራል ፖሊስ በተደጋጋሚ አቤቱታ አቅርቤ ለፍትሕ ሚ/ር ደብዳቤ ጻፈልኝ። ይሄ ድርጅት በመንግሥት ተመዝግቧል ወይስ አልተመዘገበም? ባስቸኳይ መልስ ስጡን ብሎ ጻፈ። ደብዳቤዉን አላየሁትም፡እንደዚያ የሚል ደብዳቤ ተጽፏል አሉኝ። ፍትሕ ሚ/ር አቶ መስፍን ጋር ሂድ አሉኝ።
መስፍን ግርማ የፍትሕ ሚ/ር የነበሩት? ብረሃነ፦ አሳቸዉ ጋር ስቀርብ አቶ መስፍን <<ይሄ ድርጅት የዉጭ ዜጎች ስለሆኑ በዉጭ ስለሚያስጠይቀን ልንጠይቃቸዉ አንችልም ።>> ሲሉ መለስሉኝ።
ከዚያ በሗላ አልጠየቅክም? ብርሃነ፦ ከዚያ በሗላ ተስፋ ቆረጥኩ። ልጠይቅም አልችልም።ብጠይቅም ተሰፋ አልነበረኝም። ሁሉንም ቦታ አቤት ብያለሁ።ከዚያ ወዲያ የት አቤት ልበል? አሁን አንተን የሚረዳህ ማን ነዉ? ብርሃነ፦ እንዲሁ የአዉቁኝ አንዳንድ በሁኔታየ ያዘኑልኝ፤የሆዴን የሚያዉቁ ሰዎች በይበልጥ የአዲስ አበባ ዶክተሮች ይረዱኝ ነበር። በ አብዛኛዉ ደግሞ አንድ ዶክተር የተባበሩኝ ነበር። ለቤት ክራይም ይከፍሉልኝ ነበር። እሳቸዉ ከዚህ ከተቀየሩ በሗላ ግን በሕክምናዉም፤በመድሃኒቱም በጣም ጨልሞብኛል።
ተከራይተህ ነዉ የምትኖረዉ? ብርሃነ፦ ተከራይቼ ነዉ።ከፈረምኩ በሗላ ከነበርኩበት አካባቢ እየመጡ አላስቀምጥ አሉኝ። እየደወሉ እቤት እየመጡ ብርሃነ አለ ወይ እያሉ ሲያሰቸግሩኝ የግድ ቤቱን ለቅቄ ወጣሁ። አሁን የት ነዉ ያለኸዉ? ብርሃነ፦ እየከፈልኩ ወይንም ከማቃቸዉ ሰዎች ካገኘሁ ከነሱ ዘንድ አድራለሁ።
እንጂ ቋሚ ቤት የለህማ? ብረሃነ፦ ቃሚ ቦታ የለኝም። አሁን ወላጅ እናትህ ዓድዋ ናቸዉ? ብርሃነ፦ ጥቁር አምበሳ ሆስፒታል እያለሁ ነች ከዚህ ዓለም ተለየችኝ። እህት እና ወንድሞችህስ? ብርሃነ፦ በዚህ የተነሳ የት እንዳለ እንኳ አላዉቅም። ሸራሮ አሉ ይባላል፡ ማን ወደ እዛ እንደወሰዳቸዉ አላቅም።
እንደምትነግረን ሥር የሰደደ በደል ደርሶብሃል። በደሉም ማብቂያ አጥቷል። እንደምናየዉ በሰዉነትህ ላይ ያለዉ ቁስል እጅግ እጅግ ያሰቅቃል። ሽታዉም አንዲሁ። አሁን የኢትዮጵያ ሕዝብ ወይም መንግሥት ምን እንዲያደርግልህ ነዉ ምትፈልገዉ? ብረሃነ፦ እካሁን የቆየሁት በኢትዮጵያ ህዝብ እና በኢትዮጵያ ዶክተሮች ድጋፍ ነዉ። ለ9 (ዘጠኝ) ዓመት ላቆየኝ ለሰፊዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ታላቅ ምስጋና አቀርባለሁ። አሁንም ቢሆን ሰፊዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ በመንግሥት እና በዉጭ ድርጅቶች የደረሰብኝን ግፍ ግምት ዉስጥ አስገብቶ ችግሬን እንዲከታተልልኝ እፈልጋለሁ።
በሁለተኛ ደረጃም፤ በዘህ እሸት የወጣትነት ዘመኔ ካለሁበት አሠቃቂ ስቃይ እና አስከፊ በሽታ እንድላቀቅ ይረዳኝ ዘንድ በተቻለ መጠን እዲተባበረኝ በትህትና እጠይቃለሁ። ዋናዉ በሽታህ ያለዉ እግርህ ላይ የሚታየዉ ነዉ? ወይስ ሌላ ነዉ? ብርሃነ፡_ ከ አንጀቴ ደም እና መግል ያለማቋረጥ ሆዴ ዉስጥ እየፈሰሰ ነዉ። (ቁስሉን እያሳየ) ይሄ በገሃድ ሚታይ እና በባለሞተኞችም የተረጋገጠ ነዉ። ካሉት በታች፤ከሞቱት በላይ ሆኜ ሕይወቴ በቋፍ ላይ ነች። 24 ሰዓት በስቃይ በችግር እተጠበስኩ (በምሬት እያለቀሰ) ነዉ ያለሁት።//-/ አመሰግናለሁ አቶ ብረሃነ። ማሳሰቢያ ከላይ የቀረበዉ ቃለ መጠይቅ ለሕዝብ ይፋ እንዲሆን በመጽሄታቸዉ አትመዉ ለታሪክ ማሕደር የተዉልንን የኢትኦጵ መጽሄት አዘጋጆች ከፍተኛ ምስጋናየን አቀርባለሁ። “የትግራይ ነፃ አዉጪ ድርጅት መሪዎች” በትግራይ ዲያቆናት እና ካህናት እንዲሁም ወጣቶች ላይ በስብእናቸዉ ያደረሷቸዉ የመብት ረገጣ ወንጀሎች ሳይጠየቁበት ዓይናቸዉን በጨዉ አጥበዉ ዛሬም በዉሸት ዓለም “ኑ!” እናሞኛችሁ ሲሉን፤ የትግራይ ህዝብ ዕምባ ከጉዳይ ሳይቆጥሩ ከነኚህ እርኩሶች ጋር እንተሻሽ የሚሉንን ዉጭ አገር የሚኖሩ በተቃዋሚነት ስም የሚፎልሉትን “የፖለቲካ ነጋዴዎች እና ግብዞችን” በድፈረት “የፖለቲካ ሽርሙጥናቸዉን” እንዲያቆሙ መጠቆም የዜጎች ሃለፊነት መሆኑን ከወዲሁ አደራ እላለሁ። የዜጎች ደም፤ እምባ፤ኡ ኡ ታ ዛሬም ከምድር በታች እና ከምድር በላይ ይጮሃል።ፍትህ ማግኘት ይኖርበታል። ፍትሕ ጠየቃችሁ ብለዉ የሚጠሉን ካሉ፤እኛን ሳይሆን የጠሉት ፍትሕን ነዉ። ጌታቸዉ ረዳ ሳንሆዘ ካሊፎርኒያ www.Ethiopiansemay.blogspot.com

Monday, September 8, 2008

ወየንቲ ብሸዉዓተ ጥይት ተኲሶም ኣቑሲሎሙ ናብ ዱር ወሲዶም ደርቢየሙኒ

ካብ ገበን ማህደር ወየንቲ
ወየንቲ ብሸዉዓተ ጥይት ተኲሶም ኣቑሲሎሙ ናብ ዱር ወሲዶም ደርቢየሙኒ
ትርጉም
ጌታቸዉ ረዳ 

አብ መጽሄት ኢትኦጵ ንቃለ መሕተት ቀሪቡ ዝነበረ ብረሃነ ገብረሕይወት ዝተብሃለ ትግራዋይ ዝሃቦ ጋዜጣዊ ቃል ምልልስ ንኣንበብትና ነቕርብ። ብርሃነ ኣብ ገድሊ ህዝባዊ ሓርነት ወያነ ትግራይ ንክጋደል ብተደጋጋሚ ተጠይቑ ምስ ኣበየ፤ ናይ ትግራዋይነትመጸዋዕታ ስለዝነጸጎ ብተደጋጋሚ ምስታኣስረ ብዘሰክሕ ግብረ ጭካነ ብሸዉዓተ ጥይት ከምዘቑሰሉዎ ይዛረብ። ህይወቱ ሙሉእ ንበተኽስያን ካብ ምግላል ንንዉ ዝእልሾን ዝደልዮን፤ድልየት ከምዘይብለይ እንተተዛረብኩዎምእዉን ፍልይ ዝበለ ግፍዒ አብ ልዕለይ ተፈጸሙ ይብል።

አብ አኽሱም ዝተዉሃቦ ናይ ድቁና ምስክርወረቐት እዉን ናይ ህወሓት ተጋደልቲ ሃባኢሎም ካብ ጁባይ ኣሕዲጎም ቀዳዲደሙለይ እዮም። እቲ ብጥይት ተኲሶም ዘዉረዱሉ መዉጋእቲ ከቢድ ስለዝኾነ ጥቁር አምበሳ ሆስፒታል ክሕከም ጸኒሑ ሰነ 20 1986 ኣብወጻእ እምበር ኣብ ዉሽጢ ዓዲ ክድሕን ከምዘይኽእል ኣራጋጊጹሉ እዩ። ፍሉይን ዝላዓለ ሕክምና ዘድልዮ ሙኻኑ ዘራጋገጸሉ ሓካይምን እዉን ዶክተር ተመስገን ናይ መጥባሕቲ ሕክምና ፈላጥ፤ ዶክተር ዘርአ ገብረማርያም መዲካል ድሬክተር፤ፕሮፌሰር ድብሊዉ ማክሊን ክፍሊ መጥባሕቲን ምዕዳንን እዮም። ጸኒሑ ብዝብራህርሆ ምኽንያት ካብ እቲ እንዳታሓከመ ተጸጊዑ ዝነበረሉ ዝነበረ መዕቖቢኡ ኣዉጺኦም ናብ ደገ ብራንዳ ከምዝደርበዩዎ ኣምሪሩ ይገልጽ።

ናይ ብርሃነ ጉዳይ ክሳብ ኬኒያ በጺሑ እዩ።ናብ ትግራይ ቅልቅል ኢሉ እውን ናይ ክልል መንግሥቲ ትግራይ ዋና ጸሓፊት ዝነበራ ወይዘሮ አረጋሽ አዳነ እዉን አዛራሪቡ እዩ። ንወይዘሮ አረጋሽ ብዘዛረበሉ እዋን ኣብ አንደር/ግራዉንድ ማለት ኣብ ዉስተ/መሬት ንነዊሕ ናብ 3 ሰዓትን ፈረቓን ዝኣክልብጥያቄ መርመራ ማይ ከይሰቲ ተኸልኪሉ ብጻምእ ማይ ምስ ቁሱልን ዱኹምን ኣካላቱ ከምዘንካላበቱዎን ዘጨነቑዎን ይዛረብ።

ኣብ ኣካላት ብርሃነ ዝራኣይ ቁስሊ ብዓይንን ብእዝኒን ዝራኣይ እንምስክሮ ነገር እዩ። ካብ ቁስሉ ንክፍወስ 6 ሚሊዮን ቅርሺ 200 ሺሕ ናይ ኬኒያ ሽልንጊ / 103 ሺህ ዶላር/ ከምዘድልዮ ዶክተር ጃን ዝተብሃለ ኣብ ኬኒያ ዝርከቡ ሓካይም ዝፈረሙሉ ብፈረንጂ ዲሰምበር 21 /1998 ዝተጽሓፈ ወረቐት እዉን ምስ ብርሃነ ኣሎ።በታን በታን ካብ አንደበቱ እንታይ ከምዝብል እነሆ።እዝኒ ዘይሰምዖ የለን፡ተጋደልቲ ህወሓት ብሸዉዓተ ጥይት ብሪጋ ተኲሶም ኣቑሲሎም ናብ ዱር በረኻ ሻምቦ/ሻምቦ ኢሎም ወሲዶምከም ኣራዊት ንዝብኢ ደርቢየሙኒ ዝብለና ዘሎ ብርሃነ እነሆ።

ስምካ መን ክብል

 

ብርሃነ ገብረሕይወት ትዉልዲ ዓድኻ

 

ብረሃነ

ዓድዋ አዉራጃ ኣብ ትዉልዲ ከባቢኻ ኣብ ትግራይ እንታይበደል በጺሑኒ ኢኻ እትብል ዘለኻ 

 

ብረሃነ

ተምሃራይ እንዳሃለኹ ማለት ናይ ቤተክህነትተምሃራይ እንዳሃለኹ ማለት እዩ፤ 1975;ካብ አኽሱም ድቁና ተቐቢለ ምስ ተመለስኩዉድቕቲ ለይቲ ዘይፈልጦም ሰባት እሳ/ዕሳናብ ዝባሃል ቦታ ኣሲሮም ወሰዱኒ። ብድሕሪኡ ናትካ ድቁና ኣይሰርሕን እቲ ሕዚ ዘሎ ጳጳስ ምስ ደርጊ ሰብ ንክቕተል ዝኣወጀ ስለዝኾነ ቅስና ይኹን ድቁና ክባርኽ ኣይኽእልን፡ ኣይግበኦን ዝብል መመኽነይታ ሃቡኒ። አዚ ዝብልዎ ዘለዉ ጳጳስ መን እዩ 

ብረሃነ፡

ሕዚ ስሞም ወንጋእ ኢሉኒ ኣሎ። በቲ ጊዜ እቲ ስሞም አብቲ ዝተዉሃበኒ ምስክር ወረቀት ሰፊሩ ነይሩ። ትግራዋይ ድዮም፡

ብረሃነ፡

እንድዒኸ፤ በቲ ጊዜ እቲ ኣምሓርኛ እዮም ዝዛረቡ ነበሩ።

ኣብቲ 1975 / ወረቐት ዝተዉሃብካሉ/ ዝተመረቕካሉ ቦታ ደርጊ ኣይኮነን እዩ ዘማሓድሮ ነይሩ/

ብርሃነ፡

 ከከተማኡ ደርጊ እዩ ሃሃገረሰቡ ድማ ንሶምተሓህት እዮም ነይሮም ዘማሓድሩዎ። ካብ ሃገረስብ ድዮም ሒዘሙኻ

 

ብረሃነኣብ ሃገረስብ እወ። ኣነ ብዛዕባ ናታትኩም ዕላማ ኣይፈልጥን ቅድሚኡ እዉን ዝፈልጦ ነገራት የብለይን ምስበልኩዎም 10 መዓልቲቅጽዓት ኢሎም ኣሲሮም መንነት ወረቐተይ ቀዲዶም ብድሕሪኡ ደርጊ ኣብዘለዎ ከባቢ ዝር ከይትብል ኢሎም ኣሲሮም አስጠንቂቖም ዋሕስ ኣቁጺሮም ሰዲደሙኒ።ካልኦት ከማይ ዝበሉ 50 ዝኾኑ ቅስና ድቁናን ዝተዉሃቦም ዝተፈላለዩ ምእመናን እዉን ወረቐቶም ተመንጢሎም። እቲ ናይ ድቁናን ቅስናን ወረቀት ድዮም ኣሕዲገሞም 

 

፡ብረሃነ/

እወ። ናይ ቅስናን ምስክር ወረቐቶምን። ብድሕሪኡ ጸኒሕና 1981 ብግዲ ናብ ግንባር ዝመቱ በሉና፡ ጥያቐ፦ 1975 ምስተታሓዝኩም ንክትዘምቱ ኣይተጠየቅኩምን/

 

 ብርሃነ፦ ይጥይቑና ነይሮም። ይኹን እምበር ግዴታ ኣይነበረን ብደርፊ ኪነት ገይሮም ይጉስጉሱና ነይሮም። ተኣከቡ እንዳበሉ የጻግሙልናይሰብኩና ተዘይኮይኖም ጽንኩር አስገዳይነትኣይነበረን። ግን ነገራት እንዳሓየሎም ምስመጸ የግድን ብግዲ ተጋደሉ በሉና።ንሕና ድማ /ንሕና ኣይነጋደልን።ንሱኹም ተጋደሉ ንሕና ክንስዕበኩም ኢና፡ ኢልና ምሳኹም ዉዕል ኣይኣተናን፡ተደሊኹም ክመቲ ዝጀመርኩሞ ባዕልትኹም ተጋደሉ፤ ንሕና ዉዕል ወይ ግዴታ ኣይተዋዓዓልናን። ንሕና ድኻታት ኢና፡ ገና ቁራስ እንጀራ እኳስ ኣይመነነናን።/ ምስበልናዮም፡ //መን ዓጽሙ ኣጎልዒሙን ደሙ አፍሲሱን ከንብረካ ደሊኻ// ኢሎም ብሕልፊ ቢሆን/ቢሄን ዝብልዎ ተጋዳላይ //ሓመድ ካብ ባይታ ቆንጢሩ አብ ኢዱዓኺቱ ናብ አፍንጫና ኣሽትትዎ እንዳበለ ኣፈራራሓና። ንሕና ድማ፤ ዋእ/እሞ እንተዳኣ ኣብ ዓድና ክንነብር ዘይንኽእል እሞ ክንነብር ዘይተፈቕዱልና ኮይንኩም ናይ ይሕለፍ ወረቐት ሃቡና እሞ ክንስደድ በልናዮም። ኣይዋሃበካን/እንዳበሉ የባሳጨዉናን የባሳብሱናን/የባጭዉልናን ጀመሩ። ዋእ/ እሞ ናበይ ዳኣ ክንከድ/ እንተበልናዮም፡ ናይ ባዕልኹም ጉዳይ/ዉራይና ኣይኮነን፡ ተደሊኹምተጋዲልኩም ሃገርኩም ነጻ ኣዉጽኡ፤ ኣይንጋደልን ተይልኩም ድማ እዛ መሬት እዚኣ ኣይትረግጹዋን።/ በሉና። ዋእ/ ካመን ኢና ናጻ እነዉጻኣ/ ደርጊ ኢትዮጵያዊ ንሰኹም እዉን ኢትዮጵአዊያን ኢኹም/ ምስበልናዮም፡ // ንስኻትኩም ሰበብ አለኩም፡/ነገር ኣለኩም/ ኢሎም ምእሳርን ምቕጻዕን ጀመሩና። ፡ክንደይ ትኾኑ

 

 ብርሃነ

1500 ንኾን

 ብድሕሪኡኸ እንታይ ገበርኹም፤/

 

 ብርሃነ፦

ብድሕሪኡ ንወለደይ አሰሩዎም። ግራዉትኹም/መሬትኩም ካብ ሎሚ ንንየዉ ብገድሊ ተወሪሱ እዩ በሉና። ቀንዲ ፋሓርቲን መጓሃሃርቲ ነገር ንስኹም ኢኹም ኢሎም አብ ልዕሊ ዉሱናት ሰባት ከቢድ ቅጽዓት ተፈጸመና። ካብ 6 ወርሒ ክሳብ ሓደ 1 ዓመት እንዳተቐጥቀጥና ብኩፉእ ብስቅያት ተኣሲርና።ገሊኦም ብጅማት ዝመስል መእሰሪ ኣትሪሮም ንነዊሕ ጊዜ ቀይዶም ስለዝቖርነዩዎም ኣእዳዎም ሓቢጡ፤በሲሉ፤ ብጽፍሮም ብኣጻብዕቶም ደም ጠብጠብ ይብል ነይሩ። ብጅማት ተኣሲሮም ኣእዳዎም ደም ዘንጠብጥብ ዝነበረ መታኣስርትኻ አስማቶም ትዝክሮም

 

ብርሃነ፦ አስማቶም ሕዚ ኣይዝክሮምን። እቲ ሓደ ሰለዳም ዝባሃል ቀበሌ እዩ ዝነብር ነይሩ።እቲ ካሊእ ድማ ማሓዛይ እዩ ብመግረፍቲ ሓደ ኢዱን ሓንቲ ኢዱን ሽባ ኮይኑ። ሓደ እግሩን ሓደ ኢዱን ሰሊሉ። ማሓዛይ እዩ። ሃለቃ ሓዲሽ ይባሃል። በቲ ጊዜ እቲ በዓለ ህማማት ስለዝነበረ፤ ካህናት ካብ ቅዳሴ ካብጸሎት ካብ ቤተ ክርስትያን እንዳተጎተቱ ይእሰሩ ነይሮም። ዓዲ ዝዋዓሉ ተዘይኮይኖም እያኣይ ዝበለ እንዳታሓፈሰ ተወሲዱ እዩ። ንምህዳም ዝፈተነ እዉን ከም ቆቋሕ ብጥይት እንዳሃደኑ እንዳጓየዩ ዳሩ ኣርእየሞ እዮም።

 

እዚዅሉዝኸዉንዘሎ ማዓዝ እዩ፡

 

 ብርሃነ፦ የካቲት ወርሒ 1981 / ጥያቐ፦ትግራይ ናጻ ምስወጸት ማለት ድዩ ብርሃነ፦እወ።በቲ ጊዜ እቲ ሰብ ከም አራዊት እዩ ዝሀደንነይሩ።አብዝኾነ ከባቢብቀትሪ ሰብ ዝባሃልዝር ኣይብልን፡ንዓይንኻ ኣይትርኢይን።ትሰብ ተዳሂሉ እዩ። ንሶም እዉን ነቲ ሰብ ከም ኣራዊት እንዳሃደኑ እዮም ዝዉዕሉ።ግራዉትና ንተጋደልቲ ህወሓት ዓዲለሞ፤ንሕና እንበልዖ እንስትዮ ሲኢንና እትጣዓም ቁራስ ጸጊሙና። ናቶም መቃባበልቲ ሓብሎቕቶም ካድረታቶም። እንተዳአ ሪኤሙና ከም ኣራዊት ጥይትና ናብ ጥቓና የትኩሱልና።ኣብጥቓና ኣብልዕሌናዝትኩስዎ ዝነበሩ ጠያይት ኣብዝባንና ኣይዓለበን እመበር ቁጽሪ የብሉን።ብድሕሪኡ አንዳጠመናን እንዳተሳቐናን ከርተት ምስበልና፡ ህዳር 21/1983 / ገረዳ ኣብዝባሃል ቀበሌ ማሕበር ንአቶ በርሄ እኽሊ ክንሽከመሎም ዉዒልና፤ አብ ገዛ ኣቲና ማኣዲ ተቐሪቡ እኽሊ ክንበልእ ከቢብና እንዳሃለና እቲ ገዛ መንነቶም ዘይንፈልጦም ዑጡቋት ተኸቢቡ። ንዉሽጢ አትዮም ናዓይ ጸዉዑኒ እሞ ናዓዉጻእ በሉኒ። ዋእዐረ በእንተ ማርያም እኽሊ እኳ አፉ ኣልክፉዎ፡ጥራሕ ከብዱክሽቅል ዉዒሉስ እኽሊ እኳ በይዛኻትኩም ይልከፍ እሞ ትወስዱዎ እንትበሉ እቶም ባዓል ገዛ ለመኑዋቶም። ዳሓን ህዚ ክምለስ እዩ፡ ንህቶ ኢና አንወስዶ ዘለና በሉዎም።ወሰዱኒ።ካልኦትእዉን በብኸባቢኡ ዝኣከቡዎም ሓወሱና።5ንኸዉን።ኩላትና ድማ ኣኼባ እንትገብሩልና ብግልጺ ንካራኸሮም ዝነበርና ገባራት ድያቆናት ኢና።ኣኻኺቦም እንትወስዱና እዚኦም ነቲ መንእሰይ ሕማቕ ትምህርቲ ስለ ዝመርሑዎ ካብደርጊ ፈሊና ኣይንሪኦምን፡ተዘይጠፊኦም ኣየስሩናን። ኢሎም ከምቶም ብዙሓት መንእሰያት ቅድሚ ሕዚ ዘጥፍኡዎም ንዓና እዉን ከጥፍኡና እዮም እንዳበልና ንንሕድሕድና ሕሹኽ/ሹኽ በልና። ናበይ እዮም ዝወስዱኹም ዘለዉብርሃነ፦ ናብ ዱር። ንሕና ኣይንፈልጥን። እንታይ ይሓይሸ በልና ሕድሕድና። ሞት ንሞቱ ኣብዚ ንሙት አንዳተባሃሃልና ጉዕዞ ኣምራሕና።ኩላትና ብሓባር ተዳሊዮም እንዳኾብኮቡና አንዳሃለዉ፡

አይተወደአን……….ክቕጽል እዩ።