«ጽምዶ»(Proxy
Actors) የአዲሶቹ እና የነባሮቹ የአምስተኛ ረድፎች መጫወቻ ሜዳ
ጌታቸው ረዳ
(Ethiopian Semay)
6/10/26
ዛሬ የምናየው ብዙ ጥንቅር እናያለን።የውጭ እና የውስጥ አከናዋኝ ወኪሎችን እንመለከታለን። ኢትዮጵያ አሁን ወደአለችበት ሁኔታ እንዴት ገባች ብለን መልስ ለማግኘት የተለያዩ መላምቶች ከያንዳንዳችን የሰነዘራሉ። መልሱ የተወሳሰብ እና ይተለያዩ ምክንያቶች ቢሆኑም ከዘመነ አክሱም ጀምሮ እስከ 13ኛ ፥ 15ኛው 16ኛው ክ/ዘመን ፣ ከዚያም ወደ 17ኛው ፥ 18 ፥ 19ኛው ክ/ዘመን እና እሰካሁን ድረስ ያላባራው ትርምስ ስንመለከት ያው በተጠቀሱት ዘመኖች ታሪክ የመዘገባቸው ተመሳሳይ የውጭና የውስጥ ወኪሎቻቸው የተጣመረ የጥቃት ዘመቻዎች ናቸው አሁን ወደ እምንገኝበት ዘመነ ዕልቂት የምንገኝበት ምክንያት።
እንደ መንደር
ጎረምሳ በየአገሩ ዘው እያለች ደረትዋን የምትነፋ ሃያልዋ አሜሪካ “ጁቡቲ ቁጭ ብላ” ምስራቅ አሪቃ ቀጠና ውስጥ ፖለቲካዊ የለውጥ ቅየሳ እያደረገችው ያለችበት
ምክንያት ምንድነው?”
በሃያላን መንግሥታት መካካል የተከሰተው ውድድር በምስራቅ አፍሪቃ ቀጠና ውስጥ ስንክሳራዊ የሆነ የፖለቲካ ክር መመዘዝ ከጀመረች ዘመናት አላት።
ብዙ የሃግረ እና የውጭ ተንታኞች እንዳስቀመጡት ካሁን በፊት የአሜሪካኖች ትልቁ ስጋት “ዓለም አቀፍ ሽብርተኝነት ነበር” ስለሆነም ሽብር ለመዋጋት ኢትዮጵያን አጋር አድርጋ ኢትዮጵያ ያሻትን ዕርዳታ ከአሜሪካኖች ይደረግላት ነበር፡ ሆኖም ዛሬ የአሜሪካ ስጋት ከሽብር ይልቅ፤ ሩሲያ እና ቻይና በጉልበት እየፈረጠሙ ስለሄዱ ስጋት ላይ ጥለዋታል። ስለሆነም መመሪያዋ በመለወጥ ትኩረትዋ ከሽብር ይልቅ ኢኮኖሚ እና ወታደራዊ ጉልበትዋ በመፈታተን ላይ ወዳሉት ወደ ሩስያ እና ቻይና በማድረግ የፖሊሲ ለውጥ አድርጋለች። ይላሉ።
ታስታውሱ እንደሆን በምስራቅ አፍሪቃ በተለይም ኤርትራ ኢትዮጵያ እና ሱዳን በነፋስ ጠረጋ ፍጥነት የተከሰተው ‘የፖለቲካ ለውጥ’ አሜሪካና አጋሮችዋ ከኋላ ሆነው ዓረቦችን በመላክ እነዚህ አገሮች በተለይም ኤርትራ እና ኢትዮጵያ ከቻይናዎች ኢኮኖሚያዊ እና ስትራቴጂያዊ የስምምነት ቀለቤቶች ከጣታቸው እጅ በማስወለቅ በአሜሪካኖች ቁጥጥር እጅ አስገብቶ የምስራቅ አፍሪካ “የምጣኔ ሓብት፤ የባሕል ፤ የሞራል እና ያካባቢው ቀጠናዎች ጸጥታ” (ሄጂመኒው) በምዕራባውያን እጅ እንዲገባ ያመቻቸው ዘንድ ኤርትራ እና ኢትዮጵያ “ሁለቱ አገሮች” የሰላም ዕርቅ እንዲያደርጉ እና በዚህ ቀጠና ውስጥ በቻይናውያን እና በሩሲያውያን ቅልጥም እየተደፈረች ያለቺው አሜሪካ ሃይሏን ለማጠናከር እንዲመቻት የወሰደቺው ዕቅድ መሆኑን የፖለቲካ ጠበብቶች ብዙዎች ይስማማሉ።
እንግዲህ እንደመግቢያ ይሆናችሁ ዘንድ ካሁን በፊት ያየነው “አብይ እና ኢሳያስ” በዚህ
ፍጥነት በሚገርም መተቃቀፍ ‘ለተመልካች እና ለሁለቱ ዜጎች’ የትዕይንቱ ክስተት ምስጢሩን ለመፍታት በሚያስችግር እንቆቁልሻዊ ሕልም
“ግን ተጨባጭ እውነታ” እንዴት ሊከሰት እንደቻለ ግልጽ በጨረፍታ እንይ።
ታዲያ እነ አብይ እንዴት መጡ የሚለው ጠያቂ ትንሽ ልበል።
አብይ የመጣው አሜሪካኖች ወይንም አረቦች አይደሉም ያመጡት የሚሉ ሰዎች ሊኖሩ ይችላሉ። ክርክራቸው እንደምገምተው ደግሞ ‘የሕዝባዊ አመጽ አልገዛም ባይነት ስለበረታባቸው ወያኔዎች ለውጥ ማድረግ ነበረባቸው እና ስለዚህም ተገድደው ጥገናዊ ለውጥ አደረጉ” የሚሉ ሊኖሩ ይችላሉ የሚል ግምት አለኝ። ክርክሩ ልክ ቢሆንም፤ አሜሪካኖቹም ሆኑ ዓረቦች ሊገቡብን የቻሉበት ምክንያት ሁሌም መርሳት የለባችሁም (የ1991 የለንደኑ ስምምነት እንዴት እንደገቡብን አትርሱ) ። ያው በ2018 (2010 ዓ.ም) እንዲሁ እንዴት እንደገቡ ያው የድግምግሞሹ ትዕንት ነው።
እንደሚታወቀው
ሃያላን መንግሥታት ቶኩላዎች
ናቸውና በቅጽበታዊ መንገድ ‘ዘው’ ብለው
ወደ አንድ አገር አይገቡም። ጣልቃ
ገብነታቸው የሚጀምረው በዝግምታ ነው። የቅኝ ሃይሎች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ለሚያደርጉት ጣልቃ ገብነት ወይንም “ጎበጣው/ሄጂመኒው” ለማሳካት አከናዋኝ
ወኪሎች መያዝ አለባቸው። ይህ ካደረጉ
በኋላ በወኪሎቻቸው በኩል የሚነድፉት
ዕቅድ መንገዱን ስታጤኑት ለማወቅ ቀላል ነው። ይኼውም ‘አድፍጠው ቆይተው አመች ሁኔታ ሲመቻችላቸው ያኔ ዘልለው
በመግባት የሚታወቁበት ስልታቸው ነው።
ኢትዮጵያ በለውጥ ማዕበል ስትናጥ አንድ ስርዓት ወደ መነቃነቁ ሲቃረብ ሌላ ሃይል ወደ ስልጣን ስያነፈንፍ
ሲያዩ ያኔ (“policy shift has been outlined in the 2018 National Defence…. የሚለው ስተመለከቱ)
“ለመቆጣጠር እያቀዱት ለነበረው የ2018 የምስራቅ አፍሪቃ እና የቀይ ባሕር ወሽመጥ “ስትራቴጂአዊ የቀጠና ፖሊሲ” ለውጥ ለማድረግ
አመች አጋጣሚ ስለመጣላቸው፤ በሕዝብ ተቃውሞ እና አመጽ “ለመወደቅ እየተነቃነቁ” ለነበሩት ሁለቱም ስርዓቶች “አማራጭ ስልት” በመንደፍ
ሕይወት ዘርተውላቸው እንዲድኑ
በማድረግ እግረ-መንገዳቸው
ፖሊሲያቸውን አሳክተዋል።
ታስታውሱ እንደሆን (ለብዙ አመት የኔን ጽሑፍ ስትከታተሉ የነበራችሁ ሁሉ ከላይ የለጠፍኩዋቸው ፎቶዎች የ1983ቱ ሴራ ፥ እና በምርጫ 97 ምን ሲያደርጉ እንደነበር በርካታ ጽሑፎች እንደጻፍኩ ታስታውሳላችሁ)
ይም ሆኖ ስልቱም አሁን አብይ እና ኢሳያስ የአሜሪካኖች እና የዓረቦች “መወጣጫ መሰላል” ሆነው በመገኘታቸው በሁለቱ ስርዓቶች አነጣጥሮ የነበረው “መጎደኛ አመጽ” ባስገራሚ ረቂቀ ስልት እንዲኮላሽ ሆነ። አሁን ደግሞ እነዚሁ የመለመልዋቸው አግሮች «ጽመዶ>> fifth columnists" (Proxy Actors),Subversives,Agents of Influence የፈለጋችሁን መገለጫ ጨምሩበት) በትግርኛው ጥሬ ትርጉሙ ብዙ ትርጉሞች አሉት (ከታች እገለጸዋለሁ) ፡ «ነባሮች እና አዳዲስ ብቅ ያሉ የታጠቁ የውስጥ አከናዋኝ ወኪሎቻቸው ወደ ጨዋታው በማስገባት “ኢሳያስ (ኤርትራ) ፥ ግብፅ ፥ ሱዳን አብደል ፋታሕ አል ቡርሃን (SAF) እና RSF ታጣቂዎችን የሚመራው ሞሐመድ ሓምዳን ዳጋሎ (ሐመድቲ)፥ ወያነ ፥ ፋኖ ፥ ጉምዝ ታጣቂ፥ አገው/ቅማንት/ ፥ አብይ አሕመድ (ኦነግ ፥ ሸኔ፥ በአብይ እና በሚስቱ የተደራጁ ፕሮተስታንት ፓስተሮች...፥ የክርስትያን እና የአማራ አንገት በቢላዋ የሚያርደው “ውሃቢያው እስላም እና ኦነግ”...) በግዝገዛው ትወና እየተቃኙ ናቸው።
«ጽምዶ» ---(1) ለእርሻ የሚጠመዱ በሬዎች በሞፍርና ቀምበር ታስረው የሚታዩበት “ክንዋኔ” ነው ፤ (2)ተልዕኮውን ለማከናወን ብቻውን የማይችል ሁለተኛ ሃይል የሚፈልግ (3)አብረው የሚሄዱ ግን በራሳቸው ሳይሆን በአንድ ጌታ (External) የሚጠመዱና የሚነዱ”(4) ተመሳሳይነት ያላቸው (ተጠማጆች) ፤ ለምሳሌ አንድ የእግር ካልሲ ቢጠፋህ የዚህ ካልሲ (የእግር ሹራብ) መጣመጃው/ተጠማጁ የት አለ? ብለህ ትጠይቃለህ? ፥ በትግርኛው«ኣነን ንስኻን መጻምድቲ ኣይኮንናን» ካለ እኔ አንተ አብሮነት (ለጋብቻም ሊሆን ይችላል) የሚያጣጥመን፤ የሚያገናኘን ምንም ነገር) የለንም ማለት ነው።(5) ትግርኛው ስለምንታይ “ጸሚድካ” ሒዝካኒ ካለ ፥ አምርኛው “ለምን ጠምደህ ያዝከኝ?” «ለምን በጠላትነት ዓይን ዓየኸኝ » ማለት ነው። (ማጥበቅ ፥ማቆራኘት ማለት ነው)። (6) ትግርኛው “መጻመዲ!!” ብሎ ቁጣ በተሞላ ሃይለ ቃል ከጠራህ “እሳት ጫሪ/ሰው ለሰው የሚያጋጭ፥ ጸብ አቀጣጣይ” ወይንም «አቃጣሪ» ማለት ነው። ይህን ካየን ወደ ሴራው እንቀጥል።
ሴራ አንድ!
በምርጫ 97 አሜሪካኖች እና እንግሊዞች አምባሳደሮች እና የመረጃ ወኪሎቻቸውን በስፋት እጃቸውን በማስገባት ግልጽ የሆነ ጣልቃ ገብነት በመተወን “ለምስራቅ አፍሪቃ የጸረ-ሽብር ጦርነት እንዲረዳቸው ሲጠቀሙበት ለነበረው የወያኔ ስርዓት ድጋፍ በመስጠት በግልጽ ጣልቃ በመግባት ሲፈጸም የነበረው ሰብአዊ ጥሰትና ጭፍጫፋ አይተው እንዳላዩ በመሆን ስርዓቱ ሥልጣን ላይ እንዲቆይ አድርገዋል። ሆኖም አመጹ ከመቸውም ጊዜ በበለጠ ስለተምቦገቦገ” አሜሪካኖቹ የሕዝቡ መነሳሳት በውስጥም በውጭም እጅግ የጋለ መሆኑን እና ወሳኝ ምዕራፍ መድረሱን ስለተረዱ፡ ወኪላቸው (ወያነ) ተዋርዶ ከሥልጣን ከመሰናበቱ በፊት “አገልጋያቸውን” ማዳን ስለነበረባቸው አዲስ ስልት ቀየሱ።
አዲሱ ስልት ሊቀይሱት የተነሱበት ዋነኛው የራሳቸው ንድፍ እንዳለ ሆኖ በአንዳንድ ቦታዎች የስርዓቱ ታጣቂዎች እና አስተዳደራዊ መዋቅሮች ፈርሰው “በአመጹት የአካባቢ ኗሪዎችና ወጣቶች ቁጥጥር ስር እና መተዳደር ሲጀምር፡ አሜሪካኖቹ በአስገራሚ ስልት ‘የዲፕሎማሲ’ ወኪላቸውን “አምባሳደር ያማሜቶን” ወደ ኤርትራ እና ኢትዮጵያ ልከው የነበረው ተቃውሞ አከሸፉት (ይህንን ታስታውሱ ይሆናል) ። አብይ የተባለ በብዙ ዜጎች ዘንድ የማይታወቅ “አስመሳይ ሰባኪ” ወደ መድረኩ ብቅ እንዲል በማድረግ ‘ከውስጥ ተጫዋች ቡድኖችን በማደራጀት’ «አዲስ ሰው እና አዲስ መንፈስ» (ከፉ መንፈስ የተጠናወተው ሴረኛና ቅጥረኛ ሰው” ወደ መሪነት መድረክ እንዲወጣ ተደረገ።
ፓራያ (የተገለለ) መንግሥት ተብሎ በዓለም እና ባብዛኛ ኤርትራኖች ተወግዞ የሞቱ ምጽአት መቃረብ ሲጠባበቁ እና ሲመኙለት የነበረው የሻዕቢያው መሪ ኢሳያስ አፈወርቂንም ከአብይ ጋር እንዲወዳጁ በማድረግ አዲስ እንቆቁልሻዊ ግን እውነታዊ ክሰተት ኤርትራ ውስጥም እንዲከሰት በማድረግ ‘ዲያብሎሳዊው ኢሳያስ’ ወደ መልአካዊነት በመለወጥ “ስቀሉት! ስቀሉት!” እየተባለ ሲወገዝ የነበረው የብዙ ሺሕ ሕዝብ ደም በእጁ የሚጮኸው “ኢሱ! ኢሱ!” ተብሎ በሕዝብ (by the infected mindless "Zombie Society") እየተሳመ እና እየታቀፈ ‘የሰላም ተምሳሌት አስመስለው በመሳል ወደ እየሱስነት” አስለውጠው ፥ ‘ሲቃወሙት የነበሩት ኤርትራኖች (ብያንስ ኤርትራ ውስጥ ያለ ሕዝብ) እንዲወዱት ተደረገ።ነፋስ ወደ ነፈሰበት የመንፈስ ባህሪ ያለው ጅላጅሉ ኢትዮጵያዊ ዜጋም ከመቃብር ተቆፍሮ የወጣው ኢሳያስን እየዘለለ መሳም እና መስገድ ጀመረ። አሁን ‘ዲያብሎሳዊው ኢሳያስ’ ተመልሶ በጽምዶነት ወደ ጠላትነቱ እንዲህ ሊመለስ።
ሴራ ሁለት! - ከዚያም ሕዝብ የማያውቀው ‘አብይ አሕመድ’ “መደመር” በሚባል ደብተራዎች ያልተማሩት አዲስ “አፍዝ ወ አደንዝዝ” ፍለስፍና በማስራጨት የተማረውን እና ያልተማረውን “ዞሚቢው” ኢትዮጵያዊ ወደ ዕብድነት በመለወጥ ዘፋኝ እና ምሁር ሳይቀር ሕሊናቸውን ሰልቦ እግር ጫማው ሥር ወድቀው እስኪሳለሙት ድረስ በመስበክ ባስገራሚ ሰበካ እግሩ ስር ተነጠፉለት።
ሴራ ሦሰት!፦ ወደ መጀምሪያው የሴራው ጉዞ ልወስዳችሁ ነው።
ይህኛው የዋና ዋና ሴራዎቸቻቸው ዋነኛው ግብ ነው። የተነሳውን ሕዝባዊ አመጽ ማኮላሸት!
እንዴት ተኮላሸ? ከኔ ጀምሮ ማንም ሃቀኛ ኢትዮጵያዊ ዜጋ “ሲነገሩ በጆሮው ሊሰማቸው” የሚፈልጋቸው እና “በአፉ-እንደ ድግምት ጸሎት ሊደግማቸው” የሚፈልጋቸውን “ኢትዮጵያ እና እግዚአብሔር” የሚባሉ ቃላቶች ለ27 አመት በኦሮሞዎች እና በትግሬ ፖለቲከኞች “መራራ ጥቃት” ተሰንዝሮባቸው ስለነበር፤ ሰልጥኖ እና በስልት ወደ ሥልጣን የመጣው አብይ አሕመድ እነዚህ ቃላቶች ወደ ነበሩበት ‘ክብረ ልዕልናቸው’ እንዲጎናጸፉ መስሕብ አድርጎ በመጠቀሙ፤ በመጀምሪያ የፓርላማ ንግግሩ የሁላችን የድጋፍ አግራሞት አገኘ። ሲናወጥ የነበረው የሕዝብ ተቃውሞ ረገብ እንዲል ’መንገዱን እኔ ላሳያችሁ’ በማለት ወያኔ ላደረገው ወንጀል ይቅርታ በመጠየቅ እስረኞችን መፍታት ጀመረ።
ከዚያ በኋላ ታላቁ ሴራ በረቂቁ ቀስ እያለ መጓዝ ጀመረ። ወደ መቀሌ ሄዶ መለስ ዜናዊን ጀግና ማለት ሲጀምር፤ ከኤርትራ ወንበዴዎች ጋር ሆነው ኤርትራ ምድር እና ምጽዋ ወደብ ድረስ ሄደው የኢትዮጵያን ልጆች በጥይት ቆልተው የባሕር ወደቦቻችንን ያስዘጉብንን በአገር ክሕደት ወንጀል መጠየቅ የሚገባቸው የትግራይ ታጋዮችን “የዲሞክራሲ ታጋዮች” እና ‘ወርቆች፤ ጀግኖች’ ማለት ጀመረ።
ከመቀሌ ወደ ባሕር ዳር በሄደበት የመጀመሪያ ከአማራው ሕዝብ ጋር ባደረገው ትውውቁ ደግሞ የአማራዎቹ አቤቱታ ማሳነስ ጀመረ። «በላያችን ላይ ሽንት እየተሸናብን “ሽንታም አማራ” እየተባልን ፤ በዜግነታችን ከተወልደንበት ምድር እንድንባረር እና ወደ ገደል ከነ ነብሳችን እንድንገፈተር ተደርጛል፤ በሚሊዮኖች አማራዎች ከምድረ ገጽ ተሰውረዋል፤ በአማራ ነገድነታችን በጥቃት ኢላማ ገብተናል! ይህ ተሎ ይቁም! » ብለው ባሕር ዳር ውስጥ መጥቶ ሲጎበኛቸው “አቤት” ላሉ አማራ ማሕበረሰብ ምሁራን እና ቀሳውስት “የተጨቆናችሁ እናንተ ብቻ አይደላችሁም” አማራ ብቻ ተለይቶ አልተጨቆነም! ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ስትሉ ቆይታችሁ እንደገና ተመልሳችሁ “አማራ አማራ” ወደ እሚለው ትሄዱ እና ታበላሹታላችሁ…” በማለት የአማራዎች አቤቱታ ሲያናንቅ አድምጠን እኔም ሆንኩ ሌሎች ባጭር ጊዜ ውስጥ የሰውየው “የአማራ ጥቃት የሚያይበት መነጽሩ የተበላሸ መሆኑን” በመንቃታችን (የመጀመሪ ተቺው እኔ ነበርኩ) የነበረው መጠነኛ ድጋፋችንን ከነጭራሹኑ አቆምን።
ጥቂቶቻችን ስጋታችን ማስተጋባት ቀጠልን። የተቀረው መሃል ሰፍሮ የነበረው ወደ አብይ ድጋፍ በመግባት ተጠራርጎ ደጋፊ ሆነ።ከዚያም ቀስ እያለ ሕዝቡን በሚያደነዝዙ ቃላቶች ተጠቅሞ የተማሩትን ማጃጃል ያዘ። የተቃዋሚ ፖለቲካ መሪዎች እና ታቃወቂ ምሁራን ሁሉም ጥርግርግ ብለው የአብይ ጠበቆች ሆኑ። የታጠቁት እና ያልታጠቁት የፖለቲካ ቆሻሻዎች ከነ ጋዜጠኞቻቸው ጥርግርግ ብለው የአብይ መናፍህ ሆኑ።
የትጥቅ ትግል “ዘመኑ ያለፈበት ነው” ብሎ ሲሰብካቸው የነገራቸውን አምነው ተቀበሉት። ቆሻሻ ፖለቲከኞች እና ጋዜጠኞቻቸውም ‘ሰላማዊ ሰልፍ’ ማድረግ እና ማስነሳት ከነጭራሹ “ረሱት እና ሰለማዊ ሰልፍ ባደረጉ የተጨቆኑ ወጣት ወታደሮች ላይ ውግዘት እና ውርጅብኝ ማውረድ ጀመሩ” ።
ብከላው በዚህ መልክ በመቀጠል፦ በውጭ ሃይላት የተሳለው “አገር ወዳድ” መሪ ተብየው “ማንም ሰው የፈለገው ባንዴራ (የካሊፌት/ሸሪዓ/ ወይንም አልሸባብ..ወይንም የግንጠላ/አገር አፍራሽ/ ባንዴራ ወይንም የግብረሰዶም ባንዴራ…የፈለገው ባንዴራ ማውብለብ እና መስበክ ይችላል በሚል የስርዐተ አልባ ስብከት በመስበኩ ምክንያት ሁሉም የፈለገውን ባንዴራ በማውለብለብ ጸረ ኢትዮጵያ ሰንደቃላማ እና ኢትዮጵያዊ ሰንደቃላማ በሚያውለበልቡ መካካል ‘ትንቅንቅ” ተጀመረ።
ተቃዋሚ እና ምሁር ተብየ “ተደማሪ” የፈለገው ሰው ማንም ባንዴራ ማውለብለብ መብቱ ነው በማለት ‘ለዘመናት የተውለበለበ አርማችንን በጠላትነት ከሚፈርጁዋት ቡድኖች ጋር ሆነው ‘አገራዊ ሰንደቃላማን” ከዲሞክራሲ ጋር እያቆራኙ ሰንደቃላማን መለወጥ እና መጻረር ‘መብቱ ነው’ በማለት “በብከላው ዘመቻ አጠናካሪዎች እና ደጋፊዎች ሆኑ (በሌላ መልኩ የባንዳዎቹ የመለስ ዜናዊ እና የነ ሌንጮ ፖለቲካ አስተጋቢዎች እና ተምበርካኪዎች ሆኑ)።
” የነፈዘው የዩቱብ ጋዜጠኛ ተብየውም ትግሉን በማቀዝቀዝ “ከፍቅር ለፍቅር” ምናምን የሚል ፖለቲካ ዩ ቱብ ቴ/ቪዥን ጣቢያው ላይ በማስተጋባት የሕዝቡን የፍትሕ ጥያቄ እንዲኮላሽ ‘ራሱን የቻለ አፍዝ ወ አደንዝዝ’ ሚናውን መጫወት ያዘ።
በየከተማው ግድያው እና ጥላቸው እንዲሁም መፈናቀሉ በሚገርም
ሁኔታ ተጧጧፈ። ሰውን በጠራራ ጸሐይ አደባባይ ላይ ገድሎ መስቀል ተጀመረ። በዓለም ውስጥ በሕዝብ መፈናቀል አንደኛ ኢትዮጵያ ነች
ተባለ። ያ ሁሉ ሲሆን ታጣቂዎቹም የኮንትሮባንድ መሳሪያዎች በየከተማው በማስገባት እንደ ባንዴራ አውለብላቢዎች እነሱም ልቅ ስለተለቀቁ ውድመቱ የት እና የት የሌለ ሆነ። መንግሥት
ነኝ የሚለው የስርዓተ አልባው የፋሺስቶች ጥምረት አገሪቱ ከድጡ ወደማጡ እየመራት መጣ።
ለ27 አመት በሕዝብ ህይወት እሳት በመለኮስ ዜጎች በሲኦላዊ ሕይወት እንዲያልፉ ሚና የነበራቸው የወያኔ ወንጀለኛ ባለሠልጣኖች እና ተባባሪ አገልጋዮቻቸው አሁንም ከሹመት ወደ ሹመት እያደጉ እና “አገር ወዳድ እየተባሉ” እየተሞገሱ “ተከብረው” እያየናቸው ሲሆን ፤በጡረታ ኑሩ የተባሉትም ከመዘበሩት ሃብታቸው በምቾት ተንደላቅቀው እየኖሩ ናቸው። “የመደመር ታላቁ ሴራ” በስልት እየተጓዘ በርካታ ሃይሎች “መንግሥትህ እኔ እና እገሌ ነን” የሚል ንግግር ለሕዝቡ በማስደመጥ ሕዝቡ ለማን እንደሚታዘዝ ግራ ገብቶት “መሪያችንን በውል አስታውቁን” ወደ ማለት ጥያቄ ገባ።
አሁን ኢትዮጵያ ስንት መንግሥት እንዳላት በበኩሌ አላውቅም። አንዳንዶቹ እኔ እና እገሌ ነን ሲሉ ሌሎቹም ከሁለት በላይ ሦስት ከዚያም አራት ናቸው የሚሉ አሉ። ማንነታቸው ያልታወቁ ኦሮሞ ነን የሚሉ ታጣቂዎችም በሚቆጣጠሩዋቸው ቦታዎች የራሳቸው አስተዳዳሪዎች እና ፖሊሶች መሾም እንደ ጀመሩ ተነግሯል። በየክልሉ ያሉትን ቁጫጭ መንግሥታትም እንዲሁ የየክልላቸው ታጣቂዎች እና ሹሞኞች ያለ ሕዝባዊ ድምጽ እና ሌላ ነገድ የማይጨምር ሹመት በመሾም የነበረው ዘረኛ እና ነገዳዊ ስርዓት እንዲቀጥል አዲስ ትንፋሽ እየሰጡት ነው። አንዳንሱም የኦሮሙማው አብይ ፈቃድ እና ዕውቅና ሰላለበት ቀስ እያልን ከመገረም ወደ መርመም ተሸጋግረናል።
በአብይ አሕመድ «መደመር» ስንገረም የታጠቁት አዳዲስ ተቃዋሚዎች ደግሞ ያንን ቡቱቶ ፖለቲካ ገልብጠው «ጽመዶ» የሚል የትግል ስልት የመቀበላቸው ዜና ካንደበታቸው ስንሰማ ከቆሸሹት ነባር ታጣቂዎች ጋር በመደመር የሕዝቡን መሰረታዊ አብየቱታ በማኮላሸቱ ሂደት እየተጫወቱት ያለውን ሚና በቀላል መታየት የለበትም። ማይክል ፓረንቲ የተባለ የፋሺዝም ተመራማሪ አሜሪካዊ ምሁር “ደርቲ ትሩዝ” (ቆሻሻው እውነታ) የሚለው አይነት የቆሻሻው እውነታ “ክስተት” እያየን ነው። የትግራይ ወጣት በዶላር ለሱዳኖች የውትድርና አገልግሎት እየሸጣቸው ስላለው ወያነ መናገሩ ፀሐይ ለሞቀው ዜና እና በባንዳነቱ ስለታወቀው «የውጭ አገሮች ፈረስ» ሰለ ሆነው «ትሕነግ» መናገር ስለሰለቸን ተክድኖ ይቆይ።
እኔን የገረመኝ ፋኖ የተባለው ታጣቂ ነው። የአማራን ሕዝብ የፈጁት አብይ ኦሮሙማ/ኦነግ/ ፥ ወያነ/ትሕነግ/ ፥ ኢሳያስ/ ሻዕቢያ/ ወዘተ... መሆናቸውን ረስቶ በነዚህ ጠላቶች ሞፈር ቀንበር «ተጠምዶ» እነዚህን ለመምታት የሚመጣ ማንኛውንም ታጣቂ መጀምሪያ እኔን ገድሎ ነው እንጂ ፥ወያኔን እና ሻዕቢያን መግጠም ያለበት የአማራን ታጣቂ ወጣት አስፈጅቼ እንጂ አያልፋትም! እያለ በሚዲያ ያወጀ ፣ «እርቃኑ የወጣ የባንዳ ቡድን» አማራን ነፃ አወጣለሁ ማለቱ ካለፈው የማይማር ታጣቂ ቡድን መፈጠሩ እጅግ ይገርመኛል።
የሚገርመው ይህንን እርቃኑ የወጣ የባንዳዎች አዋጅ በባንዳነት ዜና የመስራት ትምሕርት ከነ መሳይ መኮንን የቀሰሙ የፋኖ ሚዲያዎች ይህንን ደግፈው ሲያሽሞነሙኑት መስማትም ከግርምት በላይ ነው።
የግንቦት 7 ቱልቱላው መሳይ መኮንን (በኋላ የአብይ ቱልቱላ ፥ ዛሬ ደግሞ የፋኖ ቱልቱላ ሁነኛ ሚዲያ) አሥመራ ድረስ ሄዶ ምነ ሲል እንደነበር ድሮ ለልተከታተላችሁኝ እንሆ እንዲህ ይል ነበር፡
«ዳዊት የተባለው የሻዕቢያ ሻለቃ ጎምበስ ብሎ ሙቅ ውሃ አዘጋጅቶ እግሬን ሊያጥበኝ ሞክሮ ነበር፤እንደዚህ የመሳሰሉ የዋሃን ሻዕቢያዎን “በነብሰ ገዳይነትና ገራፊነት” የሚስሏዋቸው ውጭ አገር ያሉ ሰይጣን ተቃዋሚዎች እንጂ ኤርትራኖቹ መላእክት ናቸው፤ዘፈናቸው፥ከተማዎቻቸው፤ የፊያሜታ ሽሩባዎች፤ የጥርሳቸው፤የአቀባበላቸው በየግድግዳው የተለጠፉት ባንዴራዎች ማማር፤ ሰርጋቸው፤ የአማርኛ እስክስታቸው፤“ውይ ስያምር!” አስምራን ለማይት ሙሉ ሕይወቴ ስመኝ ዛሬ ምኞቴ ተሳካልኝ አብየት ደስ ስትል! መሪውም ሕዝቡም» እያሉ በቪዲዮ “ኢሳያስን መልአክ፤ ጣሊያን የገነባቸው ሕንጻዎችዋ ያዘመሙ እና የፈራረሱ፥ ቀለሞቸዋ የተላላጡ «ከሃቫና ኪዩባ» የባሰባት አስመራ ከተማ እያወዳደሰ የባንዳነት ፖለቲካ ሲሰራብን ነበር።
ከወያነ እና ከሻዕቢያ ሞት በፊት የአማራ ሞት ይቅደም እያለ ያሉት የፋኖ ባንዳዎች የተጠመዱት ጸረ አማራ እና ጸረ ኢትዮጵያ ሃይላት ጋር ነው። ፋኖ አቅም የለውምና ተጠማጅ እንጂ አጥማጅ አይደለም። አሳዛኙ ክስተት ይህ ነው።አቅም የሌለው በሬ የሚፈታው እና የሚጠመደው አቅም ባለው “ውጫዊ” (ጌታ) ነው።
ፋኖ ለሻዕቢያ ስል እወድቃለሁ ሲል ፣መጠመዱን ሲያውጅ የባንዳዎች ደወል መስማት ለጆሮአችን አዲስ አይደለም። ከፋኖ በፊት አንዳርጋቸው ጽጌ ፥ ብርሃኑ ነጋ፤ ንአምን ዘለቀ አፍሬም ማዴቦ ፣ መሐመድ አሕመድ ውዝተ... ለሻዕቢያ ጥብቅና ሲቆሙ አይተናል። በመላው አለም እና በተባበሩት አወሮጳ እና በተባበሩት መንግሥታት የሰባዊ መብት ጉዳይ ሕንጻዎች ፊት ቆመው ጸጉራቸውን በሓዘን መልክ ተላጭተው፤ ወጣት ሴቶችም የሐዘን ጥቁር ልብስ ለብሰው፤ ወጣት ሴቶች ቀይ ቀለም የተቀባ እንባ በመቀባት፣ ቀሳውስትና ዲያቆናት እንዲሁም የክርስትና እና እስልምና ተከታይ ምዕመናኖች ሁሉ ሰላማዊ ሰልፍ በመውጣት ኢሳያስ ለፍርድ ይቅረብ ብለው ኤርትራዊያን የወጡበት ሰላማዊ ሰልፍ ፣ በሚያሳፍር ታሪክ ግን በንአምን ዘልቀ የተመራ ግንቦት7 ለኢሳያስ አፈወርቅ ድጋፍ በመስጠት ፌርማ ያሰባሰቡ ኢትዮጵያዊያን ከኤርትራዊያን ሰለፈኞቹ ጋር ሲጣሉ አይተናል።
ነፃ አውጪዎቻችን ናቸው ብለው ወገባቸውን ዳግም ለውርደት ያለጠለጡ
አሳፋሪ ምሁራን ተብየዎች ግንቦት
7ን ሲደግፉ አይተናል።
ሆኖም የጊዜ ጉዳይ እንጂ በለመዱት የማለቅለቅ ባሕሪ መጓዛቸው እንደማይቀር የተነበይን ሰዎች በወቅቱ በንሰደም እንዳልነውም ፤ ዛሬ ትንቢታችን እውን ሆኖ እያየን ነው።
ዛሬ ደግሞ ፋኖ ጽምዶ በሚባል የብታችነትን የሚያጋልጥ አገርን እና ሕዝብን ለውርደት የሚሰጥ የባንዳ ጥመረት በመቀበሉን በተፈራ ማሞ እና በአስረስ ማረ ዳምጤ ምላስ አድምጠናል። የትግርኛው ምሳሌ እንደነገረን “ደርሆ ጻሕቲራ ጻሕቲራ መሕረዲኣ ኣውጸአት ካራ” (ዶሮ፤ ቧጭራ ቧጭራ፤ አወጣች ከምድር ማረጃዋ ካራ!)። ግንቦት 7 ዘልሎ፤ ዘልሎ መጨረሻ ትክክለኛውን ስፍራውና ስሙን አግኝቶ አይተናል፤ፋኖ ደግሞ የህጻናትን እምባ በደም ያስለቀሰ፤ ብዙ ሕዝብ የፈጀ፤ በጀንሳይድ እና በጦር ወንጀለኛነት የተከሰሰ አረመኔው “የሳሕል ጅብ” ኢሳያስ አፈወርቅን እና ወያኔን አምኖ መጠመድ ቀደም ብሎ የተፈጸሙ ስሕተቶች እና ማስጠንቀቂያዎች ሳይማሩ ያንን ለመድገም ለአማራ ሕዝብ “እሸሸ ገዳሆ!” ከነዚህ ጠላቶች ጋር እንዲጨፍርና ከነሱ ሞት በፊት እንዲሞትላቸው ጥሪ እያደረጉለት ነው።
ቆሻሻ እውነታ ደግሞ ስንመለከት «ከአብይ በላይ ጠላት የለንም» በማለት እየታየ ካለው ቆሻሻው እውነታ እራሳቸውን በማዋሃድ የተወረወለላቸውን ትንሽዋን ቁራሽ በማመስገን ብዙሃኑ ወደ ትልቁ ግብ አሻግረው እንዳይጠይቁ ሞራላቸው/መንፈሳቸው/ ያደቁታል። አብይም ይሁን ወያኔ እና ኢሳያስ ለአማራ ሕዝብ እና ታሪክ ካንዱ ጀብ ሌላ አይሻልም።ጅቦች ሁሉ እኩል ናቸው።
በሚገርም ግለታዊ መንፈስ ሲራመድ የነበረው ወጣት በፋኖ የአምራር ውድቀት “ዶርማንት ስታተስ” (የፈዘዘ፤የተጃጃለ) ወጣት እንዲሆን ወያኔ እና ኢሳያስ ወደ በጹእነት እርከን እንዲታይ ግፊት አድርገዋል።
እነዚህ “ዛሬ ከማንኛወም ጊዜ የበለጠ ያልታየ የጋራ ትግል እናደርጋለን የሚሉ ጅሎች” በተገንጣይ ፖለቲከኞች መዳፍ ገብቶ” ለውትግራይ፥ለአገው፣ ለጉሙዝ ፥ለኦሮሞ ፣ሪፑብሊክ ምስረታ የተዘጋጀላቸው ባንዴራ አብረን እናውለብልብ ይልዋቸው ቀን ምን ሊውጣቸው ነው? እንዚህ ድርጅቶች ዋና ጠላታችወ አማራ ነው። ትግላቸው ጸረ ኢትዮጵያ ያነገተ ሴራ ነው። ሰልሆነም ፋኖ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚል ከሆነ (ከሆነ ማለት ነው!!!) ከጠላት ጋር መደመር አይቻልም።“ታላቁ የመደመር ሴራ” እና “ታላቁ የጽምዶ ሴራ” መንትያዎች ናቸው።
ለሰንደቃላማችን እስከመጨረሻ ድረስ ቆመናል እያሉ ሲዋሹን የነበሩት የግንቦት 7 ቆሻሻዎች ባየንበት ክሕደት አሁን ደግሞ ወያነ እና ኢሳያስ ከሚሞቱ ከናንተ በፊት እኛ አማራዎች እንሙትላችሁ የሚሉ ፋኖዎች መስማት ኢትዮጵያን ከፋሺስቶች ነፃ ማስወጣት ቀርቶ የመነሻ ሚናቸውን ስተው “ትግሉን በማቀዝቀዝ “የታላቁ ሴራ” ተዋናይ አባሎች ሆነዋል። «ጽምዶ»(Proxy Actors) የአዲሶቹ እና የነባሮቹ የአምስተኛ ረድፎች መጫወቻ ሜዳ!
ሰላም እንሰንብት
ጌታቸው ረዳ (Ethiopian Semay)