Monday, November 26, 2012

አዲስ መጽሐፍ-ደቂቀ ተወልደመድኅን

አዲስ መጽሐፍ
ደቂቀ ተወልደመድኅን
ደራሲ
ጌታቸው ረዳ
(ህዳር 2004 ዓ.ም)
ዋጋ $20.00
P.O.Box 2219
San Jose, CA
95109
(408) 561-4836
ስለ መጽሐፉ ለማንበብ ከዚህ ቀጥሎ ያለውን ጽሑፍ ይመልከቱ።
 
ይህ ታሪክ በአገር ውስጥ ደራሲ ሲታተም የመጀመሪያ መጽሐፍ ነው። ያልተጻፉ ብዙዎቹ ታሪኮቻችንን አፈላልገን አሁን ላለው ሕዝብ እና ለተተኪው ትውልድ በሃሰት ሳይሆን ታሪኩን በእውነት ዘግቦ ታሪኩን እንዲገነዘብ ማድረግ አገራቸውን በሚያፈቅሩ ዜጎች መከናወን ያለበት ከባድ የሕሊና ግዴታ እና ሸክም ነው።
ታሪክ ማለት በአመዛኝ መልኩ በሁለት ጎራዎች በተከፈሉ ተቃራኒ እይታዎች የተከናወኑ የማሕበረሰቡ ህይወት የሚያትት ዘገባ ነው።ደቂቀ ተወልደመድኅን ብየ የሰየምኩት ይህ መጽሐፍ የሚያትተው፤በጥንቱ ዘመን ትግራይ ውስጥ በዓድዋው ተወላጅ በአለቃ ተወልደመድኅን ገብሩ እና በአክሱም ተወላጅ በአለቃ ጐበዜ ጐሹ የተመራው የኢቫንጀሊካል(ፕሮተስታንት/ከኒሻ)ሃይማኖት እንቅስቃሴ ከአካባቢው የኦርቶዶክስ ሃይማኖት መሪዎች፤ አማኞችና የአካባቢው ተወላጅ በነበሩት አስተዳዳሪዎች መሃል የታየው የእምነት “ፍጭት” በጥልቅ የሚያትት ነው። በፍጭቱ ሂደት የተወሰዱ የጭካኔ እርምጃዎች ዘግናኝ የሆኑ የከፉ እርምጃዎች (ኤክስትሪም ሜዠር) ተወስደዋል።
የተጠቀሱት ሁለቱ መሪዎች ወደ ፕሮተስታንት እምነት ከመከነሻቸው በፊት ወላጆቻችውም ሆኑ እራሳቸው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት አማኞች እና በተዋህዶ ትምህርት የመጠቁ የተከበሩ ሊቃውንት ነበሩ። በአዲሱ እምነታቸው ምክንያት የገጠማቸው ተቃውሞ ላለመሸነፍ እስከመጨረሻ ተጋትረው በጽናት በመቆም በመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች ላይ እየተከራከሩ በርካታ ተከታዮች በማፍራታቸው አስተዳዳሪዎች፤ የሃይማኖት መሪዎችና መነኰሳት ከየገዳማቱ የተሰባሰበ ብርቱ ተቃውሞ ደርሶባቸው ለእስራት፤ለእርዛት፤ ለግርፋት፤ ለቤት እጦት፤ከማሕበረሰብ መገለል እና በመጨረሻም ለስደት ተዳርገዋል።
ይህ መጽሐፍ ለመጻፍ ያነሳሳኝ ምክንያት ህወሓት/ወያኔዎች ለአማራ እና ለአማርኛ ቋንቋ መረን የለቀቀ የጎሳ ጥላቻቸው በጐሰኝነት ጥማት የታመመው ልቦናቸውን ለማርካት ሲሉ፤በ14ኛው ክፍለዘመን የነገሠው የቤተክህነት ሊቅ በነበረው በገናናው ንጉሥ ዘርአ ያዕቆብ ላይ የጥላቻ መርዛቸውን በንጉሡ ታሪክ ላይ በመርጨት፤ የውሸት መጽሐፍ በመጻፍ፤ በእዛው ዘመን በነበሩት በታወቁት የትግራይ መነኩሴው በአባ እስጢፋኖስ እና ተከታዮቻቸው (ደቂቀ እስቲፋኖስ በመባል ይታወቃሉ) የተመራው ለየት ባለ ባልተለመደ መልኩ የተከሰተው የሃይማኖት ክርክር (እንቅስቃሴ) ምክንያት፤የትግራይ አበምኔቶች ተቃውሞአቸውን በጋለ ቁጣ በማሳየት ክርክሩ እየጦፈ ከቁጥጥር በላይ እየሆነ በመሄዱ በደቂቀ እስጢፋኖስ ላይ ሕግን ያልተከተለ የሃይል እርምጃ መውሰድ እንደጀመሩ ታሪኩን ከክቡር ፕሮፌሰር ጌታቸው ይሌ የተጻፈውን “ደቂቀ እስጢፋኖስ” መጽሐፍ ያነበባችሁ ዜጎች የምታስታውሱት ታሪክ ነው። በዚህ መልኩ ነገሩ እየጋለ ሲሄድ የትግራይ አበምኔቶቹ ለክርክሩ እልባት ለማስገኘት ይመቻቸው ዘንድ ጉዳዩን ወደ ቤተክህነቱ ሊቅ ወደ ንጉሥ ዘርአ ያዕቆብ ሥልጣን በላይ ንጉሡ ወደሚኖርበት ወደ ድብረብርሃን (ሸዋ) ድረስ በመውሰድ ክርከሩን አስቀጠሉት።
በክርክሩ ወቅት በንጉሡ እና በአባ እስጢፋኖስ መሃል መግባባት የነበረ ቢሆንም፤ ተቃዋሚዎቻቸው ንጉሡን ለማሳመን ብዙ ክሶች ደርድረው ለማሳበቅ በመጣር ባንዳንድ ጎዳዮች ላይ ያለመግባባት ተከስቶ፤ንጉሡ ከረር ያለ ቅጣት በመኖኩሴው በአባ እስጢፋኖስ ላይ በይኖ ቅጣቱ ተግባራዊ እንደሆነም የሚታወስ ነው። ያ ብይን በማስታወስ ነው ዛሬ ወያኔዎች በ14ኛው ክፍለዘመን የተፈጸመው ሃይማኖታዊ የአስተዳዳር ውሳኔ በጎሳ ፖለቲካ ተርጉሞው “አማራ” እያሉ የሚጠሩት ንጉሥ ዘርአ ያዕቆብ የትግሬ ጥላቻ ስለነበረው እንደ እነ አባ እስጢፋኖስ እና ተከታዮቻቸው የመሳሰሉ የትግራይ የሃይማኖት ፈላስፎች አብበው እንዳይወጡ በማሰብ በእንጭጩ እንዲቀጩ አድርጓል፡ በማለት ንጉሥ ዘርዓ ያዕቆብን በጸረ ትግሬነት ከስሰውታል።
በጣም የሚገርመው “የሸዋ አማራዎች” የትግሬ ጥላቻቸውን የጀመሩት በዛው በ14ኘው ክ/ዘመን ጀምሮ ነው በማለት አማራው እና ትግሬው በጠላትነት እንዲተያይ መርዛቸውን በመርጨት የጻፉትን የሃሰት መጽሐፋቸውን ከሸፈቱበት “ከደደቢት” ያመነጩት የፈጠራ “አተላ ታሪክ” መሆኑን የማሳይበት በመረጃ የምከራከርበት ሌላው መጽሐፌ ነው። እኔ በዚህ መጽሀፍ ያቀረብኩት የታሪክ ሰነድ ”ትግራይ ውስጥ” በ19ኛው ክ/ዘ መግቢያ ከላይ በተጠቀሱት ሁለት ሰዎች የተመራው ተመሳሳይ የሃይማኖት እንቅስቃሴ ተነስቶ በነበረበት ወቅት በወቅቱ የነበሩ የአካባቢው ተወላጅ የመንግሥት ባለሥልጣኖች አዲሱን የሃይማኖት ክርክር ባስነሱትና በመሩት በዓድዋው ተወላጅ በአለቃ ተወልደመድኅን ገብሩ፤በአክሱማዊው በአለቃ ጐበዜ ጐሹ እና ተከታዮቻቸው ላይ የተፈጸመው የ19 ክ/ዘመን ኢፍትሃዊ እና የግፍ ድርጊት በትግሬ ተወላጆች አስተዳዳሪዎችና ውሳኔ አስፈጻሚዎች የተከናወነ የእርስ በርስ ድርጊት ስለነበር፤“የትግሬዎች የውስጥ ገመና” ላለማጋለጠጥ ሲሉ፤ወያኔዎች ይህንን ታሪክ አውቀው በመደበቅ ‘እንደ ጥዋት ውሃ የነጡ ወርቆቹ የትግሬ ነገሥታት እና አስተዳዳሪዎች በሙሉ’ “የፍትሕ ሰዎች፤መብት አስከባሪዎች፤አገር ወዳዶች” የደቂቀ ምኒሊክ እና ደቂቀ ዛርአ ያዕቆብ አማራዎች ግን “አገር ሻጮች፤ከዳተኞች፤የዜጎች መብት ተጋፊዎች፤ ፍትሕ አልባዎች፤የትግራይ የጀግንነት እና ፍትሕ ታሪክ ዘራፊዎች…”  እያሉ አጉል ስለሚመጻደቁ ያንን ውስጥ ገበናቸውን ላለማስወጣት ሲሉ  እፊታቸው ላይ ተገትሮ እያዩት ያለውን በየቤታቸው የተደበቀው የቅርብ ጓዳቸውን ትተው በ14ኛው ክ/ዘመን ተፈጸመው በሺሕ ኪሎሜትር ርቀት ወደ እሚገኘው ደብረብርሃን / ወደ ሸዋ ክ/ሃገር/ አሻግረው በመመልከት የራሳቸውን የቅርብ ዘመን ጉድፍ እንዳላዩት ሆነው ሆን ብለው “ዓይናቸወን በጥቁር ጨርቅ ሸፍነው” የ19ኘውን ክ/ዘ ትልቁን የትግራይ የግፍ ተራራ አይተውት እንዳላዩት አጎንብሰው በጐሰኝነት ስሜት፤ዘልለውት በማለፍ  ወደ 14ኛው ክፍለዘመን ጉብ ብለው በወቅቱ የተፈጸመው ሃይማኖታዊ እና አስተዳዳራዊ ብይን ወደ ጐሳ ፖለቲካ የተረጐሙትን የወያኔዎችን ማለቂያ የሌለው የታሪክ ብረዛ እውነቱን ለሕሊና ፍርድ እንዲቀርብና የገዛ መልካቸውን በዚህ መጽሐፍ እንዲያዩበት ይረዳቸው ዘንድ የጻፍኩት የመጽሐፍ መስተዋታቸው ነው።
ለእናንተ የኢትዮጵያ እውነተኛ አገር ወዳዶች የሆናችሁ ሁሉ የማስተላልፈው መልእክት ቢኖር ‘መጽሐፉን በመግዛት’ ወያኔዎች የትግራይን አዲስ ትውልድ ለመመረዝ በብዛት እያሳታሙ የሚያሰራጯቸው በውሸት የታጀቡ ጎሰኛ መጽሕቶቻቸውን መቋቋም የሚቻለው ከወገንተኛነት የጸዱ ሚዛናዊ መጽሐፍቶችን እየገዛችሁ መጪው ትውልድ እንዳይሞኝ መከላከያ ሰነዶች እንዲኖረው ማድረግ ነው። ይህ ጐጠኛ ባሕሪያቸው ለመመርመር ይህ መጽሐፍ ስጽፍ የታዘብኩት ነገር ካለ፤ “በ 14ኛው ክ/ዘመን የተፈጸመውን ግፍ፤ በ19ኛው ክ/ዘመን የኖሩ አስተዳዳሪዎች እና ማሕበረሰቦች ሲደግሙት፤በ20ኛው ክ/ዘመን እየኖሩ ያሉት ወያኔዎች በ14ኛው እና በ19ኛው ክ/ዘመን  የተፈጸመውን ግፍ ሳይማሩበት ያንኑን ድርጊት እነሱም እንደገና ሲደግሙት ስመለከት፤ ከ14ኛው ክ/ዘመን ሕሊና መውጣት ያቃታቸው እነዚህ ትውልዶች በ14ኛው ክ/ዘመን የተፈጸመው ግፍና ስሕተት አንስተው የ14ኛው እና የ19ኛው ክ/ዘመን የነበሩትን መሪዎች ሊከስሱ እና ሊወቅሱ የሚችሉበት ሞራል ከየት እንዳገኙት ሳስበው “ድፍረታቸው” በጣም ይገርመኛል።”
ስለ መጽሐፍ ማንሳት ላልቀረ አንድ ነገር ልበል። ካሁን በፊት ያሳተምኳቸው መጽሐፍቶች ከወያኔ በላይ መጽሓፍቶቼ እንዳይሰራጩና ለሕዝብ እንዳይዳረሱ ብዙ ሴራዎች የጐነጐኑ ቀናተኛ ግለሰቦች እና በተቃዋሚነት የቆሙ የፖለቲካ መጻጉእ የድርጅት አባሎችና ድረገጾቻቸው እንደነበሩ ካሁን በፊት አስታውሼአችሁ እንደነበር የሚታወስ ነው። ሆኖም በጠንካራ አርቆ አሳቢ አገር ወዳድ ግለሰቦች ብርታት እና ትብብር መጽሐፍቶቼ ከሞላ ጎደል ተሰራጭተው ለትውልድ እንዲተላለፉ ያደረጉ ወጣቶች፤ ግለሰቦች እና ደምበኞች እጅግ የከበረ ኢትዮጵያዊ አክብሮት እና ምሳጋናዬን ለማስተላለፍ እወዳለሁ። ዛሬም በቁጥር እጅግ በጣም ጥቂት የሆኑ ቅጆች ያሰተምኩት ይህ መጽሐፍ ለትውልድ እንድታስተላልፉለት እንደገና በድጋሜ ጥሪዬን አቀርባለሁ።
“አንዲት ኢትዮጵያ” እንደቀድሞዋ ህያው ሆና የተነጠቁባትን ዳር ድንበሯን፤ሰንደቃላማዋን እና ክብሯን ከዋየኔ በፊት ለዘመናት ታፍራ እንደነበረቺው ለማስመለስ የወያኔ የውሸት ሰነዶች ከታሪክ መድረክ አሳፍረን የምናስወግደው በእውነት የተመረኰዘ ሰነድን በማቅረብ ትውልድን ማስተማር ስንችል ብቻ ነው። ከዚህ ወዲያ ለትውልድ የምናወርሰው የተከበረ ገድል ሊኖር አይችልም።
እኔ ጐሳዬ ትግሬ ነኝ። ለብዙ ጊዜ የነሱን ውሸት ለመጋራት ብዙ የማታለያ የምቾት መማለጃ ምልጃዎች አቅርበውልኛል።ጠንካራ ኢትዮጵያዊነቴ መበገር ስላልቻሉ፤ ተስፋ ብቆርጥ ብለው በዚህ ይደናገጥና ይተወን ይሆናል በማለት ትግሬነቴን ለመንጠቅ አጉል የሆኑ ብዙ የውሸትና ጐሰኛ ሙከራዎች እና ስድቦች ለብዙ አመታት በወያኔ ጀሌዎች ተሰንዝረውብኛል።የግብዝነታቸው ክምር መጠኑ ሲበዛ አንዳንዴ በጣም እያሳቀኝ መዝናኛ አደርጋቸዋለሁ።ውሸት እና የዘረኛ ዓላመውን ስላልተከተልክ ማንነትክን ለመንጠቅ ከሚሞክር ግለሰብ ወይንም ድርጅት የከፋ አራዊት በምድር ውስጥ ሊኖር አይችልም።በአራዊት ባሕሪያቸው ማንነቴን ለመጋፋት በተጋፉኝ ቁጥር እየቀያየሩ የሚለብሷቸው  የናዚዎችና የፋሺስት ካባቸው እራሳቸው በጫሩት እሳት ሳቃጥልላቸው እጅግ እረካለሁ።መዝናኛም አደርጋቸዋለሁ።ደስታየ ግላዊ ሳይሆን ሕዝባዊ ደስታ ነው። በነዚህ የታሪክ አተላዎች ምክንያት፤ አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ቆሽቱ  ያረረውን ያሀል አዲስ መጽሐፍ አሳትሜ ፋሺስታዊ ካባቸው ባቃጠልኩላቸው ቁጥር ዜጎች በጣም ሲደሰቱ ስመለከታቸው “ድካሜ እንደ ጉም ይበንናል” ደስታየ ወሰን የለውም። ወያኔን በታሪክ መድረክ መጋፈጥ ጠንካራ መንፈስ እና ቆራጥነት የሚጠይቅ ቢሆንም ‘የሕሊና እርካታ እና እፎይታ/ፕለዠር/ ነው’ የምለውም ለዚህ ነው።
እነኚህ አውሬዎች የሰው ሥጋ የለበሱ የአዳም እና የሄዋን ቋንቋ የሚናገሩ “ያልተገሩ አራዊቶች” ትግሬነቴን ለመንጠቅ በሚያደርጉት የአራዊት ባሕሪያቸው ምክንያት ጓዳቸው እያስፈተሹ መሆናቸውን መገንዘብ አቅቷቸዋል። ዛሬ ወያኔም ሆነ ማንኛውንም ጎሰኛ በፈጣሪ ሥልጣን ውስጥ ገብቶ የዘር የደምና የአጥንት ጥራትና ቆጠራ ውስጥ የሚፈተፍት መስፍናዊ አውሬ ካለ የትግሬን ጎሳ አመሰራረት ታሪክ ወይንም የኢትዮጵያን ህብረተሰብ የደም ትስስር አያውቅም ማለት ነው።ሌላ ቀርቶ ከአውሬነት ሕሊና መውጣት አቅቶት አገርን ያክል ለባዕዳኖች ሲያስረክብ ከነበረው  ‘ከመለስ ዜናዊ’ አስገራሚ የህይወት ቅስፈትና የፈጣሪ ቁጣ እንኳ መማር አቅቷቸው የባንዳ እና የፋሺስት ታሪክ ትቶላቸው የሄደውን መመሪያውን እንቀጥልበታለን ብለው ሲግማሙ ሳስተውላቸው “አራዊቶቹ” ዛሬም ከዛው ተብትቦ አስሮ ከወጠራቸው አራዊት ሕሊናቸው ሰብረው መቸ መውጣት እንደሚችሉ ሳስበው ለነሱ እሳቀቃለሁ። እራሳቸውን ነፃ ማውጥ ካልቻሉ ከአውሬ ሕሊና መውጣት ያቃታቸው እነኚህ የሰው አውሬዎች የሚያሰራጯቸውን የውሸት መጽሐፍቶቻቸው መጪው ትውልድ እንዲታገላቸው ያመቸው ዘንድ የበኩሌን ድርሻ ለመወጣት መጽሕፈቶች ጽፌአለሁ። ከናንተ የሚጠበቀው ግዴታ ደግሞ ይህ ታሪካዊ አዲስ መጽሐፍ በማሰራጨትና “የእውነት ብርሃን” ላለማየት ዓይናቸው ጨፍነው፤ የውሸት እንቅልፍ ተኝተው፤ እያንኰራፉ ያሉትን አብዛኛዎቹ የትግሬ ምሁራን ከተኙበት ቀስቅሳችሁ እንዲያነቡት ይህ የብርሃን መጽሐፍ ዓይናቸው ላይ እንዲበራ ማድረግ ይጠበቅባችሗል።
በጣም አመሰግናለሁ
ጌታቸው ረዳ
P.O.Box 2219
San Jose, CA
95109
(408) 561-4836

Monday, November 5, 2012

MELES ZENAWI WAS THE SYSTEM





MELES ZENAWI WAS THE SYSTEM

Mankelklot Haile Selassie (PhD)

November 3, 2012  


I have read 18 articles, taking down points and statements to organize this article that I am going to share. I borrowed the opinions and the implications of the opinions from the 18 articles, embodied them into my thinking, and applied them in the five, briefly discussed, specific sub-topics I have already outlined. So, this article is the outcome of a kind of mini research. This article is also the extension as well as the buildup of the last two articles, namely, Step Out and Step up the Leadership, August 10, 2012, written before the death of Meles was officially confirmed, and, Mengistu Killed Ethiopians Meles is Killing Ethiopia, September 25, 2012, which was written after the death of Meles was officially confirmed.

Now I will begin with the most important subtopic, which, in my opinion, will help determine the moves one takes including the assessment of ones strategies established before the death of Meles Zenawi. I argue that, after Meles, strategies aught to be substantively reviewed and changed according to the needs identified.

Meles Zenawi was the System

Meles was undeniably the system in Ethiopia. The legislative, the judicial, and of course the executive systems were shaped and completely controlled by him until his death. He was also the engine for the system to run. And, it had to run exactly to fulfill the wishes of his personal, concretely exhibited, political and economic interests. Therefore, it is commonsense to conclude that when the creator and the gate keeper does not exist anymore all these branches will begin to crack and expose themselves to a harshly scrutinizing environment. The truth is, they did crack and exposed themselves big time. Add to this, this is what I learnt from reading the articles, the corruption that he was systematically manipulating to his benefit and controlling it, as he was using fertilizers and improved seeds on the peasants for political advantage. He was feeding from, and sleeping on the top of this corrupt and unbelievably rotten system. He was living and breathing this corrupt rotten system. He very well knew the rottenness of the system. So, one can imagine what this guy left behind.

Now, my primary argument is that after the death of Meles, the existing system, the system that he left behind, is not completely as it used to be. If we agreed, I think we do, that there is political crisis in Ethiopia now, then we should also agree that the system is already cracking, not intact and running smoothly because Meles is not there to keep it intact and run smoothly. Therefore, on deeper level of observation, to say the system is not changed is not correct. It is misleading. For one to have a properly articulated and fitting strategy accompanied with the tactics to implement it, pinpointing the extent of the crack or opening, that is, where and how deep the opening is will enable one where and how to put the pressure to widen it. Imagine a large dam with a crack where water is leaking out. Once there is a crack on the dam and the water continues to leak it is a question of time for the pressure from the body of the water to burst it open. What follows after the burst is anyone’s guess.

But, here is the crux of the problem. Particularly for the opposition political organizations, to exert pressure and widen the crack, a) particularly those in Diaspora must be inside Ethiopia, they have no alternative but to be inside Ethiopia, and b) one would not be, what ever the degree of the political crisis that exists, outright against the controllers of the remnants, as a group, of the system. It appears they are working as a group, collectively. A deliberate and a calculated move of this caliber requires primarily the change of the strategy held during Meles’s rule. This is very fundamental. Changing the strategies mean accepting the change of the political situation inside Ethiopia. It follows then, if one accepted the existence of political crisis in Ethiopia, which is the change, crisis brought about by the death of Meles Zenawi, wouldn’t it be naturally logical to come up with an immediate and measurable new strategy and tactics where one, through time, irreversibly replace the remnants of Meles and empower the people of Ethiopia. Remnants include the whole parliament, a body, that is morally and mentally corrupted, never able to think by itself except through Meles Zenawi and TPLFites embedded in all sectors of the administration. Stop whining and find out the means to sit down for negotiation and take advantage of this widespread political crisis. I have negotiation as a subtopic to which I would come back later and share my opinion about it.

 
Activities from Inside

This aspect of the struggle is very critical. In my latest two articles, mentioned above, political organizations were consistently the target of my discussion. Here too they are the major targets, particularly those in Diaspora, because they are, of course including those inside Ethiopia, the ones who are potentially organized to hold the power and run the country to change it. Now, clearly the ball is in their court. Unlike any other time, now, the environment is fertile to start activities from inside. What I discussed under the subtopic “Meles Zenawi was the System” mainly refers to the opposition political organizations. Unless the opposition political organizations “step out and step up” the leadership, the immediately needed measurable struggle will be without radar and anchor.

I want to be very specific here. My focus is on individual political organizations in a position of independent thinking and moves. I am no more a proponent of a formal, that is a structured, united opposition political organizations. I have witnessed a number of united political organizations. It did not work, it is not working now, and, it will not work in the future. So, why waste time on it. However, if individual political organizations, after affirming their strong independent individual moves, and already have started moving forward, strongly believe in forming a coalition, say to negotiate and establish bases in the field in Ethiopia, then informal unity can be the order of the day. In fact it is more effective if all those opposition political organizations in Diaspora come together and seriously discuss the issue of getting inside Ethiopia now. If they got the chance to enter Ethiopia as a group they would have measurable impact on the political situations. But still, even this has to be left to individual’s discretion. There should not be any pressure from the community. And the opposition political organizations should not be influenced by it either.

If the political organizations are sincere and observably aggressive in activities, it is inevitable for the progressive individuals and activist civic organizations to follow them and provide them with the support they need. The civic organizations mushrooming all over the places to the extent of intending to assume the political leadership, more or less to replace them, and progressive individuals ineffectively scattered all over the places, is due to lack of political organizations, including those in Diaspora, providing measurable leadership. Providing measurable leadership does not mean manufacturing press releases and commentaries. It only means a quantifiable and assessable political activities being performed inside Ethiopia. If not it is back to manufacturing press releases and commentaries. Bottom line of this position is self perpetuation and turning into professional political institutions.

Now it is the time to be in the field. There is a window of opportunity for the opposition political organizations particularly in the Diaspora to enter Ethiopia and start to change the system. It is irresponsible to squander this God given opportunity. Unfortunately in the case of Ethiopia no change will be brought about without sacrifices. The sacrifices include taking the step that is logical and correct and yet bitter to swallow. The opposition political organizations in Diaspora are extremely important factors, by any measurable standards, to establish a stable system in collaboration with those inside Ethiopia. For the Diaspora political organizations, to find out the means and the resolve as to how to be in the field and start working inside Ethiopia immediately is individual opposition political organization’s responsibility. If they could not solve this issue then they are no where to solve the misery of Ethiopian people of over 80 nationalities. Further more, if they could not keep up with the changes of the political situations inside Ethiopia, it is better to disband their organizations rather than pursuing a fake existence. For how long could one stay faking anyway?

Picking up the Flags of the Fallen

I think it is very important to thankfully acknowledge the political struggle that reached to this level and kept alive by the blood shade by Ethiopia’s sons and daughters in a hand-to-hand combat, facing Meles’s guns aimed at them. Meles Zenawi the murderer, very sadistically aimed at their heads to completely finish them. A lot of blood have been shade particularly by the youths.

Therefore, to pick up the flag of the fallen and continue the struggle, one has to be in the meadow where hand-to-hand fighting have taken place. It is time to stop invoking those who sacrificed themselves until and unless one has

 
picked up their flags and given oneself to the extent of being sacrificed. It is ridiculous to invoke the sacrifices made for ever. It has to stop and it is time, in fact it is long over due, to take the places of those sacrificed.

Every year since 1974 we are witnessing the sacrifices particularly made by the young ones in all walks of life. Students in particular. The 1974 revolution by decimating the generation that was highly intelligent and driven by conviction and determination, created absolute vacuum. As the result, the impact of the 1974 revolution is still affecting the efficiency and the effectiveness of the struggle inside as well as outside of Ethiopia today. To this day the caliber and the determination of the generation of that period is not replaced. As the result of the absolute vacuum created Meles and his cronies were able to do what ever they wished to do in protecting their political and economic interests. Still, until that generation is replaced, I think through time it would be replaced, it is only a question of time, long term stability hence economic development and the eradication of poverty cannot be fully guaranteed.

Therefore, picking up the flag of the fallen is to completely change the system where for example individual right is unleashed. In the case of Ethiopia, individual right is, in my opinion, the precursor for cultivating and raising a generation that would replace the 1974 sacrificed generation. One of the reasons to go for negotiation is, with non wavering objective, to produce a generation that is capable of turning around the political and the economic situation for the benefit of the society hence the completion of the objectives of those who sacrificed themselves. Aim at the bigger picture and negotiate!!! Take advantage of the crack created between and amongst the ruling party leadership. In the absence of Meles Zenawi, TPLF is no more in control of the political situation. It cannot be a full fledged threat anymore. By using the small crack created during the May 2005 code of conduct election agreement the Ethiopian people got the chance to beat Meles and his cronies. This is a good historical example to be used as a reference point and to be emulated. How the then opposition leadership abandoned the 26 million who came out to vote is another issue. At the time, I have condemned their inaction in one of my articles, including in my radio programs.

 
Negotiation

Negotiation does not necessarily mean reconciliation. Don’t bring the case of South Africa here. There is a big difference between South Africa and Ethiopia. In South Africa it was whites against blacks. In Ethiopia it is Ethiopians against Ethiopians. In South Africa the economies could have not be run without the whites. The know how and the skill to develop the economy and to keep up with the science and technology are completely in the hands of the whites. It would have been political and economic suicide for the South African blacks to go against what they did. In Ethiopia the economies could be run by Ethiopians. In Ethiopia, since the society is completely against the regime there is an alternative to the negotiation. If the negotiation failed uprising is an inevitable route. Uprising, if it took place, means completely uprooting, with a lot of damage, all those TPLFites embedded in the different sectors of the administration. Therefore think about Ethiopia independently with independent solution. There is nothing that Ethiopia lacks given properly channeled and strategically implemented.

Under this subtopic the targets of my discussion are the opposition political organizations particularly those in Diaspora. The time is now to demonstrate ones relevancy and determination to hold power and completely change the system and establish irreversible multiparty democracy, the beginning of the empowerment of Ethiopian society, and, the beginning of looking deeply inward to find out the real causes of the hindering problems to pursue aggressive economic development. In the case of Ethiopia, the ultimate target aught to be poverty eradication.

Power is the master key to get the political and the economic situations under ones control in order to eradicate poverty. The main purpose of negotiation is ultimately to have this power. I think this is very fundamental. Unless one holds power there is absolutely nothing one can do. Of course, one should have passionate desire to hold power and ones for all remove the misery of poverty. It is meekness, if not an outright mistake, to shun holding political power. Therefore, for the opposition political parties, both inside and outside of Ethiopia, right now, the overriding objective must be, unashamedly, at any cost, to hold power. Think about it very seriously and rationally. Negotiation is one of the means, now, perhaps the only means, to make an aggressive move for power. I will repeat below, to refresh your mind, what I said in my article of Sept. 25, 2012, “Mengistu Killed Ethiopians Meles is Killing Ethiopia.”

Therefore, particularly for the Diaspora political organizations, the first step is to write an official letter to Prime Minister Hailemariam Dessalegna indicating the desire to be part of constructive political activities inside Ethiopia. Simply put request negotiation. This could be done in groups or independently. The official letter, hence the request for negotiation, should be simple without any very serious preconditions. The question of the constitution, the question of political prisoners, the question of the judicial system, and the question of individual rights, in my opinion can be addressed later as things stabilize and close understanding is created. I have the full confidence that if the opposition political parties, including those in Diaspora, a very important aspect of the future political and economic struggle, were allowed to fully participate in the political process, then it would follow that at the time the opposition political organizations achieve or share the leadership they can resolve the constitution, the political prisoners, the justice system, and the individual rights issues slowly but surely once for all. It is inevitable, once the opposition political parties are from inside the system and the civic activists from out side the system, if you will, the issues I mentioned to be alive.

Use international organizations both governmental and non governmental to put pressure on the group who are running the country. It is better to do it now before the political environment changes. That is, before the groups become stronger and more sophisticated. Before they think and act like Meles. This is the right and the opportune time to think fast and deep before it is too late. The unfortunate culture developed among the opposition political forces is tardiness, that is, slow to move and slow to react.

Let me say this, to sum up this power issue. Right now, given the current political situation inside Ethiopia the route to power is first to negotiate then to participate in the election to come. Therefore, here, power means people’s power. It means people empowerment. It means establishing, ones for all, a government of the people, by the people, for the people.

Forming a Transitional Government

This kind of political move diverts the needed resources, in terms of manpower and logistics, from the real struggle. Therefore it should be avoided and never hesitate to totally condemn it.

There is an invitation by ENTC group spearheaded by Elias Kifle of Ethiopian Review and Dr. Feseha Eshetu, to form a transitional government. Elias Kifle was openly advocating in favor of Hailemariam Desalege, the new Prime Minister. The question is, instead of strengthening his support for the Prime Minister, why is he trying to erode Hailemariam’s traction? It shows the lack of integrity. How can one trust such an individual?

In the first place, at this time to form a transitional government is a wrong move. What is needed is to think and act as to how to be inside Ethiopia and be with the people. Ones for all the focus has to be how and when to enter Ethiopia and be on the side of the people. What is more serious is to look into these two individuals who are proposing this opportunistic move. Dr. Feseha Eshetu was the messenger of Meles Zenawi to kill the Ethiopian Youth National Movement. That is exactly what he did. A very destructive action from a destructive individual. What is amazing is that ignoring what he did to the Youth Movement, there are hypocrite organizations who are still dealing with him, a reflection of the vacuum created by the 1974 revolution.


I did indicate this destructive act of Dr. Feseha in my article of June 28, 2012, “What Happened to Ethiopian Youth National Movement.” Dr. Feseha is not a credible individual to be trusted in any organizational structures and activities. He has the potential to sell out the organization. What he did to the Youth Movement is a perfectly measurable example. If he had the burning desire to help the Ethiopian people he had the opportunity to stay in Ethiopia join political organizations or form his own political party to pursue his objective of helping the society.

 
The second individual, Elias Kifle, is the agent of Isayas Afeworq of Eritrea. He has the potential to introduce Isayas’s interests in the activities of the organizations that he would be part of. The transitional government intended to form could be one of them. It is worthwhile to remember the role of Isayas in the formation of the failed AFD. About 15 years ago Isayas prophesied about Ethiopia by saying: “This country called Ethiopia cannot have the age (life) of existence beyond ten years.” Tobia No. 37, 1990 (E.C). The harboring of liberation fronts did not help his prophesy to be fulfilled either. It is mere idiotic and self-centered shortsightedness for any opposition political organizations of Ethiopia to develop political relationship with Isayas, such as what the bankrupting, as exposed by Ginbot 7-D, Ginbot-7 is doing. Ultimately, this types of actions boil down to the question of integrity. It is a fact that Isayas is not for the unity of Ethiopia.

 
In my opinion, fortunately, Isaya’s motive has nothing to do with the Eritrean people except with those extremist ones. The people of Eritrea was separated from their brothers and sisters illegally and undemocratically. It was illegal because it was done by the non-elected groups the active and major role played by Meles. It was undemocratic because the people of Ethiopia did not participate in it. Therefore the people of Eritrea should come back to its original home. The war between the two, May 1998 - June 2000, was about to achieve this objective. Thanks to Meles Zenawi it failed. He stopped the fighting about sixty miles from Asmara. Had the fighting continued Asmara would have been captured and EPLF would have gone back to its foxholes. The people of Eritrea as they did not show any mass support for EPLF, this time too, they would have simply, without any complaint, switched their position and join the Ethiopian people. Here, it is very important to look at the bigger picture. People are very important to a country. The greater the number of population the greater the reality of having more scientists and researchers, more quality doctors and nurses, more quality teachers, larger and daring entrepreneurs, and the greater the potential of having of those different branches of the military forces who would defend and protect the country.

Once I am at this big picture issue I would like to attach to it another big picture to look at. A monumental history is being made in Ethiopia. Leadership is moved from North to South. The torch is transferred from the Northern Ethiopia to the Southern Ethiopia. A subliminal process indicating the development of the unity of Ethiopian people. The Southern People should not take it lightly. Nor Prime Minister Hailemariam Desalegne should take it lightly either. He should stand to the test. He must molt out himself, leaving behind his old baggage of dependency, to think and take independent moves and actions. The shadow of Meles Zenawi is unnecessarily denying him his independency. Self imposed crippling. He should wake up. It is he who is going to be judged based on his performance. Not Meles‘s. Meles is dead. The Southern people in particular and the Ethiopian people in general as well as the progressive democratic individuals and civic groups aught to lineup behind him and keep him motivated and accountable. Let history workout its course it started. In my opinion it is critically important to view this Passing of the Torch, from the Northern People to the Southern People, if you will, positively and determine to cultivate it. It is a phenomenon subtly brought about by Mother Nature. Don’t be against it. Look beyond the person, Hailemariam Desalegne, at the bigger picture.

Coming back to the two individuals, they claim that the formation of transitional government can force EPRDF, the party in turmoil and political crisis, to come to the negotiation table. The proposal is simply a fake one intended for building up ones statuesque, a mechanism invented by these two individuals. There is nothing they will not do to build their personal status at the expense of the political struggle. The more they perform their fake shows the more they would be exposed. There is the potential, if not already have started, to convert it into a money making machine. There are credible political organizations who has the potential, independent at that, to hold power to decide whether to negotiate or not to negotiate. They do not need the hoopla of the so called Ethiopian National Transitional Council.

Mankelklot Haile Selassie (PhD)

November 3, 2012

 

Tuesday, October 30, 2012

መለስ ማን ገደለው?


ንባብዎን ከመጀመርዎ በፊት፡
አረሜኔዎቹ የወያኔ ትግራይ የፈሺስት ፌዴራል ፓርላማ አባላት መሪያቸው መለስ ዜናዊን ማን እንደገደለው ስለሚያውቁ አንድ የፓርላማ አባል “ኢትዮጵያ ገራችን እና ሕዝቧን እግዚአብሔር በበረከት ይጐብኛት” ብሎ ንገግሩን በመደምደሙ “በኢትዮጵያ አምላክ” ላይ ተቃውሞዋቸውን በማሰማት “በስላቅ በመሳቅ” በኢትዮጵያ አምላክ ላይ ሲያፌዙ የተቀዱት  ለማየት ዩቱብ ላይ ይህንን አድራሻ በመጫን Ethiopia - "God Bless Ethiopia" quote brought the biggest laugh at the Parliament http://youtu.be/v09ak8RKNKY   የአጋስሶቹ የሕሊና ብቃት ለመመዘን ለጽሑፌ ማገናዘቢያ እንዲረዳዎ ይመልከቱ።    
                
Muna is combing Tina’s hair; the two Ethiopians prostitutes will soon be heading to a club. “The best is to find an American soldier,” says Tina. “The French are the most generous clients; they pay for our apartments so that we do 
           
The Godless anti Christ and anti Ethiopia Meles Zenawi buried In the compound of God's house by the priests who worshipped him as their leader 
መለስ ማን ገደለው?
ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያን ሰማይ ድረገጽ አዘጋጅ)getachre@aol.comwww.ethiopiansemay.blogspot.com

ተቃዋሚ ጋዜጠኞችም ሆኑ ምሁራን መለስ ዜናዊን የገደለው በሽታ ምን እንደሆነ እና መቸ ወር እና ቀን እንደሞተ ባሉት ዙርያዎች ለማወቅ እያብሰለሰሉ ጥያቆችን ማንሸራሸር እንጂ “መለስን የገደለ ሃይል ማነው?” የሚል ጠለቅ ያለ ሰውዬው ከነበረው ከኢትዮጵያዊ ባህል፤አገራዊ እና ሃይማኖታዊ የራቀ ሸካራ ግንኙነት ከፖለቲካው ትንተና ባሻገር እነኚህ የተጠቀሱ ሦስቱ የአገሪቱ አድባራዊ (ስፒሪት) ምሶሶሰዎች ባለው ዙርያ ሊያስከትሉበት የቻሉት መለኰታዊ ቅጣቶች ብዙም ትኩረት አልሰጡትም።

ዘመናዊ ጋዜጠኞችም ሆኑ የተማሩት ክፍሎች ትኩረታቸው ምድር ላይ ከሚታያቸው ጉዳይ ማያያዝ እንጂ የዓለም ሕዝቦች የሕይወት ታሪክ መዛግብቶቻቸው ከሚኖሩበት ከኢትዮጵያ ሰማዬ ሰማያት ማለትም ከምድሪቱ በላይ ያለው ሃይል መመርመር ዘመኑ ያለፈበት የቂሎች እምነት እንዳያስብላቸው ስለሚሰጉ፤ለመለስ መሞት እንደ ሽፋን ሆኖ ተከስቶ ከገደለው በሽታ በላይ ያለው ቀጪ ሃይል ማየት ስላልቻሉ ስለ ገደለው በሽታ እና የሞተበት ቀን እንደትልቅ ጉዳይ አድረገው ሲተነትኑ ይታያሉ።

 ይህ እንደዋዛ የሚታይ እይታ ሳይሆን ፤ ለመለስ መሞት ምክንያቶች “ኢትዮጵያን እንደ አገር ተከብራ እንድትኖር፤ያቆዩዋትና የተከላከሉላት” *የባህል እና የሃይማኖት* ተቋማት በወያኔ ሓርነት ሕዝቢ ትግራይ መሪዎች በተለይም ድርጅቱን በመራው በመለስ ዜናዊ የስልጣን መማገጥ ተሰነጣጥቀዋል። መለስ ዜናዊ በኢትዮጵያ ያነጣጠረው ጥቃት የምድርቱ ሕግ ሊገቱት አልቻሉም እና ኢትዮጵያን የፈጠረ ሃይል ገድሎታል።

 ወያኔዎች ልብ ያላሉት ነገር፤ “ኢትዮጵያ” የምትባል አገር በውስጧ የሚኖሩት ፍጡራን ሳይሆኑ ባለቤቶቿ ፤በምድሪቱ ውስጥ ሰፍረው የሚገኙ እልፍ ኣእላፍ እንሰሳዎች እና ሕዝብ በጥበቡ ያሰፈራቸውና የፈጠራቸው ንብረቶቹ የእግዚአብሔር መሆናቸውን ልብ አላሉትም። ልብ ስላላሉትም መሬቱም ሕዝቡም እንሰሳዎቹም ወንዞቹም ተራሮቹን እያንቀጠቀጡ በቁጥጥራችን አስገብተናል በማለት በማን እህሎኝነት ብዙ ግፍ ፈጽመዋል። እነኚህ ግፎች በወያኔ ትግራይ የሃይማኖት መሪያቸው በአባ ጳውሎስ እና በፖለቲካ መሪያቸው በመለስ ዜናዊ እና በኪነት እና በባሕል መሪያቸው በእያሱ በርሔ  ላይ ባንድ ዓመት ውስጥ የወረደው የእግዚአብሔር ቅጣት በጣም አስገራሚ ተአምር መሆኑን ልብ እንድትሉት ደጋግሜ አደራ እላለሁ።

 ይህ ትኩረት የተናገርኩት ዘሬ ሳይሆን ኢትዮጵያን ወደብ አልባ ባደረጉበት ሴራ እና አልጀሪስ ስምምነት ከተደረገ በሗላ የጻፍኩበት ቦታ የት እንደሆነ አሁን ትዝ ባይለኝም” ያስታወሳችሁ ብትኖሩ የጻፍኩትን ልብ እንድትሉት ደግሜ አሳስባለሁ። “ ልጆቿ ከድተዋት ብቻዋ ቀርታ ሰንደቋ እና ሕዝቧ እየተዘለፈ ለውርደት የተዳረገቺው ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ ፈጣሪዋ ስታመለክት “ዓለም” ያላየቺው ቅጣት ይወርድባታል።” ብየ ነበር። በተለይ ሃያል ነን በሚሉ አገሮች አንደ አውሮጳ፤አሜሪካ እና አረቦች እንዲሁም ሶማሌ’፡ ቅጣት ይደርስባቸዋል ብዬ ነበር። አሜሪካን አገር የደረሰው እና እየደረሰ ያለው የመከራ ዘመን እያያችሁት ነው። እነ ሶርያ እነ ኢራቅ እነ ሊቢያ እነ ግብፅ እንዲሁም ምጢጧ ሶማሌ “ኢትዮጵያን” ለመበተን የኤርትራ ሽምቅ ተዋጊዎች እያስታጠቁ  ራዲዬ ጣቢያ ከየመዲኖቻቸው እያስተላለፉ እርስበርሳችን ያጋደሉንን ያህል፤ ዛሬ እነ ሶርያ እነ ኢራቅ ሊቢያ  ሶማሌ;…….ፍዳቸውን ከፈጣሪ እያገኙ መሆናቸው ስትመለከቱት ‘በእጁ ጠፍጥፎ የሰራትን ኢትዮጵያ’ የተጫወቱባትን ያህል ፈጣሪዋም በበኩሉ ጊዜውን ቆጥሮ ትእግስቱ ካሟጠጠ በሗላ አንድ ባንድ ሲቀጣቸው ምን ትታዘባላችሁ?።  ይህ ትንቢት ከመድረሱ በፊት  ጽፌዋለሁ። ምናልባትም ሃዋርያ ጋዜጣ ላይ ወይንም ኢንተርኔት ላይ። ያስታወሳችሁት ሰዎች ከላችሁ እርዱኝ።

 በህይወት ያሉ ተመሳሳይ ሞኞቻቸውም የሚናገሩትን አንደበት ልብ ብንል ለፈጣሪ የሚፈሩ አይደሉም። ለምሳሌ “ስየ አብርሃ” ባንድ የክርክር መድረክ ከመለስ ካድሬዎች ጋር በፖለቲካ እንካ ስላንትያ ገጥሞ መልስ ሲሰጥ “አታስፈራሩን! ካስፈራራችሁን፤እስካሁን ድረስ ያልተናገርነውን (የደብቀን ያቆየነውን) ምስጢር እናወጣዋለን” ብሎ ነበር። እየሰማችሁኝ ነው? ሰዎች የሚፈሩት ምድር ላይ ያሉት “አስፈራሪዎች” እንጂ ጠረፍ ላይ በኢትዮጵያ ሰማይ በመስኮቱ ብቅ ብሎ ወደ ታች እየተመለከታቸው ያለውን የሰማዩ ንጉሥ የሚሰጣቸው ሕጎች እና ማስጠንቀቂያዎችን አያስፈራቸውም።ሰውን እንጂ ከነሱ በፊት የነበረ፤ከጊዜ በፊት የኖረ ለወደፊቱም የሚኖር እና ዓለምን እና እነሱን የፈጠረ አምላክ አይፈሩም። ለአምላክ ሕግ የማይፈራ ባለሥልጣን እራሱ ባጭር ቀጭቶ ምድሪቱንም ለአምላክ ቁጣ ይዳርጋል (ለዚህ ነው አልኩ ባልኩት ትንቢቴ ውስጥ እኛንም እንዳይጨምሩን እንጸልይ ያልኩት)። ሃይማኖት ለመስበክ አላማየ አይደለም። ልብ እንድትሉት ግን አሳስባለሁ።

 የመለስ ሞት ምክንያቶች ሁለት ናቸው።

(1)  ባህል እና ሃይማኖት በማንኳሰስ የተፈጥሮ ሕጎችን ተጻሯል

(2) የሕዝብ ሃይል/ሥልጣን በጉልበት ይዞ ብሔራዊ ወንጀሎችን ፈጽሟል።

እነዚህ የተጠቀሱ 2 መሰረታዊ ክሮች ከምድር ጋር ሳይሆኑ እትብታቸው የተለቆመው ከተፈጥሮ እና ከፈጣሪ ስለነበሩ አላግባብ በጥሷቸዋል።እነዚህን የበጠሰ ሕግ ወጥነት ነውና በምድር የመኖር መብቱ ባጭሩ ይቀጠፋል።

 መለስ ሲቀጠፍ ጎራው በሁለት ተከፍሏል።ደጋፊዎቹ “መለስ ለምን ሞተ፤ሞተ? ሲሉ ተቃዋሚዎቹ ደግሞ “መለስ እንኳን ሞተ!ሞተ!” በሚል መስመር ፍጥጫ ውስጥ ገብተዋል። አንዳንድ በጐልማሳነት ዕድሜ ያሉ የወያኔ ቄሶችም “መለስን ወደ ፈጣሪ በመለወጥ” “መለስ እውነት ነው” በማለት “እግዚአብሔር እውነት ነው” የሚለውን ሃይማኖታዊ መመሪያ በመለስ ዜናዊ በመተካት “ፍፁም” አምላክ ብለውታል (በወያኔዎቹ የዋሺንግተን ዲሲ አምባሲ አዳራሽ ለቀብሩ ሃዘን ሲደረግለት የተቀዳው ስእለ ድምፅ ‘ዮ- ቱብ’ ‘አውዲዩ-ቪዲዮ’ ይመልከቱ) ።
ፈጣሪን ልሳን መልእክተኞች የምንላቸው ቄሶች ‘ሰውን’ ወደ “ፍጹምነት/እውነት” በመለወጥ ሲያመልኳቸው ፈጣሪን እያስቆጡ ለሃገር ውድቀት እና ቅጣት እየዳረጉን ነው። ይህንን አምልኮ “አምባገነኖች” በሚገባ ስለሚያውቁት ከኛ ይልቅ “ፍፁማን” ተብለው ከሚመለኩት ሰዎች አንደበት የተነገረውን መፈተሽ ያስፈልጋል። ከላይ ለጠቀስኳቸው ተፈጥሮአዊ እና ዓለማዊ መብቶች መፈረካከስ ምክንያቱና መነሻው የመለስ ለኢትዮጵያ አምላክ የነበረበው ንቀት እና የስልጣን አልጠግብ ባይነት ነው። መለስ ስልጣን ከመውደዱ የተነሳ ገደብ ያጣ አገርን እና ባህልን ያናጋ ግለሰብ ነበር።  ይህንን ልብ በሉ “አምባገነንነት የፈጠሪን ቅንድብ የሚያስቆም ከባድ ወንጀል ነው”። ፈጣሪን የማይፈሩ መሪዎች ስለ ሕገ ወጥነት ጉዳይ ሲነሳ አምባገነኖች  የውንጀላ ጣታቸውን የሚቀስሩት፤ ወደ እራሳቸው ሳይሆን፣ወደ ሌላ አምባገነን ነው። መረጃ ልስጥ። ለአፍሪካ ውድቀት ምክንያት መለስ ዜናዊ ምክንያቶች የሚባሉ ነገሮች ተጠይቆ ሲመልስ እንደሚከተለው ነበር የመለሰው።

“የአፍሪካ ውድቀት ሁሌም የግለሰቦች አምልኮ ነው።” ሲል አፍሪካን ለውድቀት የዳረጋት በመሪዎች ላይ  አምልኮ ማሳደር እንደሆነ አስምሮበት ነበር።እነኚህ የተመለኩ መሪዎችስ እነማን ናቸው? ሲባል መለስ እንዲህ ሲል ይመልሳል። “ስማቸውም ሁሌ በ “መ”  ፊደል ዘር የሚጀምር ይመስላል። በዚህ ረገድ ሞቡቱ እና መንግሥቱ ነበሩን።መለስን ግን ከዚህ ዝርዝር ውስጥ ማስገባት አልፈልግም” ሲል የመለሰውን መልስ “የአቶ መለስ ጥቅሶች” በሚል ርዕስ “መለስ ከልጅነት እስከ እውቀት” ተብሎ ‘በትኩእ ባሕታ’ የተጻፈ መጽሐፍ ተጠቅሷል። 
እሱ ከሄደ በሗላም  መለስን “ወደ ፍፁም/እውነት (አምላክነት) በመለወጥ” አምልኮ የአሳደሩበት ያደራጃቸው ቀሳውስቶቹ  ለኢትዮጵያ ወጣቶችና ለሃይማኖት መበስበሰስ ምከንያት ናቸው።በ‘መ’ ፊደል ዘር የሚጀምር የአምባገነኖች ስም ሲጠቅስ ራሱን ለምን አልጠቀሰም? የሚል ጥያቄ ቢያስከትልም፡ የህጻናት፤የወጣቶች እና አረጋዊያን ደም ያለ ሕግ እንዲፈስ ያደረገ መሆኑን እያወቁ፤የራሱ ቀሳውስቶች መለስን በፈጣሪነት እና በፍፁም እውነትነት በማመን ለምን ሰበኩለት? ስንል ፍካሬ እየሱስ ላይ የተጻፈውን ማቴ፤7፡15 እንዲሁም 23፡5-7 ዘዳ 32 ብንመለከት የክህነት ልብስ በመልበስ መርዝ የሚረጩ ተኩላዎች በመካካላችን እንደሚቀላቀሉ እና እንደሚያሳስቱን ያስጠነቀቀው ትንቢት እውነታውን እያየን ነው ይላሉ መንፈሳዊ ምሁራን።
መለስ ዜናዊ የራሱን ሃሳዊ መሲሆችን በመመልመል ከቄስ እስከ ሃኪም  ከአረጋዊ እስከ ጎልማሳ እና ታዳጊ ብላቴናዎች ድረስ የተፈጥሮ እና የሰው ልጆች ሕግ የሚጻረሩ ርዕዮተአለሞችን እንዲቀበሉት በማድረግ የኢትዮጵያ ሕዝብ “ፋሺስቶችና ጉልተኞች” የሚከተሉትን “የጎሳ እና የደም ጥራት” መለኪያ አድርጎ በቋንቋ ልሳን ተከልሎ እንዲተዳደር ቀይሶ ሕዝብን አናክሶ “በወንድማማቾች ማሃል ደም እንዲፈስ አድርጓል”።
(1)በባህል እና (2)በሃይማኖት እምነታችን የሕዝቡን እይታ እንዲበላሽ መለስ የሰራቸውን ስራዎቹ ለሞት ቅጣት ያደረሱት እንዴት እንደሆነ እንመለክት። ሕብረተሰብ እንደሚበሰብስ ባለፈው ገልጫለሁ። ሕብረተሰብ አይበሰብስም {“ሕዝቡ በስብሷል ከማለት ለዘብ ያለ ቃላት” ብትጠቀም ጥሩ ነበር} ብለው ስልክ የደወሉልኝ ወገኖቼ አሉ። መንፈሳቸው ይገባኛል። ክፋት የለውም።  ነግር ግን ‘ዘመነ ሎጥ’ የሰዶም እና የጎመራ ከተሞች ሕዝብ በስብሶ ለቅጣት እንደተዳረገው ሁሉ የኛ ሕዝብም ግስጋሴው ከዛው ያልተናነሰ  የባህል እና የሃይማኖት ወረራ ተፈጽሞበት በምድሪቱ ላይ እንዲስፋፋ መለስ ዜናዊ አስተዋጽኦ አድርጓል። የሕዝቡ መንቀዝ (መበስበስ) መረጃው ወደ ሗላ አመጣዋለሁ። 

(2) ‘በፍፁምነት’ በመልአክትነት ያመለኩት የራሱ ቀሳወስቶች ብቻ ሳይሆኑ የተማሩ አምላኪዎቹም “መለስ ዜናዊ” የተባለ “አዲስ ሃይሞኖት” መስርተናል በማለት ይፋ አድርገዋል።
ከዛሬ ጀምሮ ሃይማኖቴ “መለስ” ወደ እሚባል ሃይማኖት ለውጬአለሁ በማለት ምሁራን ዜጎችም መለስን ወደ ሃይማኖትነት ለውጠውታል። መረጃ ላቅርብ። በወያኔው “ዓይጋ ፎረም’ ድረገጽ  “ዓዳል ኢሳው” በተባሉት ጸሐፊ የቀረበውን ጽሑፍ ይመልከቱ። “I am again a born believer & my religioun is Meles Zenawi (Adal Isaw September 2, 2012)  “ፍሪኪሽ ቢሄቭዮር” (ለማመን የሚቸግር ባህሪ)የሚሉት እንዲህ ዓይነት የባህል እና የሃይማኖት መዛባት እንዲታይ መለስ ዜናዊ እና ድርጅቱ ያካሄዱት የአእምሮ ጠለፋ ምሁሩንም ኩፉኛ ጠልፈውታል።
 
በዚህ በሁለተኛው (በሃይማኖት መዛባት) እየታየ ያለው የሃይማኖትና የሕብረተሰብ መበስበስ ጎዳና ልጀምር።

ከላይ የተጠቀሱት ጸሃፊ I am again a born believer & my religioun is Meles Zenawi” ብለው ፡መለስ ዜናዊ” የተባለ አዲስ ሃይማኖት ለመመስረት የተነሱት “መለስ ዜናዊ” የተባለ “ሃይማኖት” ተከታይ የተነተኑልንን እንስኪ አንዳንዱን ልጥቀስ። 
“ I believe, Meles Zenawi was born for reasons other than the ordinary ones that you and I were born for” ይህ ሰው እየሱስ ነው፤ ከማንኛችንም በላይ የተለየ ተልእኮ እንዲፈጽም በምክንያት የተፈጠረ ከፈጣሪ የተላከልን ልዩ  ፍጡር/መልእክተኛ ነው። ነው እያሉን ያሉት። ይቀጥሉና የመለስ ዜናዊ ሃይማኖት ተከታይ እንዲህ ይላሉ “
“I have a reason to revert back to the religion that I have abandoned early in life. Things were trite and nothing was out of the ordinary then, and, I had to walk away from my religion as a result. But now, and after many years of abandoning my religious belief, I am a born-again believer and my religion is Meles Zenawi.” ……”I believe in Meles Zenawi and he is my religion from now on till the end of my time”….
“ Indeed; Meles Zenawi is my religion for he is a rarity—a gift from the Goddess of Ethiopia. And hence, he is the religion that I have now”. ((Adal Isaw September 2, 2012
 adalisaw@yahoo.com) 

እንግዲህ እንዳያችሁት ጸሃፊው መለስን የተመለከተው “አርበኛ፡ “አንበሳ”…የሚሉት ሙገሳዎች/መለኪያዎች ያንሱታል ነው የሚሉት። ለሱ የሚመጥነው “ለምክንያት የመጣ እኛን ተመስሎ ለማዳን ወደ እዚህ ምድር ከኢትዮጵያ አምላክ የተላከልን አዳኚያችን ነው” ብሏል በሰፊው ጸሐፊው ሲተንትኑ (ሊንኩን አንብቡት)። ይህ ጉድ እና በጣም አሳፋሪ የባህል፤የሃይማኖት መበስበስ እየታየ ያለው መነሻው የግዛቤ እጥረት እንደሆነ ምንም የሚያከራክር አይደለም። መለስ ዜናዊ የፈጸማቸው ወንጀሎች አምላክ እንዳትፈጽሙ ያላቸውን አብዛኛዎቹ በተለይም ትላልቆቹ (ትልቅ እና ትንሽ የሚባል የሕግ ጥሰት ካለ) አትግደል፤ አትዋሽ፤ በሕዝብ እና በአገር ክሕደት እንዳትፈጽም፤ ፈጣሪህን አክብር፤”ክረስትያን ወይንም እስላም” አማኝ ከሆንክ በምድሪቱ ውስጥ ግብረሰዶምነት አንዳይከናወኑ አጥብቀህ ኮንን/ተቆጣጠር፤ ከሌቦች፤ነብሰገዳዮች፤ከአመጸኞች ጋር አትመሳጠር፤ የአገሪቱን ዳር ድምበር ጠብቅ፤ አርበኞቿ እና ሰንደቅአላማዋን አክብር… የሚሉትን ትእዛዞች የጣሰ ክፉ ሰይጣን ነበር። መቸም በዚህ መረጃ ይታጣል የሚል ሰው ከተገኘ ሞኝ ነው ማለት ነው። ስለዚህ ይህ “ፍፀም” ሆኖ ወደ አምላክነት እና ወደ ሃይማኖት የተለወጠ የወያኔ መለኰት “ፍፁም” ነው ብሎ ማለት አስቂኝ ብቻ ሳይሆን የወንጀሉ ተባባሪ እና በሕዝባችን፤በቤተሰባችን፤በጓደኞቻችን፤በአገራችን የፈሰሰው የሰው ልጆች ደም ደንታ ቢስነት መሆን ነው።

(2)መለስ ዜናዊ ለኢትዮጵያን ባህል እና አርበኞች ክብር አልነበረውም።

መለስ ዜናዊ ሰፊ አገር ያስገኙለት የድሮ የጦር አርበኞችና ነገሥታትን ሙገሳና ክብር መስጠቱ ይቅርና በአትሌቲክስ/ስፖርት አገራቸውን ያስጠሩ አርበኞች በተቻለው መጠን መንፈሳቸው እና ህይወታቸው እንዲሰበር ከማድረግ የቦዘነበት ጊዜ አልነበረም። መለስ ዜናዊ ስልጣን ሲቆጣጠር እሴቶቻችንን ነበር መልቀም የጀመረው። አርበኛው ማሞ ወልዴን ታስታውሳላችሁ? ዊክዴፒያ/ኢንሳይክሎፒዲያ የተባለው የታሪክ ማህደር እንዲህ ይላል፡ “In 1993, Wolde was arrested on the accusation that he participated in a Red Terror execution during the regime of the dictator Mengistu Haile Mariam. He argued that although he was present at the killing, he was not a direct participant. The IOC pressured the Ethiopian government to release him. In early 2002 he was convicted to six years of imprisonment, but released because he had spent nine years in detention already waiting for his trial.”

እየተከታተላችሁኝ ነው? አንደኛ በግድያው አልተሳተፍኩም፤ ሆኖም እዛው ቆሜ ነበር በማለት የተከራከረበት ክስ 6 አመት ሲያስፈርድበት፤ እሱ የታሰረው ግን 9 ዓመት ነበር። ይታያችሁ አንግዲህ፤ መለስ ዜናዊ የተባለ “ፍፁም አምላክ” እና “መለስ ዜናዊ የተባለ ሃይማኖት” በሚያስተዳድራት አገር 6 አመት የተፈረበት ሰው 9 አመት ፈጽሞ ወደ 10ኛው አመት እያመራ እንዳለ በ9ኝ አመቱ ፍርድ ስለተሰጠው፤ ከሚገባው በላይ ስለታሰረ አሰናብተውታል። ሲሰናበት የጉበት በሽታ ይዞ በመውጣቱ ወዲያውኑ ለሞት ተዳረገ።  ይህ “መለስ ዜናዊ የተባለ ከፈጣሪ የተላከ ልዩ መልአክ” 6 አመት የሚያስፈርድን ክስ 9 አመት እንዲበሰብስ የሚያደርግ መልአክ ከየትኛው ሰማይ እንደወረደ የዜናዊ ሃይማኖት  ተከታዮች እንዲያብራሩልን እንጠብቃለን።

የማሞ ወልዴ ባለቤት ወ/ሮ አበራሽ ከባድ የሕሊና እና የኑሮ ጫና ለማወቅ መሉ ንባኑን ለማግኘት ይህንን ይመልከቱ፤http://www.kennymoore.us/kcmarticles/woldehonolulu/woldestory.htm

“ፆታህንም መቀየር ትችላለህ”

መለስ ዜናዊ እና ፓርላማው ሹሟሙንቶቻቸውን ሲሾሙ በመጽሐፍ ቅዱስ ወይንም ቁርአንን ወይንም የኢትዮጵያ ሰንደቃላማን  አስይዘው መሃላ አያስፈጽሟቸውም። ምክንያቱም መመሪያቸው ፋሺስታዊ እና ኮሚኒስታዊ ፈጣሪ አልባ መመሪያቸው በሞሆኑ። ለዚህም ግብረሰዶምን እንደነውር አይቆጥሩትም እና በአንደበታቸው ሲያበረታቱት ተደምጠዋል። “ፆታህን መቀየር ትችላልህ” በማለት ፃየፍ ይህ ብልግና የተሞላበት መልስ የሰጠ መሪ ማን ነው? መለስ ዜናዊ! ይህ ስብእናን እና አርበኛን የሚያቆሽሽ ኢትዮጵያዊ ባህል የሚጻረር የብልግና ስድብ ምላሽ የተናገረው ለማን ነበር? ታሪኩን እንመልከት።

መለስ ዜናዊ የስፖርት አርበኞችን ያከብራል፤ለሙዚቀኞችን፤ ለከያኒያንን አክብሮት ነበረው፤ እያሉ ከራሳቸው ከአፍቃሬ ወያኔ ባለሞያዎቹ አለቃቸው ሲሞት እያለቀሱ ሲያከብራቸው እንደነበረ አስደምጠውናል። እውነታው ግን ውርደትን እንደ ክብር እና ጀግንንት የተቀበሉት እነኚህ ካፍንጫቸው አካባቢ ውጭ አርቀው ማየት ያቃታቸው ሕሊናቸው በገንዘብ የተጭበረበረ የስፖርት ባለሞያዎች መለስ በህይወት እያለ ምን እያለ ክብራቸውን ይጋፋ እንደነበር ንግግሮቹ እና ቃለ ምልልሶቹ በመጽሐፍ መልክ ካድሬዎቹ ጠርዘው ባሳተሙለት መጽሐፍ ውስጥ ሲላቸው የነበረውን ነግረውናል። ይህንን እንመልከት፦

“አንድ ዝነኛ አርቲስት ክስ ተመስርቶበት ከታሰረ ትንሽ ቆየት ብሎ ነበር። በዚህን ወቅት አንድ ታዋቂ አትሌት በውጭ አገር አስደናቂ ድል ተቀዳጅቶ ወደ አገሩ ሲገባ ጠ/ሚኒስተር መለስ አድናቆታቸውን ለመግለፅ ኤየርፖርት ድረስ ሄደው ይቀበሉታል። አትሌቱም አንድ አንገብጋቢ ጥያቄ እንዳለው ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ይናገራል።

“ምን ችግር አለ ጠይቃ” አሉት ጠ/ሚኒሰትሩ።

“እከሌ የተባለ አርቲስት ካልተፈታ ዜግነቴን እቀይራለሁ”።” “አንኳን ዜግነትሀ ፆታህንም መቀየር ትችላለህ! አሉት ጠ/ቅላይሚኒስትሩ።

 (መለስ ከልጅነት እስከ እውቀት- ደራሲ ትኩእ ባህታ)

እንዲህ ያለ ነውር፤ ያውም የዓለም አምበሶች የተባሉ ሯጮች ያስናቀ የወንዶች ወንድ “ሱሩህን ፈትትህ ከወንድ ጋር ተዳራ” የሚል በነውር የተሞላ አርበኛን የሚንቅ በትዕቢት የተሞላ መሪ አንኳን በተቀደሰቺው ኢትዮጵያ ይቅር፤ ነውር በሚያከብሩ ነውራም አገሮችም ለአንድ አርበኛቸው እንዲህ ያለ ሰብአዊ ጥያቄን ለጠየቀ አገር ያስጠራ አትሌት ነውር የመለሰ መሪ በታሪክ የለም። ግበረሰዶም እፈጽማለሁ ካልከኝም መብትህን አከብራለሁ የሚለው የግብረሰዶማዉያን መብት አስጠባቂ የነበረው መለስ ዜናዊ በንግግር ብቻ ሳይወሰን በግብርም ግብረሰዶም በኢትዮጵያ እንዲስፋፋ እሱ እና ተከታዮቹ የተቻላቸውን ጥረዋል። እስላም እና ክርስትያን በመጽሓፋቸው የኰነኑትን እኩይ ስነምግባር አገር እንዲበሰብስ አስተዋጽኦ አድርገዋል። በዚህም አምላክ ተቆጥቶ መለስን ባጭር ቀስፎታል።መረጃው እነሆ፤

ታዋቂው ጋዜጠኛ ኢየሩሳሌም አርአያ በኢትዮጵያን ሰማይ ብሎግ ድረገጽ ላይ “በኢትዮጵያ አስደንጋጩ የባሕል ወረርሽኝ” በሚል ርዕስ ለሕዝብ ያስነበበውን የግብረ ሰዶም መከሰት በኢትዮጵያ መለስ ዜናዊ እና ስርዓቱ ምን ያህል አስተዋጽኦ እንዳደረገ በሰፊው እንዳስነበበን ታስታውሳላችሁ። ከ10 እና 12 ዕደሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ሃያ (20) ታዳጊ ሕፃናት በውጭ አገር ሰዎች እንደተደፈሩና ደፋሪውም ወደ አገሩ እስኪመለስ ደረስ ሆን ተብሎ መንግስት ቸል እንዳለው ዘገባዎች አመልክተዋል። ችግሩ ጠለቅ ብልን እንድንረዳው ጋዜጠኛ እየሩሳሌም ግበረሰዶማዉያን በደብቅ ሳይሆን በቡድን ወደ መደራጀት ደረጃ እንደደረሱ ሁኔታውን እንዲህ ይገልጸዋል፤-

“ግብረሰዶማዊያን ማሕበር (ቡድን) እስከ መደራጀት ደርሰዋል። ከላይ እንደጠቀስኩት የመለስ አስተዳደር ምን አቋም እንዳለዉና እንደሚከተል ጠንቅቀዉ የተረዱ ግብረሰዶማዊያን 2000.. ሚሊኒየም በማስታከክሕጋዊ ዕውቅና ይሰጠንእስከማለትና የመለስ ዜናዊን በቀጥታ እስከመጠየቅ ደርሰዋል።ስለዚሁ ጉዳይ ወይም ጥያቄሪፖርተርጋዜጣ የዜና ሽፋን በወቅቱ ሰጥቶታል።” ይላል ጋዜጠኛ አርአያ ተስፋማርያም (እየሩሳሌም አርአያ)።

ቀጥሎም፤

“በአገር ዉስጥ ከሚታተሙ የኪነጥበብና ማሕበራዊ ነክ የግል መጽሔቶች ሳይቀር ሕብረተሰቡን የሚንቁ ጽሑፎችን ማዉጣት ይዘወል። አንድቢኒያምነኝ ያለ ግበረሰዶማዊ ባወጣዉ መጣጥፍ- በአዲስ አበባ ብቻ 7 ሺሕ (ልብ በሉ ሰባት ሺሕ ነዉ!) ግብረሰዶማዉያን በአንድነት እንደተሰባሰቡና ማሕበር እንደመሰረቱ፤ለሚመለከተዉ የመንግሥት አካል ሕጋዊ ዕዉቅና እንዲሰጣቸዉ ጥረት እያደረጉ መሆኑን (ግብረሰዶማዉያንን (Gay) ገይ በሚገልጽ ሁኔታ በአዲስ አበባ ዕምብርት (በስማቸዉ መሆኑ ነዉ) ትልቅ ናይት ክለብ ለመክፈት አስፈላጊዉ ዝግጅት መጠናቀቁና ለዚህም የሚያስፈልገዉ ገንዘብ በበቂ ሁኔታ መመደቡን፤ አባላቱ ያቋቋሙት ማሕበር የፋይናንስ ችግር የሌለበት መሆኑን፤የበለጠ ለመደራጀት ሲሉ የአባላት ቁጥር በየፊናዉ እየመለመሉና እያበራከቱ መሆኑን እዉቅና ካገኙ በሗላ በስማቸዉ ጋብቻ የሚፈፅሙበት የሃይማኖት ተቋማት (ቸርች) እንደሚመሰርቱ፤ 2000 .. ጀርመን ከሚገኝ ወንድ ጓደኛዉ ጋር የጋብቻ ስነስርኣት አከናዉኖ መምጣቱንበሰፊዉ ከዘረዘረ በሗላ አያይዞምሕብረተሰቡን እያግለን፤ግብረሰዶማዉያንን ማግለል ይቁምእያለ በጽሑፍ ዘላብዷል። ይኸዉ ግለሰብ በተደጋጋሚ ተመሳሳይ ይዘት ያለዉ መግብረሰዶማዊያን ማሕበር (ቡድን) እስከ መደራጀት ደርሰዋል። ከላይ እንደጠቀስኩት የመለስ አስተዳደር ምን አቋም እንዳለዉና እንደሚከተል ጠንቅቀዉ የተረዱ ግብረሰዶማዊያን 2000.. ሚሊኒየም በማስታከክሕጋዊ ዕዉቅና ይሰጠንእስከማለትና የመለስ ዜናዊን በቀጥታ እስከመጠየቅ ደርሰዋል።ስለዚሁ ጉዳይ ወይም ጥያቄሪፖርተርጋዜጣ የዜና ሽፋን በወቅቱ ሰጥቶታል።መጣጥፍ በመጽሔት ያቀረበ ሲሆን በዛው ጽሑፍ ያካተተዉ ተጨማሪ ጉዳይ በአዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች የመዝናኛ ክለቦች ተከፍተው በስራ ላይ እንዳሉና ግብረሰዶማውያን በአንድነት ተሰባስበው እንዲዝናኑ ሲባል ታስቦበት የተከፈቱ መሆናቸውን አክሎ ገልጿል።”

ጋዜጠኛ አርአያ በግብረሰዶማውያኑ ዳንስ ቤት ድረስ በመሄድ ያተዘበው ዘገባ ሲያጠቃልል እንዲህ ይላል።

“ነበር።እንደተገለጸዉ አስኳሉ ሸራተን የሆነዉ ወረርሺኝ በይፋ ከከፈታቸዉ የምሽት መዝናኛ መካከል የሚከተሉት ይገኛሉ። በአካል ጭምር ተገኝቼ ያረጋገጥኳቸዉ ቦሌ ቴሌ መድሃኒያለም ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ የሚገኘዉሸገርሕንፃ ሦስተኛ ፎቅ በሰፊ አዳራሽ (ሁለት ቦታ ተከፍሎ) ተከፈተዉሻምፒዮንወይም በሌላኛዉ መጠሪያዉዲቫይንየተባለዉ የግብረ ሰዶማዉያን መዝናኛ በዋናነት ይገኛል። የባሩ ባለቤት በአሜሪካ ለረጂም ዓመት የኖረና 1999.. እንግሊዝ-ለንደን ከተማ ከወንድ ጓደኛዉ ጋርጋብቻመስርቶ እንደተመለሰ ተረጋግጧል፡፤ ለጋዜጠኛነት ስራየ እንዲሁም ባሕላዊ ወረርሽኝ ለመከላከል ባለብኝ ግዴታ በመነሳት ወደተጠቀሰዉ ባር በእኩለ ሌሊት አመራሁ። የገጠመኝ ሁኔታ ከሰማሁት የበለጠ ነበር! በምሽት ደብዛዛ የብርሃን ጨረር የተሞላዉ ይህ ባር እንደነገሩ ሁለት ቦታ ተከፍሏል። እንደ ዊስኪና ሌሎች የአልኮሆል መጠጦች በዉድ ዋጋ የሚቸበቸቡበትና በዲጄ በሚለቀቁ የዉጭ ዘፈኖች ታጅበዉ የሚደነስበት ሲሆን፤ በሌላኛዉ ክፍል ደግሞ እጅግ ከደበዘዙና ብዙም የብርሃን ጨረር ከማይፈነጥቁ አምፑሎች በመታገዝ ግብረሰዶማዉያን የሚፈጽሙት የሚያቅለሸልሽ አፀያፊ ተግባር የሚፈፅሙበት ነዉ። ከሰኞ በቀር በሁሉም የሳምንት ቀናቶች ይህ ወራዳ ተግባር ይፈጸማል።በጣም የሚገርመዉ ፈረንጆች ወንድ ለወንድ ፤ሴት ለሴት ሆነዉ (ካፕል- ካፕል መሆኑ ነዉ) እየተላላሱ በሚያጠይፍ አኳሗን መመልከቴ ነበር።ይሕች ያልታደለች፤ተቆርቋሪ መንግሥት ያጣች አገርድሕነት አሳሯን የሚያሳያት አልበቃ ብሎ፤ የነርሱ ቆሻሻ ባሕል ማራገፊያ መሆኗ ስታይ ያቃጥላልአልኩ በወቅቱ ለራሴ የእኔን ሃሳብና ቁጭት የሚጋራ ድፍን ሙሉ አገር እንደሆነ አልጠራጠርም። በሌላ ቀን ጥቆማ ወደ ደረሰኝ መዝናኛ ስፍራ አመራሁ። ቦታዉ ከቦሌ ትምህርት ቤት ሽቅብ እንደተጓዘቦሌ ኬክ ቤት ያገኛሉ፡ ከኬክ ቤቱ በግምት 200 ሜትር ርቀት ላይ ከመንገዱ ግራና ቀኝ በመደዳ ከሚገኙ በርካታ ባር ቤቶች ከቀን በኩል ቅድሚያ የሚያገኙትላጌቶየተባለዉን የግብረሰዶማዉያን መናኻርያ ባር ነዉ። በሚታይ ጉልሕ ጽሑፍ የመዝናኛዉ ታፔላ ተሰቅሏል። በግራዉንዱ አልፈዉ ባሩ ወደ ሚገኝበት አንደኛ ፎቅ ይደርሳሉ። ከእነሱ በቀር ሌላ ተጨማሪ ሌላ ሕንጻ የለም። የባሩ ባለቤት አስመራ የቆየናላጌቶየሚል ተመሳሳይ መጠሪያ የሰጠዉ መዝናኛ ከፍቶ እስከ ዘጠናዎቹ አመታት አጋማሽ ሲሰራ እንደቆየ ከራሱና ከኤርትራዉያን ጭምር ማረጋገጥ ተችሏል። አስመራ ያለዉ መንግስት በግብረሰዶም ዙርያ ጠንካራ አቋም ያለዉ ሲሆን በዚህ ርካሽ ተግባር ተሰማርቶ የተገኘ ማንኛዉም ግለሰብ ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ በሞት እንዲቀጣ ይደረጋል። ይህ ግለሰብ ሻዕቢያ ሲደርስበት አምልጦ በየመን በኩል አዲስ አበባ ይገባል። አስመራም አዲስ አበባም የሚታወቅበት መጠሪያ ስሙላጌቶበባሩ ስያሜ ነዉ። ይህ ማለት ( Gay-ጌይ) የሚለዉን ለማመላከት ነዉ የሚሉ አሉ።በየዕለቱ በዚህ ባር አካባቢ ፖሊሶች አይጠፉም። ግለሰቡ ኤርትራዊነቱን ሸሽጎሻዕቢያ ሊገድለኝ ሲል ያመለጥኩ የትግራይ ተወላጅ ነኝእያለ ከማደናገሩ በተጨማሪ ሴትጥንዶችወይምሌዝቢያንበብዛት አይጠፉም። ለመግለጽ የሚቀፉ እንቅስቃሴ ሲያደርግ የሚታየዉ ኤርትራዊዉ እና ግብረሰዶማዉያኑ አባላቶቹ በሚለቀቀዉ ዘፈን (ዘፈኖቹም የነጭ እና የሻዕቢያ ናቸዉ)ጣልቃም አየአቅጣጫዉአሞሬ”…አሞሬየሚሉት ቃላት ይወረዉራሉ። ትርጉሙን ስጠይቅፍቅረኛየማለት እንደሆነና “Gay”ዮቹ ቋንቋ እንደሆነ ተረዳሁ። ሽንት ቤት ሳመራ ባየሁት ነገር አስታወኩ! ወዴት ያመራን ይሆን?” በማለት ደምድሞታል።

በዚህ የባህል ወረራ መበስበስ ጥቃት የደረሰባት ኢትዮጵያ የእግዚአብሔር ቁጣ ወርዶ መለስ ዜናዊን  እንደ “ሎጥ” ዘመን ሕብረተሰብ ዋና አበስባሽ መሪው መለስ ዜናዊን በሞት ቀጥቶታል።




በአገራችን ውስጥ በጀርመን ፊልም ሰሪዎች ቅንብር አንድ የሃይማኖት ሴራ ለመፈጸም ሙከራ ተደርጎ ነበር።


ማርያም መግደላዊት ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር የተለየ ፍቅርና ፆታዊ ግኢነኙነት እንደነበራት የሚገልፀው እየሱስ አልዓዛርን ከሞት በተአምር ማስነሳቱ ተጥሶ በአፉ -ለአፍ ሳይንሳዊ መፍትሔ ተጠቅሞ እንደሆነ ያሳያል። ይባስ ብሎ ሓዋርያት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ውስጥ ሲሰሩ ይገልጻል።

በፊልሙ ስክሪፕት ላይ ሳይጻፍ (በተንኮል ሰናሱሩን ለማሳለፍ) በልምምዱ (ተዋናዮቹ እንዲለማመዱት የተደረገው) ወቅት የተከሰተው አስደንጋጩ ክፍል ደግሞ እየሱስን አሳልፎ የሸጠው ይሁዳ ጋር ከንፈር ለከንፈር እንዲሳሳሙ የተደረገበት አስደንጋጭ ክስተት ለፊልሙ ተመርጠው በነበሩት በኢትዮጵያ ገዳማት እና በተክርስትያናት ቅጥር ግቢ ውስጥ ድርጊቱ እንዲቀረጽ ተደርጎ በጀርመንኛ እና  

በአማርኛ ቋንቛ አንዲሆን በተንኮለኞዩ በጀርመኖች እና ተባባሪ ኢትዮጵያዊያን ፊልሙ አንዲቀረጽ ተዶልቶልን እንደነበር መዲና የተባለው ጋዜጣ ታህሳስ 2004 ዓ.ም ዜናው አውጥቶት እንደነበረ ይታወሳል። ሆኖም በጠንካራ አገር ወዳድ እና ሃይማኖታቸውን በሚያከብሩ ወገኖች ሴራው ከሽፏል። ክርስቶስ ግብረሰዶም ፈጻሚ እንደነበረ እና ኢትዮጵያዊ ንም አጸያፊው ተግባር እንዲከተሉ የሚገፋፋ የሰይጣኖች ሴራ ነበር። የወያኔ ስርዓት የላመጣብን ጉድ የለም

በጣም የሚገርመው ደግሞ በዚህ አስጸያፊ ግብረሰዶም ስነ ምግባር የሚያበረታቱ ድረገጾች እና በግብረሰዶማዉያኖቹ የታተሙ መጽሐፍቶች ቢኖሩ ስፈልግ ፤ ይህንን አግኝቻለሁ።EthiopiaLGBT.com (GBT የሚለው ገይ፤ባይሴክሹዋል፤ እና ትራንስ ጀንደር ማለት ነው)እና Ethiopiangay.com  እና ከዚህ ሌላ  “የሰዶም ነብሳት” የሚል የግብረሰዶም አበረታታች መጽሃፍ ታትሟል። መለስ ዜናዊ ሲሞት ከልብ ካለቀሱለት አልቃሾቹ እነኚህ ክፍሎች አንደኞቹ ክፍሎች ነበሩ። የዚህ ጉደኛ መጽሑፍ ደራሲ ቃለ መጠይቅ ለማንበብ አድራሻ ገብታችሁ አንብቡት። በጽሑፏ ላይ ወደ 500 የሚሆኑ የወንድ ሸርሞጦች አዲስ አባባ እንዳጣበቧት ይጠቁማል። “መሃረነ ክርስቶስ!!http://www.ezega.com/news/NewsDetails.aspx?Page=news&NewsID=2805

መደምደሚያ፡

  አሁን በቅርቡ “ጎልጉል” በተባለ የህዋ ሰሌዳ ጋዜጣ “ቀጭኑ ዘቄራ” በተባለ የብዕር ስም የተዘገበ የዛሬቱ ኢትዮጵያ ወጣቶች እና የወያኔ ባለሥልጣናት እና ካድሬዎቻቸው የተላበሱት የበሰበሰ የመንፈስ እና የባህል ወረርሺኝ በየዝግ ቤቶች እየዞረ የታዘበው አስገራሚ ዘገባ እንድትመለከቱት ላስነብባችሁ እና ልደምድም።

በሬ ለምኔየፍየል ቁርጥና ጥብስ መለያ ማስታወቂያ ነው። ከኦሎምፒያ ወደ መስቀልፍላወር በሚወስደው መንገድ ላፓሬዚን አለፍ እንዳሉ ወደ ግራ ሲታጠፉ ያገኙታል። ለጉዳዬ የሚመቸኝን በሬ ለምኔ ላመላክት እንጂ ብዙበሬ ለምኔቤቶች አዲስ አበባ ተከፍተዋል። ያዲሳባ ቀምጣላ ካድሬዎች፣ ልማታዊ ባለሀብቶች፣ አቀባባዮችና ባለጊዜዎችና አጫፋሪዎቻቸው እድሜ ለማራዘም ፍየል ይመገቡና ማታ ልቅ የግብረ ስጋ ለማድራት አይጨነቁም።
 





………እጠቆምኩት ቤት ስትገቡ ፍየል የሚያገላብጡት የሚታወቁ ባለሥልጣናትና ታዋቂ ካድሬዎች ናቸው።……አንዱንሮዚናዝግ ቤት ላስተዋውቃችሁ። ሮዚና ዝግ ቤት ማንም ዘው ብሎ አይገባም። ሮዚና ሲደርሱ እንደ መኖሪያ ቤት ጥሩምባ አሰምተው ከተንበሪውን የሚያስከፍቱ ደንበኞች ብቻ ናቸው።ደንበኞችስል እንግባባለን ብዬ አስባለሁ።

ሮዚና ወገቧ ሸንቃጣ፣ አንጀት የሚባል ነገር ያልሰራባት፣ ዳሌዋ ሰፊና ክብ፣ ሽክ ያለች፣ አንገቷ ውድ ነገሮች የሚቀመጡበት፣ ሽታዋ የሚያውድ፣ ዓይነ ርግቧ በቀለም እንደ ስዕል የሚዋብ፣ ሳሳ ያለ ልብስ የምትለብስ፣ እንግዳዎቿን በምትዘጋባቸው ቤት እየተዘዋወረች የምትቀበል አራዳ ነች። አስተናጋጆቿ በጣም ትንንሽ ልጆች ሲሆኑ ጸሃይ አይነካቸውም። ስራቸው ለሮዚና እንግዶች መስተንግዶ ሳይስተጓጎል መስጠት ነውየሚጠጣ ያቀርባሉ፤ ፍም እሳት አዘጋጅተው ቡና ያፈላሉ፤ ለማሟሟቂያ የቡናው ስነ ስርዓት በየክፍሎቹ ከተከናወነ በኋላ የጫቱ ሙቀት እየጨመረ ሲሄድ ሺሻ ይለኮሳል። ህጻናቱ ሺሻ እያሞቁ ደንበኞቹን ለማስተናገድ ከቡና ማፍያው በርጩማ ተነስተው ፍራሹ ላይ ሲወርዱ ከአባታቸው ጋር በሰንበት የሚጫወቱ እንጂ የስራ ግንኙነት ያላቸው አይመስሉም። ጫት እየቀነጠሱ፣ ሺሻ እያሞቁ ደንበኛቸውን ባፍ ባፉ መከደም ዋና ስራቸው ስለሆነ ተክነውበታል።……..ተጋብዤ የተመለከትኩት ክፍል የነበረችው ልጅ ሪታ ትባላለች። ንግግሯ የቀምጣላ ልጆች አይነት ነው። ስትስቅ አማርኛ አይመስልም። ጠይም ቀለሟ የጸዳ፣ ለጋ ነች። እንደ ጋባዤ አገላለጽጥፍሯ ይበላል ዕድሜዋ ከአስራ አምስት አይበልጥም። ቡና እንደጨረሰች ስስ ነገር ለብሳ ደንበኛዬ ጎን ቁብ አለች። መቃም ትችልበታለች። ጫት ላኪዎች በትዕዛዝ የሚልኩትን ጫት ትጠጣዋለች። ያለ ምንም ማጋነን የቅጠል አበላሏን ፍየል ብታየው በቅናት ምላሷን ትቆርጠዋለች። ምን አደከማችሁ ቅማ ታቃቅማለች። አልፎ አልፎ ሮዚና ለጉብኝት ብቅ ብላ ስትመለስ ቤቱን ታውደዋለች።ምርቃናው ሲጨምር ወዳጄ ቀስ በቀስ ከልጅቷ ጋር ተጣበቀ። እጆቹም ሁለመናውም እሷ ላይ ሆነ። በቃ ደረቱ ላይ ጣላት። ደረቱ ላይ አንጋሏት ሺሻውን ይምጋል። ብቸኝነቱ ሊውጠኝ ሲደርስ መሄድ አለብኝ ብዬ ተነሳሁ። ፒኮክ እንደምጠብቀው ነገርኩትና ተለየሁት። ህጻኗን ልጅ ደረቱ ላይ አንጋሏት ስመለከት ልጄን አቅፌ ሳስገሳው ትዝ አለኝ። የሚያስገሳት እንጂ የሚዳራት አይመስልም። እንዲህ ያሉትን ትውልድ አምካኝ ቤቶች ማጥፋት ቀላል ነው። ግን ተጠቃሚዎቹ ህግ አስከባሪና ህግ አወጪዎቹ በመሆናቸው አይታሰብም። አንዳንድ ዝግ ቤቶች በሲቪል ጠባቂዎች የሚጠበቁ ናቸው። አንዳንዴ ቤተመንግስቱንና ሟቹን የቤተመንግስት ነዋሪ ይጠብቁ የነበሩት በፈረቃ ይታደማሉ። ዝግ ቤቶች

ያራዳ ልጅበማለት ሳንቲም የሚለምኑ፣ ሎተሪ የሚያዞሩ የጎጃም ጉብሎች፣ የመንገድ ላይ ነዋሪዎች፣ ቀበሌና አድራሻ የሌላቸው ወንድምና እህቶች፣ ኑሮ ያዞራቸው የኑሮ ሰለባዎች ይታያሉ። አዲስ አበባ ሁሉን ተሸክማ እየመሸላት ይነጋል።
 

አፕሬቲቬን እየቀነደብኩ ስለ ሮዚ ቤት እያሰብኩ ቆዘምኩ። ቤቱ ውስጥ ያሉት ህጻናት የተመረጡ ናቸው። መልምሎ የሚያመጣቸውና ስልጠና የሚሰጣቸው አለ። በህጻንነታቸው ተከትበው ሺሻ ስር ሲርመጠመጡ በዛው ሱስ ይዟቸው ገደል የከተታቸው፣ ኖረውም ተስፋ ያጡ፣ ታመው የፈረደባት እናት እጅ የወደቁ አሉ። አገሩ እንዲህ ሆኗል። የኢትዮጵያ ህዳሴና የኢኮኖሚ እድገት ያተረፈው እንዲህ ያሉትን ዜጎች ነው። በርግጥ አገሪቱ ኢኮኖሚዋ አድጓል። ያደገው ግን ለዝግ ቤት ተጠቃሚዎች እንጂ ለሌሎች አይመስልም። እድገቱ የሚታያቸው በዝግ ቤትና ቤታቸውን ለሌሎች ዘግተው አገሪቱን እያለቡ ላሉት ይመስላል።

በሃሳብ እየቀባጠርኩ፣ አፕሬቲቬን እየሳብኩ ቆየሁ። ወዳጄ ተመችቶታል መሰል አልመለስ አለኝ። ፒኮክ ስለሰለቸኝ ደወልኩለትና እንስራ እንገናኝ አለኝ። ወደ እንስራ አመራሁ። እንስራ ደግሞ ሌላ ትዕይንት አለ።

እንደምን ከረማችሁ አሁን እንስራ ነኝ። እንስራ ለማታውቁ ላስተዋውቃችሁ። እንስራ ቦሌ ቴሌ አካባቢ የሚገኝ የምሽት ንዳድ ቤት ነው። በመለስ ሞት ምክንያት ተፋዞ ከርሞ ነበር። እንስራ ሲገቡ በጡንቸኞች ይዳብሳሉ። ፍተሻ መሆኑ ነው። እንስራ በር ላይ ተዳብሰው ሲዘልቁ ቀለሙ አይን ይወጋል። የደም ጢስ የሚጨስበት ይመስላል። እንስራ ውስጡ በዲጄ ይናጋል፤ ይነዳል። በምድር ቤት ውስጥ የሚደለቀው ሙዚቃ ከተለያዩ አቅጣጫ ከሚፈሰው የተደበላለቀ ቀለም ጋር አንድ ላይ ተዳምሮ የሲኦል ቤተ ሙከራ ይመስላል። መድረኩ ላይ እየተገመዱ የሚላቀቁት ተዋንያኖች እንግዳ ያስደነግጣሉ። ቁመታቸው ረጃጅም የሆኑ እንስቶች የተጠና ዳንስ ይተውናሉ።

እርቃናቸውን ያለ ልብስ የሚናጡት እንስቶች ሃፍረታቸው ላይ የቻይና ማራገቢያ የምትመስል አነፍናፊት ከመለጠፋቸው ውጪ ሁሉም ነገር እንደ አዳምና ሄዋን እንደ ድሮው፣ እንደ ጥንቱ ነው። እርቃን!! ዳንሱብልግና ተኮርይባላል። ወገብና መቀመጫን በማላመጥ ሲወዘውዙት ማየት ይመስጣል።ኮረኮንችየሚባለው ምንነቱ የማይታወቀውን አልኮል በሉት ዊስኪ እየተጋቱ አብረው የሚያውካኩትን ለተመለከተ አገራችን ውስጥ ችግር በቃል ደረጃም የሚታወቅ አይመስልም።
ከየአቅጣጫው የሚወርደው ባለቀለም ጨረር የሰውነታቸውን ቀለም እንደ እስስት ይቀያይረዋል። እየነደደ ወርዶ የሚቀንሰው ብርሃን ውስጥ ኮሮኮንች ያሳበዳቸው ይዘላሉ። አንዳንዶች መድረኩ ላይ ሳያስቡት ደርሰውበት ዓይናቸውን ከእምብርት በታች ቸክለው ይቅበዘበዛሉ። አንዳንዶች ጥንድ ሆነው መጥተው ብቻቸውን ያሉ ይመስል በሜዳ ላይ ወሲብ መሰል ዳንስ ተማርከው ዓይናቸው ሲቅበዘበዝ አለመስማማት የሚፈጠርበት አጋጣሚ አለ።

ስድስት የሚሆኑት ዳንሰኞች አጎንብሰው መቀመጫቸውን ሲወዘውዙት፣ ተሸብርከውእንካ፣ አምጣሲሉ፣ ሙዚቃው ሲያቃጥርየኮረኮንቹኮታ ሳይታወቅ ይበረታል። ከቦሌ አካባቢና ከዩኒቨርሲቲ መንደር የሚዝናኑ መስለው የሚነግዱ በተመሳሳይ ራቁታቸውን ከጊዜያዊ ጓደኞቻቸው ጋር ያስነኩታል። የዩኒቨርሲቲ ዳይ ካነሳሁ አንዴ ወደ አንጋፋው የዝሙት ገበያ ናዝሬት ፔንሲዮን ላምራችሁ።

ናዝሬት ፔኒስዮን እንደ ዛሬው ሳይሆንሻሞየሚባልበት ለሞት መጣደፊያ አልኮል መቸርቸሪያ ባር ነው። ናዝሬት ፔንሲዮን አካባቢው የጫት መቃሚያና የድለላ ስራ እምብርት በመሆኑ ሰው ስፍሩ ነው። ናዝሬት ፔንሲዮን በብዛት የንግድ ስራ ኮሌጅ ተማሪዎች እንደሚታደሙበት አንድ ወቅት መረጃዎች በይፋ ተሰራጭተው ነበር።

በተለይ ከክፍለሃገር የሚመጡ ተማሪዎች ከመንግስት የሚሰጣቸው ወርሃዊ ድጎማ ለቀለብና ለማደሪያ ስለማይበቃቸው ናዝሬት ፔንሲዮን ለስራ መሰማራታቸው ያደባባይ ወሬ ነበር።ይሞታል ወይ?” ያለች ተማሪም ነበረች። ውዱ መሪያችን፣ ነብሳቸውን ይማረውና፣ ስጋቸውን እየሸጡ የሚማሩ ተማሪዎችን አስተዋውቀውናል። እኚህ መሪያችን ናቸውልማታዊ ሴቶችን አፈሩ፣ ለሴቶች ልዩ ትኩረት አዘነቡየሚባሉት፣ እየተባሉ ያሉት። የኮሜርስ ብቻ ሳይሆን በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በተለይ ወደ ሀዋሳና አርባ ምንጭ ችግሩ ያስከተለው ቀውስ ቤተሰብን አንገት ማስደፋት የደረሰበት ደረጃ ደርሷል።

ቤተሰብ ልጄ ተምራ ተመረቀች ብለው ሲጠብቁ አጅሬው የቀሰፋቸው ጥቂት አይደሉም። ሃዋሳ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና የቡና ቤት ኮማሪቶች ገበያዬንወሰድሽብኝ ከፍተኛ ጸብ ውስጥ ሲገቡ ማየት የተለመደ እንደሆነ ሀዋሳ በነበርኩበት ወቅት ያስተዋልኩትና ያረጋገጥኩት ጉዳይ ነው። አንዴ እኔው ራሴ አብራኝ እንድትጠጣ ለጋበዝኳት ልጅ ይህንን ጥያቄ አቅርቤላትገበያችንን ዘጉትበማለት የስድብ ናዳ እያወረደች ነበር ሁሉንም ያጫወተችኝተማሪዎቹን ማለቷ ነበር። የሴቶች ተሳታፊነት አደገ ይሏል እንዲህ ነው። ነብስ ይማር።

ወደ እንስራ ልመልሳችሁ። እንስራ ጥቂት እንደቆየሁ ወዳጄ ያችኑ ልጅ አንጠልጥሎ መጣ። መጨለጥ ቀጠለ። አስቀድሞም ሲጠጣ ስለቆየ ለመስማት ጊዜ አልወሰደም። እንደውም እንደ አዲስ ጀበና መንተክተክ ጀመረ። ህጻኗን ከፊትለፊቱ ወትፏት በቁሙ እንደውሻ ይቀነዝራል። መብራቱ ስለሚመች ስጋት የለም። በቁሟ በዳንስ እያስመሰለ ፈትጎ ሊገላት ምንም አልቀረም። ይህ ሰው ያለውን ኃላፊነት እዚህ ከሚያደርገው ተግባሩ ጋር በማገናዘብ ሳስበው አመመኝ። እንዲህ ያሉ ብዙትልልቅ ሰዎችይመሩናል። በችጋር ይጠብሱናል። ሲሞቱ በደቦ ያስለቀሱናል። በጀት ከልክለው በረሃብ ያቃጥሉናል። ሲሞቱ ደግሞ በጀት መድበው ደረት ያስመቱናል።ያገራችሁን ህዳሴ ከእኛ ጠብቁእያሉ ያለ ሃፍረት ይሰብኩናል። አጽማቸውን እናመልክ ዘንድ ይመኛሉ። ከወዳጄ ጋር የትና እንዴት እንደተገናኘን አስታውቃለሁና ተረጋጉ። አሁን በፈጣሪ እጅ ላይ ሆኖ እየኖረ እንደሆነ፣ ከቤቱም እንደማይወጣ ሰምቻለሁ። ሮዚ አራዳዋ አለች እንዳማረባት። ህጻናቱ ግን ሰላም እንሰንብትና ሳምንት እንገናኝ!!”
መለስን ከቀጣ የፈጣሪ ቁጣ ያድነን። አመሰግናለሁ። ጌታቸው ረዳ getachre@aol.com
www.ethiopiansemay.blogspot.com