Tuesday, October 1, 2019

ዐቢይ አሕመድ ባድመ ላይ የሰቀለው የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ !!! (አቻምየለህ ታምሩ) October 1, 2019 Ethio Semay


ዐቢይ አሕመድ ባድመ ላይ የሰቀለው የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ !!! (አቻምየለህ ታምሩ)
October 1, 2019 Ethio Semay

ዐቢይ አሕመድ ባድመ ላይ የሰቀለው የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ !!!
አቻምየለህ ታምሩ

ዐቢይ አሕመድ ስለ ባድመው ጦርነት አውርቶ አይጠግብም። ሻዕብያን ካሸነፉ በኋላ በሳሞራ ትዕዛዝ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ የሰቀለው እሱ እንደሆነ ነግሮናል። ዛሬ ታዲያ ተረኛ ሲሆን ሕ ወጥ ያድረገውና ከሰሞኑ ደግሞ ባገሩ   ከፍ ብሎ በመውለብለቡ  ሕገ መንግሥታቸውን እንደሚጥስ የነገረን ባድመ ላይ እሱ ራሱ 1991 .. የሰቀለውን የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ነው። እንግዲህ! ዐቢይ አሕመድ  አሕመድ ሕገ ወጥ ሊያደርገው የሞከረው የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ የመንፈስ አባቶቹ ተላላኪ በነበረበት ወቅት ጌቶቹ ጥጋብ ንፍት አድርጓቸው ሱሪ ካስታጠቃቸው  ከሕዝባዊ ግንባር ሓርነት ኤርትራ ወይንም ከሻዕብያ ጋር  በተቆራቆሱበት  ወቅት  ጦርነቱን   አሸነፍን ብለው  1991 .. ከታች በሚታየው መልኩ  በባድመ ምድር  ከፍ አድርጎ  የሰቀለውንና ሌተናት ኮሎኔልነትማዕረግ  ያስገኘበትን ሰንደቅ ዓላማ ነው። ልብ በሉ! ወያኔዎችና ኦነጋውያን  ሕገ መንግሥታችን  የሚሉትን የሕወሓትና የኦነግ  ፕሮግራም  በኦፊሴል  በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የጫኑት በሕዳር 1987 .. ነው።  ከታች  በተንቀሳቃሹ ምስሉ  ላይ የሚታየውን   የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ የመስቀል ሥነ ሥርዓት በባድመ የተካሄደው ግን  1991 .. ነው። ይህ ማለት 1987 .. የጫኑብንን ሕ መንግሥታቸውን ዐቢይ አሕመድ ራ   1991 .ልሙጡን ሰንደቅ ዓላማ ባድመ ላይ ሲሰቅለው ጥሶታል ማለት ነው። ዐቢይ አሕመድ አክብሩልኝ የሚለው ሕገ መንግሥት እንግዲህ እሱ ራሱ ባፍጢሙ የደፋውን ደንብ ነው። (posted on Ethio Semay)


No comments: