ነፃ
እና ኩሩው የኢትዮጵያ ሕዝብ አሁንም በፋኖ ፤ በወያኔ፤ በኦነግ እና በአብይ ኦሮሙማ በጣሊያናዊ
የጎሳ አስተዳደር ሰንሰለት ታስሮ እየተጎተተ እሰከመቸ ይቀጥላል?
ጌታቸው ረዳ
Ethiopian Semay
11/13/2025
በዓለም ጂኦግራፊያዊ
ክልል ውስጥ ራሱን የቻለ፣ ነፃ እና ኩሩ ሕዝብ ሆኖ እስከ 1966 ዓ.ም ድረስ
ኢትዮጵያውያዊ ዜጋ አንዳንድ ችግሮች ቢሮሩትም እንደዛሬው ለክፋት
የሚጥል የዘር
እና የባህል ወረራ ሳይደረግበት ህልውናውንና
ነፃነቱን ተጠብቆለት ቆይቶ ሳይታሰብ በድንገት በ1966 ነባሩን ሥርዓት ተወግዶ “በኮሚዩኒዝም” ሥርዓት ሲተካ ወደ ጥቃት ገበያ
ተጎትቶ ገባ።
ከዚያ ዘመን ጀምሮ እስካሁን ድረስ ነጻነቱ ተወስዶበታል። ለጥቃት ገበያ ያዘጋጁት ደግሞ ደጋገመን እንደገለጽነው «ወያኔ ኦነግና ሻዕቢያ» ሲሆኑ ያንን የፋሺስቶች ፖለቲካ አፈርሳለሁ ብሎ ፤ በብዙዎቻችን ግምት ለኢትዮጵያ ሕልውና መከታ ይሆናል ብለን ስንጽፍለት የነበረው “የአማራ ፋኖ” ኢትዮጵያዊ የትግል ፐሮግራም እና አመራሮችን ሳያዘጋጅ በወያነ ጦርነት የማረከውን ጠመንጃ ሳያስበው “ጠመንጃህን ፍታ” ሲባል ድንገት ባንኖ ወደ ጫካ ሲገባ ለ27 አመት ሲጋተው የነበረው አውራጃዊና መንደርተኛዊነት በሽታ ተጋብቶበት “የነገድ ፖለቲካ” ተረካቢ ሆኖ «የንገሥታት ልጆች ነን፤ በእናቶቻችን ማሕጸን እያለን ለመሪነት የታጨን ልዩ አፈጣጠር ያለን አማራዎች ነን ፤ወደ እሚል ፈጹም በቅዠት የሚፎልል ፋሺስታዊ የሆነ “ኢትዮጵያውነትን” የሚያኮሥስ መንደርተኛ በመሆን “ሞቴ ከወያነ እና ከሻዕቢያ በፊት ያድርገው” እያለ ለጸረ ኢትዮጵያ ኃይላት (ፕሮክሲ) ወኪል ነኝ የሚል አዋጅ አውጆ የአገራችን አደጋ ተጨማሪ አካል ሆኖ ተከስቷል።
የኢትዮጵያ ሕዝብ በአዲሰ አበባ እና በእየ ክፍለሃገሩ “በኡሉሙናቲና በግበረሰድማዊ ቡደኖች” እየታፈነ በረንዳ አደር ሕጻናትና ጎልማሶች “ኩላሊታቸውና ልባቸው” ለሽያጭ፤ ለግድያ እና ለወረበሎች እገታ እየተዳረገ ጭንቅ ውስጥ ሲገኝ ፡ ጫካ ውስጥም ፋኖ የተባለ “ፐሮክሲ ሚሊሺያ” ጫካ ከገባ ጀምሮ የአማራ ሕዝብ ስቃይ አባብሶ እርስበርስ በቡድን ተከፋፍሎ ሲጋደልና ባንክ ሲዘርፍ ሕዝብ ሲያግት፤ ትምሕርት ቤቶች በመዝጋት “የጫካ አናርኮ ፋሺስት” ወደ መሆን ተሸጋግሯል ስንል “አማራዎች” ይህንን ሃቅ ላለመቀበል “ኮግኒቲቭ ሪዞናንስ” ውስጥ ገብተዋል።
“ነባሩ የአማራ ማሕብረሰብ”
ከጥንት ጀምሮ ስፍር ቁጥር በሌላቸው መከራዎች ከውስጥም ከውጭም ባላንጣዎች በተደጋጋሚ በገሃድና በተዘዋዋሪ ለጥቃት የተመዘገበ ማሕብረሰብ
ነው። ቢሆንም ባአንድም ሆነ በሌላ መልክ ያጋጠሙት ፈተናዎችን
በመጋፈጥ ለተግዳሮቶች ምላሽ በመስጠት በጽናት የቆየ ሕዝብ ነው።
ባለመታደል ሆኖ (የገዛ ልጆቹ) የአምሐራ እና የአገው ወጣቶች
በጥቃቱ ተዋናይ እና “ፐሮክሲ/የወያነና ሻዕቢያ ወኮሎች” ሆነው ዛሬም በዛው የአደጋ
ጉዞ እይተጓዙ እያየሁ ነው። ይህ ማሕብረሰብ ለመታደግ እንደ ዜጋ ያለኝን ያህል መራራ የትግል
አስተዋጽኦ አበርክቻለሁ። ሆኖም ልጆቹ ባሳዛኝ ክስተት ዛሬም ለበርካታ አመታት ጭቃ
ውስጥ ሲጨማለቁበት በነበረው የ27 አመት መዳከር ዛሬም ‘በጫካም ‘በቲክ-ቶክ እና ‘ዩ-ቱዩብ’ ካንደበታቸው የምንሰማው ክርክርና
መልዕት ካለፈው ሊማሩ አልቻሉም።
የአማራ ጠላቶች “ወኪል” (ፐሮከሲ) ከመሆን በመቆጠብ ፤ «ወላጆቻችን ተማርከዋል እኛም ተደግመናል» በሉ እያሉ ኢትዮጵያዊያን (ሙርከኞችን) (የገዛ ነገዳቸው ጭምር) ባልተቀጣ ስድ የወረበላ ባሕሪ በማስጨነቅ፤ እንዲሁም የሽፍቶች ባሕሪ የተላበሰ የትግል ጔድን ከማሳደድና ከመግደል ተቆጥቦ፤ በራስ ትግልና በሕዝብ በመተማመን የአማራ ተግዳሮቶች በብቃት መክቶ ኢትዮጵያን ቀዳሚ የትግል ዓርማ አድርጎ ካልታገሉ በድል ለመውጣት አይቻልም።
ፋኖዎቹ በብሔራዊ ሰንደቅ-ዓላማ ከመጠቅለልና ግድንግድ መሰቀል ደረታቸው ላይ ከማንጠልጠል ባለፈ
አገራዊ ዓላማ የላቸውም።
በአውራጃና በመንደር የተከፋፈሉ ፋኖዎች ተግባራዊና
ዘላቂነት ያለው አገራዊ ራዕይ ሰለሚጎድላቸው እኛ አማራዎች ተጨቁነናል በሚል “ሽፋን” ብቻ ጠመንጃ ለታጠቁ መሪዎች እና “የገቢ ምንጭ ለሆነላቸው 24
ሰዓት “በቲክ-ቶክ” ተጥደው በነገድ ስም ለሚነግዱ ‹‹የነገድ ኢንተርፕረነሮች›› (ethnic entrepreneurs) ሲሳይ ሆኖ እያየን ነው። (ለምሳሌ ለመጥቀሰ “አንድ
አማራ /አኪላ... ወዘተ የሚባሉ RT-Ethiopia በሚል “ዩ ቱዩብ” የሚተላለፈው እጅግ አደገኛ ፋሺስት ኤለመንቶችን አድምጡዋቸው
፤ትገረማላችሁ።
ሰማይ ሰማያት የሚንሳፈፉ መሃይምነታቸውና ጉራቸው “Snobbishness”, “naked egoism” “hubris”, “Chaotic mind” የሚያስተጋቧቸው የተመሰቃቀለ አዕምሮአቸው ለከት የለውም።)
አሁን እያየናቸው ያሉት ፋኖዎች ጨቆኑን ከሚሉዋቸው ጨቋኞቻቸው ተሽለው ሊወጡ አልቻሉም። እየጠፋ ያለውን ሕዝብ ሸክሙን እና ስቃዩን የሚያቃልል አመራርና ቡድን ይፈልጋል። አሁን ያለው ፋኖ ራሱን ካልፈተሸና “አማራ” “አማራ” የሚለውን የመነገጃ “መፈክር” ሰከን አድርጎ “ሃገራዊ ራዕይ” ያነገበ “ፈቃደኛ የሆነ” ሁሉንም ዜጋ ይሚያሳትፍ ትግል ካልጀመረና ካላሳተፈ በተያያዘው የዕብደት መንገድ ከቀጠለ የጫካ ጀብደኝነት ከማሳየት አልፎ እየጠፋ ያለውን ሕዝብና የታሰሩ ሃገራዊያን መሁራንን ማዳን አይቻልም።
ለሕብረተሰቡም ምክር አለኝ፡
የተንሰራፋውን ጎሰኝነት ለመቋቋም ከነገድ ፖለቲካ የፀዳ ዕቅድና የተባበረ ክንድ ማድረግና በጠመንጃ ለሚያስፈራሩ ፋኖዎችም ወያንዎችም፤ ኦነጎችም ሆኑ የኦሮሙማው ወኪሎችን በቃችሁ ማለትና ምግብ መከልከልን አካባቢያቸው እንዳይደርሱ ማድረግን ራስን አስትባብሮ መሪን መፈለግና “አገራዊ ራዕይ” የሌላችውን የጠላት ወኪሎችን “ፕሮክሲዎችን” መጋፈጥን መለማመድ አለበት። በደርግ ጊዜ ትግራይ ውስጥ እያለን ይህንን ነበር ሰናደርግ የነበርነው። ያለ ድፍረት ምንም መራመድ አይቻልም።
በአሁኑ ጊዜ በሕብረተሰባችን ሕይወት እየታየ ያለው ፖለቲካዊ፤ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ችግር ለመፍታት የፖለቲካ መሪ በመታጣቱ (ታላቁ እስክንድር የተቻለውን አድርጎ ሕዝቡ አልነሳም ሲለው ጥሎት ወደ ጫካ መሄዱ ሊመሰገን እንጂ መውቀስ አይቻልም። እስክንድር በጀመረው “የትግል ድፍረት” ሕዝቡና “የፖለቲካ/ተቃውሚ/ መሪዎች” ተሳታፊዎችና አጋሮቹ ሆኖው ቢገኙ ኖሮ “መጠነኛ ኦክሲጅን” እንተነፍስ ነበር።አሁን ባሳዛኝ ሁኔታ እስክንድርን ከማመስገን ይልቅ ጥላሸት መቀባትና እሰከ መግደል ተመኙት።የፖለቲካ ረዢም አመታት የትግል ትዝብቴ እንደ እስከንድር ነጋ ያለ ሃገራዊ ፖለቲከኛ የስም ማጥፋትና የሃሰት ዘመቻ (በግራም በቀኝም በፊትም በኋላም) የደረሰበት ፖለቲከኛ አይቸም ሰምቸም አላውቅም። ሕዝቡ መርዘኛና ምቀኛ ፤ የታገለለትን አርበኛ የሚጥል፤ አርበኛ ገዳይ መሆኑ የታዘብኩብት አጋጣሚ ነው።
የእስክንድር ወፍራም ቆዳነትና የፖለቲካ Astute ነት “ሸብረክ አለማለቱ” የሚገርም
ጥንካሬው ሳያደንቁ ማለፍ አይቻልም። የጽናቱ የመንፈስ ብርቱነት በሃገራችን ታሪክ ከቶ ታይቶ አይታወቅም!! ታዲያ እንዲሀ ያለ ጠንካራ ሰው በጫካም፣ በሃገርም ተከታይ አለማግኘት “በፖለቲካ መዝገብ አዲስ ክስተት” ያደረገዋል።
ለ35 አመት የታየው ይህ የመሪ እጦት (leadership
bankruptcy) አፋጣኝ መፍትሄ ካላገኘ የኢትዮጰያ ሕዝብ ካለው ቀውስ ወደ ባሰ ቀውስ ገብቶ “እንደ ሱዳን” የሃገራችን የመኖር ዕድልዋም አስተማማኝ አይሆንም።
መሪ ካጣ፤ ሕዝቡ ከታጠቁም ካልታጠቁም ፤ በጎሳ የጣሊያናዊ ፖሊሲ እያያስተዳደረን ካለው ከመንግሥት ቅኝ ገዢ ሥርዓትም ራሱን ከነዚህ “የመከራ መሪዎች“ ራሱን ነፃ ለማወጣት በራሱ መንገድ መወጣጫው መፈለግ ይኖርበታል።
ነፃ እና ኩሩው የኢትዮጵያ ሕዝብ አሁንም በፋኖ ፤ በወያኔ፤ በኦነግና በአብይ ኦሮሙማ በጣሊያናዊ
የጎሳ አስተዳደር ሰንሰለት ታስሮ እየተጎተተ እሰከመቸ ይቀጥላል?
ጌታቸው ረዳ Ethiopian
Semay
.jpg)
No comments:
Post a Comment