የኢሳያስ ድመት
ጌታቸው ረዳ
(Ethiopian
Semay) 5/3/25
በወላጆቻችን በአክሱማውያን ፤ ንጉሥ አምደፅዮን ፤ ዘርአ ያዕቆብና በዮሐንስ ፤ በአሉላ በሃይለሥላሴና በመንግሥቱ ጊዜ...መሬታችንና ይዞታችን የነበረች ጥንታዊትዋ የሚሊዮን ዘመናት የቅድመ አያቶቻችንና አያቶቻችን ደምና አጥንት የተገበረባት “ባሕረ ነጋሽ” ፤ የጣሊያን ስሪትዋ የዛሬዋ “ኤርትራ” ከምቾት ወደ ባርነት በመጎተት “ሃገር ተብላ” በመጠራትዋ ብቻ ከፈነደቁት “የኢሳያስ ፖለቲካ አምላኪዎች” ውስጥ አንድዋ በፎቶ የምታይዋት ሰላም ኪዳነ (PhD) የተባለች “የትሯማ ተመራማሪትና ኢሳያስን የምቃወም የኤርትራ አክትቪስት” (ነኝ የምትል) እንግሊዝ አገር ሰለ እምትኖር ቴድሮሰ ጸጋየ “ርዕዮት ሚዲያ” በሚያዘጋጀው ሚዲያ ቀርባ ሰለነበርቺው እንግዳ እንነጋገራለን።
ይህች ልጅ የኢሳያስ ተቃዋሚ
ነኝ ትበል እንጂ “ሕሊናዋ “በእስቶክሆልም ሲንድሮም” የተነጠቀች «ዓሰብ ለኢትዮጵያ ከመትስጥ የኤርትራን ሕዝብ ሞት፤ ስደት ፤ድህነትና ግርፋት እየቀጠለ “እየቀፈፈኝም” ቢሆን የኢሳያስ ባርያ መሆን ይሻለናል» ስትል በርእዮት ሚዲያ ቀርባ “ኢሳያሳዊት ድመት” መሆንዋን “እየቀፈፋትም” ቢሆን ነግራናለች። (ልብ በሉ ፤ እስዋ በተንደላቀቀ ህይወት እንግሊዝ ሃገር ነው የምትኖሮው፤ ወላፈኑ አይሰማትም)
ተወያዮችን መልሕቅ ውስጥ የማሰገባት ብርቱ ችሎታ ያለው ቴድሮስ ፀጋየ እዚች ልጅ ጋር ሲደርስ
እንዴት እንደተሞኘ ባይገባኝም ፤ ይህችን ብልጣብልጥ “rare
voice” ሲል አሞካሽቷት ሰምቸው ፤እኔ ደግሞ ከኤርትራ ምሁራን “ምን የሚል ያላሰሙን አዲስ ድምጽ ታሰማን ይሆን?”ብየ ባደምጣት “ታጥቦ ጭቃ፤ የኢሳያስ ድመት ሆና ቁጭ!”።
አሳዛኝ የሚያደረገው የኤርትራ እንቆቁልሽ የዛሬዋ
ኤርትራ የተመሰረተቺውና የተመራቺው በኢትዮጰያዊያኖቹ “በትግራይ ተወላጆቹ በወልደአብ ወ/ማርያምና በኢሳያስ አፈወርቂ ቅኝት እንጂ
“በሃገሬው ተውላጆች አለመሆኑ ነገሩ እንቆቁልሽ ያደርገዋል”።
ወደ ባርነት የገባችው “ባሕረ ነጋሽ” “ሞታ ተገንዛ የሞተችበት” ቀን በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችዋ ጥለዋት በመፈርጠጥ “የሸሹዋት” ይህች ልጅ ብቻ ሳትሆን የኤርትራ ውሾች ሳይቀሩ ተሰድደው በትግራይ መጠለያ ጣቢያ ሲመዘገቡ በዜና ተመዝግቦ አድምጠናል።
“የሲኦል ኗሪዎች ለመሆን” ጥቂቶች በሚያላገጡባት ምድር "ኤርትራ" የምትባል የኢሳያስ ስሪትና ንብረት ለመፍጠር ነፃነታችን ተጎናጽፈናል ቢሉም “የነፃነት ጣእም” ያልገባቸው ፤ ስደት ፤ባርነትና ሞት “እንደ ነፃነት” የሚያጣጥሙ ሕዝቦች በዓለም ውስጥ ኤርትራኖች ብቻ ሆነው ስንመለከት እጅግ አስገራሚ ነው።
የሳሕል ተራራ “ጋንግሰተሮች” የሚንደላቀቁባት ምድር ኤርትራ በሚያሳዝን ሁኔታ ነፃ-አውጪዎቻቸን ናቸው ብለው “በዕልልታ የተቀበላቸውን ሕዝብ” ባርያቸው አድርገው የተቃዋሚ ኤርትራን ሬሳ ወደ አገር እንዳይገባ በማገድ፤ ሲያሻቸው፤ መግረፍ፤ ሲፈልጉ የሕክምና ዶክተሮችን “በኤይድ ቫይረስ” ወግቶ መበከልን ኤርትራኖች ራሳቸው የሚዘገቡዋቸው ዜናዎችን ስንመለከት፤ እውነትም የነፃነት ትርጉም “ኤርትራኖች ዘንድ ስትደርስ ትርጉም የላትም” የሚል ድምዳሜ ደርሻለሁ።
ታዲያ ይህች ማፈርያ የሆነች ሴት ግን በተዘዋዋሪ ንግግርዋ ስንተረጉመው “ዓሰብ ከማጣት
ኢሳያስ እየገዛን መቀጠሉ የሕክምና ዶክተሮቻችንን “በኤች አይ ቪ አይድ ቫይረስ” ቢበከሉ እየቀፈፈኝም ቢሆን ደስተኛ ነኝ” እንደማለት
ስትል መስማት እውነትም የነፃነት ትርጉም “ኤርትራኖች ዘንድ ስትደርስ ትርጉም የላትም” የምለው ለዚህ ነው።
በሕዝቡ ላይ “የመናገር ነፃነትን መንፈግ ፤የስደት፤የሞትና የፍርሃት” ቀንበር የጫኑበትን “የሳህል ጋንግስተሮች” የነፃነት ህይወት “ኤርትራኖች” የገዢዎቻቸውን “የነጻነት ቀን” ፤ የነፃነታችን ቀን ነው ብለው እየጨፈሩ መመልከት እውነትም “ባሮች ጌቶቻቸው ሲታመሙ የሚታመሙ፤ ሲጨፍሩ አብረው የሚጨፍሩ፤ ሲስቁ አብረው የሚስቁ” አዳዲስ ባሮች በምድር ይከሰታሉ ተብሎ በትንቢት የተነገረው በኤርትራኖች ላይ አየነው። ይህ የተከሰተባቸው ምክንያት የኢትዮጰያ ሕዝብ ዕንባ እና የእርግማን ውጤት ነው።
የትግራይ ተወላጆች የሆኑት ኢሳያሰና ወልደአብ ወ/ማርያም የፈለሰፉትና የመሩት የኤርትራዊነት ፖለቲካ ከሚያመልኩ የሳሕል ፖለቲካ ባርያዎች መካከል አንድዋ ይህች ኢትዮጵያ ውስጥ ያደገች አሰመራ ድረስ ሄዳ ለስርዓቱ ስትሰግድና ስትጨፍር የነበረች ዛሬ እንግሊዝ ሃገር በስደት የምትኖር “የኢትዮጰያ ጡት እየጠባች ያደገች
ጡት ነካሽ ከሃዲት” ኢሳያስን አምርሬ እቃወማለሁ ብትልም፤ ውስጠ ሕሊናዋ
ስንመረምር ግን «የሕዝቡ ስድትና ሞት፤ ግርፋትና ባርነት ቢቀጥልም ዓሰብ ከማጣት “ቅር እያላትም ቢሆን” በኢሳያስ ባርነት
ቀምበር ውስጥ መኖር መምረጥዋ፤ ኢሳያስ ቢሞትም የታጥቁ የሱ ጋንግስተሮች፤ ወይንም ልጁ ቢገዛት “ቅር እንደማይላት” ንግግርዋ
የማሃይማንና የነውር ንግግር መሆኑን እያወቅችና “እየቀፈፋትም” ግልጽ አድርጋለች።
ይህም በየ BBC እና Al Jazeera እንዲሁም በየ አደባባዩ በስሜት የሚነዱ የዋሆች በተሰበሰቡበት
አደባባይ ላይ ወጥታ ኢሳያስን እቃወማለሁ እያለች የድመት ጩኸት በታሰማም ወዲያም ተርጉሙት ወዲህ የንግግርዋ ትርጉም የሚነግረን “ዓሰብ ለኢትዮጰያ ከሚሰጥ “ኢሳያስና ጋንገሰተሩ እስከዘላለሙም
ቢቆዩ እነሱ ቢረገጡኝ እመርጣለሁ"ማለትዋ “የኢትዮጵያና የትግራይ ጅብ ከሚበላኝ በኤርትራዊ ጅብ ብበላ ይሻለኛል” ዓይነቱ አባባል የተማረቺበት የዘረኛነት ጥግ ማሳያ ነው
(a typical Eritrean racist character)።
ነፃነታቸው ባወጁ በማግሥቱ ስለ ነፃነታቸው ምን እንደተሰማኝ ‘ራዲዮ ኢትዮጰያ’ ጠይቆኝ ነበር።
እንደ “ሰላም ኪዳነ” የመሳሰሉ “Good for nothing” ደግሞ ኢትዮጰያ በድላናለች ቅኝ ገዢያችን ነች ብለው ነፃ ወጥተናል ብለው ላንመለስብሽ ብለወ “ድንጋይ” ወርውረውባት “በዘፈንና በግጥም የሰደቡዋትን”፤ “ያወገዝዋትን” ኢትዮጵያ "ነፃ በወጡ በሳልስቱ" እግርዋ ላይ ወድቀው ተሳልመው፤ጥገኝነት ስጪን ብለው "ሊለምኑ" ነው: ብየ ነፃነታቸው ባወጁ በማግስቱ በራዲዮ ኢትዮጰያ ተጠይቄ የመለስኩት መልስ ነበር”።
በወቅቱ ያመነኝ አልነበረም፡ ኤርትራዊያኖቹና ትግሬዎች ‘ማርና ወተት እንደሚዘንብላቸው ሲሰብኩና ያምኑም ስለነበር፤ እነሱ ቀርቶ የኛዎቹ ኢትዮጰያዊያንም በፕሮፓጋንዳ ተጠልፈው ሰለነበር አላመኑኝም።እንዳልኩትም እንደገና አንመለስብሽም" ባልዋት ምድር አዲስ አበባ ውስጥ “አህዮች” እያሉ ኤርትራ ውስጥ ከጨፈጨፍዋቸው የአማራዎች ጉራጌዎች ፤ ኦሮሞዎች፤ የጋምቤላዎች የጋሞዎች ፤የሶማሊ…አገር መዲና አዲስ አበባ ውስጥ ጥገኛ ሆነው ለምነው ገብተው ሰው እያስቆሙ ሲዘርፉ፤ ሲጨፍሩ የኢሳያስ ባንዴራ እያወለበለቡ ማየት (ዕድሜ ለአሜከላው አብይ አሕመድ) ለኛ ኢትዮጵያዊያን “ሞትና ውርደት” እንደሆነ ተሰምቶናል። (ሰለ እነሱ በናፍርላቸውም/ሓፍረቱና ሞቱ የነሱ ቢሆንም)።
እርግጠኛ ነኝ ዶ/ር ሰላም ኪዳነም ያሳደገቻት “አመድ አፋሽዋ” ወደ እምየ አዲስ አበባ እየህደች ዛሬም እየህደች ትጨፍር ይሆናል። ኤርትራኖች ዘንድ “ሓፍረት የሚባል የለም” ኢትዮጰያዊያኖች ምን ይሉን ይሆን አይሉም። ለነገሩ “አህያ” ተበሎ ተሰድቦም ፤ንብረቱ ተነጥቆም ዝም የሚል “ገራገር ሕዝብ” መሆኑ ያውቃሉና ፤ ሐፍረት የላቸውም (በዛው ላይ "ተራራው ጋረደኝ" ፤ “ጓል አሰመራ” እያለ የሚዘፍን አቃጣሪ ኢትዮጰያዊ አዝማሪም በብዛት አለ።
ዳሩ ግን እነሱ ምን ያድርጉ? ድሮ በወያኔ ዛሬ ደግሞ በአብይ እነኚሀ ሁሉ “ባንዳ መሪዎች”
እስካሉ ድረስ “በአህዮች አገር” እንዲጨፍሩ ተፈቅዶላቸዋልና ነፃ በሚልዋት ነፃ ኤርትራቸው ውስጥ ያልተፈቀደላቸው ነፃነት አዲስ አበባ ውስጥ አገኙዋት! “በሞኞች መንደር ቀምበር ይቆረጣል” ይባል የለ! (የነ ዶ/ር ሰላም ኪዳነ ምሳር)
የሚገርመው ደግሞ ኢትዮጰያዊያን ሆነው አዲስ አበባም ውጭ አገርም ሆነ በየ ቲክ-ቶኩ የኢሳያስ
ባንዴራ በጋራ ሆነው ከድኩማን «ማይም ኢትዮጰያዊያን» ጋር ትከሻ ለትከሻ ገጥመው እስክስታ እየመቱ ሲያውለበልቡ ማየት የሚገርም አስደንጋጭ
ትዕይንት ነው።
“Wherever there is an ignorant
mass, you will see a flag of an ignorant leader fluctuating with glory!” “መሃይም ሕዝብ ባለበት ቦታ ሁሉ የመሃይም መሪ ባንዲራ በክብር ሲውለበለብ ይታያል!”
(መህመት ሙራት ኢልዳን) እንዳለው
ሁሉ
መሃይም ሕዝብ ባለበት አዲስ አበባ ውስጥ ፤ያውም የባሕር በራችን የዘጋንን የመሃይም መሪ ባንዲራ በክብር ሲውለበለብ ከማየት የሚያም ነገር የለም!”
ማጠቃልያ
ለወ/ሮ ሰላም ኪዳነ እና መሰሎችዋ የምለው ነገር ፤በትግሬዎች መሰሪ ፖለቲካ ምክንያት ለናንተ ወግነው
ኢትዮጵያን የባሕር በር አሳጥዋት። “ዓሰብና ምፅዋ የዓረቦችና የእስራኤል
አይሁዶች መናሃርያ ሆኖው እንዲቆዩ የኢሳያስን መኖር መርጠሻል።
እኛ ደግሞ የምንለው «ዓሰብም ምፅዋም ነፃ የወጡት በጉለበታችን ነው እንጂ በብሩር (በብር) ሳሕን ያቀበለን የለም» ብሎ መሪሽ እንደሚለው ሁሉ፤-
እኛም «በሃይል የኄደ በሃይል ይመለሳል” «ሕግ ያልገዛው ነፃነት ሃይል ይገዛዋል»፡ እያልን የዓሰብም ሆነ የምፅዋ ጥያቄ አንድ ቀን ፤ “አምደፅዮን” “ዘርዓ ያዕቆብ” እና “አሉላ” መሳይ “ሃገራዊ መሪ” ለወደፊቱ ብቅ ሲል ያኔ ዕንቅልፍ ስታጡ «ሰላም ያሳጣችሁ ዕለት» ሳትወዱ ድርድር ገብታችሁ ዓሰብን ወይንም መላዋን ምድሪቱ ታሰርከባላቸሁ። እንዲህ የ60ዎቹ ቀልድ እየቀለዳችሁማ አትኖሩም!!!
በመጨርሻም ኤርትራ የሞተችበት ቀን የነፃነት ቀናችን እያላችሁ በየቀኑ ትበጠረቃላችሁም ፤ ታከብሩታላችሁም፡ እንኳን የሞታችሁበት፤ ለስደት የዳረገቻችሁ ነፃነታችሁ ቀን አደረሳችሁ! ለእኛ ግን የተሞኘንበት ቀን ሲሆን ፡እናንተ ግን ሁሌም ዕድለኞች ናችሁና ተሰድዳችሁ የምትጨፍሩባት ኢትዮጵያ በማግኘታችሁ “ከመሞት መሰንበት” ይሉታል ነፃነት ማለት ይህ ነው።
ኢትዮጵያ ሆይ “የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ” የተባለው ለካ ለእንደዚህ ዓይነት ብልጠትም ነው።የጊዜ ጉዳይና ሃገር ወዳድ መሪ ማጣት እንጂ እንዲህ የ60ዎቹ ቀልድ እየቀለዳችሁማ አትቀጥሏትም!!!።
ጌታቸው ረዳ

No comments:
Post a Comment