Tuesday, April 29, 2025

እፊታቸን ላይ ውሃ እንደ ያዘ እንስራ ፍርክሽክሹ የወጣው የፋኖዎቹ ትግል አምሐራ አምሐራን መግደል ጀምሯል! ነገ የገደሉትን ሬሳ ወደ መጎተት ተዛውሮ እንዳናይ ያሰጋል ጌታቸው ረዳ Ethiopian Semay 4/28/2025

 

እፊታቸ ላይ ውሃ እንደ ያዘ እንስራ ፍርክሽክሹ የወጣው የፋኖዎቹ ትግል አምሐራ አምሐራን መግደል ጀምሯል! ነገ የገደሉትን ሬሳ ወደ መጎተት ተዛውሮ እንዳናይ ያሰጋል

ጌታቸው ረዳ

Ethiopian Semay

4/28/2025


“አድማጭ የታዘበኛል” የማይሉ ሲዋሹ እጅግ እስከ-ጥግ ድረስ የሚቀደዱ፤ የተቃዋሚያቸውን ስም ለማጠፋት ሲፈልጉ  ራሳቸውን ለትዝብት የሚጥሉ፤ ዓለም ይዘግቡዋቸውን የሃገራችን ታሪኮችን የሚያጠለሹ “የወያነ ፤ የኦነግ/አብይ-ኦሮሙማ እና ፤ የሻኧቢያ መሪዎች” የውሸት ባሕሪ ለብዙ አመት ታዝበናቸዋል። ዛሬ ደግሞ በጎበዝ አለቆች የሚመሩ ፋኖ ብሎ ራሱን በውሸት የሚኮፈስ የነዚህ ደረጀቶች ባሕሪ” የተላበሰው የጎጃሙ የፍሺስት ዱርየ ታጣቂዎች መሪ የሆነው የዘምነ ካሴ “አፈቀላጤ” ነኝ የሚል “ጮርቃ” የመገዳደል ጦርነት እንዳወጀ ሲናገር አሁን ጥዋት ሰማሁት (አዲስ አዋጅ ባይሆንም)።

ይህ «ትንሽ ሰው» የመግደል አዋጅ ብቻ ሳይሆን ሲዋሽም ዳርቻ የለውም።፡እስክንድርና ጋዶቹ የሚመሩት “የአምሐራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት” “ድርጅቱ ስላዳከምነው የትጥቅ እርዳታ የሚያገኘው ከአብይ አሕመድ ነው” ሲል “አድማጭና ታሪክ” ይታዘበኛል ሳይል ሳይሰቀጥጠው የድርጅቱን መሪዎችና የድርጅቱን አወቃቀር ዓላማና ስም በውሸት ከማጠልሸቱ ባሻገር፤ ይህ ለአምሐራና ለኢትዮጵያ የቆመ ብቸኛ የሽምቅ ታጣቂ እኛ ብቻ ስለሆንን “መደምሰስ አለበት፤ ጀምረናቸዋል፤ ጦርነት ገጥመናል፤ አዳከመነዋል፤ እናጠፋቸዋለን!” ሲል በፋሺት የብሔረተኛ ድንፍታ ሲጎረን ዛሬ ጠዋት ሰማሁትና ገረመኝ።

 ከበዙ አመታት በፊት የአንድነት ሃይሎች ነን ሲሉ የነበሩ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ድረጀቶችና ምሁራን “ቤተ ክርስትያናት ሲቃጥሉ የሚያቃጠለው ወያኔ ነው ፤ ሃየማኖት የሚጻረር  ሃገራችን ውሰጥ ካለ ወያኔ ሌላ የለም እያሉ “ከኦነግ” እና ‘’ከእስላማዊ ኦሮሞ ነጻ አውጪ” ግምባር ጋር በየ ሃገራቱና ከተማዎች” እያዞሩ ባንዴራቸውን በየ አዳራሹ እያስጌጡና ገራገሩን አድማጭ እያስጨበጨቡ ጥብቅና ቆመው ሳያቸው በነበረው ወቅት ሰልገረመኝ «በዚህ ቀውስ ውስጥ እንዴት ልንገኝ ቻልን?» በሚል አንድ ጽሑፈ ጽፍይ ነበር።

አሁንም በደጋሚ የአምሐራን ሕልውና እጠብቃለሁ ብሎ “በሚያስቅ ጉጉት” ራሱን ለማንገሥ ሲል «እኔ አጠናፉ አባተ አይደለሁም ፤ “እኔ የፋኖ ንጉሥ ነኝ ፤ ሳልወለድ ትንቢት የተነገረልኝ ፤ከዘር የተላለፍልኝ አንጋሽና ነጋሽ ነኝ” እያለ የጎጃም ጀልዎቹን የሚያስፈነድቅ በልጣብልጥ የ የጎጃሙ ታጣቂ መሪ ዘመነ ካሴ እስክንድርን ካላጠፋሁ (የድሮ ነገሥታትን እያነሳ) “ጎጃም መንገሥ አይችልም” በሚል ማሃይም አስተሳሰብ ጦርነት እንደገጠመ አስነግሯል።

 እንደምናውቀው ይህ ሰው መምሕራንና ተማሪዎች ሲያዋከብ፤ ሲጠልፍ፤ ሲያግት ፤ ሲያስር ፤ ሲረሽንና የፋኖ ታጣቂዎቸን እኔ ካልመራሁ ብሎ (እያፈነ ሲያሰገድልና አስገድዶ ሲያታግል - ኮ/ል ጌታሁንና በሥሩ የነበሩ በመቶዎች የሚቆጠሩ ታጣቂዎችን (ወደ ዘመነ ታጣቂ ታፈነው ምን እንደደረሰባቸው እና የተቀሩትም እንዴት ወደ ዘመነ እንደተቀላቀሉ ታሰታውሳላችሁ) ፤ የጋዜጠኞችንና የዶክተሮችን አፈና እና እገታ ልብ ይለዋል)። አሁን ደግሞ “እስክንድርንና ታጋዮቹን” ካለገድልኩና ካላጠፋሁ ብሎ ከአምሐራ ታጋዮች ጋር ጦርነት ጅመርያለሁ ደምስሻለሁ ሲል እውነተኛ አምሐራዎች መጠየቅ ያለባችሁ «በዚህ ቀውስ ውስጥ እንዴት ልንገኝ ቻልን?» ማለት አለባችሁ።

ብዙ አመሐራ ወጣቶች ፋሺዝምና የብሔርተኛነት እንቀሰቃስዎች ባሕሪ ምን እንደሚመስል  የሚያውቁ አየምሰሉም። በፋሺስታዊ እንቅስቃሴዎች መካከል የተለመዱ ጭብጦች የሚያጠቃልሉትን እንመልከት፡-

“ፈላጭ ቆራጭነት፣ ብሔርተኝነት (የዘር ብሔርተኝነት እና ሃይማኖታዊ ብሔርተኝነትን ጨምሮ) ፤ ወታደራዊ ድንፋታነተን ፤ የአካባቢ አጉራዘለል አለቃነት ስሜትና አልገዛ/አለገብርም የሚልውንም ማንበረከከ የፋሺዝም ባሕሪያቶች ያጠቃለሉ ናቸወ። ጎጃም ውስጥ አቆጠቁጦ እያየነው ያለውንም ይህንኑ ባሕሪ ነው።ሰለዚህም አምሐራ ምሑራንና ወጣቶች በዚህ ቀውስ ውስጥ እንዴት ልንገኝ ቻልን? በለው ቢጠይቁና ቢመራመሩ ችግሩ ሊታያቸው ይችል ይሆናል እላልሁ።

በዚህ ጥያቄ ውስጥ እንዴት ልንገኝ ቻልን? የሁላችን ጠያ መሆን ያለበት የመወያያ ርዕስ መሆን ያለበት ነው። ለጥያቄው መልስ ስጡ ብትባሉ ብዙዎቻችሁ የምትሰጡት መልስ የለመዳቸሁት መልስ ሰልሆነ “ዲሞክራሲ” በመታጣቱ ነው እንደምትሉ በእርግጠኛነት መናገር እችላለሁ።

 እንዲህ ያለ ድምዳሜ ልትይዙ የቻላችሁበት ምክንያት “የፖለቲካ መሪዎችና ተቃዋሚ ሚዲያዎች” በዚህ እምነት ብዙ ጊዜ ደጋግመው ሲያስተምሩና ሲሞግቱ በመስማታችሁ፤ ያንን እንደ እውነታ ተይዞ ዲሞክራሲ ያለማመን  ለዚህ ዳርጎናል፤ ወደ እሚለው ድምዳሜ ልትድርሱ አስችሏችሗል (እውነታ ቢኖሮውም ቅሉ)  ለመሰደዳችን እና ለመበጣበጣችን ዓይነተኛ ምክንያት ዲሞክራሲ በመታጣቱ ሳይሆን፤የምንከተላቸው መሪዎችና ድርጅቶች/ወይንም መንግስት እና ሚዲያ፤ “ስለሚዋሹንም ጭምር ነው። አንዳንድ የፋኖ መሪዎች እየተከተሉት ያለው ባሕሪ ይህንኑ ነው።

ማስተዋል ያለባቸሁ ጥያቄ ያለ ዲሞክራሲ ለዘመናት የኖሮው የኢትዮጵያ ማሕበረሰብ የራስ ግጭት ሲከሰት ተሰብስቦ እየፈታ ፤ የሚያጔጉ 3 የባሕር በሮች ዋና ሆኖ ፤ ሕዝቡም የነጮችና የዓረቦች ገረድና ዘበኛ ለመሆን ወደ ስደት ሳይሄድ፤ እንዴት ኖረ ብለን ብንጠይቅ ፤  መሪዎቹ “በውሸት አትማሉ” የሚለው ሃየማኖታዊና ሕጋዊ መመሪያ በመተግበር ነው።  ቅማል ሱሪ ያስፈታል ፤ ውሸት ሃገር ይፈታል” የሚለው ዕውቀት ስለነበራቸው ነው።

መሪዎች (ጫካም ይኑሩ ከተማ)  እንደ ዛው በዚህ 50 አመት ውስጥ ያሳዩት የውሸት ባሕሪ በታሪካችን አላየንም። ሕዝቡን እየዋሹ አስከፊ ዘመን አምጥተውለት እነሆሲሰደድ፤ሲዋረድ፤ ሲንገላታእንደዛሬ ስቃይ ደርሶበት አያውቅም 

ለዚህ ሁሉ መከራና መበጣበጥ “መሪዎች” ገድለው ሳይቀጡ፤ እንደገና ሥልጣን ሲሰጣቸው ፤ ሲዋሹ ድጋፍና ጭብጨባ ሲቸራቸው ፡ አምባገነኖችን እየካብን በአገራችን ውስጥ ቁቡል ሆኖ በመታየቱ ነው

ለብጥብጥ ባሕሪ ምክንያት ዲሞከራሲ ማጣት ሳይሆን፤ ከዚህ ዘልቀን መሰረታዊ መነሾውን መመርምር ያስፈልጋል። የሚጎመዝዙ ዋሾ መሪዎችና ነብሰ ገዳዮችና ወረበላ ታጣቂና መሪዎች በፋኖ ድርጅቶች ውስጥ በገፍ ተፈልፍለዋልአሰገራሚ ያደረገው ደግሞ “የፋኖ መሪዎ በዋሹ ቁጥር፤ ሕብረተሱም አብሮ ይዋሻል፤ወይንም ሲዋሹ ይታገሳቸዋል፤ወይንም ያምናቸዋል። ውሸት ሕብረተሰብን የሚገድል እና የሚያጋድል፤የሚያሳስት መሰረታዊ የሆነ ማሕበራዊ ነቀርሳ እንደመሆኑ መጠን ፤ ‘ዋሾ’ መሪዎች በዋሹ ቁጥር ሕብረተሰቡም አብሮ እየዋሸ ወይንም ‘እየታገሳቸው’ በሄደ ቁጥር የሚፈለገው ሰላማዊ የሆነ ፍትሕ የነገሰበትና ‘ተጠያቂነትን’ የሚያከብር ስርዓት እንዳይመጣ እንቅፋት ይሆናሉ ማለት ነው። አሁን እየሰማነው ያለውና እያየን ያለው የፋኖ ይህንኑ ነው። (በተለይ ትችቴ በዘመነ ታጣቂ ላይ ነው፡ በወያኔ የታዘብኩት ባሕሪ በዚሀ ልጅ እያየሁበት ነው)።

 ውሸት የሚል ቃል ስደጋግም በቀላል አትዩት። ውሸትና ዋሾ መሪዎች” የመቀበል ባሕል እያጎለበትን በመምጣታችን ለቀውሳችን ተጠያቂዎች መሪዎቹ ሳይሆኑ እኛ የመሆናችን ጉዳይ አስገራሚ ያደርገዋል። ተጠያቂነት ያለው ስርዓት እንዳይሰፍን ዋሾ ‘መሪዎች’ ልቅ እየለቀቅን፤ እነሱ ሲያብዱ ባልታሰበ ድንገተኛ እምርታ እኛም እነሱ ጋር እየዋሸን እና እያበድን ቀስ በቀስ “ዕብድ ሕብረተሰብ” ወደ መሆን እየተሸጋገርን ነው፡ ይህንን እንመን።

 በፋኖ ላይ የታየው ባሕሪ ፡ፋኖ ከመመስረቱ በፊት የነበረ ነው (ወያኔ ባሕሪ ከዘመነ አመራር የማመሳስለውም በምክንያት ነው)። ለ37 አመት ፤ የሃይማኖትም የፖለቲካ መሪዎችም ከእውነት ርቀው “እየዋሹና ወንጀል እየሰሩ” ሕዝብን ሲመሩ ባመጡት ሰበብ የቀወሰ ሕብረተሰብ በብዛት እየተበራከተ መምጣቱ አሁን ያለው ፋኖ ላይ ገሃድ ወጥቶ እያየነው ያለው የሥልጣን ጉጉትና የመዋሸት ባሕሪ የዚ እውነታ ስበት (ገራቪቲ) ነው።

ይህ “እገሌን ካላጠፋሁ አላርፍምና ፤ ጥላሸት የመቀባት (የመዋሸት) ባሕሪና ወንጀል ሠርቶ ሳይጠየቁበት ተንደላቅቆ በነፃነት መኖር አፍሪካ ውስጥ ቢታይም በተለይም “ኤርትራም ሶማሌም እኛም  ማንታችንን ያጣን ማሕበረሰብ ወደ መሆን የተከሰተበት ሰበብ ይኼው ተጠያቂነት ያለመኖር ምክንያት ነው።

በኮሎኒያሊስቱ ኦሮሙማው መንግሥትም ይሁን በፋኖ መሪዎች እያየነው ያለው ፋሺስታዊ ብሔረተኛነትና ክፍለሃገራዊነት ልክ እንደ ፍትሓዊና የሕልውና መከላከያ መንገድ አድርገው ሕብረተሰቡ ሲዋሹት ሕብረሰተቡም አብሮ በመዝለሉ የቀው ተዋናይ እና ሰለባ ሆኗል።

ውለን አድረን ለጠንን ባልንበት ዘመን ወደ አራዊት ባሕሪ ተለውጠን አምሐራን አምሐራን በመግደል የተጀመረው ወንጀል ሬሳ እንዳይቀበርም እየተደረገ መሆኑንም እየሰማን ነውአሁን ደግሞ አምሐራን አምሐራን መግደል መጀመራቸውና “እንዳይኖሩ ሁሉንም እንጨርሳቸዋለን” እያሉ ያለ ምንም ሰቀቀን በሚዲያ “የጭፍጨፋ ወንጀል” እንደሚፈጽሙ በኩራት በመደንፋት ስብእናቸውን አሽቀንጥረ የጣሉ ወያኔ የሚያስንቁ “የጫካ ነብሰገዳይ ወረበላዎች” አፍጠው መተዋል። አምሐራዎች ኢትዮጰያዊ የአምሐራ ባሕሪያቸውን ጥለው ወደ አረመኔያዊ ባሕሪ ገብተል።

ፋሺስታዊና አክራሪ የብሒረተኛነት በሸታ ፋኖ ውስጥ ገብቶ ይፋ ሆኖ እየኮሩበት ነው። የብሔርተኛ ፖለቲካ መጨረሻው ስብእናን ነጥቆ የራሱ ያልሆነውን ነገድ በቻ ሳይሆን አሁን እያየነው እንዳለው የጎጃም የዘመነ ፋኖ አምሓራን ለመጨፍጨፍ ዛቻ እንዳወጀው ሁሉ በመጨረሻም የራሱንም ወገን እንደሚበላ እያያችሁት ነው።

አስቸኳይ የእርማት መንገድ እንዴት እንደሚወሰድ ባላውቅም ፤ እርማት ካለተደረገበት መግደል ብቻ ሳይሆን ዘመነ ካሴ እንደደነፋው «ጥይት አርከፍክፌበት ጥይት ካለቀብኝ መላ ስውነቱን በእሳት አቃጥለዋለሁ” ሲል እንደተናዘዘው ሁሉ» ብሔርተኛ ክዚያም አልፎ ሬሳውን መሬት ለመሬት እየጎተተ፤ እየረገጠ፤ ሬሳ እንደሚያቃጥል (ሰንደቃላማ ያለበትን የእስክንድር (መስል) ከናቲራ ሲያቃጥሉ የዘመነ የጎጃም ፋኖ ወረበላ ታጣቂዎች የሚናገሩትና የሚሰሩት ሥራ ጥሩ ማሳያ ነውበሞተ ሬሳ ላይ ጥላቻውን እንዲገልጽ የሚያስገድድ አደገኛ በሽታ እንደሆነ ነው ደጋግመን ስናስጠነቅቅ የነበረው

አሁን በጎጃሙ ዘመነ ካሴና በቃል አቀባዩ (ደም የጠማው ማሃየሙ ማርሸት) ዛሬ የዘር ጭፍጨፋ (የጅምላ ገደያ አዋጀ) ሲያወጅ ያደመጥኩት እስክንድርና መከታው ማሞ፤ ኮ/ፋንታሁን ሙሃቤ ፤ ደረጀ በላይ ፤ ሰለሞን አጣናውና አበበ...፤ ጌታ አስራደ ወዘተ..የመሳሰሉ ሐቀኛ አምሐራ ኢትዮጵያዊያን የሚመሩት “የአፋሕድ ፋኖ” ታጣቂ ላይ “የመጨፍጨፍ አደገኛ “የሽብር አዋጅ” በወቅቱ ማስቆሚያ ካልተበጀለት ያስጠነቀቅነውን ማስጠነቂያ ሳንሞት በዓይናችን ለማየት በዝገታ እያየን ነው

 ታሰታውሱ እንደሆን “ወያኔን” ሰቃወምና ስተች አምርረው የጠሉኝ ሺዎች ነበሩ፤ ስለው የነበረው አልተቀብሉኝም፡ ዛሬ ያ እውነታ ተረደተውት ይፋ ወጥቶ ስለው የነበረውን እውነታ ተቀብለው እያየሁ ነው። የጎጃም ፋኖ የዘመነ ተከታዮችም እኔን ይጠሉኛል የስደቡኛልም። በዛው የመሰደብ ውሽንፍር ሰላለፈኩ አለገረመኝም።

ተከታዮቹ በወንዝ ልጅነትና አካባቢነት እየተሰባሰቡ መሪዎቻቸው ሲዋሹና ወንጀል ሲፍጽሙ ሽፋንና መድረክ እየተሰጣቸው፤ በግልብነት  እየተጓዙ ፖለቲካው እና ሃይማኖቱ ወደ እንሰሳ ባሕሪ አስገብተውታል።የማታ እራት ለማግኘት “ጠላ፤ የስሙኒ አረቄና ሲጋራ” እየሸጡ ለጆቻቸው የሚያሳደጉ ድሃ እናቶች አሰርው ፤ ገርፈው በማሰቃየት “እንዳይሸጡ” አግደው ወደ ልመና እንዲሰማሩ እያስገደዱዋቸው ይገኛሉ። አፈሙዛቸው ወደ ድሆችም አዙረውታል። ለዚሀ ነው “ወረበላዎች” ናቸው የምለው።

ይህንን የወርበላ ታጣቂ ቡድን በመከተል “ውሸትና ወገንተኛነት ፖለቲካውንም ሃይማኖቱንም የዜና አውታሮችን ሳይቀር ተቆጣጥሮአቸዋል። በውሸት የሰከሩ ዜጎች የሚሰሩት ስራ በገሃድ እያየንና እያደመጥን ነው። ውሸት አየር ነገር አይደለችም። በማሕበረሰቡ ሕሊና ውስጥ የምትኖር፤ ጠበቃዎችና ተከላካዮች ያሏት የሰዎች ባሕሪ ነች።

ሕብረተሰቡ ከሚዋሹ ታጣቂ መሪዎች አብሮ የማበዱ ምክንያት እራሱ ሕብረሰተሰቡ ብቻ ሳይሆን፤ ውሸትን በመድረክ አደባባይ እንዳይጋለጥ “ውሸትን የሚያደንቁ” በየ ቲከ ቶከና ዩቱበር እንደ አሸን የፈሉ “የተካኑ ስም አጢፊዎችን” በማሰማራት ፍተኛው የአጥፊነት ድርሻውን የያዙ ከፈሎችም አሉ

ሚዲያዎች፤ የድርጅቶችን ጸያፍ ድርጊታዊ ምስጢሮችን ፤ አውራጃዊና ከባቢያዊ የትውልድ ሐረግነትን በመከተል አንዳንዱም ለፖለቲካ እና ጊዜያዊ ተወዳጅነት ለማግኘት ሲሉ ፤ የሽብር ስራዎች ወደ እሚቃወሙት መንግስት ብቻ እያዞሩ የፋኖ ሽብርተኞች የሚፈጽሙዋቸው ሽብሮች ውሸቶች ፤ አፈናዎች፤ እገታዎችና ግድያዎችን በመደበቅ የተባባሪነት ሙያ እያካሄዱ ናቸው።

እነኚህ የቲከቶክና ዩ-ቱበሮች (የሚዲያ ክፍሎች) ለምሳል “ዘመድኩነ በቀለ” የተባለው “ሲፍረዘኒክ” እዚህ ልጥቀስና እነዚህ መሳይ “ጥላሸት ቀቢዎች” ሕብረተሰቡ ካልነቃባቸው አደገኛ የሕብረተሰብ ጠንቆች ሊሆኑ እንደሚችሉ ደጋግሜ ገልጫለሁ። የዘመነ ካ ፕሮፓጋንዲስት የሆነው ይህ ሰው አድማጮቹን የማሳምን ችሎታው ከፈተኛ ነው፡ ሆኖም ቀረብ ብሎ በጥንቃቄ ሲያጠኑት “ገለባ ፕሮፓጋንዳ ነው”። ሆኖም ሂትለር እንዳለው፦

«በብልሃት እና የማያቋርጥ ፕሮፓጋንዳ ሰዎች ገነትን እንደ ገሃነም እንዲመለከቱ እና በጣም መጥፎውን ሕይወት እንደ ገነት እንዲቆጥሩ ማድረግ ይቻላል። የላል፤ ሂትለር።

እየሆነ ያለውም ይህ ነው። እነኚህ ክፍሎች፤ በሕዝብ ምርጫና ፍላጎት የተከሰቱ ስላልሆኑ፤ በድምፅ ብልጫ የሚመረጡ ወይንም የሚወርዱ አይደሉም። እነኚህ ሚዲያዎች በተለያየ ስም እየተጠሩ፤ ለትርጉም የማይመቹ፤ “እራሳቸው በራሳቸው የመረጡ” ከማሕበረሰቡ ጫንቃ መውረድ የማይችሉ  “ነገሥታት” ናቸው። ሰልሆነም ፤ በይፋ ካልተጋፈጥናቸው፤ አደገኛ ድርጅቶችና ግለሰቦችን ወደ ሕዝቡ እያስተዋወቁ፤ የሕዝብ ሕሊና በመጥለፍ፤ ወደ ስልጣን ጎትተው ሊያመጡብን የሚያስችላቸው ዕድል እያመቻቹ ነው። በሌላ አነጋጋር አስፈሪ “ሞንስተሮችን” (ዘንዶአዊ-ድራጎኖችን) በነዚህ የሚዲያ ሰዎች ብዕርና ምላሰ ውስጥ ተወልደው ያድጋሉ ማለት ነው

ሚዲያዎች ጎጂም ጠቃሚም ሊሆኑ ይችላሉ። አደገኛ ባህሪ ሲከተሉ ግን ማሕበረሰቡ ከሚቆጣጠረው ዓለም ውጭ የሚኖሩ Dual character ድርብ ጸባይ የያዙ ክፍሎች የመሆን ባሕሪ አላቸው። እነኚህ ክፍሎች አገርን ማበጣበጥ፤ ጨቋኝ መሪና ግለሰብን ማንገስ የሚያስችል ሰላቢ የብዕር ችሎታ ስላላቸው፤ ማሕበረሰብን ማፋለስ ወይንም የማረጋጋት ችሎታ አላቸው። ውሸት በነዚህ ክፍሎች ትጎለብታለች ወይንም ትታገዳለች። ስለሆነም፤ ለቀውሳችን ምክንያት መዋሸትና ወንጀል ፈጽሞ ተጠያቂ ያለመሆን ባሰመርንበትም አሻግረን ለመድረስ የምንጓጓለት ወደ “ዲሞክራሲ” የሚወስደን መንገድ አጉራ ዘለሎችን በማወደስ ዘጊ ሃይል ሊሆኑ ይችላሉ። ስልዚህም እያስቸገሩን ያሉት ‘ሚዲያዎች እና መሪዎች” በውሸት ነቀርሳ ሲበከሉ፤ የሚፈለገው ሰላማዊና የዲሞከራሲያዊ (የእኩልነት) ስርዓት ልናይ አንችልም።

ያለ ምንም ማመንታት ወደ ቀውስ ገብተናል። ውሸትን እና ውሸታም የመንግሥትም፤ የፖለቲካ ድርጅት ሆኑ የሽምቅ ታጣቂ ተዋጊ መሪዎች (እውነትና ማሰርጃ ባለው ውንጀላ) ካልተተቹና ካልተጠየቁ፤ ቀጣዩም “ወሃ ቅዳ ውሃ መልስ” (garbage in garbage out!) ነው ። ባሳዛኝ ሁኔታ የፋኖ ትግል እየሆነ ያለው «ገዳይ ውጣ - ገዳይ ግባ» ነው።

እፊታችን ላይ ውሃ እንደ ያዘ እንስራ ፍርክሽክሹ የወጣው የፋኖዎቹ ትግል አምሐራ አምሐራን ለመግደል የዘመነ ፋኖ ታጣቂ በይፋ አውጀዋል። ማወጅ በቻ ሳይሆን ታጋዮች መግደል ጀምሯል! ነገ የገደሉትን ሬሳ ወደ መጎተት ተዛውሮ እንዳናይ ግን ያሰጋል።

ጌታቸው ረዳ

Ethiopian Semay

No comments: