ተፈጥሯዊ ድፍረስና
ጌታቸው ረዳ
5/31/25
እንደምታስታውሱት በቅርቡ ህዳር 2012 ላይ የትግራይ ፋሺስቱ ድርጅት ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በኢትዮጵያ ብሄራዊ መከላከያ ሰራዊት የሰሜን ዕዝ ዋና መምሪያ በሚገኘው በመቀሌ እና ሌሎች ካምፖች ላይ ድንገተኛ የጭፍጨፋ ጥቃት በመሰንዘር የትግራይ ጦርነት መቀሰቀሱ የታወሳል።
በጦርነቱ ወቅት የአብይ አሕመድ አጨብጫቢ ሆኖ በመገኘት ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጰያ በመሄድ በአብይ አሕመድ ሚዲያዎች ላይ እየተገኘ ስለ ወያኔ እርኩስነት ቃለ መጠይቅ በማድረግ አሁን እያሞካሸው ያለውን ወያኔና ተዋጊዎቹን “ተደምስሰው መጥፋት አለባቸው” እያለ አብይን “መሪያችን“ በማለት የሚያወድስበት ቃል እስኪያጥረው ድረስ ሲያሞካሸው እንደነበር በዙዎቻችሁ ታስታወሳላችሁ።
አሁን ደግሞ “የኢሳያስ ነፃነት” ለማክበር ወደ አስመራ በተደጋጋሚ በመሄድ ሰለሞን ተካለኝ የመለስ ዜናዊን ቅንድብ በማድነቅ “ቅንድቡ” እያለ እንደዘፈነለት ሁሉ አሁን ደግሞ ይህ ልጅ “የኢሳያስ ርዝማኔና ቁመና” እንደ ሴት በማድነቅ “እያፏሸገ” አብይ አሕመድን ሲያጠላላ ይደመጣል።
እርግጥ ልጁ የፖለቲካ ድንቁርና
ያጠቃው “እዚሀ ግባ የማይባል ያልበሰለ” በመሆኑ በልጁ ላይ ዝርዝር መጻፍ አንባቢን ማሰልቸት ስለሚሆን ቪዲዮውን በቻ ማድመጥ ይበቃል።
“ፋሺቶች” ከሚጠቀሙባቸው “የውስጥ
ሙታንታ አጣቢዎቻቸው” (የሃብታሙ አያሌው አገላለጽ ልዋስና) እንዲሀ ያሉ “አገልጋዮች” በማሰማራት መልእከታቸውን ያሰራጫሉ (አምና
አበይን ሲያገለግል ነበር ፤ ዛሬ ደግሞ ወያኔና ሻዓብያን እያገለገለ ነው)።
እንዲህ ያሉ “ተፈጥሯዊ ድፍርስና” ያጠቃቸው ሰዎችና ድርጀቶች ወዳጄ ይነጋል፤እንዲህ ይገልጻቸዋል፦
«በኢትዮጵያ የዘመናችን ድፍርስና
amorphous ፖለቲካ እንደወያኔና እንደ ኦህዲድ ሥነ ተፈጥሯዊ ብልሽት የሚገርመኝም ሆነ የሚያሣዝነኝ የለም፡፡» ይላል።
እንዲሀ ያለ “ተፈጥሯዊ ድፍርሰና” በዚህ ልጅ ስታደመጡ ይህ ልጅ አያሳዝናችሁም?
Ethiopian
Semay
No comments:
Post a Comment