Saturday, April 19, 2025

ትግራይ ያበቀለቺውን ሰይጣን አምበርክከን አስረን ኮነ ፍስሐ ወ ሰላም አሰሮ ለሰይጣን ብለናል! 4/20/25 ሚያዚያ 12/2017 Ethiopian Semay

 

ትግራይ ያበቀለቺውን ሰይጣን አምበርክከን አስረን ኮነ ፍስሐ ወ ሰላም አሰሮ ለሰይጣን ብለናል!


ዛሬም ከወላጆቻችን ሰንደቅ ዓላማ አብረን ቆመናል! 

4/20/25 ሚያዚያ 12/2017

Ethiopian Semay

ከዘመነ አክሱም ጀምሮ እስከ ዛሬ 2017 ዓ.ም ድረስ በየ አመቱ እየተከበረ ያለው የትንሳኤ በዓል ዕንኳን አደረሳቸሁ እያልን መልካም መኞታችንን ሰናበስር፡ ዕጣንዋን እያሸተትን ቅብአ ሜይሮዋን እየተቀባን በታቦተ ጽዮን ደረት ላይ ግራና ቀኝ ታቅፈን ያደግን እኛ 2 የአክሱም ፍሬዎች የእየሱስ ትንሳዔ ስናከብር አሮ በወያን መቃብር ላይ የኛም ዳግም ትንሳዔ አብስረናል።

የትግራይ ተወላጅ ሆኖ ወያነ ትግራይን መቃወም ማለት እናንተ ከምትገምቱት በላይ የሲኦል ህይወት ማሳለፍን ይቀላል። በሁለት ወገን ያም አያምነንም ፤ ያም አያምነንም፡ በሁለት ጅራፍ የመገረፍ ያህል ነው።

የትግራይ ምሁራን ምን ያህል ግፍ እንደፈፀሙብን ዛሬ መለስ ብለው ቢያስቡት ለጥቂት ሰዎች ጥቅም ብለው ያደሩበት እሽክርና ይፀጽታቸው ይሆን ብለን በጥያቄ እናልፈዋለን።

“ወያነ ትግራይ” ራሱን ብቸኛ የትግራይ መሬት ባለቤት  አድርጎ ራሱን እንደፈጣሪ በመቁጠር ትግሬነታችንን በመንጠቅ ፤የስም ማፋት ዘመቻ በመክፈት ፤ በወላጆቻችን ቀብር እንኳ እንዳንገኝ ያገን “የአጋንንት መንጋ” የሆነው ይህ የፋሺስቶች ድርጅት፤ ሁለት ትውልድ በፈጀ “በረዢም የትግል ትንንቃችን” ጥለነው ፤ እነሆ ጅራቱን እንደ ውሻ ቆልፎ ፤ ተዋረዶ፤ ሐፍረት ተከናንቦ “ድቅድቅ ጨለማ ውስጥ አስገብተን፤ ጭቃ ውስጥ ጥለነው ሲጨማለቅ ማየታችን ለሁለታችን “ድርብ ትንሳዔ” ነውና ፤ እንደ ፈጣሪያችን እየሱስ መከራን ተቀብለን እነሆ “ትግራይ ያበቀለቺውን ሰይጣን አምበርክከን ፤ አስረነው ፤ ኮነ ፍስሐ ወሰላም በለናል!”

እስመ ተዘከረነ እግዚአብሔር በሕማምነ

እስመ ለዓለም ምሕረቱ

ወአድኅነነ እምዕደ ፀርነ

እስመ ለዓለም ምሕረቱ  

ዘይሁብ ሲሳየ ለኩሉ ዘሥጋ

እስመ ለዓለም ምሕረቱ 

ግነዩ ለአምላከ ሰማይ።


እኛን በመዋረዳችን አስቦልናል፤

ምሕረቱ ለዘለዓለም ነውና፤

ከጠላቶቻችን እጅ አድኖናልና

ምሕረቱ ለዘለዓለም ነውና፤

ለሥጋ ሁሉ ምግብን የሚሰጥ

ምሕረቱ ለዘለዓለም ነውና፤

የሰማይን አምላክ አመስግኑ።(መዝሙረ ዳዊት)

 መልካም ፋሲካ!

Ethiopian Semay

No comments: