Tuesday, June 29, 2021

አብይ አሕመድ መጨረሻው ላይ ሕዝብ አስጨርሶ ሸብረክ ይላል ብያችሁ ነበር፤ ይኼው እንታረቅ አለ!

 

አብይ አሕመድ መጨረሻው ላይ ሕዝብ አስጨርሶ ሸብረክ ይላል ብያችሁ ነበር፤ ይኼው እንታረቅ አለ!

ጌታቸው ረዳ (Ethio Semay)

6/18/2021

ዛሬ ሁለት የተለያዩ ዜናዎችን ተመለከትኩ።  አንደኛው አንዲህ ይላል። መቀሌ ነፃ ወጣች እንኳን ደስ ያለን!” የሚል “Cyber Power of Tigray” በሚባል ውጭ አገር የሚገኝ የዩቱብ ሚዲያ ውስጥ ውጭ አገር የሚኖሩ የወያኔን የሚከተሉ “ፓፒዎች” መቀሌ ነጻ ወጣች እያሉ ዕልለታቸውን እያቀለጡት አረፋ ሲያደፍቁ ሰማሁኝ (ትምክሕታቸውን ብትሰሙ አብየት፤ ዕድለኞች ናችሁ እንካን ትግርኛ አላወቃችሁ! ትበሳጩም ትስቁም ነበር!)። ሌለው የትግራይ መንግሥት መግለጫ (“መግለፂ መንግስቲ ትግራይ“) የሚል ወያኔ ያስተላለፈው በ 06-28-2021 መቀሌ ነፃ መውጣትዋን የአዋጅ መግለጫ አወጣ። አዲስ አባባ የሚገኘው የአብይ አሕመድ አገልጋይ የሆነው “ኢ ቢ ሲ” የተባለው የመንግሥት ሚዲያ ደግሞ አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 21 ፣ 2013 (ኣፍ ቢ ሲ/  -ፋና) የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የፌዴራል መንግስት ሰብዓዊነትን መሰረት ባደረገና ተጨማሪ ጉዳት በማያስከትል መልኩ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲያደርግ ጥያቄ ማቅረቡን አስታወቀ።” የሚል ዜና አስደመጠን።

የሚገርም ነው!

ጦርነቱ በወያኔ ተገባደደ ማለት ባይሆንም፤ ይህ ሁሉ የተለያዩ ውሸቶች እየነዛ “ሽብርተኛ ጋር መደራደር አይታሰብም” ሲል የቆየ መንግሥት በራሱ ቴ/ቪዥን ሸብረክ ብሎ የቶክስ ስምምነት እናድርግ ብሎ ሲያውጅ፤ መስማት ከሓፍረትም ሓፈርተኛ መንግሥት ነው። የወያኔ ፋሺሰቶችና የኦሮሙማ ፋሺሰቶች በሚያደርጉት ጦርነት ሁለቱም ያጋጫቸው አገር በመጠበቅ ሳይሆን፤ “ሥልጣን” ሽምያ እንደሆነ የምናውቀው ሃቅ ነው። አሁንም ሥልጣን ለመጋራት ከተስማሙ ሽበረክ ማለታቸው የግድ ነው። በተለይ አብይ አሕመድ አቋመ ቢስ ስለሆነ “ዕርቅ እያለ ‘ሸብረክ” ማለቱ አይቀሬ ነው ብየ በዚህ ፌስ ቡክ ላይ ጽፌ አለሁ። ይኼው ችሎታ ቢሱ ማፈሪያ “መንግሥት” ተብየው “የቶከስ አቁም ስምምነት ጠየቀ። በማን ሰም ነው የቶክስ አቁም ስምምነት እናድርግ እያለ ያለው? በትግራይ ገበሬ በከርምት እርሻ ሥራ ስም። ይህ ግን ግልጽነት የሌላው ውሸት ነው። ተሸንፎ ከሆነም ተሸንፌአለሁ ማለት እንጂ ዝባዝንኬ አያስፈልግም። ያውም ወዳጄ አምሳሉ ገብረኪዳን እማ ከኔው አስተያየት በዘለቀ የሚለው “ሁለቱም ሕዝብን ለማስጨረስ አማራውን ለማጃጃል እንጂ የምር ጦርነት አልነበረም፤ስለዚህ ውሎ አድሮ ይታረቃሉ፤ ጥላቻም አልነበራቸውም” ይላል። ይህ አስተያየት አሁን አሁን ስንመለከት “አሌ’ ማለት አንችልም። 

በዚህ መሃል ተጠቂ የሆነው፤ ለጭለማ ህይወትና ስደት የተዳረገው ሕዝብ ተጠያቂዎቹ ‘የትግሬ ምሁራን’ በዘረጉት ትምክህት የማሕበረሰብን አንድነትና የተረጋጋ ህይወት የሚያደፈርስፋሺስታዊ ማኒፌስቶበመቀበላቸው ሰበብ እንደሆነ ግልጽ ነው።  የነገድ ፖለቲካ አስተማሪዎቻቸውን ወያኔዎች በማምለካቸውለሕዝቡ የችግር ሰበብ ሆነውታል። እነሆ ዛሬ መራራው አማራጭ ከፊታቸው ተደቅኗል። መቀሌ ነጻ ወጥታ ትግራይ ነፃ አገር ሆና ሕዝቡ በሰላም በደስታ ይኖራል ብሎ የሚለው ከሞኝነትና የደንቆሮ አመለካከት ካልሆነ በተግባር የማይሆን ቅዠት ስለሆነ የሚሳካ አይሆንም።

የሕዝቡ መከራ ሊረዝም የሚችልበት ምክንያት ግን አርግጠኛ ሆኜ የምላችሁ “እንደምታውቁት ልክ እንደ ኦሮሞ ማሕበረሰብ 95% በሚያስብል ግምት ኦነግን እንደተከተለ ሁሉ በተመሳሳይነት ቁጥር ትግሬዎችም እንዲሁ 1928 . ጣሊያኖች ለኢትዮጵያዊያን ትተውልን የሄዱት የቀየሱትን የፋሺዝም ርዕዮትየአንጎል አጠባተጠቂዎች ናቸው። የትግራይን ሕዝብ ከኢትጵያዊነት ስነ ልቦና ለማላቀቅ ረዢም ጊዜ ተወስዶ በርካታ የአእምሮ ማጠቢያ ቴክኒኮችን (ዘፈኖችን፤ተውኔቶችን፤መጽሐፍቶችን፤ንግግሮችን….ወዘተ) ተካሂደዋል። አሁን ደግሞ በዚህ ጦርነት እውነታን እና ውሸትን ተጨማምሮበት የሕዝቡን ልቦና ይበልጥ ወደ ፋሺሰቶቹ ርዕዮት በመደገፍ ከወያኔ ጋር ቆሟል።

ትግራይ ውስጥ በተቃዋሚነት የቆሙ ብዙዎቹ “የወያኔ የውስጥ አርበኞች ናቸው”” ትግራይ እንዲያስተዳድር የተላከው የቶክስ አቁም ስምምነት ይደረግ ብሎ አለ፤ የሚባልለም ያው ዶ/ር አብርሃም በላይ የተባለውም ሳይቀር ደደቢት በረሃ ውስጥ ወያኔ የመሰረተው የየካቲቱ 11/1967 . የኢትዮጵያን የባሕር ወደቦችን ለጠላት ለመስጠት እና ፋሺዝም ለማንገስ ፤ አማራን ለመጨፍጨፍ የተመሰረተው የትግል ቀንና ወር መከበር አለበት ብሎ ባፈው የካቲት መቀሌ ውስጥ የሰማእታት ክብር ሲያከብር ውሏል። እርሱም ድሮ ወያኔ መኖሩን እናውቃለን፤ አሁንም የውስጥ አርበኛ  ወያኔ አለመሆኑ ማስረጃ የለንም። ጸረ አማራው አደገኛው አብርሃም ገበርመድህን የተባለው ዓድዋዊው ዘረኛ “ዘፋኝም” (ብዙ ከብት ኢትዮጵያዊ አብራሃም አብርሃም እያለ በየ እስፖርት ሜዳ ለይ የእሱን መናኛ ዘፈን ሲጨፍር የሚውልለት ሞልቷል) ከወያኔዎች ጋር አድብቶ መቀሌ ከተማ እና በራሃ ውስጥ እየተመላለሰ ሲደበቅ ወራት አሳልፎ ከተደበቀበት ተገኝቶ እጁን ሲሰጥ ዶ/ር አብርሃም ተብየው መቀሌ ውስጥ “አንድ ቀን አስሮ ለቀቀው” ይኸየው ዛሬ እርቅ ምናምን እያለ አብይ ያዘዘውን ዕርቅ  ዶ/ር አብርሃም የተባለው የትግራይ ጊዜዊ አስተዳዳሪ ነው አሁን የቶክስ ስምምነት እናድርግ እያለ ያለው።  ለዚያ መስዋዕት የሆኑትን እና ለነመለስ ዜናዊ ጭምር የቆመው የመቀሌው ሃውልትም በክብር መያዝ አለበት እያሉየወያኔ ፖለቲካ ተቃዋሚ ነንእያሉ ነገር ግን የወያኔንአርቲፋክት” (ቅርስ/አሻራ) የሚያከብሩ የፋሺዝም አሽቃባጮች በብዛት አብይ አስተዳደር ውስጥ አሉ የምንለው ለዚህ ነው።

አብይ እነ ዓረና ፤ባይቶና ወዘተ….የተባሉ የትግሬ ተቃዋሚ ተብየ ወያኔዎች  አዲስ አባባ ቁጭ ብለው በየሚዲያው ስለ ወያኔ ጉብዝና ሲያወሩ አብይ አሕመድም የጸጥታውም ምንም አይላቸወም። አብይ የሚጎብዘው ጠምነጃ የሌለው በብዕር የሚታገለውን እስክንድር ነጋ ላይ ነው። አምሳሉ ገብረኪዳን የሚለውም ይህ ነው። አብይ ከወያኔ ጋር ድብቅ ነገር ከሌለው እንዴት እነዚህን መርዘኞች አዲስ አባባ እየኖሩ በየሚዲያው መርዝ ሲረጩ ዝም አላቸው?

የም ሆነ ይህ የትግራይ ሕዝብ ዛሬም ከዚህ ወያኔ ከተባለው ድረጅት እራሱን ካላላቀቀ በተደጋጋሚ እንደምታውቁት የትግራይ ምሁራን ራሳቸውን ለፋሺዝም አምልኮ ስለሸጡ፤ የሕዝቡን መከራ በዚህም በዚያም አባብሰውታል፤ ችግሩም ቀጣይ ነው።  አሁን መቀሌ ነፃ ወጣች “ቱማታ፤ዕልልታ” የወያኔ ፋሺቶች እያስጮሁት ያለው አጉል ጉራ ተመሳሳይነቱለብ/ሞቅ ባለው/ ድሰት የተጣደቺዋን የእንቁራሪቷ ታሪክ የተሰማት ደስታ እና መጨረሻ ውሃው ቀስ እያለ እየፈላ እንዴት ጠብሶ እንዳቃጠላት ሁሉ፤ የትግራይ ሕዝብም ሆነ ወጣት በወያነ ምሁራን የተሳሳተ ርዕዮት በጭፈራ ጦዞ የትዕቢት ሐረጎችን ያዘሉ ዘፈኖችን እያመነዠከ ቀስ እያለ በቀበኞቹ ተንኮል እራሱን ማቃጠሉ አይቀሬ ነው።

በዚህ አጋጣሚ “የኢትዮ ሚዲያ “የትግራይ ትዕወት” (ትግራይ ታሸንፋለች) ፈካሪዎች እነ “አብርሃ በላይም” እንደተመኛችሁት መቀሌ ነፃ ወጥታለችሗለች፤ አብይ አሕመድም ሸብርክ ብሎላችሗል እና እንከን ደስ አላችሁ እላለሁ!! ነፃ አገራችሁ አሸንፋችሗል እና ነጻ አገራችሁን ይኸየው “በትግራይ ትዕወት” መሰረት ተረከቡዋት “በብሩር የወርቅ ሳሕን” እነሆ አብይ አሕመድና ቡቹሎቹ ሰጥቶአችሓል! አንኳን ደስ አላችሁ!

የሚያሳዝነኝ የሚስኪኑ የአማራው ጦር ደም መቀለጃ መሆኑን! ልቤ ውስጥ ብትገቡ ጭሱ ያፍናችሗል፡ ልቤ እንዴት አየጨሰ ያለ መሰላችሁ!?

አስገራሚ አገር!!

አመሰግናለሁ

ጌታቸው ረዳ

No comments: